ASER MEDIA

ASER MEDIA ASER MEDIA is a news and current affairs channel. follow us on Facebook, tiktok, and YouTube.

22/08/2025

መቐለ -ሰብ ክጨውዩ ዝተትሓዙ (ቪድዮ)
------
ባጃጅ ንኣሸንዳ ተባሂሉ ኣብ ዝተኸልከላሉ፣ መዓት ኣኽበርቲ ፀጥታ ኣብ ዝተዋፈሩላ ከተማ መቐለ ሓደ ገናሒ ባጃጅ ምስ ክልተ ቀተልቲ ኮይኖም ካብ ኣርባምንጭ ባናና ብምምፃእ ዝፍለጥ ነጋዳይ ዓፊኖም ንምውሳድ ፈቲኖም፡፡ ዋላ ሓደ ኣክባሪ ፀጥታ ኣይተረኸበን፡፡ እቲ ዝተጨወየ ሰብ ነቶም ጨወይቲ ተቓሊሱ እታ ባጃጅ ክትግልበጥ ብምግባሩ እቲ ሕብረተሰብ ብፍላይ ድማ መናእሰይ ድማ ሓጊዞምዎን ነቶም ጨወይቲ ተኸታቲሎም ብምሓዝን ናይ ፖሊስ ሥራሕ ሰሪሖም፡፡ እቶም ኣብቲ ፎቶ ዝረኣዩ ዘለው ለያቡ ገበነኛታት ቅድም ኢሎም ዝፈተፀሙ ገበናት ዝፈጸሙ ክኾኑ ስለዝኽሉ ኣዚዩ መምሃሪ ቅፅዓት ኢዩ ዘድልዮም፡፡
ኣብ ትግራይ ዘሎ መሓውር ፀጥታ ግን ብካእ ኣካል ክምርመር ኢዩ ዘለዎ፡፡

ግብፅ በናይል ተፋሰስ ላይ "ዓለም አቀፍ ሕግን የጣሰ የተናጠል እርምጃን" እንደማትቀበል ለበርካታ የአፍሪካ አገራት አስታወቀች----የሕዳሴ ግድብ በመጪው መስከረም ይመረቃል መባሉን ተከትሎ ግ...
22/08/2025

ግብፅ በናይል ተፋሰስ ላይ "ዓለም አቀፍ ሕግን የጣሰ የተናጠል እርምጃን" እንደማትቀበል ለበርካታ የአፍሪካ አገራት አስታወቀች
----
የሕዳሴ ግድብ በመጪው መስከረም ይመረቃል መባሉን ተከትሎ ግብፅ "የዓለም አቀፍ ሕግን በጣሰ መልኩ በምሥራቃዊ ናይል ተፋሰስ የሚደረግ የተናጠል እርምጃን" እንደማትቀበል ለበርካታ አፍሪካ አገራት አሳወቀች።
የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደላቲ የናይል ተፋሰስ አገራት ከሆኑት ከሱዳን፣ ከደቡብ ሱዳን፣ ከኡጋንዳ፣ ከኬንያ እንዲሁም ከተፋሰሱ ውጭ ካሉት ከጂቡቲ እና ከሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር በተናጠል ባደረጉት የስልክ ውይይት ነው ይህንን ያስታወቁት።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት 14 ዓመታትን የፈጀው እንዲሁም አምስት ቢሊዮን ዶላር ገደማ ወጪን የጠየቀው ታላቁ የሕዳሴ ግድብ አምስተኛ ዙር ሙሌት ተጠናቆ ምረቃው በመጪው መስከረም እንደሚካሄድ ኢትዮጵያ በቅርቡ ማሳወቋን ተከትሎ ነው።
በግድቡ የውሃ ሙሌት እና ከግድቡ በሚለቀቀው የውሃ መጠን ላይ ከታችኛው ተፋሰስ አገራት ጋር ሕጋዊ እና አስገዳጅ ሦስትዮሽ ስምምነት ካልተፈረመ ኢትዮጵያ የውሃ ሙሌቱን ማከናወን እንደሌለባትም ስትወተውት የቆየችው ግብፅ ይህንኑ በመድገም ስታስጠነቅቅ ቆይታለች።
ይህንን አቋሟን በተለይም ኢትዮጵያ የሕዳሴን ግድብ አስመርቃለሁ ባለች ማግስት ያጠናከረች ሲሆን፤ ሚኒስትሩ "በናይል ወንዝ ላይ ዓለም አቀፍ ሕግን የሚቃረኑ የተናጠል እርምጃን ውድቅ ማድረጋቸውን" የግብፅ ሚዲያዎች አጽንኦት ሰጥተውታል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በተደጋጋሚ የግብፅ ባለሥልጣናት የሚያንጸባርቁትን በመድገም የውሃ ደኅንነት ለግብፃውያን የህልውና ጥያቄ እንደሆነ ገልጸው፤ የጋራ የውሃ ሃብቶችን በተመለከተ የዓለም አቀፍ ሕጎችን ማክበር አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
ከሰሞኑ የግብፁ አብደል ፋታህ አል ሲሲ አገራቸው በናይል (አባይ) ያላትን የውሃ ድርሻ እንዲነካ እንደማትፈቅድ ማስጠንቀቃቸው ይታወሳል።
ፕሬዝዳንት አል ሲሲ ከላይኛው የናይል ተፋሰስ አገራት አንዷ ከሆነችው የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ ጋር ከሰሞኑ በጣምራ በሰጡት መግለጫ "በድጋሚ ለግብፃውያን ማረጋገጥ የምፈልገው 105 ሚሊዮን ዜጎቻችን እና 10 ሚሊዮን የሚሆኑ በአገራችን ያሉ እንግዶቻችን በሕይወት የሚያቆየው ውሃ እንዲነካ ፈጽሞ እንደማንፈቅድ ነው" ሲሉ ፕሬዚዳንት አልሲሲ አጽንኦት ሰጥተዋል።
የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታን ከጅምሩ እንዲሁም የተካሄዱ አምስት ውሃ ሙሌቶችን በጽኑ ያወገዙት አልሲሲ፤ ከሰሞኑም በነበረው የጋራ መግለጫም በናይል ላይ የሚደረግ የተናጠል እርምጃን አገራቸው ውድቅ እንደምታደርግ አቋማቸውን አስታውቀዋል።
"ግብፅ በውሃ ደኅንነቷ ላይ የተደቀነን የኅልውና ስጋት ችላ ትለዋለች ብሎ የሚያስብ ማንኛውም አካል ተሳስቷል። ሁኔታውን መከታተላችንን እንቀጥላለን፤ ዓለም አቀፍ ሕጎችን መሠረት በማድረግ የሕዝቦቻችንን የኅልውና ሃብቶች ለማስጠበቅ ማንኛውንም እርምጃ እንወስዳለን" ሲሉ አልሲሲ አስጠንቅቀዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከተለያዩ የአፍሪካ ሚኒስትሮች ጋር ያደረጉት ውይይትም ይህንን የፕሬዚዳንቱን አቋም ያንጸባረቀ ሲሆን፤ ድንበር ተሻጋሪ በሆኑ ውሃዎች እና ተፋሰስ አገራት የሚተዳደሩበት መርህ የጋራ መግባባት ላይ የተመሰረተ ሊሆን ይገባል ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከአገራቱ ጋር ባደረጉት ውይይት የአለም አቀፍ መርሆች ላይ የተመሰረተ የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የትብብር አስፈላጊነትን አጽንኦት መስጠታቸው ተገልጿል።
እንዲሁም በደቡባዊ የናይል ተፋሰስ አገራት ለሚከናወኑ የልማት ፕሮጀክቶች በግብጽ የልማት አጋርነት ኤጀንሲ (ኢኤፒዲ) የሚደረገው መርሃ ግብር እና እገዛ ላይ ላይ ውይይት መደረጉን የግብፅ ሚዲያዎቸ ዘግበዋል።
ግብፅ በአውሮፓውያኑ 1959 የተፈረመውና የአብዛኛውን የውሃውን ድርሻ የሚሰጣትን የቅኝ ግዛት ስምምነት ሙጥኝ ብላ ታሪካዊ ተጠቃሚነት በሚል መርኅ የወንዙን ውሃ ሙሉ በሙሉ በበላይነት ለብቻዋ የመጠቀም ፍላጎት እንዳላት በመጥቀስ ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ ትቃወማለች።
ስምምነቱ ኢትዮጵያን ያላካተተ ከመሆኑ በተጨማሪ ግብፅ 55.5 ቢሊዮን ኪዩቢክ ውሃን እንዲሁም ሱዳን 18.5 ቢሊዮን ኪዩቢክ ውሃ እንድታገኝ እና 86 በመቶ የናይልን ውሃ የምትገብረውን ኢትዮጵያ ያለ ውሃ የሚያስቀር አግላይ እና ኢፍትሃዊ እንደሆነም ይጠቀሳል።
በየዓመቱ ከሚፈሰው 84 ቢሊዮን ኩየቢክ ውሃ 12 በመቶው በትነት የሚያልቅ ሲሆን፣ ይህ ስምምነት በዋነኝነት ግብፅን ትገዛ የነበረችውን ብሪታንያን ለጥጥ ምርቷ በዋነኝነት ተጠቃሚ አድርጓታል።
የነጭ ናይል መነሻ እና 15 በመቶ የሚሆነውን ውሃ ድርሻ የምታበረክተው የኡጋንዳ ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ ከአልሲሲ ጋር ከነበራቸው ቆይታ በኋላ ይህንን የግብፅን ታሪካዊ ተጠቃሚነት በጠቀሰ መልኩ አስተያየታቸውን በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ አስፍረዋል።
"የናይል ሁኔታ ሰፋ ባለ መልኩ ልናየው ይገባል። አንዳንዴ ችግሮች የሚመነጩት ከአቀራረባችን ነው። በታሪካዊ መብቶች ላይ ከማተኮር ይልቅ፤ የናይል ተፋሰስ አገራት ዓለም አቀፍ ፍላጎትን ልናጤን ይገባል" ሲሉ በኤክስ ገጻቸው ጽፈዋል።
ሙሴቪኒ አክለውም "ዓላማችን ለሁሉም ብልጽግና፣ የመብራት አገልግሎተ ተደራሸነት፣ መስኖ እንዲሁም የመጠጥ ውሃ ለሁሉም በሚደርስበት መሆን አለበት" ሲሉ አጽንኦት ሰጥተው "እነዚህን ዓላማዎች በሙሉ በማዕቀፋችን በማካተት ሳይንሳዊ እና ፍትሃዊ መንገዶችን በመጠቀም ማሳካት ይቻላል" ብለዋል።
ግድቡን በሚመለከት በተከታታይ ሲካሄዱ የነበሩ የግብፅ፣ የሱዳን እና የኢትዮጵያ ሦስትዮሽ ድርድሮች አንዱ ወገን ሌላኛውን ለድርድሩ አለመሳካት ተጠያቂ በማድረግ ያለውጤት መበተናቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የናይል ወንዝ ላይ ያላት ድርሻዋን ባረጋገጠ መልኩ ፍትሃዊ እና ምክንያታዊ አጠቃቀም ላይ ስምምነት እንዲደረስ እና ግንባታው የግብፅ የውሃ ደኅንነት ላይ አደጋ እንደማይጋርጥ ስታስታውቅ ቆይታለች።
---
ዘገባው የቢቢሲ አማርኛ ነው

ብቐትሩ ኣብ ከተማ መቐለ ክጨውዩ ዝፈተኑ ተታሒዞም---ካብ ኣርባምንጭ ዝኸደ ጋሻ ብሓይሊ ናብ ባጃጅ ኣእትዮም ክጨውዩ ዝፈተኑ ጨወይቲ እቲ ወዲ ብዘስመዖ ኣውያት ሰብ በፂሑ ኣድሒኑዎ ኣሎ፡፡ እ...
22/08/2025

ብቐትሩ ኣብ ከተማ መቐለ ክጨውዩ ዝፈተኑ ተታሒዞም
---
ካብ ኣርባምንጭ ዝኸደ ጋሻ ብሓይሊ ናብ ባጃጅ ኣእትዮም ክጨውዩ ዝፈተኑ ጨወይቲ እቲ ወዲ ብዘስመዖ ኣውያት ሰብ በፂሑ ኣድሒኑዎ ኣሎ፡፡ እቶም ጨወይቲ እውን ምስ ባጃጆም ተታሒዞም ኣለው፡፡ ኣብ ከተማ መቐለ ኣሸንዳ ክሳብ ዝውዳእ ኣገልገሎት ባጃጅ ደው ክብል እኳ እንተተኣወጀ እቶም ለያቡ ግን ነዚ ንጎኒ ብምሕዳግ ኣሸንዳ ከኽብር ዝመፀ ጋሻ ክጨውዩ ፈቲኖም ኢዮም፡፡

በዓል ማርያ ኣብ ዓዲግራት - ተመዛበልቲ  ምዕራብ ትግራይ!ይኣክል ሓምሻይ ዓመት ኣብ ቴንዳ!!
22/08/2025

በዓል ማርያ ኣብ ዓዲግራት - ተመዛበልቲ ምዕራብ ትግራይ!
ይኣክል ሓምሻይ ዓመት ኣብ ቴንዳ!!

ሞት ዝቐፀለላ ትግራይ----ናብ ሎሚ ዘውግሕ ኣብ ከተማ ዓድዋ ሓደ ሰብ ሞይቱ ተረኺቡ ኣሎ፡፡ ኣብ ከተማ ዓድዋ ከባቢ ሃንጋሪ ዝበሃል ቦታ ናብ ሎሚ ለይቲ ዕለት 16/12/2017 ዓ.ም ዘውግሕ...
22/08/2025

ሞት ዝቐፀለላ ትግራይ
----

ናብ ሎሚ ዘውግሕ ኣብ ከተማ ዓድዋ ሓደ ሰብ ሞይቱ ተረኺቡ ኣሎ፡፡ ኣብ ከተማ ዓድዋ ከባቢ ሃንጋሪ ዝበሃል ቦታ ናብ ሎሚ ለይቲ ዕለት 16/12/2017 ዓ.ም ዘውግሕ መንነቱ ዘይተፈለጠ ሰብ ሞይቱ ተረኺቡ መንነቱን ኣማውታኡን እናተጻረየ ይርከብ።

ትግራይ ሰብ ብዝወፀሉ ዘይምለሳ ዓዲ ትኸውን ኣላ፡፡

የአንድ ሰው ህይወት ቀጥፎ፤ አንዱን ለከፍተኛ ጉዳት የዳረገው የሆቴል ውስጥ ፀብ-------ቪ አይ ፒ ላውንጅ እና ሬስቶራንት በሚባል ሆቴል በሁለት ግለሰቦች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት የሰ...
22/08/2025

የአንድ ሰው ህይወት ቀጥፎ፤ አንዱን ለከፍተኛ ጉዳት የዳረገው የሆቴል ውስጥ ፀብ
-------
ቪ አይ ፒ ላውንጅ እና ሬስቶራንት በሚባል ሆቴል በሁለት ግለሰቦች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት የሰው ህይወት ማለፉን ተከትሎ ምርመራ እያጣራ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡
ድርጊቱ የተከሰተው ነሀሴ 07 ቀን 2017 ዓ/ም በግምት ከቀኑ 7 ሰዓት ከሩብ ገደማ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ሃያ ሁለት አካባቢ በሚገኘው" ቪ አይ ፒ ላውንጅ" በተባለ ሆቴል ውስጥ ነው።
በዕለቱ በድርጅቱ በጋርድነትና በዲጄ ሰራተኝነት ተቀጥረው በሚሰሩ ልደቱ አያኖ እና ናትናኤል ልዑል በተባሉ ግለሰቦች መካከል ምክንያቱ ባልታወቀ አለመግባባት በተፈጠረ ጸብ ምክንያት ናትናኤል ልዑል የተባለው ግለሰብ ጭንቅላቱ ላይ ከፍተኛ ጉዳት የደረስበት መሆኑን ፖሊስ በስፍራው ደርሶ ካሰባሰበው መረጃ ማረጋገጥ ተችሏል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በቅርብ ርቀት የነበሩ ሰዎች ተጎጂውን ወደ ህክምና በመወሰድ ልደቱ አያኖ የተባለው ግለስብ ከአካባቢው እንዳይሸሽ እየጠበቁት በነበረበት አጋጣሚ ድብደባው በተፈፀመበት አልጋ ክፍል ቁጥሩ 505 አምስተኛ ፎቅ ላይ ባለ ክፍል ውስጥ ገብቶ በሩን ከውስጥ በመዝጋት ከክፍሉ ባለ መስኮት ወደ መሬት ወድቆ ጉዳት ደርሶበት ወደ ሆስፒታል ተወስዶ እርዳታ እየተደረገለት ህይወቱ ያለፈ ሲሆን ትክክለኛ የአሟሟቱን ሁኔታ ለማወቅ ምርመራው ቀጥሏል ።
ከባድ ጉዳት የደረሰበት ናትናኤል ልዑል የተባለው ግለሰብ አሁንም በህክምና ተቋም ውስጥ ተኝቶ ክትትል እየተደረገለት ይገኛል።
በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ ማስረጃ የማሰባሰብ ስራዎችን በመስራት እና የአስክሬን ምርመራ ውጤት በመጠባበቅ ላይ እንደሚገኝ የገለፀው የአዲስ አበባ ፖሊስ፤ የምርመራ ስራው እንደተጠናቀቀ ሙሉ መረጃውን ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል።
ከዚህ የወንጀል ሁኔታ ጋር በተያያዘ አንዳንድ ግለሰቦች በማህበራዊ ሚዲያ የሚያስራጩት መረጃ ተገቢነት የሌለው መሆኑን ያስታወቀው ፓሊስ ሀሰተኛ መረጃ የህግ ተጠያቂነትን የሚያስከትል መሆኑን ጨምሮ አስታውቋል ። ከትክክለኛው የመረጃ ምንጭ ውጭ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች የሚለቀቁ መረጃዎች እውነተኛነታቸዉን የሳቱ መሆኑን ህብረተሰቡ ተገንዝቦ ለችግሩ የመፍትሄ አካል እንዲሆን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ጥሪውን አቅርቧል። ( )
የሟች አስከሬን ወደ ትውልድ ሃገሩ (ቁጫ) ተወስዶ መቀበሩ ይታወሳል፡፡

መልእኽቲ ሠናይ ትምኒት አሸንዳ ካብ ጃዋር መሐመድጃዋር መሐመድ ብትግርኛ ዘሕለፎ ሠናይ ትምኒት አሸንዳ
22/08/2025

መልእኽቲ ሠናይ ትምኒት አሸንዳ
ካብ ጃዋር መሐመድ
ጃዋር መሐመድ ብትግርኛ ዘሕለፎ ሠናይ ትምኒት አሸንዳ

 #አሸንዳአሸንዳ ኣብ ተምቤን ዓብዪ ዓዲ ፕረዚደንት ክልል ትግራይ ታደሠ ወረደ ኣብ ዝተረኸበሉ ይኽበር ኣሎ
22/08/2025

#አሸንዳ
አሸንዳ ኣብ ተምቤን ዓብዪ ዓዲ ፕረዚደንት ክልል ትግራይ ታደሠ ወረደ ኣብ ዝተረኸበሉ ይኽበር ኣሎ

የባንክ ሠራተኞች በተለይ አዳዲስ...በየመንግሥት መስርያቤት አየዞሩ ሠራተኛው ከ20 እስከ 100 ብር ... ከዛም በላይ አካውንት ያስከፍቱታል። ከዛ በኋላ ተጨማሪ ገንዘብ ስለማያስገቡ ወይም ...
21/08/2025

የባንክ ሠራተኞች በተለይ አዳዲስ...
በየመንግሥት መስርያቤት አየዞሩ ሠራተኛው ከ20 እስከ 100 ብር ... ከዛም በላይ አካውንት ያስከፍቱታል። ከዛ በኋላ ተጨማሪ ገንዘብ ስለማያስገቡ ወይም ሰለማያንቀሳቅሱት አካውንቱ ይዘጋል::
በዚህ ጉዳይ መሠረት ሚድያ የሠራው ፎቶ ላይ አለ።

21/08/2025

ኣሸንዳ - ናይቀደም ደርፊ (ምስ ናይ ሎሚዘበን)

የኢቢሲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከኃለፊነታቸው ተነስተው  ሌላ መስርያቤት እንዲመሩ ተሸሙ-----አቶ ጌትነት ታደሠ የኢቢሲ (የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን) ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆነው ለሁለት ኣመታት ገደማ ያ...
21/08/2025

የኢቢሲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከኃለፊነታቸው ተነስተው ሌላ መስርያቤት እንዲመሩ ተሸሙ
-----
አቶ ጌትነት ታደሠ የኢቢሲ (የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን) ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆነው ለሁለት ኣመታት ገደማ ያገለገሉ ሲሆን አምባሳደር ሽፈራው ሽጉጤ (ዶ/ር) ይመራ ወደ ነበረው የኢትዮጵያ ህብረት ስራ ኮሚሸን ኮሚሽነር ሆነው ተሸመዋል፡፡
በተለያዩ የመገናኛ ዜዴዎች ስማቸው ሲነሳ የነበረው አቶ ጌትነት በቅርቡ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን የተቀበሉት አምባሳደር ሽፈራው ሽጉጤ ሲመሩት የነበረውን መስርያ ቤት እንዲመሩ ተመድቧል፡፡

''የመደመር መንግስት መጽሐፍ ከውጤትና ከተጨባጭ ልምድ የተቀዳ ነው'' ----- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ   የመደመር መንግስት መጽሐፍን ይበልጥ አስፈላጊና ጠቃሚ የሚያደርገው ከውጤትና...
20/08/2025

''የመደመር መንግስት መጽሐፍ ከውጤትና ከተጨባጭ ልምድ የተቀዳ ነው''
-----
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

የመደመር መንግስት መጽሐፍን ይበልጥ አስፈላጊና ጠቃሚ የሚያደርገው ከውጤትና ከተጨበጭ ልምድና ተሞክሮ የተቀዳ መሆኑ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተናገሩ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመደመር መንግሥት በተሰኘው አዲሱ መጽሐፋቸው ዙሪያ ከፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ባደረጉት ቆይታ ÷ የመደመር ጽንሰ ሃሳብ በግል ሕይወታቸው ለረጅም ጊዜ የተለማመዱበትና በሰሩባቸው ተቋማት ተጠቅመውበት ውጤት ያስመዘገቡ መሆኑን አስረድተዋል፡

የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ሃሳብ በተለያየ ደረጃ ማለትም በግለሰብም ሆነ በቡድን አሊያም በተቋም ደረጃ ሊተገበር እንደሚችል ተናግረዋል፡፡

የመደመር ጽንሰ ሃሳብ ከውስን ሥፍራዎች አልፎ ወደ መንግስት ሃሳብና አቋም ያደገው በሒደት እንደሆነም አብራርተዋል፡፡

ሃሳቡን የወል በማድረግ በብዙዎች ዘንድ ቅቡል እንዲሆን ከስልጠና ባለፈ በውይይቶች፣ በትችቶችና በመረጃዎች እንዲዳብር ተደርጓል ነው ያሉት፡፡

መጽሐፉ ታሪክን የሚዳስስ፣ ወደ ፊት በመራመድ የዓለምን የነገ ሁኔታና የእኛን በነገ ውስጥ ያለን ጉዞ እንደሚተነትንም ጠቅሰዋል፡፡

መጽሐፉን ይበልጥ ጠቃሚና አስፈላጊ እንዲሆን ያደረገው ደግሞ ከውጤት፣ ከተጨበጭ ልምድና ተሞክሮ የተቀዳ መሆኑ ነው ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

መጽሐፉ በሒደት ከተገኙ ልምዶች እየዳበረ፣ ሃሳብ እያጎለበተ፣ አንዳንዱም እየታረቀና እየታረመ ፍሬያማ ጽንሰ ሃሳብ እንዲሆን ዳብሮ መውጣቱን ጠቁመዋል፡፡

የመደመር መንግስት መጽሐፍ ማንኛውም ፍሬ ያለድካም እንደማይገኝ ሁሉ በብዙ ድካም መዘጋጀቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) አስገንዝበዋል፡፡

በኢትጵያና በአፍሪካ ታሪክ መንግስታት የሚመሩበትን ንድፍ ሃሳብ በግልጽ በዚህ መልኩ የሰነዱት ሰነድ እንዳላገኙ ጠቅሰው ÷ ስለሆነም መጽሐፉ ለብዙዎች ፈር ቀዳጅ እንደሚሆን፣ መንግስታት ምን አስበው እንዴት እንደሚሰሩ ለህዝባቸውና ለታሪክ የሚተውት ሰነድ እንደሚሆን እተማመናለሁ ብለዋል፡፡

የመደመር መጽሐፍ የመጀመሪያው ቅጽ ለአጠቃላይ እሳቤው መሰረት የሚጥል መሆኑን ጠቁመው ÷ በዚህም የመደመር ብያኔና የሰው ልጅ ፍላጎት እንዲሁም የመደመር የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና ሌሎች ገጾች መዳሰሳቸውን አውስተዋል፡፡

በሁለተኛው የመደመር መጽሐፍ ቅጽም ጽንሰ ሃሳቡ የወል እንዲሆን ሃሳቡን በቀላሉ በምሳሌና በነባራዊ ሁኔታዎች ለማስረዳት መሞከሩን ነው የተናገሩት፡፡

ሀገራዊ ለውጡን ለመድፈቅ የተደረጉ ሙከራዎችን ለማክሸፍ እና ዋጋ የተከፈለበት ለውጥ ሀቀኛ ለውጥ ሆኖ የሚጠበቅበትን ውጤት እንዲያመጣ አቅጣጫ የተቀመጠው በዚሁ ጽንሰ ሃሳብ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡

በለውጡ መንገድ ለውጡን ሊቀለብሱ፣ ሊጠልፉና ተሃድሷዊ በሆነ መንገድ ሊያስኬዱ የሚፈልጉ ሃይሎች እንዳሉ ተረድተን ሊደርሱብን በማይችሉት ፍጥነት ብንጓዝ አቅም እያነሳቸው እየተንጠባጠቡ ይቀራሉ በሚል በጋራ የተወሰነበት እንደሆነም ተናግረዋል፡፡

በአጠቃላይ ሁለተኛው የመደመር መጽሐፍ ቅጽ ለውጡ አሸንፎ እንዲወጣ ሃሳቦች የተቀመሩበት መሆኑን ነው ያስገነዘቡት፡፡

ሶስተኛው የመደመር መጽሐፍ ደግሞ የመደመር ጽንሰ ሃሳብ የትውልድ ሃሳብ እንዲሆንና ትውልድን በመደመር ሃሳብ እንዴት መገንባት እንደሚቻል የተመላከተበት ነው ብለዋል፡፡


#ትግራይ

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ASER MEDIA posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ASER MEDIA:

Share