Ethio Muslim

Ethio Muslim በሽገር ከተማ ስም የሚፈርሱ መስዶችን እቃወማለዉ መስጂድ ፈርሶየሚገነባ ከተማ የለም🇸🇦🇸🇦🇸🇦🇪🇹🇪🇹🇪🇹

መብሩክ ብያለሁ አልፈ መብሩክ 🫶🏿🥰ለኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ምክትል ተቀዳሚ ፕሬዝዳንት ለክቡር ሼይኽ አብዱልከሪም ሼይኽ በድረዲን እና ለስራና ክህሎት ሚ/ሚንስተር ዲኤታ...
15/12/2025

መብሩክ ብያለሁ አልፈ መብሩክ 🫶🏿🥰
ለኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ምክትል ተቀዳሚ ፕሬዝዳንት ለክቡር ሼይኽ አብዱልከሪም ሼይኽ በድረዲን እና ለስራና ክህሎት ሚ/ሚንስተር ዲኤታ ክብርት ነቢሐ ሙሐመድ አብዱልሃኪም መልካም ጋብቻ ብያለሁ። አላህ በበረካ የተሞላ ትዳር ያድርግላችሁ! 🤲 አሏሁመ ሶሊ ወሰሊም ዓላ ሰይዲና ሙሐመድ 🥰

15/12/2025

ሃጅ በ1994 እንዲህ ነበር

ማንም በልጅ ህመም አይፈተን ! ከዚህ ቀደም የቄራ ሰላም መስጂድ ጀመዓ ሁሉ በመልካም ስሟ የሚያውቃት እህታችን ሰሚራ ልጇ ሀኒፍ ወደ ቱርክ ሀገር ሄዶ በደጋግ ሰዎች እገዛ እና ርብርብ ከነበሩ...
15/12/2025

ማንም በልጅ ህመም አይፈተን !

ከዚህ ቀደም የቄራ ሰላም መስጂድ ጀመዓ ሁሉ በመልካም ስሟ የሚያውቃት እህታችን ሰሚራ ልጇ ሀኒፍ ወደ ቱርክ ሀገር ሄዶ በደጋግ ሰዎች እገዛ እና ርብርብ ከነበሩበት ህመሞች መካከል አንደኛውን ታክሞ ነበር ከአንድ አመት በኃላ ተመልሰሽ አምጪው ብለዋት ወደ ሀገር የተመለሰው።
ለተከታታይ ሁለት አመት በጣም ደህና ሲሆን እና ለውጥ ሲያመጣ እናት ሰሚራም ልጄ ደህና ነው ድጋሚ ለመውሰድም አቅም የለኝም ብላ የሀገር ውስጥ ህክምና ብቻ እየተከታተለች ቆይታ ነበር።
ነገር ግን አሁን ላይ በድጋሚ ወደ ውጪ ሄዶ ህክምና ማድረግ እንዳለበት በሀገር ውስጥ ክትትል የሚያደርጉለት የጥቁር አንበሳ ሆስፒታሎች ቦርድ ነግረዋታል።
እህታችን ሰሚራ ከዚህ በፊት እኛን ወንድም እህቶችዋን እገዛ ጠይቃ ልጇን አሳክማ ስለነበር አሁንም በድጋሚ ሰው አላስቸግርም አላህ እንዳደረገው ይሁን ስትል አንድ ሀኪም እንዲህ አላት። "ከዚህ ቀደም ለመጀመሪያው ህክምና ስትመጪ እና ህክምናውን ከባድ እንደሆነ ስነግርሽ አላህ አለ ጥሎ አይጥለኝም ልጄ ይድናል የአቅሜን አደርጋለሁ" ብለሽ ነበር ምነው አሁን ከአላህ ተስፋ ቆረጥሽ በማለት ሲናገራት እህታችን በድጋሚ እናንተ ደጋግ እህት ወንድሞቿ ፊት የተጠየቀችውን 4,000,000 (አራት ሚሊየን ብር) እገዛ ለመጠየቅ ተገዳለች።

ሁላችንም የአቅማችንን እገዛ በማድረግ ልጇን እናትርፍላት።
አላህ ኒያችሁን ይሙላላችሁ እህት ወንድሞች

1000433513758 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
116309998 አቢሲኒያ
014311316960600 አዋሽ
(ሰሚራ ኑርሰፋ)
+251 90 462 3864

ፖሊስ የጠፋን ህጻን ቤተሰብ ለማግኘት የህብረተሰቡን ትብብር ጠየቀአዲስ አበባ - የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ቤተሰቡ የጠፋበትንና በህመም ላይ የሚገኝን የ4 ዓመት ህጻን ለማፈላለግ የ...
15/12/2025

ፖሊስ የጠፋን ህጻን ቤተሰብ ለማግኘት የህብረተሰቡን ትብብር ጠየቀ

አዲስ አበባ - የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ቤተሰቡ የጠፋበትንና በህመም ላይ የሚገኝን የ4 ዓመት ህጻን ለማፈላለግ የህብረተሰቡን እገዛ ጠይቋል።

ህዳር 30 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፡- ስሙን መናገር ያልቻለውና በግምት 4 ዓመት የሚሆነው ይህ ህጻን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4፣ ቄራ መስኪድ ግቢ ውስጥ ህዳር 16 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 2:00 ሰዓት አካባቢ መገኘቱን የክፍለ ከተማው ፖሊስ አስታውቋል።

ህጻኑ ሲገኝ የመስኪዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ኡስታዝ ሙስጠፋ ወርቁ ለወረዳው ፖሊስ ማሳወቃቸው ታውቋል።

ቤተሰብ እስኪገኝ ድረስ በበጎ አድራጊው አቶ እስማኤል መሀመድ ቤት ውስጥ እንክብካቤ ሲደረግለት ቆይቷል።

በአሁኑ ሰዓት በኢትዮ ጠቢብ ሆስፒታል የህክምና ክትትል ላይ ይገኛል። በጎ አድራጊ ግለሰቦች ለህክምናው የሚጠበቀውን ድጋፍ በማድረግ ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ መሆናቸው ተገልጿል።

የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የህጻኑ ወላጆች ወይም አሳዳጊዎች እንዲገኙ ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ አሳስቧል።

የህጻኑን ቤተሰብ የሚያውቅ ወይም ማንኛውንም መረጃ የያዘ ማንኛውም ግለሰብ በስልክ ቁጥሮች፡

* 011-5-52-80-44
* 011-1-11-01-11

ላይ በመደወል ወይም የፖሊስ መምሪያውን የህጻናትና ሴቶች ምርመራ ክፍል በመሄድ ማሳወቅ እንደሚችል ፖሊስ ባስተላለፈው ጥሪ ጠይቋል።

ህብረተሰቡ የልጆቹ ወላጆች እንዲገኙ ልጥፉን በሼር እንዲተባበሩ ጥሪ ቀርቧል::

Via የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ

🌴🌴🌴

🇸🇦በአስቂኝ ቪዲዩዎቹ የሚታወቀው ፈገግተኛው   በአስቃቂ የመኪና አደጋ ህይወቱ አልፏል። አላህ ይዘንለትበሚገርም ሁኔት በሞተ በ24 ሰአታት ውስጥ በስሙ መስጅድ ለመገንባት 3.7 ሚሊየን ሪያል...
15/12/2025

🇸🇦በአስቂኝ ቪዲዩዎቹ የሚታወቀው ፈገግተኛው በአስቃቂ የመኪና አደጋ ህይወቱ አልፏል። አላህ ይዘንለት

በሚገርም ሁኔት በሞተ በ24 ሰአታት ውስጥ በስሙ መስጅድ ለመገንባት 3.7 ሚሊየን ሪያል ተሰብስቦለታል፣በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎች ጀናዛው ላይ ተገኝተው ዱአ አድርገውለታል።
አላህ የሰው መውደድ ሲሰጥህ እንዲነው♥
Hijra Tube ኢስላማዊ ድህረ ገፅ

ጥያቄ፦ ስመጥር አትሌት ነህ። ገንዘብም አለህ። በውጭ ሀገር እንደምናውቀውም አትሌቶች ቅንጡ መኪኖችን ያሽከረክራሉ። አንተስ ውድ መኪና ለምንድነው የማትነዳው?ቀነኒሳ በቀለ፦ እውነት ለመናገር ...
14/12/2025

ጥያቄ፦ ስመጥር አትሌት ነህ። ገንዘብም አለህ። በውጭ ሀገር እንደምናውቀውም አትሌቶች ቅንጡ መኪኖችን ያሽከረክራሉ። አንተስ ውድ መኪና ለምንድነው የማትነዳው?

ቀነኒሳ በቀለ፦ እውነት ለመናገር በኛ ሀገር ''አለኝ...'' ብለህ ቅንጡ መኪና ይዘህ ለመውጣት ኅሊናህ አይፈቅድልህም። ምክንያቱም ከቤት ወጣ ብለህ እስከምትመለስ ምግብና ማደሪያ አጥቶ የሚለምንህ ብዙ ነው። በዚህ ሁኔታ አንተ ''አለኝ...'' ብለህ በዚህ ሕዝብ ላይ ''ልታይ... ልታይ'' ማለት ምን ያደርጋል?

አንድ አበባል አለ። ደሃ በበዛባት ሀገር ሀብታምም ደሃ ነው!

ታላቁ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በአንድ ወቅት በሚዲያ ካደረገው ንግግሩ የተቀነጨበ።

ሼር በማድረግ ተባበሩት 🙏🙏አሠላም አለይኩም  ሂጅራ  ቤተሰብ ቶፊቅ  እባላለሁ  አዲስ አበባ ኤድናሞል አካባቢ ሞባይል በመሸጥ ነው ቤተሰቤን ማስተዳድረው ከላይ በምስሉ ምትመለከቱት ልጅ   የ...
14/12/2025

ሼር በማድረግ ተባበሩት 🙏🙏

አሠላም አለይኩም ሂጅራ ቤተሰብ ቶፊቅ እባላለሁ

አዲስ አበባ ኤድናሞል አካባቢ ሞባይል በመሸጥ ነው ቤተሰቤን ማስተዳድረው ከላይ በምስሉ ምትመለከቱት ልጅ የተባለ ወይም እኛ ስራ ቦታ ላይ #ዜዶ ብለን ነው ምንጠራው ስራቦታ ላይ ለረጅም አመት ሱቅ ሲላላክ የነበረ ሲሆን

በትናንትና እለት 03.04.18 አርብ እስክመለስ ካዝና ሰብሮ samsung S25 Ultra 2 ፣samsung S24 Ultra 1፣ iPhone 17 pro max 1 በድምሩ 4 ስልክ ዋጋቸው 750,000 ይዞብኝ ተሰውሯል።

ቤተሰቦች ትብብራቹ በጣም ያስፈልገኛል ለጠቊመኝ ወሮታውን እከፍላለዉ

0912-65-91-00
0912-41-43-75
0936-31-15-16

የአዶናይ ወላጅ አባት ብረሃነ ሓይለ ሚካኤል  ኢትዮጵያ ለሚገኘው የካናዳ ኤምባሲ ማመልከታቸው ታውቋል።ማመልከቻው  በማለት ኢሜል ማድረጋቸው ተሰምቷል።ማስረጃዎቹም ተያይዘው ቀርበዋል።ካናዳዊ ሆ...
12/12/2025

የአዶናይ ወላጅ አባት ብረሃነ ሓይለ ሚካኤል ኢትዮጵያ ለሚገኘው የካናዳ ኤምባሲ ማመልከታቸው ታውቋል።ማመልከቻው በማለት ኢሜል ማድረጋቸው ተሰምቷል።ማስረጃዎቹም ተያይዘው ቀርበዋል።ካናዳዊ ሆኖ እያለ እንደት የኢትዮጵያ አዋርድ ላይ ተወዳደረ የሚል ሌላ ጥያቄ ተነስቶ እያየን ነው።

የአዶናይ እናት ትናንት ለቢቢሲ ትግርኛ በሰጡት ቃል
"ልጄ ያጠፋው ነገር የለም። ያሰረው መንግሥት ሁኔታውን አጣርቶ እንደሚለቅቀው አምናለሁ።የራሱን ምቹ ሕይወት ትቶ መጥቶ ሰዎችን የሚያግዝ እኔንም የሚያበረታን ልጄ ነው።" ማለታቸው ይታወሳል።
Wasu Mohammed - Mereja
አሁናዊ ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን join በማድረግ በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4

“ከባሕልና ወግ ባፈነገጠ” መልኩ  መልዕክት አስተላልፈዋል የተባሉ ቲክቶከሮች እስር ዛሬም ቀጥሏልየአዲስ አበባ ፖሊስ ማምሻውን ባሰራጨው መረጃ “ከሀገራችን ባሕልና ወግ ባፈነገጠ መልኩ የማኀበ...
12/12/2025

“ከባሕልና ወግ ባፈነገጠ” መልኩ መልዕክት አስተላልፈዋል የተባሉ ቲክቶከሮች እስር ዛሬም ቀጥሏል

የአዲስ አበባ ፖሊስ ማምሻውን ባሰራጨው መረጃ “ከሀገራችን ባሕልና ወግ ባፈነገጠ መልኩ የማኀበራዊ ሚዲያን ሲጠቀሙ የነበሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው” መሆኑን አስታውቋል።

በቲክቶክ ስሙ Lil_jay ወይም ጎይጋር ኮት ውይዋል እና ከእርሱ ጋር ያልተገባ አፀያፊ ድርጊት ስትፈጽም የነበረችው ኸሊሌ ጊቦ አያና የተባሉ ግለሠቦች የቲክቶክ አካውንት በመጠቀም ለመልካም ጠባይና ሥነ ምግባር ተቃራኒ የሆነ መልዕክትንና ተንቀሳቃሽ ምስልን በቀጥታ ሲያስተላልፉ በመገኘታቸው በቁጥጥር ሥር ውለዋል።

ሁለቱ ወጣቶች በቁጥጥር ሥር የዋሉት ዛሬ ታህሳስ 02/2018 ዓ.ም. በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ልዩ ቦታው ፍሊንትስቶን ሆምስ ከሚባል ቦታ መሆኑን ፖሊስ አስታውቋል። በተመሳሳይ ሁኔታ በዛሬው ዕለት በፖሊስ የተያዘው በቲክቶክ ስሙ ፕሬዚዳንት ማሜ ወይም ባህሩዲን ሙሰማ የተባለው ግለሰብ ነው። ይህም ቲክቶከር “ከሀገራችን ባሕልና ወግ ያፈነገጡ መልዕክቶችን ሲያስተላልፍ” በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ልዩ ቦታው ቦሌ ሚካኤል ጃፋር መስጅድ አካባቢ በቁጥጥር ሥር ውሏል።

ማኀበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ትውልድን ወደ አላስፈላጊ ድርጊት እንዲገባ የሚያስተምሩና የሚገፋፉ መሠል እኩይ ተግባራትን በሚፈጽሙ ግለሠቦችና ቡድኖች ላይ የሚወሰደው ሕጋዊ ርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አሳስቧል

3 ዓመት ሊሞላው 1 ወር  ከ18 ቀን ቀርቶታል አልተገኘም አባት :- ልጄን አፋልጉኝ እባካችሁ ሼር አድርጉልኝህፃን ማሂር ሰይድ ይባላል እድሜው  ሁለት አመት ከስድስት ወር ሲሆን በጋምቤላ ክ...
12/12/2025

3 ዓመት ሊሞላው 1 ወር ከ18 ቀን ቀርቶታል

አልተገኘም

አባት :- ልጄን አፋልጉኝ እባካችሁ ሼር አድርጉልኝ

ህፃን ማሂር ሰይድ ይባላል እድሜው ሁለት አመት ከስድስት ወር ሲሆን በጋምቤላ ክልል ማጃንግ ብሄረሰብ ዞን ሜጢ ከተማ

በ2015 ዓመት ምህረት ጥር 16, ከቀኑ 8:00 ሰዓት አካባቢ ባልታወቁ ሰዎች ሲወሰድ :-

* ባባ 😭
* ባባ 😭
* ባባ 😭

እያለ ቢጮህም ልንደርስለት ግን አልቻልንም 😭??

ይሀው 2 ዓመት
ከ10ወር ከ15 ቀን ሙሉ በመከራና በስቃይ ቆየን

እባካችሁ የኢትዮጵያ ህዝብ ልጄ አፋልጉኝ

* በጣም ናፈቀኝ
* ልጄን አፋልጉኝ

እባካችሁ

* 0911334363
* 0913915460

አባት : ሰይድ መሀመድ

🌴🌴🌴

🕌🇰🇵 !የሰሜን ኮሪያ ፕሬዝዳንት ኪም ጆንግ ዑን "በሃገርቱ ተጨማሪ መስጂዶችን እገነባለሁ በተጨማሪም የሸሪዓ ህግን እተገብራለሁ አለ" ፕሬዝዳንቱ አክሎም "ሰብዓዊነትን ከፍልስጤሞች ተምረናል"...
03/12/2025

🕌🇰🇵 !
የሰሜን ኮሪያ ፕሬዝዳንት ኪም ጆንግ ዑን "በሃገርቱ ተጨማሪ መስጂዶችን እገነባለሁ በተጨማሪም የሸሪዓ ህግን እተገብራለሁ አለ" ፕሬዝዳንቱ አክሎም "ሰብዓዊነትን ከፍልስጤሞች ተምረናል" ነው ያለው።
! 🕌 🇵🇸

በምርጥ የጥበብ ስራዎቹ ባዝናናን ባስተማረን ልክ ያልከፈልነው ባለውለታችን ነው ። አንዳንድ ወዳጆቻችንን ለመደገፍ እስኪወድቁ መጠበቅ ግድ አይመስለኝም።ይስሀቅ ትልቅ የፈጠራ አቅም አለው ድርጅ...
03/12/2025

በምርጥ የጥበብ ስራዎቹ ባዝናናን ባስተማረን ልክ ያልከፈልነው ባለውለታችን ነው ። አንዳንድ ወዳጆቻችንን ለመደገፍ እስኪወድቁ መጠበቅ ግድ አይመስለኝም።

ይስሀቅ ትልቅ የፈጠራ አቅም አለው ድርጅቶች የማስታወቂያ ስራዎችን ብታሰሩት፣ትልልቅ ፋብሪካ ያላችሁ አምራቾች እውቅናውን መያዣ አድርጋች የምርታቹ አከፋፋይ ኤጀንት ብታደርጉት፣ብራንድ አንባሳደር ብታደርጉት በብዙ ታተርፋላችሁ።

ወደ ቀድሞ ስራዎቹ ለመመለስ አሁን ብዙ የሚያስጨንቁት ነገሮች እንዳሉ ጥሩ ሙድ ውስጥ እንዳልሆነ...በጀመራቸው ስራዎች ምክንያት እዳ ውስጥ እንደገባ ነግሮኛል። ዩቲዩብንም ለመጀመር እንኳን እነዚህን እዳ ለመክፈል በሚል በፊት የሚሰራባቸው እቃዎች በሙሉ ሽጧቸዋል። እናም ወደ ቀድሞ ስራው ለመመለስ እዳዎቹን ከፍሎ በአዲስ መንገድ ስራዎቹ ለመመለስ የኛን ድጋፍ ይፈልጋል።

በማንኛውም መንገድ ኢስሃቅን ማገዝ የምትፈልጉ ሰዎች ከስር ባስቀመጥኩት አካውንት የቻላችሁት በማድረግ እዳዎቹን እንዲከፍል እና ወደ ቀድሞ ስራ እንዲመለስ እናድርገው። ሼር በማድረግ ሌሎች እናዳርስ

ንግድ ባንክ 1000598465693 Yishak Zewdu Amare
አቢሲኒያ:- 106172919 Yishak Zewdu

Address

Riyadh

Telephone

+966536725022

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Muslim posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category