Befeta Remane

Befeta  Remane This page is created to encourage people by politically,economically and socially aspects

31/01/2026

በጣም አሳዛኝ ሞት!

ትናንት ማታ በቤቴ ተኝቼ ነበር። ቤቴ ከመግባቴ አንድ ሰዓት ገደማ በፊት አንድ ፀባይ ሰናይ የሆነ ጎሮቤቴ (የሀዋሳ ዩንቨርሲቲ ጤና ሳይንስ መምህርና ተመራማሪ ዶክተር እንድሪያስ ማርቆስ) ከዩንቨርሲቲው ስብሰባ ሲመለስ በጋራ መኖሪያ ቤታችን ኮርደር ላይ ስንተላለፍ ተገናኝተን ደስ በሚል አኳኋን ሰላምታ ሰጥቶኝ ሰላም ተባብለን ነበር ወደየቤታችን የገባነው።

ከተገናኘን በኋላ ልክ በግምት አንድ ሰዓት ተኩል ገደማ አከባቢ ልዩነት ባለቤቴ ጋደም ካልኩበት በአስቸኳይ እንድወጣና ወደ እሱ ቤት እንድደርስ አስጠራችኝ። እኔም ግራ እየተጋባው ወደ ባልደረባችን ቤት ደረስኩ። ስደርስ ባለቤቱና አራት ጨቅላ ህጻናቱ በድንጋጠ ያለቅሳሉ። ጩሄቱን ሰምተው ቀድመው የደረሱ ጎሮቤቶችና ባለቤቴ ግራ ተጓብተዋል። ዶክተሩ ተዝለፍልፎ በሶፋው ላይ ፀጥ ብሏል።

በርካታ ጎሮቤቶችም የጩሄት ድምፅ ሰምተው ተጨምረው መጡ። በፍጥነት ተሸክመን ከፎቁ አወረድን፤ መኪናዬን በፍጥነት አዘጋጅቼ በከፍተኛ ፍጥነት አዳሬ ሆስፕታል አደረስን። ዶክተሩ ግን መጀመሪያም የለም፤ሄዷል😥

ዶክተሮች በፍጥነት እርዳታ ለመስጠት ሞከሩ፤ ነገር ግን ምንም አይነት እንቅስቃሴ የለም። መጀመሪያም እንደሞተ ነገሩን😥

አሟሟቱን ከባለቤቱ አንደበት፦

"ምንም አይነት ህመም አልነበረበትም፤ ከዩንቨርሲቲው ስብሰባ ተመልሶ፣ ምግቡን በልቶ፣ ከልጆቹ ጋር ተጫውቶ ፀሎት እያደረጉ እያለ ለትንሽ ደቅቃ ተንቀጠቀጠና በተኛበት ሶፉ ላይ ፀጥ ብሎ ቀረ። በጭንቅላቱና በደረቱ ላይ ውሃ ደፋን; ግን ፀጥ ብሎ ሲቀር ነው የጮህነው" አለችን።

ከሌሊቱ 6 ሰዓት ገደማ የዶክተሩን አስክሬን እንደሚሆን አድርገን ወደ ቤት ስንመለስ ጨቅላ ልጆቹ አባታችን ይመለሳል በሚል እሳቤ በቤታቸው ደጅ ቁጭ ብለው በዝምታ የሚመጣውን ሁሉ ያያሉ😥

በህይወቴ እንዲህ አይነት ሀዘን ተሰምቶኝ አያውቅም😭😭!...ቁጭ ብለው የሚጠባበቁትን ልጀች ፊት ለማየት አቅም አጣን! ከባለቤቴ ጋር ሆኔን በፍጥነት ቤታችን ገብተን አለቀስን። መተኛት አልቻልንም። ምን ብለን እናስገባቸው?😭!?...እንደምንም ደፈር ብዬ፦

"ህክምናው ስለሚቆይ ገብታችሁ ተኙ" ብዬ እንዲገቡና እንዲተኛ አደረኳቸው። ለኛ ግን እስከ ሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት እንቅልፍ አለን...

ሰው ከንቱ!

ፈጣሪ ለቤቴሰቦች ወዳጅ ዘመዶቹ መፅናናትን እንዲሰጣቸው እመኛለሁ

RIP😭
Source Dr Tessema Elias

18/12/2025

ወቅታዊ መረጃ፡ ስለ እህታችን ናዝራዊት አበራ አዲስ ተስፋ ሰጪ ዜናዎች

በቻይና በእስር ላይ ስለምትገኘው ኢትዮጵያዊት ናዝራዊት አበራ ወቅታዊ ሁኔታ ከቅርብ ቤተሰቦቿ የተገኘ አዲስ መረጃ ደርሶናል። ናዝራዊት ካለችበት አስቸጋሪ ሁኔታ አንፃር አሁንም ብርቱ ሆና እንደሚገኝ ተገልጿል።

ቀደም ሲል ተከስሶባት የነበረው የሞት ቅጣት በይግባኝ ወደ እድሜ ልክ እስራት መቀየሩ የሚታወስ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ደግሞ ቅጣቱን ይበልጥ ለማቃለል ሌላ የይግባኝ ጥያቄ ቀርቦ በሂደት ላይ ይገኛል። ይህም ለቤተሰቦቿ ትልቅ ተስፋ ሆኗል።

ናዝራዊት በእስር ላይ ቢሆንም ጊዜዋን በከንቱ እያሳለፈች አይደለም፦

* ባላት የእንግሊዝኛ ቋንቋ ችሎታ ለሌሎች እስረኞች ትምህርት እየሰጠች ትገኛለች (በእስረኞች ዘንድም እጅግ ተወዳጅ ናት)።

* በቻይንኛ ቋንቋ የመጀመሪያ ዲግሪዋን የያዘች ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በርካታ የቻይንኛ መጻሕፍትን በማንበብ እውቀቷን እያዳበረች ትገኛለች።

ከዚህ ቀደም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ጉዳዩን በቅርበት ሲከታተሉት የቆዩ ሲሆን፣ ከቻይና ባለስልጣናት ጋርም በተደጋጋሚ ተወያይተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለቤተሰቦቿ ስልክ በመደወል ድጋፋቸውን መግለጻቸውም ተጠቁሟል። በቅርቡም እህቶቿ እና ፓይለት የሆነው ወንድሟ ወደ ቻይና በመጓዝ በአካል አይተዋት ተመልሰዋል።

አንዳንድ በማህበራዊ ሚዲያ የሚዘዋወሩ ያልተረጋገጡ መረጃዎች በቤተሰቧ ላይ ከፍተኛ ድንጋጤ እየፈጠሩ ይገኛሉ።

ቀናቶች ቀሯት የሞት ፍርድ የሚባል ነገር የለም
እባካችሁ ቤተሰብ አታስጨንቁ

ፈጣሪ መጨረሻውን ያሳምርላት፤
በሰላም ወደ ሀገሯ የምትመለስበትን መንገድ ያቅናላት!

🙏🙏🙏

Via Tina

🌴🌴🌴

18/12/2025
17/12/2025
03/10/2025

የተማሪዎች ምገባ ፕሮግራም በደጃዝማች ወንድይራድ ትምሕርት ቤት፣ አዲስ አበባ 1948 ዓም / Student feeding program at Dejazmatch Wonderad School in Addis Ababa 1956
#ታሪካችን

16/03/2024

የጥቁር_አዝሙድ_አስደናቂ_ጥቅሞች
_____
1ኛ. ለእርጋታ
• አንድ የሾርባ ማንኪያ ትክክለኛውን የጥቁር አዝሙድ ዘይት በባዶሆድ መውሰድ ቀኑን ሙሉ መረጋጋትና ንቃት ያጎናጽፋል፡፡
• እንዲሁም ከራት በኋላ ወደ መኝታ ከማምራት በፊት አንድ የሾርባ ማንኪያ ትክክለኛውን የጥቁር አዝሙድ ዘይት መውሰድ ለሊቱን ሙሉ የተረጋጋና ደስ የሚያሰኝ እንቅልፍ ያስገኛል፡፡
• አንድ ትልቅ የሾርባ ማንኪያ የጥቁር አዝሙድ ዘይት አንድ ሲኒ ቡና ውስጥ ጨምሮ መጠጣት የአእምሮ ጭንቀትን አስወግዶ መረጋጋትን ያስገኛል፡፡
2ኛ. ለሳልና ለአስም
• በዘይቱ ደረትንና ጀርባን ማሸት በቀን ሦስት የሾርባ ማንኪያ መጠጣት፣ ሁለት ማንኪያ በሙቅ ውኃ ውስጥ ጨምሮ እንፋሎቱን መሳብ ይረዳል፡፡
3ኛ. የመጫጫንና ስንፍናን ለማስወገድ
• አንድ የሾርባ ማንኪያ ዘይት በአንድ ብርጭቆ ብርቱካን ጭማቂ ውስጥ ጨምሮ ጧት ጧት ለአሥር ተከታታይ ቀናት መውሰድ ልዩነቱን ያገኙታል፡፡
4ኛ. የማስታወስ ችሎታንና ፈጣን የግንዛቤ አቅምን ለማጎልበት አንድ የሾርባ ማንኪያ የጥቁር አዝሙድ ዘይት፣ 100 ሚሊ ሊትር የፈላ ናና (Nena) ተክል ጋር ተቀላቅሎ ለአሥር ተከታታይ ቀናት መውሰድ፡፡
5ኛ. ለኩላሊት ጠጠር (የስኳር ሕመም ያለባቸው ማርን መተው ነው) ሩብ ኪሎ ጥሬ ጥቁር አዝሙድ፣ ሩብ ኪሎ ንጹሕ ማር ማዘጋጀት፡፡ ጥቁር አዝሙድን በሚገባ መፍጨትና ከማር ጋር ቀይጦ በሚገባ ማዋሀድ፡፡ ከዚያም ሁለት ማንኪያ ከቅይጡ ቀንሶ በአንድ ብርጭቆ የሞቀ ውኃ ውስጥ ጨምሮ በጥቁር አዝሙድ ዘይት አንድ ሻይ ማንኪያ በማከል በባዶ ሆድ መጠጣት፡፡
6ኛ. ለብሩሕ ገጽና ለውበት
አንድ ማንኪያ ጥቁር አዝሙድ ዘይት አንድ ማንኪያ የወይራ ዘይት ጋር አዋሕዶ ፊትን መቀባት አንድ ሰዓት ቆይቶ በውኃና በሳሙና መታጠብ ልዩነቱን በጉልህ ያገኙታል፡፡የጥቁር
7ኛ. ከበሽታ ሁሉ ለመጠበቅ
አንድ የሾርባ ማንኪያ አዝሙድ ዘይት ከአንድ ማንኪያ ማር ጋር አዋሕዶ ያለማቋረጥ ጧት ጧት መውሰድ በጣም ጤናማ ያደርጎታል።
8ኛ. በጭንና ጭን መካከል የቆዳ መቆጣት ሲያጋጥም በቅድሚያ አካባቢውን በውኃና በሳሙና በሚገባ ማጠብ፣ ቀጥሎ በሚገባ ማድረቅና በጥቁር አዝሙድ ዘይት ማታ ቀብቶ ማደርና ለሦስት ተከታታይ ቀናት ይህንኑ መፈጸም፡፡ ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ውጤቱን ያዩታል፡፡
9ኛ. ለልብና ለደም ሥሮች ሕመም
የጥቁር አዝሙድ ዘይት ከትኩስ መጠጥ ጋር በተከታታይ
መውሰድ ስብን ለማሟሟትና የደም ሥሮችን ለማስፋት
ይረዳል፡፡
10ኛ. ለለምጽና ለመሳሰሉት
ተጠቂውን የሰውነት ክፍል በቱፋሕ (ፖም) ወይም አፕል
ኮምጣጤ ማሸት ከዚያም የጥቁር አዝሙድ ዘይት ለ15 ቀናት መቀባት፡፡
11ኛ. ለቁርጥማት ሮማቲዝምና የጀርባ ሕመም
የተወሰነ የጥቁር አዝሙድ ዘይት በጥቂቱ በማሞቅ የታመመውን አካል አጥንትን ዘልቆ እስኪሰማ ድረስ በዘይቱ በደንብ መታሸት በቀን ሦስት ጊዜ አንድ የሾርባ ማንኪያ ዘይት መጠጣት፡፡
12ኛ. ለራስ ምታት
በጥቁር አዝሙድ ዘይት ግንባርንና በጆሮ አካባቢ ያለውን አካል ማሸት ለሦስት ተከታታይ ቀናት አንድ ሻይ ማንኪያ የጥቁር አዝሙድ ዘይት በባዶ ሆድ መጠጣት፡፡
13ኛ. ለጨጓራና ለአሲድ
አንድ ኩባያ ወተት የአንድ የሾርባ ማንኪያ የጥቁር አዝሙድ
ዘይት በቀን ሦስት ጊዜ መውሰድ፡፡ ከሦስት ቀናት በኋላ በሽታው ሙሉ በሙሉ ይወገዳል፡፡
14ኛ. ለራስ ማዞርና ለጆሮ ሕመም
አንድ ጠብታ የጥቁር አዝሙድ ዘይት ጆሮ ውስጥ መጨመር
በሻይ መልክ አዘጋጅቶ መጠጣት፡፡
15ኛ. ለቆዳ መቀረፍ
በዚህ አይነቱ ሕመም የተጠቃው የአካል ክፍል በጥቁር አዝሙድ ዘይት መቀባት ሕመሙ እስኪወገድ ድረስ ይህንኑ መቀጠል፡፡

07/07/2023
በአማራ ክልል የፀጥታ ተቋማት ባልደረቦች የነበሩትን ጨምሮ በርካቶች መታሰራቸውን የደኅንነት ምክር ቤት አስታወቀ።የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት ምክር ቤት ባወጣው መግለጫ፣ በአማራ ክልል የፀጥታ...
09/06/2022

በአማራ ክልል የፀጥታ ተቋማት ባልደረቦች የነበሩትን ጨምሮ በርካቶች መታሰራቸውን የደኅንነት ምክር ቤት አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት ምክር ቤት ባወጣው መግለጫ፣ በአማራ ክልል የፀጥታ ተቋማትን “የከዱ” የተባሉ አባሎችን ጨምሮ በተለያዩ ወንጀሎች ላይ ተሳትፈዋል የተባሉ አካላት በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ገለጸ።

ምክር ቤቱ ትላንት ሰኔ 1 ቀን 2014 ዓ. ም. ባወጣው መግለጫ ላይ “ከፀጥታ ተቋማት የከዱ አባላትን የመያዝ፣ በተለያዩ ወንጀሎች የተሳተፉ አካላትን በቁጥጥር ሥር የማዋል” ሥራ መከናወኑ ተገልጿል።

በአማራ ክልል ባለፉት ሳምንታት መንግሥት “የሕግ ማስከበር” በሚል በወሰደው እርምጃ፣ “ተበትነው የፀጥታ ስጋት ሲሆኑ የቆዩ የጦር መሣሪያዎች የመሰብሰብ፣ በሕገ ወጥ ተግባራት ተሰማርተው የነበሩ አክቲቪስቶችን ሥርዓት የማስያዝ” ሥራ መካሄዱንም የደኅንነት ምክር ቤቱ መግለጫ ይጠቁማል።

እነዚህንም “ሕዝቡን ለእፎይታ ያበቁ ተግባሮች” ሲል ምክር ቤቱ ገልጿቸዋል።

የፌደራል መንግሥት እና የአማራ ክልል መንግሥት በአማራ ክልል የጦር መሣሪያን በመመዝገብ የጀመሩት ዘመቻ ኋላ ላይ ከ4000 በላይ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር የዋሉበት እንደሆነ ተገልጿል።

መንግሥት ዘመቻውን “የሕግ ማስከበር” ቢለውም፣ ዘመቻው መንግሥትን የሚተቹ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችና ማኅበረሰብ አንቂዎችን እንዲሁም ፋኖ የተባለውን ኢ-መደበኛ አደረጃጀት ኢላማ ያደረገ ነው ብለው የሚከራከሩም አሉ።

ምክር ቤቱ የፋኖን ታጣቂዎች በስም ባይጠቅስም ከመንግሥት ፀጥታ መዋቅሮች ውጭ ያሉ የታጠቁ አደረጃጀቶች "እንደፈለጉ" ሊሆኑ እንደማይችሉ በመግለጫው አስፍሯል።

“በአገር ውስጥ ኃይልን በብቸኝነት የመጠቀም መብት ለመንግሥት የተሰጠ መብት ነው። ዜጎች በሰላም ጊዜ አልሚ፣ በጦርነት ጊዜ ተፋላሚ መሆናቸውም ከጥንት የነበረ ነው። ያ ማለት አገር ስትወረር ሁሉም ለአገሩ ተፋላሚ ይሆናል። አገር ሰላም ስትሆን ደግሞ ሁሉም ወደ ሕጋዊ ማዕቀፍ ይገባል ማለት ነው” ብሏል።

ጽንፈኝነት በኢትዮጵያ ምን ያህል ስጋት ነው?ከ 5 ሰአት በፊት

10 የተቃዋሚ ፓርቲዎች የጋራ የምክክር መድረክ አቋቋሙ6 ሰኔ 2022

በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የወረዳ አስተዳዳሪን ጨምሮ 19 ሰዎች ተገደሉ6 ሰኔ 2022

ብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤቱ ሚያዝያ 14 ቀን 2014 ዓ. ም. ስለ አገር አቀፍ የፀጥታና ደኅንነት ያደረገውን ግምገማ ተከትሎ ባስቀመጠው አቅጣጫ፣ ከአማራ ክልል በተጨማሪ በኦሮሚያ እና በቤንሻንጉል ጉሙዝም የተወሰዱ እርምጃዎች እንዳሉ በትናንትናው መግለጫ አትቷል።

በመግለጫው መሠረት በኦሮሚያ ክልል “በሺዎች የሚቆጠሩ የሸኔ አባላት ተገድለዋል”።

“የሸኔን ልዩ ልዩ ቡድኖች የመደምሰስ፣ ሕገ ወጥ እንቅስቃሴዎችን የማምከን፣ በጠላት እጅ የነበሩ አካባቢዎችን መልሶ የመቆጣጠር፣ መንግሥታዊ መዋቅሩን የማጥራት” እርምጃዎች እንደተወሰዱ ጠቅሶ፣ እነዚህንም “ውጤታማ” ሲል ገልጿቸዋል።

ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት የሚለው እና መንግሥት ‘ሸኔ’ የሚለው ታጣቂ ቡድን መካከል ውጊያ ሲካሄድ መሰንበቱ አይዘነጋም።

መንግሥት በሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) ታግዞ በተካሄደው በዚህ ውጊያ ንጹሐን ዜጎች ሰለባ መሆናቸውን የኦሮሚያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በተደጋጋሚ መክሰሳቸው ይታወሳል።

በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ “የታጠቁ ሽፍቶችን ሥርዓት ማስያዝና መደምሰስ” መከናወኑን ጠቅሶ እነዚህን ሥራዎች “አበረታች” ሲል ምክር ቤቱ ገልጿቸዋል።

በክልሉ ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያን የመሰብሰብ እንዲሁም ተፈናቃዮችን ወደ ቀያቸው የመመለሥ ሥራ መሠራቱን አክሏል።

በቤንሻንጉል ጉሙዝ በክልሉ መንግሥትና በተለይም የጉሙዝ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጉሕዴን) መካከል ዘላቂ ሰላም ለማውረድ የሚደረጉ ጥረቶች በተደጋጋሚ መሰናክል ሲገጥማቸው ቆይቷል።

ከቀናት በፊት በካማሺ ዞን በምትገኘው ምዥጋ ወረዳ በክልሉ ልዩ ኃይሎችና በጉሕዴን ታጣቂዎች መካከል በተካሄደ የተኩስ ልውውጥ ሳቢያ 19 ሰዎች መሞታቸው ይታወሳል።

በሌላ በኩል በሶማሌ እና በኦሮሚያ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች “ሊደረግ ታስቦ የነበረው የአል-ሸባብ እንቅስቃሴ በፀጥታ አካላት ቅንጅት ከሽፏል” ሲል ብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤቱ ገልጿል።

በደቡብ እና በጋምቤላ ክልሎች “የታጠቁና የተደራጁ ሽፍቶችን መልክ የማስያዝ እንቅስቃሴ” መከናወኑን ጠቅሶ፣ በተጨማሪም የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴን ለመግታትና በተለያዩ ማኅበረሰቦች መካከል የሚከሰቱ ግጭቶችን የመፍታት ሥራ መሠራቱን መግለጫው አትቷል።
በተለይም የጉሙዝ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጉሕዴን) መካከል ዘላቂ ሰላም ለማውረድ የሚደረጉ ጥረቶች በተደጋጋሚ መሰናክል ሲገጥማቸው ቆይቷል።

ከቀናት በፊት በካማሺ ዞን በምትገኘው ምዥጋ ወረዳ በክልሉ ልዩ ኃይሎችና በጉሕዴን ታጣቂዎች መካከል በተካሄደ የተኩስ ልውውጥ ሳቢያ 19 ሰዎች መሞታቸው ይታወሳል።

በሌላ በኩል በሶማሌ እና በኦሮሚያ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች “ሊደረግ ታስቦ የነበረው የአል-ሸባብ እንቅስቃሴ በፀጥታ አካላት ቅንጅት ከሽፏል” ሲል ብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤቱ ገልጿል።

በደቡብ እና በጋምቤላ ክልሎች “የታጠቁና የተደራጁ ሽፍቶችን መልክ የማስያዝ እንቅስቃሴ” መከናወኑን ጠቅሶ፣ በተጨማሪም የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴን ለመግታትና በተለያዩ ማኅበረሰቦች መካከል የሚከሰቱ ግጭቶችን የመፍታት ሥራ መሠራቱን መግለጫው አትቷል።

ምክር ቤቱ “ዓለም አቀፍ የሚዲያ ትኩረትን ለመሳብ የሚፈልጉ” ያላቸው ቡድኖች በአዲስ አበባ በተደጋጋሚ የቃጡትን ጥቃት የፀጥታና ደኅንነት መዋቅሩ ማክሸፉን አያይዞ ገልጿል።

መንግሥት በአማራ ክልልና በሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች እየተወሰደ ያለውን እርምጃ በተመለከተ ከዚህ ቀደም ባወጣው መግለጫ፣ የሕግ የበላይነትን ማስከበር የዜጎችን ሰላምና ደኅንነት እንዲሁም የአገርን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ብቸኛው መፍትሄ ነው ማለቱ ይታወሳል።

በተለያዩ አካባቢዎች የሚታየውን ሕገ ወጥነትና የሰላም መደፍረስን መንግሥት እንዲቆጣጠር ሕዝቡ በተደጋጋሚ ሲጠይቅ ነበር ያለው መግለጫው፣ ብሔራዊ የፀጥታ ምክር ቤት አስፈላጊው እርምጃ እንዲወሰድ መወሰኑን አስታውሷል።

በዚህ መግለጫውም በአጠቃላይ የተጀመረው ሰላምና ጸጥታ የማስፈን እንዲሁም ሕግና ሥርዓትን የማስከበር ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አፅንኦት ሰጥቷል።

ጤና ይስጥልኝ ውድ የቴሌግራም ቻናል  ተከታታዮቻችን ለዛሬ ስለ ደም ዓይነቶች ምን ያህል ያውቃሉ?አብረን እንከታተልABO blood GrouSystem👉 ይህ  ቻናል  በኦን ላይን  የህክምና ምክ...
08/03/2022

ጤና ይስጥልኝ ውድ የቴሌግራም ቻናል ተከታታዮቻችን ለዛሬ ስለ ደም ዓይነቶች ምን ያህል ያውቃሉ?
አብረን እንከታተል
ABO blood GrouSystem
👉 ይህ ቻናል በኦን ላይን የህክምና ምክር አገልግሎት የሚሳጥ ቻናል ስለሆና ሳይብስክረይብ በማድረግ ተጣቃሚ እንድትሆኑ በማላት በአክብሮት እጠይቃችሁዋለሁ።
ከታች የምገኛውን የዩቱብ ቻናል ሳይብስክራይብ አድርጉልን!!!
👇👇👇👇👇👇👇

https://www.youtube.com/channel/UCrRUibbbtUZ3G8A-oY1zEIg
👇👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/
https://t.me/Doctor_Engineer
የደም ዓይነት በቀይ የደም ሴሎች ሽፋን(ገጽ) ላይ የሚገኝ በውርስ የወሰድነውን አንቲጅን(Antigen) መሠረት ያደረገ የደም ክፍፍል ነው፡፡
አራት ዋና ዋና የደም ዓይነቶች አሉ እነሱም ኤ፣ ቢ፣ ኤቢ እና ኦ ናቸው፡፡
የደም ዓይነት ከእናትና አባት በወረስነው ዘረመል(ጂን) ይወሰናል፡፡
ሰውነታችን በአማካይ ከአራት እስከ ስድስት ሊትር ደም ይይዛል፡፡
ደም ከቀይ የደም ሴል፣ ነጭ የደም ሴል እና ፕሌትሌትስ (በፈሳሽ መሰል ፕላዝማ) የተሰራ ወይም የተገነባ ነው፡፡
የፕላዝማ(Plasma) 90% ውሃ ሲሆን በተጨማሪ ፕሮቲን፣ ሆርሞንና ውጋጅ ቆሻሻዎችን ይዟል፡፡
የደማችን 60% የሚሆነው ፕላዝማ ሲሆን 40% የሚሆነው ደግሞ የደም ሴሎች ናቸው፡፡
የደም ሴሎቻችን እያንዳንዳቸው የራሳቸው ተግባር አላቸው ቀይ የደም ሴሎች ኦክስጂን ወደተለያየ የሰውነት ክፍል ያደርሳሉ ካርበን ዳይኦክሳይድ እና ቆሻሻዎችን ከሰውነታችን ያስወግዳሉ፤ ደም ቀይ ቀለም እንዲኖረው አድርገውታል፡፡
ነጭ የደም ሴሎች ሰውነታችን በሽታ የመከላከል ሥርዓት አንዱ ክፍል ሲሆን ኢንፌክሽንን በመዋጋት ይረዳናል፡፡
ፕሌትሌትስ ደም እንዲረጋ በማድረግ የደም መፍሰስን ይከላከላሉ፡፡
የደም ዓይነታችን የሚለየው/የሚታወቀው በደም ውስጥ በሚገኙ አንቲጅን(Antigen) እና አንቲበዲ(Antibody) አማካይነት ነው፡፡
አንቲበዲ(Antibody) ሰውነታችን ከውጪ ለሚገቡ ጀርሞችን ለመከላከል የሚጠቀምበት የበሽታ መከላከያ ሥርዓት ክፍል ነው፡፡
አንቲጅን በቀይ የደም ሴሎች ገጽ ላይ የሚገኙ ፕሮቲኖች ናቸው አንቲበዲዎች በፕላዝማ ውስጥ የሚገኝ ፕሮቲን ሲሆን ከውጭ ወደሰውነታችን የገቡ ማንኛውንም ነገሮች በመለየት እንዲወገዱ ለበሽታ የመከላከል ስርዓት ጥቆማ ያደርጋል፡፡
የኤ.ቢ.ኦ የደም ሥርዓት ክፍፍል ምን ይመስላል?
አራት ዋና ዋና የደም ዓይነቶች አሉ፡፡
• ኤ(A)፦ በቀይ የደም ሴል ላይ ኤ አንቲጅን ብቻ ይገኛል (በፕላዝማ ውስጥ ደግሞ ቢ አንቲበዲ ይገኛል)፡፡
• ቢ(B)፦ በቀይ የደም ሴል ላይ ቢ አንቲጅን ብቻ ይገኛል (በፕላዝማ ውስጥ ደግሞ ኤ አንቲበዲ ይገኛል)፡፡
• ኤቢ(AB)፦ በቀይ የደም ሴል ላይ ኤ እና ቢ አንቲጅን ይገኛሉ (በፕላዝማ ውስጥ ደግሞ ምንም ዓይነት አንቲበዲ አይገኝም)
• ኦ(O)፦ በቀይ የደም ሴል ላይ ምንም ዓይነት አንቲጅን አይገኝም (በፕላዝማ ውስጥ ሁለቱም ኤ እና ቢ አንቲበዲ ይገኛሉ)፡፡
የትኛው የደም ዓይነት ለየትኛው የደም ዓይነት መስጠት ይችላል?
✓ ኦ(O) የደም ዓይነት ለማንኛውም ሰው ደም መለገስ ይችላል፡፡
✓ ኤ(A) የደም ዓይነት ያለው ሰው ኤ እና ኤቢ የደም ዓይነት ላለቸው ደም መለገስ ይችላል፡፡
✓ ቢ(B) የደም ዓይነት ያለው ሰው ቢ እና ኤቢ የደም ዓይነት ላለቸው ደም መለገስ ይችላል፡፡
✓ ኤቢ(AB) የደም ዓይነት ያለው ሰው ኤቢ የደም ዓይነት ላለው ሰው ብቻ ደም መለገስ ይችላል፡፡
ከየትኛው የደም ዓይነት መቀበል ይችላሉ?
✓ ኦ(O) የደም ዓይነት ካለዎት ከ ኦ(O) ብቻ ይቀበላሉ፡፡
✓ ኤ(A) የደም ዓይነት ካለዎት ከ ኤ(A) እና ከ ኦ(O) ብቻ ይቀበላሉ፡፡
✓ ቢ(B) የደም ዓይነት ካለዎት ከ ቢ(B) እና ከ ኦ(O) ብቻ ይቀበላሉ፡፡
✓ ኤቢ(AB) የደም ዓይነት ከማንኛውም የደም ዓይነት መቀበል ይችላሉ፡፡
ከኤ(A) እና ቢ(B) አንቲጅን በተጨማሪ ሌላ ሶስተኛ አንቲጅን አለ እሱም አር.ኤች ፋክተር(Rh factor) ይባላል፡፡

በደም ውስጥ ሊኖርም ላይኖርም ይችላል በደም ውስጥ ሲገኝ ፖዘቲቭ (+) ይባላል በደም ውስጥ ሳይገኝ ሲቀር ደግሞ ነጌቲቭ(-) ይባላል፡፡

• ሌሎች መረጃዎች ቶሎ ቶሎ እንድደርስዎ ፔችንን ላይክ ሼር ያድርጉ
ለበለጠ መረጃ ሊንኩን ተጭነው የኛ ቤተሰብ ይሁኑ

ስለምትከታተሉን ከልብ አመሰግናለሁ መልካም ጤንነት
👉 ይህ ቻናል በኦን ላይን የህክምና ምክር አገልግሎት የሚሳጥ ቻናል ስለሆና ሳይብስክረይብ በማድረግ ተጣቃሚ እንድትሆኑ በማላት በአክብሮት እጠይቃችሁዋለሁ።
ከታች የምገኛውን የዩቱብ ቻናል ሳይብስክራይብ አድርጉልን!!!
👇👇👇👇👇👇👇

https://www.youtube.com/channel/UCrRUibbbtUZ3G8A-oY1zEIg
👇👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/
https://t.me/Doctor_Engineer

ሀላብ ኦሶ ጃለ

04/03/2022

ምኒሊክና አድዋ የነጻነትና የብዘሃነት ኢትዮጵያ መሰረቶች !

በአጼ ምኒሊክ መሪነት አድዋ ላይ ያገኘነው ድል ብዘሃነታችን ማትረፍ ብቻ ሳይሆን ህልውናችንንም ጭምር ያስከበረ ድል ነው። እኛ ኢትዮጵያውያን የጣሊያንን የነጭ ሰራዊት አድዋ ላይ በማሸነፋችን በጥቁር ዘር ላይ ነጮች የድገሱትን የጥፋት ድግስ በማቆም የአለም ታሪክ ይሄድ የነበረበትን አደገኛ አቅጣጫ አስቀይረናል ። መልካም 126ኛው የአደዋ ድል በአል። ዋንጫችንን ለምኒሊክ ከፍ እናድርግ!

የዛሬ ኦሮሞነት፣ አማራነት፣ ትግሬነት፣ ሶማሌነት፣ ጉራጌነትና ወዘተ የተረፈው አደዋ ምድር ላይ ኦሮሞ፣ አማራውም፣ ጉራጌው፣ ትግሬውና ወዘተ ደሙን በጋራ አፍሶ አጥንቱን ከስከሶ ነው።
የእምነት የቋንቋ የባህል ልዩነታችን የድክመታችን ምንጭ ሆኖ፣ አድዋ ላይ በጋራ ተሰባስበን ጣሊያንን ማሸነፍ ባንችል ኖሮ፣ ዛሬ ኦሮሞነት፣ አማራነት፣ ትግራዋይነት፣ ሲዳማነትና ውዘተ የሚባል ነገር አይኖርም ነበር።

ክርስትና፣ እስልምና፣ ዋቄ ፈታ፣ አክሲዮም ጽዮን፣ ላሊበላ፣ አልነጃሺ፣ እሬቻ፣ ጨምበላላ፣ ገዳ፣ ቡሄ፣ አሽንዳ፣ አተቴ፣ ሌሎችም በተለያዩ ብሄር ብሄርሰቦች ወስጥ የሚገኙ ድንቅ የእምነት የባህል እሴቶችቻን አይኖሩም ነበር። የሺ ዘመናት እድሜ ያላቸው የተዋህዶ ክርስትና እና የእስልምና ሃይማኖት መትረፍ የቻሉት ክርስቲያኑ ከሙስሊሙ ጎን ሙስሊሙ ከከርስቲያኑ ጎን አድዋ ላይ ወድቆ ነው።

እሬቻ የተረፈው፣ እሬቻ ዛሬ በአል ሆኖ የሚከበረው ኦሮሞና አማራ አንድ ላይ ከሌሎች የሃገሪቱ ህዝቦች ጋር በጋራ ጣሊያንን አድዋ ስለሰበሩት ብቻ ነው። የዘመኑ አንዳንድ ደንባራ የኦሮሞ ልሂቃን እንደሚሉን ኦሮሞው አማራውን ወይም አማራው ኦሮሞውን ሰብሮት ቢሆን ኖሮ እንኳን እሬቻ ሁላችንም አንኖርም ነበር። አማራና ትግሬ ብቻቸውን አድዋ ላይ ጣሊያንን ገጥመው ተሸነፈው ቢሆን ኦሮሞነት አይኖርም ነበር።

ዛሬ በኢትዮጵያ ውስጥ በመቶ ሚሊዮኖች ተከታዮች ያሏቸው፣ ታሪክ የራሱን የዘመናት አሻራ ያሳረፋባቸው፣ ከማንነታችን ጋር የተጋመዱ የክርስትና እና የእስልምና ልዩ እምነቶች አሉን። አድዋ ላይ ተሸነፈን ቢሆን ኖሮ እምነቶቻችንም የኦርቶዶክስ ተዋህዶ፣ ወይም እስልምና ወይም ዋቄ ፈታ ወይም ሌላም ሃገራዊ እምነት መሆኑ ቀርቶ ጣሊያኖች የሚጭኑብን የጣሊያኖች እምነት ብቻ ይሆን ነበር። ከዛም በታች ተዋርደን ሁሉም ቀርቶ “ደግሞ ለባሪያ የምን እምነት” ተብለን እንደ ውሻ በቤተእምነት ደጃፍ ላይ እንዳንደርስ እንደረግ ነበር።

ስማችን ኦኬሎና አርዬት፣ ለሜሳና ጫልቱ፣ ሃጎስና ሃዳስ፣ ሃሰንና ዘይነብ፣ ሃይለ ሚካኤልና ወለተማሪያ፣ አንበርብርና ተዋበች፣ ዘበርጋና ኬርየዢ፣ ኤራቶና መፋያት፣ በርገኖና ጫኪሴ፣ ገቲሶና ሚሸሜ፣ ግሽና እና አቸም፣ ወዘተ የሚል ሆኖ የምናገኘው አያቶቻችን በጋራ ብዝሃነታችን ሲከላከሉ ደማቸውን በማፍሰሳቸው አጥንታቸውን በመከስከሳቸው ነው።

ቅደመ አያቶቻችን በጋራ ጣሊያንን መመከት ተስኗቸው ቢሆን ኖሮ ዛሬ ሁሉም የእዚህ ሃገር ወንድና ሴት በሙሉ ሰብአዊ ክብራችንን ገፎ በባርነት ሊገዛን ባህር አቋርጦ መጥቶ በነበረው በጣሊያን የባሪያ ገዥ ስም ነበር የምንጠራው። ወንዱን ከዚህ መልስ “ማሪዎ” ተብለሃል ሴቷን ደግሞ ከዚህ መለሰ “ማርገሪታ” ተብለሻል እየተባለ የጅምላ ስም ይታደለን ነበር። ለባርነት በተዳረጉ በሌሎች ሃገሮች ይህ የስም አሰጣጥ ተግባራዊ መደረጉን አንርሳ!

ልብሳችን፣ ምግባችን፣ ሙዚቃችን፣ ጭፈራችን፣ ቋንቋችንና ተውፊታችን እንደ ብዝሃነታችን የተዋበና ያማረ ሆኖ መትረፍ የቻለው በጋራ አድዋ ላይ የወደቁ የቅደመ አያቶቻችን የመስዋእትነት ልጆች ስለሆነን ብቻ ነው።

አድዋ ላይ ተሸንፈን ቢሆን አለባበሳችንም አመጋገባችንም አንድ ወጥ የጣሊያን አለባበስና አመጋገብ፣ መልካችንም የጣሊያን ዲቃላ፣ ነጫጭባ፣ ሙላቶ ይሆን ነበር።

አድዋ ላይ ተዋርደን ቢሆን ኖሮ ሁላችንም የምንናገረውም ቋንቋ ጣሊያንኛ ይሆን ነበር። ወይም ከጣሊያን ጋር ተስማማተው ኢትዮጵያ ላይ የሰፈሩ አውሮፓውያን ጌቶቻችን ቋንቋ ይሆን ነበር።
ዛሬ የልዩነትና የመጋጫ ምክንያት አድርገን የምናቀርበው የዘውግ ማንነት፣ የቋንቋ፣ የባህል፣ የዘር ልዩነት ወድሞ፣ ተጨፍልቆ እንደሰው በኩራት ሳይሆን፣ ጣሊያን በፋብሪካው ከሚያመርተው ርካሽ የፋብሪካ እቃ ወይም በገመድ ጣሊያኖች አስረው በየፓርኩ ከሚጎትቷቸው ውሾች የተለየ ማንነት የማይኖረን፣ ከቢጫው ዘር በታች የተመደብን የመጨረሻው የተዋረድን የአለም ፍጥረቶች ሆነን እናርፈው ነበር። ያም እድለኞች ከሆንን እንጂ፣ እንዲህ አይነቱ እድል ላይገጥመን ይችል ነበር።

ኢትዮጵያ በብዝሃነት ያሸበረቀችው፣ የኢትዮጵያ ልጆች በቅኝ ከተገዙ የአለም ህዝቦች የተለየን ሆነን የተረፍነው፣ ነጭ ከኛ የተለየና የተሻለ ፍጡር ነው ብለን የማናምነው፣ በአለም አደባባይ አንገታችንን ቀና አድርገን መራመድ የቻልነው፣ የእምነት፣ የባህል፣ የቋንቋና ሌሎችም ብዝሃነታችን የሚያንጸባርቁ እሴቶቻችን ማትረፍ የቻልነው፣ በጋራ የቆሙ በጋራ የወደቁ ቅድመ አያቶቻችን ልጆች ስለሆንን ነው። አማራውን የኦሮሞው ኦሮሞውን የአማራው ትግሬውን የጉራጌው ጉራጌውን የትግሬው፣ ሲዳማውን የሱማሌው ሱማሌውን የሲዳማው ልጅ የሚያደርገው የኛ ቅድመ አያቶች አንዳቸው ለአንዳችን መትረፍ ተያያዘው በጋራ መስዋእትነት በመክፈላቸው ነው።

ምኒሊክ ከመላው ኢትዮጵያ ወረኢሊና በኋላም አድዋ ላይ እንዲሰባሰብ የጠራው ህዝብ ሳይገኝ ቀርቶ ቢሆን፣ ተገኝቶም በወኔና በጀግነት ሳይዋጋ ቀርቶ ቢሆን የዛሬው የየግላችን የማንነታችን መለያ አድረገን መናቆሪያ ያደረገነው ቋንቋችን፣ ባህላችን፣ እምነታችን፣ የኔ ነው አትድረሱብኝ የምንለው አሰፋፈራችን ያበቃለት ነበር።

በ19ኛው ምእተ አመት መጨረሻ፣ ነጮች ለጥቁር ዘር የደገሱት ድግስ ምን እንደሆነ በደንብ ለሚረዳ፣ የእኛ ቅደመ አያቶች አድዋ ላይ ተሸንፈው ቢሆን ኖሮ አገራችንን ባህር አቋርጦ ለመጣ ጠላት ማስረከብ ብቻ ሳይሆን እንደሰው በዚች ምድር ላይ መኖራችንም አጣራጣሪ ነበር።

የነጮች ህልም በተፈጦሮ ሃብት፣ በመልካም አየር ጠባይና በመሬት ስፋት የታደለችውን አፍሪካ ከውስጧ ነባሩን የጥቁር ዘር አጥፈተው እንደ አውስትራሊያና እንደ ሰሜን አሜሪካ የነጮች መፈንጫ ለማድረግ ነበር። አላማቸው ለአውሮፓ ኢንዱስትሪዎች ጥሬ ሃብት ከአፍሪካ መውሰድ አልነበረም። የቅኘ ግዛት አላማቸው ጥሬ እቃው ፍለጋ መሆኑ ቀርቶ ሰው ማስፈሪያ ፍለጋ ሆኖ ነበር።

ስለሆነም ነው እኛ ኢትዮጵያውያን በአድዋ ድል ስንኮራ የሚያይ የጥቁር ዘር በሙሉ እኛም የተረፍነው በእናንተ ቅድመ አያቶች መስዋእትነት ነው። ክብር ለአድዋ ሰማእታት” የሚለን።
አድዋ ላይ ቀደምቶቻችን ጣሊያንን ድል በመንሳት ያተረፉት ከብዘሃነታችን ጋር የተያያዙ የየአካባቢያችን ትውፊቶች፣ የታሪክ ቅርሶችና ቁንቋዎች ብቻ አይደለም። እነዚህ የየአካባቢውን እምነቶች፣ ተውፊቶች፣ የታሪክ ቅርሶች፣ የሁሉም የሃገሪቱ ህዝብ ሃብቶች እንዲሆኑ በማደረግ ጭምር ነው።

ለወላይታው ወጣት የአክሱም ሃውልት ትርጉም የሚሰጠው ያለ እሱ ቅድመ አያቶች የአድዋ ምድር መስዋእተነት አክሱም የጣሊያን እንጂ የትግሬ ሃገር አለመሆኗን፣ ሃውልቱም የኢምፔሪያል ጣሊያን የድል አድራጊንት ምልክት እንጂ የአንድ አፍሪካዊ ህዝብ የታላቅ ስልጣኔ ማስታወሻ እንደማይሆን ስለሚታወቅ ነው። ሌሎችም ከደቡብ እስከ ስሜን ከምእራብ እስከ ምስራቅ ያሉ የታሪክ ቅርሶች በሙሉ የአካባቢው ሳይሆኑ የመላው የሃገሪቱ ዜጎች መኩሪያና መመኪያ ቅርሶች ተደርገው የሚታዩት በዚህ ሎጂክ ነው። ያለሁሉም መስዋእትነት አንዳቸውም አይተርፉምና ነበርና ነው።

ደግሞ ደጋግሞ በታሪክ እንደታየው፣ የታሪክ ጸሃፊዎችም እንደሚያስገነዝቡን ሀገራትን ሃገር ከሚያደርጋቸው ትልቁና ጠንካራ ኩነት ዋናው የአንድ ሃገር ህዝቦች ራሳቸውን ከወራሪ ጠላት በመከላከል በጋራ የከፈሉት መስዋእተነትና በጋራ የሚተዳጁት ድል ነው። አድዋ የዘመናዊት ኢትዮጵያ የሃገር መሰረት የሆነውም፣ ከመሆንም ውጭ አማራጭ እንዳይኖረን ያደረገው በዚህ ታሪካዊ ትርጉሙ የተነሳ ነው።

23/02/2022


_____
1ኛ. ለእርጋታ
• አንድ የሾርባ ማንኪያ ትክክለኛውን የጥቁር አዝሙድ ዘይት በባዶሆድ መውሰድ ቀኑን ሙሉ መረጋጋትና ንቃት ያጎናጽፋል፡፡
• እንዲሁም ከራት በኋላ ወደ መኝታ ከማምራት በፊት አንድ የሾርባ ማንኪያ ትክክለኛውን የጥቁር አዝሙድ ዘይት መውሰድ ለሊቱን ሙሉ የተረጋጋና ደስ የሚያሰኝ እንቅልፍ ያስገኛል፡፡
• አንድ ትልቅ የሾርባ ማንኪያ የጥቁር አዝሙድ ዘይት አንድ ሲኒ ቡና ውስጥ ጨምሮ መጠጣት የአእምሮ ጭንቀትን አስወግዶ መረጋጋትን ያስገኛል፡፡
2ኛ. ለሳልና ለአስም
• በዘይቱ ደረትንና ጀርባን ማሸት በቀን ሦስት የሾርባ ማንኪያ መጠጣት፣ ሁለት ማንኪያ በሙቅ ውኃ ውስጥ ጨምሮ እንፋሎቱን መሳብ ይረዳል፡፡
3ኛ. የመጫጫንና ስንፍናን ለማስወገድ
• አንድ የሾርባ ማንኪያ ዘይት በአንድ ብርጭቆ ብርቱካን ጭማቂ ውስጥ ጨምሮ ጧት ጧት ለአሥር ተከታታይ ቀናት መውሰድ ልዩነቱን ያገኙታል፡፡
4ኛ. የማስታወስ ችሎታንና ፈጣን የግንዛቤ አቅምን ለማጎልበት አንድ የሾርባ ማንኪያ የጥቁር አዝሙድ ዘይት፣ 100 ሚሊ ሊትር የፈላ ናና (Nena) ተክል ጋር ተቀላቅሎ ለአሥር ተከታታይ ቀናት መውሰድ፡፡
5ኛ. ለኩላሊት ጠጠር (የስኳር ሕመም ያለባቸው ማርን መተው ነው) ሩብ ኪሎ ጥሬ ጥቁር አዝሙድ፣ ሩብ ኪሎ ንጹሕ ማር ማዘጋጀት፡፡ ጥቁር አዝሙድን በሚገባ መፍጨትና ከማር ጋር ቀይጦ በሚገባ ማዋሀድ፡፡ ከዚያም ሁለት ማንኪያ ከቅይጡ ቀንሶ በአንድ ብርጭቆ የሞቀ ውኃ ውስጥ ጨምሮ በጥቁር አዝሙድ ዘይት አንድ ሻይ ማንኪያ በማከል በባዶ ሆድ መጠጣት፡፡
6ኛ. ለብሩሕ ገጽና ለውበት
አንድ ማንኪያ ጥቁር አዝሙድ ዘይት አንድ ማንኪያ የወይራ ዘይት ጋር አዋሕዶ ፊትን መቀባት አንድ ሰዓት ቆይቶ በውኃና በሳሙና መታጠብ ልዩነቱን በጉልህ ያገኙታል፡፡የጥቁር
7ኛ. ከበሽታ ሁሉ ለመጠበቅ
አንድ የሾርባ ማንኪያ አዝሙድ ዘይት ከአንድ ማንኪያ ማር ጋር አዋሕዶ ያለማቋረጥ ጧት ጧት መውሰድ በጣም ጤናማ ያደርጎታል።
8ኛ. በጭንና ጭን መካከል የቆዳ መቆጣት ሲያጋጥም በቅድሚያ አካባቢውን በውኃና በሳሙና በሚገባ ማጠብ፣ ቀጥሎ በሚገባ ማድረቅና በጥቁር አዝሙድ ዘይት ማታ ቀብቶ ማደርና ለሦስት ተከታታይ ቀናት ይህንኑ መፈጸም፡፡ ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ውጤቱን ያዩታል፡፡
9ኛ. ለልብና ለደም ሥሮች ሕመም
የጥቁር አዝሙድ ዘይት ከትኩስ መጠጥ ጋር በተከታታይ
መውሰድ ስብን ለማሟሟትና የደም ሥሮችን ለማስፋት
ይረዳል፡፡
10ኛ. ለለምጽና ለመሳሰሉት
ተጠቂውን የሰውነት ክፍል በቱፋሕ (ፖም) ወይም አፕል
ኮምጣጤ ማሸት ከዚያም የጥቁር አዝሙድ ዘይት ለ15 ቀናት መቀባት፡፡
11ኛ. ለቁርጥማት ሮማቲዝምና የጀርባ ሕመም
የተወሰነ የጥቁር አዝሙድ ዘይት በጥቂቱ በማሞቅ የታመመውን አካል አጥንትን ዘልቆ እስኪሰማ ድረስ በዘይቱ በደንብ መታሸት በቀን ሦስት ጊዜ አንድ የሾርባ ማንኪያ ዘይት መጠጣት፡፡
12ኛ. ለራስ ምታት
በጥቁር አዝሙድ ዘይት ግንባርንና በጆሮ አካባቢ ያለውን አካል ማሸት ለሦስት ተከታታይ ቀናት አንድ ሻይ ማንኪያ የጥቁር አዝሙድ ዘይት በባዶ ሆድ መጠጣት፡፡
13ኛ. ለጨጓራና ለአሲድ
አንድ ኩባያ ወተት የአንድ የሾርባ ማንኪያ የጥቁር አዝሙድ
ዘይት በቀን ሦስት ጊዜ መውሰድ፡፡ ከሦስት ቀናት በኋላ በሽታው ሙሉ በሙሉ ይወገዳል፡፡
14ኛ. ለራስ ማዞርና ለጆሮ ሕመም
አንድ ጠብታ የጥቁር አዝሙድ ዘይት ጆሮ ውስጥ መጨመር
በሻይ መልክ አዘጋጅቶ መጠጣት፡፡
15ኛ. ለቆዳ መቀረፍ
በዚህ አይነቱ ሕመም የተጠቃው የአካል ክፍል በጥቁር አዝሙድ ዘይት መቀባት ሕመሙ እስኪወገድ ድረስ ይህንኑ መቀጠል፡፡
16ኛ. ለቡግር
ጥቁር አዝሙድ አድቅቆ መፍጨት የሰሊጥ ዘይትና አንድ ማንኪያ የስንዴ ዱቄት ጨምሮ በአንድነት መለወስ ማታ ማታ ተቀብቶ ማደርና ጠዋት ለብ ባለ ውኃና በሳሙና መታጠብ፡፡
17ኛ. ለስብራት አፋጣኝ ጥገና
የምስርና የሽንኩርት ሾርባ፣ ቅቅል እንቁላል፣ አንድ ትልቅ ማንኪያ የደቀቀ ጥቁር አዝሙድ በአንድነት ቀላቅሎ ቢያንስ አንድ ቀን ወስዶ በቀጣዩ ቀን አርፎ እንደገና በሁለተኛው ቀን መውሰድ፤ ስብራቱ የዘመናዊ ሕክምና በጀሶ ከታሰረ በኋላ በአቅራቢያ ያለውን አካል በጥቁር አዝሙድ ዘይት ማሸት፤ እስሩ ከተፈታ በኋላ ደግሞ ለብ ባለ የጥቁር አዝሙድ ዘይት በየቀኑ ማሸት ነው፡፡
18ኛ. ለጠባሳና ለመሳሰሉት
አንድ እፍኝ ጥቁር አዝሙድ በሚገባ ማፍላት የተጎዳውን አካል ማጠብና ለሩብ ሰዓት በተዘጋጀው ፍል ጥቁር አዝሙድ ውስጥ መንከር፡፡ አካሉን ማንቀሳቀስ፡፡ ሳይሸፈን አድካሚ እንቅስቃሴ ሳያደርጉ መቆየት፡፡ ከመኝታ በፊት በየቀኑ ይህን መደጋገም፡፡
19ኛ. ለደም ብዛት
ትኩስ መጠጥ ባሰኘው መጠን ጥቂት የጥቁር አዝሙድ ዘይት ጠብታዎችን ጨምሮ መጠጣት፡፡ በተጨማሪም ገላውን ጥቁር አዝሙድ በመቀባት ቢያንስ በየሳምንቱ አንድ ጊዜ የፀሐይ ሙቀት ቢወስዱ።
20ኛ. ለኩላሊት ኢንፌክሽን
የጥቁር አዝሙድ ዱቄት በወይራ ዘይት ለውሶ ሕመም
በሚሰማበት ቦታ መለጠፍ፤ በተጨማሪም አንድ ማንኪያ የጥቁር አዝሙድ በየቀኑ በባዶ ሆድ ለአንድ ሳምንት ጥሬውን መቃም፣ ከዚያ በኋላ ኢንፌክሽኑ ይወገዳል፡፡
21ኛ. ለሐሞት ከረጢት
አንድ ማንኪያ የጥቁር አዝሙድ፣ ሩብ ማንኪያ የተፈጨ ሬት፣ አንድ ኩባያ ማር ጋር መለወስና ጧትና ማታ መብላት፡፡ ፊትዎ ቅላት እስኪያሳይና ችግሩ እስኪወገድ ድረስ ይህንኑ መፈጸም፡፡ በየዕለቱ በባዶ ሆድ አንድ ሲኒ የወይራ ዘይት መጠጣት አይርሱ፡፡
22ኛ. ለልብና ለደም ዝውውር ችግር
የልብ ሕመምተኛ ሰው በማናቸውም ወቅት እንደ ምግብም፣
እንደመጠጥም እንደአስፈላጊነቱ መውሰድ ይኖርበታል
22ኛ. ለልብና ለደም ዝውውር ችግር
የልብ ሕመምተኛ ሰው በማናቸውም ወቅት እንደ ምግብም፣
እንደመጠጥም እንደአስፈላጊነቱ መውሰድ ይኖርበታል፡፡
23ኛ. ለትውከት
ጥቁር አዝሙድ ከቅርንፉድ ጋር በደንብ ማፍላት ማጣፈጫዎች ሳይጨምሩ በቀን ሦስት ጊዜ መጠጣት፡፡ ሁለተኛ ዙር መጠጣት አያስፈልግም፡፡
24ኛ. ለቃርና ለመሳሰሉት
የተወሰኑ የጥቁር አዝሙድ ቅባት ጠብታዎች በአንድ ኩባያ ትኩስ ወተት ውስጥ ጨምሮ በማር አጣፍጦ መጠጣት፡፡ የቃር ስሜትዎ እንዳልነበር ሆኖ ይጠፋል፡፡ በእንግሊዘኛ (Lettuce) የተሰኘውን ተክል በብዛት መብላትንም አይዘንጉ፡፡
25ኛ. ለዓይን በሽታ
በጥቁር አዝሙድ ዘይት በዓይንና በጆሮ መካከል ያለውን
የሰውነት አካል ከመኝታ በፊት ማሸት በማናቸውም ትኩስ
መጠጥ ውስጥ አልያም የሥራ ሥር ጭማቂ እንደ ካሮት
የመሳሰሉት ውስጥ ጥቂት ጠብታዎች ጨምሮ መጠጣት ነው፡፡
26ኛ. የምግብ ፍላጎትን ለማሳደግ
ከምግብ በፊት ጥቂት ደቂቃዎች ቀደም ብሎ አንድ ማንኪያ
ጥቁር አዝሙድ ቅመሙን በጥርሶችዎ ማድቀቅ፣ ከዚያም ጥቂት ኮምጣጤ ጠብታዎች የተቀላቀለበት አንድ ስኒ ቀዝቃዛ ውኃ ያወራርዱት፡፡
27ኛ. ለቅማልና ለቅጫም
ጥቁር አዝሙድ አድቅቆ መፍጨት በኮምጣጤ ለውሶ ለመታ በሚያገለግል መልኩ ማዘጋጀት ፀጉርን ተላጭቶ መቀባት አሊያም ቆዳው ድረስ ዘልቆ እንዲገባ ማድረግና ለሩብ ሰዓት ለፀሐይ ማጋለጥ፡፡ ከአምስት ሰዓታት በኋላ መታጠብ፡፡ ለአንድ ሳምንት ያህል ይህንኑ ደጋግሞ መፈጸም፡፡
28ኛ. ለጥርስ፣ ለቶንስልና ለጉሮሮ ሕመም
የጥቁር አዝሙድ አፍልቶ መጉመጥመጥና ለጉሮሮ ችግር እጅግ ጠቃሚ ነው፡፡ አንድ ማንኪያ አዘጋጅቶ ለብ ባለ ውኃ ውስጥ ጨምሮ መጠጣትና በዘይቱም የጉሮሮን ውጫዊ አካል መቀባት በውስጥ ደግሞ መንጋጋን መቀባት፡፡
29ኛ. ከደም ላይ ኮሊስትሮን (ስብን) ለማስወገድ
አንድ ማንኪያ የጥቁር አዝሙድ ዱቄት አንድ ማንኪያ
የእኸሊ ቅጠል ከአንድ ስኒ ንጹሕ ማር ጋር ለውሶ በባዶ ሆድ መብላት፡፡
30ኛ. ለሽንት መታቀብ ችግር
ከእምብርት በታች ያለውን የሰውነት አካል በጥቁር አዝሙድ
ቅባት ከመኝታ በፊት ማሸት፡፡ አንድ ማንኪያ የጥቁር አዝሙድ ዘይት በአንድ ኩባያ ውኃ አፍልቶ በማር አጣፍጦ ከመኝታ በፊት በእለቱ መጠጣት፡፡
31ኛ. ፊት ላይ እንደ ቡጉር ክብ ሆኖ ለሚወጣ አተርን ያክል ጠጣር ነገር (WATER) በሽታ በሽታው የሰፈረበትን አካባቢ በረጅላ (Purslane) ተክል በሚገባ ማሸት ከዚያም የጥቁር አዝሙድ ዘይት 15 ቀናት መቀባት በቀን ሦስት ጊዜ አንድ አንድ ማንኪያ የጥቁር አዝሙድ ዘይት መጠጣት፡፡
32ኛ. ለሚያስነጥስ
ከባሕር ዛፍ የተጨመቀ ዘይት 40% ከጥቁር አዝሙድ ዘይት ጋር ደባልቆ በሁለቱም አፍንጫ በቀን ሦስት አራት ጊዜ ጠብታ ማድረግ ነው፡፡

መረጃውን ያገኘነው ከየኢትዮ ጤና ነው።
👉 ይህ ቻናል በኦን ላይን የህክምና ምክር አገልግሎት የሚሳጥ ቻናል ስለሆና ሳይብስክረይብ በማድረግ ተጣቃሚ እንድትሆኑ በማላት በአክብሮት እጠይቃችሁዋለሁ።
👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/Doctor_Engineer

Address

Vellore
632001

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Befeta Remane posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Befeta Remane:

Share