Ethio Muslim

Ethio Muslim በሽገር ከተማ ስም የሚፈርሱ መስዶችን እቃወማለዉ መስጂድ ፈርሶየሚገነባ ከተማ የለም🇸🇦🇸🇦🇸🇦🇪🇹🇪🇹🇪🇹

ይህ ፍልስጤማዊ ለልጄ ዱቄት ለሚሰጥልኝ ለማንኛውም ታማሚ ኩላሊቴን ለመስጠት ፍቃደኛ ነኝ ይለል ኩላሊትን በአንድ እሽግ ዱቄት ቀይሩኝ አለ የአላህ 💔🥹
02/08/2025

ይህ ፍልስጤማዊ ለልጄ ዱቄት ለሚሰጥልኝ ለማንኛውም ታማሚ ኩላሊቴን ለመስጠት ፍቃደኛ ነኝ ይለል ኩላሊትን በአንድ እሽግ ዱቄት ቀይሩኝ አለ የአላህ 💔🥹

ስትወለድ ጀምሮ ሙስሊም የነበረች ነው ሚመስለው። ውበቷ ጥንካሬዋ!"አዎ ራቆታችን ነበርን ኢስላም ግን አለበሰን"አለች። ይሄን ውበት እንኳን እሳት አልበ,ላው! እኔ ወድጃታለሁ የናንተን አላውቅ...
02/08/2025

ስትወለድ ጀምሮ ሙስሊም የነበረች ነው ሚመስለው። ውበቷ ጥንካሬዋ!

"አዎ ራቆታችን ነበርን ኢስላም ግን አለበሰን"አለች።

ይሄን ውበት እንኳን እሳት አልበ,ላው! እኔ ወድጃታለሁ የናንተን አላውቅም

ግብፅ😳😡😡😡😡ግብጽ በጋዛዉያን ላይ እስራኤልን ካልሆንኩ ሙቼ እገኛለሁ ብላለች ጧት 180 መኪና ወደ ጋዛ ቢገባም ይህ የምትመለከቱት ሁሉ መኪና ግብጽ ወደ ጋዛ እንዳይገባ መግቢያዉን በወታደር ...
25/07/2025

ግብፅ😳😡😡😡😡
ግብጽ በጋዛዉያን ላይ እስራኤልን ካልሆንኩ ሙቼ እገኛለሁ ብላለች ጧት 180 መኪና ወደ ጋዛ ቢገባም ይህ የምትመለከቱት ሁሉ መኪና ግብጽ ወደ ጋዛ እንዳይገባ መግቢያዉን በወታደር ክርችም አድርገዋለች የአላህ እርግማን አልሲሲ ላይ ይዉረድ☝️የጋዛ ረሃብ ወደ አንተ ላይ ያንዣብብ☝️

ግብፅ😳😡😡😡😡ግብጽ በጋዛዉያን ላይ እስራኤልን ካልሆንኩ ሙቼ እገኛለሁ ብላለች ጧት 180 መኪና ወደ ጋዛ ቢገባም ይህ የምትመለከቱት ሁሉ መኪና ግብጽ ወደ ጋዛ እንዳይገባ መግቢያዉን በወታደር ...
25/07/2025

ግብፅ😳😡😡😡😡
ግብጽ በጋዛዉያን ላይ እስራኤልን ካልሆንኩ ሙቼ እገኛለሁ ብላለች ጧት 180 መኪና ወደ ጋዛ ቢገባም ይህ የምትመለከቱት ሁሉ መኪና ግብጽ ወደ ጋዛ እንዳይገባ መግቢያዉን በወታደር ክርችም አድርገዋለች የአላህ እርግማን አልሲሲ ላይ ይዉረድ☝️የጋዛ ረሃብ ወደ አንተ ላይ ያንዣብብ☝️

24/07/2025
አትቀልዱ ምርጫው የ10ሺህ  ሰዎች ነውና!💥💥💥♦♦♦♦🔥🔥🔥🎯🎯🎯በአሕመዲን ጀበል🔺🔺🔺🔺🔺የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮችን ምክር ቤትን(መጅሊስን) ምርጫ ስናስብ በሀገር ደረጃ ያሉትን የፌደራል መጅሊ...
24/07/2025

አትቀልዱ ምርጫው የ10ሺህ ሰዎች ነውና!
💥💥💥♦♦♦♦🔥🔥🔥🎯🎯🎯
በአሕመዲን ጀበል
🔺🔺🔺🔺🔺

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮችን ምክር ቤትን(መጅሊስን) ምርጫ ስናስብ በሀገር ደረጃ ያሉትን የፌደራል መጅሊስ የጥቂት የሥራ አስፈጻሚ አመራሮች ምርጫ እንደሆነ እያሰብን ከሆነ ለስህተት እንዳረጋለን። በዚህ ምርጫ የሚመረጡት ጥቂት ግለሰቦች ሳይሆኑ ከፌደራል እስከ የወረዳ እርከን መጅሊስ ላሉ ሥፍራዎች የሚሆኑ የ10ሺህ ሰዎች ምርጫ ነው። ይህም፦

ሀ) ለፌደራል መጅሊስ 15 አባለት ይመረጣሉ።

ለ) ለክልል መጅሊሶች ለእያንዳንዳቸው 13 የሥራ አስፈጻሚ አባላት ሲመረጡ በሀገሪቱ ላሉ ለ12 ክልሎችና 2ቱ የከተማ መስተዳደሮች በድምሩ 182(አንድ መቶ ሰማኒያ ሁለት ሰዎች) ሰዎች ይመረጣሉ።

ሐ) ለእያንዳንዱ ዞን 11 የሥራ አስፈጻሚዎች ሲመረጡ በአጠቃላይ ሀገሪቱ ባሉ 119 ዞኖችና በዞን ደረጃ ላሉ ከተሞች በድምሩ 1,309(አንድ ሺህ ሦስት መቶ ዘጠኝ ተመራጮች) ሰዎች ይመረጣሉ።

መ) ለእያንዳንዱ ወረዳ 9 የሥራ አስፈጻሚ አባላት ሲመረጥ በሀገሪቱ ላሉ 914 ወረዳዎችና ልዩ ወረዳዎች በድምሩ 8,226 (ስምንት ሺህ ሁለት መቶ ሃያ ስድስት) ተመራጮች ይመረጣሉ።

ሠ) በመላ ሀገሪቱ ከፌደራል እስከ ወረዳ በሁሉም እርከኖች በድምሩ 9, 732(ዘጠኝ ሺህ ሰባት መቶ ሰላሳ ሁለት) የመጅሊስ የሥራ አስፈጻሚዎች በዚህ ምርጫ ይመረጣሉ ማለት ነው።

ረ) ከወረዳ በታች የቀበሌ መዋቅር ያለባቸውን የሀገሪቱን አከባቢዎችን ምርጫን ከጨመርንበት የተራጮች ብዛት በእጅጉ ያድጋል። ምርጫው የሚደረገው በመስጂድ ደረጃ በመሆኑ በእያንዳንዱ ወረዳ(ወይም ቀበሌ) ዉስጥ ባሉ ምርጫ በሚካሄድባቸው መስጂዶች ላይ ለየወረዳው (ቀበሌው) የሥራ አስፈጻሚነት እጩነትና ለወረዳ መጅሊስ ምክር ቤት የሚመረጡትን ሁሉንም ተመራጮችን ስንጨምርበት የተመራጮች ብዛት በብዙ እጥፍ ይጨምራል። በመሆኑም ምርጫው የ10ሺዎች ምርጫ በመሆኑ እንደቀልድ ሊታይ አይገባም። በዚህ ረገድ ምርጫው ስኬታማ እንዲሆን የሚከተሉትን ወሳኝ ነጥቦችን በአንክሮ ማየት የግድ ይላል።

1) ምርጫው የሚጀምረው ለየወረዳው የሚሆኑ ሰዎችን በመስጂድ ደረጃ በማስመረጥ ነው። ቀጥሎ በወረዳ ደረጃ ከተመረጡ ሰዎች ዉስጥ ተመራጮች እርስ በእርስ እየተመራረጡ እስከ ፌደራል መጅሊስ ይሄዳሉ። ይህ የሚሆን ከሆነ ደግሞ በየወረዳው የሚመረጡ ሰዎች ምናልባት ወደላይ ሄደው የክልል ወይም የፌደራል መጅሊስ አመራር ሊሆኑ ይችላሉ ማለት ነው። ስለሆነም ለወረዳም ብለን የምንመርጣቸው ሰዎች ለወረዳ እርከንም ቢሆን ከፍተኛ ብቃት ያላቸውና ለፌደራል መጅሊስ የሥራ አስፈጻሚ ጭምር መሆን በሚችሉ ደረጃ ያሉ ሰዎችን ለይቶ በጥንቃቄ መምረጥ ይገባል ማለት ነው።

2) በመስጂድ ደረጃ በሚደረገው ምርጫ በሁሉም ሥፍራ እያንዳንዱ ሰው የአመራር ክህሎት የሌለው፥ ለሕዝበ ሙስሊሙና ዲኑ ታማኝነቱን የሚጠራጥርና የሕዝቡን ጥቅም አሳልፎ የሚሰጥ ሰው እንዳይመርጥ ብርቱ ምክክርና ጥረት ካደረገ ሁሉም ተመራጭ የሚመጣው በመስጂድ ብቻ በመሆኑ አስመራጮቹ ታማኞች እስከሆኑ ድረስ በመስጂድ ያልተመረጠ ሰው በሌላ መንገድ ወደ ምርጫው ስርዓት መግባት አይችልም። ስለሆነም ለመጅሊስ ተገቢውን ሰው የመምረጥ ጥረትና ጥንቃቄ ቁልፉ ስፍራ በመስጂድ ደረጃ የሚደረገው ምርጫ ነውና ተገቢውን ሰው ለመምረጥ ጥልቅ ምክክርና ጥረት ማድረግ ያስፈልጋል።

3) በመላ ሀገሪቱ ለሁሉም የመጀሊስ እርክን የሚመረጡትን 10ሺህ ተመራጮች ማንነት፥ ብቃትና ደረጃ የማወቅ እድል የለህም። ያንተ እድል ባንተ ሰፈር መስጂድ የሚመረጡትን በአግባቡ መምረጥ ነው። ስለሆነም እያንዳንዳችን በየሰፈራችን መስጂድ ለወረዳችን መጅሊስ የሚመረጡትን አካላት በጥንቃቄ ከመረጥን በተዘዋዋሪና በጋራ 10ሺህ ሰዎችን እንደመረጥን ሊወሰድ ይችላል።

4) እስካሁን እንዳብራራነው ምርጫው የሚካሄደው ከታች ጀምሮ ወደላይ ተመራጮችን በየእርከኑ በመምረጥ ነው። በማህበራዊ ሚዲያ ላይ እገሌ የኔ ምርጫ ነው። እርሱን መርጬዋለሁ።» የሚለው የአየር ላይ ምርጫ አንዳች ዉጤት አያመጣም። ምርጫው የሚደረገው በየመስጂዱ በመሆኑ በአየር ላይ መረጥኩት ያልከው አካል በሰፈሩ ያሉ የመስጂድ ጀመዓዎች ካልመረጡት ወደ መጅሊስ አይመጣም። ስለሆነም ትኩረትህንና ትኩረትሽን ወደ ሰፈራችሁ መስጂድ በማድረግ እነማንን እንደምንመርጥ ምክከር በማድረግ በጋራ መዘጋጀት ነው። በተጨማሪም በማህበራዊ ሚዲያም ሌሎችም በየሰፈራቸው ብቁና ተፈላጊ ሰዎችን እንዲመርጡ ማነሳሳት ይቻላል።እኔም በሚዲያዎች ስለመጅሊስ ምርጫ ግንዛቤ ለማስጨበጥ እያደረግኩት ያለሁት ጥረት 10ሺህ ተመራጮቹን በየአከባቢው ተከፋፍሎ የሚመርጠው ሕዝበ ሙስሊሙ የመጅሊስን ተልዕኮን የሚያሳኩ ሰዎችን እንዲመርጥ ለማገዝ ነው።

5) አንድ ንጉስ ነበር። ንጉሠን ብዙ ሰዎች ይወዱታል። ንጉሡም ምን ያክል ሰዎች እንደሚወዱት ማወቅ ፈለገ። የሚወዱትን ሰዎችን ለመለየት ይረዳው ዘንድ በአደባባይ ላይ ትልቅ ባርሜል አስቀመጠ። እያንዳንዱ እርሱን የሚወዱት ሰዎች እየመጡ በባርሜሉ ቀዳዳ አንድ ኩባያ ወተት እንዲጨምሩ አዘዘ። ሰዎች እየመጡ በባርሜሉ ቀዳዳ መጨመር ጀመሩ። አንደኛው የንጉሡ ወዳጅ «ሁሉም ሰው ወተት ይጨምራል። እኔ ዉሃ ብጨምር ማን ያያኛል? በዚያ ላይ ሌሎቹ ወተት ስለሚጨምሩ የኔ ዉሃ መጨመር ምንም የሚያመጣው ለውጥ የለም» ብሎ አስቦ በኩባያ ዉሃ በማምጥት ጨመረ።

የመጨመሪያው ጊዜ አበቃና ባርሜሉ ተከፍቶ ሲታይ ሁሉም ዉሃ ሆኖ ተገኘ። ለካ እንደዚያ ሰውዬ የየራሱን ሚና ሳይወጣ «ሌሎች ወተት ይጨምራሉ። የኔ ዉሃ መጨመር ምንም ለውጥ አያመጣም» እያሉ ዉሃ ሲጨምሩ ነበር። ከዚህ የተነሳ ባርሜሉ ሙሉ ወተት ሳይሆን ዉሃ ሆኖ ተገኘ። ሕዝቡ ንጉሡን ቢወደውም በተግባር ግን ኃላፊነቱን ባለመወጣቱ ንጉሡን እንደማይወደው ተቆጠረ።

የኛም ነገር እንደዚያ እንዳይሆን መጠንቀቅ ያስፈልገናል። ሁላችንም የሕዝበ ሙስሊሙ ሁኔታና የመጅሊስ ነገር እንደሚመለከተን እናምናለን። እስካሁን በነበሩት የመጅሊስ አስተዳደሮች ላይ ያለን የግምገማ መጠኑ ይለያይ እንጂ ከእስካሁኖቹ የተሻለ መጅሊስ እንደሚያስፈልገን እናምናለን። እንፈልጋለንም። ወንድም ዶ/ር ኢብራሂም ሙሉ ሸዋ እንዳለው «መጅሊስን ብንተወው እንኳ እርሱ አይተወንም።» ስለሆነም ሳይረፍድ በዚህ ምርጫ ወደ መጅሊስ ብቁ፥ንቁና ታማኝ የሆኑ አመራሮችን በመምረጥ ሚናችን እንወጣ።በስልሳ ሚሊዮን ሙስሊሞች ጉዳይ አትዘናጉ።የየበኩላችሁን ሚና መወጣት ሲገባችሁ ምርጫውን እንደቀልድ አትመልከቱት። ምርጫው የ10ሺህ ሰዎች ነውና!

Eustaz abubkere አልሀምዱ ሊላህ ከባለቤቴ ጋር ከተጋባን ድፍን 22 ዓመት ሞላን አራቱን የመጀመሪያ ዓመታት በሳውዲ አሳልፈናል እዛ በቆየንባቸው ዓመታት አብረን ዑምራወችን እንዲሁም  ...
23/07/2025

Eustaz abubkere አልሀምዱ ሊላህ ከባለቤቴ ጋር ከተጋባን ድፍን 22 ዓመት ሞላን አራቱን የመጀመሪያ ዓመታት በሳውዲ አሳልፈናል እዛ በቆየንባቸው ዓመታት አብረን ዑምራወችን እንዲሁም ሀጅ አላህ ወፍቆናል አላህ ይቀበለን! ከዚያ ተመልሰን አገር ከገባን ደሞ አሁን 18 ዓመት ሆነን ።
እኔ ወደ አገር ጠቅልለን ከገባን ቡኃላ በተደጋጋሚ አላህ ለሀጅም ለኡምራም ቢወፍቀኝም ባለቤቴ ግን ልጆቿንና ቤቷን ትኩረት አድርጋ እስከ አሁን መሄድ አልቻለችም።

ባለቤቴ በጣም ለእኔ ምቹና ፀባየ ሸጋ ነች እነዚህ 22 የትዳር ዓመቶችን አብረን የዘለቅነው ከአላህ ችሮታና እዝነት ቡኃላ በእርሷ ትዕግስትና ምግባረ ሰናይነት ነው ማለት እችላለሁ እኔማ ብስጩና ተናዳጅ እንዲሁም አስቸጋሪ ከሚባሉ ባሎች የምመደብ ሳልሆን አልቀርም። የሆነ ሆኖ እርሷ ሀሳቤን ሳትነቅፍ ፣ እኔ ላይ ሳታፈጥና ሳትረብሽ ለዚህ በቅተናል።

إذا صلت المرأة خمسها وصامت شهرها وحفظت فرجها وأطاعت زوجها قيل لها ادخلي الجنة من أي أبواب الجنة شئت

ሴት ልጅ አምስት አውቃት ሶላቷን ከሰገደች በአመት አንድ ወሯን ከጦመች ከዝሙት እራሷን ከጠበቀች ለባሏ ታዛዥ ከሆነች የትንሳኤ ቀን በፈለግሽው የጀነት በር ግቢ ትባላለች) ተብሎ በአሽረፈል ኸልቅ ከተዘገበላቸው ሴቶች ውስጥ የእኔዋ መልከኛ እና አመለ ሸጋዋ ውዷ ባለቤቴ አንዷ ትመስለኛለች ።

ሁል ጊዜ ለግል ጥቅሟ የምትጓጓ አይደለችም እኔ ለዑምራ በተነሳሁ ቁጥር ልጆቿ ባባ እሷንስ አትወስዳትም? የሚል ጥያቄ በተደጋጋሚ ሲያነሱ መልስ የምትሰጠው እርሷ ነች አባታችሁ ሁኔታወች ሲመቻቹለት ይወስደኛል ትላቸዋለች።
እናማ ትናንትና ኡምራ ለሚሄዱ ሰወች ስልጠና እሰጥ ነበርና በዚህ ጉዞየ ውዷን ባለቤቴን ሳልነግራት ለመውሰድ ነይቸ ጉዳዩንም ጨርሸ ስለነበር መላ ቤተሰቤን ወደ ኡምራ ከመሄዴ በፊት እራት እጋብዛችኋለሁ ግን ግብዧው ከስልጠና ቡኃላ ነው ብየ አዳራሽ ውስጥ አስገብቻቸው እዛው ለእናታቸው የኡምራ ጉዞ እድሉን ቪዛና ትኬቷን አስረክቢያታለሁ ።
"تهادوا تحابوا"
ተብሎ የለ
ያ አሏህ በእኛ ሙስሊሞች ልብ ውስጥ ሀረመይን ያለውን ቦታ ከእርሷ ፊት ላይ አየሁት ደስታዋ ወደር አልነበረውም ለካስ የሀረመይን ፍቅር ባዩት ላይ ይጠናል የተባለው ትክክል ነው ሰውነቷ ከደስታ ብዛት ተንቀጠቀጠ፣ አነባች አለቀሰች ፣ የተከሰተውንም ማመን አቃታት እራሷን ሳትስትብኝ ሁሉ ብየ ደነገጥኩ የትልቋ ልጃችን ለቅሶ ደሞ የባሰ አስደንግጦኛል አላህ…
መተሳሰብ መፋቀር መዋደድ እንዴት ደስ ይላል ሌሊቱን መላ ቤተሰቡ በደስታ አደርን ሰኞ ኢንሻአላህ ወደ ሀረም እናቀናለን!

ለማንኛውም ባለ ትዳር እህቶች ከእርሷ ብዙ ትማራላችሁ ብየ ነው ይህን የከተብኩት

እህቴ ሆይ በባለቤትሽ ላይ ታጋሽ ከእርሱ አፀፋ የማትፈልጊ አፍቃሪ ፣ቤተሰቦቹን አክባሪ በጎ ሰው በመሆን ለባልሽ መተናነስን ካሳየሽና ለእርሱ አገልጋይ ከሆንሽ እርሱም (ሚስሉን ቢሚስል ) በሚለው ሚዛን ለአንች አገልጋይ ባሪያ ይሆንልሻል መልእክቴ ነው!

አላህ ሁላችንንም እሱ ለሚወደው ነገር ሁሉ ያብቃን !!
እኛንም ባሎችን
خيركم خيركم لأهله
ከእናንተ ውስጥ በላጮቹ ለባለቤቱ ኸይረኛ የሆነው ነው ተብሏልና ኸይረኞች ያርገን !!

04/07/2025
ጃቢርን ተክዞ ሲመለከቱት «ጃቢር ሆይ!  ምነው ተከዝክሳ? » አሉት። «ያ ረሱለላህ አባቴኮ ሸሂድ ሆነ ፣ ቤተሰብም እዳም ጥሎ ነው የሔደው»  አላቸወ። አላህ ባባትህ ላይ የሰራውን ለምን አላ...
04/07/2025

ጃቢርን ተክዞ ሲመለከቱት «ጃቢር ሆይ! ምነው ተከዝክሳ? » አሉት። «ያ ረሱለላህ አባቴኮ ሸሂድ ሆነ ፣ ቤተሰብም እዳም ጥሎ ነው የሔደው» አላቸወ።

አላህ ባባትህ ላይ የሰራውን ለምን አላበስርህም? አላህ ለማንም ያላደረገውን አባትህን በቀብር ውስጥ በቀጥታ አናግሮታል። ባሪያዬ ሆይ ተመኝ? አለው ። እርሱም «ጌታዬ ሆይ! ወደ ዱንያ መልሰኝና ባንተ መንገድ ዳግም ልገደል? ብሎ ጠየቀው።

አላህም « አንዲት ነፍስ ከሞት በኋላ ወደርሷ ላትመለስ ቃሌ ነው» አለው። ጌታዬ ሆይ! እንግዲያውስ ከኔ ኋላ ላሉት ይህን ብስራት አብስርልኝ አለው። አላህም፦

{ولا تحسبن الذين قتلوا في سبيل الله أمواتا بل أحياء عند ربهم يرزقون}
የሚለውን አንቀፅ አወረደ።

«እነዚያን በአላህ መንገድ የተገደሉትን ሙታን ናቸው ብለህ አታስብ፤ ይልቁንም ጌታቸው ዘንድ ሲሳይን እየተለገሱ ህያው ናቸው» (ኣለ ዒምራን 169)

ዐብዱላህ ቢን ሐራም ሰሃባ የሶሃባ አባት! ረዲየላሁ ዐንህ! ነገ ኡሁድ ሊሆን ለሊት ላይ ልጁን ጃቢርን ጠራው።

ጃቢር ሆይ! ነገ መጀመሪያ ከሚገደሉት የረሱል ﷺ ባልደረቦች ውስጥ ስሆን ይታየኛል። ከረሱል ﷺ በመቀጠል ጥዬ የምሞተው ውድ ሰው አንተ ልጄ ነህ ። እዳዎቼን ክፈል፣ እህቶችህን ተንከባከብ። በማለት ተናዘዘው።

ሲነጋም ከመጀመሪያዎቹ ሸሂዶች ሆነ።

ዛሬ ላይ አለም አቀፍ ወንጀል የተደረገው ጂሃድ አላህ ዘንድ ሽልማቱ እንዲህ ነበር።
የቴሌግራም ቻናል ፦ t.me/ismaiilnuru

ይህ የተውሒድ ምልክት ነው።ተውሒድም ከአላህ ውጭ ማንንም አልመፍራት ነው።ጣቢያው ሲመታ ይህች እንስት በቀጥታ ስርጭት ለኢራናዊያን የፅናትን መልዕክት እያስተላለፈች ነበር።ጥቃቱ እንደተፈፀመም ...
24/06/2025

ይህ የተውሒድ ምልክት ነው።ተውሒድም ከአላህ ውጭ ማንንም አልመፍራት ነው።ጣቢያው ሲመታ ይህች እንስት በቀጥታ ስርጭት ለኢራናዊያን የፅናትን መልዕክት እያስተላለፈች ነበር።ጥቃቱ እንደተፈፀመም የሚሰማው ድምፅ "አላሁ አክበር!" የሚል ነው።አላህ ታላቅ ነው።

ይህች የኢራን ብሔራዊ ጣቢያው ጋዜጠኛ በላይቭ ስርጭት ላይ ሳለች ነው ስቱዲዮዋ በአየር ጥቃት በከፍተኛ ድምፅ የፈነዳው።አምስት ደቂቃ ሳይሞላም በራሱ ጣቢያ ምንም እንዳልተፈጠረ ስራዋን ቀጥላለች።ዘይነባዊት እንስት!

ኢራን በጧቱ የእስራኤልን ከተማ እያፈ*ረሰች መሆኑን የተመለከተው ትራምፕ "ተው ስምምነቱን አታፍርሱ እባካችሁ" የሚል ልመና አስተላልፏል። ያ የትራምፕ ዛቻ ያ ድንፋታ በኢራኖች ክንድ ተንፍሷል...
24/06/2025

ኢራን በጧቱ የእስራኤልን ከተማ እያፈ*ረሰች መሆኑን የተመለከተው ትራምፕ "ተው ስምምነቱን አታፍርሱ እባካችሁ" የሚል ልመና አስተላልፏል። ያ የትራምፕ ዛቻ ያ ድንፋታ በኢራኖች ክንድ ተንፍሷል። አሁን ጦርነቱን ከፈለጉ ያቆሙታል ካልፈለጉ ያስቀጥሉታል።

ስታሸንፍ እንዲህ ጠላትህን ለማኝ ታደርገዋለህ።
ሱልጣን አህመድ

Address

Riyadh

Telephone

+966536725022

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Muslim posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category