ቋንቋዬ ነሽ ሚዲያ Quanquayenesh Media

ቋንቋዬ ነሽ ሚዲያ Quanquayenesh Media የቴክኖሎጂ ፈረስ በፈለገበት እንዳይዘውረን በሃይማኖት ልጓም ይዘን የሚጠቅመውን እናስተላልፍበታለን
(3)

♦️ ኩታበር ደብረ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሊመረቅ ነው።
25/09/2025

♦️ ኩታበር ደብረ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሊመረቅ ነው።

♦️አስደሳች  ዜና ከግሸንከሸንኮራ ዮሐንስ እስከ ግሸን በእግርየግሸን ደብረ ከርቤ የንግሥ በዓልን ለማክበር ከሰሜን ሸዋ ምንጃር ሸንኮራ (ሸንኮራ ዮሐንስ) መነሻቸውን አድርገው የእግር ጉዞ የ...
25/09/2025

♦️አስደሳች ዜና ከግሸን

ከሸንኮራ ዮሐንስ እስከ ግሸን በእግር

የግሸን ደብረ ከርቤ የንግሥ በዓልን ለማክበር ከሰሜን ሸዋ ምንጃር ሸንኮራ (ሸንኮራ ዮሐንስ) መነሻቸውን አድርገው የእግር ጉዞ የጀመሩ መንፈሳዊ ተጓዦች ግሸን አምባ በሰላም ደርሰዋል።
በተጨማሪም ከትግራይ፣ ከጎጃም ፣ ከጎንደር ፣ ከላሊበላ ፣ ከሰቆጣ እና ከተለያዩ አካባቢዎችም በእግር ጉዞ አድርገው በርካቶች በሰላም ግሽን ደርሰዋል ።

ይህን ያደረገ እግዚአብሔር ይመስገን።

የግሸኗ እመቤት በመንገድ ላይ ያሉትንም ልጆቿን በሰላም እቅፍ ድግፍ አድርጋ ለደጇ ታብቃልን!!!

👉ዘገባው የግሸን ማርያም ሚዲያ ነው

✝️እልልልልል
25/09/2025

✝️እልልልልል

ደብረ ከርቤ

25/09/2025

✝️ዕለቷ ደረሰች ፫ ቀናትም ብቻ ቀራት ።

ኩታበር አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን። ከደሴ ወደ ግሸን ስትሄዱ 18 ኪሎ ሜትር ላይ የሚገኘው ከተማ።

ደጁን ሳትረግጡ ከጻድቁ በረከት ሳትካፈሉ እንዳታልፉ አደራራራራ።

በሩቅ ያላችሁ ደግሞ እግራችሁ ባይደርስ እንኳ እጃችሁና ድምጻችሁ መድረስ ይችላል።

1000636704303 ንግድ ባንክ ኩታበር ደብረ ቅዱሳን ሕንጻ አስመራቂ

✝️ ለሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም ጥቅምት ፭ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር እንደሚያካሂድ ተገለጸ።በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክር...
24/09/2025

✝️ ለሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም ጥቅምት ፭ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር እንደሚያካሂድ ተገለጸ።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት በምስራቅ በለሳ ወረዳ ቤተ ክህነት ሥር በሚገኘው በሙታንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም በ አስራ አንድ ወራት ብቻ ሰፊ የልማት ሥራዎችን ማከናወን መቻሉ ተገለጸ።
በገዳሙ የሚገኙ ገዳማውያን በበዓታቸው ጸንተው እንዲኖሩ ብሎም ምዕመናን በረከት እንደ ያገኙ ቀጣይ ሥራዎችም መታቀዳቸው ተገልጿል ።
የተጠናከረ የአብነት ት/ቤት ፣ዘመናዊ ት/ቤት ፣ ክሊኒክ ከታቀዱት መካከል መሆናቸው ተገልጿል።
በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ተገኝተው አባታዊ መመሪያ እና መልዕክት ያስተላለፉት ብጹዕ አቡነ መቃርዮስ የምዕራብ ካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሁሉም ኦርቶዶክሳዊያን ገዳሙን እንዲያግዙ አደራ ብለዋል ።

ሁለንተናዊ ልማትን ለማጠናከር እና ለማከናወን በሚሊኒየም አዳራሽ ጥቅምት ፭ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር እንደሚካሄድ የተገለጸ ሲሆን ለመላው ኦርቶዶክሳዊያን ጥሪ ቀርቧል ።
በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል በተዘጋጀው መግለጫ ብፁዕነታቸውን ጨምሮ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት እና ከሀገረ ስብከቱ አባቶች ተገኝተዋል።

✝️የ፲፬ (14) ዓመት ናፍቆት... ሊፈፀም ፫ቀናት ብቻ ቀሩት። ኩታበር አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን። ከደሴ ወደ ግሸን ስትሄዱ 18 ኪሎ ሜትር ላይ የሚገኘው ከተማ።ደጁን ሳትረ...
24/09/2025

✝️የ፲፬ (14) ዓመት ናፍቆት...

ሊፈፀም ፫ቀናት ብቻ ቀሩት። ኩታበር አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን። ከደሴ ወደ ግሸን ስትሄዱ 18 ኪሎ ሜትር ላይ የሚገኘው ከተማ።

ደጁን ሳትረግጡ ከጻድቁ በረከት ሳትካፈሉ እንዳታልፉ አደራራራራ።

በሩቅ ያላችሁ ደግሞ ደስታችሁን ባላችሁ ነገር ግለጡ። ምርቃት መቼም ባዶ እጅ አይመጣምና በዚህም መምጣት ትችላላችሁ።

1000636704303 ንግድ ባንክ ኩታበር ደብረ ቅዱሳን ሕንጻ አስመራቂ

24/09/2025

✝️ አድራሻዬ ኦርቶዶክስ ናት... እንኳን አደረሳችሁ

24/09/2025

የከቨር እና አጭር የስቱዲዮ መዝሙራት ሰሪዎች

አዳዲስ ዘማርያን በአገልግሎት እንድትበረቱ መዝሙር እየሰራን እንሰጣችኋለን። እየሰጠናችሁም ነው። የሰውን መዝሙር ግን ያውም ያለዘማሪው ፈቃድ ሰርቶ መገለጥ ልክ አይደለም። የደራሲውን፣ የዘማሪውን፣ የፕሮዲወሰሩን መብት መጣስ ነው። እናንተም በራሳችሁ የማትቆሙ የራሳችሁ መንፈሳዊ ታሪክ የሌላችሁ ትሆናላችሁ። እግዚአብሔር ባለጠጋ ነው። አዲስ መዝሙር ዘምሩ። ህጋዊ ያልሆነ ስራ ግን ለሚዲያችሁም ችግር ያመጣል። ተው። በራሳችሁ ሥራ እንድንሰማችሁ እንናፍቃለን።

23/09/2025

✝️ ስለ መስቀል በዓል አከባበር የብጹዕ ሥራ አስኪያጁ መልእክት።

✝️ መስከረም ፲፮ እና ፲፯ ቀን ፳፻፲ወ፰ ዓ.ም በታላቅ ድምቀት የሚከበረውን  የመስቀል በዓል አስመልክቶ ከብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የሸገር ከተማ እና የ...
23/09/2025

✝️ መስከረም ፲፮ እና ፲፯ ቀን ፳፻፲ወ፰ ዓ.ም በታላቅ ድምቀት የሚከበረውን የመስቀል በዓል አስመልክቶ ከብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የሸገር ከተማ እና የደቡብ ምዕራብ ሸዋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የምስካዬ ኅዙናን መድኀኔዓለም ገዳም የበላይ ኃላፊ የተሰጠ መግለጫ ፡፡

ወወሀብኮሙ ትእምርተ ለዕለ ይፈርሑከ።ከመ ያምስጡ እምገጸ ቅስት፣ወይድኃኑ ፍቁራኒከ

ለሚፈሩህ ምልክትን ሰጠሃቸው..... (መዝ. 59/60፡4)

በመላዋ ኢትዮጵያና በዓለም ሁሉ የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልጆች፣ እንኳን ፳፻፲ወ፰ ዓ.ም ዘመነ ማርቆስ በዓለ መስቀል አደረሳችሁ፡፡

መስቀል የሰላም፣ የፍቅርና የዕርቅ ምልክት ነው። ቅዱስ ዳዊት ከቀስት ፊት ያመልጡ ዘንድ ለሚፈሩህ ምልክትን ሰጠሀቸው ብሎ እንደተናገረው የአዳም ልጆች ሁሉ ከጠላት ዲያብሎስ ወጥመድና ከጠላት ቀስት ያመለጡበት ምልክት መስቀል ነው፡፡ በቀደመ በደሉ ከእግዚአብሔር ርቆ የነበረ ሁሉ በመስቀል ተስቦ ወደ ክርስቶስ ቀርቧል፡፡

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በኤፌሶን መልእክቱ ፪ ፥ ፮ እንደተናገረው

“ጥልንም በመስቀሉ ገድሎ በእርሱ ሁለታቸውን በአንድ አካል ከእግዚአብሔር ጋር ያስታርቅ ዘንድ ነው”፡፡ በኃጢአት ምክንያት በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ጥል ነበረ፡፡ ይህን ሰው ከእግዚአብሔርና ሰው ከሰው ተጣልቶ የነበረበትን ጥል ክርስቶስ በመስቀሉ አስወግዶታል፡፡ ክርስቶስ በመስቀሉ ሰውን ከራሱ ጋር አስታረቀ፣ ሕዝብና አሕዛብንም አንድ አደረገ፡፡

መስቀል እግዚአብሔር ዓለምን የታረቀበት፣ ለዘለዓለም ሕይወት የሚሆን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን የሰጠበት ክርስቶስ የሚታይበት የመዳን ምሥጢር ነው፡፡ በዚህ ምክንያት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መስቀልን እጅግ ከፍ ከፍ አድርጋ ታከብረዋለች፡፡ በዓለ መስቀልን የምናከብረው በመስቀሉ የተደረገልንን በማሰብና ጌታችንና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስን በማመስገን ነው፡፡ ይህን በተመለከተ ቅዱስ ያሬድ “በመስቀልከ ክርስቶስ ረዳእከነ፣ በመስቀልከ እሞት ባላሕከነ፣ ሕይወተ ጸጎከነ፣ ወወሃብከነ እምጽልመት ብርሃነ - ክርስቶስ ሆይ በመስቀልህ ረዳኸን፣ በመስቀልህ ከሞት አዳንከን፣ ሕይወትን ሰጠኸን፣ ከጨለማ የምንወጣበት ብርሃንንም ሰጠኸን” ብሏል፡፡ ይህም ቅዱስ ጳውሎስ “እግዚአብሔር ሙላቱ ሁሉ በእርሱ እንዲኖር በእርሱም በኩል በመስቀሉ ደም ሰላም አድርጎ በምድር ወይም በሰማያት ያሉትን ሁሉ ለራሱ እንዲያስታርቅ ፈቅዶአልና” በማለት ካስተማረው ጋር የተስማማ ነው (ቆላ ፩ ፲፱ ፡፡

በዚህ መሠረት በዓለ መስቀል የሰላም በዓል ነው፡፡ በበዓሉ ፍቅር ይገለጽበታል፡፡ መከባበርም ይታይበታል፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የሥርዓት ምንጭ እንደመሆኗ በዓሉን በሥርዓት ስናከብር በሚገለጠው ውበት ኦርቶዶክሳዊ ማንነታችን ይገለጻል፡፡ ስለዚህ አለባበሳችን፣ ዝማሬያችንና አጠቃላይ እንቅስቃሴያችን ሁሉ በሥርዓት የሚከናወንና ሰላምን የሚሰብክ ሊሆን ይገባል፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልጆች ይህን የመሰሉ የአደባባይ በዓላትን በምናከብርባቸው ጊዜያት ሁሉ ተለይተን የምንታወቅባቸው አለባበሶች አሉን፡፡ እነዚህም ከቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓትና ከኢትዮጵያዊ ባህላችን ጋር የተስማሙ ናቸው፡፡ ነጭ ልብስ ለብሶ ሰላምን መስበክ ከጥንት አባቶቻችን ጀምሮ በበዓላት የሚከናወን ሥርዓት ነውና ይህንኑ ልንከተል ይገባል፡፡

ከዚህ ሥርዓት የወጡና በተለያየ መንገድ በሚዘጋጁ አልባሳት ልዩነትን የሚፈጥሩ አለባበሶችን ማስወገድ ይገባል፡፡
በዓለ መስቀል ከሀገር አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ዕውቅና ያለው መንፈሳዊ በዓል ነው፡፡ በመሆኑም በአለባበሳችንም ሆነ በምናስተላልፋቸው ማናቸውም መልእክቶች ሰላምን ለዓለም ማወጅ አለብን፡፡ እኛ ክርስቲያኖች መስቀል እንደ ምልክት የተሰጠን እግዚአብሔርን በማመንና በመፍራት ስለምንመላለስ ነው፡፡ በመሆኑም መስቀል የሰላም ምልክት መሆኑ በሁለንተናችን ሊገለጥ ይገባል፡፡ የምንሰባሰበው በዓለ መስቀልን ለማክበርና በመስቀል ያዳነንን ጌታችንን ለማመስገን ነው እንጂ በተለየ እምነትና አስተሳሰብ ያሉትን ለመንቀፍ ወይም ለማንቋሸሽ አይደለም፡፡ ስለዚህ በሁሉም መንገድ የሚተላለፉ መልእክቶች ፍቅርን የሚሰብኩ እንጂ ጥላቻን የሚያውጁ እንዳይሆኑ እናሳስባለን፡፡

ይህንን ታላቅ በዓል በተሟላ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓትና በሰላማዊ መንገድ ለማክበር የረጅም ጊዜ ዝግጅት ተደርጓል፡፡ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ከተዋቀሩ ዓቢይና ንዑሳን ኮሚቴዎች ጀምሮ በሚመለከታቸው መምሪያዎች በቂ ቅድመ ዝግጅት ተደርጓል፡፡ እንዲሁም በዓሉ በሰላም ተጀምሮ በሰላም እንዲጠናቀቅ የሀገሪቱ የጸጥታ አካላት የበኩላቸውን ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ የበዓሉ ተሳታፊዎችም የበኩላችሁን ድጋፍና ትብብር እንድታደርጉ እንጠይቃለን፡፡

በዓሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ክብረ መስቀሉን ለዓለም የምታውጅበት፣ በመስቀሉ የተገኘውን ሰላም የምታበሥርበትና ትውፊትና ሥርዓቷ በይፋ የሚገለጥበት ታላቅ በዓል ነው፡፡ ይህን በበጎ የማይመለከቱና ሰላምን የማደፍረስ ተልዕኮ ያላቸው አካላት በዚሁ አጋጣሚ ተጠቅመው የቤተ ክርስቲያንን ስም ለማጉደፍና ገጽታዋን ለማበላሸት ሊንቀሳቀሱ ይችላሉ፡፡ ስለዚህ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልጆች ሁኔታውን በንቃት መከታተል የተለየ ነገር ሲያጋጥምም ለጸጥታ አካላትና በቅርብ ለሚገኙ የበዓሉ አስተባባሪዎች እንድታሳውቁ እናሳስባለን፡፡

ሰንደቅ ዓላማን በተመለከተ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማና በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ አራት በተደነገገው መሠረት የቤተ ክርስቲያናችን ዓርማ ብቻ የተፈቀዱ ናቸው፡፡ ከዚህ ውጪ ምንም ዓይነት መልእክት ያላቸው ዓርማዎችና ምልክቶች፣ እንዲሁም በሃይማኖት ሽፋን የሚደረጉ ማናቸውም የውዝግብ ምክንያት የሚሆኑ እንቅስቃሴዎች ከሕገ ቤተ ክርስቲያን ውጪ የሆኑና ቤተ ክርስቲያናችንን የማይወክሉ መሆናቸው ሊታወቅ ይገባል፡፡ በመጨረሻም ከዚህ ይፋዊ መግለጫና ቤተ ክርስቲያናችን ከምታስተዳድራቸው መገናኛ ብዙኃን ውጪ በተለያዩ ሚዲያዎች የሚተላለፉ አሉታዊ መልእክቶች ኃላፊነቱ የግለሰቦቹ ይሆናል፡፡ አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር በዓሉን የሰላም፣ የፍቅርና የአንድነት ያድርግልን፣ የመስቀሉ በረከት ከሁላችሁ ጋር ይሁን።

ቋንቋዬ ነሽ ሚዲያ
ሰኞ መስከረም ፲፪ /፳፻፲ወ፰ ዓ.ም
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ

22/09/2025

✝️የኮምቦልቻ ቅዱስ ሚካኤል የመዝጊያ መርሐ ግብር

Adress

Asogatan 79 I Stockholm
Stockholm
11829

Webbplats

Aviseringar

Var den första att veta och låt oss skicka ett mail när ቋንቋዬ ነሽ ሚዲያ Quanquayenesh Media postar nyheter och kampanjer. Din e-postadress kommer inte att användas för något annat ändamål, och du kan när som helst avbryta prenumerationen.

Kontakta Affären

Skicka ett meddelande till ቋንቋዬ ነሽ ሚዲያ Quanquayenesh Media:

Dela