Ethio Muslim

Ethio Muslim በሽገር ከተማ ስም የሚፈርሱ መስዶችን እቃወማለዉ መስጂድ ፈርሶየሚገነባ ከተማ የለም🇸🇦🇸🇦🇸🇦🇪🇹🇪🇹🇪🇹

10/10/2025

ከጉንዳንዉ ታሪክ ጀረባ

የሞተሰው  ከፈን ከእራሱ እስከ እግር ጥፍሩ ይሸፈናል አንዳንድ ጊዜ በምስሉ እንደምታዩት የእራስ ክፍሉ ያልተሸፈነ እናያለን ምክንያቱ ለምን እንደሆነ ያውቃሉ?
05/10/2025

የሞተሰው ከፈን ከእራሱ እስከ እግር ጥፍሩ ይሸፈናል አንዳንድ ጊዜ በምስሉ እንደምታዩት የእራስ ክፍሉ ያልተሸፈነ እናያለን ምክንያቱ ለምን እንደሆነ ያውቃሉ?

05/10/2025

Mkan sallam

በመካነሰላም በግፍ የተገደሉት የመስጂድ ኢማምአላህ ጀነተል ፊርደውስን ይወፍቃቸውከሸሒዶች ይቀበላቸውአሚን🤲
05/10/2025

በመካነሰላም በግፍ የተገደሉት የመስጂድ ኢማም

አላህ ጀነተል ፊርደውስን ይወፍቃቸው
ከሸሒዶች ይቀበላቸው
አሚን🤲

አለሀምዱሊላህ ነው ቃሉ!አቡኪ ቀዶ ጥገና አድርጎ ተነስቶ ሁላ ከመተኛት ይልቅ ሊጠይቁት የሚመጡ ሰዎችን ቁጭ ብሎ ነበረ የሚያናግረው! ህመሙን አይታችሁ እንድትጨነቁ ሳይሆን ደህና መሆኑን አይታ...
03/10/2025

አለሀምዱሊላህ ነው ቃሉ!

አቡኪ ቀዶ ጥገና አድርጎ ተነስቶ ሁላ ከመተኛት ይልቅ ሊጠይቁት የሚመጡ ሰዎችን ቁጭ ብሎ ነበረ የሚያናግረው! ህመሙን አይታችሁ እንድትጨነቁ ሳይሆን ደህና መሆኑን አይታችሁ እንድትጠነክሩ ነው ፍላጎቱ!

ለመጡት ሁሉ ከዛ ከምናውቀው ፈገግታ ጋር አለሀምዱሊላህ ነው ቃሉ ፥ "ይኸው ደህና ነኝም።" ይላል! ... ቀዶ ጥገናውን ከተሰራ በኋላ ሻል ብሎት የነበረም ቢሆን በድጋሜ ሆስፒታል ለመመለስ ተገዷል።

ከትላንት ዛሬ የተወሰነ ለውጥ አለው ብለውኛል ቤተሰቦቹ አለሀምዱሊላህ! አሁንም ቢሆን ሆስፒታል ነውና ዱአችሁን አደራ 🙏
ሙሉ አፊያውን አላህ ይወፍቅልን 🤲 ከነ ግርማሞገሱ አላህ ከኛ ጋር ረጅም እድሜን ያቆይልን 🤲

30/09/2025

✍️. 📚✅
================================
1️⃣. ቁርኣን የአሏህ ቃል መሆኑን እመኚ
2️⃣. ስትቀሪውም ስታቀሪውም ኢኽላስ ይኑርሽ
3️⃣. ቁርአን ባዘዘው ለመስራት ጥረት አድርጊ
4️⃣. የሐፈዝሽውን ላለመርሳት ሙራጀዓ አድርጊ
5️⃣. ትርጉሙን ለማወቅ ጉጉት ይኑርሽ

6️⃣. ለቁርአን ክብር ይኑርሽ
• ሻወር ቤትና መፀዳጃ ቤት ይዘሽው አትግቢ
• እግርሽን ቁርአን ወዳለበት አቅጣጫ አትዘርጊ
• በእግርሽ እንዳትረግጭው
• ወረቀቱን በስርአት ግለጭ
• ከቁርአን በላይ ምንንም ነገር አታስቀምጭ
• ከጀርባሽ አትጣይው
• ስትቀሪ መሬት ላይ አታስቀምጭው

7️⃣. የቁርአን አንቀፅ የተፃፈበትን ወረቀት ቆሻሻ መጣያ ቦታ ላይ ከመጣል ተጠንቀቂ
8️⃣. የቁርአን አንቀፆችን ግድግዳ ላይ፣ እቃዎች ላይ እና ልብስ ላይ ከመፃፍ ተጠንቀቂ
9️⃣. የቁርአን አንቀፅ ወይም ሱራህ የስልክ መጥሪያና አላርም ማንቂያ አታድርጊ
🔟. ቁርአንን ያለ ውዱእ አትንኪ
1️⃣1️⃣. ቁርአን ከመቅራትሽ በፊት አፍሽን በሲዋክ አፅጂ
1️⃣2️⃣. ቁርአን መቅራት ስትፈልጊ (አዑዙ ቢላሂ ሚነሸይጧኒ ረጃም) (ቢስሚላሂ ረሕማኒ ረሒም) በይ።
1️⃣3️⃣. ስትቀሪ አትፍጠኚ፣ አቀራር አታበላሺ
1️⃣4️⃣. ቁርአን ስትቀሪና ስታዳምጪ አልቅሺ
1️⃣5️⃣. በወንዶች አጠገብ ካልሆንሽ ድምፅሽን አሳምረሽ ቅሪ
1️⃣6️⃣. ሳል እና ማዛጋት ሲይዝሽ መቅራት አቁሚ
1️⃣7️⃣. ያለ አስፈላጊ ሐጃ በመሀል አታውሪ
1️⃣8️⃣. የቁርአን አንቀፅን ለመጠበቂያ ብለሽ በልጆች አንገት ላይ አታንጠልጥይ
1️⃣9️⃣. በየቀኑ የምትቀሪው የማይቀር ዊርድ ይኑርሽ
2️⃣0️⃣. ወደ ቂብላ ዙረሽ ተቀምጠሽ ቅሪ
2️⃣1️⃣. ከሙስሐፉ እንጂ ከስልክሽ አትቅሪ
2️⃣2️⃣. ቁርአን ያለ እውቀት አትፈስሪ
~
[አዳቡል ሙሂማ ሊኒሳኢል ኡማ 30-33]
[ዐብዱ ረ፞ሕማን ብኑ ዐሊይ አሲምሒይ]

ለዲንህ ዋጋ ስጥ

(ይህን ታላቅ ሰው አለማድነቅ አይሆንልኝም!!)ሙሐመድ አሊ (ቡርሃን) ዘመኑን የቀደመ ደራሲ  ወይም ያለ ዘመኑ የተፈጠረ ደራሲ ነው፡፡ አንዳንዴ ወደኋለኛው ዘመን በምናብ ተጉዞ የሚተነትናቸው ...
24/09/2025

(ይህን ታላቅ ሰው አለማድነቅ አይሆንልኝም!!)

ሙሐመድ አሊ (ቡርሃን) ዘመኑን የቀደመ ደራሲ ወይም ያለ ዘመኑ የተፈጠረ ደራሲ ነው፡፡

አንዳንዴ ወደኋለኛው ዘመን በምናብ ተጉዞ የሚተነትናቸው ደራሲያን ፣የሳይንስ ሰዎች ፣የፍልስፍና አብሰልሳዮች ፤ የቅርብ ጓደኞቹ ፣ቡና አጣጮቹ ፣ወደረኛ ተሟጋቾቹ ያስመስላቸዋል፡፡

ባለፉት ሰባት ዓመታት ከ2003 - 2010 ባለው ጊዜ ብቻ 33 መጽሐፍትን ጽፎ 23ቱ ታትሟል፡፡ ሁለቱ ከአንባቢ አቅም በላይ ይሆናል በሚል ሥጋት አንባቢ እስኪፈጠርላቸው ተጠብቀዋል፡፡ አንድ የሱን ምልከታ ተደራሲ ባይረዳውስ በሚል የተለያዩ ምሁራንን ሃሳብ ለማግኘት ሲባል ከኅትመት ቆይቷል፡፡ ሌሎቹም በአሳታሚዎች የጊዜ ሰሌዳ ተራቸውን እየጠበቁ ነው፡፡
የሙሐመድ ብእር ጠጣር ሃሳቦችን ነው የሚዘራው ፣ከዘለለት ጉዳዮች የተሻገረና አንባቢያን አእምሮ ውስጥ ታትሞ የሚቀሩ ሃሳቦች ላይ ትኩረት ማድረግ ይፈልጋል፡፡
ለማንበብ የሚመርጣቸው ሃሳቦች እንዲሁ ብዙዎቻችን የምንመርጣቸውን አይደሉም፡፡ በቀን ከሁለት በላይ መጽሐፍትን አንብቦ ሊያድር ይችላል፡፡
በአት ተውባ የታተሙ
1- አስደናቂ የሕክምና ጥበብ
2- ኢትዮጵያውያን ሶሃቦች
3- 6ቱ የሐዲስ ሊቃውንት
4- " " " 2
5 -ትዳርና ሕይወት
6- ኢማሙ አል ገዛሊ
7- ዑመር አልፋሩቅ
8- 4ቱ የፊቂህ ኢማሞች
9- የነብዩላህ ኢብራሂም ታሪክ
10- ታጋሾችን አበስራቸው

በነጃሺ ማተሚያ የታተሙ
1- ኢስላም ወርቃማው የሳይንስ ማዕከል
2- የፍልስፍና ጥበባትና እስልምና
3- ቢዝነስና ሥነ-ምግባር
4- ኢብኑ ተየሚያ
5- አብዱልቃድር ጀይላኒ

በዓለማዊ የታተሙ የፍልስፍና መጽሐፍት
1- ፍልስፍና ሕይወት
2- የማንነት ክንፎች
3- የጥበብ ፈለግ
4- ሰንደቅ የለሽ ዓላማ
ያልታተሙ ዓለማዊ
1- አምፖልና ኩራዝ
2- የተስፋ ብርሃን
3- ዘርመላሽ (ልብወለድ)

ፊልም
1- ዓለም በቃኝ
2- ውሃና ወርቅ (ያልወጣ)

የዲን ያልታተሙ
1- ሰው የመሆን ፋይዳ
2- እስልምና ምሥራቅ ወምእራብ
3- አምማ ጁዝዝ ትርጉም
4- ሳይኮሎጂ 1
5- " " 2
6- ጀነት
7- የሶሃቦች ታሪክ
8- የነብያት ታሪክ
9- እስልምና ለጀማሪዎች

መምህር
በተለያዩ ት/ቤቶች
ኬሚስት (ለተለያዩ ድርጅቶች የምርቱቸው ውህዱንና ማሽን የሠራ)

የፕሮግራም ዝግጅት
-አፍሪካ ቲቪ ከ2007 - 2010
- አሊፍ ሬዲዮ ከ2009- 2010
ኢንተርቪው
-በሸገር ሬዲዮ
በብሥራት ኤፍኤም
- በኤል ቲቪ ፍልስፍና ፕሮግራም
- በኢኤንኤን የበዓል እንግዳ

ሙሐመድ አሊ ዩሱ

የያሲኔ ወዳጅ - ከቂሊንጦ

አደራ ጠባቂው ወንድም ጀማል !ሚድሮክ የሚለውን ስም ሁላችንም እናውቀዋለን። ኢትዮጵያ ውስጥ ያልተሰማራበት መስክ አለ ማለት ያዳግታል። በሰማይም በየብስም በባህርም የሚሰሩ ስራዎች ላይ ሼህ አ...
21/09/2025

አደራ ጠባቂው ወንድም ጀማል !

ሚድሮክ የሚለውን ስም ሁላችንም እናውቀዋለን። ኢትዮጵያ ውስጥ ያልተሰማራበት መስክ አለ ማለት ያዳግታል። በሰማይም በየብስም በባህርም የሚሰሩ ስራዎች ላይ ሼህ አልአሙዲን አሉ፣ እሳቸው ካሉ ሚድሮክ አለ፣ ሚድሮክ ካለ ከ 74000 በላይ ሰራተኞችና ከነሱ ጀርባ ደግሞ በሚሊየኖች የሚቆጠር ቤተሰብ አለ።

ሚድሮክ ግዙፍ ነው። ሚድሮክ የሐገር ጌጥ፣ የድሆች መጠለያ፣ የበጎ አድራጎቶች ቁንጮ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ቤተሰቦች የገቢ ምንጭ እንዲሁም ከፍተኛ ግብር ከፋይ ሆኖ ከሁለት አስርት አመታት በላይ የቆየ አንጋፋ ድርጅት ነው።

ነገር ግን ድርጅቱም ሆነ የድርጅቱ ባለቤት ላይ በገጠመ ችግር ድርጅቱ ላይ ከፍተኛ የሆነ አደጋ እንደደመና አንዣበበ።
ችግሩ ብዙ ነው። ከድርጅቱ ግዙፍነት አንፃር፣ ካለው ከፍተኛ የሃብት መጠንና የሰራተኛ ብዛት አንፃር፣ ከተሰማራበት መጠነ ሰፊ የኢንቨስትመንት መስክና ከጀመራቸው እልፍ አእላፍ ፕሮጀክቶች አንፃር ለዚያ የሚመጥን ማኔጅመት ባለመኖሩ ምክኒያት ብዙ ድርጅቶቹ አደጋ ውስጥ ወደቁ።

ሼህ እልአሙዲን ከሳውዲ እንዳይወጡ በመደረጋቸው ምክኒያትና በተለያየ ጫና ለአመታት የለፉበትን ድርጅት በቅርበት ሊከታተሉ ባለመቻላቸውና እዚ የተቀመጡት ማኔጅመንቶች ደግሞ በከፍተኛ ቸልተኝነትና የግል ጥቅምን በመጋበስ ስራ ውስጥ በመጠመዳቸው 74 ሺ ሰራተኛን የተሸከመ የሐገር ምሰሶ ዘመም ማለት ጀመረ። ዝርፊያው ተጧጧፈ፣ ሙስናው ሰፋ፣ ብክነቱ የድርጅቱን መሰረት ነቀነቀ፣ ትልልቅና ግዙፍ ድርጅቶች ሊሸጡ ነው የሚል ወሬ መስተጋባት ጀመረ። አደራ ጠባቂ ተብለው የተቀመጡ ብዙዎች አደራቸውን በሉ። የ ሰባ አራት ሺ ሰራተኛ ህይወትና ከነሱ ጀርባ ያሉ ሚሊየኖች ላይ.....ተቀለደ።

“ሳይደግስ አይጣላም” እንዲሉ አበው....

የዚህ ግዜ ነው አቶ ጀማል አዲሱ CEO ሆኖ ድንገት ብቅ ያለው። አቶ ጀማል የሼሁን ጫማ እየለካ ያደገ፣ ሼሁን እንደአርአያ ሲመለከት የኖረ አላህን የሚፈራ ጉልበተኛ ወንድም ነው።

ጀማል አደራውን ጠበቀ። በአጭር ግዜ ውስጥም ተአምር ሰራ። ከፍተኛ የሆነ የአስተዳደር እርምጃዎችን ወሰደ። ያዘመሙ ግዙፍ ድርጅቶች በሁለት እግራቸው ዳግም ቆሙ! ከዚያም አልፈው ከፍተኛ ትርፋማ ሁኑ። በኪሳራ ሊሸጡ ነው የተባሉ ድርጅቶች ሳይቀር አይተው የማያውቁትን ትርፍ ማግኘት ጀመሩ። ሰራተኛ ሊቀንስ ነው የተባለው ሚድሮክ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰራተኞች መቅጠር ጀመረ። ፕሮጀክቶችን ሊያቋርጥ ነው የተባለ ድርጅት አዳዲስ ፕሮጀክቶችን ጀመረ።

አቶ ጀማል አደራን የመወጣት ምሳሌ ሆነ። የሰባ አራት ሺ ሰራተኛ ህይወትንና ከነሱ ጀርባ ያለን ሚሊዮን ሰው ህይወት ታደገ። ጭራሽ ሚድሮክ ኢትዮጵያንና ሚድሮክ ቴክኖሎጂን ከሆራይዘን ኢትዮጵያ ጋር አዋሃደ፣ ከዚያም ታላቁን ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕን ፈጠረ። አርባ አምስት የተበታተኑ ድርጅቶችን ወደስድስት በመሰብሰብ ለእየአንዳንዱ ብቁ ማኔጅመንቶችን በመመደብ ታላቁን Resurrection በአጭር አመት ውስጥ ሰርቶ አሳየ! እንደኤልፎራ ያሉ ከሃያ አመት በላይ በኪሳራ ሲሰሩ የነበሩ ድርጅቶች በአጭር ግዜ ውስጥ በዶሮ ምርት ከምስራቅ አፍሪካ አንደኛ ሆኑ!

ታማኙ አቶ ጀማል የሚመራው ሚድሮክ ዛሬ ኢትዮጵያ ውስጥ ትልቁ የገቢም የወጪም ምርት ከመንግስት ልማት ድርጅቶችም በላይ አምራች ነው። ትልቁ ኤክስፖርተር ነው። ትልቁ ደሞዝ ከፋይ ነው። ትልቁ ግብር ከፋይ ነው። ብቸኛው የወርቅ ኮሜርሻል ማይነር ነው። ሻይ ቅጠል፣ ቡና ፣ አበባ፣ የቆዳ ምርቶችን ወዘተ ሳይቀር ለተለያዩ አለማት የሚልክ እጅግ ትርፋማ ድርጅት ሆኖ ቀጠለ።

አቶ ጀማል በዚህ አላበቃም። ባለቤት እንደሌለው ሲዘረፍ የነበረውን የሚሊየኖችን ቤት ያቆመ ድርጅት ዝርፊያውን አስቁሞ ብቻ አልተቀመጠም። ኢትዮጵያ ውስጥ በመንግስት ለሚካሄዱ ትልልቅ “ዜጋ ተኮር” ፕሮጀክቶች ከፍተኛ በጀት በመመደብ ከድሆች ጎን ቆመ። ድሃ የሚወድ ሰው ክብር አለው። አቶ ጀማል ጠቅላይ ሚኒስትሩም እንደመሰከሩለት አይነት ሰው ነው። ባጭሩ ሼህ መሀመድን የሚያኮራ፣ ሐገርን የሚያስጠራ፣ ለሚሊየኖች አለኝታ የሆነን ድርጅት ፈጥሮ አሳየ።

አደራ ጠባቂው አቶ ጀማል ብዙ ሊከበርና ሊደነቅ የሚገባው ሰው ሆኖ አግኝቸዋለሁ። ሰው ማለት የወደቀን የሚያነሳ፣ ሃላፊነቱን የሚያውቅ፣ ላመነው ሰው እምነቱን ሳይሸራርፍ የሚወጣ ፣ በሐገር ፍቅር የተለከፈ፣ ሰራተኞቹን የሚወድ፣ ለደሃ የሚራራ ማለት ነው።

ክብር ለሚገባው ክብር እንሰጣለን! የአቶ ጀማልን ሙሉ ኢንተርቪው ያድምጡት https://youtu.be/g2QH8kPV47M?si=ad6A-i0ffAYqL1Sh

ቁርአን የህይወት መንገዱ፣ጎዳናው ማማሩ፣ከፍታ ላይ መውጫ፣የስኬት መስመሩ፣የልብ ብርሃን ፣የደስታ ቀመሩ፣ቁርአን እኮ ነው ፣የሁሉ ሚስጢሩ፣እዳይስት መስመሩን፣መንገደኛን መርቶ፣ ያበራል ህይወትን...
20/09/2025

ቁርአን
የህይወት መንገዱ፣ጎዳናው ማማሩ፣
ከፍታ ላይ መውጫ፣የስኬት መስመሩ፣
የልብ ብርሃን ፣የደስታ ቀመሩ፣
ቁርአን እኮ ነው ፣የሁሉ ሚስጢሩ፣
እዳይስት መስመሩን፣መንገደኛን መርቶ፣
ያበራል ህይወትን፣በደስታ ተክቶ፣
ከቶ ወዴት ይሆን ፣መሮጥ መገስገሱ፣
ቁርአን ሳይዙ፣ ሳያነቡ ከርሱ፣
አሁኑ እጀምረው፣ማንበብ መማሩን፣
ያኔ ያምርልናል፣ ዱንያ አኼራችን
ያኔ ያምርልናል፣ዱንያ አኼራችን፣ያች የሱና እህቴ የሸሪዓ ፋና
ያቺ ውብ እህቴን ሳያት ተከናንባ፤
የዲኑን ባንዲራ ሂጃቧን ደርባ።
አላህ ያዘዛትን የአቅሟን ከሰራች፤
የሸይጧንን መንገድ አልከተል ካለች፤
ሰላት ከሰገደች ሂጃብ ከለበሰች፤
ለፈረንጆች ባህል አልገዛም ካለች፤
ቦዲውን ጅንሲዉን አውልቃ ከጣለች፤
እሷስ ውብ ናት እንቁ ሀረግ የመሰለች።
የምትከታተል በሰለፎች ፋና ፣
በድኗ ከመጡ የሆነች ቆፍጣና ፣
ሁሌም ትዋባለች በቁርአን ሱና።

 #ከኢትዮጵያ የ12 ክፍል ተማሪወች ከፍተኛውን ውጤት ያመጣውን ጀግና ከቤተሰብ አልፎ  #ለሀገር ኩራት በመሆኑ በድጋሚ እንኳን ደስ አለህ በሉት!
15/09/2025

#ከኢትዮጵያ የ12 ክፍል ተማሪወች ከፍተኛውን ውጤት ያመጣውን ጀግና ከቤተሰብ አልፎ #ለሀገር ኩራት በመሆኑ

በድጋሚ እንኳን ደስ አለህ በሉት!

አይ ዱንያ 😢😢በምስሉ ላይ የምትመለከቱት    (ሳታም አል-ፋይሃ )ይባላል በሀይል ከተማ ሳውዲ አረቢያ ነዋሪ ነው በ መልካም ስነ ምግባሩ እና በኢማኑ የታወቀ ሰው ነበር።ትላንት ይህ ሰው  ከ...
12/09/2025

አይ ዱንያ 😢😢
በምስሉ ላይ የምትመለከቱት (ሳታም አል-ፋይሃ )ይባላል በሀይል ከተማ ሳውዲ አረቢያ ነዋሪ ነው
በ መልካም ስነ ምግባሩ እና በኢማኑ የታወቀ ሰው ነበር።

ትላንት ይህ ሰው ከሚስቱና ከሰባት ወንዶችና ሴቶች ልጆቹ ጋር ሁሌ እንደሚኖረው ኖርማል ሒወት እየኖረ ነበር።

በመጨረሻ ሰአቶቹ ሁለት ነገሮች ነበረ ያደረገው ልጆቹን ሰላት ከመድረሱ በፊት በመናፈሻ ቦታ ተሰብስበው ሲጫወቱ የሚያሳይ ቪዲዮ ፓስት አርጓል፣ ከዛም በሚገርም ሁኔታ መሞቱ የታወቀው ይመስል በትዊተር ገፁ ላይ “ ” የሚል ፁሁፍ ለጠፈ ።

ከጥቂት ሰአታት በሗላ ከባድ የመኪና አደጋ አጋጥሟቸው እሱና ሰባቱ ወንድና ሴት ልጆቹ ህይወታቸው አልፏል። ሁሉም ሞቱ😢
አላህ ይዘንላቸው🤲

ዱንያ እንዲ ናት አለን ስንል ድንገት እልም የምንልባት ጠፊ አለም 🥹

ድንገት ለሚጠናቀቅ ህይወት ለአኼራችን ሚጠቅመንን እንስራ ዛሬን ለማደራችን ምንም ዋስትና የለንም እያንዳንዱን ጊዜ ለሞት ዝግጁ እንሁን ‼

اعْلَمُوا أَنَّمَا الْحَيَاةُ الدُّنْيَا لَعِبٌ وَلَهْوٌ وَزِينَةٌ وَتَفَاخُرٌ بَيْنَكُمْ وَتَكَاثُرٌ فِي الْأَمْوَالِ وَالْأَوْلَادِ ۖ كَمَثَلِ غَيْثٍ أَعْجَبَ الْكُفَّارَ نَبَاتُهُ ثُمَّ يَهِيجُ فَتَرَاهُ مُصْفَرًّا ثُمَّ يَكُونُ حُطَامًا ۖ وَفِي الْآخِرَةِ عَذَابٌ شَدِيدٌ وَمَغْفِرَةٌ مِّنَ اللَّهِ وَرِضْوَانٌ ۚ وَمَا الْحَيَاةُ الدُّنْيَا إِلَّا مَتَاعُ الْغُرُورِ

ቅርቢቱ ሕይወት ጨዋታና ዛዛታ፣ ማጌጫም፣ በመካከላችሁም መፎካከሪያ፣ በገንዘቦችና በልጆችም ብዛት መበላለጫ ብቻ መኾንዋን ዕወቁ፡፡ (እርሷ) በቃዩ ገበሬዎችን እንደሚያስደስት ዝናም፣ ከዚያም በቃዩ እንደሚደርቅና ገርጥቶ እንደምታየው፣ ከዚያም የተሰባበረ እንደሚኾን ብጤ ናት፣ በመጨረሻይቱም ዓለም ብርቱ ቅጣት ከአላህም ምሕረትና ውዴታ አልለ፡፡ የቅርቢቱም ሕይወት የመታለያ ጥቅም እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡(ቁ57:20)
Hijra Tube ኢስላማዊ ድህረ ገፅ

Address

Riyadh

Telephone

+966536725022

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Muslim posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category