Befeta Remane

Befeta  Remane This page is created to encourage people by politically,economically and socially aspects

16/03/2024

የጥቁር_አዝሙድ_አስደናቂ_ጥቅሞች
_____
1ኛ. ለእርጋታ
• አንድ የሾርባ ማንኪያ ትክክለኛውን የጥቁር አዝሙድ ዘይት በባዶሆድ መውሰድ ቀኑን ሙሉ መረጋጋትና ንቃት ያጎናጽፋል፡፡
• እንዲሁም ከራት በኋላ ወደ መኝታ ከማምራት በፊት አንድ የሾርባ ማንኪያ ትክክለኛውን የጥቁር አዝሙድ ዘይት መውሰድ ለሊቱን ሙሉ የተረጋጋና ደስ የሚያሰኝ እንቅልፍ ያስገኛል፡፡
• አንድ ትልቅ የሾርባ ማንኪያ የጥቁር አዝሙድ ዘይት አንድ ሲኒ ቡና ውስጥ ጨምሮ መጠጣት የአእምሮ ጭንቀትን አስወግዶ መረጋጋትን ያስገኛል፡፡
2ኛ. ለሳልና ለአስም
• በዘይቱ ደረትንና ጀርባን ማሸት በቀን ሦስት የሾርባ ማንኪያ መጠጣት፣ ሁለት ማንኪያ በሙቅ ውኃ ውስጥ ጨምሮ እንፋሎቱን መሳብ ይረዳል፡፡
3ኛ. የመጫጫንና ስንፍናን ለማስወገድ
• አንድ የሾርባ ማንኪያ ዘይት በአንድ ብርጭቆ ብርቱካን ጭማቂ ውስጥ ጨምሮ ጧት ጧት ለአሥር ተከታታይ ቀናት መውሰድ ልዩነቱን ያገኙታል፡፡
4ኛ. የማስታወስ ችሎታንና ፈጣን የግንዛቤ አቅምን ለማጎልበት አንድ የሾርባ ማንኪያ የጥቁር አዝሙድ ዘይት፣ 100 ሚሊ ሊትር የፈላ ናና (Nena) ተክል ጋር ተቀላቅሎ ለአሥር ተከታታይ ቀናት መውሰድ፡፡
5ኛ. ለኩላሊት ጠጠር (የስኳር ሕመም ያለባቸው ማርን መተው ነው) ሩብ ኪሎ ጥሬ ጥቁር አዝሙድ፣ ሩብ ኪሎ ንጹሕ ማር ማዘጋጀት፡፡ ጥቁር አዝሙድን በሚገባ መፍጨትና ከማር ጋር ቀይጦ በሚገባ ማዋሀድ፡፡ ከዚያም ሁለት ማንኪያ ከቅይጡ ቀንሶ በአንድ ብርጭቆ የሞቀ ውኃ ውስጥ ጨምሮ በጥቁር አዝሙድ ዘይት አንድ ሻይ ማንኪያ በማከል በባዶ ሆድ መጠጣት፡፡
6ኛ. ለብሩሕ ገጽና ለውበት
አንድ ማንኪያ ጥቁር አዝሙድ ዘይት አንድ ማንኪያ የወይራ ዘይት ጋር አዋሕዶ ፊትን መቀባት አንድ ሰዓት ቆይቶ በውኃና በሳሙና መታጠብ ልዩነቱን በጉልህ ያገኙታል፡፡የጥቁር
7ኛ. ከበሽታ ሁሉ ለመጠበቅ
አንድ የሾርባ ማንኪያ አዝሙድ ዘይት ከአንድ ማንኪያ ማር ጋር አዋሕዶ ያለማቋረጥ ጧት ጧት መውሰድ በጣም ጤናማ ያደርጎታል።
8ኛ. በጭንና ጭን መካከል የቆዳ መቆጣት ሲያጋጥም በቅድሚያ አካባቢውን በውኃና በሳሙና በሚገባ ማጠብ፣ ቀጥሎ በሚገባ ማድረቅና በጥቁር አዝሙድ ዘይት ማታ ቀብቶ ማደርና ለሦስት ተከታታይ ቀናት ይህንኑ መፈጸም፡፡ ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ውጤቱን ያዩታል፡፡
9ኛ. ለልብና ለደም ሥሮች ሕመም
የጥቁር አዝሙድ ዘይት ከትኩስ መጠጥ ጋር በተከታታይ
መውሰድ ስብን ለማሟሟትና የደም ሥሮችን ለማስፋት
ይረዳል፡፡
10ኛ. ለለምጽና ለመሳሰሉት
ተጠቂውን የሰውነት ክፍል በቱፋሕ (ፖም) ወይም አፕል
ኮምጣጤ ማሸት ከዚያም የጥቁር አዝሙድ ዘይት ለ15 ቀናት መቀባት፡፡
11ኛ. ለቁርጥማት ሮማቲዝምና የጀርባ ሕመም
የተወሰነ የጥቁር አዝሙድ ዘይት በጥቂቱ በማሞቅ የታመመውን አካል አጥንትን ዘልቆ እስኪሰማ ድረስ በዘይቱ በደንብ መታሸት በቀን ሦስት ጊዜ አንድ የሾርባ ማንኪያ ዘይት መጠጣት፡፡
12ኛ. ለራስ ምታት
በጥቁር አዝሙድ ዘይት ግንባርንና በጆሮ አካባቢ ያለውን አካል ማሸት ለሦስት ተከታታይ ቀናት አንድ ሻይ ማንኪያ የጥቁር አዝሙድ ዘይት በባዶ ሆድ መጠጣት፡፡
13ኛ. ለጨጓራና ለአሲድ
አንድ ኩባያ ወተት የአንድ የሾርባ ማንኪያ የጥቁር አዝሙድ
ዘይት በቀን ሦስት ጊዜ መውሰድ፡፡ ከሦስት ቀናት በኋላ በሽታው ሙሉ በሙሉ ይወገዳል፡፡
14ኛ. ለራስ ማዞርና ለጆሮ ሕመም
አንድ ጠብታ የጥቁር አዝሙድ ዘይት ጆሮ ውስጥ መጨመር
በሻይ መልክ አዘጋጅቶ መጠጣት፡፡
15ኛ. ለቆዳ መቀረፍ
በዚህ አይነቱ ሕመም የተጠቃው የአካል ክፍል በጥቁር አዝሙድ ዘይት መቀባት ሕመሙ እስኪወገድ ድረስ ይህንኑ መቀጠል፡፡

07/07/2023
በአማራ ክልል የፀጥታ ተቋማት ባልደረቦች የነበሩትን ጨምሮ በርካቶች መታሰራቸውን የደኅንነት ምክር ቤት አስታወቀ።የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት ምክር ቤት ባወጣው መግለጫ፣ በአማራ ክልል የፀጥታ...
09/06/2022

በአማራ ክልል የፀጥታ ተቋማት ባልደረቦች የነበሩትን ጨምሮ በርካቶች መታሰራቸውን የደኅንነት ምክር ቤት አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት ምክር ቤት ባወጣው መግለጫ፣ በአማራ ክልል የፀጥታ ተቋማትን “የከዱ” የተባሉ አባሎችን ጨምሮ በተለያዩ ወንጀሎች ላይ ተሳትፈዋል የተባሉ አካላት በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ገለጸ።

ምክር ቤቱ ትላንት ሰኔ 1 ቀን 2014 ዓ. ም. ባወጣው መግለጫ ላይ “ከፀጥታ ተቋማት የከዱ አባላትን የመያዝ፣ በተለያዩ ወንጀሎች የተሳተፉ አካላትን በቁጥጥር ሥር የማዋል” ሥራ መከናወኑ ተገልጿል።

በአማራ ክልል ባለፉት ሳምንታት መንግሥት “የሕግ ማስከበር” በሚል በወሰደው እርምጃ፣ “ተበትነው የፀጥታ ስጋት ሲሆኑ የቆዩ የጦር መሣሪያዎች የመሰብሰብ፣ በሕገ ወጥ ተግባራት ተሰማርተው የነበሩ አክቲቪስቶችን ሥርዓት የማስያዝ” ሥራ መካሄዱንም የደኅንነት ምክር ቤቱ መግለጫ ይጠቁማል።

እነዚህንም “ሕዝቡን ለእፎይታ ያበቁ ተግባሮች” ሲል ምክር ቤቱ ገልጿቸዋል።

የፌደራል መንግሥት እና የአማራ ክልል መንግሥት በአማራ ክልል የጦር መሣሪያን በመመዝገብ የጀመሩት ዘመቻ ኋላ ላይ ከ4000 በላይ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር የዋሉበት እንደሆነ ተገልጿል።

መንግሥት ዘመቻውን “የሕግ ማስከበር” ቢለውም፣ ዘመቻው መንግሥትን የሚተቹ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችና ማኅበረሰብ አንቂዎችን እንዲሁም ፋኖ የተባለውን ኢ-መደበኛ አደረጃጀት ኢላማ ያደረገ ነው ብለው የሚከራከሩም አሉ።

ምክር ቤቱ የፋኖን ታጣቂዎች በስም ባይጠቅስም ከመንግሥት ፀጥታ መዋቅሮች ውጭ ያሉ የታጠቁ አደረጃጀቶች "እንደፈለጉ" ሊሆኑ እንደማይችሉ በመግለጫው አስፍሯል።

“በአገር ውስጥ ኃይልን በብቸኝነት የመጠቀም መብት ለመንግሥት የተሰጠ መብት ነው። ዜጎች በሰላም ጊዜ አልሚ፣ በጦርነት ጊዜ ተፋላሚ መሆናቸውም ከጥንት የነበረ ነው። ያ ማለት አገር ስትወረር ሁሉም ለአገሩ ተፋላሚ ይሆናል። አገር ሰላም ስትሆን ደግሞ ሁሉም ወደ ሕጋዊ ማዕቀፍ ይገባል ማለት ነው” ብሏል።

ጽንፈኝነት በኢትዮጵያ ምን ያህል ስጋት ነው?ከ 5 ሰአት በፊት

10 የተቃዋሚ ፓርቲዎች የጋራ የምክክር መድረክ አቋቋሙ6 ሰኔ 2022

በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የወረዳ አስተዳዳሪን ጨምሮ 19 ሰዎች ተገደሉ6 ሰኔ 2022

ብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤቱ ሚያዝያ 14 ቀን 2014 ዓ. ም. ስለ አገር አቀፍ የፀጥታና ደኅንነት ያደረገውን ግምገማ ተከትሎ ባስቀመጠው አቅጣጫ፣ ከአማራ ክልል በተጨማሪ በኦሮሚያ እና በቤንሻንጉል ጉሙዝም የተወሰዱ እርምጃዎች እንዳሉ በትናንትናው መግለጫ አትቷል።

በመግለጫው መሠረት በኦሮሚያ ክልል “በሺዎች የሚቆጠሩ የሸኔ አባላት ተገድለዋል”።

“የሸኔን ልዩ ልዩ ቡድኖች የመደምሰስ፣ ሕገ ወጥ እንቅስቃሴዎችን የማምከን፣ በጠላት እጅ የነበሩ አካባቢዎችን መልሶ የመቆጣጠር፣ መንግሥታዊ መዋቅሩን የማጥራት” እርምጃዎች እንደተወሰዱ ጠቅሶ፣ እነዚህንም “ውጤታማ” ሲል ገልጿቸዋል።

ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት የሚለው እና መንግሥት ‘ሸኔ’ የሚለው ታጣቂ ቡድን መካከል ውጊያ ሲካሄድ መሰንበቱ አይዘነጋም።

መንግሥት በሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) ታግዞ በተካሄደው በዚህ ውጊያ ንጹሐን ዜጎች ሰለባ መሆናቸውን የኦሮሚያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በተደጋጋሚ መክሰሳቸው ይታወሳል።

በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ “የታጠቁ ሽፍቶችን ሥርዓት ማስያዝና መደምሰስ” መከናወኑን ጠቅሶ እነዚህን ሥራዎች “አበረታች” ሲል ምክር ቤቱ ገልጿቸዋል።

በክልሉ ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያን የመሰብሰብ እንዲሁም ተፈናቃዮችን ወደ ቀያቸው የመመለሥ ሥራ መሠራቱን አክሏል።

በቤንሻንጉል ጉሙዝ በክልሉ መንግሥትና በተለይም የጉሙዝ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጉሕዴን) መካከል ዘላቂ ሰላም ለማውረድ የሚደረጉ ጥረቶች በተደጋጋሚ መሰናክል ሲገጥማቸው ቆይቷል።

ከቀናት በፊት በካማሺ ዞን በምትገኘው ምዥጋ ወረዳ በክልሉ ልዩ ኃይሎችና በጉሕዴን ታጣቂዎች መካከል በተካሄደ የተኩስ ልውውጥ ሳቢያ 19 ሰዎች መሞታቸው ይታወሳል።

በሌላ በኩል በሶማሌ እና በኦሮሚያ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች “ሊደረግ ታስቦ የነበረው የአል-ሸባብ እንቅስቃሴ በፀጥታ አካላት ቅንጅት ከሽፏል” ሲል ብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤቱ ገልጿል።

በደቡብ እና በጋምቤላ ክልሎች “የታጠቁና የተደራጁ ሽፍቶችን መልክ የማስያዝ እንቅስቃሴ” መከናወኑን ጠቅሶ፣ በተጨማሪም የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴን ለመግታትና በተለያዩ ማኅበረሰቦች መካከል የሚከሰቱ ግጭቶችን የመፍታት ሥራ መሠራቱን መግለጫው አትቷል።
በተለይም የጉሙዝ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጉሕዴን) መካከል ዘላቂ ሰላም ለማውረድ የሚደረጉ ጥረቶች በተደጋጋሚ መሰናክል ሲገጥማቸው ቆይቷል።

ከቀናት በፊት በካማሺ ዞን በምትገኘው ምዥጋ ወረዳ በክልሉ ልዩ ኃይሎችና በጉሕዴን ታጣቂዎች መካከል በተካሄደ የተኩስ ልውውጥ ሳቢያ 19 ሰዎች መሞታቸው ይታወሳል።

በሌላ በኩል በሶማሌ እና በኦሮሚያ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች “ሊደረግ ታስቦ የነበረው የአል-ሸባብ እንቅስቃሴ በፀጥታ አካላት ቅንጅት ከሽፏል” ሲል ብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤቱ ገልጿል።

በደቡብ እና በጋምቤላ ክልሎች “የታጠቁና የተደራጁ ሽፍቶችን መልክ የማስያዝ እንቅስቃሴ” መከናወኑን ጠቅሶ፣ በተጨማሪም የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴን ለመግታትና በተለያዩ ማኅበረሰቦች መካከል የሚከሰቱ ግጭቶችን የመፍታት ሥራ መሠራቱን መግለጫው አትቷል።

ምክር ቤቱ “ዓለም አቀፍ የሚዲያ ትኩረትን ለመሳብ የሚፈልጉ” ያላቸው ቡድኖች በአዲስ አበባ በተደጋጋሚ የቃጡትን ጥቃት የፀጥታና ደኅንነት መዋቅሩ ማክሸፉን አያይዞ ገልጿል።

መንግሥት በአማራ ክልልና በሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች እየተወሰደ ያለውን እርምጃ በተመለከተ ከዚህ ቀደም ባወጣው መግለጫ፣ የሕግ የበላይነትን ማስከበር የዜጎችን ሰላምና ደኅንነት እንዲሁም የአገርን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ብቸኛው መፍትሄ ነው ማለቱ ይታወሳል።

በተለያዩ አካባቢዎች የሚታየውን ሕገ ወጥነትና የሰላም መደፍረስን መንግሥት እንዲቆጣጠር ሕዝቡ በተደጋጋሚ ሲጠይቅ ነበር ያለው መግለጫው፣ ብሔራዊ የፀጥታ ምክር ቤት አስፈላጊው እርምጃ እንዲወሰድ መወሰኑን አስታውሷል።

በዚህ መግለጫውም በአጠቃላይ የተጀመረው ሰላምና ጸጥታ የማስፈን እንዲሁም ሕግና ሥርዓትን የማስከበር ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አፅንኦት ሰጥቷል።

Address

Vellore

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Befeta Remane posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Befeta Remane:

Share