ASER MEDIA

ASER MEDIA ASER MEDIA is a news and current affairs channel. follow us on Facebook, tiktok, and YouTube.

የካሜራ ባለሞያው እስካሁን ድረስ የገባበት አልታወቀም።ከተሰወረ 140 ቀናት ሆኖታል።የካሜራ ባለሞያው ወጣት ፊልሞን (ፊላሪ) ነሀሴ 4/ 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 2:00 ሰዓት በመቐለ ከተማ ዓዲ...
03/01/2026

የካሜራ ባለሞያው እስካሁን ድረስ የገባበት አልታወቀም።

ከተሰወረ 140 ቀናት ሆኖታል።

የካሜራ ባለሞያው ወጣት ፊልሞን (ፊላሪ) ነሀሴ 4/ 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 2:00 ሰዓት በመቐለ ከተማ ዓዲ ሓቂ ክፍለ ከተማ በባጃጅ እየተጓዘ ሳለ ነው የተሰወረው። ከተሰወረ በጥቂት ቀናት ውስጥ ፓሊስ ጉዳዩን ተከታትሎ በአጭር ጊዜ ሁኔታውን እንደሚያሳውቅ ተናግሮ ነበር።ይሁን እንጂ ወጣት የፊልም ባለሙያው ከተሰወረ ዛሬ ቅዳሜ ታህሳስ 25 ቀን 2018 ዓ/ም 140 ቀናት ቢቆጠሩም ፤ ፓሊስ የሚጨበጥ መረጃና ወጤት አላሳወቀም።የካሜራ ባለሞያው ባለትዳርና የሁለት ህፃናት አባት ሲሆን ሰርቶ ሲያስተዳድራቸው የነበሩት ቤተሰቡ ሃዘን አልበቃ ብሏቸው ለችጋር ተጋልጠው " የእርዱን " እጃቸውን ዘርግተዋል።

የወጣት የፊልም ባለሙያው መሰወር እጅግ ያሳሰባቸው ወዳጅ ዘመዶች " ሁሉም ሰብአዊ ፍጡር በፍለጋ ይተባበረን " በማለት ተማፅነዋል። ከአስከፊው የትግራይ ጦርነት በኋላ በክልሉ የሰዎች ስወራና እገታ መባባሱ ይታወቃል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ

ብንእሱ ዝዓበዬ-----እዚ ሓው ፎቖዶ መንደራት (ገጠራት) ክጎዪ ውዒሉ ይሓድር! ክሰርሕዎ ዝነበሮም ካልኦት ኮይኖም ክነሱ - እዚ “ሚኪ ሕንሽሽ” ዝበሃል ብርቱዕ - ዘይህከ ንኡስ ሓላፍነቶም ...
01/01/2026

ብንእሱ ዝዓበዬ
-----
እዚ ሓው ፎቖዶ መንደራት (ገጠራት) ክጎዪ ውዒሉ ይሓድር! ክሰርሕዎ ዝነበሮም ካልኦት ኮይኖም ክነሱ - እዚ “ሚኪ ሕንሽሽ” ዝበሃል ብርቱዕ - ዘይህከ ንኡስ ሓላፍነቶም ናይዝረስዑ ጽጉባት ዕዮ ክዓዪ ይውዕል፡፡ ሓደ መዓልቲ ድኻሙ ከምዝሐፍሎ ንሹ ኮነ ተመልከቱ እምነት ኣለዎም! ምርቓ እተን ፅጉማትን ደቀን ብኲናት ዝሰኣና አደታትን ኣምላኽ ከምዝቕበሎ እውን ዘጠራጥርአ ይኮነን! ሚኪ ከም ኣብነት ኣልዒልና እምበር ከማኡ ዝበሉ ኣብ ጎኒ ህዝቦም ደው ዝበሉ መናእሰይ ንርኢ ኣሎና ኢና - ይቕናዓዮም!

ከማኻ ዝበሉ የብዘሓዮም ክቡር ሓው!

አል ሻባብ ሶማሊያውያን በእስራኤል ላይ ጠመንጃ እንዲያነሱ ጥሪ አቀረበ-------------እስራኤል ለሶማሊላንድ የሰጠችውን የነጻ አገርነት ዕውቅና በመቃወም እስላማዊው ታጣቂ ቡድን አል ሻብብ...
01/01/2026

አል ሻባብ ሶማሊያውያን በእስራኤል ላይ ጠመንጃ እንዲያነሱ ጥሪ አቀረበ
-------------
እስራኤል ለሶማሊላንድ የሰጠችውን የነጻ አገርነት ዕውቅና በመቃወም እስላማዊው ታጣቂ ቡድን አል ሻብብ ሶማሊያውያን በእስራኤል ላይ ጠመንጃ እንዲያነሱ ጥሪ አቀረበ። የቡድኑ ቃል አቀባይ ባስተላለፈው በቪዲዮ በተቀረጸ መልዕክት ሶማሊያውያን አገራቸውን ከእስራኤል ለመከላከል ታጥቀው እንዲነሱ ጥሪ አስተላልፏል።

ክሲ ደብረፅዮን........መንግስቲ ፌደራል  ስምምዕ ፕሪቶርያ ብምጥሓስ ኣብ ትግራይ ኣብ ልዕሊ ተመዛበልቲ ዝተጠናኸረ ጃምላዊ ጥምየት ክቕፅል ይገብር ኣሎ ።ህፁፅ ፃውዒት ንህፁፅ ሰብኣዊ ምት...
31/12/2025

ክሲ ደብረፅዮን........
መንግስቲ ፌደራል ስምምዕ ፕሪቶርያ ብምጥሓስ ኣብ ትግራይ ኣብ ልዕሊ ተመዛበልቲ ዝተጠናኸረ ጃምላዊ ጥምየት ክቕፅል ይገብር ኣሎ ።

ህፁፅ ፃውዒት ንህፁፅ ሰብኣዊ ምትእትታው ብዝብል ኣቦ ወንበር ውድብ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ -ህወሓት ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ናብ ኣቦ ወንበር ኮሚሽን ሕብረት ኣፍሪካ ማሕሙድ ዓሊ ዩስፍ ኣብዝለኣኽዎ ቅሉዕ ደብዳበ ኣብ ትግራይ ኣብ ልዕሊ ተመዛበልቲ ኮነ ኢልካ ዝፍፀም ዘሎ ጥሜት ህፁፅ ኣቓልቦ ዝጠልብ እዩ ኢሎም ።

ኣብ ትግራይ ዝርከባ ማእኸላት ተመዛበልቲ- ሕፃፅ ፣ ሽረ ፣ ዓድዋ፣ ኣብይ-ዓዲ፣ ዓዲግራት፣ መቐለን ወዘተ...-ብኣማኢት ኣሽሓት ዝቑፀሩ ሰባት ራብዓይ ዓንቀፅ ስምምዕ ፕሪቶርያ ብዝጥሕስ ስርዓታዊ ጥምየት የጋጥሞም ኣሎ ክብሉ ዶክተር ደብረፅዮን ኣብሪሆም ።

ብጥምየት ኣካላቶም ማሲኑን ተዳኺሙን ዓፅሚ ዝተርፉ ወገናት ፣ ግቡእ ሕክምና ዝተሓረሞም ቁስሎም ኣደዳ ፅንፅያ ዝተቓልዑ ዜጋታት ብዙሓት ሙዃኖምን ከምሳዕቤኑ ድማ ህፅናት ብዕሸሎም ኣረጋውያን በብ ሰሙኑ ሂወቶም ይስእኑ ኣለው ዝበሉ ዶክተር ደብረፅዮም እዚ ድማ ኣብ ስምምዕ ፕሪቶርያ ዓንቀፅ ኣርባዕተ ንዝሰፈረ ነጥቢ እቲ ስምምዕ ዝጠሓሰ ሙዃኑ ገሊፆም ።

ሕዚ እውን መንግስቲ ፌደራል ንስምምዕ ፕሪቶርያ ብምጥሓስ ኣብ ትግራይ ኣብ ልዕሊ ተመዛበልቲ ዝተጠናኸረ ጃምላዊ ጥምየት ክቕፅል ይገብር ኣሎ ዝበሉ ዶክተር ደብረፅዮን እቲ መንግስቲ ኣብ ክንዲ ህፁፅ ሓገዝ ዘቀላጥፍ ናብ ናይ ሓሶት ክስታትን ፕሮፓጋንዳን ምእታው እዩ መሪፁ ኢሎም።

ዛጊድ ትርጉም ዘለዎ ደገፍ ክገብር ዘይከኣለ ኮሚሽን ምሕደራ ስግኣት ሓደጋ ፌደራል ስቓይ ተመዛበልቲ ብዝኸፍኣ ኣብ ዘጋድድ ናይ ፕሮፖጋንዳ መግለጺታት እዩ ኣድሂቡ ዘሎ ዝብሉ ዶክተር ደብረፅዮን ካብኡ ብዝገደደ ኣብ ልዕሊ ስቓይ ወገናቶም ኣደንጊፅዎም ሓገዝ ንምግባር ኣብዝተንቀሳቐሱ ነጠፍቲ ማሕበራዊ ሚድያ ንህዝቦም ሓገዝ ምግባሮም ከም ገበን ተቖፂሩ ከፈራርሖም ከሸቑርሮም እዩ ተራእዩ ኢሎም።

ብጥምየት ንዝተጎድኡ ወገናት ሓገዝ ኣብ ልዕሊ ዘተኣኽከቡ ፈጠርቲ ፅዕንቶ ቲክቶከራት ብምፍርራሕ ንግዳይ ጥምየት ኢሎም ዝኣከብዎ ብዓሰርተታት ሚልዮናት ብር ናብ ሒሳብ መንግስቲ ፌደራል ከእትውዎ ተገዲዶም እዮም ክብሉ ከም ኣብነት ጠቒሶም ።

ብመሰረት ስምምዕነት ፕሪቶርያ ናብ መረበቶም ክምለሱ ዝግብኦም ልዕሊ 1 ሚልዮም ወገናት ሕዚ እውን ኣብ ከቢድ ፀገም ይርከቡ ዝበሉ ኣቦ ወንበር ውድብ ህወሓት ዶክተር ደብረፅዮ ነቲ ስምምዕ ኣብ ምኽታም መንጎኛታት ዝነበሩ ኣካላት ብቕልጡ ፍሉይ ኣቃልቦ ክህብሉ ፀዊዖም ።

ዶክተር ደብረፅዮን ኣብ ደብዳብኦም ህፅፅ ሰብኣዊ ተበጻሕነት ክህሉ ፤ ጉዳይ ዝወሃብ ረድኤትን ተበፃሕነት ናጻ መርመራ ክካየድ ፤ ፡- መንግስቲ ፌደራል ዘካይዶ ዘሎ ገደብ ምትእኽኻብ ገንዘብ ዜጋታት/ዲያስፖራ ተበግሶ ሓገዛት ገበናዊ ምግባር ከብቅዕ ፤ ህዝባዊ ተሓታትነት ክረጋገፅን ብድምሩ ስምምዕ ፕሪቶርያ ብምሉእነት ምትግባር ቅልጡፍ ስጉምትታት ዘድልዩ ጉዳያት ሙዃኖም ኣስሚሮምሉ ።

በትግራይ ክልል የተፈናቃዮች የሰብአዊ ድጋፍን በተመለከተ ከአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን የተሰጠ መግለጫ****************** የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን በትግራይ ክልል ሰሜ...
24/12/2025

በትግራይ ክልል የተፈናቃዮች የሰብአዊ ድጋፍን በተመለከተ ከአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን የተሰጠ መግለጫ
******************
የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን በትግራይ ክልል ሰሜን ምዕራብ ዞን፣ አስገደ ወረዳ፣ ሕፃፅ ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ተፈናቃዮች የሰብአዊ ድጋፍ አቅርቦትን በተመለከተ መግለጫ ሰጥቷል።
በመግለጫውም፣ መንግሥት በጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ዜጎቻችንን የቅድሚያ ቅድሚያ ትኩረት በማድረግ የምግብ ሰብአዊ ድጋፍ እያቀረበ እንደሚገኝ ገልጿል።
ሆኖም በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች በሕፃፅ ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ዜጎቻችን የሰብአዊ ድጋፍ እንዳልደረሳቸው የሚገልጽ የተሳሳተ እና የመጠለያ ጣቢያውን አጠቃላይ ሁኔታ የማይገልጽ ዘገባ ሆኖ መገኘቱን ነው ኮሚሽኑ ያስታወቀው።
የሰብአዊ ድጋፍን በሚመለከት በመደበኛነት ዓመቱን በሙሉ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው የምግብ ስርጭት ሳይቆራረጥ እየተከናወነ መሆኑን ኮሚሽኑ በመግለጫው አመላክቷል።
"በሕፃፅ ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያም የሚገኙ ዜጎቻችን ዓመቱን ሙሉ ተመሳሳይ ድጋፍ ሲደረግላቸው የነበረ ሲሆን ከመስከረም ወር 2018 ጀምሮ እስከ ታኅሣሥ ወር 2018 ድረስ የተሟላ እና ያልተቆራረጠ የምግብ ሰብአዊ ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑን መረጃዎቻችን ያሳያሉ” ሲል ነው የገለጸው።
በአስገደ ወረዳ ሕፃፅ ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያ ባለፉት አራት ወራት የተደረገውን ድጋፍ በቁጥር ለመግለጽ፣ 14 ሺህ 413 ዜጎች ድጋፍ ሲደረግ ቆይቷል። በተጨማሪም ከአጎራባች መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ዜጎችን ጨምሮ በመስከረም ወር 16 ሺህ 775፤ በጥቅምት ወር 18 ሺህ 290፤ በኅዳር ወር 17 ሺህ 813 እንዲሁም በታኅሣሥ ወር የሚያስፈልገው ለ14 ሺህ 413 ዜጎች የሚያስፈልግ ምግብ ተሰራጭቷል ሲል በዝርዝር አስቀምጧል።
በዚህም በድምሩ 11 ሺህ 406 ኩንታል ምግብ (ስንዴ፣ ማሽላ፣ ጥራጥሬ እና የምግብ ዘይት) ባለፉት አራት ወራት እንዲዳርሳቸው ተደርጓል። ይህ ድጋፍ በገንዘብ ሲተመን ከ257 ሚሊዮን (ከሁለት መቶ አምሳ ሰባት ሚሊየን) ብር በላይ እንደሚሆን ገልጿል።
በሌላ በኩል በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የተለያዩ የሰብአዊ ድጋፍ ችግሮች መኖራቸውን እና ተጨማሪ የፌዴራል ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ቢጠየቅ ኖሮ በኮሚሽናችን በኩል አስፈላጊውን ድጋፍ ለመፈጸም የሚያስችል ዝግጁነት ያለን መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን ሲል በመግለጫው አስታውቋል።
ከላይ የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ ለተፈናቃይ ማኅበረሰብ የሚላከው ድጋፍ ለታለመለት ዓላማ ብቻ መዋሉን የማረጋገጥ እና ክፍተቶች ቢኖሩም እንዲሟላ የማድረግ ኃላፊነት የክልሉና የአካባቢው ጊዜያዊ አስተዳደር መሆኑን ለማሳሰብ እንወዳለን ብሏል ኮሚሽኑ።

ትግራይ - ሎሚ ነዚኣ ትመስል!
23/12/2025

ትግራይ - ሎሚ ነዚኣ ትመስል!

ሕፃፅ'አረጋውያን ይበዙበታል' በተባለው የሕጻጽ የተፈናቃዮች መጠለያ የተከሰተው ምንድን ነው?-----------------------------በትግራይ ክልል በሰሜናዊ ምዕራብ አካባቢ ካሉት የተፈ...
23/12/2025

ሕፃፅ
'አረጋውያን ይበዙበታል' በተባለው የሕጻጽ የተፈናቃዮች መጠለያ የተከሰተው ምንድን ነው?
-----------------------------
በትግራይ ክልል በሰሜናዊ ምዕራብ አካባቢ ካሉት የተፈናቃይ ካምፖች መካከል አንዱ በሆነው ሕጻጽ በርካቶች በረሃብ ውስጥ መሆናቸውን ለቢቢሲ ትግርኛ ተናገሩ።
ተፈናቃዮቹ በእርዳታ የሚደርሳቸው ምግብ ድጋፍ በቂ ካለመሆኑም በላይ ከፍተኛ የጥራት ችግር እንዳለበት ገልጸዋል።
በምዕራብ ትግራይ በመቶዎች የሚቆጠሩ ተፈናቃዮች በሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት እጥረት ምክንያት "በረሃብ እና በበሽታ" የመጠቃት አደጋ እንደተጋረጠባቸው ተናግረዋል።
ከአስር ሺህ በላይ ተፈናቃዮች በሚኖሩበት የሕጻጽ መጠለያ ውስጥ በርካታ አዛውንቶች፣ ነፍሰ ጡር እናቶች እና ሕጻናት በምግብ እና በሕክምና እጦት እየተሰቃዩ መሆኑን ነዋሪዎች ለቢቢሲ ትግርኛ ተናግረዋል።
የሕጻጽ የተፈናቃዮች ማዕከል አስተባባሪ ቄስ አብርሃ አርአያ እንዳሉት ቢያንስ 300 ሰዎች ባለፉት ስድስት ወራት የእርዳታ እህል አላገኙም።
በመጠለያ ጣቢያው ውስጥ የሚገኙት አንድ እናት ለቢቢሲ ትግርኛ ስለሁኔታው ሲያስረዱ "አረጋውያን አሉ፤ ጉድ ነው የምናየው። አንዳንድ ለነፍሴ ያለ የሚያመጣልን እንጀራም ደርቆ እርሱም አይበላም። በውሃ ነክረው ፈትፍተው ለመብላት ይሞክራሉ" ብለዋል።
የትግራይ ጦረነት ሲቀሰቀስ ቤተሰቦቻቸው ተበታትነው ወደ ሱዳን መሰደዳቸውን የሚናገሩት እኚህ እናት አሁን ብቻቸውን መቅረታቸውን ይናገራሉ።
"እዚህ ሰው ሁሉ በረሃብ አንጀቱ ተጣብቋል" ያሉት ተፈናቃይዋ "ዋናው ችግር ምግብ የሚባል ነገር የለም። የሚሰጡንም እህል የሚሆን አይደለም። ባለፉት ስድስት ወራት የሰጡን እህል፣ እህል የሚባል አይደለም" ሲሉ የሚሰጣቸው የእርዳታ እህል ጥራት ችግር አንዳለበት ያስረዳሉ።
". . .ያቺንም የምትሰጠውን የማያገኝ አለ። ማሽላው ራሱ የተበላሸ ነው፤ ብዙ ቆሻሻ አለው። ታጥቦ ራሱ እህል መሆን አይችልም። ያቺም የተበላሸች እህል ስንት ነፍሰ ጡር፣ ስንት አረጋውያን ስንት አራስ አያገኛትም" ሲሉ ያለውን ችግር አስረድተዋል።
"እስከ ዛሬ በሕይወት መቆየታችን ራሱ ተመስገን ነው የሚባለው። ከአሁን በኋላ ደግሞ ምን እንደምንሆን አናውቅም።"
በትግራይ ክልል በመቀለ፣ በሽረ፣ በተምቤን፣ በአቢ አዲ፣ በሰሜን ምዕራብ አካባቢ ደግሞ ሰለህለሃ በአጠቃላይ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ተፈናቃዮች እንደሚገኙ የክልሉ መንግሥት ይገልጻል።
በሕጻጽ መጠለያ ውስጥ የተፈናቃዮች አስተባባሪ የሆኑት ቄስ አብርሃ አርአያ በበኩላቸው በካምፑ ውስጥ ዘግይተው የመጡ አረጋውያን መኖራቸውን ገልጸው እነርሱ አሁን ለችግር መጋለጣቸውን ያስረዳሉ።
እነዚህ በዕድሜ የገፉ ተፈናቃዮች "እህል ውሃ ቢያገኙም ጧሪ ስለሌላቸው ከጤና ሁኔታም አንጻር ያለባቸው ችግር የበረታ ነው" ማለታቸውን ቢቢሲ ትግርኛ ዘግቧል።
የረሃብ ችግሩ በተለያዩ አካባቢዎች ቢከሰትም የሕጻጽ አካበቢ የተለየ የሚያደርገው "አረጋውያን የሚገኙበት ካምፕ ስለሆነ ነው" ሲሉ አስተባባሪው ተናግረዋል።
የካምፑ አስተባባሪ ብዙዎች ታምመው እንዳሉ ገልጸው በቅርብ ጊዜ ውስጥ "አምስት ሰዎች ሕይወታቸውን ማጣታቸውን" ተናግረዋል።
በአጠቃላይ ከ2014 ዓ.ም ወዲህ "330 ሰዎችን ቀብረናል" ያሉት አስተባባሪው፤ ሰዎቹ የሞቱት በረሃብ ምክንያት መሆን አለመሆኑን አላስረዱም።
በአሁኑ ወቅት በሕጻጽ ካምፕ ወደ 14 ሺህ ሰዎች እርዳታ የሚያገኙ ቢሆንም ባለፉት ወራት 300 የሚሆኑት ምንም ዓይነት እርዳታ አለማግኘታቸውን አስተባባሪው ጨምረው ተናግረዋል።
የሚሰጣቸው እህል ማሽላ መሆኑን የሚናገሩት አስተባባሪው፣ ማሽላውም የተበላሸ እንደሆነ እና ሌላ ተጨማሪ ገንቢ ምግብ አንደማያገኙ፣ ሕክምናም ሆነ ንፁህ የመጠጥ ውሃ ችግር እንዳለባቸው ገልጸዋል።
"ለስድስት ወራት እህል የማያገኝ ሰው አለ። የሚያገኘውም አንድ ወይንም ሁለት ኪሎ ነው። የሚመጣውም እህል ጥራት የሌለው ነው። አይጥም የማትበላው እህል ነው የሚደርሰን። ድረሱልን ብለን ጥሪ አድርገን የሚረዳን አላገኘንም።"
የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ግደው አዘናው ይህንን የተፈናቃዮች የረሃብ ችግር በተለያዩ የተፈናቃዮች ካምፕ እየታየ መሆኑን ይናገራሉ።
ችግሩ እንዲበረታ ያደረገው ተፈናቃዮች ለአምስት ተከታታይ ክረምት በዚህ መጠለያ ጣቢያ ውስጥ ማሳለፋቸው መሆኑን የጠቀሱት አስተዳዳሪው፣ በቂ እርዳታም እንደማያገኙ ይገልጻሉ።
ለአንድ ሰው የሚሰጠው እርዳታ በወር 15 ኪሎ ማሽላ ነው የሚሉት አቶ ግደው ይህም በቂ አንዳልሆነ እና ደኅንነቱ የተረጋገጠ ባለመሆኑ ተነሳ ችግር ማጋጠሙን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
በአሁኑ ሰዓት በመጠለያ ጣቢያው ውስጥ የሚገኙ ሰዎች ያለባቸው ችግር ከተነገረ በኋላ የተለያዩ ሰዎች ድጋፍ ለማድረግ እየተረባረቡ እንደሚገኝ የዞኑ አስተዳዳሪ ጨምረው ገልጸዋል።
በሕጻጽ የመጠለያ ጣቢያ አረጋውያን የሚበዙበት መሆኑ፣ ተፈናቃዮች ሲመጡ ዘግይተው የመጡ አረጋውያን መኖራቸው እና እነርሱ የሚያግዛቸው የሚጦራቸው ባለመኖሩ ችግሩን የበለጠ እንዲከፋ ማድረጉን አስተዳዳሪው ተናግረዋል።
ይህንን ችግር ለመፍታት እየተንቀሳቀስን ነው የሚሉት አስተዳዳሪው ሰኞ ታኅሣሥ 13/2018 ዓ.ም. ከ400 ኪሎ በላይ ዱቄት ከሽሬ አካባቢ ወደ ሕጻጽ መጠለያ ካምፕ መወሰዱን ጨምረው አስታውቀዋል።
ግለሰቦች እርዳታ ለማድረግ እየተንቀሳቀሱ መሆኑን እና የባንክ አካውንት ተከፍቶም እርዳታ ማሰባሰብ መጀመሩን አስተዳዳሪው ተናግረዋል።
የራያ ዩኒቨርስቲም የተለያዩ እርዳታዎችን በመያዝ ወደ አካባቢው እንደተጓዘ የተናገሩት አቶ ግደው፣ በሽረ አካባቢ የሚኖሩ ሰዎች እንዲሁ በማኅበራዊ ሚዲያ እርዳታ ለማሰባሰብ እየተንቀሳቀሱ መሆኑን አስተዳዳሪው ተናግረዋል።
በትግራይ ክልል በተካሄደው ደም አፋሳሽ ግጭት ከሦስት ዓመታት በፊት በፕሪቶሪያ ስምምነት ቢቆምም አሁንም በሺህዎች የሚቆጠሩ ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው መመለስ አልቻሉም።
ሕጻፍ የተፈናቃዮች ካምፕ ቀደም ሲል የኤርትራ ስደተኞች ማቆያ ስፍራ የነበረ ሲሆን፣ በትግራይ ከተካሄደው በኋላ ግን ከተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች የተፈናቀሉ ሰዎች መጠለያ ሆኗል።

23/12/2025

ሞንጆሪኖ - ስምዕዋ
“ተመዛባለይ ህዝብና - ፈለማ ውድብ ትድሓን ኢዩ ዝብል”

ድሕሪ ማይ ናብ በዓቲ!
22/12/2025

ድሕሪ ማይ ናብ በዓቲ!

ሕፃፅ---------ኣብዚ ዘበን ሰብ ብጥሜት ክሞት ካብ ምርኣይ ዘሕዝን እንታይ ክህሉ! እሞ ድማ ንስልጣኖም ክብሉ ብዝሻኾቱ መራሕቱ ዝተልዓለ ትግራዋይ ክመውት ከሎ ምርኣይ ኣመና የሕምም!! ሎ...
22/12/2025

ሕፃፅ
---------
ኣብዚ ዘበን ሰብ ብጥሜት ክሞት ካብ ምርኣይ ዘሕዝን እንታይ ክህሉ! እሞ ድማ ንስልጣኖም ክብሉ ብዝሻኾቱ መራሕቱ ዝተልዓለ ትግራዋይ ክመውት ከሎ ምርኣይ ኣመና የሕምም!! ሎሚ እውን ቅድሚ 50 ዓመት ዝነበረ ሕቶ ንመንግስቲ ኢትዮጵያ ዝሓቱ መራሕቲ ዝሓዘት ትግራይ - እሞ እቲ ቅድሚ 50 ዓመት ዝተሓተተ ሕቶ ቅርጥፍ ኣቢሎም ዝበልዑ መራሕቲ ንድሕሪት 50 ዓመት ተመሊሶም ተመሳሳሊ ሕቶ ክሓቱ ምርኣይ ክሳርኡ የሕመካ!!
ኣብ ሕፃፅ ሰብ ብደው ብጥሜት ይሃልቕ ኣሎ!!

" ከጥር 23 ጀምሮ ስስ የፕላስቲክ ከረጢቶችን (ስስ ፌስታል) መጠቀም፣ ማምረትና ወደሀገር ውስጥ ማስገባት አይቻልም ! " የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን-----------------ከጥር 23 ጀም...
22/12/2025

" ከጥር 23 ጀምሮ ስስ የፕላስቲክ ከረጢቶችን (ስስ ፌስታል) መጠቀም፣ ማምረትና ወደሀገር ውስጥ ማስገባት አይቻልም ! "
የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን
-----------------
ከጥር 23 ጀምሮ ስስ የፕላስቲክ ከረጢቶችን (ስስ ፌስታል) መጠቀም፣ ማምረትና ወደሀገር ውስጥ ማስገባት ያስቀጣል ተብሏል።የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ፤ ከጥር 23/2018 ጀምሮ ለአንድ ጊዜ አገልግሎት ብቻ የሚውሉ ስስ የፕላስቲክ ከረጢቶችን የሚጠቀሙ፣ የሚያመርቱና ወደሀገር ውስጥ የሚያስገቡ አካላትን መቅጣት ሊጀመር መሆኑን አሳውቋል።

ለአንድ ጊዜ አገልግሎት ብቻ የሚውሉ የፕላስቲክ ምርቶችን ማምረት፣ ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባትና ይዞ መገኘት የሚከለክለው አዋጅ ከሐምሌ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የጸደቀ ቢሆንም፣ ባለስልጣኑ የስድስት ወራት የሽግግር ጊዜ ሰጥቶ መቆየቱን ገልጿል።" አዋጁ እንደወጣ የወረቀትና ሌሎች አማራጭ ከረጢቶች ወደ ገበያ በመምጣታቸው የፕላስቲክ ስርጭት ቀንሶ የነበረ " ያለው ባለስልጣን መ/ቤቱ " አሁን ላይ ግን በድጋሚ በገበያው ውስጥ እየታዩ ይገኛሉ " ብሏል። በሽግግሩ ወቅት አዋጁን ሙሉ በሙሉ ለመተግበር የሚያስችሉ የዝግጅት ሥራዎች ሲከናወኑ እንደቆዩ፤ በዚህም ጉዳዩ ከሚመለከታቸው የፕላስቲክ አምራቾች፣ ተጠቃሚዎች እና አማራጭ የወረቀት ከረጢት አምራቾች ጋር ውይይት መደረጉን አመልክቷል።
የወረቀትና ሌሎች የከረጢት ዓይነቶችን ማምረት የሚፈልጉ አካላትን ወደ ገበያ ለማስገባት ማሽኖችን ከቀረጥ ነፃ እንዲያስገቡና የብድር አቅርቦት እንዲያገኙ ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በቅንጅት እየተሠራ መሆኑንም አሳውቋል። " የሽግግር ጊዜው ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም ያበቃል " ያለ ሲሆን " ከዚህ ዕለት በኋላ ሕገወጥ እንቅስቃሴ ላይ የሚገኙ አካላት ተጠያቂ ስለሚሆኑ ሁሉም አስፈላጊውን ዝግጅት ያድርግ " ሲል አሳስቧል።

#የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ነው።

የሱዳን ዋነኛ የኃይል ማሠራጫ በድሮን በመመታቱ ካርቱም እና ፖርት ሱዳንን ጨለማ ዋጣቸው----------------------------ግዙፍ የሱዳን የኤሌክትሪክ ኃይል ማሠራጫዎች ላይ በተፈጸሙ ...
18/12/2025

የሱዳን ዋነኛ የኃይል ማሠራጫ በድሮን በመመታቱ ካርቱም እና ፖርት ሱዳንን ጨለማ ዋጣቸው
----------------------------
ግዙፍ የሱዳን የኤሌክትሪክ ኃይል ማሠራጫዎች ላይ በተፈጸሙ የድሮን ጥቃቶች ምክንያት በትልልቆቹ የሱዳን ከተሞች ውስጥ መጠነ ሰፊ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት መቋረጥ መከሰቱ ተዘገበ።
የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት የተቋረጠባቸው ከፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ጋር እየተፋለመ ያለው የሱዳን ጦር ሠራዊት የሚቆጣጠራቸው ዋና ከተማዋ ካርቱም እና የጄነራል አል ቡርሐን መቀመጫ የሆነችው የወደብ ከተማ ፖርት ሱዳን ናቸው።
የዐይን እማኞች እንደተናገሩት በሱዳን ጦር ኃይል ቁጥጥር ሥር በምትገኘው በምሥራቃዊ ናይል ግዛት ውስጥ በምትገኘው አትባራ ጥቃት ከተፈጸመባቸው የኤሌክትሪክ ኃይል ማሠራጫ ማዕከላት ከፍተኛ የእሳት ነበልባል እና ጭስ አይተዋል።
ሱዳን የጦር ሠራዊቱን በሚመሩት በጄነራል አብደል ፋታህ አልቡርሐን እና በተቀናቃኛቸው ጄኔራል ሐምዳን ዳጋሎ በሚመራው ፈጥኖ ደራሽ ኃይል መካከል የተራዘመ የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ትገኛለች።
ሁለቱ ኃይሎች በሚያካሂዱት ሦስት ዓመት ሊሞላው በተቃረበው ጦርነት በመሠረተ ልማቶች ላይ ከባድ ውድመት መድረሱ እየተዘገበ ነው።
አሁን በድሮን በተፈጸመው ጥቃት በሱዳን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ውስጥ ወሳኝ ማዕከል የሆነው አል-ሙቅሪን የተባለው ማሠራጫ ማዕከል ዒላማ በመሆኑ ነው መጠነ ሰፊ የኃይል መቋረጥ በዋና ዋና ከተሞች ላይ ያጋጠመው።
አንድ የሱዳን መንግሥት ባለሥልጣን ለፈረንሳይ ዜና ወኪል ኤኤፍፒ እንደተናገሩት በኃይል ማሠራጫው ማዕከል ላይ የመጀመሪያው ጥቃት ከተፈጸመ በኋላ እሳቱን ለማጥፋት የሞከሩ ሁለት ሰዎች ሕይወታቸው ያለፈ ሲሆን፣ ሌሎች በርካታ ሰዎች ደግሞ ሁለተኛው ዙር ጥቃት በተፈጸመበት ጊዜ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
ጥቃቱ የተፈጸመበት ወሳኙ የሱዳን ኤሌክትሪክ ኃይል ማሠራጫ ማዕከል አል-ሙርቂን የሚያሠራጨውን የኤሌክትሪክ ኃይል የሚገኘው ከአገሪቱ ትልቁ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ነው።
ማዕከሉ ኤሌክትሪኩን ወደ በርካታ ቁልፍ የሱዳን አካባቢዎች የሚያሠራጭ በመሆኑ የደረሰበት የድሮን ጥቃት ያስከተለው ጉዳት ውጤቱ በብዙ ቦታዎች ላይ ኃይልን በማቋረጥ ከፍተኛ ጉዳትን ያደርሳል።
በጄነራል ዳጋሎ የሚመራው ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ በሱዳን ጦር ሠራዊት ቁጥጥር ሥር ባሉ በርካታ አካባቢዎች በሚገኙ የሰላማዊ ሰዎች መገልገያ የሆኑ መሠረታ ልማቶችን በተደጋጋሚ ዒላማ በማድረግ የድሮን ጥቃት ይፈጽማል ተብሎ ይከሰሳል።
ከዚህ ቀደም በካርቱም እና በሁለተኛዋ ከተማ ፖርት ሱዳን አውሮፕላን ማረፊያዎችን ጨምሮ በርካታ ዒላዎችን በድሮን መምታቱን መግለጹ ይታወሳል።
ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ በጦር ሠራዊቱ ተሸንፎ ከዋና ከተማዋ ካርቱም የወጣ ቢሆንም ሌሎች ወሳኝ የሱዳን ግዛቶችን ባለፉት ወራት ተቆጣጥሮ ይዞታውን እያሰፋ ነው።
በመጪው ሚያዝያ ሦስት ዓመት በሚሞላው የሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት ምክንያት በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መሞታቸው እና 12 ሚሊዮን ሱዳናውያን ለመፈናቀል መዳረጋቸው ተዘግቧል።
በተጨማሪም ጦርነቱ የእርዳታ አቅርቦትን በማደናቀፉ በተለያዩ የሱዳን ክፍሎች ውስጥ ረሃብ ሊከሰት ይችላል በማለት ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የረድኤት ድርጅቶች እያስጠነቀቁ ነው።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ASER MEDIA posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ASER MEDIA:

Share