Benishangul Gumuz Media

Benishangul Gumuz Media Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Benishangul Gumuz Media, Media/News Company, Assa.

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሚዲያ የክልሉን ህዝብና መንግስት የመረጃ ፍላጎት በጋዜጠኝነት መርህ ላይ የተመሰረቱ አስተማሪ፣አዝናኝ፣ አሳዋቂ ዜናዎች፣ ፕሮግራሞች እንዲሁም ዶክመንተሪዎች ሰርቶ በማቅረብ በኤሌክትሮኒከስ ሚዲያ እና በማህበራዊ ሚዲያ የአየር ሰዓት ሽፋን ለማዋል የተቋቋመ ድርጅት ነዉ።

የካማሺ ዞን ከፍተኛ አመራሮች የአርሶ አደሩን የ2017/2018 የምርት ዘመን የስራ እንቅስቃሴ እየጎበኙ ነው።አመራሮቹ በደምቤ ወረዳ ተገኝተው የ2017/18 የምርት ዘመን  የአርሶ አደር እር...
22/07/2025

የካማሺ ዞን ከፍተኛ አመራሮች የአርሶ አደሩን የ2017/2018 የምርት ዘመን የስራ እንቅስቃሴ እየጎበኙ ነው።

አመራሮቹ በደምቤ ወረዳ ተገኝተው የ2017/18 የምርት ዘመን የአርሶ አደር እርሻ እንቅስቃሴና ትምህርት ቤቶች የውስጥ ገቢያቸውን ለማሳደግ እየተሰራ ያለውን የልማት ስራዎች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

የካማሺ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብጅጋ ፃፊዮ በጉብኝቱ ወቅት እንደገለፁት ማህበረሰቡ በሙሉ አቅሙ ወደ ልማት በማስገባት የኢኮኖሚ አቅሙን ለማጎልበት በሁሉም ወረዳዎች ስትራቴጂካዊ ልማታችን ንቅናቄ መድረኮች መካሄዳቸውን አስታውሰዋል።

በዚህም ህዝቡ የልማት ንቅናቄውን ተቀብሎ ወደ ስራ መግባቱን ማሳያ የሚሆኑ በኩታ ገጠም፣ በጓሮ እርሻና በተረጅነት ቅነሳና በሌሎች ዘርፎች አበርታች ስራዎች ተሰርተዋል ብለዋል።

በተለይ ትምህርት ቤቶች የውስጥ ገቢያቸውን በማሳደግ ጥራት ያለው ትምህርትን ተደራሽ ለማድረግ የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው ብለዋል።

በአጠቃላይ የ2017/18 የምርት ዘመን እየተሰራ ያለው የመኸር እርሻ እንቅስቃሴ ከባለፈው አመት ጋር ሲነፃፀር የተሻለና ማህበረሰቡ በሚገባ ፊቱን ወደ ልማት ያዞረበት አመት መሆኑን ተናግረዋል።

የደምቤ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ወንድሙ ቦቦ በበኩላቸው በሁሉም ትምህርት ቤቶች እየተሰራ ያለውን የእርሻ ስራዎች አጠናክሮ በማስቀጠል በቀጣይ የትምህርት ዘመን የተማሪዎችን የምገባ ፕሮግራም ለማስጀመር ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በመጨረሻም የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መረሃ ግብር ማካሄዳቸውን የዞኑ ኮሙኒኬሽን መምሪያ መረጃ አመላክቷል።

افتتاح مكتب للشؤون الإسلامية في كرمك بميزانية تجاوزت 1.6 مليون برأسوسا – افتُتح في قضاء كرمك بمنطقة أسوسا مكتب جديد للشؤ...
22/07/2025

افتتاح مكتب للشؤون الإسلامية في كرمك بميزانية تجاوزت 1.6 مليون بر
أسوسا –
افتُتح في قضاء كرمك بمنطقة أسوسا مكتب جديد للشؤون الإسلامية، تم بناؤه بتمويل من فاعل خير، وبتكلفة تجاوزت 1.6 مليون بر.
وخلال حفل الافتتاح، أوضح رئيس مجلس الشؤون الإسلامية الإقليمي في بني شنقول غوموز، الحاج إبراهيم سراج، أن المكتب يُعد تجربة يُحتذى بها في مجال العمل الخيري والدعوي، مشيرًا إلى أن المجلس الأعلى يعمل على تعزيز الوحدة والتضامن بين المسلمين في المنطقة.
من جانبه، أكد كبير الإداريين في قضاء كرمك، آتو موسى عبد الرحيم، أن تنفيذ المشاريع الخدمية في القضاء يتم بمشاركة فاعلة من المجتمع، مثمنًا الجهود التطوعية المبذولة في هذا الإطار. كما وجه الشكر للشاب الذي ساهم في بناء المكتب وتجاوَز نطاق الأعمال الموكلة إليه.
وفي تصريح له، أكد الشاب عبد الباسط نسر، الذي تكفل ببناء المكتب، أن تكلفة المشروع بلغت أكثر من 1.6 مليون بر، مشددًا على أهمية دعم المبادرات المجتمعية لخدمة القضايا الدينية والاجتماعية.
تقرير/ ماجده خليفه عبدالرحمن

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያስገነባቸው አዳዲስ የአውሮፕላን ጥገና፣ የእድሳት ማዕከልና ወርክሾፖች አገልግሎት አሰጣጡን የሚያሳድጉ ናቸውየኢትዮጵያ አየር መንገድ ያስገነባቸው አዳዲስ የአውሮፕላን...
22/07/2025

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያስገነባቸው አዳዲስ የአውሮፕላን ጥገና፣ የእድሳት ማዕከልና ወርክሾፖች አገልግሎት አሰጣጡን የሚያሳድጉ ናቸው

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያስገነባቸው አዳዲስ የአውሮፕላን ጥገና፣ የእድሳት ማዕከልና ወርክሾፖች አገልግሎት አሰጣጡን የሚያሳድጉ መሆናቸውን የኢፌዲሪ አየር ሀይል ዋና አዛዥ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቦርድ ሊቀመንበር ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ ገለጹ።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ተጨማሪ አዳዲስ የአውሮፕላን ጥገና፣ የእድሳት ማዕከል እንዲሁም ወርክሾፖችን ዛሬ አስመርቋል።

በምረቃ መርሃ ግብሩ የኢፌዲሪ አየር ሀይል ዋና አዛዥ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቦርድ ሊቀመንበር ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰውና የአየር መንገዱ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።

ማዕከላቱ የአየር መንገዱ እና ከተለያዩ ሀገራት የሚመጡ አውሮፕላኖች ጥገና እና እድሳት የሚካሄድባቸው መሆኑ ተገልጿል።

የተገነቡት የአውሮፕላን ክፍሎች የማዕከላዊ መጋዘን እና የአውሮፕላን ክፍሎች ወርክሾፕ የተለያዩ የአውሮፕላን ክፍሎች በቴክኖሎጂ በታገዘ አሰራር ተደራጅተው የሚቀመጡበት መሆኑ ተገልጿል።

በዛሬው እለት የተመረቁት መሰረተ ልማቶች ከአየር መንገዱ የራእይ 2035 ግቦች ውስጥ አንዱ መሆኑም ተመልክቷል።

የኢፌዲሪ አየር ሀይል ዋና አዛዥ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቦርድ ሊቀመንበር ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ ማእከላቱ የአየር መንገዱን የእድገት ከፍታ የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል።

እንዲሁም አየር መንገዱ ያለውን የረጅም ጊዜ ራእይ የሚያሳይ መሆኑን ጠቅሰው፤ መሰረተ ልማቱ ቀጣይነት ላለው የእድገት ጉዞ ወሳኝ መሆኑንም ተናግረዋል።

በዛሬው እለት የተመረቁ ማእከላትም በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርጉ መሆናቸውን አመላክተዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው በበኩላቸው፥ ማእከላቱ የአየር መንገዱን አገልግሎት አሰጣጥ የሚያሳድጉ ናቸው ብለዋል።

ግንባታቸውን ለማጠናቀቅ ሁለት አመት መፍጀቱን ገልጸው፤ ተጨማሪ አቅም በመፍጠር ገቢን ለማሳደግም ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቁመዋል።

እንዲሁም የማእከላዊ መጋዘኑም የእድሳት እና ጥገና ስራውን የሚያቀላጥፍ መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀጣይ አየር መንገዱ የእድገት ጉዞውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ማመልከታቸውን ኢዜአ ዘግቧል ።

በካማሺ ዞን ካማሺ ወረዳ 31 ለሚሆኑ አቅመ ደካሞች የሶላር ሃይል ድጋፍ ተደረገላቸው።የሶላር ሃይል ድጋፉ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውሃና ኢነርጅ ሀብት ልማት ቢሮ የተገኘው ሲሆን ከ3 መቶ ሺ...
22/07/2025

በካማሺ ዞን ካማሺ ወረዳ 31 ለሚሆኑ አቅመ ደካሞች የሶላር ሃይል ድጋፍ ተደረገላቸው።

የሶላር ሃይል ድጋፉ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውሃና ኢነርጅ ሀብት ልማት ቢሮ የተገኘው ሲሆን ከ3 መቶ ሺ ብር በላይ የሚገመት ወጪ እንደወጣበት የካማሺ ዞን ውሃና ማዕድን ኢነርጂ ሀብት ልማት መምሪያ ሃላፊ ወይዘሮ ሙሉነሽ ዘውዴ ገልፀዋል።

መንግስት የህዝቡን የመሰረተ ልማት ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ ለመመለስ በሂደት ላይ መሆኑን አንዱ ማሳያ ነው ያሉት መምሪያ ሃላፊዋ ቀሪ የመሰረተ ልማት አውታሮችን ለማህበረሰቡ ተደራሽ ለማድረግ የተገኘውን ሰላም ዘለቄታዊ እንዲኖረው ማድረግ ከሁሉም ይጠበቃል ብለዋል።

ድጋፉ ለአቅመ ደካሞች ለአካል ጉዳተኞች በዛሬው ዕለት ርክክብ መደረጉን የካማሸ ዞን ኮሙኒኬሽን መምሪያ ዘግቧል።

የክልሉ ፍትህ ትራንስፎርሜሽንና የፍርድ ቤቶች (የዳኝነት ዘርፍ የለውጥ) ፍኖተ ካርታ ዓመታዊ ዕቅድ አፈጻጻም ግምገማ ተካሄደ፡፡የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት የፍትህ ትራንስፎርሜሽንና የ...
22/07/2025

የክልሉ ፍትህ ትራንስፎርሜሽንና የፍርድ ቤቶች (የዳኝነት ዘርፍ የለውጥ) ፍኖተ ካርታ ዓመታዊ ዕቅድ አፈጻጻም ግምገማ ተካሄደ፡፡

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት የፍትህ ትራንስፎርሜሽንና የፍርድ ቤቶች ፍኖተ-ክርታ የ2017 ዓ.ም ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ተካሂዷል፡፡

ሪፖርቱ በፍርድቤቶች ፍኖተ-ካርታ በኩል በበጀት ዓመቱ የፍርድ ውሳኔ ጥራትና ቅልጥፍና ጨምሯል፤ የአገልግሎት አሰጣጥ መሻሻል አሳይቷል፤የባህላዊ ፍርድ ቤት በክልል ደረጃና ማኦ ኮሞ ልዩ ወረዳን ጨምሮ በሶስቱም ዞኖች በተመረጡ ወረዳዎች ተቋቁሟል፡፡

የውሳኔ ጥራት ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በከፍተኛ ፍርድቤቶች በ10% እና በወረዳ ፍርድ ቤቶች 7% ጨምሯል፡፡

በአጠቃላይም በዘንድሮው ዓመት ከቀረቡ መዛግብት ወስጥ 93 % ውሳኔ አግኝተዋል፡፡

ለዚህም ተጠቃሽ ምክንያቶች የችሎት ተደራሽነት፤በቴክኖሎጅ ሥራ መጀመር፤ ተንቀሳቃሽ ፋይሎችን፤ ወደሶፍት ኮፒ መቀየር፣ለዳኞችና ሠራተኞች የአቅም ግንባታ ሥልጠና መስጠት፤ ጠቃሚ አዋጆች ለምሳሌ የዳኝነት አገልግሎት ታሪፍ አዋጆች መውጣት ወዘተ.ተጠቃሽ ናቸው ተብሏል፡፡

በፍትህ ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ በውልና ማስረጃ እየተሠራ ያለው ሥራ፤የንቃተ-ሕግ ትምህርትን በመገናኛ ብዙሃን በስፋት ማድረስ መቻሉ፤የሙግት መፍቻ አማራጮች መጨመር፤የጠበቆች ማኅበርና አሶሳ ዩንቨርስቲ የሚሰጡት ነጻ የህግ ድጋፍ አገልግሎት መጨመር፣ ለዐቃብያነ ሕግ፤ ለፖሊስ አባላትና ሌሎች አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መሠጠቱ፤ በዘርፉ ባለቤቶች ፍትህ ቢሮ፣ በማረሚያቤቶችና ፖሊስ ኮሚሽን ያለው ትኩረት መጨመርና ጠንካራ ቅንጅታዊ አሠራር መዳበር፤ የክልሉ ም/ቤት ተከታታይነት ያለው ክትትል ማድረግ፤ ተጠቃሾች እንደሆኑ ታይቷል፡፡

በሁለቱም በኩል የተሻለ አፈጻጻም ያለ ቢሆንም ከዚህም በላይ ውጤት ማምጣት እንዳይቻል በቴክኖሎጂ ያለመደገፍ ችግር ለዚህም በጀትና የቴክንሎጂ መሳሪያዎቹ በጣም ውድ መሆናቸው በተግዳሮት የተነሱ ናቸው፡፡

ውይይቱን የመሩት የክልሉ ም/ቤት አፈጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ የግምገማ ውይይቱን ሲያጠቃልሉ የተሰሩ ሥራዎች አበረታች መሆናቸውን በቅርቡ በፌደራል ደረጃ ሲገመገም ክልሉ በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ዓይተናል፤ ከባለፉት ጊዜያት አንጻር በርካታ አፈጻጸሞች ተመዝግበዋል፤ ይሁን እንጂ በቴክኖሎጅ በኩል በማቴሪያልም ይሁን አፕልኬሽን ማበልፀግ ረገድ ብዙ መሥራት የሚጠይቅ በመሆኑ ሁሉም አካል በትኩረት መሥራት ይገባዋል ብለዋል፡፡

ለዚህም ከመንግስት ብቻ ሳይሆን ግብረሰናይ ድርጅቶችና ልማታዊ ባለሀብቱ ሊደግፍ የሚችልበት ሁኔታ እንዲመቻች፤ በጀት ላይም ያለን ሀብት ውስን ቢሆንም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ምክክር የሚደረግ ቢሆንም መጠበቅ ሳያስፈልግ በተቻለ መጠን ያለንን አብቃቅተን መሥራት ይኖርብናል ሲሉ አሳስበዋል፡፡

በግምገማ መድረኩ የክልሉ ም/ቤት አፈጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ፤ምክትል አፈጉባኤ የተከበሩ አቶ መለሰ ኪዊ፤ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ሰንበታ ቀጀላ፤ የፍትህ ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ መሀመድ ሀሚድ፤ የፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ኮሚሽነር አምሳሉ ኢረና የማረሚያቤቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር መንግስቱ ቴሶ እና ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት መካሄዱን የክልሉ ምክር ቤት መረጃ አመላክቷል።

‎በአሶሳ ዞን በኩርሙክ ወረዳ በአንድ  የበጎ አድራጊ ግለሰብ ከ1ነጥብ 6 ሚሊያን ብር በለይ  የተገነባው የወረደው የእስልምና ጉዳዮች ጽ/ቤት ተመረቀ።‎በምረቃ መረኃ ግብሩ  የቤኒሻንጉል ጉሙ...
22/07/2025

‎በአሶሳ ዞን በኩርሙክ ወረዳ በአንድ የበጎ አድራጊ ግለሰብ ከ1ነጥብ 6 ሚሊያን ብር በለይ የተገነባው የወረደው የእስልምና ጉዳዮች ጽ/ቤት ተመረቀ።

‎በምረቃ መረኃ ግብሩ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሃጅ ኢብራሂም ሲራጅ እንዳሉት በአሶሳ ዞን በኩርሙክ ወረዳ በአንድ በጎ አድረጊ ግለሰብ የተገነባው የወረዳው እስልምና ጉዳዮች ጽ/ቤት ለሌሎችም ተሞክሮ ይሆናልም ብለዋል።

በክልሉ የሙስሊሙን አንድነት እና አብሮነትን አጠናክሮ ለማስቀጠል ጠቅላይ ምክር ቤቱ ትኩረት ሰጥቶ እያሰራ እንዳሚገኝ ጠቅሰዋል።

‎የኩርሙክ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙሣ አብዱራሂም በበኩላቸው በወረዳው በማህበረሰቡ ተሳትፎ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል ።

በወረዳው የእስልምና ጉዳዮች ጽ/ ቤት ግንባታ ውጪ ሸፍኖ ለሰራው ወጣትም ምስጋና አቅርበዋል ።

ጽ/ቤቱን የገነባው ወጣት አብዱልባስጥ ነስር እንዳሉት ደግሞ ለጽ/ቤት ግንባታ ከ1 ነጥብ6 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ እንደወጣባትም ተናግረዋል።

‎ሪፖርተራችን ቲጃኒ አደም እንደዘገበው።

‎በ2018 በጀት ዓመት ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታና ለአደረጃጀቶች መጠናከር ትኩረት እንደሚደረግ የቤኒሻንጉል  ጉሙዝ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢሳቅ አብዱ...
22/07/2025


በ2018 በጀት ዓመት ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታና ለአደረጃጀቶች መጠናከር ትኩረት እንደሚደረግ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢሳቅ አብዱልቃድር ገለፁ።

‎ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የቆየው የ2017 በጀት ዓመት ዓመታዊ ማጠቃለያ የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ እና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ መናበብ መድረክ ተጠናቋል።

‎በማጠቃለያ መድረኩ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢሳቅ አብዱልቃድር እንዳሉት የህዝቦችን አንድነትና አብሮነትን የሚሸረሽሩ አፍራሽ ኃይሎችን ሴራ ማክሸፍና ገዥ ትራክቶችን አጉልቶ ለማወጣት ይሰራል ብለዋል።

‎በተለይ ደግሞ በ2018 በጀት ዓመት ብልፅግና ፓርቲ ጠንካራ ሀገረ መንግስት በመገንባት እና አደረጃጀቱን በማጠንከር በህዝብ ዘንድ ቅቡልነት እንዲኖረው በትኩረት እንደሚሰራም አሳውቀዋል።

‎ለተያዘው ዕቅድ ስኬታማነት የብልፅግና ፓርቲ አባላትና አመራሮቹ በመንግስትና በፓርቲ የሚከናወኑትን የልማት ስራዎች ተቀዳሚ ተግባር አድርገው መሰራት እንዳለባቸው ኃላፊው አሳስበዋል።

‎ ብልፅግና ፓርቲ ለማከናወን ከአቀዳቸው ዕቅዶች መካከል 7ተኛውን ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ሰላማዊ ፣ ዲሞክራሲያዊ እና ፍትሃዊ እንዲሆን እንደሚሰራም አቶ ኢሳቅ አስታውቀዋል።

‎በአዲሱ በጀት በኢኮኖሚያዊ ፣በማህበራዊ እንዲሁም በፓለቲካዊ ዘርፍ የሚከናወኑ ተግባራት ሁሉ የማንሰራራት ዓመት እንድሆን ይሰራልም ብለዋል።

‎የክልሉ ህብረተሰብ ከተረጂነት ለማላቀቅም ምርትና ምርታማነት ማሳደግ፣ የኑሮ ወደድነት መቀነስ እንዲሁም የበጎ አድራጎት ስራዎች እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ በትኩረት እንደሚሰራም ተናግረዋል።

‎የብልፅግና ፓርቲ አመራሮች በበኩላቸው በህብረተሰቡ ዘንድ የሚነሱ የመልማት ጥያቄዎችን ምላሽ እንዲያገኙ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንዲመጡ ገልፀዋል።

‎በማጠቃለያ መድረኩ በ2017 በጀት ዓመት በብልፅግና ፓርቲ የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ለፓርቲ ጽህፈት ቤቶች እንዲሁም አመራሮች የዕውቅና ምስጋና መርሃ ግብር ተካሂዷል።

‎ ሪፖርተራችን ታከለ ፈረደ እንደዘገበው።

Tha alqidáárá thá Kúrmúkú almáktabá mbá álmajilisú mbá áshúkqúlá áddiiná álqisilaamú mbá gióólá bóñgórá sqúllá sha Abdul...
22/07/2025

Tha alqidáárá thá Kúrmúkú almáktabá mbá álmajilisú mbá áshúkqúlá áddiiná álqisilaamú mbá gióólá bóñgórá sqúllá sha Abdulbásitq Násir áhórólá alú ma thikquga ágúrá álmajilisú mbá Ikqilíím Benishangúl Gumúz na Háj Ibrahím Mahámmad Siráj.

Alyóóm;15/11/2017HI (BGM) Asósa: Shá álé thíkqa aañá mbá hululá are álé roothuqi tha ashúkqúlá áddiinú álú tha alqidáárá thá Kúrmúkú almáktabá mbá álmajilisú mbá áshúkqúlá áddiiná álqisilaamú mbá gióólá bóñgórá sqúllá sha Abdulbásitq Násir áhórólá alú ma thikquga ágúrá álmajilisú mbá Ikqilíím Benishangúl Gumúz na Háj Ibrahím Mahámmad Siráj.

Háj Ibrahím Mahámmad Siráj mín aañá zííné, almáktabá mbá gióólá á Abdulbásitq Násir mbá ma alkátib tha almáktabáloyú sha áné maa mbá náfaqaláqi tháñ ashúkqúlá kqedqéqí ziizí ma dqukqúnúñ tha ashúkqúlá áddiinúyú ma kqaakqáb ñinéñ roothóne.

Maabá ma agúrálo tha roothá kqedqeyú almusilimííni kqíllíñ aañá holi máré magú bikqa iyú kqusqua tha áddiinú gíñ walá adígá áddiin thaarthéqí walá zííqí ñinéñ ásqárónáne hu.

Tha alqidáárá thá Kúrmúkú maabá ma agúr na abbá Múúsa Abdurrahím shambá roothóné, míthili alqidáárá máre boñgórí dqafaruqí zííqígú aañá shááraki máré tha ashúkqúlá álheerúyú ñinéñ roothóne.

Tha alqidáárá máreyú maabí shimbilú u boñgórí shákqali ashúkqúlá álheerú thá thábá damua bánáqá álmasájid thá aañá dqafaruqíyúgú ñinéñ pqúlíñónneqi.

Háj Hamdanníl Minálla mbá ma agúr tha almáktabá álmajilisúyú mbá tha alqidáárá thá Kúrmúkú shambá roothóné, thá Kúrmuk maré zííqí aañá hí máré tha asháqábú shá máré ábadqiiña ashúkqúlá addiinúqi ma pqishí ñinéñ roothóne.

Thambálo alú ñine pqishiga áñ sha maré squló añ sha álé shááraka márthé albarnámíjá alu ahoró u áné thikquolá márthéqí ashán shúgó álé shákqala ashúkqúlá álheerú ñinéñ ádqafarónáne thá guuráloyú ma alwasía.

Boñgórá mbá gió almáktabá álmajilisú na Abdulbásitq Násir mín aañá zííné, almáktabáló mbá gió máré thá fuudá tímma 1.6 maliún bír thá shooréqí shá áné maa mbá wássalí tha ashúkqúlá kqedqe alú alkitáábá dqafaruqí jáházá máré ñinéñ roothóne.

Maabí shimbilú mbágú thikquqí thá aañá dqafaruqíyú shimbilá gídí máré ashán Álla ñinéñ dááne márthéqí ma náfáqá máréqi tháñ tha ashúkqúlá álheerú álú mbá máre thá Alló sha thíkqí máré álú máré shákqala ashúkqúlá álheerú tháñ ñinéñ kqalóóne.

Ádam Hisén ñinéñ muusqóne hu.

በክረምቱ አልፎ አልፎ የሚኖር ከባድ ዝናብ ሊያስከትል ከሚችለው ቅጽበታዊ ጎርፍ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል-የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩትአዲስ አበባ፤ሐምሌ 15/2017(ኢዜአ)፦በመጪዎቹ አስር...
22/07/2025

በክረምቱ አልፎ አልፎ የሚኖር ከባድ ዝናብ ሊያስከትል ከሚችለው ቅጽበታዊ ጎርፍ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል-የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 15/2017(ኢዜአ)፦በመጪዎቹ አስር ቀናት አልፎ አልፎ የሚኖረው ከባድ ዝናብ ለጎርፍ ተጋላጭ በሆኑ ተፋሰሶች ላይ ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊያስከትል ስለሚችል ህብረተሰቡ ጥንቃቄ ሊያደርግ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለፀ።

ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው በመጪዎቹ አስር ቀናት በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብ፣ በሰሜን ምዕራብ እና በመካከለኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ በበርካታ ቦታዎቻቸው ላይ ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው እርጥበት ይኖራቸዋል።

በተጨማሪም በሰሜን ምስራቅ፣ በምስራቅ እና በደቡብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው እርጥበት እንደሚኖራቸው መረጃዎች እንደሚያሳዩ ገልጿል።

የሚጠበቀው እርጥበት ለወቅቱ የግብርና ስራ እንቅሥቃሴ በአመዛኙ አዎንታዊ ሚና እንደሚኖረው ትንበያው ያሳያል።

ስጋቶችን ለመቀነስና የሚኖሩትን መልካም አጋጣሚዎች በላቀ ሁኔታ ለመጠቀም የቀረቡትን ቦታ ተኮር የግብርና ሚቲዎሮሎጂ ምክረ ሀሳቦች በተገቢው ሁኔታ መተግበር እንደሚያስፈልግ አመላክቷል።

በሚኖረው እርጥበት ዘር መዝራት፣ ትርፍ ውሃን ከማሳ በማጠንፈፍ ማስወገድ፣ የአፈር መሸርሸር ስጋትን ለመቀነስ የጎርፍ መቀልበሻ ቦዮችን ማዘጋጀት እንደሚያስፈልግም ጠቁሟል።

ረባዳማ በሆኑ ማሳዎች የውሃ ማንጣፈፍ ስራዎች መስራትና የደረሱ የበልግ ሰብሎችን በሚኖሩ ደረቅ ቀናቶች መሰብሰብ እንዲሁም የሚገኘውን እርጥበት በመጠቀም የመኸር ዘር መዝራት እንደሚገባም አብራርቷል።

በቀጣዮቹ አስር ቀናት በሚኖረው ዝናብ በአብዛኛው ተፋሰሶች ላይ ከመጠነኛ እስከ ከፍተኛ መጠን ያለው የገፀ ምድር የውሃ ፍሰት እንደሚኖርም መግለጫው ያመላክታል።

አልፎ አልፎ ከሚኖረው ተደጋጋሚ የሆነ ከባድ ዝናብ ጋር ተያይዞ በተለይም ለጎርፍ ተጋላጭ በሆኑ ተፋሰሶች ላይ ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊያስከትል እንደሚችል አስረድቷል።

ስለሆነም በወንዝ ዳርቻ እንዲሁም ረግረጋማ አካባቢ የሚኖሩ ማህበረሰቦች ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸውና የሚመለከታቸው የዘርፉ አካላት አደጋን በመቀነስ መልካም እድሎችን እንዲጠቀሙም አስገንዝቧል።

የጎርፍ መቀልበሻ ቦዮችን ማዘጋጀት፣ወራጅ ውሃን በእግርም ሆነ በቀላል ተሽከርካሪ ለማቋረጥ አለመሞከር፣ የጎርፍ የፍሳሽ መውረጃ ቦዮችን ማፅዳት፣ የዝናብ ውሃ ማሰባሰብና ማጠራቀም እንደሚገባ ማመላከቱን ኢዜአ ዘግቧል።

22/07/2025

ከአሶሳ ከተማ አስተዳደር ወረዳ 2 ቀበሌ 1 አመራርና ነዋሪዎች ጋር የተደረገ ቆይታ!!
ክፍል- ሁለት

22/07/2025

የቀን 6፡00 የአማረኛ ዜና 15 11 2017 ዓ.ም

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መቶ በመቶ በራስ አቅም በመንግስትና ህዝብ የተገነባ ነው ሲል የግድቡ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ገለጸ፡፡ጽ/ቤቱ በዛሬው ዕለት ለመገናኛ ብዙሃን በሰጠው መግለ...
22/07/2025

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መቶ በመቶ በራስ አቅም በመንግስትና ህዝብ የተገነባ ነው ሲል የግድቡ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ገለጸ፡፡

ጽ/ቤቱ በዛሬው ዕለት ለመገናኛ ብዙሃን በሰጠው መግለጫ ላይ እንዳስታወቀው፥ በበጀት ዓመቱ ለግድቡ 1 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ተሰብስቧል፡፡

በበጀት አመቱ የተሰበሰበው ገንዘብ ከዕቅዱ የ7 በመቶ ብልጫ እንዳለው የጽህፈት ቤቱ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍቅርተ ታምር በመግለጫው ላይ ጠቅሰዋል፡፡

ኢትዮጵያውያን በሞራል፣ በገንዘብ፣ በጉልበት፣ በዕውቀት፣ በፕብሊክ ዲፕሎማሲ እና በአካባቢ ጥበቃ በመረባረብ የተመዘገበው ስኬት በትውልድ የሚዘከር ህያው ድል ነው ብለዋል፡፡

ግንባታው ከተጀመረበት ግዜ ጀምሮ በቦንድ ግዥና በስጦታ በሀገር ውስጥ 20 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር እንዲሁም ከዳያስፖራው ማህበረሰብ 1 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ መሰብሰብ ተችሏል፡፡

በተጨማሪም ከልዩ ልዩ ገቢዎች 1.7 ቢሊየን ብር በላይ መሰብሰቡን የገለጹት ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚዋ፥ በአጠቃላይ እስከ ሰኔ 30/2017 ዓ.ም ከህብረተሰቡ ከ23 ነጥብ 6 ቢሊየን በላይ ብር ተሰብስቦ ለግድቡ ግንባታ ውሏል ነው ያሉት።

እንደዚሁም በጠቅላላው የግድቡ ግንባታ ከተጀመረበት አንስቶ ከ84 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት የጉልበትና የተፋሰሰ ሥራዎች መሰራቱም በመግለጫው ላይ መብራራቱን ፋና ዘግቧል።

Address

Assa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Benishangul Gumuz Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Benishangul Gumuz Media:

Share