
07/10/2025
''ኤርትራ እና ህወሓት ጦርነት ሊከፍቱብኝ ነው''
ኢትዮጵያ
-----
ህወሐመት ለ2 ቀናት የቆየ ብሔራዊ የአንድነት ኮንፈረንስ ማካሄዱ ይታወሳል። በኮንፈረንሱም የተጋረጡበትን ችግሮች ለመፍታት አቅጣጫ አስቀምጧል። ከፍተኛ የህወሓትና የጦር ጀነራሎች የተሳተፉበት ጉባኤ ለኤርትራ ህዝብ ጨምሮ ለተለያዩ አካላት ጥሪ ቀርቧል።
በወልዲያ በተፈጸመው ጥቃት ተሳትፈዋል አለች።
የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኤርትራ መንግሥትና ህወሓት “ፅምዶ” በተሰኘ አዲስ ጥምረት ኢትዮጵያን ለመውጋት እየሰሩ ነው ሲል ከሷል። በቅርቡ በሰሜን ወሎ በነበረው የመከላከያና ፋኖ ውግያ መሳተፋቸውም ገልጿል።
በቅርቡ በአማራ ክልል ወልዲያ ከተማን ለመያዝ በፋኖ ታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት ውስጥ ሁለቱ ተዋናዮች ተሳትፈዋል ያሉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዎን ጤሞቲዎስ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ለሆኑት አንቶኒዮ ጉተሬዝ መስከረም 22 ቀን 2018 በጻፉት ደብዳቤ፤ “በኤርትራ መንግሥትና በህወሓት አንጃ መካከል ያለው ቅንጅት ባለፉት ጥቂት ወራት ይበልጥ ግልጽ ሆኗል” ብለዋል።
ሚኒስትሩ በደብዳቤው ቅንጅቱ “በኢትዮጵያ ላይ ጦርነት ለመክፈት በንቃት እየተዘጋጀ ነው” ሲሉ ገልጸው፤ ሁለቱንም ተዋናዮች “የግጭቱን አድማስ ለማስፋት እንደ ፋኖ ያሉ ታጣቂ ቡድኖችን በገንዘብ በመደገፍ፣ በማሰባሰብ እና በመምራት” ከሰዋል።
ደብዳቤው በወልድያ ከተፈጸመው ጥቃት በተጨማሪ በራያና ወልቃይት ግጭቶች መከሰታቸውንም ጠቁሟል። እነዚህም ድርጊቶች፣ በፌዴራል መንግሥትና በህወሓት መካከል የተደረሰውን የፕሪቶሪያ ስምምነት መጣሳቸውን ገልጿል።
ደብዳቤው ኤርትራን “የእነዚህ አስከፊ ድርጊቶች ዋነኛ ነዳፊ” በማለት የወቀሰ ሲሆን፣ “በፋይናንስ፣ ቁሳዊና ፖለቲካዊ ድጋፍ” አማካኝነት ግጭቶችን እያካሄደች ነው ብሏል።
የኤርትራ መንግስት በበኩሉ ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ መንግሥት ጠብአጫሪ ድርጊቶችን እየፈፀመ ነው በማለት ከሶ ነበር።
የህወሓት ቡድንም እንዲሁ የኢትዮጵያ መንግስት የፕሪቶሪያ ስምምነት አልተገበረም በማለት ስሞታ አቅርቦ ነበር።