Doch HD

Doch HD █░░•No Racism •No Hate ░░█
█░░•No Distortions░░█
________________________

❚█Just Getting Started█❚

Doch HD ገና በጅምር ላይ ያለ የመረጃና የመዝናኛ ሚዲያ ነው። በዚህም መረጃ ሰጪ ቪዲዮ እና ምስል እንዲሁም ፅሁፍ በየቀኑ በየሰዓቱ ከእኛ ይመልከቱ። ዶች

"እግዚአብሔር ግን ደረቱን ሰጠኝ"- ዶክተር ጴጥሮስ ወልደጊዮርጊስ "ከተመኩ አይቀር መመካት በእግዚአብሔር ብቻ ነው።ትላንት ከአፈር ያነሳኋቸው፣ ዛሬ  ጀርባቸውን ሲሰጡኝ፣ ጓደኞቼ ናቸው ያልኳ...
11/07/2025

"እግዚአብሔር ግን ደረቱን ሰጠኝ"- ዶክተር ጴጥሮስ ወልደጊዮርጊስ

"ከተመኩ አይቀር መመካት በእግዚአብሔር ብቻ ነው።

ትላንት ከአፈር ያነሳኋቸው፣ ዛሬ ጀርባቸውን ሲሰጡኝ፣ ጓደኞቼ ናቸው ያልኳቸው ስልኬን መመለስ ፈርተውና አፍረው ሲዘጉብኝ፤

እግዚአብሔር ግን ደረቱን ሰጠኝ፣ ተዋጋልኝ፣ አሸናፊም አደረገኝ።"

ዶክተር ጴጥሮስ ወልደጊዮርጊስ
የቀድሞ የቦንጋ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት

ክልላዊ ዐበይት ዕለታዊ መረጃዎችን በአጭሩ፤(ሐምሌ 04 ቀን 2017 ዓ.ም)በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፦•ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ  አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የክልሉ...
11/07/2025

ክልላዊ ዐበይት ዕለታዊ መረጃዎችን በአጭሩ፤

(ሐምሌ 04 ቀን 2017 ዓ.ም)

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፦

•ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳስቧል።ኮሚሽኑ በክልሉ 34 ወረዳዎች የአደጋ ስጋት እንዳለባቸው ገልጾ በካፋ ዞን ጨና ወረዳ በደረሰ አደጋ 290 ሰዎች መፈናቀላቸውን ጠቁሟል።👉https://telegra.ph/SWDC-07-11

•በክልሉ 56 ሺህ ላሞችና ጊደሮችን በሰው ሰራሽ ዘዴና በተሻሻሉ ኮርማዎች ማዳቀል መቻሉን የክልሉ ግብርና ቢሮ ግልጿል። በዚህም 26 ሺህ 610 ጥጆች ማግኘት መቻሉ ቢሮው ያስታወቀው።??https://telegra.ph/SWAB-07-11

•የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ ቤት የ2017 በጀት ዓመት የ4ኛ ሩብ ዓመት ማጠቃለያ ኮንፈረንስ አካሂዷል። ኮንፍረንሱ የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ እውቅና በመስጠትም ፍጻሜውን አግኝቷል።👉https://telegra.ph/Mizan-07-11

•በካፋ ዞን ሳይለም ወረዳ መንግስት ለዘመናት የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ሆነው የሰነበቱ የልማት ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ ምላሽ እየሰጠ መምጣቱ ይበልጥ የህብረተሰቡን ተነሳሽነት እያሳደገ መምጣቱን ነዋሪዎች ገልጸዋል። ነዋሪዎቹ ከወረዳው አስተዳደር ጋር በመተባበር በራስ አቅም የተለያዩ የልማት ስራዎችን ማከናወን መቻላቸውን ተናግረዋል ።👉https://telegra.ph/Saylem-07-11

•የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የአስተዳደር ብልጽግና ህብረት አፈጻጸሙን ገምግሟሎ።ህብረቱ በበጀት ዓመቱ ዕቅዳቸውን ውጤታማ እንዲያደርጉ ተገቢው የድጋፍና ክትትል ስራዎች መሰራታቸውን ተብራርቷል።👉https://telegra.ph/SWPP-07-11

•በኮንታ ዞን የ2016 ዓ/ም በክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፍቃድ አፈፃፀምና በ2017 ዓ/ም ዕቅድ ላይ የውይይት መድረክ ተካሂዷል። በዞኑ የ2017 ዓ.ም የክረምት ወራት በጎ ፍቃድ አገ/ሎት በችግኝ ተከላና የአቅመ ደካማ ቤት ግንባታ በማብሰር በይፋ ተጀምሯል።👉https://telegra.ph/Konta-07-11

•ከምርምር ስራዉ ጎን ለጎን በአረንጓዴ አሻራ ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያላቸዉ ችግኞችን በማዘጋጀት ለአርሶ አደሩ ተጠቃሚነት እየሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የቴፒ ግብርና ምርምር ማዕከል አስታውቋል።በማዕከሉ የ2017 የክረምት አረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያላቸዉ ችግኞች ተተክለዋል።👉https://telegra.ph/Teppi-07-11

•በምዕራብ ኦሞ ዞን በመኤኒት ጎልዲያ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት በጫት ቀበሌ የወባ መከላከል ዘመቻ የሚደረግ የአከባቢ ፅዳትና ውሃ ያቆሩ ቦታዎችን የማዳፈኑ ተግባርን አላማ ያደረገ የንቅናቄ ስራዎች በይፋ መጀመሩን ተገልጿል ። የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ግርማ ፖሊሲ ወቅቱ ክረምት ከመሆኑ ጋር በተያያዘ አሁን ያለንበት ወቅት ለወባ በሽታ ስርጭት ምቹ በመሆኑ የወባ ትንኝ መራቢያ ቦታዎችን የማዳፈንና የማፋሰስ ስራዎች በህዝብ ንቅናቄ ልዩ ትኩረት ተሰጦ መሰራት እንዳለበት ገልጸዋል ።👉https://telegra.ph/West-Omo-07-11

•በዳውሮ ዞን የታርጫ ከተማ አስተዳደር በዛሬው ዕለት በሁሉም መንደሮችና በመንግሥት ተቋማት የጽዳት ዘመቻ አካሂዷል። በዘመቻው የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችና ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል በነቂስ መሳተፉም ተጠቁሟል።👉https://telegra.ph/Tarcha-07-11

ዶች

ዶክተር ጴጥሮስ ወልደጊዮርጊስ "በተሻለ ክብርና ከፍታ አፍሪካን የማገልገል ዕድል አገኘሁ"ሲሉ ተናገሩ።የቀድሞው የቦንጋ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት አፍሪካን በይበልጥም ሀገራቸውን "በተሻለ ክብርና ...
11/07/2025

ዶክተር ጴጥሮስ ወልደጊዮርጊስ "በተሻለ ክብርና ከፍታ አፍሪካን የማገልገል ዕድል አገኘሁ"ሲሉ ተናገሩ።

የቀድሞው የቦንጋ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት አፍሪካን በይበልጥም ሀገራቸውን "በተሻለ ክብርና ከፍታ የማገልገል ዕድል" ማግኘታቸውን ተናግረዋል።

ዶክተር ጴጥሮስ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ "ከተመኩ አይቀር በእግዚአብሔር ነው" ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት ባህር ማዶ የሚገኙት የቀድሞ ፕሬዝዳንቱ በቅርብ ቀን ወደ ሃገራቸው እንደሚመለሱ የጠቀሱ ሲሆን ያገኙት "ዕድል" ምን እንደሆነ በቅርቡ ያሳውቃሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ሙሉ ፅሁፋቸው እንዲህ ቀርቧል፦

"ውድ ወገኖቼ!

በቅንነት ያገለገልኩት አምላኬ አሁን ተዓምር ሰርቶልኛል። ማንም፣ ምንም በማይቀለብሰው መልኩ፣
ልያስብ እንኳ በማይችለው መልኩ ተደርጎልኛል።

ከተመኩ አይቀር መመካት በእግዚአብሔር ብቻ ነው።

ትላንት ከአፈር ያነሳኋቸው፣ ዛሬ ጀርባቸውን ስሰጡኝ፣ ጓደኞቼ ናቸው ያልኳቸው ስልኬን መመለስ ፈርተውና አፍረው ስዘጉብኝ......

እግዚአብሔር ግን ደረቱን ሰጠኝ፣ ተዋጋልኝ፣ አሸናፊም አደረገኝ።

በአደባባይ የማመሰግነው ወድጄ አይደለም ! በውለታው ተገድጄ ነው።

ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ወደ ሀገሬ እመለሳለሁ።

በተሻለ ክብርና ከፍታ አፍሪካን፣ በተለይም ሀገሬን የማገለግልበትን በር ዛሬ እግዚአብሔር ከፍቶልኛል።

ክብር ለልጅነቴ አምላክ! እሰግድለታለሁ።

አመልከዋለሁ።

አገለግለዋለሁ።

እነሆ ነገሩ ተገለበጠ።"

ዶች

ዋ ቱንጎ ሸኧ (wa tunggo shɛɛ) "እንዴት አደራችሁ"  #ሱሪ        #ደቡብምዕራብሳኒ ኬና ቦ ቻልላ (sani ke na bo challa)" መልካም ቀን"
11/07/2025

ዋ ቱንጎ ሸኧ (wa tunggo shɛɛ)
"እንዴት አደራችሁ" #ሱሪ #ደቡብምዕራብ

ሳኒ ኬና ቦ ቻልላ (sani ke na bo challa)"
መልካም ቀን"

ክልላዊ ዐበይት ዕለታዊ መረጃዎችን በአጭሩ፤በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፦•የቴፒ አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ደረጃ ለማሻሻል እየተሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።በ193...
10/07/2025

ክልላዊ ዐበይት ዕለታዊ መረጃዎችን በአጭሩ፤

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፦

•የቴፒ አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ደረጃ ለማሻሻል እየተሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።በ1937 ዓ.ም የተመሰረት ት/ቤቱን ደረጃ ለማሻሻል ህብረተሰቡን በማሳተፍ ነው እየተሰራ የሚገኘው።👉https://telegra.ph/Teppi-07-10

•በካፋ ዞን ሳይለም ወረዳበ78 ሚሊዮን ብር ውጪ የተገነቡ የያዶታ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጃና የያዶታ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የቀዶ ጥገና ማዕከል ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል። ፕሮጀክቶቹን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች መርቀው ከፍተዋል።👉https://telegra.ph/YADOTA-07-10

•ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ የቆንዳ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን መርቀው ከፍተዋል። 120 ሚሊዮን ብር ወጪ በተደረገበት ሆስፒታሉ ምርቃት ላይ ርዕሰ መስተዳድሩ ጨምሮ ሌሎች የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።👉https://telegra.ph/Konda-07-10

•በክልሎች የክለቦች ሻምፒዮና እየተሳተፉ የሚገኙት የክልሉ ተወካይ ክለቦች የምድብ ሁለተኛ ጨዋታቸውን አድርገዋል። በዚህም ጊምቦ ዳዲበን ሲያሸንፍ ማሻ ወረዳ ድል አልቀናውም።👉https://telegra.ph/SW-CLUBS-07-10

•በካፋ ዞን ጨና ወረዳ ኮዳ ቀበሌ በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ 240 ሰዎች መፈናቀላቸው ተገልጿል። ሌሎች የወረዳው ቀበሌዎችም የአደጋ ሥጋት እንዳለባቸው ተጠቁሟል። 👉https://telegra.ph/CHENNA-07-10

•በየደረጃው ከሚገኙ የባለድርሻ አካላት ጋር በተደረገው የተቀናጀ ርብርብ የ12ኛ ክፍል ክፍል የማጠናቀቂያ ፈተና በሁሉም የማስፈተኛ ተቋማት በሰላም መጠናቀቅ መቻሉን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታውቋል። ከፈተናው በኋላም የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር መከናወኑን ቢሮው ገልጿል።👉https://telegra.ph/TARCHA-07-10

ዶች

በሻምፒዮናው የዛሬ ጨዋታ ማሻ ወረዳ ድል አልቀናውም።የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልልን በኢትዮጵያ የክልል ክለቦች ሻምፒዮና ከወከሉት ሁለት ክለቦች አንዱ የሆነው ማሻ ወረዳ በሁለተኛ የ...
10/07/2025

በሻምፒዮናው የዛሬ ጨዋታ ማሻ ወረዳ ድል አልቀናውም።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልልን በኢትዮጵያ የክልል ክለቦች ሻምፒዮና ከወከሉት ሁለት ክለቦች አንዱ የሆነው ማሻ ወረዳ በሁለተኛ የምድብ ጨዋታው ድል አልቀናውም።

በዛሬው እለት 10 ሰዓት ላይ በተደረገው የምድብ ጨዋታው ማሻ ወረዳ ከዶንቦስኮ ዓድዋ ሁለተኛ የምድብ ጨዋታውን አድርጎ 2ለ1 ተሸንፏል።

ማሻ ወረዳዎች በ29ኛው ደቂቃ ጎል ለማስቆም ቀዳሚ ቢሆኑም በመጀመሪያ አጋማሽና በሁለተኛው አጋማሽ በተቆጠረባቸው ሁለት ጎሎች ሽንፈት አስተናግደዋል።

ዶች

አንጋፋው ጋዜጠኛ ጌጡ ተመስገን ካፋ ዞን ገዋታ ወረዳ ገብቷልበደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ካፋ ዞን ገዋታ ወረዳ የቆንዳ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በዛሬው እለት ይመረቃል።በዚህም የ...
10/07/2025

አንጋፋው ጋዜጠኛ ጌጡ ተመስገን ካፋ ዞን ገዋታ ወረዳ ገብቷል

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ካፋ ዞን ገዋታ ወረዳ የቆንዳ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በዛሬው እለት ይመረቃል።

በዚህም የክልልና የዞን እንዲሁም የወረዳ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሀላፊዎች የሚገኙ ሲሆን ይህንኑ መርሃግብር ለመታደም ነው ጋዜጠኛው በዚያ የተገኘው።

ጌጡ በመርሃግብሩ ከተወዳጁ የመድረክ መሪ አስራት አሉቦ ጋር በመሆን መድረክ የሚመሩ ይሆናል።

ዶች

ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ በ78 ሚሊዮን በላይ ብር በጀት በያዶታ የተገነቡ 2 ፕሮጀክቶችን መርቀው ከፈቱ።የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ...
10/07/2025

ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ በ78 ሚሊዮን በላይ ብር በጀት በያዶታ የተገነቡ 2 ፕሮጀክቶችን መርቀው ከፈቱ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በካፋ ዞን ሳይለም ወረዳ ከ78 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ግንባታቸው የተጠናቀቁ የተለያዩ ፕሮጀክቶች መርቀው ከፍተዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በ66.9 ሚሊዮን ብር የተገነባውኝ የያዶታ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅና በ11.3 ሚሊዮን ብር የተገነባውን የያዶታ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ቀዶ ጥገና ማዕከል ነው መርቀው የከፈቱት።

በዚህም መርሃግብር የክልሉን ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ሃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸውን ጨምሮ ሌሎች የክልል፣ የዞንና የወረዳ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሃላፊዎች ተገኝተውበታል።

ዶች

የክልሉ ተወካይ ጊምቦ ዳዲበን 2ተኛ የምድብ ጨዋታውን 2ለ0 አሸነፈ።የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልልን በኢትዮጵያ የክልል ክለቦች ሻምፒዮና ከወከሉት ሁለት ክለቦች አንዱ የሆነው ጊምቦ ...
10/07/2025

የክልሉ ተወካይ ጊምቦ ዳዲበን 2ተኛ የምድብ ጨዋታውን 2ለ0 አሸነፈ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልልን በኢትዮጵያ የክልል ክለቦች ሻምፒዮና ከወከሉት ሁለት ክለቦች አንዱ የሆነው ጊምቦ ዳዲበን ሁለተኛ የምድብ ጨዋታውን አሸንፏል።

በዛሬው እለት ረፋድ 3 ሰዓት ላይ በተደረገው የምድብ ጨዋታው ጊምቦ ዳዲበን የሲዳማ ክልል ተወካዩን ዳራ ቃባዶ አቻውን ገጥሞ 2ለ0 ማሸነፍ መቻሉን ዶች ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

የጊምቦ ዳዲበን የማሸነፊያ ግቦችን ብሩክ ዳንኤል በ18ኛው ዲቂቃ እንዲሁም ተሻገር ክፍሌ በ87ተኛው ደቂቃ ያስቆጠሩ ሲሆን ክለቡ ነጥቡን 4 ማድረስ ችሏል።

ሌላኛው የክልሉ ተወካይ ማሻ ወረዳ ዛሬ ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ከዶንቦስኮ ዓድዋ ሁለተኛ የምድብ ጨዋታውን የሚያደርግ ሲሆን በመጀመሪያ ጨዋታው ነጥብ መጋራት መቻሉ የሚታወስ ነው።

ዶች

ክቡር አቶ ፀጋዬ ማሞ በአንጋፋው ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን ህልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ።የቀድሞው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመንግሥት ዋና ተጠሪ ክቡር አቶ ፀጋዬ ማሞ በአንጋፋው...
10/07/2025

ክቡር አቶ ፀጋዬ ማሞ በአንጋፋው ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን ህልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ።

የቀድሞው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመንግሥት ዋና ተጠሪ ክቡር አቶ ፀጋዬ ማሞ በአንጋፋው ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን ድንገተኛ ህልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገልፀዋል።

አቶ ፀጋዬ በዚህ የማህበራዊ ትስስር ላይ ፅሁፋቸው የጋዜጠኛውን ህልፈት ለማመን መቸገራቸውን ገልፀው እጅግ አሳዛኝ ዜና መሆኑን ተናግረዋል።

የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታው የጋዜጠኛው ነብስ በሰላም ታርፍ ዘንድ ተመኝተዋል።

ዶች

ስለ ሚዛን አማን ተናግሮ የማይጠግበው አንጋፋው ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን አረፈ።ኢቲቪን ጨምሮ ለበርካታ አመታት በጋዜጠኝነት ሞያ ያገለገለው ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን በድንገት ከዚህ አለም በሞት ተለይቷ...
10/07/2025

ስለ ሚዛን አማን ተናግሮ የማይጠግበው አንጋፋው ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን አረፈ።

ኢቲቪን ጨምሮ ለበርካታ አመታት በጋዜጠኝነት ሞያ ያገለገለው ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን በድንገት ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል።

ጋዜጠኛው በ1963 ዓ.ም በትግራይ ወቅሮ የተወለደ ሲሆን ስለ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያዋ ሚዛን አማን ተናግሮ አይጠግብም ነበር።

አንጋፋውና በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በተለይ "የሚዲያ ዳሰሳ" በሚል ፕሮግራሙ የሚታወቀው ጋዜጠኛው በአገረ አሜሪካ በትምህርት ላይ የነበረ ሲሆን በድንገት ህይወቱ አልፏል ።

ጋዜጠኛ ታደሰ ስለ ሚዛን አማን ከተማ ታሪክም ረጃጅም ፅሁፎችን በማስፈር የሚታወቅ የሀገሩን ህዝብ ወዳድ ባለሞያ ነበር።

ዶች

"ጱንዴ ኮኝ፤የለኝ፤ሸክትኝ" እንደምን አደራችሁ!?  #መኧንቱኝዱ ኬ ሸይመልካም ቀን!
10/07/2025

"ጱንዴ ኮኝ፤የለኝ፤ሸክትኝ" እንደምን አደራችሁ!? #መኧን

ቱኝዱ ኬ ሸይ
መልካም ቀን!

Address

Скопје

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Doch HD posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Doch HD:

Share