Amhara

Amhara חדשות יומיים של אמהרה
💚💛❤️አማራ💚💛❤️
የሀሳብ ከፍታ-ተራራ፣
እየገደሉት-የሚራራ፣
እያጠፉት-የሚበራ፣
የድል አጥቢያ-የድል ጮራ፣
አይ አማራ።

23/02/2026

እየጠራ መጣ....
ጎበዝ ብሩክ አበጋዝ እና ሃይለ እየሱስ አዳሙን ይቅርታ ብላችሁ ተወዳጇቸው።

"ስለታሰሩ ሰዎች ከእስራታቸው ታስፈታልን ዘንድ እንማልዳለን..."ጋዜጠኛ አባይ ወልዱ በአማራነትህ ብቻ ለደረሰብህ ሁሉ እሱ ይሁንህ!!!
06/01/2026

"ስለታሰሩ ሰዎች ከእስራታቸው ታስፈታልን ዘንድ እንማልዳለን..."

ጋዜጠኛ አባይ ወልዱ በአማራነትህ ብቻ ለደረሰብህ ሁሉ እሱ ይሁንህ!!!

"…ሰጥናኤል ሥላሴን በካደ ጊዜ፣ መላእክት በታወኩ፣ በተረበሹ ጊዜ፣ የፈጠረንን አምላካችንን እስክናገኝ ድረስ በያለንበት ጸንተን እንቁም ብሎ ቅዱሳን፣  መላእክትን በቃሉ ያጽናናቸውያረጋጋቸው፣...
28/12/2025

"…ሰጥናኤል ሥላሴን በካደ ጊዜ፣ መላእክት በታወኩ፣ በተረበሹ ጊዜ፣ የፈጠረንን አምላካችንን እስክናገኝ ድረስ በያለንበት ጸንተን እንቁም ብሎ ቅዱሳን፣ መላእክትን በቃሉ ያጽናናቸውያረጋጋቸው፣ በጨለማና በሞት ውስጥ ለሚኖሩ ብርሃንን የገለፀና የሰበከ፣ ነቢዩ ዳንኤልን ከአናብስት አፋ ያዳነው፣ ራእዩን ያብራራለት፣ ከእግዚአብሔር ዘንድ መልስን ይዞ የመጣለት፣ ሠለስቱ ደቂቅን ከእቶን እሳት ያዳነቸው፣ ወደ ካህኑ ዘካርያስ ቤት ተልኮ የቅዱስ ዮሐንስን ልደት ያበሰረ፣ የዘካርያስን አንደበት በሥልጣኑ የዘጋ፣ የለጎመ፣ ሕፃኑ ቅዱስ ዮሐንስ ሲወለድ አንደበቱን የከፈተ…

…ሱባኤ የተቆጠረለት ትንቢት የተነገረለት መሲሁ፣ አዳኙ ክርስቶስ ከድንግል ማርያም እንደሚወለድ ለራሷ ለድንግሊቱ በመናገር የክርስቶስን ልደት ያበሠረ፣ ሰብአ ሰገልን በኮከብ ምልክት መርቶ ያመጣቸው፣ ድንግል ማርያምና ሕፃኑን ክርስቶስን በምድረ በዳ በስደታቸው የመራ፣ ሄሮድስን የቀሰፈው፣ ወደ ዮሴፍና ወደ ኒቆዲሞስ የተላከ፣ ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣን ከእቶን እሳት ያዳናቸው፣ የብርሃን ራስ ወርቅ የተቀዳጀ፣ የአሸናፊና የኃይል መልአክ፣ ነበልባላዊ ዖፈ ሰማይ፣ በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩት ብርሃንን የገለፀና የሰበከ እሱ "…በእግዚአብሔር ፊት የሚቆመው ገብርኤል ነው።"
ሉቃስ 1:19

• እንኳን ለዓመታዊው ለቅዱስ ገብርኤል በዓል አደረሳችሁ።

04/09/2025

አሞኛል ፤ ከትላንቱ ዛሬ ብሶብኛል ፤ ከነገው ግን ዛሬ ይሻለኛል።

Coffee farm Gojam, Amhara, Ethiopia
27/08/2025

Coffee farm Gojam, Amhara, Ethiopia

‎በ2018 ዓ/ም በሁሉም የአማራ ግዛት ትምህርት ቤቶች፣ መምህራንና የትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ ከፓለቲካ ነፃ ሆነው ምዝገባ መጀመር ዲያስፖራውና ባለሃብቱ ደግሞ የትምህርት ቁሳቁስ ማሟላት ይገ...
23/08/2025

‎በ2018 ዓ/ም በሁሉም የአማራ ግዛት ትምህርት ቤቶች፣ መምህራንና የትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ ከፓለቲካ ነፃ ሆነው ምዝገባ መጀመር ዲያስፖራውና ባለሃብቱ ደግሞ የትምህርት ቁሳቁስ ማሟላት ይገባል።
‎ዛሬን መሰራት ለነገ አሻራ ማስቀመጥ ነውና፤በተማሪዎች ምዝገባና የትምህርት ማስጀመር ፋኖም ይሁን ገዢው መንግስት መስማማትና የጋራ አቋም ሊይዙ ይገባል።
‎"ምክንያታዊ ትውልድ መገንባት የሚቻለው በትምህርትና በተማሩ ሰዎች ነው"

23/08/2025

ጉቦ ካልከፈላችሁ አገልግሎት ያማታገኙበት መስሪያ ቤት ወይም ተቋም የትኛው ነው?
ኮሜንት ላይ ፃፉ‼️

በአዲሱ ዓመት መስከረም 1/2018 ዓ/ም የሚጀመረው የአዲስአበባ - ደብረማርቆስ የፈጣን መንገድ እና የአባይ ድልድይ ዲዛይን
15/08/2025

በአዲሱ ዓመት መስከረም 1/2018 ዓ/ም የሚጀመረው የአዲስአበባ - ደብረማርቆስ የፈጣን መንገድ እና የአባይ ድልድይ ዲዛይን

15/08/2025

ጎጃም ማለት ግን ምን ማለት ነው🤔

‎ነሃሴ 1/2008 ዓ/ም ሲታወስ‎‎ነሐሴ 1 ሌቱ ለንጋቱ ቦታውን አስረክቦ ዘወር አለ ንጋቱም ወገግ ማለት ሲጀምር የባህር ዳር ከተማ ህዝብም ከወንድ እስከ ሴት ከህፃን እስከ አዛውንት በየ ቀ...
07/08/2025

‎ነሃሴ 1/2008 ዓ/ም ሲታወስ

‎ነሐሴ 1 ሌቱ ለንጋቱ ቦታውን አስረክቦ ዘወር አለ ንጋቱም ወገግ ማለት ሲጀምር የባህር ዳር ከተማ ህዝብም ከወንድ እስከ ሴት ከህፃን እስከ አዛውንት በየ ቀበሌው ተደራጅቶ እና ተቀናጅቶ ድምፁን ለማሰማት መፈክሩን ይዞ ባንዴራውን ለብሶ ከተለያየ አቅጣጫ እየተንቀሳቀሰ ሊገናኝ ቀጠሮ ወደያዘበት አዝዋ ሆቴል ፊትለፊት ሚሊኒየም አደባባይ አካባቢ ይተም ጀመር።

‎መንገዶች በህዝብ ማዕበል ተሞሉ መበደል መገደል ያንገሸገሻቸው ስርአቱ በአማራ ህዝብ ላይ ያደረሰው ግፍ እና በደል ልባቸውን የነካቸው ድምፃቸውን ከፍ አድርገው እያሰሙ ፍትህ ለተገፋው አማራ በሚሉ መፈክሮች ታጅበው የከተማዋን ጎዳናወች አጥለቀለቁ።

‎ወልቃይት ብረሳሽ ቀኘ ትርሳኝ ፣ አማራነት ወንጀል አይደለም ፣ አማራነት ይከበር፣ሞት ቢደገስልን እንኳን አንፈራም ፣ እምቢ እንደ በላይ እና ሌሎች መፍክሮችን በማንገብ ስርአት ባለው መልኩ ድፁን ማሰማት ቀጠለ።

‎ይህ ሰላማዊ ድምፅን የማሰማት ሂደት ምቾት ያልሰጣቸው #የብአዴን _ህውሃት_ኢህአዴግ_አመራሮች ስርጎ ገቦችን ሰልፉ ውስጥ አስገብተው "ከጎንደር ለሰልፉ የመጡ ወገኖቻችን አባይ ማዶ ላይ አታልፉም ተብለው ታግተዋል" የሚል የውሸት ወሬ ሰልፉ ላይ ነዙ፤ የባህር ዳር ህዝብም ማነው ወንድሜን ያቆመው፣ ማነው ደጀ ላይ ደሜን እንዳይገባ የሚከለክለው ብሎ ወደ አባይ ማዶ ተመመ።

‎ህዝቡ አባይ ማዶ ሲደርስ የጠበቀው መንገድ ተዘጋበት የተባለ ወገኑ ሳይሆን እርሱን ለመግደል እጃቸውን ቃታ ላይ ያደረጉ ምቹ ቦታ ይዘው የመሸጉ የብአዴን ህውሃት ኢህአደግ ነፍሰ ገዳይ ወታደሮች ነበሩ።

‎አባይ ማዶ ላይ ወንድምህ እንዳያልፍ ዘጉበት ብለው በውሸት ፕሮፖጋንዳ ነዝተው ወደ ማረጃው ቄራ ነድተው ያመጡት የብአዴን ሰርጎ ገብ ካድሬወች ህዝባችን ወደ ማረጃው ቀለበት ሲገባ ግማሹን እንዳያልፍ ድልድዩ ላይ ዘግተው ያለፈውን በጥይት አረር ያለ እርህራሄ ቆልተው ህፃን አዋቂ ሴት ወንድ ሳይሉ ገደሉ አቆሰሉ።

‎ህዝቡ ጥይት ካነገተው ቃታ ከሳበው ጋር አንገት ለአንገት ተናንቆ ለማንነቱ ለነፃነቱ በጀግንነት ተዋድቋ፤ እየተኮሱበት ሳይሸሽ ከጎኑ ያለው እየወደቀ ሳይሸበር አምባገነኖችን እስከ መጨረሻው ታግሏል።

‎ነሃሴ 1/ 2008 ባህር ዳር ለማንነት ለነፃነት ለእኩልነት ብዙ ሩጠው ያልጠገቡ መፈክር ብቻ ያነገቡ ሰላማዊ ጥያቄን በሰላማዊ መንገድ ይዘው የተነሱ ልጆቿን በግፍ ያጣችበት ቀን ነው ፤ነሃሴ 1 የከተማዋ መንገዶች በደም ጎርፍ ታጥበዋል በወጣቶች አስከሬን ተሞልተዋል፤ ድምፅን በሰላማዊ መንገድ ያሰሙ ያለእርህርልሄ በግፍ ተጨፍጭፈዋል።

‎ይህ ቀን መቸም የማንረሳው ሁሌም የምናወሳው ለትግሉ ዋጋ የከፈሉትን አንስተን አስታውሰን ሰማእትነታቸውን የምንዘክርበት ለከፈሉት ዋጋ ክብር የምንሰጥበት ቀን ነው።

‎ክብር ለነፃነት ለማንነት ለእኩልነት ለታገሉ ዋጋ ለከፈሉ እየከፈሉም ላሉ ውድ ነፍሳቸውን ለሸለሙ ይሁን።

07/08/2025

ነሃሴ 1/2008 ዓ/ም ባህርዳር በታሪኳ በደም የታጠበችበት ቀን ነው።
ብዙ አብሮ አደግ ጓደኞቻችን ያጣንበት ጥቁር ቀን
😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭

Address

Tel Aviv

Telephone

+251999999999

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share