10/18/2025
የ30 ዓመቱ ወጣት ስምኦን ጌታቸው በተተኮሱበት ጥይቶች ተገደለ።
ስምዖን ጌታቸው እሁድ October 12, 2025, በ10:40 PM አካባቢ, በ3800 9 Street, Southeast, ዋሽንግተን ዲሲ በነበረበት ጊዜ በተደጋጋሚ በተተኮሱበት ጥይቶች መገደሉን ፖሊስ አስታውቆአል። የስምዖን ጌታቸውን ግድያ በተመለከተ ገዳይን ለፍርድ የሚያቀርብ መረጃ ላቀረበም እስከ ሃያ አምስት ሺ ዶላር ($25,000) ሽልማት እንደሚሰጥ ፖሊስ አስታውቆአል።
የስምዖን ጌታቸው የፍትሃት ስነ ሥርዓት ሰኞ (Monday, October 20, 2025, 10:00 AM) ዋሽንግተን ዲሲ 1350 Buchanan St, NW, በሚገኘው በደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን የሚከናወን ሲሆን፣ ፍትሃቱም ካለቀ በኋላ የቀብሩ ሥነ ስርዓት በ1:30 PM በNorbeck Memorial Park, 16225 Bachellors Forest Road, Olney. MD 20832 ይፈጸማል::
ለስምዖን ጌታቸው የቀብር ማስፈጸሚያ ይረዳ ዘንድ ቤተሰቦቹ የGofundme አካውንት ከፍተዋል...
https://www.gofundme.com/f/help-lay-simon-getachew-to-rest
እግዚአብሔር የስምዖን ጌታቸውን ነፍስ ይማርልን፣ በገነትም ያኑርልን። ለቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ ጽናቱን ይስጥልን።