ማለዳ - Media

ማለዳ - Media ማለዳ - Meda : ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር መረጃዎችን ያደርሳል ።

Information, is power.

በማለዳ - Media : ማስታወቂያ ለማሰራት :-
0939435610
0945716332
ይደውሉ ። አልያም በውስጥ መስመር ያናግሩን ። If you can control information, you can control people.

የ3 ልጆች እናት የሆኑትን እናት እናሳክማቸው !!😢  : እኚህ እናት አየለች አበበ ይባላሉ ። የ3 አዳጊ ልጆች እናት ናቸው ። በጡት ካንሰር ተጠቅተው ከአንድ ዓመት በላይ ሕመም ላይ ይገኛሉ...
05/10/2025

የ3 ልጆች እናት የሆኑትን እናት እናሳክማቸው !!😢

: እኚህ እናት አየለች አበበ ይባላሉ ። የ3 አዳጊ ልጆች እናት ናቸው ። በጡት ካንሰር ተጠቅተው ከአንድ ዓመት በላይ ሕመም ላይ ይገኛሉ።

በዚህ ጊዜ ውስጥ ያላቸውን ጥሪት አሟጥጠው ተከታታይ የኪሞ ቴራፒ ሕክምና መውሰድ ችለዋል ። በሕመሙ ሳቢያ አንደኛውን ጡታቸውን አጥተዋል።

ያ ሁሉ አልፎም ግን አሁን ደግሞ አስቸኳይ የጨረር ሕክምና ማድረግ እንዳለባቸው፣ አለዚያ ግን አሳሳቢ እንደሚኾን የሕክምና ባለሙያዎች ገልጸውልናል። ለዚህም 70 ሺ ብር ተጠይቋል።

እትዬ አየለች በሽታው ከያዛችው ወዲህ ሥራ አቁመው፣ የነበረቻቸውን ጥሪት ለሕክምና በማዋላቸው አሁን ምንም ፍራንክ እጃቸው ላይ ባለመኖሩ ይህን ገንዘብ መክፈል አልቻሉም።
ያለንን አዋጥተን እኚህን የ3 አዳጊ ልጆች እናት እንታደግ የሚል ሰብዓዊ ጥሪ ቀርቦልናል።

አየለች አበበ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000721306503
አቢሲንያ ባንክ
20798882

*ማስታወሻ መርዳት ባንችል የሚረዳ ይኖራልና መረጃውን ለሌሎች በማጋራት እንተባበር !❤️🙏❤️

የኪሊያን ምባፔ ታላቅ ድርጊት ! ❤️🙏  : በትናትናው ጨዋታ ላይ ርያል ማድሪድ በ69ኛው ደቂቃ ላይ ፔናልቲ  ያገኛል። የመጀመሪያ የፔናልቲ መቺ  ኪሊያን ምባፔ ነው። ነገርግን ፈረንሳዊው ኮ...
05/10/2025

የኪሊያን ምባፔ ታላቅ ድርጊት ! ❤️🙏

: በትናትናው ጨዋታ ላይ ርያል ማድሪድ በ69ኛው ደቂቃ ላይ ፔናልቲ ያገኛል። የመጀመሪያ የፔናልቲ መቺ ኪሊያን ምባፔ ነው። ነገርግን ፈረንሳዊው ኮከብ ምባፔ ፔናልቲውን ለቪኒሲየስ ጁኒየር አሳልፎ ሰጠው። ከዛም ቪኒ ፔናልቲውን ወደ ጎል ቀይሮ በቀጥታ ምባፔ ሄዶ አመሰገነው።

ኪሊያን ምባፔ የላሊጋ ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪ ነው። የበለጠ መሪነቱን የሚያስቀጥልበት እድል ነበረው። ነገርግን በግሩም የጓደኝነት ጥግ ለቪኒሽዬስ ጁኒዬር በመስጠት በራስ መተማመኑ እንዲጨምር ማድረግ ቻለ።ክብር 🙏

05/10/2025

ፍቅሬ አትግፊኝ !!ለፍቅር የፈሰሰ እንባ !!😭😭....
:
:
゚viralシ

“ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ 325 ሚሊዮን ዶላር ኪሳራ ደርሶበታል “የዓለም ባንክ    : የዓለም ባንክ እና የዲጂታል ልማት አጋርነት በቅርቡ ባወጡት "የኢትዮጵያ የቴሌኮም ገበያ ግምገማ" ሪፖርት መ...
05/10/2025

“ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ 325 ሚሊዮን ዶላር ኪሳራ ደርሶበታል “የዓለም ባንክ
: የዓለም ባንክ እና የዲጂታል ልማት አጋርነት በቅርቡ ባወጡት "የኢትዮጵያ የቴሌኮም ገበያ ግምገማ" ሪፖርት መሠረት፣ አዲስ የገባው የቴሌኮም ኩባንያ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከፍተኛ የገበያ ፈተናዎችን እየገጠመው ነው ብሏል ።

ሪፖርቱ ሳፋሪኮም በ2024 በጀት ዓመት 325 ሚሊዮን ዶላር ኪሳራ እንደደረሰበት ገልጿል ። አመታዊ ገቢው (53.6 ሚሊዮን ዶላር) ለፈቃድ ክፍያው ወጪ እንኳን በቂ አይደለም ብሏል።
ለዚህ ዋናው ምክንያት ደግሞ በመንግሥት ከተያዘው ኢትዮ ቴሌኮም ጋር እኩል ያልሆነ የመወዳደሪያ ሜዳ አለመፈጠሩ ነው።

ኢትዮ ቴሌኮም የፈቃድ ክፍያ አለመክፈሉ እና ሳፋሪኮም ከኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች በሚደረጉ ጥሪዎች አማካኝነት በወር 1.6 ሚሊዮን ዶላር እንዲያጣ የሚያደርግ የጥሪ ዋጋ (MTR) ቅናሽ ማድረጉ የውድድሩን ፍትሐዊነት ጎድቶታል።

በተጨማሪም ኢትዮ ቴሌኮም የሳፋሪኮም መተግበሪያዎችን አግዷል እና በቴሌብር የዳታ ግዢ ላይ ቅናሽ በማድረግ ደንበኞችን በኔትወርኩ ላይ እንዲቆዩ ያደርጋል ተብሏል።

ዓለም ባንክ እነዚህን ችግሮች ለመፍታት የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን (ECA) እንደ ስታርሊንክ ላሉ የሳተላይት ኦፕሬተሮች ፈቃድ እንዲሰጥ፣ የፍቃድ አሰጣጥ ሥርዓቱን እንዲያስተካክል እና በፍትሐዊ ባልሆነ ውድድር ዙሪያ የተነሱትን ስጋቶች በጥልቀት እንዲመረምር መክሯል።
(ቅዳሜገበያ)

 : ዶ/ር ደራራ ቢዲሶ በአሜሪካ በጥይት ተገደለ!😭  :ኢትዮጵያዊው   ዶ/ር ደራራ ቢዲሶ ቦሮጄ በአሜሪካ ባልታወቁ ግለሰቦች በተተኮሰባቸው ጥይት፣ በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።ዶ/ር...
05/10/2025

: ዶ/ር ደራራ ቢዲሶ በአሜሪካ በጥይት ተገደለ!😭

:ኢትዮጵያዊው ዶ/ር ደራራ ቢዲሶ ቦሮጄ በአሜሪካ ባልታወቁ ግለሰቦች በተተኮሰባቸው ጥይት፣ በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

ዶ/ር ደራራ በቅርቡ በታዋቂው Vanderbilt University የልዩ ባለሙያነት (Specialized Doctor) ትምህርታቸውን አጠናቆ፣ በዚያው በVanderbilt University Medical Center ውስጥ በስራ ላይ እያለ ነበር አሰቃቂ ድርጊት የተፈጸመበት።

የዶ/ር ደራራ አባት የቀድሞው የሲዳማ ታጋይ የነበሩት አቶ አየለ (ቢዲሶ) ቦሮጄ ልጅ ነው ። ያልተኖረ ወጣትነት፣ እውቀትን ለወገን ለማካፈል በታሰበበት ሰዓት ላይ በሰው አገር በድንገት በዚህ ሁኔታ መቀጠፍ እጅግ አሳዛኝ ነው ። ነፍስ ይማር !!😭

አዲሱ የተሸከርካሪ ሰሌዳ ከሁለት ወራት በኋላ አገልግሎት ላይ ይውላል !!  : የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ባወጣው የተሽከርካሪ ሰሌዳ ለውጥ መመሪያ መሠረት አዲሱ የተሸከርካሪ ሰሌ...
05/10/2025

አዲሱ የተሸከርካሪ ሰሌዳ ከሁለት ወራት በኋላ አገልግሎት ላይ ይውላል !!

: የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ባወጣው የተሽከርካሪ ሰሌዳ ለውጥ መመሪያ መሠረት አዲሱ የተሸከርካሪ ሰሌዳ የመቀየር ሥራ ከሁለት ወራት በኋላ እንደሚጀመር በሚኒስቴሩ የትራንስፖርት አገልግሎት እና ቁጥጥር ዘርፍ አማካሪ አቶ አሰፋ ሀዲስ #ለአሐዱ ተናግረዋል።

ከዚህ በፊት የተመዘገቡ ተሽከርካሪዎች የቀድሞውን ሠሌዳ በመመለስ አዲስ የተሸከርካሪ የመለያ ቁጥር ሠሌዳ እንዲወስዱ የማድረግ ሥራ እንደሚሰራ አመልክተዋል።

በኢትዮጵያ የተሽከርካሪዎች የመለያ ቁጥር ሰሌዳ አይነቶችና ምልክቶች መወሰኛ እና የአገልግሎት አሰጣጥ መመሪያ 1050/2017 ሆኖ መጽደቁ ይታወሳል።

በመመሪያው መሰረት አሁኑ በሥራ ላይ ያሉ የተሽከርካሪ ሰሌዳዎች ላይ የሚቀመጠው የተለያዩ ክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች መለያዎች ተመሳሳይ መለያ እንዲኖራቸው ያስገድዳል።

በሀገሪቱ የሚመዘገቡ ሁሉም ተሸከርካሪዎች የሚለጥፉት የመለያ ቁጥር ሠሌዳ ላይ ፤ የኢትዮጵያ ካርታ እንዲሁም ኢትዮጵያ ባጸደቀችው ዓለም አቀፍ ስምምነት መሠረት የተሰጣትን ሀገራዊ ልዩ ምልክት " ETH " እና " ኢት " የሚል የግእዝ ፊደላት እና የላቲን ፊደላት ይዘት እንዲኖረው ይደረጋል።

መመሪያው አሁን በሥራ ላይ ያሉ የተሽከርካሪ ሰሌዳዎች ላይ የሚቀመጠውን የተለያዩ ክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች መለያዎችን አላካተተም።

05/10/2025

ጋዜጠኛ ሶፎኒያስ ዋሲሁን አስነካው !!
❤️🙏❤️..
..
አበባ
:
:
゚viralシ

05/10/2025

ቲጂ አገልግል ሥራ ጀምራለች ❤️🙏..........
አበባ
:
:
゚viralシ

አትሌት ፅጌ ዱጉማ ምን ገጠማት !?🥹  : የ23 ዓመቷ አትሌት ፅጌ ድጉማ በህመም ምክንያት ከኒውዮርኩ የ1 ማይልስ ውድድር ውጪ ሆነች፤ አትሌቷ ከውድድር ውጪ የሆነችው በገጠማት ህመም ምክንያ...
05/10/2025

አትሌት ፅጌ ዱጉማ ምን ገጠማት !?🥹

: የ23 ዓመቷ አትሌት ፅጌ ድጉማ በህመም ምክንያት ከኒውዮርኩ የ1 ማይልስ ውድድር ውጪ ሆነች፤ አትሌቷ ከውድድር ውጪ የሆነችው በገጠማት ህመም ምክንያት ነው የተባለ ሲሆን፤ወደ አዲስ አበባ ሳትመለስ ለህክምና በሚል ከቶኪዮ በቀጥታ ወደ ኔዘርላንድስ መጓዟም ተረጋግጧል።

የ2024 የፓሪስ ኦሎምፒክ በ800ሜ የብር ሜዳልያና የ2024 የግላስኮው የአለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና በ800ሜ የወርቅ ሜዳልያ ባለቤት በመሆን የሀገሯን ስም ከፍ አድርጋ ማስጠራት የቻለችው አትሌት ፅጌ ዱጉማ በቶኪዮ ወርቅ ሊያመጡ ይችላሉ ተብሎ ከፍተኛ ግምት ከተሠጣቸው አትሌቶች አንደኛዋ ነበረች።

አትሌቷ ግን በፍፃሜው ውድድር ለሜዳልያ የሚያበቃ ብቃት ባለማሳየቷ ውድድሯን በ መጨረሷ ብዙዎች አሁን ድረስ ውጤቷን አምነው ለመቀበል በመቸገራቸው አትሌት ፅጌ ዱጉማ ምን ቢገጥማት ነው ከሜዳልያ ውጪ ልትሆን የቻለችው በማለት ጥያቄ እያነሱ ይገኛሉ።

ከታማኝ የመረጃ ምንጮቻችን እንዳገኘነው መረጃ ከሆነ አትሌቷ ሆዷ አካባቢ ህመም ገጥሟት እንደነበረና በዚህም ምክንያት ውድድሩ አተጠናቀቀ በኃላ ከልዑኳን ቡድኑ ጋር ወደ አዲስ አበባ ልታደርገው የነበረውን በረራ በመሠረዝ ለከፍተኛ ህክምና በሚል ወደ ኔዘሬላንድስ(ሆላንድ)መብረሯና እስከአሁንም እዛው ህክምናዋን በመከታተል ላይ እንደሆነ ነው የተሠማው።

እንደ እነዚሁ ታማኝ የመረጃ ምንጮቻችን ከሆነ አትሌት ፅጌ ዱጉማ አሸናፊ ለሚሆነው አትሌት 60ሺ ዶላር በሚያስገኘው የኒውዮርኩ የአንድ ማይል ተጠባቂው ውድድር ላይ ተሳታፊ እንደምትሆን ይፋ ከሆነ በኃላ አትሌቷ ሆዷ አካባቢ ገጠማት በተባለው ህመም ምክንያት ውድድሯን መሠረዟ ነው የተሠማው።

በአጭር ርቀት ለሀገርዋ ታሪክ ትሠራለች በሚል ተስፋ የተጣለባት አንፀባራቂዋ ጥቁሯ ኮከብ ይሄንኑ የገጠማትን ህመምና ለህክምና መጓዟን ለፌዴሬሽኑ ስራ አስፈፃሚዎች የገለፀች ቢሆንም ፌዴሬሽኑ በጉዳዩ ዙሪያ እስከአሁን የተነፈሠው ነገር የለም።

አትሌቷ ገጠማት በተባለው ህመም፣ወደኔዘርላንድስ ለህክምና በመጓዟ ዙሪያና ውጤት ያጣችበት ትክክለኛው ምክንያት ምንድነው በሚለው ዙሪያ አሠልጣኝ ጌታሁን ታደሠን አነጋግረን ለመምጣት ጥረት እናደርጋለን።

(✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)

04/10/2025

አምለሰት ሙጬ ስለ ጅማ ኮሪደር !!
❤️🙏❤️...
#አምለሰት #ቴዲአፍሮ #ቴዲ
እንዲህም አይነት ፍቅር አለ ፤ ፈጣሪ ካንቺ ጋር ይሁን !!😢😢😢...
አበባ
:
:
゚viralシ

የህፃን ኤልያናን ነፍስ እንታደግ !!😢  : ህፃን ኤልያና ፀጋዬ ትባላለች ። የ4ወር ህፃን ናት ። ህፃና ኤልያና ከተወለደች ጀምሮ በከፍተኛ የልብ ህመም እየተሰቃየች ትገኛለች ።ስለሆነም የጥ...
04/10/2025

የህፃን ኤልያናን ነፍስ እንታደግ !!😢

: ህፃን ኤልያና ፀጋዬ ትባላለች ። የ4ወር ህፃን ናት ። ህፃና ኤልያና ከተወለደች ጀምሮ በከፍተኛ የልብ ህመም እየተሰቃየች ትገኛለች ።ስለሆነም የጥቁር አንበሳ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ህፃኗ 6 ወር ሳይሞላት አስቸኳይ የቀዶ ጥገና ህክምና እንደሚያስፈልጋት አሳውቆናል ።

ህክምናው በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል እንደማይሰጥ ለማወቅ ተችሏል ። ሆኖም ግን እኛ የህፃኗ ወላጆች ህፃኗን ለማሳከም ባደረግነው ጥረት አዲስ አበባ በሚገኘው ኢትዮ ኢስታንቡል የግል ሆስፒታል እንደሚሰጥና 1,500,000 (አንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ ብር) እንደሚያስፈልገን ተነግሮናል ።

ይሄ ገንዘብ ከአቅማችን በላይ በመሆኑ የህፃኗን ህይወት ለመታደግ የእርዳታ እጃችሁን እንድትዘረጉልን ስንል በልዑል እግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን፡፡

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፡- 1000406884523
አባይ ባንክ፡-117991113078131
ቴሌ ብር፡-0985368425

*ማስታወሻ መርዳት ባንችል የሚረዳ ይኖራልና መረጃውን ለሌሎች በማጋራት እንተባበራት !!❤️🙏❤️

04/10/2025

እንዲህም አይነት ፍቅር አለ ፤ ፈጣሪ ካንቺ ጋር ይሁን !!😢😢😢...
አበባ
:
:
゚viralシ

Address

22 Stanley Road
London

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ማለዳ - Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share