Afro Soccer Ethiopia / አፍሮ ሶከር ኢትዮጵያ

Afro Soccer Ethiopia / አፍሮ ሶከር ኢትዮጵያ የኢትዮጵያን ቀደምት ከዋክብት እያነገስን ፤ አዲሶቹን እያሳደግን ፤ ታሪካቸውን ለመጪዎቹ እናሻግራለን ✅ ክብር ለቀደምት ተጫዋቾቻችንን

12/06/2025

Saint George S.A

12/06/2025

ወሎዬው 🎁 #ደሴ Saint George S.A

12/06/2025

ሙሉጌታ ወልደየስ

#ቡና ቡና ዘጠናዎቹ

12/06/2025

የሌጀንዱ ልጅ
Ethiopian Football Federation Ethiopian Coffee SC Saint George S.A

ይህ ሌጀንድ ማነው  ?በኢትዮጵያ እግርኳስ ታሪክ የገዘፈ ስም ካላቸው  ተጫዋቾች መካከል አንዱ የሆነው ይህ ሌጀንድ ማነው? ሲጫወት ያያችሁት ትውስታችሁን አጋሩን ።(ለምስሉ ጥራት ይቅርታ 🙏)...
12/06/2025

ይህ ሌጀንድ ማነው ?

በኢትዮጵያ እግርኳስ ታሪክ የገዘፈ ስም ካላቸው ተጫዋቾች መካከል አንዱ የሆነው ይህ ሌጀንድ ማነው? ሲጫወት ያያችሁት ትውስታችሁን አጋሩን ።
(ለምስሉ ጥራት ይቅርታ 🙏)

🎁ኮከቦቻችን በዘመናት እርዝማኔ ተሸፍነው እንዳይረሱ እናስታውሳቸው 🎁

የኢትዮጵያን ቀደምት ከዋክብት እያነገስን አዲሶቹን እያሳደግን ታሪካቸውን ለመጪዎቹ እናሻግራለን ✅
🎁🎁🎁አፍሮ ሶከር ኢትዮጵያ🎁🎁🎁
🎁🎁🎁 የኢትዮጵያ ሌጀንዶች ቤት 🎁🎁🎁

አንተነህ አላምረው ፡ የሜዳው ሞገስ ከቀደምት የእግርኳሳችን ከዋክብት ተርታ አማካዩ አንተነህ አላምረው ስሙ ሰፍሯል ። ይህ የመሀል ሜዳ  ሞገስ ከክለብም ሆነ ከብሄራዊ ቡድናችን ጋር ዋንጫዎች...
12/04/2025

አንተነህ አላምረው ፡ የሜዳው ሞገስ

ከቀደምት የእግርኳሳችን ከዋክብት ተርታ አማካዩ አንተነህ አላምረው ስሙ ሰፍሯል ። ይህ የመሀል ሜዳ ሞገስ ከክለብም ሆነ ከብሄራዊ ቡድናችን ጋር ዋንጫዎችን አንስቷል ።

ግዙፉ አማካይ አንተነህ አላምረው ኢትዮጵያ ያዘጋጀችውን የ1980 የሴካፋ ውድድር ኳስ አቀባይ ሆኖ ታድሟል ። በወቅቱ የነበረው የህዝቡ የድል ጥም እና ጥልቅ የአሸናፊነት ስሜት በዚህ ከሜዳው ዳር ተቀምጦ ኳስ ሲያቃብል በነበረ ብላቴና ልብ ውስጥ ታላቅ ምኞት ፈጠረ ፤ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ቡድን ማሊያ ለብሶ ተአምር የመስራት ፤ ህዝብን በድል የማስጨፈር ምኞት ። ከዚህ ውድድር በኋላ ትንሹ አንተነህ ምኞቱን ለማሳካት በብዙ ጣረ ። ባደረገው ጠንካራ እና ተከታታይ ልምምድ ራሱን አበቃ ። እናም በወቅቱ ከነበረው ከምድር ጦር ታዳጊ ቡድን ጀምሮ በኢትዬጵያ ቡና ፤ በመቻል፤ በኪራይ ቤት ፤ በቅዱስ ጊዬርጊስ ፤ እና በሱዳኑ አልሂላል ክለብ በመጫወት የራሱን ታሪክ በጥረቱ ለመፃፍ በቃ ፤ ከምንም በላይ ደግሞ ለብሄራዊ ቡድናችን በመጫወት ህዝብን በድል በማስጨፈር ምኞቱን አሳካ

🏆ስኬቶቹ 🏆

👉አንተነህ በቅዱስ ጊዮርጊስ ከአሰልጣኝ አስራት ሀይሌ ጋር ስኬታማ ጊዜያትን አሳልፏል ፤ የፕሪምየር ሊጉን ዋንጫ ፥ የጥሎማለፍ ዋንጫ ፥ እንዲሁም የአሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫን አሳክቷል። ከኢትዮጵያ ቡና ጋርም በ1995 የጥሎ ማለፍ ዋንጫን አንስቷል ።
👉ኢትዮጵያ የአፍሪካን ቡድኖች ስትገጥም የተጋጣሚን ገዛዝፍት ተጫዋቾች ሚገዳደርልን ብሄራዊ ደጀናችን አንተነህ አላምረው ነበር ። ይህ ኮከብ ብሄራዊ ቡድናችንን ለረዥም አመታት ያውም በወጥ አቋም አገልግሏል ። በተለይ ከ1990 እስከ 1997 የዋሊያዎቹ ቋሚ ተሰላፊ ነበር። በ1997 ኢትዮጵያ ባዘጋጀችው የአላሙዲን ሲኒየር ቻሌንጅ ካፕ የሴካፋ ውድድር አንተነህ አይረሴ ታሪክ ሰርቷል ።በፍፃሜው ጨዋታ ኢትዮጵያ ብሩንዲን 3-0 አሸንፋ ሻምፒዮን ስትሆን ሶስተኛዋን ጎል በማስቆጠር ወደ ክቡር ትሪቡን በመሄድ እንደተመኘው ህዝቡን በደስታ አስጨፈረ ፤ በዛች ቅጽበት ደስታውን የገለፀበት መንገድ እና ያሳየው ወታደራዊ ሰላምታ የህዝቡን የድል ጥም ጠንቅቆ የተረዳ እና በሚገባ ያሳካ "ጥም ቆራጭ " መሆኑን አረጋግጧል ።

አንተነህ በዘመኑ ማሟለም ሻንቆን (አስፔታ)፥አሸናፊ ግርማን ፤ እና ሳሙኤል ደምሴን(ኩኩሻ ) ከመሳሰሉ ስመ ጥር ኮከቦች ጋር ተጫውቶዋል ።

👉 አንተነህ አላምረው በ1998 ወደ ካናዳ ተጉዞ ኑሮውን በዚያው አድርጓል

አንተነህን ሲጫወት ያያችሁት ትውስታችሁን አጋሩን
(ለምስሉ ጥራት ይቅርታ 🙏)

🎁ኮከቦቻችን በዘመናት እርዝማኔ ተሸፍነው እንዳይረሱ እናስታውሳቸው 🎁

የኢትዮጵያን ቀደምት ከዋክብት እያነገስን አዲሶቹን እያሳደግን ታሪካቸውን ለመጪዎቹ እናሻግራለን ✅
🎁🎁🎁አፍሮ ሶከር ኢትዮጵያ🎁🎁🎁
🎁🎁🎁 የኢትዮጵያ ሌጀንዶች ቤት 🎁🎁🎁

ሙሉጌታ ከበደ ፡ ታሪኩን ከራሱ አንደበትክፍል 2"ከአዬር ሀይል ጋር በነበረው ጨዋታ አባቴም ስቴዲዬም ተገኝቶ ነበር። የእናት አገር ጥሪ ... አባቴ ኢዲዩ ነገር ነው ... ባለ ስልጣኖቹን አ...
12/04/2025

ሙሉጌታ ከበደ ፡ ታሪኩን ከራሱ አንደበት
ክፍል 2

"ከአዬር ሀይል ጋር በነበረው ጨዋታ አባቴም ስቴዲዬም ተገኝቶ ነበር። የእናት አገር ጥሪ ... አባቴ ኢዲዩ ነገር ነው ... ባለ ስልጣኖቹን አይወዳቸውም ነበር ... እርሱ የፍርድ ቤት ዳኛ ነበር። ስለ ኳስ ምንም አያቅም። ከስራ መልስ ፒያሳ፥ የሳህሉ ግሮሰሪ ጎራ ይላል። ወንድሞቼ በረንዳ ላይ ካፖርት ይዘው ይጠብቁታል። እኔ ካፖርት ይዤ የሄድኩ እለት ውስጥ እገባለሁ። አብሬው ቁጭ ብዬ ፋንታ እጠጣለሁ። ሌሎቹ ወንድሞቼ አንቱ ነው ይሉት የነበረው። እኔ ደግሞ አንተ ...
የዛን ቀን ጎረቤታችን ጋሽ መንገሻ ናቸው ስታዲዬም ያመጡት። ናደው ዘካርያስ ሲያቅፉኝ አይቷል፥ መነጸሩን ከፍ ዝቅ አያደረገ። የከተማው ሰው በኳስ ያቀኛል፥ ጎል አግብቼ ቀጥ ብዬ አባቴን አየሁ ... ያየሁትን ማመን አቃተኝ ...መነጽሩን ከፍ እና ዝቅ እያደረገ ይጮሀል ... የኔ ልጅ እኮ ነው እያለ፥ አጠገቡ ላሉት ይነግራል። አብረውት የነበሩት ጋሽ መንገሻ ኋላ ይሄን ነግረውኛል (በሳቅ ...)፥ የደሴ ሰው እኔን ያቀኛል፥ ለአባቴ ነበር ሁሉ ነገር አዲስ የሆነበት"

"ያን ቀን ማታ ቤት ስገባ ፊቱ በደስታ ተሞልቷል። እናቴን ጠርቶ እንዲህ አለ፦
ጥሩዬ ልጅማ ወልጃለሁ ... ስሜን የሚያስጠራ ...
በምን?
በኳስ ነዋ! በጣም ጎበዝ እኮ ነው
አውቃለሁ ጎበዝ እንደሆነ
እንዴት አወቅሽ?
ይነግሩኛል እኮ! ሰፈር ውስጥም፣ እድር ቤትም ሳይቀር ልጅሽ ጎበዝ ኳስ ተጫዋች ነው ይሉኛል። መንገድ ላይ እቃ ይዤ የሚያዩኝ - የሙልጌታ እናት - ላግዝሽ ብለው የያዝኩትን ይሸከሙልኛል
በይ ከዛሬ ጀምሮ ልጄ ሸሮ እንዳይበላ፥ስጋ ሁሌም ስሪለት (በሳቅ እንደገና ...) እሱ እኔን መጥቀሙ ነበር"

"በቀጣይ የወሎ ምርጥ ከትግራይ ምርጥ ጋር ትግራይ ጋር ጨዋታ ነበረን። ለእርሱ እየተዘጋጀን ነበር። እንደ ሁልግዜው ልምምድ ላደርግ ሻንጣዬን ይዤ ወደ ሆጤ ሜዳ ልሄድ ስል አባቴ ጠራኝ
አቤት አባቴ ...
ሙላቴ ዛሬ አትሂድ አሞኛል ...
አባቴ ወደ ትግራይ ለጨዋታ ስለምንሄድ ...
አይ! አትሂድ ታምሜያለሁ ... ሻንጣዬን አስቀምጬ የተኛበት አጠገብ ሄጄ ቁጭ አልኩ። እናቴም ነበረች። ወንድሞቼም ነበሩ። ሳይሻለው ቀረ ... ድንገተኛ ነበር ... አባቴ ሞተብኝ ... እኔም ሀዘን ተቀመጥኩ ... ከወሎ ምርጥ ጋር አብሬ ሳልሄድ ቀረሁ...1974"

"የወሎ ምርጥ ትግራይ ላይ ተሸነፈ። አንዳንዶች ሙልጌታ አብሮ ስላልሄደ ነው አሉ። ለመልሱ ጨዋታ ትግራዮች ከተማችን መጥተዋል። እኔም ሀዘኔን ጨርሼ የወሎ ምርጥን ተቀላቅዬ ሆቴል ገባሁ። አታምነኝም (በትዝታ ወደኋላ እየሄደ)... ከመሀል ሜዳ ድሪብል እያደረኩ ሄጄ አገባሁባቸው። ያንን ጎል ብዙ ሰው ያስታውሰኝ ነበር። ትግራይ ስሄድም እንዴት አገባኸው እያሉ ይጠይቁኝ ነበር። ያን ቀን 3 ለባዶ አሸነፍን።"

"ስዩም አባተ አዲስ አበባ ያለው የህዝብ ማመላሻ ቡድን አሰልጣኝ ነበር። ኮርስ ሊሰጥ ደሴ መጥቶ ነበር። ስጫወት ሆጤ ሜዳ አይቶኛል። ወደ'ኔ መጥቶ ጠዬቀኝ ...
የት ነው የምትሰራው?
ህዝብ ማመለሻ
እኛ ጋር ?
አዎ
በቃ እንደተመለስኩ፥ አመቻችቼ ወደ አዲስ አበባ እኔ እውስድሀለሁ ...
ስዩም ይሄን ነግሮኝ፥ ወደ አዲስ አበባ ተመለሰ። እሱ አዲስ አበባ ያለው የህዝብ ማመለሻ አሰልጣኝ ነበር፥ እኔ ደግሞ ደሴ ያለው ህዝብ ማመላሻ ድርጅት ሰራተኛ ... የሚሆን ስላልመሰለኝ የስዩምን ቃል፥ ይሆናል ብዬ አላሰብኩትም ነበር"

"ከቀናቶች በኋላ አቶ በጽዓ ጋር ስልክ ተደወለ። አቶ ግርማ ነበሩ። አዲስ አበባ ያለው የህዝብ ማመላለሻ ዋናው መስሪያ ቤት ሀላፊ፥ አቶ በጽዓ ደግሞ የኔ አለቃ፥ ጸሀይ ለምን ትሞቃለህ ብለው ደሞዜን መጀመሪያ አካባቢ ሲቆርጡብኝ የነበሩ (እንደገና ሳቅ) ....
'አቶ በጽዓ አንተ ጋር የሚሰራ፥ ሙልጌታ የሚባል ልጅ አለ?
አዎ
ወደኛ አዛውረውና ቶሎ ላክልኝ
ኧረ ጌታዬ ጓድ ናደውም ሆነ ኢሰፓዎቹ ይናደዱብኛል ...
ምክንያት ፈጥረህ ቶሎ ላክልኝ ...
ስልኩ ተዘጋ። ጸሀፊዋና፣ የአቶ በጽዓ ሚስት ስለ ሁኔታው ነግረውኛል። ጧት ስራ እንደገባሁ፥ አቶ በጽዓ ቢሮ ተጠራሁ።
'ሙልጌታ ከዛሬ ጀምሮ የስራ መደብህ ተቀይሯል። የአውቶብስ ተቆጣጣሪ አድርገንሀል። ህዝብ ጭነው የሚሄዱትን አውቶቡሶች እያስቆምክ ትቆጣጠራለህ፥ ትርፍ የጫኑትን ትቀጣለህ። ለግዜው ከደሴ እስከ ሸዋሮቢት ባለው መስመር መድበንሃል። ጨርሻለሁ ' አሉኝ። ቢሯቸውን ለቅቄ ወጣሁ።

ነገሩ ገብቶኛል። ባለቤታቸው እንደነገረችኝ ነው። ከሸዋሮቢት በኋላ፣ እስከ ደብረሲና እንደሚመድቡኝ፣ ከዛም እስከ አዲስ አበባ ... ከዛ በኋላ እኔን አዲስ አበባ የማስቀረቱ ስራ የስዩም አባተ እና የጋሽ ግርማ ይሆናል ማለት ነው። ደሴ ላሉት ኢሰፓዎችም አዲሱ ስራ፥ ማዘናጊያ ይሆናል። ሙልጌታ የታለ ካሉ፥ ስራ ላይ ነው የሚል መልስ ይሰጣቸዋል። ይሄንን ነበር ጋሽ በጽዓ ያቀዱት። በመሀል ቤት፥ ግጭት እንዳይፈጠር ማምለጫ መንገዳቸው ነበር።"

"ስራዋ ጥማኛለች። ጉቦ ታገኝባታለህ (በሳቅ ...)፥ ትርፍ የጫነ ረዳት ሁሉ ኪሴ ውስጥ ብር ያስገባል። ማታ ቤት ስገባ ብዙ ብር ይዤ እገባለሁ። እህቴ ጸዳለች ይህን አልወደደችም። አንተ ሙልጌታ ይኼ ስራ ከኳስ እንዳይለያይህ ትለኝ ነበር። እርሷ ፍላጎቷ እኔ በኳሱ እንድገፋ ነበር። እኔ ግን ስራዋን ወድጃታለሁ። በማገኛት ብር ከጓደኞቼ ጋር ጠላ ቤት ሄደን፥ ጠላ እንጠጣ ነበር (በሳቅ እንደገና)... ስራው እንዴት መሰለህ ...ከአውራ መንገዱ ገባ ብለህ ጫካው ውስጥ ትደበቅና፣ አውቶብሶቹን ድንገት ማስቆምና መፈተሽ፥ ትርፍ ከያዙ መቅጣት ..."

"አንድ ቀን ግን ያላሰብኩት ነገር ተፈጠረ። ድንገት ያስቆምኩት አውቶብስ፥ ባለቤትነቱ የጎረቤታችን ነበር። የጋሽ ይማም ሀሰን ... የአባቴ ጓደኛ ናቸው። የተከበሩ ትልቅ ሰው ... ከማመላሻው ሀላፊዎች ጋር ግንኙነት ነበራቸው። እርሳቸውን ደፍሮ የሚቀጣ አልነበረም። ረዳቱን እንዳየሁት አወቅሁት፣ እርሱ አላወቀኝም። ይሄን ሁሉ ትርፍ ለምን ጫንክ አልኩት ... የቅጣት ትኬት ቆረጥኩበት ..."

"በማግስቱ ጧት ፊቴን ታጥቤ ልወጣ ስል፥ ጋሽ ይማም በራችንን አንኳኩተው፥ ከዘራቸውን ይዘው ገቡ። እንዳዬኋቸው ሸሸሁ። የዛኑ ቀን፥ በጽኣ ጋር ደውለው የማንን ጥጋበኛ አመጣህብን ብለው መበሳጨታቸውን ሰምቻለሁ።

በጽዓ ነበር የደሴ ልጅ መሆኔንና የከበደ ቃሲም ልጅ እንደሆንኩና ነግሯቸዋል። ጎረቤታቸው መሆኔን አውቀዋል። እናቴ ብቅ አለች...
ወይዘሮ ጥሩዬ ያንቺ ልጅ ተቆጣጣሪ ሆኖ አስቀጣኝ እኮ ...
ምን ያድርግ፥ ስራው አይደል ስትል መለሰች። ራቅ ብዬ ጋሽ ይማም ገና እቀጣዎታለሁ አልኳቸው (በሳቅ ..) ልጃቸው አባዋ እና ቤቢ ጓደኞቼ ነበሩ ... በኋላ ለእነሱም ስለተፈጠረው ለእነሱም ነገርኳቸው ... እርሳቸውም አስጠንቅቀውኝ ሄዱ ..."

"ከቀናት በኋላ ምድቤ ደብረሲና ደረሰ፥ እንደገና ከጥቂት ቀናት በኋላ ደግሞ እስከ አዲስ አበባ ተመደብኩ። አሁን መናገር አለብኝ ብዬ ወሰንኩ። ጓድ ናደውን ማስቀዬም አልፈለኩም። ቀጥ ብዬ ቢሯቸው ገባሁ። ጓድ ናደው ...

ይቀጥላል...

🎁ኮከቦቻችን በዘመናት እርዝማኔ ተሸፍነው እንዳይረሱ እናስታውሳቸው 🎁

የኢትዮጵያን ቀደምት ከዋክብት እያነገስን አዲሶቹን እያሳደግን ታሪካቸውን ለመጪዎቹ እናሻግራለን ✅
🎁🎁🎁አፍሮ ሶከር ኢትዮጵያ🎁🎁🎁
🎁🎁🎁 የኢትዮጵያ ሌጀንዶች ቤት 🎁🎁🎁

"እኔ የኢትዮጵያ ማራዶና ነኝ" ዮናስ ተፈራ ✅ስም ፡ ዮናስ ተፈራ✅ የትውልድ ስፍራ ፡ዲላ ከተማ ✅የጨዋታ ስፍራው ፡ አማካይ 🎁ያሳካው ዋንጫ ፡ 🏆1980 የሴካፋ ዋንጫ 🏆1978 አዲስ አበባ ...
12/02/2025

"እኔ የኢትዮጵያ ማራዶና ነኝ" ዮናስ ተፈራ

✅ስም ፡ ዮናስ ተፈራ
✅ የትውልድ ስፍራ ፡ዲላ ከተማ
✅የጨዋታ ስፍራው ፡ አማካይ
🎁ያሳካው ዋንጫ ፡
🏆1980 የሴካፋ ዋንጫ
🏆1978 አዲስ አበባ ዋንጫ
🏆 1981 የኢትዮጵያ አሽናፊዬዎች አሽናፊ ዋንጫ
✍️የጨዋታ ዘመን ፡ ከ1976 እስከ 1986 ዓ/ም ለ10
✍️ ብዙ የተጫወተው ፡ ለኢትዮጵያ ቡና
✅ልዩ ችሎታው ፡ ከርቀት አክርሮ በመምታት ግብ ማስቆጠር
✅አይረሴ ንግግሩ ፡ "የማደንቀው ማንም ተጫዋቾች የለም። እኔን የሚበልጥም ተጫዋች የለም ፣ እኔ የኢትዮጵያ ማራዶና ነኝ።" በማለቱ ተመልካች "የዲላ ማራዶና" ይሉት ነበር ።
💔ዮናስ በ1992 አልፏል። ለዮናስ ቡናና ቅዱስ ጊዮርጊስ የመታሰቢያ የዋንጫ ጨዋታ አድርገውለታል።

ዮናስ ተፈራን ሲጫወት ያያችሁት ትውስታችሁን አጋሩን ።

🎁ኮከቦቻችን በዘመናት እርዝማኔ ተሸፍነው እንዳይረሱ እናስታውሳቸው 🎁

የኢትዮጵያን ቀደምት ከዋክብት እያነገስን አዲሶቹን እያሳደግን ታሪካቸውን ለመጪዎቹ እናሻግራለን ✅
🎁🎁🎁አፍሮ ሶከር ኢትዮጵያ🎁🎁🎁
🎁🎁🎁 የኢትዮጵያ ሌጀንዶች ቤት 🎁🎁🎁

ሙሉጌታ ከበደ ፡ ታሪኩን ከራሱ አንደበት "አንዳንዴ ሳስበው የእናቴ ነገር ይገርመኛል። 16 ልጅ እንዴት ችላ አሳደገች እላለሁ። ብርቱ ነበረች። አባቴ ከእኔ እናት 12 ልጆችን ወልዷል። ከሌላ...
12/01/2025

ሙሉጌታ ከበደ ፡ ታሪኩን ከራሱ አንደበት

"አንዳንዴ ሳስበው የእናቴ ነገር ይገርመኛል። 16 ልጅ እንዴት ችላ አሳደገች እላለሁ። ብርቱ ነበረች። አባቴ ከእኔ እናት 12 ልጆችን ወልዷል። ከሌላ ደግሞ 4። ታናሼ ሞቶብናል። ሌሎቻችንን አሳድጋናለች። ጠንካራ ነበረች - ጥሩዬ ፈለቀ"

"ከቦረኖች ጋር ስንጫወት እናቴ ጎል እንዳላገባ ታስጠነቅቀኝ ነበር። እኔ ልቤ ለወረኢሉ ያደላል። የተወለድኩት እዛ ስለሆነ - ወረኢሉ አውራጃ ለገሂዳ ከተማ - ልዩ ቦታዋ ደረቅ አምባ። አባቴ - ከበደ ቃሲም የወረኢሉ ሰው ነው። እናቴ ደግሞ የመካነ ሰላም - ቦረና። በልጅነቴ ወደ ደሴ መጣን። እዛው ደሴ እቴጌ መነን፣ ሆጤና ወ/ሮ ስኂን እስከ 12 ተማርኩ። ቤታችን ለሆጤ ሜዳ ቅርብ ነበር። ከትምህርቴ ይልቅ ኳሱን እወድ ነበር። በባዶ እግሬ - ያቺን የ1 ብር የላስቲክ ኳስ ሰው እስኪገርመው ድረስ አለፋት ነበር። የትምህርት ቤቶች ውድድር ሲደረግ እናቴ ለቦረኖች ታግዛለች። የቦረኖች አስተማሪዎች እናቴን ያውቋታል። ቤታችን መጥተው ለእናቴ 'ይሄ ሙልጌታ ብዙ ጎል እንዳያገባብን ንገሪልን ብለዋትት ሄዱ።'' እሷም አስጠነቀቀችኝ። 'ሙላቴ (ሙላቴ ነው የሚሉኝ አባትና እናቴ) የእነዚህ የቦረናዎችን ነገር አደራ አለችኝ። መልስ ሳልሰጥ ዝም አልኩ።"

"የጨዋታው ቀን እነሱ አልጨፈሩም። ሲያሸንፉ እዬጨፈሩ በኛ ቤት በኩል ያልፉ ነበር። ወደ አጥሩ በር ተጠግታ ስታይ ያ የቦረና ጭፈራ የለም። ትንሽ ወንድሜን፣ ተፈሪን ጠርታ ጠየቀችው። ተፈሪ ሁኔታዋን ስላዬ ዋሻት። ብዙም ሳይቆይ አስተማሪዎቹ ቤት መጡ። 'ምነው እማማ ጥሩዬ፥ እንደዛ እንዳለመነው ...'
'አገባባችሁ?'
'አዎ'
'ስንት'
'አራት' " ውጤቱን ነግረዋት ሄዱ።

"ወረኢሉዎች ሲጫወቱ ሸራ ጫማ ከጓደኞቼ ሰብስቤ እሰጣቸዋለሁ። ልቤ ለእነሱ ስስ ነበር። ከአንድ በላይ ጎልም አላገባባቸውም። ያን ቀን ምሽት ተቆጣችኝ ' ሙላቴ ሙት ዛሬ እራትህን አልሰጥህም' አለችኝ። እንደተናደደች አውቄያለሁ። አባቴ ጋደም ብሎ ነበር። ወደ'ሱ ተጠግቼ ነገርኩት። የወረኢሉ ቲፎዞ ነኝ። ወረኢሉን ነው የምወደው ... ዛሬ ቦረናን .. ብዬ ሳልጨርስ ምን አደረካቸው አለኝ ..
አገባሁባቸው
ስንት....
አራት... አባቴ ውጤቱን ስነግረው ይስቃል። ጥሩዬ እራቱን ስጪው እንጂ ሲል ጠዬቀ .. እናቴም ሳትጨክን ቀረች"

"ከተማው ውስጥ ታዋቂ እየሆንኩ መጣሁ። ትምህርቴን ከጨረስኩ በኋላም ለከፍተኛ 2 መጫዎቴን ቀጠልኩ። ጓደኞቼ እነ አንዱአለም ብር እየተከፈላቸው ለኦሜድላ መጫዎት ጀመሩ። እኔም እነሱ ጋር እሄዳለሁ ስል የከፍተኛው ሊቀመንበር በመቶ ምናምን ብር ደመወዝ እዛው አስቀረኝ።"

"አንድ ቀን ወደ ገበያ ስትሔድ ህዝባዊ የኑሮ እድገት ጋር ሰው ተሰብስቦ አየች። የስራ ማስታወቂያ የሚለጠፈው እዛ ግቢ ነበር። 'ሙላቴ ሰው ማስታወቂያ ሲያነብ አይቻለሁ፥ ቤት ከምትውል ሄደህ ሞክር' አለችኝ። ለህዝብ ማመላሻ የስታትስቲክስ ክፍል ሂሳብ ሰራተኛ ነበር የተፈለገው። አመለከትኩ። ቤታችን ለተከራዬው ልጅ መመዝቤን ስነግረው፥ ማስታወቂያውን የለጠፈው እሱ መሆኑን ነገረኝ። የፈተናውን መልስም አምጥቶ ሰጠኝ (በሳቅ...) የጽሁፍ ፈተናው ቀን ሰው ይደምራል ፥ ይቀንሳል ... እኔ ቶሎ ጨርሼ ወጣሁ። እድሜ ለሀብታሙ... የቃል ፈተናውንም ፈታኙ ራሱ ሀብታሙ ነበር (እንደገና ሳቅ ...) ምን አለፋህ ባ'ጭሩ ህዝብ ማመላለሻ ተቀጠርኩ"

"አዲሱ ቢሮዬ ይቀዘቅዝ ስለነበር፣ ጸሀይ ለመሞቅ ስወጣ ስራ አስኪያጁ ያዬኝ ኖሯል ለካ። አልወደደኝም። ደሞዜን ይቆርጥብኝ ጀመር። 'አስካለ (ጸሀፊው ነች) የ3 ቀን ደሞዙ እንዲቆረጥ አዝዣለሁ ይላል፥ ሌላ ቀን የ4 ቀን፣ ሌላ ግዜ ደግሞ የ5 ቀን ...አማረረኝ። ልምምድ ስለማይፈቅድልኝ ከ11 ሰአት በኋላ፥ በምሽት ብቻዬን ሆጤ ሜዳ ልምምዴን እየሰራሁ ነበር ለከፍተኛ 2 ለመጫወት የተገደድኩት። የልምምድ ሰዓት ይፈቀድለት የሚል ደብዳቤ ከከፍተኛ አጽፌ ባመጣም፣ ወረቀቱን ቀዳዶ ጣለው። ጸባችንንም አየከረረ መጣ። ባለቤቱ አብራኝ ተምራለችና በእሷ ለማስጠዬቅ ሞከርኩ። ምን አድርጌው ነው? እሷም ትፈራዋለችና ሳትጠይልኝ ዝም አለች። ያለመግባባቱም ቀጠለ"

"ለወሎ ምርጥ ተመርጬ ለእናት አገር ጥሪ ለመጫዎት አንድ እሁድ ሆጤ ሜዳ ተገኘሁ። የከተማው ህዝብ ሜዳ ተገኝቷል። በእናት አገር ጥሪ ጨዋታ አይቀርም። 1974 ዓ.ም ነበር። ይሄ አለቃዬም ጨዋታውን ሊያይ መጥቷል። በርቀት አይቼዋለሁ። ናደው ዘካርያስ የኢሰፓ አንደኛ ጸሀፊ ነበሩ። ሜዳ ውስጥ ተጨዋቾችን እየተዋወቁ ነበር። እኔ ጋር ሲደርሱ አቅፈው አበረታቱኝ። ናደው በጣም ኳስ ይወዳሉ። በእርሳቸው ግዜ ከተማችን ውስጥ ኳስና ኪነት ገናና ነበር። ናደው አቅፈው ሲስሙኝ ያ አለቃዬ ተመልክቷል። ናደው የተከበሩና እና የሚፈሩ ሰው ነበሩ። አለቃዬ አላመነም። ሀብታሙ አጠገቡ ነበር። ይሄ እኛ ጋር የሚሰራው ልጅ ነው?
አዎ
ጥሩ ተጫወትኩ። ጎልም አገባሁ። አየር ሀይልን አሸነፍን። ስቴዲዬሙ በደስታ ቀለጠ።"

"በማግስቱ ሰኞ ወደ ስራ፥ በሰራተኞች የሰርቪስ መኪና እየሄድን ነው። ወደ ሸዋበር። መስሪያ ቤታችን እዛ ነበር። የእያዩ ጀምበሬ ልጅ ሰርቪሱን ይነዳል። አጠገቡ የአለቃችን ሚስት አለች። ከኋላ እኔና ሀብታሙ ቁጭ ብለናል።
ማታ ስላንተ ነበር ባለቤቴ ሲያወራ ያደረው አለችኝ - የአለቃዬ ባለቤት።
ምን አለሽ?
እስከዛሬ ለምን አልነገርሽኝም?
በፊት የነገርከኝንም ነግሬዋለሁ አለችኝ

ቢሮ እንደገባሁ አስጠራኝ። የተቆረጠብኝን ደሞዝ በሙሉ ተስተካክሎ ተሰርቶ እነወዲመለስልኝ ማዘዙን አሳወቀኝ፣ የልምምድ ግዜም በማንኛውም ሰአት ተፈቅዶልሀል አለኝ ...በኳስ ጎበዝ መሆኔንም ነገረኝ "

"ከአዬር ሀይል ጋር በነበረው ጨዋታ አባቴም ስቴዲዬም ተገኝቶ ነበር። የእናት አገር ጥሪ ... አባቴ ኢዲዩ ነገር ነው ... ባለ ስልጣኖቹን አይወዳቸውም ነነር ... እርሱ የፍርድ ቤት ዳኛ ነበር። ስለ ኳስ ምንም አያቅም። ከስራ መልስ ፒያሳ፥ የሳህሉ ግሮሰሪ ጎራ ይላል። ወንድሞቼ በረንዳ ላይ ካፖርት ይዘው ይጠብቁታል። እኔ ካፖርት ይዤ የሄድኩ እለት ውስጥ እገባለሁ። አብሬው ቁጭ ብዬ ፋንታ እጠጣለሁ። ሌሎቹ ወንድሞቼ አንቱ ነው ይሉት የነበረው። እኔ ደግሞ አንተ ...
የዛን ቀን ጎረቤታችን ጋሽ መንገሻ ናቸው ስታዲዬም ያመጡት። ናደው ዘካርያስ ሲያቅፉኝ አይቷል፥ መነጸሩን ከፍ ዝቅ አያደረገ። የከተማው ሰው በኳስ ያቀኛል፥ ጎል አግብቼ ቀጥ ብዬ አባቴን አየሁ ... ያየሁትን ማመን አቃተኝ ...".
ይቀጥላል.....

🎁ኮከቦቻችን በዘመናት እርዝማኔ ተሸፍነው እንዳይረሱ እናስታውሳቸው 🎁

የኢትዮጵያን ቀደምት ከዋክብት እያነገስን አዲሶቹን እያሳደግን ታሪካቸውን ለመጪዎቹ እናሻግራለን ✅
🎁🎁🎁አፍሮ ሶከር ኢትዮጵያ🎁🎁🎁
🎁🎁🎁 የኢትዮጵያ ሌጀንዶች ቤት 🎁🎁🎁

ማንን ታስታውሳላችሁ?እነዚህ ተጫዋቾች እነማን ናቸው? ሲጫወቱ ያያችዋቸው ትውስታችሁን አጋሩን (ለምስሉ ጥራት ይቅርታ 🙏)🎁ኮከቦቻችን በዘመናት እርዝማኔ ተሸፍነው እንዳይረሱ እናስታውሳቸው 🎁የ...
12/01/2025

ማንን ታስታውሳላችሁ?

እነዚህ ተጫዋቾች እነማን ናቸው? ሲጫወቱ ያያችዋቸው ትውስታችሁን አጋሩን
(ለምስሉ ጥራት ይቅርታ 🙏)

🎁ኮከቦቻችን በዘመናት እርዝማኔ ተሸፍነው እንዳይረሱ እናስታውሳቸው 🎁

የኢትዮጵያን ቀደምት ከዋክብት እያነገስን አዲሶቹን እያሳደግን ታሪካቸውን ለመጪዎቹ እናሻግራለን ✅
🎁🎁🎁አፍሮ ሶከር ኢትዮጵያ🎁🎁🎁
🎁🎁🎁 የኢትዮጵያ ሌጀንዶች ቤት 🎁🎁🎁

ገብረኪዳን ነጋሽ ፡ ጋምብሬ✅የጨዋታ ስፍራ ፡ የግራ መስመር አማካይ ፤ ተመላላሽ "የኮሪደሩ ንጉስ " ይሉታል የዛን ዘመን የቡድን አጋሮቹ ። እርግጥም ጋምብሬ በግራ መስመር ተመላላሽ ስፍራ ወ...
12/01/2025

ገብረኪዳን ነጋሽ ፡ ጋምብሬ

✅የጨዋታ ስፍራ ፡ የግራ መስመር አማካይ ፤ ተመላላሽ

"የኮሪደሩ ንጉስ " ይሉታል የዛን ዘመን የቡድን አጋሮቹ ። እርግጥም ጋምብሬ በግራ መስመር ተመላላሽ ስፍራ ወደር የሌለው ኮከብ ነበር ።ዘርፈ ብዙ የእግርኳስ ክህሎት የታደለው ይህ ተጫዋች በተለይ ፍጥነቱ፤ ጣጣቸውን ጨርሶ የሚያቀብላቸው የጎል ኳሶቹ ፤ የደብልፓስ እና የድሪብሊንግ ብቃቱ እጅግ ያስደምማል ።ግራ ተመላላሽ መደበኛ የጨዋታ ስፍራው ቢሆንም ኳስ ሲይዝ ከጨራሽ አጥቂዎችም ፈጥኖ ፔናሊቲ ቦክስ ውስጥ እየገባ ተከላካዮችን ያተራምሳል፤ ጎል ያስቆጥራል፤ የጎል ኳስ ያቀብላል ፤ በየትኛውም የሜዳ ክፍል ቡድኑን ያግዛል ።
✅ጅማሮው
⚽አዲስ አበባ ከየካ ሚካኤል ሰፈር የተገኘው ገብረኪዳን ነጋሽ ስሙን በኢትዮጵያ እግርኳስ ታሪክ ውስጥ በደማቁ የፃፈበትን ብቃት አንድ ብሎ ማዳበር የጀመረው ቄራ አልማዝዬ ሜዳ ላይ በመጫወት ነበር ። በወቅቱ የኳስ ተሰጥኦውን ያዩ የተለያዩ ክለብ መልማዮች ጥያቄ ቢያቀርቡለትም ጋምብሬ ግን የቡናን ማሊያ መልበስን መረጠ ...

✅ጋምብሬ ለኢትዬጵያ ቡና

⚽ጋምብሬ ከ1980 እስከ 1992 ለ12 አመታት ለኢትዮጵያ ቡና ተጫውቷል ። ከቡና ጋር ባሳለፈበት በዚያ ወርቃማ ዘመኑ በርካታ ድሎችን ተጎናፅፏል ፡
🏆1 የጥሎ ማለፍ ዋንጫ
🏆1 አሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ
🏆1 የኢትዮጵያ ዋንጫ በድምሩ ሶስት ዋንጫዎችን ከቡና ጋር አሳክቷል
🔑ይህ አማካይ 27 ጨዋታዎችን በአምበልነት መርቷል

⚽ጋምብሬ ከቡና በኋላ
1992 ከቡና ከተለያየ በኋላ ለትራንስ ፤ ለመድን ፤ ለምድር ባቡር ፤ ለአየር መንገድ ፤ እና ለአዳማ ከነማ ተጫውቷል ።

⚽ ብሔራዊ ቡድን ግልጋሎት
👉ጋምብሬ ከ1983 እስከ 1990 ድረስ ለ7 አመታት ለኢትዬጵያ ብሔራዊ ቡድን ግልጋሎት ሰጥቷል ። ሆኖም ከብቃቱ አንፃር የኢትዮጵያን ብሔራዊ ቡድን እንዲያገለግል በቂ እድል ካልተሰጣቸው የተገፉ ኮከቦች መካከል ጋምብሬ አንዱ ነው ።

✅አብሯቸው ከተጫወታቸው

ጋምብሬ አብሯቸው ከተጫወታቸው ቀደምት ከዋክብት መካከል አክሊሉ ገ/ማርያም (ዞፔው)-አሸናፊ በጋሻው-አፎዎርቅ ኪሮስ-አንዋር ያሲን-አበራ መንግስቴ-በለጠ ወዳጆ -አሰግድ ተስፋዬ (ጅሬስ) -ኤልያስ ጁሀር-ሳሙኤል ደምሴ (ኩኩሻ) ደረጄ ባቢ ይገኙበታል ።
✅ጋምብሬ ለ20 አመታት ከተጫወተ በኋላ ጫማውን ሰቅሏል ። ጫማውን ከሰቀለ በኋላ በግል ስራ ተሰማርቶ የተወሰኑ አመታትን ቢቆይም የእግርኳስ ፍቅር አላስችል ብሎት በ2011 በአሰልጣኝነት ተመለሰ ። የኢትዮጵያ ቡናን ታዳጊ ቡድን ተረክቦ ጥቂት አመታትን አሰልጥኗል ። በማስከተልም የዋናውን ቡድን የአሰልጣኝ ዲዲዬ ጎሜዝ እና የአሰልጣኝ ካሳዬ አራጌ ምክትል ሆኖ አሰልጥኗል ። በግሉም ፕሮጀክት ከፍቶ ታዳጊዎች ላይ እየሰራ ሲሆን በትርፍ ጊዜውም የጤና ቡድኖችን እያሰለጠነ ይገኛል ።

ጋምብሬ ከሚወደው ሞያ ሳይርቅ ቤተሰብ መስርቶ አዲስ አበባ እየኖረ ይገኛል ።

Afro Soccer Ethiopia/አፍሮ ሶከር ኢትዮጵያ
(ለምስሉ ጥራት ይቅርታ 🙏)

🎁ኮከቦቻችን በዘመናት እርዝማኔ ተሸፍነው እንዳይረሱ እናስታውሳቸው 🎁

የኢትዮጵያን ቀደምት ከዋክብት እያነገስን አዲሶቹን እያሳደግን ታሪካቸውን ለመጪዎቹ እናሻግራለን ✅
🎁🎁🎁አፍሮ ሶከር ኢትዮጵያ🎁🎁🎁
🎁🎁🎁 የኢትዮጵያ ሌጀንዶች ቤት 🎁🎁🎁

Address

Alexandria, VA

Telephone

+251704149670

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Afro Soccer Ethiopia / አፍሮ ሶከር ኢትዮጵያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Afro Soccer Ethiopia / አፍሮ ሶከር ኢትዮጵያ:

Share

Category

Afro Soccer Ethiopia

Promotes Ethiopian Football players’ Talent , Gives Transfer Information Services , (Foreign Clubs , Ethiopian Clubs , Agents , Managers , Scouts )