Woldia Online

Woldia Online Woldia Online is news and entertainment website!!
(1)

  (ይስማዕከ ወርቁ)(፩) የግዕዝን ቋንቋ ከሰኩላሪዝም (Secularism) አንጻር ስናዬው...የግዕዝ ቋንቋ የሦስተኛ ክፍል የተማሪዎች መጽሐፍ ደርሶኝ እያገላበጥኩ ሁሉንም አየሁት።  የሶስተ...
18/09/2025



(ይስማዕከ ወርቁ)

(፩) የግዕዝን ቋንቋ ከሰኩላሪዝም (Secularism) አንጻር ስናዬው...

የግዕዝ ቋንቋ የሦስተኛ ክፍል የተማሪዎች መጽሐፍ ደርሶኝ እያገላበጥኩ ሁሉንም አየሁት። የሶስተኛ ክፍል የተማሪዎች መጽሐፍ 83 ገጽ አለው። ሲያጠናቅቅ ከግዕዝ ቋንቋ ወደ አማርኛ ቋንቋ የሚፈታ የሙዳዬ ቃላት ይዟል።

መጽሐፉን ሳዬው በትክክል የተዘጋጀ መሆኑን አይቻለሁ። የንግግሩ ቃላት ሁሉ እምነትን እንዳይነካ ሆኖ በጥንቃቄ የተዘጋጀ መሆኑን አረጋግጫለሁ። የግዕዝ ቋንቋን የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት አስጠግታው እንደኖረች እሙን ነው። ይህን ሁሉም ያምናል። ሙስሊሙም ክርስቲያኑም። ግን ወደ ልጆቹ ሲመጣ አስጠግታ ያቆየችው ሃይማኖት አለችና የእነርሱን እምነት እንዳይሰብክ ልጆቻቸውን መከላከሉ ከእናትና ከአባት የሚጠበቅ ነው። ግን እነርሱ ሳይሆኑ የሚከራከሩት መጽሐፉን ያላዩት የፖለቲካ ጥገኞች የሆኑ ሰዎች መሆናቸውን መጽሐፉን እኔም ካየሁት በኋላ አረጋግጫለሁ። እንዲያውም ከተዋህዶ ሃይማኖት ጋር የግዕዝ ቋንቋ ተጠግቶ ስለኖረ አስጠግታው የኖረችውን ሃይማኖት ጥቅሶች እንዳያመጣ ስግቼ ነበር። እንደዛ ያለ ነገር ግን መጽሐፉን በማነብበት ወቅት አላገኘሁም። የግዕዝ ቋንቋ እና ሃይማኖት የተለያዩ እንደሆኑ ይህን መጽሐፍ ያዘጋጁት ሰዎች፣ ብልህ እንደሆኑ መጽሐፉን ሳነብ አረጋግጫለሁ። የመጽሐፉ "ኮፒ ራይት" ይዞኝ እንጂ ሙሉውን ለእናንተ እለጥፈው ነበር። የአዘጋጁት ሰዎች እና የተረከበው አካል መፍቀድ አለበት።

በአማርኛም የትኛውንም እምነት መስበክ ይቻላል። የእስልምናንም ሆነ የትኛውንም የክርስቲያን እምነት በማንኛውም ቋንቋ መስበክ ይቻላል። የግዕዝን ትምህርት በትምህርት ስርዓቱ ውስጥ ለማስገባት ያሰቡ ሰዎች ሴኪውላር ማድረግ ያስፈልጋቸዋል። በፖለቲካዊ ርዕዮተ ዓለም ሰኩውላሪዝምን (Secularism) ስናዬው፣ ሃይማኖትና መንግሥት የተለያዩ ናቸው። እኔ ግን እንደ ሀሳብ የምሰጠው፣ ኢትዮጵያ ከፖለቲካ የፀዳ ትልቅ የቋንቋ ተቋም ያስፈልጋታል። በዛ ተቋም ተገምግሞ አልፎ ቢሄድ ኖሮ እስከ አሁን የግዕዝ ቋንቋ ባላነታረከን ነበር። ማንም መንገደኛ አያደናግረንም ነበር። ከቋንቋዎች ሁሉ ደግሞ የመጀመሪያውና ኢትዮጵያን የምናስጠራበት ቋንቋ አንዱና ዋነኛው ግዕዝ ነው። የኢትዮጵያ ቀርቶ የአፍሪካ ሁሉ ኩራት ነው።

ግዕዝ ቋንቋውን ግን የኦርቶዶክስ ሃይማኖት አስጠግታው ስለኖረች፣ ከዛ አንዳንድ ጥቅሶች እንዳይገቡ መጠንቀቅ ያሻል ብዬ ነበር ግን መጽሐፉን ሳነበው ምንም የሚያጨቃጭቅ ነገር አላዬሁበትም። በጥራዝ ነጠቅ ያወሩ ሰዎች ነበር የሚያደናግሩን። በተለይም ከዚህ በፊት የተለጠፉ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ያላቸውን ሰዎች መጽሐፍ ከጎግል ላይ እያወጡ በትምህርት ስርዐቱ ውስጥ የገባ መስሎን እኔም ብዙ ሰዎችን በስልክ መከራቸውን ሳበላ ነበር። ግን በፍፁም እንደዛ እንዳልሆነ መጽሐፉን ሳነብ አረጋገጥኩ። ወደ ፊት በስርአተ ትምህርቱ ውስጥ የግዕዝ ትምህርት እየሰፋ ሲሄድ፣ መጽሐፍ የሚያሰናዱ ሰዎች እንደዚህ መጽሐፍ ጥንቃቄ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። የማንኛውንም እምነት እንዳይነካ፣ የትኛውንም ሃይማኖት እንዳይጎሽም አድርገው የማስተላለፍ ግዴታ አለባቸው። ይህ ግዴታ ነው።

(፪) የግዕዝ ቋንቋ አስተማሪዎች እነማን ይሁኑ?

የግዕዝን ቋንቋ የሚያስተምሩት ዲያቆናትና ቄሶች ናቸው ይባላል። ሃይማኖቱ አስጠግቶት ስለኖረ፣ እምነትን እንዳነካ አድርገው የተማሩት እንዲያስተምሩ መሆን አለበት። ያውም ከዩኒቨርስቲ የተመረቁ ቢሆን ይመረጣል። የግዕዝ ቋንቋ ሰኩላር (Secular) እየሆነ ሲመጣ ግን ሙስሊሞቹ ሰኩላር (Secular) ሆነው ማስተማር አለባቸው። አንድን ቋንቋ እየተጸየፍክ ግን እንኳን ለማስተማር ለመማርም አትበቃም። አንዳንድ የወሎ ሙስሊሞች ግዕዝ ያውቃሉ። እኔ ዛምራ የተባለው ልቦለዴን በምጽፍበት ወቅት ያገኘኋቸው አንድ ሙስሊም ሰው በግዕዝ ቋንቋ አውርተውኛል። እንዴውም የመጀመሪያውን ምዕራፍ የሰጠሁት አንድ ሙስሊም ልጅ ወደ ቅኔ ቤት ሲገባ የሚያሳዬውን ጠባይ በመንተራስ የተፃፈ ነው።

(፫) የግዕዝ ቋንቋ የጠንቋዮች እና የደብተራዎች እውቀት ነው ለሚሉ...

ጠንቋይ ማለት አደናጋሪ ማለት ነው። አምታቺ ነው። የማታውቀውን ቃል ያነበልብልሃል። የማታውቀውን ቃል ከግዕዝ ቃል እያወጣ መተት ደገምኩልህ ሊልህ ይችላል። እንዲያውም ከድግምት ቃላት ውስጥ አረብኛም በብዛት አለበት። ትናንት አንዱ የለጠፈውን የመተት ቃል አይቼ በሳቅ ፈረስኩ። የለጠፈውም ሰው እርሱ ሙስሊም ነኝ ይላል። ግን ቃላቱን አይቼ ስመረምረው ባብዛኛው የአረብኛ ቃላት አሉበት። ጫጫጫጫ ጃጃጃጃጃ ከሚለው ውስጥ አንዳንድ በተን በተን ያሉ የግዕዝ ቃላት አሉበት። ጳጳጳጳ ፓፓፓፓፓፓ ከሚለው ውስጥ ደግሞ ብዙ የአረብኛ ቃላት አሉበት። አስማተኞች መተተኞች እንዳይበሉን እንወቅ። ካላወቅክ ደግሞ ይበሉሃል። ይሸጡሃል። እንዳትሸጥ እወቅ። በሁሉም ቋንቋ መተት አለ። ድግምት አለ። በእንግሊዝኛም፣ በጀርመንኛም፣ በፈረንሳይኛም ድግምት አለ። እንዲያውም በአፍሪካ ቋንቋዎች አይብስም? በናይጀሪያማ አስማቱን የግላቸው ያደረጉት ይመስላል። ከዛ ውጪ ወደ አስማቱ ስንወርድ የተለያዩ የሚያምታቱ እና ብዙሃኑ የማያውቃቸውን ቃላት አሰማተኞች ይደርታሉ። ካላወቅህ ተበላህ ነው የምልህ። ይሸጡሃል። ይለውጡሃል። ገንዘብህን ንብረትህን ትበላለህ።

የግዕዝ ትምህርትን አትማሩ ማለት ግን የጠንቋዮች ስብከት ሊሆን ይችላል። ምክንያቱም አስማቱን ካወቅክባቸው በምን ሊደግሙት ይችላሉ? ይህ ይሰመርበት።

(፬)ከህክሞና አንፃር...

የግዕዝ መጻሕፍት የህክምና፣ የስነፈለግ፣ የኬሚስትሪ የእፅዋት ሳይንስን፣ የፊዚክስ ሁሉ አጭቀው ነው የያዙት። ይህን ፍለጋ ነው ነጮች የግዕዝን ቋንቋ ለማዎቅ የሚፈልጉት። ከዚህ አንጻር ሌላ ጊዜ መመለስ አለብኝ። አሁን ተዘርዝሮ አያልቅም።

እኔ በልጅነቴ ነው ሰባተኛ ክፍል ሆኜ ወደ ሀዋሳ የሄድኩት። ሀዋሳ ማለት የብዙ ቋንቋ ተናጋሪ ያለበት ከተማ ናት። ተማሪቹ አፋቸውን የፈቱበት የየራሳቸው ቋንቋ አላቸው። በተጨማሪም አማርኛ፣ እንግሊዝኛ እና ሲዳምኛ ትምህርት ቤት እንማራለን። ብዙዎቹ ተማሪዎች ባለ ብዙ ቋንቋ (Multilingual) ናቸው። እኔ ግን በልጅነቴ የግዕዝ ቋንቋ በመማሬ በእርሱ እንኳን ተጽናናሁ እንጂ ከአማርኛ በቀር በምንም አልግባባቸውም ነበር። አማርኞዬም ለእነርሱ ይከብዳቸው ይመስለኛል። ብቼኝነቴ ከመጽሐፍ ጋር አቆራኘኝ። ብቼኝነቴ እንድጽፍ ገፋፋኝ። ስለዚህ ሰናጠቃልለው የግዕዝ ቋንቋንተማሪዎች መማራቸው ሊበረታታ ነው የሚገባው። በሌላ ክፍለ ሀገር ያሉት ባለ ብዙ ቋንቋ ተናጋሪዎች ናቸው። ቢያንስ አንድ ቋንቋ በተጨማሪ ቢማሩ ጥሩ ነው ብዬ አስባለሁ። ጥሩ ጊዜ ከመጣ ደግሞ በሁሉም ክፍለሀገር ቢሰጥ ጥሩ ነው። ግዕዝ ማለት የሁላችንሞ ቋንቋ ነው። ከመጽሀፉ ላይ አልፎ አልፎ ለምስክርነት እንዲረዳ ተጠቅሜአለሁ። ሰናይ ጊዜ።

የቀድሞው የወልድያ ከተማ ከንቲባ የነበሩት መሐመድ ያሲን ስለ  #ግዕዝ ይሄን ብለዋል   አዎ ቋንቋ ይወለዳል፤ ያድጋል፤ ይሞታል። ግእዝ ግን እንዲሞት ተፈረደበት እንጂ ራሱን አልገደለም‼️ #...
17/09/2025

የቀድሞው የወልድያ ከተማ ከንቲባ የነበሩት መሐመድ ያሲን ስለ #ግዕዝ ይሄን ብለዋል

አዎ ቋንቋ ይወለዳል፤ ያድጋል፤ ይሞታል። ግእዝ ግን እንዲሞት ተፈረደበት እንጂ ራሱን አልገደለም‼️

#መቅድም

የግእዝ ትምህርትን በተመለከተ በ3 ተከታታይ ክፍሎች ያለኝን የግል አመለካከት መሰረት በማድረግ ባጋራሁት ፅሁፍ መነሻነት በውስጥ መስመር በርካታ አስተያየቶችና ጥያቄዎች እየደረሱኝ ይገኛል።

ይህ ከሆነ ዘንዳ ከዚህ በታች ካሰፈርኩት አመለካከት የተለየ አቋም ያለው ግለሰብ የፈለገውን ስያሜ ወይም ትችት ሊሰጥ ይችል ይሆናል። ይህንን ግን በራሱ ገፅ እንዲያደርገው ከወዲሁ እመክራለሁ።

#ማሳሰቢያ

📝 ይህንን አተያይ በጨዋ ደንብ በሐሳብ ለሚሞግቱ ትልቅ ክብር አለኝ። የሚሰጡት አመክኒዮም አሳማኝ ከሆነ ለመቀበል ዝግጁ ነኝ።

🙈 ነገር ግን ለስድድብ፣ ለብሽሽቅ፣ ለዘለፋ ተብለው የሚሰጡ ትችቶችን መልስ ለመስጠት በሚል የማጠፋው ጊዜ አይኖረኝም።



❶ ያኔ በኢትዮጵያ በጥንት ዘመን ለ200 ዓመታት ገደማ የመንግስት የስራ ቋንቋ እና የህብረተሰቡ መግባቢያ ቋንቋ የነበረው ግእዝ፤

❷ የኢትዮጵያን ጥንታዊ ታሪክ ስነ ሃውልቶች የተሸከመው ግእዝ፤

❸ አያሌ ድርሳናት (ስለ ህክምና፣ ስለ ፍልስፍና፣ ስለ ማዕድናት፣ ስለ ፈዋሽ እፅዋት፣ ስለ ከዋክብት፣ ስለ አርኪዮሎጂ፣ ስለ ድንቅ ሐገራዊ ታሪኮች፣ ስለ ቀን ቆጠራ ወዘተ…) የተከተቡበት ግእዝ፤

❹ ለትግርኛና አማርኛ ቋንቋዎች መወለድ ስር ሁኖ ያገለገለው ግእዝ፤

❺ ሥርወ ቃላትን ለመመርመር ሰዋሰውን ለመለየት በእጅጉ የሚጠቅመው ግእዝ፤

❻ ሐገራችን ኢትዮጵያ የዘመናት ዑደት ስፍር ቀምራ የራሷን አሃዝ ያደላደለችበት ግእዝ፤

❼ ሐገር እንጂ ብሄር የሌለው ብቸኛ ቋንቋ ግእዝ፤

❽ ኢትዮጵያ አንድነቷን ጠብቃ እንድትኖር የቀድሞ ነገስታት ይመሩበት የነበረው የአስተዳደር ዘይቤ የተከተበበት ግእዝ፤

➒ ነጮች ጥቅሙን በቅጡ ተገንዝበው ኢትዮጵያውያንን በአስተማሪነት በመቅጠር በየዩኒቨርስቲዎቻቸው ዜጎቻቸውን የሚያስተምሩት ግእዝ ወዘተ…

እንዴትና ስለ ምን በጊዜ ሂደት የተናጋሪው ሰው ቁጥር ቀንሶ ከብሄራዊ ቋንቋነቱ ሊወርድ ቻለ❓ለግእዝ ቋንቋ መዳከም አቢይ ምክኒያት የአማርኛ መተካት ብቻ ሳይሆን ለቋንቋው የሚሰጠውና የተሰጠው ትኩረት መላላቱ የማያወላውል ምክኒያት መሆኑ ነው። በዚህም ተተኪው ትውልድ የትላንቱን ለዛሬ ማበርከት ያልቻ ሆኖ ይገኛል። በመሆኑም ትላንት የኢትዮጵያ የከፍታ መሰረት የነበረው ግእዝ ከነበረበት የብሔራዊና የውል ቋንቋነት ይቅርና ዛሬ ዛሬ ለእውቀት እንማረው መባል ሲጀመር የልዩነት ማዕከል እየተደረገ ይገኛል።

ግእዝ ከአሁኑ ዘመን ጋር እኩል ለመጓዝ የማይጠቅም ጊዜ ያለፈበት ያረጀ ቋንቋ ነውን❓አንዳንድ ሰዎች ከግእዝ ይልቅ እንግሊዝኛ፣ ቻይንኛ፣ ፈረንሳይኛ ወዘተ… ቢማሩ በእጅጉ የሚያተርፉ መሆኑን በመከራከሪያነት ሲያነሱ ይስተዋላል። እነዚህን መማር ጥቅሙ የላቀ መሆኑ አይካድም። ነገር ግን “አባቱን አያውቅ አያቱን ይናፍቅ” ያሰኛል።

በአሁኑ ዘመንስ ከሙታንነት ተቀስቅሶ በትውልዱ ላይ ሊጫን የተፈለገ የሃይማኖት መስበኪያስ ነውን❓በኔ ምልከታ ዛሬ ግእዝን ያወቀና የተማረ ሁሉ ነገረ ሀይማኖት ተረዳ ማለት አይደለም። ምክኒያቱም ቋንቋን ማወቅና መማር እምነትን የሚያስቀይር ቢሆን ኖሮ በእርግጥም ዛሬ ላይ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የግብጽ ኦርቶዶክስ አማኞች እስልምናን በተቀበሉ ነበር። ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ በግእዝ የተጻፉ ብዙ የእስልምና እምነት መፀሀፎች ሲኖሩ በአረብኛም የተከተቡ ብዙ የኦርቶዶክስ ድርሳናት ይገኛሉ። ስለሆነም ግእዝ ሃይማኖታዊ ቋንቋ አይደለም። It’s Part of Our LIVING History.

ዛሬስ በዩኒቨርሲቲ ደረጃ መሰጠቱን ደግፎ ነገር ግን በ1ኛ እና 2ተኛ ደረጃ ትም/ት ቤቶች እንዲሰጥ መወሰኑን በይፋ መቃወም የቋንቋውን ጠቃሚነት ካለመረዳት በሚመነጭ አመለካከት ይሆን❓ይህንን ጥያቄ የሚያነሱ አካላት ሊገነዘቡት ያልቻሉት ነገር ቢኖር ጥያቄው በራሱ የግእዝን መማር አስፈላጊነት የሚጠቁም መሆኑን ነው። በተጨማሪም አሁን እየተጠቀምንበት ያለው አማርኛ ቋንቋ ሆሄያቱ የግእዝ ፊደላት ሁነው ሳለና በዚሁ ቃላት እየፃፉ ግእዝን ማስተማር አያስፈልግም ሲሉ እንደመስማት የሚያሳዝን ነገር ከወዴት ይገኝ ይሆን።

እንደ ጥቅል እነዚህንና ተያያዥ ተጠየቆችን ስንመለከት ኢትዮጵያዊያን በአለም ፊት አንገታቸውን ቀና አድርገው በኩራት የሚናገሩለትን ማለትም ጥንታዊ የስርዓተ መንግስትና የስልጣኔ መነሻ፣ የራሷ ቋንቋና ፊደል፣ የቀን አቆጣጠር ወዘተ… ያላት ብርቅየ ሐገር ለመሆኗ መነሻ የሆነው ግእዝ በእርግጥም እንዲሞት ተፈረደበት እንጂ ራሱን አልገደለም የሚል ድምዳሜ እንዲያዝ ያደርጋል።

ዛሬም ዳግም እንዳይነሳ መቃብሩን አርቀው እየቆፈሩና በላዩ ላይ የልዩነት ቋጥኝና አለት እየጫኑበት ያሉት እሱ (ግእዝ) ባስገኘው የሚኮሩ ነገር ግን እሱን (ግእዝን) መማር በሚረግሙ አካላት ከሆነ ሰንበትበት ብሏል። እነሆ ይፋዊ ጥቃትም ውግዘትም በግእዝ ላይ ተከፍቶበት ይገኛል። ለዚህም ነው በድጋሚ ግእዝ እንዲገደል ተወሰነበት እንጂ ራሱን አላጠፋም የምንለው።

#መደምደሚያ

ግእዝ ከአማርኛና ሌሎች ኢትዮ-ሴማዊ ቋንቋዎች ጋር ሲወዳደር ንጹህ ሴማዊ ቋንቋ ነው። በተጨማሪም ግእዝ በመላው የአፍሪካ ሐገራት ውስጥ የመጀመሪያውና ብቸኛ አፍሪካዊ የራሱን ፊደላት የያዘ ቋንቋ ሲሆን በዓለምም ላይ ዋናና የስልጣኔ አራማጅ ከሚባሉት ቋንቋዎች አንዱ ሁኖ ይገኛል።

ስለሆነም ኢትዮጵያ የቀደምት ስልጣኔ ባለቤት መሆኗን በእርግጥም የምንኮራበት ከሆነ ለኩራታችን ምንጭ የነበረውን ግእዝ ከታች ጀምሮ ለማስተማር በትግበራ ላይ ስለሚገኝ በቀጣይ ስርዓተ ትምህርቱ እየዳበረ እንዲሄድ ለማሻሻያነት ግብዓት የሚሆኑ ጉዳዩችን በተደራጀ መንገድ ለሚመለከተው ተቋም በማቅረብ የዜግነት ግዴታዎን ሊወጡ ይገባል።

በመጨረሻም ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሐገር፣ የታሪክ እና የቅርስ ባለአደራ ነው‼️

የወልድያ እስልምና ጉዳዮች ፅ/ቤት የግዕዝ ትምህርት እንዲሰጥ መወሰኑን ተቃወሙ
17/09/2025

የወልድያ እስልምና ጉዳዮች ፅ/ቤት የግዕዝ ትምህርት እንዲሰጥ መወሰኑን ተቃወሙ

የእርማት ስህተት አጋጥሞ ነበር አሁን ተስተካክሏል!!መጀመሪያ የተገለጸ ውጤት እና አሁን የተስተካከለ ከደሴ የይሁኔ ወልዱ ስፔሻል ት/ቤት የ ፊዚክስ ውጤት የሁሉም ተማሪ ከ 60 በታች የነበረ...
16/09/2025

የእርማት ስህተት አጋጥሞ ነበር አሁን ተስተካክሏል!!

መጀመሪያ የተገለጸ ውጤት እና አሁን የተስተካከለ
ከደሴ የይሁኔ ወልዱ ስፔሻል ት/ቤት
የ ፊዚክስ ውጤት የሁሉም ተማሪ ከ 60 በታች የነበረ ሲሆን በአሁኑ ሰአት የሁሉም ተስተካክሏል!!

1. ዌብ ሳይት፡ https://result.eaes.et

2. ቴሌገራም፡ https://t.me/EAESbot

3. አጭር የጽሑፍ መልዕክት (SMS)፡ 6284 ማረጋገጥ ትችላላችሁ

16/09/2025

ስለ ግዕዝ ትምህርት
የሚሰማችሁን በጨዋ ደንብ
Comment አድርጉ
የመልስ ምት Reply ማድረግም
መብት ነው!!

ይሄ ደብዳቤ ግን ትክክለኛ ነውን?በተለያየ ቦታ ከእርማት ጋር ተያይዞ ቅሬታ እየተነሳ ነው የደሴው የይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ስፔሻል ትምህርት ቤት ተማሪዎች ውጤት  እንደሚያሳየው ፊዚክስ ከ 60...
16/09/2025

ይሄ ደብዳቤ ግን ትክክለኛ ነውን?
በተለያየ ቦታ ከእርማት ጋር ተያይዞ ቅሬታ እየተነሳ ነው የደሴው የይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ስፔሻል ትምህርት ቤት ተማሪዎች ውጤት እንደሚያሳየው ፊዚክስ ከ 60 በላይ ያመጣ ተማሪ የለም ማትስን ግን ከ 90 በላይ በርካታ ተማሪዎች አምጥተዋል የፊዚክስ ፈተናም ከ60 እንደታረመ ወደ መቶ አልተቀየረም የሚሉ በርካቶች ናቸው ይህ ደብዳቤም ተመሳሳይ ይዘት አለው ደብዳቤው ትክክለኛ መሆኑን ግን ማረጋገጥ አልቻልኩም
የደብዳቤውን ትክክለኛነት ለማረጋገጥም ወደ ትምህርት ቤቱ ደውለን ደብዳቤው ከትምህርት ቤቱ መውጣቱን ስንጠይቅም ነውም አይደለምም ማለት አልፈለጉም በዚህ ጉዳይ ላይ ግን ትምህርት ሚኒስተር ጥርት ያለ ነገር ቢሰጥ ጥሩ ነው !!

569/600ያዕቆብ እስራኤል ምስክር ወልድያ ላይ ከፍተኛ ውጤት ሁኖ ተመዝግቧል !!
15/09/2025

569/600
ያዕቆብ እስራኤል ምስክር
ወልድያ ላይ ከፍተኛ ውጤት ሁኖ ተመዝግቧል !!

13/09/2025

ሸህ መሃመድ ሁሴን አሊ አልአሙዲ ያደረጉት ንግግር
"የሰራተኛ ቁጥር ጨምሩ"

"መካከለኛ ገቢ ያለው የህብረተሰብ ክፍል ተፈጥሮ ማየት እፈልጋለሁ"

"የዋጋ ግሽፍቱ ደሀውን የህብረተሰብ ክፍል እየጎዳው ስለሆነ ሸክሙን ቀለል የሚያደግ መስክ ላይ ኢንቨስት አድርጉ"

ሼህ መሐመድ አላሙዲን አዲስ አመትን አስመልክቶ ለሰራተኞቹ ካስተላለፈው ንግግር የተቀነጨበ...!!

እንኳን ለ2018 ዓ.ም አዲሱ ዓመት አደረሳችሁ አደረሰንአዲሱ ዓመት የሰላምና የጤና ይሁንላችሁ!!Woldia Online
10/09/2025

እንኳን ለ2018 ዓ.ም አዲሱ ዓመት አደረሳችሁ አደረሰን
አዲሱ ዓመት የሰላምና የጤና ይሁንላችሁ!!
Woldia Online

አዳጎ📷 Woldia Online
10/09/2025

አዳጎ
📷 Woldia Online


እንኳን ደስ አለን!!
09/09/2025

እንኳን ደስ አለን!!

23/08/2025

አሸንድየ በላሊበላ !!

Address

Riyadh

Telephone

+251920212121

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Woldia Online posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Woldia Online:

Share