EthioTube

EthioTube Current events, breaking news, entertainment, exclusive interviews, variety shows & much more on Ethiopia. Watch All Things Ethiopia.

መንጃ ፈቃድ የታገደበት አሽከርካሪ “የተሐድሶ ሥልጠና” ሳይወስድ ወደሥራ እንዳይመለስ የሚከለክል መመሪያ ተግባራዊ እየተደረገ ነው- አሽከርካሪዎች የተሐድሶ  ሥልጠና ከወሰዱ በኃላ የሚወስዱትን...
08/11/2025

መንጃ ፈቃድ የታገደበት አሽከርካሪ “የተሐድሶ ሥልጠና” ሳይወስድ ወደሥራ እንዳይመለስ የሚከለክል መመሪያ ተግባራዊ እየተደረገ ነው

- አሽከርካሪዎች የተሐድሶ ሥልጠና ከወሰዱ በኃላ የሚወስዱትን ፈተና የማለፍ ግዴታ ተጥሎባቸዋል

ተደጋጋሚ ጥፋት አጥፍተው የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃዳቸው የታገደባቸው አሽከርካሪዎች፤ “ጥፋታቸውን ሊያርም” በሚያስችል መልኩ “እውቀትና ክህሎትን” መሰረት ያደረገ የተሐድሶ ሥልጠና ሳይወስዱ ወደ ሥራቸው እንዳይመለሱ የሚከለክል መመሪያ ተግባራዊ እየተደረግ መሆኑን ኢትዮ ቲዩብ ተረድቷል።

“የአጥፊ አሽከርካሪዎች የተሐድሶ ሥልጠና አሰጣጥ” የተሰኘ መጠሪያ ያለው መመሪያ የወጣበት ዓላማ አሽከርካሪዎች በተደጋጋሚ ከሚፈጽሟቸው ስሕተተቶች እንዲታረሙ ለማስቻል መሆኑ ተመላክቷል። የአሽከርካሪዎችን እውቀት እና ክህሎት በማሳደግ የሚደርሰውን የሞት፣ የአካል ጉዳትና ከፍተኛ የንብረት ውድመትን መቀነስ፤ መመሪያው የወጣበት ሌላኛው ዓላማ ነው።

በተደጋጋሚ ጥፋት ምክንያት መንጃ ፈቃዳቸው በታገደባቸው አሽከርካሪዎች ላይ ተፈጻሚ እየሆነ ነው የተባለው የተሐድሶ ስልጠና፤ አደጋን ተከላክሎ ማሽከርከር፤ የፍጥነት መንገድ አጠቃቀም፣ ሙያዊ ሥነ-ምግባር የተሰኙ ይዘቶች እንዳሉት ኢትዮ ቲዩብ ከሰነዱ ላይ ተመልክቷል። የመንገድ ትራፊክ አደጋ መንስኤዎች እና መከላከያ መንገዶች፣የመጀመሪያ ደረጃ ሕክምና እርዳታ ላይ ሥልጠናው የሚያተኩርባቸው ተጨማሪ ይዘቶች ናቸው።

የተሐድሶ ሥልጠናው ለአንድ ሳምንት በቀን 2 ሰዓታት የሚሰጥ ሲሆን፤ ይህን አጭር ሥልጠና አሽከርካሪዎች በክፍል ውስጥ በመገኘት የመከታተል ግዴታ ተጥሎባቸዋል። የተሐድሶ ሥልጠናው ከተጠናቀቀ በኋላ ደግሞ የሚሰጠውን ፈተና የማለፍ ግዴታ እንዳለባቸው “የአጥፊ አሽከርካሪዎች የተሐድሶ ሥልጠና አሰጣጥ” በተሰኘው መመሪያ ላይ ሰፍሯል።

በፈጸማቸው የማሽከርከር ስሕተት የመንጃ ፈቃዱ የታገደበት ማንኛውም አሽከርካሪ፤ ይህን የተሐድሶ “ስልጠና ሳይወስድ” እና “ሰርተፍኬቱን ሳይዝ” ማሽከርከር እንደማይችልም ተደንግጓል። የተሽከርካሪ ባለቤቶችም፤ መንጃ ፈቃዱ ታግዶበት የተሐድሶ ሥልጠና ያልወሰደ አሽከሪካሪ እንዲያሽከረክር መፍቀድ እንደሌለባቸው በመመሪያው ላይ ተብራርቷል። ሆኖም ይህን መመሪያ ጥሶ ሲያሽከርክር የተገኘ ግለሰብ “ከማንኛዉም የማሽከርከር አገልግሎት” ለ 3 ወራት በድጋሚ እንደሚታገድ ተገልጿል።

በትግራይ ክልል በኮሌራ በሽታ የ 3 ሰዎች ሕይወት አለፈበትግራይ ክልል በሚገኙ ሁለት ወረዳዎች  በተከሰተ የኮሌራ በሽታ የሦስት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ። በበሽታው የ...
08/10/2025

በትግራይ ክልል በኮሌራ በሽታ የ 3 ሰዎች ሕይወት አለፈ

በትግራይ ክልል በሚገኙ ሁለት ወረዳዎች በተከሰተ የኮሌራ በሽታ የሦስት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ። በበሽታው የተያዙ 89 ሰዎች ሕክምና ተደርጎላቸው ማገገማቸውንም ቢሮው ገልጿል።

በሽታው እንደተከሰተ የተረጋገጠው፤ በክልሉ ደቡባዊ እና የደቡብ ምስራቅ ዞን በሚገኙ ሰለዋ እና ሳምራ በተሰኙት ወረዳዎች እንደሆነ ተመላክቷል። በተጠቀሱት ወረዳዎች ከመከሰቱ ሦስት ሳምንት በፊት በአማራ ክልል ዋግኽምራ ዞን በሽታው መታየቱን የትግራይ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር አማኑኤል ኃይለ መናገራቸውን ትግራይ ቴቪ ዘግቧል። በዚህ ሳቢያ ቢሮው በሁለቱ ወረዳዎች “በልዩ ሁኔታ” ክትትል ሲያደርግ እንደደቆየም ኃላፊው አክለዋል።

በክትትሉም በሳምረ ወረዳ 11 ሰዎች፤ በሰለዋ ወረዳ ደግሞ 78 ሰዎች በበሽታው ተይዘው የነበረ ቢሆንም የሕክምና ክትትል ተደርጎላቸው ማገገማቸው ተመላክቷል። በሰለዋ ወረዳ ሁለት ሰዎች ወደ ጤና ተቋም ከመድረሳቸው በፊት ሕይወታቸው ማለፉን አቶ አማኑኤል አስረድተዋል። አንድ ታማሚ ደግሞ በሳምረ ወረዳ በሕክምና ላይ እያለ ሕይወቱ ማለፉን ተናግረዋል።

የክልሉ ጤና ቢሮ የበሽታውን ሥርጭት ለመግታት የጤና ባለሙያዎች ቡድን ወደ ሁለቱም ወረዳዎች በመላክ፤ የኬሚካል ርጭት፣ የመድኃኒት አቅርቦት እና ለማኀበረሰቡ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራዎች መስራቱን ገልጿል።

📢 DMV አከባቢ ለምትገኙ 📢----Join Bethlehem Bekele Belatchew, author of Reflections of Healing and founder of Kinet Bet, tomorr...
08/10/2025

📢 DMV አከባቢ ለምትገኙ 📢
----
Join Bethlehem Bekele Belatchew, author of Reflections of Healing and founder of Kinet Bet, tomorrow at acclaimed filmmaker and storyteller Haile Gerima’s Sankofa Video, Books & Cafe for an intimate conversation on healing, wellness, community, the power of storytelling — and, of course, poetry.

📅 Sunday, August 10, 2025
🕒 3:00 – 5:00 PM
📍 Sankofa Video, Books & Cafe | 2714 Georgia Ave NW, Washington, DC

🎤 RSVP: www.sankofaevents.com

“ታሪካዊ ጠላቶቻችን ለግድያ የሚፈላለጉ ኃይሎችን በጥቅም በማስተሳሰር ኢትዮጵያን ከመንገዷ ለማስቀረት የመጨረሻውን ሙከራ እያደረጉ ነው” ብልፅግና ፓርቲየኢትዮጵያ “ታሪካዊ ጠላቶች” እና “ተላ...
08/08/2025

“ታሪካዊ ጠላቶቻችን ለግድያ የሚፈላለጉ ኃይሎችን በጥቅም በማስተሳሰር ኢትዮጵያን ከመንገዷ ለማስቀረት የመጨረሻውን ሙከራ እያደረጉ ነው” ብልፅግና ፓርቲ

የኢትዮጵያ “ታሪካዊ ጠላቶች” እና “ተላላኪዎቻቸው ለግድያ የሚፈላለጉ ኃይሎችን በጥቅም በማስተሳሰር” ኢትዮጵያን ከመንገዷ ለማስቀረት የመጨረሻውን ሙከራ በማድረግ ላይ እንደሚገኙ ብልጽግና ፓርቲ ገለጸ። ገዢው ፓርቲ ከሐምሌ 30 እስከ ነሐሴ 2 ቀን 2017 ዓ.ም. ያደረገውን መደበኛ ስብሰባ አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ፤ “በቀይ ባሕር የነበረውን ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና ለመመለስ ከአንድ ምዕራፍ በላይ መራመዱን” አስታውቋል።

የብልፅግና ፓርቲ ምክር ቤት ባደረገው ስብሰባ በዓለማቀፋዊ፣ አህጉራዊ፣ ቀጣናዊ እና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በዝርዝር መወያየቱን ገልጿል። በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል የነበረው ጦርነት በፕሪቶሪያ ስምምነት መቋጨቱን ተከትሎ፤ “ጦርነቱ እንዲራዘም የሚገልጉ ጠላቶቻችን” በተለያዩ አካባቢዎች የሚንቀሳቀሱ “ጽንፈኞችን” በመጠቀም የመንግሥትን ኃይልና የሕዝብን አንድነት ለመከፋፈል ጥረት እያደረጉ ነው ሲል ፓርቲው ከስሷል።

ገዢው ፓርቲ ጠላት ያላቸው አካላት “በየአካባቢው ግጭትን በማበራከት”፣ “በዲጂታል ሚዲያ መንግሥትን በማሳጣት” የሕዝብንና የመንግሥትን አንድነት ለመፈታተን ሙከራ ማድረጋቸውን አስታውቋል። ሆኖም “በቀይ ባሕር የነበረውን ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና ለመመለስ ከአንድ ምዕራፍ በላይ መጓዙን እና ዓለም አቀፍ አጀንዳ” ማድረግ መቻሉን” ገልጿል።
ይህ “ተጨባጭ ለውጥ” ለሀገሪቱ “ታሪካዊ ጠላቶች እና እነርሱ ተላላኪዎች የሚዋጥላቸው” ባለመሆኑ “ኢትዮጵያን ከመንገዷ ለማስቀረት የመጨረሻውን ሙከራ” በማድረግ ላይ እንደሚገኙ ዛሬ ባወጣው መግለጫው ላይ ሰፍሯል።
ይህን ሙከራቸውን “ስድስት ስልቶችን ለመጠቀም መነሳታቸውን” ምክር ቤቱ ገምግሚያለሁ ብሏል። ፓርቲው ከዘረዘራቸው “ስልቶች” ውስጥ “ለግድያ የሚፈላለጉ ኃይሎችን በጥቅም ማስተሣሠር” የሚለው ይገኝበታል። “ኢትዮጵያን በሁከት ውስጥ ማቆየት”፤ “በመልካም አስተዳደር ችግር የተነሣ የሚፈጠሩ የሕዝብ ቅሬታዎችን ለዐመጽ መጠቀም” ብልፅግና ፓርቲ የጠቀሳቸው ስልቶች ናቸው።
ከነዚህ በተጨማሪ “ብሶት ቀስቃሽ አጀንዳዎችን ማራገብ”፣ “ሚዲያዎችን የሁከት መቀስቀሻ መሣሪያ ማድረግ” እንዲሁም “በውጭ ምንዛሬ እና በሸቀጦች በኩል የኢኮኖሚ አሻጥርን መሥራት” የሚሉ መሆናቸውን ጠቁሟል። ገዢው ፓርቲ እነዚህን ሙከራዎች ለማምክን፤ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ለሚወስኑ ታጣቂዎች “አስፈላጊውን ሁሉ” እንደሚያደርግ አስታውቋል። ይህን አማራጭ ባልተቀበሉ ኃይሎች ላይ ግን “በተጠናከረ መንገድ ሕግ ለማስከበር እርምጃ እንደሚወስድ” ገልጿል።

ፍላይ አዲስ ትራቭል ሶሉሽን ጋዜጠኛና ፕሮሞተር አብርሃም ግዛውን የድርጅቱ ብራንድ አምባሳደር አድረጎ ለአንድ ዓመት በአንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ ብር (1,500.000.00 )ብር ሾመ።  ...
08/08/2025

ፍላይ አዲስ ትራቭል ሶሉሽን ጋዜጠኛና ፕሮሞተር አብርሃም ግዛውን የድርጅቱ ብራንድ አምባሳደር አድረጎ ለአንድ ዓመት በአንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ ብር (1,500.000.00 )ብር ሾመ።
***
ፍላይ አዲስ ትራቭል ሶሉሽን ባለፉት አራት ዓመታት አውሮፓ ፖላንድ ቱርክ ጣሊያን ካናዳ ሩሲያ እና ሌሌሎች በርካታ የአለም ሀገራት ለትምህርት ለስራና ለህክምና እንዲሁም ለጎብኝት ጉዞ ለሚያደርጉ ዜጎች የጉዞ እና አጠቃላይ ሂደቱችን የማማከር አግልግሎቶችን በመስጠት ታዋቂና ተመራጭ ለመሆን የቻለ ድርጅት ሲሆን ይህንኑ ስራውን ይበልጥ ወደ ህብረተሰቡ እንዲደርስ እና እንዲተዋወቅ ለማድረግ በተለያዩ የጋዜጠኝነት ወይም የሚዲያ ሥራዎች የፕሮሞሽን የተለያዩ ሁነቶች (ኢቨንቶችን)በማዘጋጀት በማስተባበርና በመምራት የሚታወቀውን ጋዜጠኛና ፕሮሞተር አብርሃም ግዛውን የድርጅቱ ብራንድ አምባሳደር አድረጎ በዛሬው ዕለት ቦሌ በሚገኘው ጎልደን ቱሊፕ ኢንተርናሽናል ሆቴል ተፈራርመዋል ።
በዚህ የፊርማ ስነ-ሥርዓት በርካታ የክብር እንግዶች የተገኙ ሲሆን ይህ የብራንድ አምባሳደር ስምምነት ለቀጣይ ሁለት አመታት ድርጅቱን ለማስተዋወቅ የተደረገ ስምምነት እንደሆን በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ወቅት ተገልጿል ።
#ማስታወቂያ

ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በትግራይ ክልል ባካሔደው ውይይት “የፕሪቶሪያው ስምምነት ተግባራዊ ይሁን” የሚለው ጉዳይ “እንደቅድመ ሁኔታ አለመቅረቡን” አስታወቀ።የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽ...
08/08/2025

ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በትግራይ ክልል ባካሔደው ውይይት “የፕሪቶሪያው ስምምነት ተግባራዊ ይሁን” የሚለው ጉዳይ “እንደቅድመ ሁኔታ አለመቅረቡን” አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በትግራይ ክልል ባካሔደው ውይይት፤ “የፕሪቶሪያው ስምምነት ተግባራዊ ይሁን”፣ “ሕገ መንግሥታዊ ስርዓቱ ይመለስ” እና “የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ መኖሪያ አካባቢያቸው ይመለሱ” የሚሉ ጉዳዮች ምክክሩን ለማካሔድ “እንደቅድመ ሁኔታ አለመቅረባቸውን” አስታወቀ።

ኮሚሽኑ ይህንን የተናገረው ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ ዛሬ ነሐሴ 02/2017 ዓ.ም. በሰጠው ማብራሪያ ላይ ነው። ማብራሪያውን ለጋዜጠኞች የሰጡት የኮሚሽኑ ቃል አቀባይ አቶ ጥበቡ ታደሰ፤ በትግራይ ክልል የምክክር ሒደቱን ለማስጀመር ተደርገዋል ስላሉት “ውጤታማ” ውይይት ሰፋ ያለ ገለጻ አድርገዋል።

በተለያዩ የፖለቲካ እና የሃሳብ መሪዎች እንዲሁም የህብረተሰብ ክፍሎች መካከል ሀገራዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ያሉትን ልዩነቶች በመለየት የምክክር አጀንዳዎችን የመቅረጽ፣ የማመቻችት ኃላፊነት በአዋጅ የተሰጠው የምክክር ኮሚሽን፤ ከአራት ዓመት በፊት የተቋቋመ ቢሆንም በትግራይ ክልል “ለመጀመሪያ ጊዜ” ተገኝቶ ይውውት ያደረገው ከሁለት ሳምንት በፊት ሐምሌ 22/2017 ዓ.ም. ነው።

ከዋና ኮሚሽነሩ ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ፤ ጋር ወደ ክልሉ ያቀናው የልኡካን ቡድን ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደርና ካቢኔያቸው ጋር ውይይት እንዳደረገ በዛሬው መግለጫ ተነስቷል። የኮሚሽኑ የልኡካን ቡድን ከህውሓት ከፍተኛ አመራሮች የፖለቲካ ፓርቲዎች፣የሲቪክ ማኀበራት እና ከትግራይ ፐብሊክ ዲፕሎማሲ አባላት ጋር ተመሳሳይ ውይይት ማድረጉንም አቶ ጥበቡ ተናግረዋል።

በውይይቱ ተሳትፈዋል የተባሉት ባለድርሻ አካላት ምክክሩን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ፤ “የፕሪቶሪያ ስምምነት ተግባራዊ እንዲሆን”፣ “የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ መኖሪያ አካባቢያቸው እንዲመለሱ” ለኮሚሽኑ ማስረዳታቸውን ቃልአቀባዩ አንስተዋል።
አቶ ጥበቡ አክለውም “ከፌደራል መንግሥቱ ጋር ውይይት ተካሔዶ ትግራይ ወደነበረችበት ሕገመንግሥታዊ ሥርዓት እንድትመለስ” እና “እያንዣበቡ ያሉ የጦርነት ስጋቶች እንዲቆሙ መደረግ አለባቸው” ሲሉ ውይይቱን አድርገዋል የተባሉት ባለድርሻ አካላት ለኮሚሽኑ መናገራቸውን አስረድተዋል። ሆኖም እነዚህ ጥያቄዎች ምክክሩን ለማድረግ “እንደቅድመሁኔታ አይደለም የተቀመጡት” ሲሉ ቃላቀባዩ በማብራሪያቸው ጠቁመዋል።
“ምክክር ምንም ዓይነት ቅድመ ሁኔታ የለውም ለመነጋገር ለመመካከር በጋራ ቁጭ ብሎ ተነጋግሮ አሉ የሚባሉ ችግሮችን ለመፍታት ቅድመሁኔታ አስያስፈልገውም” በማለት አብራርተዋል።
“ከዚህ አኳያ በትግራይ የተደረጉ ውይይቶችም እነዚህ ጉዳዮች ካልተፈጸሙ ምክክሩ አይካሔድም፣ወደ ምክክር አንገባም በሚል መንፈስ አይደለም የቀረቡት” ሲሉ አስረድተዋል። ቀርበዋል የተባሉት ጉዳዮች ቢስተካከሉ “[ምክክሩ] የበለጠ አካታች፣ አሳታፊ የሆነ እና ባጠረ ጊዜ ሁሉንም የክልሉን አካባቢዎች በሸፈነ ሁኔታ ለማካሔድ የራሱ ጥቅም አለው” በሚል የተነሱ መሆናቸውን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።
በክልሉ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ተጨማሪ ውይይቶች እንደሚደረጉ የጠቆሙት አቶ ጥበቡ፤ በቀጣይ ተሳታፊ ልየታ እና የአጀንዳ ማሰባሰቡ ስራ እንደሚካሔድ ተናግረዋል። ከነዚህ ተግባራት በፊት ግን ቅድሚያ መሰጠት ያለበት “መተማመኑን መፍጠር”፣ “ የምክክሩን አስፈለጊነት እና ፋይዳ ሕዝቡ ሆነ ሌሎች ባለድርሻ አካላት በቅጡ እንዲረዱት እና በንቃት እንዲሳተፉ የማድረግ ሥራዎች” ናቸው ብለዋል።

ዘሪቱ ከበደ "ከልጅነት እስከ ልጁነት" የተሰኘ አዲስ ግለታሪክ መጽሐፏ በቅርብ ቀን እንደሚወጣ ይፋ አደረገች።
08/08/2025

ዘሪቱ ከበደ "ከልጅነት እስከ ልጁነት" የተሰኘ አዲስ ግለታሪክ መጽሐፏ በቅርብ ቀን እንደሚወጣ ይፋ አደረገች።

ምን እየተባባሉ ይመስላችኋል?
08/07/2025

ምን እየተባባሉ ይመስላችኋል?

የብሔራዊ ባንክ ገዥ በትይዩ የውጪ ምንዛሪ ገበያ የሚንቀሳቀስ ገንዘብ እንደሚወረስ አስጠነቀቁየኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከአሜሪካ እና ከዱባይ የሚዘወሩትን ጨምሮ በውጪ ምንዛሪ ትይዩ ገበያ ላይ ...
08/07/2025

የብሔራዊ ባንክ ገዥ በትይዩ የውጪ ምንዛሪ ገበያ የሚንቀሳቀስ ገንዘብ እንደሚወረስ አስጠነቀቁ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከአሜሪካ እና ከዱባይ የሚዘወሩትን ጨምሮ በውጪ ምንዛሪ ትይዩ ገበያ ላይ ዘመቻ ጀምሯል። ባንኩ ከፍተኛ ልዩነት የሚታይባቸው ይፋዊ እና ትይዩ ተመኖች ተዋህደው ወጥ የውጪ ምንዛሪ ገበያ እንዲፈጠር ይፈልጋል። ነጋዴዎችን ጨምሮ ኢ-መደበኛውን ገበያ ለሚጠቀሙ ገንዘባቸው ሊወረስ እንደሚችል የብሔራዊ ባንክ ገዥ አስጠንቅቀዋል። ዘገባው የጀርመን ድምጽ ነው።

08/03/2025
08/03/2025
ጀኔራል ጻድቃን "የትግራይ የለውጥ ንቅናቄ"  መመስረታቸው ተሰማ• የሕወሓት የበላይነት እንዲያከትም የሚታገል ነው ተብሏልየቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት ጀኔራል ጻድቃ...
08/02/2025

ጀኔራል ጻድቃን "የትግራይ የለውጥ ንቅናቄ" መመስረታቸው ተሰማ

• የሕወሓት የበላይነት እንዲያከትም የሚታገል ነው ተብሏል

የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት ጀኔራል ጻድቃን ገ/ተንሳይ፣ እሳቸውና ጀኔራል ተክላይ አሸብር ከስምረት ፓርቲ፣ ከትግራይ ነጻነት ፓርቲ፣ ከባይቶና እና ከአረና ፓርቲ ጋር የሕወሓትን የበላይነት ለማስወገድ "የትግራይ የለውጥ ንቅናቄ" የተሠኘ ስብስብ መመስረታቸውን እንደገለጡ የትግራይ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።

የንቅናቄው ዓላማ "በሕዝባዊ እምቢተኝነት" በትግራይ የሕወሓት የበላይነት እንዲያከትም መታገል እንደኾነ ጀኔራል ጻድቃን የትግራይ ብሮድካስቲንግ አገልግሎት ከተሰኘ የበይነ መረብ ጣቢያ ጋር ባደረጉት ቆይታ ተናግረዋል ተብሏል።

ጀኔራል ጻድቃን፣ የትግራይ ሕዝብና የክልሉ ጸጥታ ኃይል፣ የሕወሓትን የበላይነት በእምቢተኝነት እንዲታገሉትም ጥሪ ማድረጋቸውን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል።

(ምንጭ፡ አዲስ አድማስ)

Address

4900 Leesburg Pike, Ste 414
Alexandria, VA
22302

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EthioTube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to EthioTube:

Share