Tarcha Renaissance

Tarcha Renaissance to transfer current and hot information to the people

ይህ በፎቶ የሚትመለከቱት የማንችስተር ሲት ተጫዋች ዶኮ  አንድ ወቅት ከበተሰቡ ጋር በአንድ አፖርታማ ውስጥ ተከራተው ይኖሩ ነበር፡፡ የተከራዩበት ቤት ሳያስቡት ተሸጠ የገዛው ግለሰብ ጥቁሮችን...
24/10/2025

ይህ በፎቶ የሚትመለከቱት የማንችስተር ሲት ተጫዋች ዶኮ አንድ ወቅት ከበተሰቡ ጋር በአንድ አፖርታማ ውስጥ ተከራተው ይኖሩ ነበር፡፡ የተከራዩበት ቤት ሳያስቡት ተሸጠ የገዛው ግለሰብ ጥቁሮችን የሚጠላ ሰው በመሆኑ እነርሱን ከምኖሩበት ቤት ቶሎ እንድለቁለት ጠየቃቸው እነርሱም እባክህን እየከፈልን እንኑርበት በማለት ይለምኑታል ሰውየው ግን በግድ ከቤቱ አስወጣቸው።ከጊዜ ቆይታ በኋላ ያ ከክራይ ቤት በግድ ውጣ ተብሎ የወጣው ዶኮ የታላቅ ክለብ ተጫዋች ሆኖ ብዙ ገንዘብ ባገኘ ጊዜ:- ያነ ከቤቱ ያስወጣቸው ሰው ያንን ተከራይተው ይኖሩበት የነበረውን በግድ የወጡበትን ቤት ልሸጥ እንደሆነ ሰማ፡፡ ቤቱን ዶኮ ገዛው ከዚያም በኋላ ቤት ለሌላቸው ለድሆች ያንን ቤት በነጻ ስጦታ ሰጣቸው። ተጫዋቹ ስናገር በህይወቴ የተደሰትኩበት ትልቁ ስከቴ ነው ብሏል፡፡
በሀገራችን በብዙ ከተሞችና በከተማችንም አንዳንድ አከራዮች ተካዮቻችሁን የሚትበድሉ ሳት እላፍ አትገባም እያላችሁ ሰዎች በቤተክርስቲያን ጉዳይ ብያረፍዱ ብያመሹ ግብ የሚትቆልፉ: አምፑል በራ ብላችሁ ቆጣር የሚታጠፉ፡አንድ ጀርካን ውሃ ይበቃሃል በማለት የውሃ ቆጣር የሚትዘጉ፡ሽንት ቤት በቀን ሁለቴ ብቻ ትጠቀማላችሁ የሚትሉ የተከራይን ቤት መኝታ ቤቱን ጭምር የሚትበረብሩ ከተከራይ እጅ ገንዘቡን እየተቀበላችሁ በነጻ እንደሰጠ ሰው እረፍት የሚትነሱ የተከራይ በተሰብ በድንገት ልጠይቅ ብመጣ አይናችሁ የሚቀላ ምን ሆናችኋል? ብትመለሱ ይሻላችኋል:: ሰው ገንዘቡን ከፍሎ እናንተ በግለሰቡ ገንዘብ መልካም ኑሮ እየኖራችሁ ግለሰቡ ገንዘቡን እየከፈለ ግን እየተሸማቀቀ ለምን ይኖራል? አንድ ቀን ለእርሱም ቀን ይመጣለታል ወይ ከእናንተ የተሻለ ቤት ወይ ከእናንተ ከተማ በተሻለ ከተማ ልኖረው እንደምችል አስቡ ሰውን አታስመሪሩ፡፡
ይህንን ስል ሁላችሁም የእግር ኳስ ተጫዋች ትሆናላችሁ እያልኩ አይደለም የዶኮ በረከት በእግሩ ላይ ነበረ፡፡የአንዳንዶቻችሁ በእጃችሁ፡በአንደበታችሁ፡በአእምሯአችሁ ወዘተ ልሆን ይችላል፡፡ባለብዙ መንገድ የሆነው እግዚአብሔር
ቤት የለላችሁ በክራይ የሚትጨነቁ እግዚአብሔር ቤት ይስጣችሁ።
አስተማርነው ካላችሁ ሼር አድርጉ፡፡

23/10/2025
ዳግም ወደ ስራ ተገብቷል መልካም ዜና ከኮንትራክተር ጋር በተያያዘ ስራዉ ቆሞ የነበረው የዳዉሮ ባህል ማዕከል ትልቁ የስብሰባ አደራሽ ግንባታ ከኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ጋር ዉል ተገብቶ ...
21/10/2025

ዳግም ወደ ስራ ተገብቷል
መልካም ዜና ከኮንትራክተር ጋር በተያያዘ ስራዉ ቆሞ የነበረው የዳዉሮ ባህል ማዕከል ትልቁ የስብሰባ አደራሽ ግንባታ ከኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ጋር ዉል ተገብቶ ዳግም ወደ ስራ ተገብቷል። የመጨረሻው ጂማሮ እንደምሆን ተስፋ እናደርጋለን።

 ------------ኢንጂነር መላኩ ተረፈ የዳውሮ ዞን መንግሥት ዋና ተጠሪ እና የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል ። 🙏   !! 🙏🙏
17/10/2025


------------
ኢንጂነር መላኩ ተረፈ የዳውሮ ዞን መንግሥት ዋና ተጠሪ እና የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል ። 🙏

!! 🙏🙏

ዜና ሹመት!!የታርጫ ከተማ ም/ቤት አቶ አስናቀ አበበ አናኮ የታርጫ ከተማ አስተዳደር ዋና ከንቲባ አድርገው ሹሟል።
16/10/2025

ዜና ሹመት!!
የታርጫ ከተማ ም/ቤት አቶ አስናቀ አበበ አናኮ የታርጫ ከተማ አስተዳደር ዋና ከንቲባ አድርገው ሹሟል።

የታርጫ ከተማ አስተዳደር ም/ቤት 2ተኛ ዙር ሥራ ዘመን 13ኛ ዓመት 1ኛ ዙር አስቸኳይ ጉባኤ ከጥቂት ደቂቃዎች በኃላ ይጀመራል።
16/10/2025

የታርጫ ከተማ አስተዳደር ም/ቤት 2ተኛ ዙር ሥራ ዘመን 13ኛ ዓመት 1ኛ ዙር አስቸኳይ ጉባኤ ከጥቂት ደቂቃዎች በኃላ ይጀመራል።

በታርጫ ከተማ አስተዳደር የሁለተኛ ምዕራፍ ኮሪደር ልማት ሥራ አካል የሆነው የውሃ ፋውንተን ግንባታ የሳይት ርክክብ መርሀ-ግብር ተከናውኗል። የታርጫ ከተማ አስተዳደር ከ13 ሚልዮን ብር በላይ...
15/10/2025

በታርጫ ከተማ አስተዳደር የሁለተኛ ምዕራፍ ኮሪደር ልማት ሥራ አካል የሆነው የውሃ ፋውንተን ግንባታ የሳይት ርክክብ መርሀ-ግብር ተከናውኗል።
የታርጫ ከተማ አስተዳደር ከ13 ሚልዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የሚያስገነባው የሁለተኛ ኮሪደር ልማት አካል የሆነው የውሃ ፋውንተን ግንባታ ለደቡብ ምዕራብ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ሥራ ተቋራጭ የሳይት ርክክብ መርሀ-ግብር ዛሬ ተፈፅሟል።
በመርሀግብሩ የታርጫ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሀላፊና የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ አስናቀ አበበ በመገኘት ይህ ውሃ ፋውንተን ግንባታ በአጭር ጊዜ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆን የከተማ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ክትትል እንደሚያደርግ ተናግሯል።
የታርጫ ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ባቲሣ ወንድሙ ኘሮጀክቱ ለከተማ ውቤትና ድምቀት ጉልህ ድርሽ ያለው ትልቅ ኘሮጀክት ስሆን ተቋሙ ሥራው እስከሚጠናቀቅ ደረሰ በትኩረት እንደሚከታተል ተናግሯል። አክለውም አቶ ባቲሣ ተቋሙ በ2018ዓ.ም ከተማችን ለኑሮ ተስማሚ፣ ምቹ፣ ጽዱና ውብ ከተማ እንዲትሆን ከማዘጋጃ ቅጥር ግቢ ጀምሮ የተጀመሩ ሥራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥሉም ገልጿል። በሳይት ርክክብ መርሀ-ግብር የታርጫ ከተማ ም/ከንቲባና የትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ግርማ ጮፎረን ጨምሮ ለሎች የከተማ አሰተባባሪ አካላትና ተገኝተዋል።
በመጨረሻም የደቡብ ምዕራብ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ተውካይ ኢ/ር ውብሸት ተሰፋዬ ድርጅታቸው በዘርፉ ያለው ልምድ በመጠቀም የውሃ ፋውንተን ግንባታ በፍጥነትና በጥራት እንደሚያጠናቅቁና ግንባታው ለአከባቢው ወጣቶች የመዝናኛ ማዕከል በማስፋትና የፀዱ ከተማ ህልም ለማሳካት ድርሻው ከፍተኛ እንደሆነም ተናግሯል።

Woldemariam Bezabih (ዶክተር ) የክልሉ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ  የኮሙኒኬሽንና ሚዲያ ዘርፍ  ኃላፊና ም/ቢሮ ኃላፊ ሆነህ በመሾምህ ከልብ ደስስስ ብሎኛል እንኳን ደስ አለህ የከ...
14/10/2025

Woldemariam Bezabih (ዶክተር ) የክልሉ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ የኮሙኒኬሽንና ሚዲያ ዘርፍ ኃላፊና ም/ቢሮ ኃላፊ ሆነህ በመሾምህ ከልብ ደስስስ ብሎኛል እንኳን ደስ አለህ የከፍታ ዘመን ይሁንልህ ቅን ወንድሜ 🙏💪🇪🇹❤🙏

#መልካም የሥራ ጊዜ ይሁንልህ ❤ወንድሜ🙏

‎ ።‎‎ታርጫ፣ መስከረም 04/2018 ዓ/ም፡ – በዚህ ዓመት ከዳውሮ ዞን በፌደራል አዳሪ ትምህርት ቤት ለመማሪ የተፈተኑ የ9ኛ ክፍል ተማሪዎች ሁሉም አልፉዋል። በጣም ጥሩ ውጤትም አስመዝግበ...
14/10/2025

‎ ።

‎ታርጫ፣ መስከረም 04/2018 ዓ/ም፡ – በዚህ ዓመት ከዳውሮ ዞን በፌደራል አዳሪ ትምህርት ቤት ለመማሪ የተፈተኑ የ9ኛ ክፍል ተማሪዎች ሁሉም አልፉዋል። በጣም ጥሩ ውጤትም አስመዝግበዋል። ይህ ውጤት የተማሪዎቹ፣ ወላጆቻቸው እና መምህራኑ የጋራ ጥረት እና የልፋት ፍሬ ነው።

‎የማለፍያ ውጤት ከመቶ 52 ሲሆን ፣ በታርጫ አድቬንቲስት ትምህርት ቤት የፈተኑ ተማሪዎች በተለይ ከፍተኛ ነጥብ አስመዘግበዋል። በዚህ ትምህርት ቤት ዝቅተኛው ነጥብ 74 ከመቶ ሆኖ ሲመዘገብ ከፍተኛው ነጥብ ደግሞ 94 ከመቶ ነው።

‎ከታርጫ አድቬንቲስት ትምህርት ቤት ከፍተኛ ነጥብ ያገኙ ተማሪዎች፡

‎· አብይ ተረፈ - 94/100
‎· ስድራቅ ስዪም - 86/100
‎· ኢስክንድር ኢዪኤል - 80/100
‎· መታደል ስላስ - 80/100
‎· ህልና በቀለ - 78/100
‎· ርብቃ ያዕቆብ - 78/100
‎· አብነት ታዬ - 74/100

‎ከታርጫ አድቨንቲስት ትምህርት ቤት በተጨማሪ ተማሪዎችን ለፈደራል ልዩ አዳሪ ትምህርት አስፈትኖ በማሳለፍ ገሣ ከተማ፣ ታርጫ ኤምቲ ፣ ማረቃ እና ቶጫ ወረዳ ትምህርት ቤቶች ይገኙበታል።

‎ይህ ስኬት በዳውሮ ዞን የትምህርት ጥራት እየጠነከረ መምጣቱን የሚያመለክት ሲሆን፣ለሌሎች ተማሪዎችም መልካም ምሳሌ እና መሪ ሆኖ ያገለግላል። ለሁሉም ተሳትፎ ያደረጉ ተማሪዎች፣ ወላጆች እና መምህራን እንኳን ደስ አላችሁ! ይህ ስኬት ለ2018 ትምህርት ዘመን መልካም መክፈቻ ነው።


‎ ለተማሪዎቹ መልካም የትምህርት ዘመን እንዲሆን እንመኛለን!

የኮሙኒኬሽን እና ሚዲያ ተቋማት የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነውበደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አዘጋጅነት የኮሙኒኬሽን እና ሚዲያ ተቋማት የምክክር ...
14/10/2025

የኮሙኒኬሽን እና ሚዲያ ተቋማት የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አዘጋጅነት የኮሙኒኬሽን እና ሚዲያ ተቋማት የምክክር መድረክ በቦንጋ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

መድረኩ ''በአጋርነት የዳበረ ኮሙኒኬሽን ለህዝብ እምነትና ለሀገር ብልጽግና'' በሚል መሪ ሃሳብ ነው እየተካሄደ የሚገኘው።

በዚሁ መድረክም የተጠናቀቀው 2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም የሚገመገም ሲሆን በ2018 በጀት ዓመት ጠቋሚ ዕቅድ ዙሪያ በመወያየት ከዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤቶች ጋር የግብ ስምምነት ይከናወናል።

በተጨማሪም በ2017 በጀት ዓመት የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ የዞን ኮሙኒኬሽን ተቋማት የእውቅና ሽልማት የሚበረከትላቸው ሲሆን በቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ ምክክርም ይካሄዳል።

በመድረኩ የክልሉ የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ነጋ አበራ፣የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊዎች፣የክልሉ ሚዲያ ኔትዎርክ ስራ አስኪያጆች፣በክልሉ የሚገኙ የተለያዩ የሚዲያ ተቋማት ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች፣ከክልል እስከ ወረዳ ያሉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።
መረጃው የክልሉ ኮሙኒኬሽን ነው

 !ዶከተር ታሜ መካከለኛ ክሊኒክ------------------------አድራሻ ;- በታርጫ ከተማ ኮሬ መንደር በቀድሞ አረጋ ሆቴል ቅጥር ጊቤ ስራ ጀምረናል!ለጤናዎ ደህንነት ከልብ እንሰራለን ...
13/10/2025

!
ዶከተር ታሜ መካከለኛ ክሊኒክ
------------------------
አድራሻ ;- በታርጫ ከተማ ኮሬ መንደር በቀድሞ አረጋ ሆቴል ቅጥር ጊቤ ስራ ጀምረናል!

ለጤናዎ ደህንነት ከልብ እንሰራለን !!

ምቹ እና ጽዱ በሆነው የህክምና ማከላችን መተው የጤናዎን ደህንነት ያረጋግጡ። ዶክተር ታሜ መካከለኛ ክሊኒክ ልምድንና እዉቀት ባካበቱ የህክምና ባለሙያዎች እና እጅግ ዘመናዊ የሆነ ህክምና መገልገያዎችን በማዘጋጀት እንዲሁም በተሟላ ላብራቶሪ ለ24 ሰዓት በዳውሮ ዞን በታርጫ ከተማ አገልግሎት መስጠት ጀመረ ።

ዶክተር ታሜ መካከለኛ ክሊኒክ የደምበኞችን ፍላጎት ቀን ከሌት የሚሰራ ሲሆን በተሟላ የህክምና መሳሪያ በየእለቱ ለደንበኞች የሚሰጠው አገልግሎቶች የሚከተሉት ናቸው።

1, የአዋቅዎች ሙሉ ምርመራና ህክም ሲሆን ከነዚህም መካከል በልዩነት የስኩር ምርመራና ክትትል, የደም ግፍት ምርመራና ክትትል , የወባ, ፣ የጨጉራ ፣ የታይፎድ፣ የታይፈስ፣ የኩላሊት፣ የሽንት ቱቦ ኢንፈክሽን ምርመራና ህክምና፣ የአለርጅ፣ የአስም፣ የሚጥል በሽታ እና ሌሎ ሙሉ ምርመራ ሕክምናና ክትትል እናደርጋለን።

2. የድንገተኛ አደጋዎች ሕክምና ክትትል ሲሆን በተለይም የመታፈን፣ የራስ መሳት፣ አቅም ማጣት፣ የትዉከትና ተቅማጥ ህመም ፣ የደም መፍስስ፣ የማንቀጥቀጥ ሕክምና እና ሌሎች

3. የሕፃናት ሙሉ ምርመራና ሕክምና የምንሰጥ ሲሆን የልብ፣ የመተንፈሻ አካል ችግር፣ ተላላፍና ተላላፍ ያልሆኑ በሽታውች ማከም፣ የሚጥል በሽታ ሕክምናና ክትትል፣ የህፃናት አመጋገብና ዕድገት ክትትልና ህክምና በማዕከላች እንሰጣለን።

4. መለስተኛ ቀዶ ጥገናና የወንዶች ግርዛት እናደርጋለን።

5. የተሟላ የላብራቶሪ ምርመራ እናደርጋለን። የደም ምርመራ፣ የወባ ፣የታይፎድና የታይፈስ፣ የስኳር፣ የሰገራና ሽንት ምርመራ፣ የጉበት ቫይረስ ምርመራ፣ የኤች አይ ቪ ምርመራ እና የእርግዝና ምርመራ በጥራት እንሰራለን።

6. እናቶች እርግዝና ምርመራና በጥንቃቄ ክትትል እናደርጋለን።

7. የቤተስብ እቅድ አገልግሎት ዘዴዎችን እናማክራለን የጤና ችግሮች ላይ የምክር አገልግሎት በነፃ እንሰጣለን።

በተጨማሪም በማንኛውም የጤና ችግር ላይ ምክር ፤ ህክምና እና ክትትል በስፔሻሊስት ሀኪሞች ይሰጣል።

ለከፍተኛ ህክምና ሪፈር የሚያስፈልጋቸውን እናማክራለን!!

ዶክተር ታሜ መካከለኛ ክሊኒክ ለጤናዎ ደህንነት ከልብ እንሰራለን !!

#አድራሻ፦
----------------
ታርጫ ከተማ ኮሬ መንደር በቀድሞ አረጋ ሆቴል ቅጥር ጊቤ ስራ ጀምረናል።

ስልክ ቁጥር
----------------
0968776969
0928193829

ዶክተር ታሜ መካከለኛ ክሊኒክ

ተቃውሞ በመቀሌ ከተማ ‼️በትግራይ ክልል መቀሌ የህወሓት አርሚ 22 ኮር 3 ሰራዊት የተቃውሞ ሰልፍ እያሰሙ ይገኛሉ። የተቃውሞ ሰልፉ መነሻ ደመወዝ አለመከፈሉ እንዲሁም የኢትዮጵያ ተሃድሶ ኮሚ...
13/10/2025

ተቃውሞ በመቀሌ ከተማ ‼️
በትግራይ ክልል መቀሌ የህወሓት አርሚ 22 ኮር 3 ሰራዊት የተቃውሞ ሰልፍ እያሰሙ ይገኛሉ። የተቃውሞ ሰልፉ መነሻ ደመወዝ አለመከፈሉ እንዲሁም የኢትዮጵያ ተሃድሶ ኮሚሽን ለህወሓት ታጣቂዎች DDR እንዲቋረጥ በመወሰኑ ምክንያት መሆኑን ምንጮቻችን ገልፀዋል። ተቃዋሚዎች በአሁኑ ሰዓት ወደ ክልሉ ፕሬዚዳንት ፅህፈት ቤት እያመሩ መሆኑን ገልፀውልናል።

Address

Government Intelligence
Terchová

Telephone

+251984119599

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tarcha Renaissance posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Tarcha Renaissance:

Share