Akiya Media

Akiya Media Akiya Media አኪያ ሚዲያ welcome to our YouTube Channel Subscribe now and gat more benefits.

ለሰባት ዓመታት ያህል "በከፍተኛ ማጭበርበር እና በአራጣ ብድር ግፍ ተፈጸመብኝ" ሲል ታዋቂ ባለሀብቶችን ከሶ ሲከራከር የነበረው የኮስሞ ትሬዲንግ የቀድሞ ባለቤት አቶ ሃይለየሱስ መንግስቱ፣ ታ...
02/08/2025

ለሰባት ዓመታት ያህል "በከፍተኛ ማጭበርበር እና በአራጣ ብድር ግፍ ተፈጸመብኝ" ሲል ታዋቂ ባለሀብቶችን ከሶ ሲከራከር የነበረው የኮስሞ ትሬዲንግ የቀድሞ ባለቤት አቶ ሃይለየሱስ መንግስቱ፣ ታሪኩ ሙሉ በሙሉ ተገልብጦበት በከባድ የማጭበርበር ወንጀል ክስ እንደተመሰረተበት ተሰማ። ከሁሉም በላይ አስደንጋጭ የሆነው ደግሞ፣ በዚህ አዲስ ክስ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንም ተከሳሽ መሆኑ ነው።

🔵የሰባት ዓመቱ የክስ ድራማ እና የፍርድ ቤቱ ብይን

እንደሚታወሰው፣ አቶ ሃይለየሱስ መንግስቱ ባቀረቡት አቤቱታ መሰረት፣ በባለሀብቷ ወ/ሮ አዜብ ምህረትአብ፣ በይልማ ስጋ ቤት ባለቤት በአቶ ተመስገን ይልማ እና በሌሎች ላይ "በከባድ እምነት ማጉደልና አራጣ ብድር" ክስ ቀርቦ ጉዳያቸው ለሰባት ዓመታት ሲታይ ቆይቷል።

ነገር ግን፣ የፌደራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት ባለፈው ሚያዝያ ወር በሰጠው ብይን፣ ተከሳሾቹ ከቀረበባቸው ክስ በሙሉ በነጻ እንዲሰናበቱ ወስኗል። ፍርድ ቤቱ ለውሳኔው በምክንያትነት ከጠቀሳቸው ዋነኛ ነጥቦች አንዱ፣ የዐቃቤ ህግ ቁልፍ ምስክር የነበሩት አቶ ሃይለየሱስ እራሳቸው የሰጡት ምስክርነት ለተከሳሾቹ ያጋደለ መሆኑን መግለጹ ነበር። ይህም የህንጻው ሽያጭ ህጋዊና በስምምነት የተደረገ መሆኑን አረጋግጧል።

🔵 አዲሱ ክስ፡ ከከሳሽነት ወደ ተከሳሽነት

የቀድሞው ክስ በነጻ ስንብት ከተዘጋ ከጥቂት ወራት በኋላ፣ አሁን እነ ወ/ሮ አዜብ እና አቶ ተመስገን ከሳሽ፣ አቶ ሃይለየሱስ መንግስቱ ደግሞ ተከሳሽ ሆነው አዲስ የፍትሐብሔር ክስ መመስረታቸው ታውቋል።

🔴 የአዲሱ ክስ ይዘት፦ ክሱ እንደሚለው፣ አቶ ሃይለየሱስ ሐምሌ 14 ቀን 2017 ዓ.ም.፣ "እኔ ነኝ የኮስሞ ትሬዲንግ ማኔጂንግ ዳይሬክተር" በማለት ፖሊስን በማጭበርበር፣ በገርጂ አንበሳ ጋራዥ አቅራቢያ በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ በአደራ ተቀምጠው የነበሩ ሶስት የድርጅቱን ተሽከርካሪዎች ወስደው አድራሻቸውን አጥፍተዋል።

🔴 የፖሊስ ተጠያቂነት፦ ክሱ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከፌደራል ፖሊስ በአደራ የተቀበለውን ንብረት፣ የባለቤትነት ማረጋገጫ ሳያጣራ እና ያለአግባብ ለአቶ ሃይለየሱስ አሳልፎ በመስጠት የኃላፊነት ጉድለት ፈጽሟል ሲል ይከሳል።

🔵 የቀረበው የካሳ ጥያቄ

በዚህም መሰረት፣ ከሳሾቹ እነ አቶ ተመስገን ይልማ፣ ተከሳሽ አቶ ሃይለየሱስ መንግስቱ ለወሰዳቸው ሶስት መኪኖች የ15 ሚሊዮን ብር ካሳ እንዲከፍላቸውና ከዚህ ቀደም ያልመለሰውን አንድ መኪናም እንዲመልስ ጠይቀዋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንም በፈጸመው የኃላፊነት ጉድለት ለደረሰው ኪሳራ ተጠያቂ እንዲሆን በክሱ ላይ ተጠቅሷል።

ይህ አዲስ ክስ፣ ለዓመታት የዘለቀውን የህግ ውዝግብ ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ ሲሆን፣ የፍትህ ስርዓቱ በቀጣይ የሚሰጠው ውሳኔ በጉጉት ይጠበቃል።

ጉዳዩን ተከታትለን ተጨማሪ መረጃዎችን ይዘን እንመጣለን።

Akiya Media Meta Newsroom

ጉድ ጉድ በሚሊኒየሙ ፕሮግራም ላይ እንግዲህ ይህን ሰውዬ እያሰባቹ ፔንጤዎች     😃🤣🤣🤣Chat GPT ፕሮቴስታንትነትን የጀመረው ሰው ማን ነው? ማርቲን ሉተር (Martin Luther)
02/08/2025

ጉድ ጉድ በሚሊኒየሙ ፕሮግራም ላይ እንግዲህ ይህን ሰውዬ እያሰባቹ ፔንጤዎች 😃🤣🤣🤣
Chat GPT ፕሮቴስታንትነትን የጀመረው ሰው ማን ነው? ማርቲን ሉተር (Martin Luther)

02/08/2025
01/08/2025

ከልብህ ወደ ፈጣሪህ ስተጠይቀው መልሱ ፈጣን ነው ብቻ ልብህ ንፁህ ይሁን !!

መልካም ዜና! ☔️

ከሀምሌ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በሁሉም የሀይማኖት ተቋማት የምህላ ጸሎት ሲደረግ ከቆየ በኋላ፣ ባሉት ሶስት ቀናት ውስጥ በአብዛኛው አካባቢዎች በቂ ዝናብ እየዘነበ ነው።

በተለይም በራያ አላማጣ፣ ኮረም፣ ወልዲያ ዙሪያና ሌሎችም ቦታዎች ዛሬም ጭምር ጥሩ የሚባል ዝናብ መዝነቡ ተገልጿል።

የዘንድሮው የክረምት ወቅት መዘግየት ሰብሎች እንዳይደርቁና ድርቅ እንዳይከሰት ስጋት ፈጥሮ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ያለው የዝናብ መጠን አበረታች ነው።

01/08/2025

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን መሃል ከተማ ዛሬ ሐምሌ 25 በረዶ የቀላቀለ ከባድ ዝናብ ጥሏል

ጦርነት አይንደልን መረበትና ግን ይመለስ ፡፡ እንተዘይ ተመልሱ ግን ጦርነት ፈሪሕና መረበትና አይንህብን !ትርጉሙ ጦርነት አንፈልግም ነገር ግን የተያዘሁ ቦታዎቻችን ይመለሱ ፡፡ ባለመመለሳቸው...
01/08/2025

ጦርነት አይንደልን መረበትና ግን ይመለስ ፡፡ እንተዘይ ተመልሱ ግን ጦርነት ፈሪሕና መረበትና አይንህብን !

ትርጉሙ ጦርነት አንፈልግም ነገር ግን የተያዘሁ ቦታዎቻችን ይመለሱ ፡፡ ባለመመለሳቸው ጦርነት ፈርተን መሬቶቻችን አሳለፈን አንሰጥም ፡፡

01/08/2025

በሳውዲ አረቢያ በመዘናኛ ቦታ የደረሰ አሰደንጋጭ አደጋ ።

በሳውዲ አረቢያ በግሪን ማውንቴን መዘናኛ በደርዘን የሚቆጠሩ ተሳፋሪዎችን የጫነ የመዝናኛ ፓርክ ግልቢያ በአየር ላይ ለሁለት በመከፈሉ 23 ቆስለዋል።
360 ዲግሪ ተብሎ የሚጠራው ግልቢያ በመዝናናት ላይ በነበሩበት ወቅት ለሁለት በመቆረጡ እና ከቁሚዎ መሶሶ ጋር በመጋጨቱ አደጋው የተከሰተ ሲሆን የመዘናኛው ምሰሶ - በመካከላቸው የፍርሃት ቀስቃሽ ትዕይንቶች የሚያሳይ ነው።

በአደጋው ቢያንስ ሦስት ተሳፋሪዎች በጣም አሳሳቢ አደጋ እንደደረሰባቸው የተለያዩ የዜና ምንጮች ዘግበዋል ።

Akiya Media Meta Newsroom

የእለት አጀንዳችንን አታሳጣን!የእለት አጀንዳችን ጆሲ እና የልጁ እናት ነኝ ያለች Sosi Grimay ናቸው። ስለተባለው ነገር ከአንድ ወገን ብቻ ሰምቼ ምንም አልልም። እኔን በጣም የገረመኝ ...
01/08/2025

የእለት አጀንዳችንን አታሳጣን!
የእለት አጀንዳችን ጆሲ እና የልጁ እናት ነኝ ያለች Sosi Grimay ናቸው። ስለተባለው ነገር ከአንድ ወገን ብቻ ሰምቼ ምንም አልልም። እኔን በጣም የገረመኝ ነገር ግን ብዙ ነገሮቻችን ከኛ እና ከሽማግሌዎች ፥ ከቤተሰባችን እና በዙሪያችን ካሉ የተለያዩ ምርጥ ሰዎች እንዲሁም ከህግ በላይ ነገሩ ከብዶ ነው አደባባይ የሚወራው? ወይስ ያልገቡን ብዙ ነገሮች ስላሉ ነው?******
አንዳንዴ የደቦ ፍርድ እና የደቦ ሀዘኔታ ለተበዳይ ነኝ ለሚል ወገን የሚሰጠው እርካታ ምንድነው? የቤተሰብ ጉዳዮችን የኢትዮጵያ ህግ ከደቦ ፍርድ በላይ ነው? ወይስ ህጉ ለብዙ ተበዳይ ነኝ ለሚሉ ከለላ አይሰጥም? ሁሌም ባሰብኩት ቁጥር የቤተሰብ ጉዳዮች አደባባይ ወጥተው መሳቂያ እና መሳለቂያ ሲሆኑ እንጂ መፍትሄ ሲያገኙ አይቼ አላውቅም።*****
እናም ጎበዝ ለመፍረድ አንቸኩል። ፍትህ ለጆሲ ፍትህን ለሶሲ እያልን ጎራ ለይተን ከምንሟሟቅ ይልቅ እንዲህ ያሉ ጉዳዮች ወደፊት እየበዙ የአንድ ሰሞን ወሬ ብቻ በመሆን እንዳይቀሩ እንዲህ አይነት ጉዳዮችን በመናቅ እዛው በግል ችግራችሁን ፍቱ ካልሆነም በህግ ጨርሱ እያልን መድረክ ባለመስጠት ፊት በመንሳት ሰዎች በራሳቸው ችግሮችን መፍታት እንዲለምዱ እናድርግ። *******
አለበለዚያ እንዲህ አይነት ነገሮች እንደማስፈራሪያም ስምንም እንደማጥፊያ አንደኛ መንገድ በማድረግ ያልተገባ ታሪክ ውስጥ እኛም እነሱም እንዳንገባ ቢታሰብበት ብዪ እመክራለሁ። እኛ ስንት ከባድ ሀገራዊ ችግሮች እያሉብን በዚ መጠመዱ ብዙም ደስም አይልም። ፍትህ ለኛ በሆነው ባልሆነው አጀንዳ ለምንለፋ ህዝቦች። አሜን!
Akiya Media Meta Newsroom

31/07/2025

እጅግ ከምወዳት በውስጥ የተላከልኝ
የፀጋዬ ገ/መድሕን
የግጥሙ አርዕስት :- እንኳን ለዓመት ጉድ አበቃን

በነቢይ መኮንን አቅራቢነት

31/07/2025

ለገበው ብቻ ሼር ላይክ ❤🙏

30/07/2025

አዲስ አበባ እና ክረምቱ 25

በአስገዳጅ ሁኔታዎች ከሥራ ኃላፊነት መልቀቄን አስመልከቶ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ !እኔ ያሬድ ኃይለማርያም ከተመሰረተ አራት አመት ተኩል ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከ...
30/07/2025

በአስገዳጅ ሁኔታዎች ከሥራ ኃላፊነት መልቀቄን አስመልከቶ የተሰጠ
ጋዜጣዊ መግለጫ !

እኔ ያሬድ ኃይለማርያም ከተመሰረተ አራት አመት ተኩል ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከልን (Ethiopian Human Rights Defenders Center) በዋና ዳይሬከተርነት ሳገለግል ቆይቼ ባጋጠሙኝ አስገዳጅ ሁኔታዎች ከአገስት 1 ቀን 2025 (ሐምሌ 25 2017) ጀምሮ ከሃላፊነቴ እና ከድርጅቱ ለመልቀቅ መገደዴን ለማሳወቅ እወዳለሁ፡፡

ይህ ድርጅት ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲቋቋምና በሌሎች አፍሪካ አገሮች ከሚገኙ አቻ ድርጅቶች ጎን ቆሞ ለሰብአዊ መብት ተሟጋቶች መብት መከበርና አቅማቸውንም ለማጎልበት በርካታ ሥራዎችን እንዲሰራ ምሪት በመስጠትና በአጭር ጊዜም ውስጥ ድርጅቱ በአገር ውስጥና ከአገር ውጭም እውቅና እና ተቀባይነት እንዲያገኝ ከፍተኛ ጥረት ሳደርግ ቆይቻለሁ፡፡

ድርጅቱ ከተመሰረተ አጭር እድሜ ያለው ቢሆንም ሲያከናውን የቆያቸው ሥራዎች እና አገሪቱ ውስጥ ለሚፈጽሙ የመብት ጥሰቶች፤ በተለይም በጋዜጠኞች፣ በሲቪል ማህበረሰብ አባላት እና በመብት ተሟጋቾ ላይ የሚፈጸሙ የመበት ጥሰቶችን በማጋለጥና መብታቸው እንዲከበርበአደባባይ በመሟገት ግንባር ቀደም ተቋም ሆኖ እንዲቀጥል ከድርጅቱ ጠንካራ ሠራተኞችና የቦርድ አባላት ጋርበመሆን ቁልፍ ሚና ስጫወት ቆይቻለሁ፡፡

ይሁንና ከአንድ አመት ወዲህ በአገር ውስጥና ከአገር ውጭ በሚገኙ ሚዲያዎች ላይ እየቀረብኩ አገሪቱ ውስጥ ስላለው የሰብአዊ መብት ጥሰቶች የምሰጠቸው መገልጫዎችና ማብራሪያዎች፣ በማህበረ ድህረ ገጾች ላይ ዜጎችን ስለ መብታቸው እንዲያውቁና በአገሪቱ ውስጥ ስላለው የሰብአዊ መብቶች አያያዝ በማስመልከት የማካፍላቸው ሃሳቦችና የምሰነዝራቸው የሰሉ ትችቶች በአገዛዝ ሥርአቱ ዘንድ በጥሩ ሁኔታ እየታ ባለመምጣታቸው የተነሳ በተለያዩ አቅጣጫዎች የተለያዩ አይነት ጫናዎችን ሳስተናግድ ቆይቻለሁ፡፡

የተለያዩ ዛቻዎች፣ ማስፈራሪያዎችና ትንኮሳዎችን በጸጥታ አካላት በኩል ሲፈጸሙ እንዲሁም በተንቀሳቃሽ ስልኮቼ ያልተለመዱ ጥሪዎችን ሳስተናግድ ያለውን ግልፅ ስጋት ችላ በማለት በሥራዬ ላይ አተኩሬ ቆይቻለሁ፡፡ ሆኖም በዚህ ሁኔታ ውስጥ በነጻነት ለመወጣትም ሆነ የተቀበልኩትን የሥራ ሃላፊነት በብቃት ለማከናወን የማልችልበት ደረጃ ላይ መድረሴን ስላረጋገጥኩ በተጓዳኝም በሥራ ጫና ብዛት ችላ ያልኳቸው የግል የጤና ጉዳዮችም ስለነበሩ እነዚህን ምክንያቶች በመጥቀስ ከወራቶች በፊት ለድርጅቱ ቦርድ የመልቀቂያ ጥያቄዬ አቅርቤ በምትኬ ሰው እንዲፈልጉ አሳውቄያለሁ፡፡

ቦርዱም ጥያቄዬን ተቀብሎ እስከ ዲሴምበር(ታህሳስ) ወር መጨረሻ 2025 ድረስ እንድቆይና አመራሩን የሚረከቡ ሠራተኞችን እያዘጋጀሁና እያሰለጠንኩ እንድቆይ ተስማምተን ነበር፡፡ ይሁንና ከላይ በገለጽኳቸው ምከንያቶች ከድርጅቱ ጋር የምቆይበት ጊዜ ከወራቶች ወደ ቀናት ለያጥር ችሏል፡፡ እኔም ሁኔታዎችን ከግምት በማስገባት ከዛሬ ሁለት ሳምንት በፊት ለድርጅቱ ሌላ የመልቀቂያ ደብዳቤ ለማስገባት ተገድጃለሁ፡፡

ይሁንና እኔ ለድርጅቱ ቦርድ የመልቀቂያ ደብዳቤ ባስገባሁ በሳምንቱ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን መሥሪያ ቤት ሐምሌ 14፣ 2017 በአንድ ከፍተኛ ሃላፊው በኩል ለሥራ ባልደረቦቼ ስልክ በመደወል ወደ ቢሯቸው ከጠሩ በኋላ እኔን በተመለከተ የተለያዩ ጥያቄዎችን ካነሱ በኋላ በግልጽ የድርጅቱ ቦርድ በአስቸኳይተሰብስቦ እኔን ከምመራው ድርጅት ሃላፊነት ጋር ተያይዞ ያላቸውን አቋምና ውሳኔን በደብዳቤ ለባለሥልጣን መሥሪያቤቱ በጽሑፍ እንዲያሳውቅ የአንድ ሳምንት ጊዜ ሰጥቷል፡፡ ምንም እንኳን እኔ ቀደም ብዮ በራሴ ፍቃድ ሁኔታዎችን ከመረመርኩ በኋላ ከሥራ የመልቀቂያ ደብዳቤ ያስገባሁ ቢሆንም የባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ግን ፍጹም አግባብነት በሌለው መልኩ በድርጅቱ የውስጥ አሰራር ጣልቃ የገባ ተግባር ፈጽሟል፡፡

የዚህም ጋዜጣዊ መግለጫ ዋና አላማዎች፤

1ኛ/ ይህ መግለጫ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ በማናቸውም ሚዲያ ልቀርብና ሃሳቤንም ላካፍል የምችለው እራሴን በመወከልና እንደ አንድ የሰብአዊ መብት ባለሙያ እንጂ እስከ አሁን ስመራ የቆየሁትንም ሆነ የትኛውንም ድርጅት ወክዬ እንዳልሆነ ለማሳወቅ ነው፡፡ በማህበራዊ ድህረ ገጾችም ከዚህ በኋላ የማካፍላቸው መረጃዎች እና የማስተላልፋቸው መልዕከቶች እኔን ብቻ የሚወከሉ እና እንደ አንድ በግል ለሰብአዊ መብቶች መከበር እንደሚቆረቆር ተሟጋች መሆኑን ለሁሉም የሚዲያ ባለሙያዎች፤ በተለይም በየጊዜው በመድረካቸው ሃሳቤን እንዳቀርብ ለሚያስተናግዱኝ መገናኛ ብዘሃን ለማሳወቅ ነው::

2ኛ/ ሁለተኛውና እጅግ ትልቅ ትኩረት እንዲሰጠው የምፈልገው ጉዳይ በተወሰነ ደረጃ መሻሻሎች ታይተወብት የነበረው የአገራችን የሲቪከ ምህዳር ዳግም እየተዘጋና ከፍተኛ አደጋዎችም ከፊቱ የተደቀኑ መሆኑን እና ሚዲያዎችም ለጉዳዩ በቂ ትኩረት ሰጥተው መንግስት በሲቪል ማህበራት ላይ እና በምህዳሩ ላይ እያሳደረ ያለውን ዘርፈ ብዙ ጫና ትኩረት ሰጥታቸው እውነታውን ለህዝብና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ማሳወቃችውን ተግታችሁ እንድትቀጥሉ ለማሳሰብ ነው፡፡ መንግስት የሲቪክ ምህዳሩን መልሶ በከፋ ጫና ውስጥ ለማቆየት እያረቀቀ ያለውን እጅግ አደገኛ የህግ ማሻሻያ ጨምሮ በሲቪል ማህበራት ላይ ውስጥ ለውስጥ እያደረሰ ላለው ጫና ከላይ የጠቀስኩት በእኔ እና በሌሎች አገር ጥለው እንዲሰደዱ በተደረጉት የኢሰመጉ የቀድሞ ዋና ዳይሬከተር አቶ ዳን ይርጋ ሌሎችም ተቋማት ጉዳይ በቂ ማሳያዎች ናቸው፡፡

3ኛ/ ላለፉት ስድስት ወራት ያህል በማህበራዊ ድህረ ገጾች በተለይም በፌስቡክና በቴሌግራም ዘወትር ቅዳሜ “መልዕከተ ቅዳሜ" በሚል ከአንድ አመት በላይ ያለምንም ማሰለስ ማህበረሰባችንን ስለ መብቱ እንዲያውቅና በአንዳንድ ወሳኝ በሆኑ የመብት ነክ ጉዳዮች ያለው ግንዛቤ እንዲሰፋ ውይይት አጫሪ የሆኑ አጫጭር መጣጥፎችን ከማካፈል ተቆጥቤ ቆይቻለሁ፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት ከላይ በጠቀስኳቸው ምክንያቶች ስመራው በቆየሁት ድርጅት ላይ ለደርሱ የሚችሉ ጫናዎችን ለመቀነስ በሚል ነበር፡፡ እኔ ወደ ማህበራዊ ሚዲያ በቋሚነት በመምጣት ሰፋፉና ጥልቅ ቁምነገሮች ላይ በማተኮር የግል ምልከታዬን ለማካፈል የወሰንኩት በአገሪቱ ውስጥ ያለው የሚዲያ ምህዳር እጅግ እየጠበበና በተለይም የሰላ ትችት በመሰንዘርየሚታወቁ የህትመት ጋዜጣዎችና መጽሄቶች በመንግስት በደረሰባቸው ከፍተኛ ጫና እና ወከባ ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚችል ደረጃ በመቋረጣቸው ማህበረሰባችን ትምህርት ሊያገኝባቸው የሚችሉ መድረኮች ጠበዋል ከሚል መነሻ ነው:: በመሆኑም ከዚህ ጋዜጣዊ መግለጫ በኋላ በቋሚነት በሙሉም የማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች ላይ በሰብአዊ መብት እና ተያያዥ አገራዊ ጉዳዮች ላይ በቋሚነት ትንታኔዎችን እና የግል ምልከታዎቼን የማካፍል መሆኑን እየገለጽኩ የተለመደው መረጃዎችን የማጋራት ትብብራችሁ እንዳይለየኝ በአክብሮት እጠይቃለሁ፡፡

በዚህ ጉዳይ ላይ ተጨማሪ መረጃ ወይም ማብራሪያ ለምትፈልጉ የሚዲያ ባለሙያዎች በማናቸውም ጊዜ በቀጥታ ልታገኙን እንደምትችሉ እየገለጽኩ እስከ ዛሬ መድረኮቻችሁን ከፍት በማድረኛ ለሰብአዊ መብት ጉዳዮች ከፍተኛ ትኩረትና ቅድሚያ በመስጠት በቃለ ምልልስ፣ ጽሁፎቼን በማጋራት ወይም በማናቸውም መልኩ መድረክላመቻቻችሁልኝ ጋዜጠኞችና የሚዲያ ባለሙያዎች ሁሉ ምስጋናዮ የላቀ ነው፡፡

አሁንም ለተገፉ እና መብታቸው ለተጣሰባቸው ሰዎች ሁሉ ድምጽ የመሆን ቁርጠኝነቱ ከእኔ ጋር ስለሆነ በማናቸው ጊዜ በሰብአዊ መብቶች ጉዳይ ለምታደርጉት ጥረት እና ለምትፈልጉት መረጃና ማብራሪያ ሁሉ የበኩሌን ቀና ትብብርና ተሳትፎ ለማድረግ ዝግጁ መሆኔን በታላቅ ትህትና እገልጻለሁ፡፡

ያሬድ ሃይለማርያም
Yared Hailemariam
በሰብአዊ መብቶች አማካሪና ተመራማሪ

Akiya Media Meta Newsroom

Address


20036

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Akiya Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share