25/09/2025
ዘመቻ አርበኛ አደም አሊ (አባ ናደው) በታላቅ በድል ተጀምሯል! (ከ 1,000 ክላሽ ላይ ተማር - ኳል )
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ መስከረም 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከጧቱ 12:00 ሰዓት የተጀመረው ዘመቻ አርበኛ አደም አሊ (አባ ናደው) በአምስቱም ኮሮች እና በዕዙ ልዩ ዘመቻ ከፍተኛ ተጋድሎ በማድረግ አስደናቂ ድሎች ተገኝተዋል።
የተገኙ ድሎች:-
፩ኛ. ምስራቅ አማራ ኮር 1 ሰሜን ወሎ ዞን ጉባላፍቶ ወረዳ በቅሎ ማነቂያና ዙሪያው ላይ ክፍተኛ ትንቅንቅ ያደረገ ሲሆን በዚህም በተለይ ቁልፍ ወታደራዊ ቦታ በሆነችው በቅሎ ማነቂያ የተገኙ ድሎች:-
አሳምነው ክፍለጦር
• ሞርተር 2
• ብሬን 2
• ክላሽ 76
• ስታር ሽጉጥ 1
• 7000 የብሬን ተተኳሽ
• 9800 የክላሽ ተተኳሽ
• 1300 የዲሽቃ ተተኳሽ
• 95 የደረት ትጥቅ
• 180 ወታደራዊ ሻንጣ
• 5 መገናኛ አይኮም
ባለሽርጡ ክፍለጦር:-
ምስራቅ አማራ ኮር 1 ባለሽርጡ ክፍለጦር የደቡብ ወሎ ዞን ወረባቦ ወረዳ መቀመጫ በሆነችው ቢስቲማ ከተማ፣ በጉቢሳና፣ በጉሃ፣ በሰቀላ እና ቴሌው ዙሪያ ከፍተኛ ውጊያ ያደረጉ ሲሆን የጉቢሳ ምሽግ ተሰብሯል።
የወረዳው ዋና መቀመጫ የሆነውን ቢስቲማ ከተማን ሙሉበሙሉ በፋኖ ቁጥጥር ስር ለማስገባት ከፍተኛ ተጋድሎ እየተደረገ ይገኛል። እስካሁን ባለው መረጃ:-
• የተደመሠሠ 78
• የቀሰለ 53
• ክላሽ 7
ባለሽርጡ ክፍለጦር የሀብሩ ወረዳ ቆላማ የአፋር አጎራባች አካባቢዎችን በመቆጣጠርና ሕዝባዊ አስተዳደር የዘረጋው የባለሽርጡ ክፍለጦር ዛሬ የሀይቅ፣ ደሴና ኮምቦልቻ ቆላማ አካባቢዎችን ከልጅ እያሱ ኮር ጋር ጥምረት በመፍጠር ወደፊት እየገሰገሰ ይገኛል።
ሐውጃኖ ክፍለጦር
• ዲሽቃ 1
• ስናይፐር 1
• ክላሽ 40
• የብሬን ተተኳሽ 5,000
• የክላሽ 3000
• የወገብ ትጥቅ 23
• የክላሽ ካዝና 18
• F1 Bomb 10
• የሞርተር ቅንቡላ 7
በምስራቅ አማራ ኮር 1 አጠቃላይ የተደመሰሰና የተማረከ:-
• የተደመሰሰ 1 ኮረኔል፣ መቶአለቃ ኢሳያስን ጨምሮ 282 የአገዛዙ ሰራዊት
• ምርኮኛ 18
• የበቅሎ ማነቂያ አስተዳዳሪ አቶ አያሌው ደሳለ ከነ ግብረ አበሮቹ ተደምስሷል።
፪ኛ. ምስራቅ አማራ ኮር 2 ሰሜን ወሎ ዞን ግዳን ወረዳ ወንዳች ከተማ በቁጥጥር ስር አውለው፣ በተለይ እዚህ ከተማ ላይ በተደረገ አስደናቂ ተጋድሎ የተገኘ ድል:-
ዞብል አንባ ክፍለጦር
• ዲሽቃ -3
• ብሬን - 8
• ክላሽ 130
• ስናይፐር - 5
• F1 Bomb - 102
• 82MM ሞርተር -2
• 120MM ሞርተር - 1
• የሞርተር ቅንቡላ - 30
- ኦራል ከነተተኳሹ
- 22ሺ በላይ ተተኳሽ
ካላኮርማ ክፍለጦር
• 1 ዲሽቃ
• 2 ብሬን
• 2 ስናይፐር
• 89 ክላሽ
• የብሬን ተተኳሽ 1500
• የክላሽ ተተኳሽ 2000
• 4 አይኮም መገናኛ
• 50 የክላሽ ካዝና
• 36 ኤፍዋን ቦምብ
• 2 የሜዳ መነፀር
ታጠቅ ክፍለጦር ወንዳች ላይ ከፍተኛ ተጋድሎ አድርገዋል።
• 20 ክላሽ
• 4 የደረት ትጥቅ
• 4 ካዝና
በምስራቅ አማራ ኮር 2 እንደ አጠቃላይ የተማረከና የተደመሠሠ:-
• ምርኮኛ 147
• ሙት 137
• በርካታ ወታደራዊ ቁሳቁስና ሬሽን ተገኝቷል።
፫ኛ. ልዩ ዘመቻ ሰሜን ወሎ ዞን አንጎት ወረዳ አካል የሆነውን ታላቅ ወታደራዊ ቁልፍና ስትራቴጅ ቦታ በተለይም ከወልደያ ላሊበላ- ከወልደያ ባህርዳር ያለውን መስመር በቁጥጥር ስር አውለውታል። ገዥ መሬት የሆነውን ድልብን ተቆጣጥረዋል። በዚህ ውጊያም በርካታ ወታደራዊ መሳሪያ ተማርከዋል።
• 1 ብሬን
• 2 ክላሽ
• 7 ምርኮኛ
፬ኛ. ላስታ አሳምነው ኮር በሰሜን ወሎ ዞን ግዳን ወረዳ ኩልመስክ፣ ወንዳች ዙሪያውን በተደገ ከፍተኛ ትንቅንቅ የተገኙ ድሎች:-
ተከዜ ክፍለ ጦር ኩልመስክ ከተማን በመቆጣጠር
• 11 የተደመሰሰ
• 3 የተማረከ
• 20 ክላሽ
• 420 የክላሽ ተተኳሽ
• 580 የብሬን ተተኳሽ
ጥራሪ ክፍለ ጦር
• 1 ሞርተር (82 ሚሊሜትር)
• 1 ዲሽቃ
• 1 ብሬን
• 1 ስናይፐር
• 54 ክላሽ
በዛሬው ዕለት መስከረም 14 ቀን 2018 ዓ.ም ጧት 12:00 ሰዓት የጀመረው ውጊያ አሁንም እንደቀጠለ ቢሆንም እስከ 8:00 ሰዓት በተካሄደው ውጊያ አጠቃላይ የተገኙ ድሎች:-
• ሞርተር - 6
• ዲሽቃ - 6
• ብሬን - 14
• ስናይፐር - 9
• ክላሽ - 438
• የተደመሠሠ ጠላት - 471
• የተማረከ - 175
• ተተኳሽ - 52,600
• ወታደራዊ ሬዲዮ - 9
• F1 Bomb - 148
• ቁስለኛ - 126 ይዞት የወጣው
• የሞርተር ቅንቡላ - 37
• 1 ሲኖ ትራክ ሙሉ ወታደራዊ ቁሳቁስና ሬሽን
አገዛዙ የሚተማመንባቸው የሰሜን ምስራቅ ዕዝ አካል የሆኑት 12ኛና 61ኛ ክፈለጦር መካከል የ12ኛ ክፍለጦር 70% ኃይላቸውን መማረክ፣ መደምሰስ እና ማፍረስ ተችሏል።
#ማስታወሻ:- የልጅ እያሱና የንጉስ ሚካኤል ኮር የአውደ ውጊያ መረጃዎች እንደደረሱን የምናሳውቅ ይሆናል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ዘመቻ አርበኛ አደም አሊ (አባ ናደው)
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
መስከረም 14/2018 ዓ.ም