Bete Amhara Media ቤተ አምሐራ ሚድያ /BAM

  • Hjem
  • Norge
  • Oslo
  • Bete Amhara Media ቤተ አምሐራ ሚድያ /BAM

Bete Amhara Media ቤተ አምሐራ ሚድያ /BAM የገፁ ተቀዳሚ ስራ ለድምፅ አልባዎች ድምፅ መሆን ነው!!!

Amazing Ethiopian village bridgeBete Amhara Media ቤተ አምሐራ ሚድያ /BAM
22/06/2025

Amazing Ethiopian village bridge

Bete Amhara Media ቤተ አምሐራ ሚድያ /BAM

best pictureይህ ቦታ ማን ይባላል??Bete Amhara Media ቤተ አምሐራ ሚድያ /BAM
22/06/2025

best picture
ይህ ቦታ ማን ይባላል??
Bete Amhara Media ቤተ አምሐራ ሚድያ /BAM

❗️ሰበር ❗️አሜሪካ ወደ ጦርነቱን መቀላቀሏ ተከትሎ የመንም በይፋ ወደ ጦርነቱን መቀላቀሏን አሳውቃለች።የመን እንዳለችው ከሆነ ከኢራን ጎን እንቆማለን ፤ የጠላት መርከብ በኛ ቀጠና ያለፈ እን...
22/06/2025

❗️ሰበር ❗️

አሜሪካ ወደ ጦርነቱን መቀላቀሏ ተከትሎ የመንም በይፋ ወደ ጦርነቱን መቀላቀሏን አሳውቃለች።

የመን እንዳለችው ከሆነ ከኢራን ጎን እንቆማለን ፤ የጠላት መርከብ በኛ ቀጠና ያለፈ እንደሆነ ዶግ አመድ ይሆናል ስተል ተናግራለች።

Bete Amhara Media ቤተ አምሐራ ሚድያ /BAM


22/06/2025

የኢራን የምድር ውስጥ ጉድ አለም ሁሉ ተደንቋል !!
Bete Amhara Media ቤተ አምሐራ ሚድያ /BAM


ኢራን የእስራኤል ከተሞችን መደብደቧ እንደቀጠለ መሆኑን ዘገባዎች አመልክተዋል።በኢራን ክፉኛ ተመቱ የተባለው ሃይፋና ቴልአቪቭ  ናቸው።ምስሎቹም የሁለቱ ከተሞችን ጉዳት ያሳያል ተብሏል።አሜሪካ ...
22/06/2025

ኢራን የእስራኤል ከተሞችን መደብደቧ እንደቀጠለ መሆኑን ዘገባዎች አመልክተዋል።

በኢራን ክፉኛ ተመቱ የተባለው ሃይፋና ቴልአቪቭ ናቸው።ምስሎቹም የሁለቱ ከተሞችን ጉዳት ያሳያል ተብሏል።

አሜሪካ በኢራን ላይ ድብደባ ማድረሷን ተከትሎ ከቴህራን በወጣ መረጃ ኢራን በዚህ ተደናግጣ የኑክሊየር መርሃ ግብሯን አታቋርጥም ሲሉ መሪዎቿ አረጋግጠዋል።

# sheger press

The best picture of the village life style      Bete Amhara Media ቤተ አምሐራ ሚድያ /BAM
22/06/2025

The best picture of the village life style


Bete Amhara Media ቤተ አምሐራ ሚድያ /BAM

“አሜሪካ ብትሳተፍም ባትሳተፍም፣ እስራኤል የኢራንን የኒውክሌር ተቋማት በሙሉ የማጥፋት አቅም አላት”- ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ++++++++++++++++++++++++  | ጠቅላይ ...
20/06/2025

“አሜሪካ ብትሳተፍም ባትሳተፍም፣ እስራኤል የኢራንን የኒውክሌር ተቋማት በሙሉ የማጥፋት አቅም አላት”
- ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ
++++++++++++++++++++++++

| ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ እንደተናገሩት፣ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቢሳተፉም ባይሳተፉም፣ እስራኤል የኢራንን የኒውክሌር ተቋማት በሙሉ የማጥፋት አቅም አላት።

ኔታንያሁ ይህንን የተናገሩት ዋይት ሃውስ ትራምፕ በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ ጣልቃ መግባት አለመግባታቸውን ይወስናሉ ከማለቱ በፊት ነው።

የወታደራዊ ጉዳይ ተንታኞች፣ እስራኤል የኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር ዋነኛ ክፍል የሆነውን ፎርዶው የነዳጅ ማበልጸጊያ ፋብሪካን ለማጥፋት የአሜሪካ እገዛ ሊያስፈልጋት ይችላል ብለው ያምናሉ።

"በሁሉም ኢላማዎቻችንን፣ ሁሉንም የኒውክሌር ተቋሞቻቸውን የማስወገድ አቅም አለን ያሉት ኔታንያሁ፤ ነገር ግን ፕሬዚዳንቱ ለመቀላቀል ይፈልጉ እንደሆነ ወይም እንደማይፈልጉ የሚወስኑት እርሳቸው ናቸው ብለዋል።"

ኔታንያሁ አክለውም እርሱ (ትራምፕ) ለአሜሪካ የሚበጀውን ያደርጋል፣ እኔም ለእስራኤል መንግስት የሚበጀውን አደርጋለሁ ሲሉ ተደምጠዋል።

Bete amhara media ቤተ አምሓራ ሚድያ

“ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ''  ዳን 10፥13እንኳን ለገናናው መላእክት ለቅዱስ ሚካኤል አመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!!! የባህራንን የእዳ ደብዳቤ ቀደህ ወደ ...
19/06/2025

“ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ''
ዳን 10፥13

እንኳን ለገናናው መላእክት ለቅዱስ ሚካኤል አመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!!!

የባህራንን የእዳ ደብዳቤ ቀደህ ወደ ህይወት የቀየርክ የባህራን የአፎሚያ ረዳት ሆይ በህይወት ዘመኔ የእኔን የእዳ ደብዳቤ ቀደህ ወደ ህይወት የቀየርክ ረዳቴ ሆይ አድርገህልኛልና ለዘላለም አመሰግንሃለሁ!!!

Bete amhara media ቤተ አምሓራ ሚድያ

እንኳን_አደረሳችሁ፧አደረሰን‼️የግሸን ማርያም በአልን ለማክበር ወደ ቦታው ለደረሳችሁ፣ በምጣት ላይ ላላችሁ እና ለመምጣት ላሰባችሁ ሁሉ የተላለፈ መልእክትበመጀመሪያ ስለ አማራ ህዝብ ነፃነት ...
27/09/2024

እንኳን_አደረሳችሁ፧አደረሰን‼️

የግሸን ማርያም በአልን ለማክበር ወደ ቦታው ለደረሳችሁ፣ በምጣት ላይ ላላችሁ እና ለመምጣት ላሰባችሁ ሁሉ የተላለፈ መልእክት

በመጀመሪያ ስለ አማራ ህዝብ ነፃነት በየጫካው፣ በቆላ በደጋ ደከመን ሳትሉ መስዎትነት እየከፈላችሁ ላላችሁ የትግል ጓዶቻችን፣ለጭቁኑ የአማራ ህዝብና ለመላው ኢትዮጵያውያን የክርስትና ዕምነት ተከታዬች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ፣አደረሰን!!!

በመቀጠልም በየአመቱ መስከረም 21 ቀን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አማኞች ዘንድ በአምባሰል ወረዳ በግሸን ደብረ ከርቤ በድምቀት የሚከበረው የእናታችን የቅድስተ ቅዱሳን የድንግል ማርያም ክብረ በዓል ከዚህ በፊት እንደተለመደው በአሉ በድምቀት ተከብሮ እንደሚውል እያሳወቅን የበአሉንም አከባበር አስመልክቶ የሚከተለውን መልእክት እናስተላልፋለን።

እኛ የአማራ ፋኖዎች ይህንን አካባቢ የጠላትን ሀይል እንድለቅ በማድረግ ቦታውን ለቆ እንድወጣ ያደረግንበት ዋና ምክንያት ህዝባችን ያለ ስጋትና ጭንቀት በአሉን አክብሮ በሰላም እንደመለስ ለማድረግ አልመን ነው።ስለሆነም የሰው ልጅ ሁሉ በኢትዮጵያ ምድር ተከብሮና ነፃነቱን አግኝቶ የሚኖርበት ሥርአት ለማንበር እንታገላለን። እየታገልንም ነው፡፡

ስለዚህ ወንዝ አቋርጣችሁ፣አቀበቱን ወጥታችሁ፣ ቁልቁለቱን ወርዳችሁ፤ በመኪናም ሆነ በአየር መጥታችሁ የግሸን ማርያም አመታዊ የንግስ በአሉን ለማክብር ከተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ለምትመጡ ሕዝብ ክርሰቲያን በሙሉ ቀጣናውን ተቆጣጥሮ የሚገኘው የአማራ ፋኖ ቤተ አምሐራ ክፍለጦር የፀጥታውን ሁኔታ በአስተማማኝ ደረጃ ጥበቃ እያደረገ ይገኛል፡፡በዚህ ወቅት በአሉን ለማክበር በቦታው ከፍተኛ ቁጥር ያለው ምእመን እየገባ ይገኛል።በግሸን የገባው ህዝባችን የተለመደውን አገልግሎት በሰላማዊ መንገድ እየተስተናገዱ ይገኛሉ።በተጨማሪም በጉዞ ላይ ያላችሁ መኖራችሁን እናውቃለን።እንድሁም በአሉን ለማክበር ለመምጣት የፈለጋችሁ ነገር ግን ስጋት ያደረባችሁ ወገኖቻችን መጥታችሁ በዓሉን አክብራችሁ ለመመለስ ምንም አይነት ስጋት እንዳይገባችሁ።ሰላማችሁንም ለማስጠበቅ ተግተን እየሰራን ነው።

የኢትዮጵያን ታሪክ፣ባህልና ሀይማኖታዊ ሥርአትና ወግ ጠሉ የፋሽስቱ የአብይ አሕመድ ሰራዊት ለአራት ወር አካባቢውን በተቆጣጠረው ጊዜ ቦታውን ከክብሩ በማውረድ ለመናገር በሚከብድ ደረጃ አጸያፊ ነገሮች በቤተክርስቲያኑ ቅጥር ግቢና በአካባቢው ሲፈጽም መቆየቱ ይታወቃል፡፡

ይሁን እንጂ እኛ ቦታውን ከተቆጣጠርን በኋለ ከአካባቢው ህብረተሰብ ጋር በመሆን በማፅዳትና የቦታውን ክብር በሚመጥን መልኩ እንደ ዱሮው መልሰን በማዘጋጀት፤
መንገዱንም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ጥርጊያውን አመቻችተን ለጉዞ ምቹ እንድሆን አድርገናል፡፡

በዓሉ በሰላም እንዲጠናቀቅ ኮሚቴ አዋቅረን መሠረታዊ የአገልግሎ ዘርፎች ለእንግዶች ሁሉ እንዲመች አድርገን እየጠበቅናችሁ እንገኛለን፡፡

ስለሆነም ከአራቱም አቅጣጫ የምትመጡ የእምነቱ ተከታይ የሆናችሁ ውድ ኢትዮጵያውያን ለሰላማችሁ ዘብ፣ ለመንፈሳዊ ጉዟቸው ከፈጣሪ ቀጥሎ ዋስ ከለላ ጠበቃ ልንሆናችሁ ዝግጅታችን አጠናቀን ጨርሰናል፡፡

ስለዚህ ያለ ስጋት መጥታችሁ በቦታው በዓሉን እንድታክብሩ በተከብረው የአማራ ህዝብ ስም በትህትና ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡

ድል ለአማራ ፋኖ
ድል ለአማራ ሕዝብ
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ

የአማራ ፋኖ ቤተ አምሐራ ክፍለጦር
Bete amhara media ቤተ አምሓራ ሚድያ

📌የቤተ አምሐራ ክፍለ ጦር ምስርታን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ!በሀገራችን ኢትዮጵያ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ በአምሐራ ሕዝብ ላይ በተለያዩ ዘመናት መዋቅራዊ ድጋፍን በመጠቀም መከራና ስቃይ ...
20/09/2024

📌የቤተ አምሐራ ክፍለ ጦር ምስርታን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ!

በሀገራችን ኢትዮጵያ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ በአምሐራ ሕዝብ ላይ በተለያዩ ዘመናት መዋቅራዊ ድጋፍን በመጠቀም መከራና ስቃይ ሲፈፀምበት ቆይቷል።በተለይም የትህነግ ቡድን መንበረ ስልጣኑን ከተቆጣጠረበት ዘመን ጀመሮ መንግሥት መር የሆነ የዘር ማጥፋት ተግባር በተጠናከረ መልኩ ቀጥሎ በዋናነት ባለፉት ስድስት አመታት በዘረኝነት ጋንግሪን የተጠቃው የኦነግ ብልጽግና ስርአት ማንነትን መሰረት ባደረገ ሁኔታ የዘር ማጥፋት ተግባርን ከእለት ወደ እለት በማንአለብኝነት ጥቃቱን በመጨመር የአማራ ህዝብን ሙሉ በሙሉ ከምድረ ገፅ አጠፋለሁ ብሎ ፓሊሲና ስትራቴጂካዊ ስልቶችን በመጠቀም አለኝ የሚለውን ዘመናዊ የጦር መሳሪያ በመጠቀም እየጨፈጨፈን ይገኛል።

እንድህ አይነቱን ህዝብ ጨፍጨፊ እና ሀገር አፍራሽ ስርአት የአማራ ሕዝብ ከተደቀነበት የህልውና አደጋ ራሱን ለማዳንና ዘሩን ለማስቀጠል ሲል በየቀጠናው ራሱን እያደራጀ ተፈጥሮአዊ ራስን የመከላከል ሂደትን ተከትሎ የአሸባሪውን ወንበር ጠባቂ ቅልብተኛ እና ህዝብ ጨፍጫፊ የሆነውን ሰራዊት የአማራ ፋኖ በየግናባሩ ድል በመቀናጀት በጠላት ሀይል ላይ ዳግም እንዳያንሰራራ እስከወዳኛው የመሸኘት ተግባርን መፈፀም ከጀመረ ከአንድ አመት በላይ አስቆጥሯል።

በዚህ ተግባር ተሰማርተው ሕዝባችንን ከጠላት ወረራ እየመከቱና ጠላትን ተስፋ እያስቆረጡ ካሉ የፋኖ አደረጃጀቶች መካከል በወሎ ጠቅላይ ግዛት ከሚንቀሳቀሱት መካከል የቤተ አምሐራ ፋኖ አንዱ ነው።

የቤተ አምሐራ ፋኖ አደረጃጀት ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ በነበረው ጦርነት ከፍተኛ ጀብድን ሲፈፅም የነበረና በብርጌድ ደረጃ የነበረ ቢሆንም በቀጠናው የሚንቀሳቀሱ የፋኖ አርበኞች ፣ ወጣቶችና የህብረተሰብ ክፍል ወታደራዊና ፓለቲካዊ ሥልጠናዎችን በማሰልጠን በትጥቅና በሰው ኃይል ከጊዜ ወደ ጊዜ ያለውን እድገት ታሳቢ በማድረግ ወደ ክፍለጦር ማደጋችንን ስናበስር ከፍተኛ ኩራትና ደስታ ይሰማናል።

በመሆኑም የሚከተሉት የስራ አስፈፃሚዎች አሉት።
1.አርበኛ ሰሎሞን አሊ____ ዋና አዛዥ
2. ፋኖ እንዳሻው ጌታሁን ____ ም/አዛዥ
3. ፋኖ ቢኒያም ማሞ ___ ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ
4. ፋኖ መኩሪያው አጋዥ ____ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ
5. ፋኖ ምስጋናው ወርቁ ____ ፋይናንስ ኃላፊ
6. ፋኖ ደምስ አባተ ____ ኦርድናንስ ኃላፊ
7. ፋኖ እርገት አያሌው ____ ሎጅስቲክ ኃላፊ
8. ፋኖ አብርሃም ገረመው ___ የሰው ኃይል ኃላፊ
9. ፋኖ ፍስሀ ቀለሙ ___ አስተዳደር ኃላፊ

በአጠቃላይ የቤተ አምሐራ ፋኖ ክፍለጦር አባላት ከላይ የተዘረዘሩትን የሥራ አስፈፃሚዎች ስንመርጥ በአካባቢው ከሚገኙ የክፍለጦር አደረጃጀቶች ጋር በመቀናጀት የጠላት ሰራዊትን የማሸነፍ አቅማችን ከወትሮው በተለየ እንደሚጨምር በማመን ነው።ስለሆነም ክፍለጦራችን የአንባሰል ሰንሰለታማ ተራሮችን እንደመቀነት አጥሮ የግሸን ማርያም እና አካባቢውን ተቆጣጥሮ ይገኛል።

እንድሁም በየአመቱ የሚገበረውን የግሸን ማርያም በአልን ሕዝበ ክርስቲያኑ በቦታው ተገኝቶ እናዳከብርና ለዚህም ምንም አይነት የደህንነት ስጋት የማይፈጠር መሆኑን ከወድሁ እየገለፅን የበአሉን የፀጥታ ሁኔታን አስመልክቶ ክፍለጦሩ ለመላው ህዝባችን በአጭር ቀን ውስጥ መልእክት የምናስተላልፍ መሆኑን እናሳውቆታለን።

ታሪካችን በተባበረ ክንዳችን እናድሳለን !!

የቤተ አምሐራ ክፍለጦር
መስከረም 10 ቀን 2017ዓ.ም
ወሎ/ቤተ አምሐራ ፣ ዐማራ፣ ኢትዮጵያ

BBete amhara media ቤተ አምሓራ ሚድያ

☝️Update!!!የሸዋ አናብስቶች አዲሱን አመት  ከጠላት አፈሙዝ ጋር እየተናነቁ በድል ብስራት እያስቀጠሉት ይገኛሉ ።የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ቀስተ - ንህ...
11/09/2024

☝️Update!!!

የሸዋ አናብስቶች አዲሱን አመት ከጠላት አፈሙዝ ጋር እየተናነቁ በድል ብስራት እያስቀጠሉት ይገኛሉ ።

የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ቀስተ - ንህብ ብርጌድ ዛሬ መስከረም 01/2017ዓ.ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሀቤቴ አውራጃ በሚዳና ሬማ ወረዳ፣ በ ሬማ ከተማ ከንጋቱ 11:00 እስከ ረፋድ 3:00 ድረስ በተካኼደው ዓውደ ውጊያ ጠላት ከፍተኛ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ጉዳት የደረሰበት ሲሆን 27 የመከላከያ ሰራዊት አባላት ወደማይቀረው ቤታቸው ሲሸኙ፤ 18 አባላቱ ከባድ ቁስለኛ ሆነዋል። የአማራው ነቀርሳ ተብለው የሚጠሩ 4 የሚሊሻ አባላት ወዲያውኑ ህይወታቸው አልፏል።

በዚሕ ዓውደ ዉጊያ ታላቅ ጀብዱ የፈፀሙት ጀግኖቹ 3 የፋኖ አባላት ለተከበረው የአማራ ህዝብ ሲሉ መተኪያ የለላትን አንድያ ነፍሳቸውን መስዋዕት ሲያደርጉ፤ 2 የፋኖ አባላት ቀላል ቁስለኛ ሆነዋል። በዝሕ ዓውደ ውጊያ የጠላት ሀይልን መናበብ በማይችልበት ደረጃ ብትንትኑን ማውጣት ተችሏል።

አሁን በዚህ ሰዓት ከተማዋ በፋኖ ከበባ ውስጥ ስትገኝ፣ የጠላት መውጫ መግቢያ በመዘጋቱ ተጨማሪ ሀይል ከአለም ከተማ እና ከመራኛ ከተማ የጠየቀ ሲሆን ሁሉም መንገዶች እና ወደ ሬማ ከተማ የሚያስገቡ በሮች በሁሉም አቅጣጫ በፋኖ ተዘግተው ይገኛሉ።

"የ አማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር የቀስተ ንህብ ብርጌድ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል"

ታጋይ ይሰዋል ትግል ይቀጥላል!
ድል ለአማራ ፋኖ!!!
ድል ለአማራ ህዝብ!!!

Bete amhara media ቤተ አምሓራ ሚድያ

ሰበር ዜናየአማራ ፋኖ በወሎ ሰለሞን አሊ የሚመራው የቤተ አምሓራ ፋኖ በአንባሰል ወረዳ በግሸን ማርያምን ሰፍሮ የነበረውን የጠላት ጦር በመድምሰስ ቦታውን ተቆጣጥሯል።ከትናንት  ቀን ጀምሮ ሙሉ...
10/09/2024

ሰበር ዜና

የአማራ ፋኖ በወሎ ሰለሞን አሊ የሚመራው የቤተ አምሓራ ፋኖ በአንባሰል ወረዳ በግሸን ማርያምን ሰፍሮ የነበረውን የጠላት ጦር በመድምሰስ ቦታውን ተቆጣጥሯል።

ከትናንት ቀን ጀምሮ ሙሉ ሌሊቱን ውጊያ ሲያካሂድ ያደረው የወራሪው ሰራዊት አባል የፋኖን ምት መቋቋም ሲያቅተው ቦታውን ለቆ ለነበልባሎቹ አስረክቧል።በውጊያውም ብዙ የጠላት ሀይል የተደመሰሰ ሲሆን ብዙ ተተኳሽና መሳሪያም ተማርኳል።

ይህን ኦፕሬሽን ለመስራት የታሰበው በዋናነት ህዝበ ክርስቲያኑ ማህበረሰብ የግሸን ማርያምን አመታዊ በአል በሰላም ለማክበር የግደታ የጠላትን ጦር ከቀጠናስ ማፅዳት እንዳለብን ታስቦ የተሰራ መሆኑን እንገልፃለን።

ማሳሰቢያ:- በዚህ ውጊያ ላይ ከፍተኛ ጀብድ የፈፀመው የአማራ ፋኖ በወሎ የክፍለ ጦር ስያሜውና አደረጃጀቱን የጨርውሰ ሲሆን በቅርቡ ለህዝባችን ይፋ እናደርጋለን።

#ድልለፋኖ
#ድልለአማራህዝብ

Adresse

Oslo

Varslinger

Vær den første som vet og la oss sende deg en e-post når Bete Amhara Media ቤተ አምሐራ ሚድያ /BAM legger inn nyheter og kampanjer. Din e-postadresse vil ikke bli brukt til noe annet formål, og du kan når som helst melde deg av.

Del