31/12/2025
በአራዳ ክ/ከተማ አስተዳደር የጉሩሞ ላዲሳ ቀበሌ ሰላምና ፀጥታን እና በ100 ቀናት ውስጥ በህዝብ ተሳትፎ የሚሰሩ የልማት ዙርያ ፖሊስ፣ ደንብ አስከባሪዎች፣ እና አጠቃላይ ከሁለቱ ቀጠና ህዝብ ጋር ሰፋ ያለ የውይይት እና ምክክር መድረክ ተካሄዷል
ጉ/ላድሳ ታህሳስ 22/2018 ዓ.ም
በመድረኩ በጭንብል ተሸፍነው በሰው አካል እና ንብረት ላይ ጉዳት የሚያደረሱ አካላት ከወዲሁ ሊገቱ እንደሚገባ እና በዓሉ ከመድረሱ በፍት እንዲሁ መወያየት አስፈላጊ እንደሆነና ተገልጿል።
ህዝቡ በሰላም ወቶ በሰላም እንዲገባና የየዕለት ተግባር እንዲወጣ ለማድረግ ፀጥታ አካላት በቅንጅት እንዲሰሩም በአጽንኦት ተመላክቷል።
በቀጣይ የሚከበሩ የገና በዓል ያለምንም ፀጥታ ችግር እንዲከበር የፀጥታ ተቋማት በቅንጅት እንዲሰሩ በሀሳብ ተነስተው በየቀጠናው የፀጥታ አጋዥ ኃይሎችን እና የሮንድ ስራ የማጠናከር ሥራ መሰራት እንዳለበት ተነስቷል።
ህዝብ ለህዝብ ትስስር የሚያጠናክር በህዝብ ተሳትፎ በየደረጃው የሚሰሩ የልማት ስራዎችን በማጠናከር በቅንጅት እንደምሰራም ተነስቷል።
የጸጥታ እና የልማት ስራዎች በጥብቅ ዲሲፕሊን የሚመራ ጠንካራ የፓርቲ መዋቅር ለመፍጠርና የህዝቡን መሰረታዊ ችግሮች ለመቅረፍ ከመድረኩ በስፋት ተነስተዋል።
በመድረኩ የቀበሌ ዋና አሰተዳደር አቶ ደሳለኝ ዳንሳ የቀበሌው ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኤፌሶን ኤርምያስ እና የፀጥታ አካላትን ጨምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።