EthioTube

EthioTube Current events, breaking news, entertainment, exclusive interviews, variety shows & much more on Ethiopia. Watch All Things Ethiopia.

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አጣብቂኝ ውስጥ ስለመግባቱ የሚያትቱት ሦስቱ ሪፖርቶችከሰሞኑ የኢትዮጵያ ማክሮኢኮኖሚ ላይ ስለተጋረጡ አስቸጋሪ ሁኔታዎች የሚያትቱ ሦስት የተለያዩ ሪፖርቶች ወጥተዋል። ሪፖርቶ...
10/15/2025

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አጣብቂኝ ውስጥ ስለመግባቱ የሚያትቱት ሦስቱ ሪፖርቶች

ከሰሞኑ የኢትዮጵያ ማክሮኢኮኖሚ ላይ ስለተጋረጡ አስቸጋሪ ሁኔታዎች የሚያትቱ ሦስት የተለያዩ ሪፖርቶች ወጥተዋል። ሪፖርቶቹ ስለ ድህነት ምጣኔ መጨመር፣ የሀገሪቱ ገንዘብ የመግዛት አቅም ደካማ ከተባሉ የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ መመደቡን እና ኢትዮጵያ የብድር መክፈያ ጊዜዋ እንዲራዘም ያቀረበችው ጥያቄ በአበዳሪዎቿ ውድቅ ስለመደረጉ የሚያትቱ ናቸው።

- የኢትዮጵያ ብር የመግዛት አቅሙ ደካማ ከተባሉ የአፍሪካ ሀገራት መገበያያ ውስጥ ስለመመደቡ ምን ተባለ?

በሀገሪቱ ያለው ፖለቲካዊ አለመረጋጋት፣ የዋጋ ግሽበት እንዲሁም የውጭ ምንዛሬ እጥረት ሳቢያ የብር የመግዛት አቅም መውደቁን ተገልጿል። ከሌሎች ሀገራት ጋር ሲነፃጸር የኢትዮጵያ ብር የመግዛት አቅም ደካማ ከሚባሉ 21 የአፍሪካ ሀገራት መገበያያ ውስጥ የ 18 ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በዚህ ደረጃ የኢትዮጵያ ብር ተሽሎ አሊያም በልጦ የተገኘው ከሱዳን፣ ጊኒ እና ሴራሊዮን ሆኗል። ከሐምሌ 22/ 2016 ጀምሮ ኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ ግብይትን በገበያ ላይ የተመሰረተ እንዲሆን አድርጋለች። ይህን ተከትሎ የብር የመግዛት አቅም በከፍተኛ ደረጃ እንዲደካም ሆኗል። ከሁለት ዓመት በፊት በባንኮች 58 ብር ገደማ ይሸጥ የነበረው 1 የአሜሪካ ዶላር ዛሬ ላይ 141 ብር እየተሸጠ ይገኛል።

- በኢትዮጵያ ያለው የድህነት ምጣኔ እንደሚጨምር የሚገልጸው የዓለም ባንክ ሪፖርት ምን ይላል?

ባለፉት 20 ዓመት፤ በሀገሪቱ ያለውን የድህነት መጠንን በመቀነስ ረገድ ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸውን የሚጠቅሰው የዓለም ባንክ ሪፖርት ከ 4 ዓመት በፊት በኢትዮጵያ 39 በመቶ የነበረው የድህነት መጠን በዘንድሮ ዓመት ወደ 43 በመቶ ሊያሻቅብ ይችላል ማለቱን ኢትዮቲዩብ ከሪፖርቱ ላይ ተመልክቷል። የኮቪድ 19 ወረርሽኝ፣ በትግራይ ክልል ሲካሔድ የነበረው ጦርነት፣ የዋጋ ግሽበት ድርቅ፣ የጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ዕድገት የተጓተተ መሆን ሀገሪቱ ድህነትን ለመቀነስ እንዳትችል ያደረጓት ተግዳሮቶች መሆናቸው ተገልጿል።

አሁን ላይ ያለው የዋጋ ግሽበት በተለይ በከተማ ነዋሪዎችን ላይ ከፍ ያለ ጫና እንዳሳደረ ሪፖርቱ ይጠቅሳል። በገጠራማ የሀገሪቱ ክፍል የሚኖሩ አርሶአደሮችም ቢሆኑ ምርታቸውን “በተገደበ ገበያ” ስለሚሸጡ ገቢያቸው አነስተኛ መሆኑ ተመልካቷል። በተጨማሪም በገጠር ከሚኖረው ማኀበረሰብ 86 በመቶ የሚሆነው ጎልማሳ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ያላጠናቀቁ ናቸው ተብሏል። ይህን የሚጠቅሰው የዓለም ባንክ በተያዘው የአውሮፓውያን ዓመት በኢትዮጵያ የድህነት መጠን ሊያሻቅብ ይችላል የሚል ትንበያውን አስታውቋል።

- ኢትዮጵያ የተቀበለችውን የ1 ቢሊዮን ዶላር ብድር የመክፈያ ጊዜ እንዲራዘምላት ያቀረበችውን ጥያቄ አበዳሪዎቿ ውድቅ ስለማድረጋቸው የሚገልጸው ሪፖርት

ኢትዮጵያ በወቅቱ ያልከፈለችውን የአንድ ቢሊዮን ዶላር ዩሮ ቦንድ በተመለከተ በገንዘብ ሚኒስቴር ልዑክ እና በግል አበዳሪዎች ኮሚቴ መካከል ሲደርግ የነበረው ድርድር ያለ ስምምነት መጠናቀቁ ተሰምቷል። ገንዘብ ሚኒስቴር ጥቅምት 4/2018 ዓ. ም. ባወጣው መግለጫ፤ የብድሩን አከፋፈል ሁኔታ አስመልክቶ ያለ ስምምነት መጠናቀቁን አስታውቋል። በድርድሩ ወቅት ኢትዮጵያ “ዋይት ኤንድ ኬዝ” እና “ላዛርድ” የተሰኙ የሕግ እንዲሁም የፋይናንስ አማካሪዎችን ይዞ መቅረቧን ተሰምቷል። ኢትዮጵያ ሁሉንም አበዳሪዎችን በእኩልነት ማስተናገድ የሚለውን አቋሟን በድርድሩ ወቅት እንዳንጸባረቀች ተመልካቷል።

ሁለቱ አካላት ስምምነት ላይ እንዳይደርሱ ካደረጉ ጉዳዮች አንዱ፤ የግል አበዳሪዎች ከሌሎች አበዳሪ አገራት ጋር በእኩል ዐይን መታየት አለባቸው የሚለው የኢትዮጵያ መንግሥት አቋም ነው ተብሏል። የቦንዱ ገዢዎችን የወከለው የአበዳሪዎች ኮሚቴም በአሁኑ ሰዓት ድርድሩ "ፍሬ አልባ" ደረጃ ላይ ነው የሚል ድምዳሜ ላይ መድረሱ ተሰምቷል በዚህ ሳቢያ "የሕግ እርምጃን ጨምሮ ሁሉንም አማራጮች እያጤነ" መሆኑ ተሰምቷል።

አካባቢን በክለዋል የተባሉ ግለሰቦች እና ተቋማትን በመቅጣት 1.8 ሚሊዮን ብር መገኘቱ ተገለጸበአዲስ አበባ ከተማ ጉለሌ እና በአዲስ  ከተማ ክፍለ ከተማ ወንዝ እና አካባቢን በክለዋል የተባሉ...
10/15/2025

አካባቢን በክለዋል የተባሉ ግለሰቦች እና ተቋማትን በመቅጣት 1.8 ሚሊዮን ብር መገኘቱ ተገለጸ

በአዲስ አበባ ከተማ ጉለሌ እና በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወንዝ እና አካባቢን በክለዋል የተባሉ 9 ግለሰቦች እና ተቋማት 1.8 ሚሊዮን ብር መቀጣታቸውን የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን አስታወቀ። ሁሴን አብደላ፣ ዳኞ አሙኔ የተባሉ ግለሰቦች እያንዳንዳቸው 150,000 ብር ተቀጥተዋል።

በተመሳሳይ ዝናሽ አሰፋ የተባሉ ግለሰብ 100 ሺህ ብር እንዲከፍሉ ተደርገዋል። ገዛኽኝ ባዴ እና ሙላቱ አስረድ የተባሉ ነዋሪዎች ደግሞ እያንዳንዳቸው 50 ሺህ ብር ተቀጥተዋል። የሽንት ቤት ፍሳሽ ወደ ወንዝ በመልቀቅ ምክንያት ጌትዬ ነጋሽ እና እሱባለው ማስረሻ የተሰኙ የጉለሌ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች እያንዳንዳቸው 150,000 ብር እንዲቀጡ መደረጋቸውን ባለሥልጣኑ አስታውቋል።

ወንዝ እና አካባቢን በመበከል በሚል ለቅጣት የተዳረጉት ሁለት ተቋማት የኦሮሚያ ግብርና ኀብረት እና ኤቲ. ኤ. ኤ. የተሰኙት መሆናቸው ተገልጿል። እነዚህ ተቋማት ደግሞ በአጠቃላይ 600,000 ብር እንዲከፍሉ ተደርጓል።

የቴክኖ ካሞን 40 የፎቶ ኤግዚቢሽን እና የማስተዋወቂያ ፕሮግራም በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር ቴክኖ ኢትዮጵያ የአዲሱ የስልክ ሞዴሉን ማስተዋወቂያ እና በካሞን 40 በተለያዩ የሀገ...
10/14/2025

የቴክኖ ካሞን 40 የፎቶ ኤግዚቢሽን እና የማስተዋወቂያ ፕሮግራም በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር

ቴክኖ ኢትዮጵያ የአዲሱ የስልክ ሞዴሉን ማስተዋወቂያ እና በካሞን 40 በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የተነሱ ፎቶዎች ኤግዚቢሽን ፕሮግራም ጥቅምት 1 በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር አካሂዷል፡፡

በፕሮግራሙ ከቦርድ ሴልፎን አዲስ አበባ ጋር በመተባበር በሀረር፣ ድሬዳዋ፣ ቁንዱዶ ተራራ እና አዲስ አበባ የተነሱ 250 ፎቶዎችን ለዕይታ በኤግዚቢሽን መልክ ያቀረበ ሲሆን ፕሮግራሙ የተለያዩ ሽልማቶችን የሚያሸልሙ አጓጊ ጌሞችን፣ የሙዚቃ ዝግጅቶችን፣ ምግብ እና መጠጥን ያካተተ ነበር፡፡
በፕሮግራሙ ከፍተኛ የመንግስት ሃላፊዎች፣ ፎቶግራፈሮች፣ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች፣ የቴክኖሎጂ አድራቂዎች እና ሌሎችም ተሳታፊ የነበሩ ሲሆን ሙሉ ቀን በዋለው ፕሮግራም ከ4000 በላይ ተመልካች ተገኝቶ ፎቶዎችን በመጎብኘት በዝግጅቱ መታደም ችሏል፡፡

በሙዚቃ ዲጄ ሼሪ፣ ዲጄ ፍላሽ ኪዶ፣ ዲጄ ፔድሩ ተመልካቹን ያዝናኑ ሲሆን በጨዋታ አዋቂ ደግሞ የተለያዩ ጌሞች ለተሳታፊው ቀርበው የተለያዩ ሽልማቶችን ለተወዳዳሪዎች ሸልመዋል፡፡
ቴክኖ ኢትዮጵያ ይህንን የፎቶ ኤግዚቢሽን ሲያካሂድ ለሁለተኛ ጊዜ ሲሆን በካሞን 30 የስልክ ሞዴሉ እንዲሁ በተለያዩ የሀገራችን ክፍል የተነሱ ፎቶዎችን እንዲሁ ለዕይታ አብቅቶ ነበር፡፡

አሁን ደግሞ በካሜራ እና በሌሎች ቴክኖሎጂዎች ከፍ ብሎ 50 ሜጋ ፒክስል የሶኒ ካሜራ ፣8 ሜጋ ፒክስል አልትራ ዋይድ አንግል ካሜራ እንዲሁም የቴክኖ ኤ አይ ቴክኖሎጂዎችን እንዲሁም ማራኪ ዲዛይንን ይዞ በመጣው የቴክኖ ካሞን 40 ስልኩ የሀገራችንን ባህል፣ ቀለም፣ መልክዕ ምድር የሚያሳዩ ከፍ ባለ ደረጃ የተነሱ ፎቶዎችን ለሁለተኛ ጊዜ ለዕይታ አቅርቧል፡፡

በፕሮግራሙ የቴክኖ ምርቶች የሆኑት አዲሱ የቴክኖ ታብሌት ሜጋ ፓድ፣ የተለያዩ የቴክኖ ሞዴል ስልኮች፣ ኤር ፖዶች ፣ስማርት ሰዓቶች፣ ላፕቶፖች እና ሌሎችም ለጎብኚዎች እንዲመለከቱ እና እንዲሞክሩ በፕሮግራሙ ቀርበው ነበር፡፡
ይህ ፕሮግራም በቴክኖ ካሞን 40 የካሜራ ሌንስ ሀገራችንን ልዩ ገፅታ ለማህበረሱ ማድረስ እና ማህበረሰቡን ከቴክኖሎጂ ጋር ማስተዋወቅ አላማው ያደረገ ጥምረት ሲሆን ወደፊትም መሰል ፕሮግራሞች ላይ ቴክኖ ኢትዮጵያ የሚሰራ ይሆናል፡፡

#ማስታወቂያ |

ካሊድ ፋውንዴሽን ከኢፌዲሪ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ጋር በመተባበር ለሶስት ሆስፒታሎች የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ፡፡ ***********************************...
10/14/2025

ካሊድ ፋውንዴሽን ከኢፌዲሪ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ጋር በመተባበር ለሶስት ሆስፒታሎች የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ፡፡
********************************************************************
በደቡብ ፈረንሳይ ሰላም ኢትዮጵያ መረዳጃ ማህበር ከወንድም ካሊድ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር በኢፌደሪ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ትብብር ለጎንደር ዩኒቨርስቲ ጠቅላላ ሆስፒታል፣ ለወልዲያ አጠቃይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እና ለኮንቦልቻ ጠቅላላ ሆስፒታል 30 ሚሊየን ብር የሚገመት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ፡፡

በርክክብ ስነ ስርዓቱ ላይ የኢፌዲሪ ጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ፣የባለስልጣን መስሪያቤቱ ም/ዋና ዳይሬክተሮች አቶ ፋሲካው ሞላ እና አቶ መስፍን ሙሉነህ፣የፋውንዴሽኑ ም/የቦርድ ሰብሳቢ አርቲስት ሰራዊት ፍቅሬ ፣የሶስቱ ሆስፒታሎች ተወካይ እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

ክብርት ሚኒስትሯ ባደረጉት ንግግር የበጎ ፍቃድ ስራ አስኪለመድ ግዜ ይወስዳል ነገር ግን ከተጀመረ በኋላ ባህል መሆን እንደሚችል ካሊድ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡
በኮቪድ ወቅት በራሳቸው ፍቃድ በራቸውን ከፍተው ማዕድ ያጋሩበትና ለሰው የደረሱበት ተግባር ዘር ሆኖ እዚህ ደርሷል በማለት አሁንም ግለሰብ፣ቤተሰብ እና ማህበረሰብ የሚገነባበት ቤት በመሆኑ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የኢፌዲሪ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ፋሲካው ሞላ ባስተላለፉት መልዕክት በፋውንዴሽኑ በርካታ ከጎዳና ላይ የሚኖሩ ወጣቶችና ሴቶችን ስልጠና በመስጠትና እራሳቸውን እንዲችሉ ማድረጉን እና በሃገራዊ ጉዳዬች ላይ የችግኝ ተከላ፣ የህዳሴ ግድብ ግንባታ፣የአቅመ ደካማ ቤቶች ግንባታ ስራ ላይ እየተሳተፉ መሆኑን ተመልክተናል ብለዋል፡:

አምራች ዜጋ እንዲፈጠር ህጻናት በመጠለያ እንዲያድጉ የተደረገውን ስራ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ትልቅ ክብር አለው ያሉት ም/ዋና ዳይሬክተሩ ወንድም ካሊድ ፋውንዴሽንን የመሰሉ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን የመመዝገብ ብቻ ሳይሆን ድጋፍ የማድረግም ሃላፊነት ባለስልጣን መስሪያቤቱ ስላለበት ለሌሎችም ሞዴል እንዲሆን እንሰራለን ብለዋል፡፡

ፋውንዴሽኑ ከዚህ ቀደም በአጭር ጊዜ ጥሪ ሰብዓዊ ድጋፍ ላይ መሳተፋን ገልጸው የዛሬው ድጋፍም ከዚህ ቀደም በገቡት ቃል መሰረት የፈጸሙት መሆኑን በመግለጽ ለዚህ ሁሉ ድጋፍ መነሻ የሆኑትን በደቡብ ፈረንሳይ ሰላም ኢትዮጵያ መረዳጃ ማህበርን አመስግነዋል ፡፡

ወንድም ካሊድ በሰጠው ማብራሪያ አሁን ላይ በፋውንዴሽኑ 120 እናቶች ከነልጆቻቸው እና ከ400 በላይ ወጣቶች መኖራቸውን ገልጸው የዛሬው ድጋፋ ከዛሬ ሁለት ዓመት በፊት በሰሜኑ የሃገራችን ክፍል በተፈጠረው ችግር ምክንያት ድጋፍ ለማድረግ የተሰራ ስራ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

ፋውንዴሽናቸው ከተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር በቅንጅት የሚሰራ ሲሆን በልዩ ሁኔታ የኢትዮጵያ አየር መንገድን እና ET ፋውንዴሽንን አመስግነዋል፡፡
በመጨረሻም ድርጅቱን የመጎብኘት እና ማዕድ የማጋራት ስራ ተሰርቷል፡፡

“በዚህ ዓመት ኮሪደር ብለን እንደ ዐዲስ የምንጀምረው[ፕሮጀክት] አይኖረንም” ከንቲባ አዳነች አቤቤበዘንድሮ ዓመት በአዲስ አበባ የሚጀመር ዐዲስ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት እንደማይኖር ከንቲባ ...
10/14/2025

“በዚህ ዓመት ኮሪደር ብለን እንደ ዐዲስ የምንጀምረው[ፕሮጀክት] አይኖረንም” ከንቲባ አዳነች አቤቤ

በዘንድሮ ዓመት በአዲስ አበባ የሚጀመር ዐዲስ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት እንደማይኖር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ። አስተዳደራቸው በ2018 ዓ.ም. የሚያተኩረው “በቤት ግንባታ” እና “በውኃ አቅርቦት” ላይ መሆኑን ገልፀዋል። ከንቲባዋ ይህን ያሳወቁት ትላንት ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም. በተካሔደው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት መደበኛ ጉባዔ ላይ በሰጡት ማብራሪያ ነው።

በየካቲት 2016 ዓ.ም. በአዲስ አበባ የተጀመረው የኮሪደር ልማት የመጀምሪያው ዙር ተጠናቅቆ ሁለተኛው ምዕራፍ በግንባታ ላይ ይገኛል። በዚህ የኮሪደር ልማት የሚሠራው “ከተማዋን የማደስ” እና “የማዘመን” ሥራ እንደሆነ አዳነች ተናግረዋል። ልማቱ የእግረኛና የተሽከርካሪ መንገድ ማስፋት እና ማስዋብ፣ የሳይክል መንገድ ግንባታ፣ የስፖርት ማዘውተሪያዎች ፣ የመኪና ማቆሚያ ሥፍራዎች እንዲሁም ለመዝናኛ አገልግሎት የሚውሉ ፓርኮች ግንባታ ላይ ያተኮረ ነው።

ሆኖም በዚህ ረገድ የተሰሩ ሥራዎች እና የተገኙ ውጤቶች ከከተማዋ ሥፋት አንፃር አነስተኛ መሆኑን ከንቲባዋ ለምክር ቤቱ አባላት ገልጸዋል። ምንም እንኳን ውጤቱ አነስተኛ ቢሆንም በዘንድሮ ዓመት የሚገነባ ዐዲስ የኮሪደር ልማት እንደማይኖር አዳነች አሳውቀዋል። የአስተዳደራቸው ዋና ትኩረት ለከተማዋ ነዋሪዎች መኖሪያ ቤት መገንባት እና የውኃ አቅርቦት ላይ መሆኑንም አመላክተዋል።

“ምክር ቤቱ ባለፈው ያፀደቀልን የ 2018 ትልቁ ትኩረት የቤት ግንባታ እና የውኃ አቅርቦት ነው ብለን አጸድቀናል። ዋናው እና ትልቁ ትኩረት የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ ነው። በመቶ ሺዎች[መገንባት] ጀምረናል” ብለዋል። ከንቲባዋ አክለውም “በዚህ ዓመት ኮሪደር ብለን እንደ ዐዲስ የምንጀምረው አይኖረንም። ጥናት እናደርጋለን ቤቶች እንገነባለን። በጥናታችን መሠረት ከሕዝብ ጋር ቅድሚያ የምሰጣቸው ያልናቸው ቦታዎች ላይ ውይይት እናደርጋለን ተግባቦት የመፍጠር ሥራዎችን እንሰራለን” ሲሉ በማብራሪያቸው ጠቁመዋል።

በ2018 ዓ.ም. የሚጀመር ዐዲስ የኮሪደር ልማት ባይኖርም በከተማዋ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት እንደሚቀጥል ግን አዳነች ተናግረዋል። ቀድመው የታቀዱ እና ግንባቸው የተጀመረ መንገዶች “የኮሪደር ልማት ስታንዳርድን በጠበቀ” መልኩ ይከናወናል ብለዋል።

በአዲስ አበባ ጀምሮ ወደ ሁሉም ክልሎች የተሻገረው የኮሪደር ልማት በ 10 ሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎችን “ያባረረ” መሆኑን የአሜሪካ መንግሥት መናገሩ ይታወሳል። መስከረም 16/2018 ዓ.ም. ይፋ የተደረገው ሪፖርት፤ በኮሪደር ልማቱ ዜጎችን “በጥቂት” እና “ካለምንም ካሳ ከማፈናቅሉ” ባለፈ ግንባታውን የሚያከናውኑት ኩባንያዎች “ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር ግንኙነት ያላቸው” እንደሆኑ ሪፖርቱ ያትታል። በዚህ ምክንያት “ያለጨረታ” የግንባታ ሥራው እንደተሰጣቸው መገለጹ አይዘነጋም።

የዓለም ዋንጫ ማጣርያ አስረኛ የምድብ ጨዋታ ውጤት🇧🇫 ቡርኪና ፋሶ 3-1 ኢትዮጵያ 🇪🇹
10/12/2025

የዓለም ዋንጫ ማጣርያ አስረኛ የምድብ ጨዋታ ውጤት

🇧🇫 ቡርኪና ፋሶ 3-1 ኢትዮጵያ 🇪🇹

በሴቶች ማራቶን ታሪክ 5ኛ ፈጣኑ ሰአት - ሀዊ ፈይሳ! ጀግኒት!-----5th of all time 😤 🇪🇹‘s Hawi Feysa storms to victory at the Chicago marathon...
10/12/2025

በሴቶች ማራቶን ታሪክ 5ኛ ፈጣኑ ሰአት - ሀዊ ፈይሳ! ጀግኒት!

-----

5th of all time 😤

🇪🇹‘s Hawi Feysa storms to victory at the Chicago marathon in 2:14:56, becoming the fifth fastest woman in history 🤯

Her compatriot Megertu Alemu finishes in second for a 1-2 Ethiopian finish ✨

በአፋር ክልል በተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ ከ43 ሺህ በላይ ሰዎች ከመኖሪያቸው ተፈናቀሉ- አንድ የ12 ዓመት አዳጊ ልጅ ሕይወት አልፏልበአፋር ክልል፣ ኪልበቲ ረሱ ዞን፣ በርሃሌ ወረዳ ትላንት...
10/12/2025

በአፋር ክልል በተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ ከ43 ሺህ በላይ ሰዎች ከመኖሪያቸው ተፈናቀሉ

- አንድ የ12 ዓመት አዳጊ ልጅ ሕይወት አልፏል

በአፋር ክልል፣ ኪልበቲ ረሱ ዞን፣ በርሃሌ ወረዳ ትላንት ምሽት በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ 43,456 ሰዎች ከመኖሪያቸው መፈናቀላቸው ተሰማ። የመጀመሪያው ርዕደ መሬት ከደረሰበት ከትላንት ጥቅምት 1/2018 ዓ.ም. ምሽት 12 ሰዓት ጀምሮ ለስድስት ጊዜያት ያህል የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን በርሃሌ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አሊ ሁሴን ለ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ተናግረዋል።

በወረዳው ካሉ ቀበሌዎች በርዕደ መሬቱ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው፤ ቡሬ እና አስ ጉቢ አላ የተሰኙ ቀበሌዎች መሆናቸውንም አቶ አሊ ገልፀዋል። በሬክተር ስኬል 5.6 በተለካው የመሬት መንቀጥቀጥ በሁለቱ ቀበሌዎች በርካታ ቤቶችን ማፍረሱን ዘገባው አመላክቷል።

በዚህ ሳቢያ ከተፈናቀሉት ከ 43 ሺህ በላይ ሰዎች በተጨማሪ 6 ሰዎች መጎዳታቸውን እንዲሁም አንድ የ12 ዓመት አዳጊ ልጅ ሕይወት ማለፉን አስተዳዳሪው አስታውቀዋል። ከተጎጂዎቹ ውስጥ ሶስቱ ወደ በርሃሌ ሪፈራል ሆስፒታል ተወስደው ሕክምና እየተደረገላቸው ነው ተብሏል። በትላንትናው ዕለት ከአፋር ክልል በተጨማሪ በትግራይ ክልል ሦስት ጊዜ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ ነበር።

የመጀመሪያው 4.2 በሬክተር ስኬል የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ከመቐለ ሰሜን ምስራቅ 47 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የተከሰተ ነው። ሁለተኛው፤ ከውቅሮ ከተማ 32 ኪሎ ሜትር በሚርቅ ቦታ ላይ ሲሆን 5.3 በሬክተር ስኬል የተመዘገበ ነው። ትላንት ማታ የተከሰተው ሦስተኛው የመሬት መንቀጥቀጥ ደግሞ በሬክተር ስኬል 5.6 ሆኖ የመዘገበ ነው

በሰሜን ወሎ ተካሔዶ በነበረው ውጊያ፤ በፋኖ ኀይሎች ተይዘው  የነበሩትን የመንግሥት የፀጥታ አባላት መረከቡን ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ አስታወቀበሰሜን ወሎ ዞን ዋና ከተማ ወልዲያ ዙሪ...
10/11/2025

በሰሜን ወሎ ተካሔዶ በነበረው ውጊያ፤ በፋኖ ኀይሎች ተይዘው የነበሩትን የመንግሥት የፀጥታ አባላት መረከቡን ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ አስታወቀ

በሰሜን ወሎ ዞን ዋና ከተማ ወልዲያ ዙሪያ ተካሔዶ በነበረው ውጊያ በፋኖ ኀይሎች ተይዘው የነበሩትን የመንግሥት የፀጥታ አባላት መረከቡን ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ አስታውቋል።

በመስከረም ወር አጋማሽ በዞኑ የተካሔደው “ድንገተኛ ውጊያ ከፍተኛ ጉዳትን ያስከተለ” እንደነበር ዓለም አቀፉ ድጋፍ ሰጪ ተቋም ገልጿል። ባለፉት 6 ቀናት ሁለት ቡድኖችን በወልዲያ እና በላሊበላ ከተማዎች በማስፈር የሰብአዊ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን ጉዳዩ ን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ ላይ አስፍሯል።

በአንድ ሳምንት ውስጥ ለወልዲያ ሆስፒታል እንዲሁም በሙጃ እና ኩልመስክ አካባቢ ለሚገኙ የጤና ተቋማት የሕክምና መሳሪያዎችን ማበርከቱን አስታውቋል። ከመሳሪያዎቹ ውስጥ የቀዶ ጥገና ሕክምና ለመስጠት የሚያገለግሉ እንደሚገኝበት ተመላክቷል። በዚህም በውጊያው ከፍተኛ ጉዳት ከደረሰባቸው ውስጥ 250 ለሚሆኑት የቀዶ ጥገና ሕክምና መስጠት እንደሚቻል ተገልጿል።

ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ ካደረገው የሕክምና ድጋፍ በተጨማሪ በፋኖ ኃይሎች ተይዘው የሚገኙ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎችን መጎብኘቱን ትላንት ባወጣው መግለጫ ላይ አመልክቷል። ኮሚቴው አክሎም ወታደሮቹን ከፋኖ ኃይሎች ተረክቦ ወልዲያ ከሚገኙ አባላቶቻቸው ጋር እንዲቀላቀሉ መደረጋቸውን አመልክቷል።

በላሊበላ ከተማ የሚገኘውን የድጋፍ ሰጪ ቡድን የሚመሩት ማርቲን ታልማን “ በቅርብ ቀናት ውስጥ በሰሜን ወሎ በርካታ ሰዎች [በውጊያው] ተገድለዋል እንዲሁም ቆስለዋል” ሲሉ ተናግረዋል። ሆኖም የጤና ተቋማት “በተገደበ አቅም” የቆሰሉ ወታደሮችን እና ሲቪሎችን እያከሙ መሆናቸውንም ቡድን መሪው አስታውቀዋል።

በጎፋ ዞን በመሬት መንሸራተት ምክንያት ለተፈናቀሉ ዜጎች የተዋጣውን 60 ሚሊዮን ብር ለመሥረቅ ሞክረዋል በተባሉ ተጠርጣሪዎች ላይ  ምርመራ ተጀመረዓመት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ተከስ...
10/09/2025

በጎፋ ዞን በመሬት መንሸራተት ምክንያት ለተፈናቀሉ ዜጎች የተዋጣውን 60 ሚሊዮን ብር ለመሥረቅ ሞክረዋል በተባሉ ተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራ ተጀመረ

ዓመት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ተከስቶ በነበረው የመሬት መንሸራተት ለተፈናቃሉ ነዋሪዎች የተሰበሰበ 60 ሚሊዮን ብር ለመዝረፍ ሞክረዋል በተባሉ ተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራ መጀመሩን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አሳወቋል፡፡

በኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነትና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክተር የሆኑት ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ እንደገለጹት፤ የምርመራ ሥራው የተጀመረው እስከአሁን በሕግ ቁጥጥር ሥር በሚገኙ ስድስት ተጠርጣሪዎች ላይ ነው ፡፡

ተጠርጣሪዎቹ፤ በጎፋ ዞን ፋይናንስ መምሪያ እና በዞኑ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ጽሕፈት ቤት በሂሳብ ሠራተኝነት እና በኃላፊነት በማገልገል ላይ የነበሩ ግለሰቦች መሆናቸውን ዳይሬክተሩ ለጀርመን ድምፅ ሬድዮ ተናግረዋል።

ግለሰቦቹ በአደጋው ለተፈናቀሉ ዜጎች ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች በድጋፍ የተዋጣ 60, 276,383 (ስልሳ ሚልዮን ሁለት መቶ ሰባ ስድሰት ሺ ሦስት መቶ ሰማንያ ሦስት ብር) ከአዲስ አበባ ንግድ ባንክ ሸገር ቅርንጫፍ በቼክ ለማውጣት በእንቅስቃሴ ላይ ባሉበት ወቅት መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

በጉዳዩ ላይ ለሕግ አካላት በደረሰ ጥቆማ መሠረት በተደረገ ክትትል ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር ሊውሉ እንደቻሉ ምክትል ኮማንደር አሸናፊ አስረድተዋል።

በአሁኑ ወቅት "ከጉዳዩ ጋር ንክኪ ሊኖራቸው ይችላል ተብለው በተጠረጠሩ ተጨማሪ ሰዎች ላይ ክትትል እየተደረገ ይገኛል" ሲሉ አክለዋልበደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ ሐምሌ 15 2016 ዓ.ም በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ ከሁለት መቶ በላይ ሰዎች ሕይወታቸው ማለፉ የሚታወስ ነው ።

በአደጋው ከቀበሌው የተፈናቀሉ ነዋሪዎችን መልሶ ለማቋቋም በአገር ውስጥ እና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን እና ድርጅቶች የገንዘብ እና የቁሳቁስ ድጋፍ ሲያደርጉ መቆየታቸው አይዘነጋም።

ዐዲሱን የተሽከከርካሪ ሰሌዳ ይፋ ያደረጉት የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ ሰንደቅዓላማ ሊለወጥ እንደሚችል ጠቆሙ በዐዲስ መልክ የተዘጋጀውን የተሽከርካሪዎች ሰሌዳ ትላንት መ...
10/09/2025

ዐዲሱን የተሽከከርካሪ ሰሌዳ ይፋ ያደረጉት የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ ሰንደቅዓላማ ሊለወጥ እንደሚችል ጠቆሙ

በዐዲስ መልክ የተዘጋጀውን የተሽከርካሪዎች ሰሌዳ ትላንት መስከረም 28/2018 ዓ.ም. ይፋ ያደረጉት የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) የሰንደቅዓላማ ለውጥ ሊኖር እንደሚችል ጠቆሙ። በዚህ ምክንያት በዐዲሱ ታርጋ ላይ ሊደረግ የታቀደው የኢትዮጵያ ሰንደቅዓላማ ሳይካተት መቅረቱን ገልፀዋል።

በሁለት ወራት ውስጥ ወደ አገልግሎት ይገባል የተባለው ሰሌዳ “የሕግ አካላት እና መዝጋቢዎች ብቻ” መመልከት የሚችሉት፤ ስለተሽከርካሪው መረጃ የያዘ “ቺብስ” የተገጠመለት ነው ተብሏል። መረጃዎቹ፤ “የተሽከርካሪው ቻንሲ”፣ “የሲሪያል ቁጥር”፣”የሦስተኛ ወገን” እና “የቴክኒክ ምርመራ” ሁኔታን የሚገልጹ እንደሆነ በትላንትናው መግለጫ ላይ ተነስቷል። ከዚህ ቀደም የክልሎችን እና የከተማዎችን ስም ይዞ ይታተም የነበርውን ሰሌዳ የሚያስቀረው ዐዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ፤ “ኢቲ” የሚለውን የሀገሪቱን መለያ ኮድ ብቻ ይዞ የተዘጋጀ ነው።

በሰሌዳው ላይ የኢትዮጵያን ሰንደቅዓላማ ለማካተት ታቅዶ እንደነበር የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ተናግረዋል። ሆኖም የሰንደቅዓላማ ለውጥ ሊኖር ስለሚችል ዕቅዱ ሊቀር እንደቻለ አስረድተዋል። “የመጀመሪያው Draft[ንድፍ] ሰንደቅ ዓላማውን ያካተተ እንደነበር ገልጸዋል። ሆኖም የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ከሰበሰባቸው አጀንዳዎች አንዱ የሰንደቅዓላማ ጉዳይ በመሆኑ ዐዲሱ ሰሌዳ “ጊዜያዊ እንዳይሆን ሲባል” አንዳይካተት ተደርጓል።

“እንደምታውቁት ሀገራችን ብሔራዊ ምክክር ላይ ነው ያለችው አንዱ የብሔራዊ ምክክር አጀንዳ ሰንደቅዓላማ ምልክት አርማዎቹ ላይ ነው። ይሄ ሰሌዳ ለረጅም ዓመት እንዲያገለግል ነው የምንፈልገው። በብሔራዊ ምክክር አሁን ባለው የሰንደቅዓላማ ቅርጽ እና መልክ ቢቀየርስ? ይሄን የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው በምክክር የሚወስነው አናውቅም ዛሬ ላይ ሆነን። ስለዚህ ጊዜያዊ ሰሌዳ እንዳይሆነብን 2 ሚሊዮን [ሰሌዳ] አስመርተን፣ቀይረን በነጋታው በምክክር ሌላ ውጤት ቢመጣ ብለን ትተነዋል” በማለት አስረድተዋል።

በቅርቡ የወጣው፤ “የተሽከርካሪዎች የመለያ ቁጥር ሠሌዳ ዓይነቶች እና ምልክቶች መወሰኛ እንዲሁም የአገልግሎት አሰጣጥ መመሪያ” ዐዲሱ የተሽከርካሪዎች ሰሌዳ ከሰንደቅዓላምው በተጨማሪ የኢትዮጵያን ካርታ ይዞ እንደሚታተም የሚገልጽ ቢሆንም ትላንት ይፋ በተደረገው ሰሌዳ ላይ ግን ሳይካተት መቅረቱን ኢትዮቲዩብ ተመልክቷል።

Address

4900 Leesburg Pike, Ste 414
Alexandria, VA
22302

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EthioTube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to EthioTube:

Share