EthioTube

EthioTube Current events, breaking news, entertainment, exclusive interviews, variety shows & much more on Ethiopia. Watch All Things Ethiopia.

መድፈኞቹ አልተቻሉም!አርሰናል 4-1 ቶተንሃምዋንጫው የማንነው ዘንድሮ? 🤔
11/23/2025

መድፈኞቹ አልተቻሉም!

አርሰናል 4-1 ቶተንሃም

ዋንጫው የማንነው ዘንድሮ? 🤔

የሊቨርፑል እና የማንችስተር ሲቲ መሸነፍን ተከትሎ የአርሰናል ደጋፊዎች ወቅታዊ ሁኔታ...
11/22/2025

የሊቨርፑል እና የማንችስተር ሲቲ መሸነፍን ተከትሎ የአርሰናል ደጋፊዎች ወቅታዊ ሁኔታ...

የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ዕለታዊ ሁኔታህዳር 13/ 2018 Marburg Virus Disease Daily update Ethiopia November 22/ 2025
11/22/2025

የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ዕለታዊ ሁኔታ
ህዳር 13/ 2018
Marburg Virus Disease Daily update
Ethiopia
November 22/ 2025

የአምናው ሻምፒዮን ሊቨርፑል በሜዳው አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቷልሊቨርፑል 0-3 ኖቲንግሃም ፎረስትየሊቨርፑል የዋንጫ ተስፋ ጨለመ ማለት እንችላለን? 🤔
11/22/2025

የአምናው ሻምፒዮን ሊቨርፑል በሜዳው አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቷል

ሊቨርፑል 0-3 ኖቲንግሃም ፎረስት

የሊቨርፑል የዋንጫ ተስፋ ጨለመ ማለት እንችላለን? 🤔

ዶክተር አንዷለም ዳኜ ላይ የግድያ ወንጀል የፈጸመው ግለሰብ በ25 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ተወሰነበትበአማራ ክልል ባሕርዳር ከተማ ምሽት ላይ ወደሚሠሩበት ጥበበ ጊዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታ...
11/21/2025

ዶክተር አንዷለም ዳኜ ላይ የግድያ ወንጀል የፈጸመው ግለሰብ በ25 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ተወሰነበት

በአማራ ክልል ባሕርዳር ከተማ ምሽት ላይ ወደሚሠሩበት ጥበበ ጊዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሲሔዱ የነበሩትን ዶክተር አንዷለም ዳኜን በጥይት የተገደለው ግለሰብ በ 25 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ተወስኖበታል።

ተከሳሽ እሱባለው ወይም ሳሙኤል ነበረ የተባለው ግለሰብ ጥር 24/2017 ዓ.ም. ምሽት ከአንድ እስከ ሁለት ሰዓት በሚሆንበት ጊዜ ዶክተር አንዷለም ዳኜን የያዘውን ንብረት ለመውሰድ እንዲመቻቸው በማሰብ ያሽከረክር የነበረውን መኪና እንዲያቆም ሲጠይቁት ፍቃደኛ ባለመሆኑ ሁለት ጥይት በመተኮስ ዶ/ር አንዷለም ዳኜን ደረቱን እና ክንዱን በመምታት እንደገደሉት የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስታውቋል።

ተከሳሹ በተመሳሳይ ጊዜ እና ቦታ ላይ ወደ ጥበበ ጊዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሲሄድ የነበረው ዶ/ር በረከት አማረ ላይ ሁለት ጥይት በመተኮስ የመኪናውን ቦዲ በመምታት ተበዳዩን የሳተው በመሆኑ በፈጸመው ከባድ የሆነ ሰው መግደል ሙከራ ወንጀል መከሰሱ ተመላክቷል። ሦስተኛው ክስ ደግሞ ሐሰተኛ የቀበሌ መታወቂያ ሰነዶችን መገልገል ወንጀል ፈጽሟል የሚል ነው።

ተከሳሹም የቀረቡበትን ክሶች ክዶ የተከራከረ ቢሆንም፣ ጉዳዩን ሲከታተል የቆየው የባሕርዳርና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የዐቃቤ ሕግን ማስረጃዎች በመስማት ተከሳሽ እንዲከላከል ብይን ሰጥቶ የመከላከያ ማስረጃዎችን ከሰማ በኋላ ተከሳሹ የቀረቡበትን ክሶች ለመካለከል ባለመቻሉ በሦስቱም ክሶች በአጠቃላይ በ25 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ በሙሉ ድምጽ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡

ዶክተር ዳኜ በ2005 ዓ.ም. የመጀመሪያ የሕክምና ዶክትሬት ዲግሪያቸውን ከጅማ ዩኒቨርስቲ ነበር ያገኙት። ከፍተኛ ማዕረግ የወርቅ ሜዳሊያና በዩኒቨርሲቲ ደርጃ የዋንጫ ተሸላሚ የነበሩት የሕክምና ባለሞያ በጀርመን፣ በእንግሊዝ፣ በሕንድ፣ በደቡብ አፍሪካ እና በቱርክ የተለያዩ ሥልጠናዎችን ወስደዋል። የጉበት፣ የሀሞት ከረጢት እና የቆሽት ሰብ ስፔሻሊስት የነበሩት ዶክተር ዳኜ ሁለት ሴቶችና የአምስት ዓመት ዕድሜ ያለው አንድ ወንድ ልጅ አባት ነበሩ።

“በኮሪደር ልማቱ የተፈናቀለው ድህነት እንጂ ድሀ አይደለም” አቶ ግርማ ሰይፉበአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ አካባቢዎች እየተሰራ በሚገኝ የኮሪደር ልማት “የተፈናቀለው ድህነት እንጂ ደሀ አይደለ...
11/19/2025

“በኮሪደር ልማቱ የተፈናቀለው ድህነት እንጂ ድሀ አይደለም” አቶ ግርማ ሰይፉ

በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ አካባቢዎች እየተሰራ በሚገኝ የኮሪደር ልማት “የተፈናቀለው ድህነት እንጂ ደሀ አይደለም” ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ፤ የከተማ ውበት እና የአረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ የሆኑት አቶ ግርማ ሰይፉ ተናግረዋል። ኃላፊው ከኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ ጋር በነበራቸው ቆይታ በከተማዋ የለማው የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማት አዲስ አበባን አረንጓዴ ለማድረግ የታቀደውን ዕቅድ 22% ማሳካቱን ጠቁመዋል።

በየካቲት 2016 ዓ.ም. በአዲስ አበባ የጀመረው የኮሪደር ልማት ከ 40 በላይ በሚሆኑ የክልል ከተማዎች ላይ እየተከናወነ ይገኛል። ልማቱ በዋናነት ዋና ዋና መንገዶችን የማስዋብ፣ የእግረኛ መንገድን የማስፋት፣ የሳይክል መንገድ ማዘጋጀት፣ መዝናኛ ቦታዎችን የመገንባት እንዲሁም የመንገድ ዳር መብራት እና ቴሌኮሚዩኒኬሽን መስመሮችን በዘመናዊ መንገድ የመዘርጋት ሥራዎች የሚከናወኑበት ነው። በአዲስ አበባ ከተማ በሁለት ዙሮች የተከናወነው የልማት ሥራ በርካታ አካባቢዎችን የሸፈነ ነው። እንደ አቶ ግርማ ሰይፉ ማብራሪያ ከሆነ ልማቱ የከተማዋን “15 በመቶ አካባቢ” የሸፈነ ነው።

ሆኖም “በጋራ በራስ አቅም የማልማት ሂደቱ ይቀጥላል” ማለታቸው ተመላክቷል። ምንም እንኳን ኃላፊው ይህንን ቢሉም በዘንድሮ ዓመት “በአዲስ አበባ የሚጀመር ዐዲስ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት እንደማይኖር” ከንቲባ አዳነች አቤቤ መናገራቸው ይታወሳል። ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም. በተካሔደው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት መደበኛ ጉባዔ ላይ በሰጡት ማብራሪያ፤ አስተዳደራቸው በ2018 ዓ.ም. የሚያተኩረው “በቤት ግንባታ” እና “በውኃ አቅርቦት” ላይ መሆኑን ገልፀዋል።

ከንቲባዋ መጋቢት 18/2016 ዓ.ም. ሰለ ኮሪደር ልማቱ በሰጡት ማብራሪያ በአዲስ አበባ ከፒያሳ እና አካባቢው በተከናወነው የኮሪደር ልማት ግንባታ ብቻ ወደ 11 ሺህ የሚሆኑ ሰዎች መነሳታቸውን መግለጻቸው አይዘነጋም። የከተማዋ ውበት እና የአረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ ግን በልማቱ ምክንያት ተፈናቀለ የሚባለው ድህነት እንጂ ድሀ አይደለም” ብለዋል። እንደሳቸው ገለጻ የኮሪደር ልማቱ “ንፁህ አየር ለመተንፈስ ፣ ውብ አካባቢ መኖር እና የሥራ ዕድልን የፈጠረ” ነው ሲሉ ገልጸዋል። ኃላፊው አክለውም “የቦታ ዲሞክራሲ የሰጠ” መሆኑን ተናግረዋል።

በአማራ ክልል ከስምንት ዓመት ሕፃን እስከ 65 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ከ2,000 በላይ ሴቶች  የአስገድዶ መድፈር ጥቃት እንደደረሰባቸው ተገለጸበአማራ ክልል፤ ከሦስት ዓመት በፊት በተቀሰቀሰው ...
11/19/2025

በአማራ ክልል ከስምንት ዓመት ሕፃን እስከ 65 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ከ2,000 በላይ ሴቶች የአስገድዶ መድፈር ጥቃት እንደደረሰባቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል፤ ከሦስት ዓመት በፊት በተቀሰቀሰው ግጭት ሳቢያ ከስምንት ዓመት እስከ 65 ዓመት ዕድሜ ያላቸው 2,697 ሴቶች የአስገድዶ መድፈር ጥቃት እንደደረሰባቸው ተገለጸ። ከሐምሌ 18/2015 ዓ.ም. እስከ ግንቦት 2017 ዓ.ም. ድረስ ባለው ጊዜ ተፈጽሟል በተባለው ጥቃት ሁለቱም ተፋላሚ ኃይሎች ማለትም “የመከላከያ ሠራዊት አባላት እና የፋኖ ታጣቂዎች መሳተፋቸው” ተሰምቷል።

ይህ የተገለጸው፤ የአስገድዶ መድፈር ጥቃት ተጎጂዎችን እና የጤና ባለሙያዎችን በማነጋገር ቢቢሲ ዛሬ ኀዳር 10/2018 ዓ.ም ባወጣው ዘገባ ነው። በአማራ ክልል ከሚገኙ 43 የጤና ጣቢያዎች እና የሕክምና ምንጮች በተሰበሰበ መረጃ ወሲባዊ ጥቃት ከደረሰባቸው ሴቶች ውስጥ 45 በመቶ የሚሆኑት “ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች” መሆናቸው ተመላክቷል። ከተጎጂዎች ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት በደረሰባቸው ጥቃት “በአባላዘር በሽታ ሲያዙ በርካቶች ደግሞ ለእርግዝና እና ለከባድ የሥነ ልቦና ቀውስ ተዳርገዋል” ሲል ዘገባው ያትታል።

ግጭቱ ባሳደረው የትራንስፖርት መስተጓጎል እና መንገድ መዘጋት ምክንያት በርካታ ተጎጂዎች የሕክምና አገልግሎት ለማግኘት መቸገራቸውን አንድ የጤና ባለሙያ ተናግረዋል። “በዚህ ምክንያት ኤችአይቪን ጨምሮ የአባላዘር በበሽታዎች መከላከያ[መድኃኒቶች] በማይሠሩበት ወቅት እንደሚደርሱ” ተገልጿል።

ከጤና ተቋማት በተሰበሰበ መረጃ መሠረት "የኤችአይቪ [ሥርጭት] እንደሚጨምር የሚያሳዩ ምልክቶች መኖራቸው”፣ “የሥነ አዕምሮ እና ሥነ ልቦና ጤና ችግሮች እጅግ የከፋ ደረጃ ሊያደርስ ይችላል" የሚል ስጋት መኖሩን ዘገባው አመልክቷል።ከዚህ በተጨማሪ በደረሰባቸው ጥቃት ምክንያትን ራሳቸውን ያጠፉ ተጎጂዎች መኖራቸውንም የጤና ባለሙያዎች መናገራቸውን አስታውቋል።

ቢቢሲ በዘገባው ወሲባዊ ጥቃቱን የፈጸሙት ሁለቱም ተፋላሚ ወገኖች ማለትም፤ የመከላከያ ሰራዊት አባላት እና የፋኖ ኃይሎች ናቸው ብሏል። ሆኖም “ከፋኖ ታጣቂዎች በበለጠ የመንግሥት ወታደሮችን ተሳታፊ መሆናቸውን” የጤና ባለሙያዎች ማናገራቸውን አስታውቋል። “አብዛኞቹ የአስገድዶ መድፈር ጥቃቶች መከላከያ ሠራዊት ካምፕ በመሠረተባቸው እና በሚቆጣጠራቸው ከተሞች አካባቢ የተፈፀሙ” መሆናቸውን ገልጿል።

ቢቢሲ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ለቀረቡበት ክሶች እና ወቀሳዎች ምላሽ እንዲሰጥ የጠየቀ ሲሆን፤ ከወራት መጠበቅ በኋላ ምላሽ አላገኙሁም ብሏል። የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል ሰብሳቢ እና የፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊ የሆኑት አቶ አስረስ ማረ ግን “ተዋጊዎቻቸው የአስገድዶ መድፈር ጥቃቶች ስለመፈፀማቸው እውቅና እንደሌላቸው እና የቀረበባቸው ክስም እንደሌለ ተናግረዋል” መባሉን ሰምተናል።

11/19/2025

ኑ የዘንድሮው 25ተኛ አመት የታላቁ ሩጫን ከቴክኖ ጋር አብረን እንሩጥ ፤ የማይረሱ ትዝታዎችን በአዲሱ ቴክኖ ስፓርክ 40 ፕሮ ፕላስ አብረን እናስቀር፡፡ በዘንድሮ ታላቁ ሩጫ ከሩጫው ጎን ለጎን ኑ አብረን ፎቶ እንነሳ ፣ የማይረሳ ጊዜ እናሳልፍ አዲሱን የቴክኖ ስፓርክ 40 ስልኮች አብረን እንሞክር እያላችሁ ነው ቴክኖ ኢትዮጵያ፡፡



#ማስታወቂያ |

ከዚህ ምስል ላይ ማንን ታውቃላችሁ? 🤔
11/18/2025

ከዚህ ምስል ላይ ማንን ታውቃላችሁ? 🤔

በደቡበ ኢትዮጵያ ክልል “ማርበርግ ቫይረስ” የተጠረጠሩ ስድስት ሰዎች መሞታቸውን መንግሥት አስታወቀከሰሞኑ በደቡብ  ኢትዮጵያ ክልል ጂንካ ከተማ መከሰቱ በታወቀው “ማርበርግ ቫይረስ” የተጠረጠ...
11/17/2025

በደቡበ ኢትዮጵያ ክልል “ማርበርግ ቫይረስ” የተጠረጠሩ ስድስት ሰዎች መሞታቸውን መንግሥት አስታወቀ

ከሰሞኑ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጂንካ ከተማ መከሰቱ በታወቀው “ማርበርግ ቫይረስ” የተጠረጠሩ ስድስት ሰዎች ሕይወታቸው ማለፉን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። ተቋሙን የሚመሩት ዶ/ር መቅደስ ዳባ ዛሬ ሰኞ ኀዳር 8/2018 ዓ.ም. ለብዙኃን መገናኛ በሰጡት መግለጫ፤ አሁን ላይ “በቫይረሱ የተያዘ ሰው የለም” ብለዋል።

የጤና ሚኒስቴር በሀገሪቱ የተከሰተውን “ማርበርግ ቫይረስ” አስመልክቶ በባለው ሳምንት ባወጣው መግለጫ 8 ሰዎች በበሽታው መጠርጠራቸውን አስታውቆ ነበር። በዛሬው መግለጫ በቫይረሱ “ተጠርጣሪ የነበሩ 17 ሰዎች” መለየታቸውን ሚኒስትሯ ገልጸዋል።

ሆኖም ይተጠረጠሩት ሰዎች በተደረገላቸው ምርመራ በ “ማርበርግ ቫይረስ” ነፃ መሆናቸው ተረጋግጧል ብለዋል። “ተጠርጣሪዎች የነበሩ ወይም ምልክት ኖሯቸው ንክኪ ሊኖራቸው ይችላል ያልናቸው 17 ሰዎች መርምረናል። እስካሁን ባለው ምልክት ኖሯቸው ሕክምና ባደረግናቸው ሰዎች ውስጥ ቫይረሱ በሰውነታቸው ውስጥ እንዳልተገኘ ነው የሚያሳየው” ብለዋል። ይሁን እንጂ እስካሁን በዚህ ቫይረስ 6 ሰዎች ሕይወት ማለፉን አስታውቀዋል። ከሟቾቹ ውስጥ ቫይረሱ እንዳለባቸው በላቦራቶሪ የተረጋገጠው ግን በሦስቱ ሰዎች ላይ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል።

“እስካሁን እንግዲ በበሽታው መጠርጠር ደረጃ ከተባለ በ 6 ሰዎች የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ምልክቶች አሳይተው ሕይወታቸው ያለፈ ሲሆን ነገር ግን በትክክለኛ በላቦራቶሪ አረጋግጠን የነበረው የሦስቱን ብቻ ነው” በማለት አስረድተዋል። አሁን ላይ “በሕክምና መለያ ቦታ ውስጥ ሆኖ በዚህ ቫይረስ ተይዞ ያለሰው የለም” ማለታቸውንም ሰምተናል። በዓለም አቀፍ ደረጃ እስካሁን ለቫይረሱ ይፋ የሆነ መድኃኒት ባይኖርም “በሙከራ ላይ ያሉ እና ሌሎች ሀገራት የሞከሯቸውን [መድኃኒቶች] በእኛ ሀገር ማምጣት የሚቻልበትን ሁኔታ ጀምረናል” ሲሉ የጤና ሚኒስትሯ በሰጡት መግለጫ አብራርተዋል።

አሁን ላይ “በሕክምና መለያ ቦታ ውስጥ ሆኖ በዚህ ቫይረስ ተይዞ ያለሰው የለም” ብለዋል።

የሕክምና ባለሙያዎችን ጨምሮ 6 ሰዎችን የገደለው “ሄሞራጅክ ፌቨር” የተሰኘው በሽታ መንስዔ “ማርበርግ ቫይረስ” እንደሚሰኝ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ ዛሬ ባወጣው መግለጫ፤ ቫይረሱ የታወቀው በላብራቶሪ የዘረመል ምርመራ ተደርጎ መሆኑን ገልጿል።

በምርመራው “በአሁኑ ሰዐት ኢትዮጵያ ውስጥ የተገኘው ቫይረስ ሌሎች ምሥራቅ አፍሪካ ሀገራት ላይ ከዚህ በፊት የተከሰቱት ጋር ተመሳሳይነት ዝርያ ያለው መሆኑ ታውቋል” ብሏል። ሆኖም በዛሬው ዕለት የበሽታውን ምልክት ያሳየ ወይም በቫይረሱ የተጠረጠረ ዐዲስ ሰው እንዳልተገኘ አስታውቋል። ሚኒስቴሩ ከሁለት ቀናት በፊት ኀዳር 3/2018 ዓ.ም. ጉዳዩን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ 8 ሰዎች በበሽታው የተጠረጠሩ መሆናቸውን ገልጾ ነበር።

ይሁን እንጂ በመግለጫው የሰዎች ሕይወት ስለማለፉ አላሳወቀም ነበር። ቢቢሲ ትላንት በሰራው ዘገባ ግን ሁለት የጤና ባለሙያዎችን ጨምሮ ስድስት ሰዎችን መግደሉን ገልጿል። ሚኒስቴሩ በዛሬው መግለጫው በአሁን ሰዓት የተለያየ የሞያ ስብጥር ያካተተ ከፍተኛ ፈጣን መላሽ ሰጪ ቡድን ወደ ክልሉ ተልኮ በሽታውን የመከላከል እና የመቆጣጠር ሥራ እየተሠራ ነው ብሏል። በሽታውን ለመካላከል የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ የዓለም ጤና ድርጅት የ46 ሚሊዮን ብር ገደማ አፋጣኝ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚሰጥ በትላንትናው ዕለት ዐስታውቋል።

ሸቀጣሸቀጥ በሚሸጥባቸው ሱቆች እንጀራ መሸጥ ተከለከለበአዲስ አበባ በሚገኙ የተለያዩ ሸቀጣሸቀጦች በሚሸጡባቸው ሱቆች ውስጥ እንጀራ መሸጥ መከልከሉን የአዲስ አበባ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ...
11/17/2025

ሸቀጣሸቀጥ በሚሸጥባቸው ሱቆች እንጀራ መሸጥ ተከለከለ

በአዲስ አበባ በሚገኙ የተለያዩ ሸቀጣሸቀጦች በሚሸጡባቸው ሱቆች ውስጥ እንጀራ መሸጥ መከልከሉን የአዲስ አበባ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን አስታወቀ። ይህን መመሪያ የተላለፉ ነጋዴዎች ላይ “የእርምት እርምጃ” እንደሚወሰድባቸውም ተቋሙ ገልጿል።

የከተማዋ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ይህን ውሳኔ የወሰነው፤ “የተለያዩ መርዛማ ነገሮች፣ ሳሙና እና ለጤና ጠንቅ የሆኑ ሸቀጦች በሚሸጡባቸው ሱቆች በቀጥታ ለምግብነት የሚውሉትን እንጀራ እና ዳቦ መሸጥ ልክ ባለመሆኑ” እንደሆነ የተቋሙ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ እንጋ እርቀታ ለአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ተናግረዋል።

በዚህ ምክንያት እንጀራ እና ዳቦ መሸጥ ያለባቸው “በምግብ ቤቶች” ፣ “በዳቦ ቤቶች” እና “በባልትና ወይም ለዚሁ መሻጫነት በተፈቀደ ቦታ ብቻ” መሆኑንም አቶ እንጋ አብራርተዋል።

ሆኖም ከተዘረዘሩት የመሸጫ ቦታዎች ውጭ እንጀራ የሚሸጡ ነጋዴዎች ከተገኙ አስፈላጊው “የእርምት እርምጃ” እንደሚወሰድባቸው አስገንዝበዋል። በዚህ ረገድ ኀብረተሰቡ እንጀራ በሱቅ መሸጡ ለጤናው ጠንቅ መሆኑን ተገንዝቦ ተባባሪ እንዲሆንና ጥቆማም እንዲሰጥ ኃላፊው ጠይቀዋል መባሉን ሰምተናል።

ከዘንድሮው ጉማ ሽልማት ምስሎች በጥቂቱ📷 Focus Studio
11/15/2025

ከዘንድሮው ጉማ ሽልማት ምስሎች በጥቂቱ

📷 Focus Studio

Address

4900 Leesburg Pike, Ste 414
Alexandria, VA
22302

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EthioTube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to EthioTube:

Share