Faf Media-ፋፍ ሚዲያ

Faf Media-ፋፍ ሚዲያ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Faf Media-ፋፍ ሚዲያ, Media/News Company, American Fork, UT.
(1)

የፋፍ ሚዲያ ቤተሰብ ስለሆኑ እናመሰግናለን!! ፋፍ ሚዲያን ሲከተሉ ይማራሉ፣ ይዝናናሉ፣ ቁምነገር ይጨብጣሉ፣ አዳዲስና ፈጣን መረጃ በፍጥነት ይደርሶታል፣ የማህበረሰብ እንቅፋት ሆነው ከርሳቸውን የሚሞሉ አካላት ይጋለጣሉ ብቻ ፋፍ የዕርሶ ደፋር አንደበት ነው። ፋፍ ዬትኛውንም ግለሰብና ቡድን የግል ፍላጎትን አያንፀባርቅም‼️

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በስልጤ ዞን ሁልባራግ ወረዳ ወራበት ሻማ ቀበሌ በገጠር ኮሪደር ኢንሼቲቭ ያስገነቡትን ሞዴል የገጠር መንደር አስመርቀዋል። በምረቃ መር...
10/10/2025

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በስልጤ ዞን ሁልባራግ ወረዳ ወራበት ሻማ ቀበሌ በገጠር ኮሪደር ኢንሼቲቭ ያስገነቡትን ሞዴል የገጠር መንደር አስመርቀዋል።

በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር እንደሻው ጣሰው (ዶ/ር)፣ የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራል፣ የክልልና የዞን የስራ ሀላፊዎች እንዲሁም የማህበረሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።

"ለሚገባቹ በምሳሌ ላስረዳቹ! እንበልና አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የኢ/ያ መንግስትን ወክሎ  የሰላም ድርድር  ለመፈራረም ፕሪቶርያ በነበረበት ወቅት፤ ከሌሎች ዲፕሎማቶች ሲወያይ ተወካይነቱን ሲ...
10/10/2025

"ለሚገባቹ በምሳሌ ላስረዳቹ! እንበልና አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የኢ/ያ መንግስትን ወክሎ የሰላም ድርድር ለመፈራረም ፕሪቶርያ በነበረበት ወቅት፤ ከሌሎች ዲፕሎማቶች ሲወያይ ተወካይነቱን ሲጠራጠሩ ተመለከተ'ና..

"ልባቹ አይታወክ! እኔ ትክክለኛ መንገድና እውነተኛ ለፕሪቶርያ ድርድር የተላኩ አምባሳደር ነኝ፤ ከእኔ በቀር ወደ አብይ የሚመጣ (የሚደርስ) የለም።" አላቸው -በዛ ሰዓትና ቦታ(በፕሪቶርያ) ለድርድሩ ለተሰበሰቡት።

ከዲፕሎማቶቹ አንዱም "ራሱ አብይ አሳየንና(አገናኘንና) ይበቃናል!" አለው።

አምባሳደሩም "ይህን ያህል ጊዜ ከናንተ ጋር ስቀመጥ አታውቀኝምን?.. እኔን ያየ አብይን አይቷል -እንዴትስ አብይ ካላየሁ ትላለህ?.. እኔ የምነግራቹሁን ቃል ከራሴ አልናገረውም፤ ነገር ግን የላከኝን መንግስት(አብይ) ስራውን ይሰራል። " በማለት መለሰለት።

ይህ ሲል አምባሳደሩ አምሳደርነቱ ወይም መልእክተኛነቱ እያስረዳቸው ነበር -በዲፕሎማሲ ቋንቋ። ..እንጂ በመልክና በተልእኮ በምስልና በስልጣን..etc፤ ስለሚሳሰሉም አንድ ስለሆኑም ፈጽሞ አይደለም -የሕገ መንግስቱ 10ት ትእዛዛት የመጀመርያውን 'የትኛውም ቅርጽና ምስል ለኔ አታድርግብኝ!' ይላልና። እሱ ብቻ ተነጥሎ አንባሳደር ስለሆነ፤ አልያም ብዙ ጠቅላይ ሚኒስትሮች ስላሉም አይደለም። ይልቅስ አምባሳደሩ የላከውን መንግስት ተልእኮውን እየተወጣ ብቻ እንደሆነ ያመለክታል።

በመጨሰሻም አምበሳደሩ "እኔ ብሄድ ይሻላቹሃል! ሌላ ዓለም የሚያየውና የሚያውቀው(ለዓለም የተላከ) አጽናኝ አምበሳደር(ነብዩ ሙሓመድ) ይመጣቹኃል።" በማለት ትምቢቱን ተናግሮ ጉዞውን ቀጠለ።"

10/09/2025

ፋኖ የሚባለው ቡድን የትግል መነሻዎች

➨1. ወልቃይትና ራያ ለአማራ ይመለሱ
አሁን ላይ ግን በአማራ ክልል አስተዳደር የሚገኙ ቢሆንም እነዚህን ግዛቶች ነጥቆ ለህወሃት ለመስጠት ከህወሃት ጋር አብሮ እየታገለ ይገኛል።

➨2.ወለጋ ላይ ንፁሃን አማራዎች ላይ የዘር ማጥፋት ወንጀል ስለተፈፀመ በጥቃት ፈፃሚዎች ላይ የበቀል እርምጃ ለመውሰድ
ነገር ግን እርምጃ እየወሰዱ ያሉት በገዛ ወገናቸው፣ በራሳቸው ክልል ውስጥ ንፁሃን ዜጎች ላይ ነው።

➨3. መንግስት ከህወሃት ጋር ያደረገው ድርድር እኛን ያላካተተ እና በአማራ እጣ ፈንታ ላይ የተደረገ ቁማር ነው፣ ይህንን ቁማር እና አደጋ ለማስቀረት
ነገር ግን በአሁኑ ሰአት ከህወሃት እና ከሻእቢያ ጋር ቅንጅት ፈጥረው እየተዋጉና ሌላ ቁማር እየቆመሩ ይገኛሉ።

➨4. አማራ ሀገሪቱ ውስጥ በየቦታው ያለስጋትና ያለገደብ የመንቀሳቀስ መብቱን ለማስከበር
ነገር ግን የክልሉ ህዝብ በራሱ ቀዬ እንኳን ከቦታ ቦታ እንዳይንቀሳቀስ ኬላ ዘርግቶ የፈለገውን እያገተ ረብጣ ገንዘብ የሚቀበል የፈለገውን ደግሞ እየገደለ የሚፎክር የሽፍታ ቡድን ሆኗል።

➨5.የአማራ ክልል የመንግስት የፀጥታ ኃይሎች በተለይ ልዩ ኃይል መበተን የለበትም።
ነገር ግን ከክልሉ ልዩ ኃይልየተመለሱ አድማ ብተና አባላት፣ የክልሉ ፖሊስ እና ሚሊሻዎች ባጠቃላይ ክልሉን ለጊዜውም ቢሆን ፈጣን ምላሽ(emergency responce) በመስጠት ከህልውና አደጋ የሚከላከሉ የፀጥታ ኃይሎች ልክ እንደውጭ ጠላት ተቆጥረው በፋኖ ይገደላሉ።

ሁሉም የፋኖ ፍላጎቶች ተቃርኗዊ ናቸው ።
ከዚህ ይልቅ ፋኖ የተደራጀበትና የሚዋጋበት ድብቅ አላማ እና አጀንዳ አለው ብንል አሳማኝ ይሆናል። አሁን አሁን ግን ያንን ድብቅ አጀንዳቸውን ይፋ እያወጡት ይገኛሉ።

#አሊ ወሎ

ጌስ እመጫን ባሊ..ፈየኮ ዉጦ ተቂበሉይ🥰
10/08/2025

ጌስ እመጫን ባሊ..ፈየኮ ዉጦ ተቂበሉይ🥰

የአመራሩ ዲሲፒሊን በጥልቅ ሊፈተሽ ይገባል!!ከባህል እና እምነት ያፈነገጡ ጋጠ ወጥ አመራሮች የህዝቡን እሴት አፍራሽ እንደመሆናቻው የማያወላዳ ቀይ ካርድ ያሻቸዋል!! ያሳፍራል!! ለአሁን ዝር...
10/06/2025

የአመራሩ ዲሲፒሊን በጥልቅ ሊፈተሽ ይገባል!!
ከባህል እና እምነት ያፈነገጡ ጋጠ ወጥ አመራሮች የህዝቡን እሴት አፍራሽ እንደመሆናቻው የማያወላዳ ቀይ ካርድ ያሻቸዋል!! ያሳፍራል!! ለአሁን ዝርዝሩን ትተነዋል!!

የወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውጤታማ እንቅስቃሴዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አስፈላጊው እገዛ ይደረጋል አሉ ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ!የወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ...
10/06/2025

የወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውጤታማ እንቅስቃሴዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አስፈላጊው እገዛ ይደረጋል አሉ ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ!

የወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በሁለንተናዊ የጤናና የህክምና አገልግሎት እያደረጋቸው ያሉ ውጤታማ እንቅስቃሴዎች ይበልጥ እንዲጎለብቱ አስፈላጊው ድጋፍ ይደረጋል ሲሉ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታ ክብርት ወ/ሮ ሳህረላ አብዱላሂ ገለጹ።

ሚኒስትር ድኤታዋ የሆስፒታሉን አጠቃላይ የስራ እንቅስቃሴዎች በመጎብኘት የሆስፒታሉን አጠቃላይ አገልግሎት ወደ ላቀ ደረጃ ማድረስ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር አድርገዋል።

ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ በውይይቱ ማጠቃለያ ባስተላፉት መልዕክት ወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይድ ሆስፒታል እያስመዘገበ ባለው አጠቃላይ የለውጥ ሂደትና በሚሰጣቸው ሁሉአቀፍ አገልግሎቶች መደሰታቸውን ገልጸዋል።

ሆስፒታሉ በራስ አቅም እና ተነሳሽነት ዘርፈ ብዙ ፕሮግራሞችን እየተገበረ መሆኑን ያነሱት ወይዘሮ ሳህረላ ሂደቱ ፍጥነትና ፈጠራ ከሚለው የመንግስት ኢንሼቲቭ የሚጣጣም መልካም ተግባር መሆኑን ተናግረዋል።

ባለፉት ዓመታት በሆስፒታሉ የነበሩ በርካታ የውስጥ ጉድለቶችን በራስ አቅም የፈታበት መንገድ ለብዙዎች ምሳሌ የሚሆን ትልቅ ውጤት መሆኑን ሚኒስትር ድኤታዋ ገልጸዋል።

በህክምና መሳሪያዎች አያያዝ፣ በፋይናንስ አጠቃቀም፣ በዲጂታላይዜሽን፣ ንጹህ ከባቢ በመፍጠር፣ በሰው ሀይልና ተቋማዊ አደረጃጀት፣ በማህረሰብ ንቅናቄና ተሳትፎ፣ በፕሮጀክቶች አፈጻጸም፣ በአዳዲስ አገልግሎቶች እንዲሁም በሌሎች ቅንጅታዊ ስራዎችና ሁለንተናዊ የለውጥ ሂደት ሆስፒታሉ ለተሞክሮ የሚበቁ ውጤቶች ማስመዝገቡን ወ/ሮ ሳህረላ መስክረዋል።

እነዚህ ሁላቀፍ ውጤቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ያሳሰቡት ሚኒስትር ድኤታዋ ሆስፒታሉን የልህቀት ማዕከል በማድረግ ሂደት ሚኒስትር መስሪያቤቱ ሚናውን ይወጣል ብለዋል።

የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ ወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በአስር አመታት እድሜው ተወዳዳሪ የሆነ አገልግሎት ማቅረብ መቻሉን አስታውሰዋል።

ሆስፒታሉ በመጣበት ስኬታማ መንገድ ወደ ተሻለ ከፍታ ለመድረስ በሚያደርገው ጉዞ ውስጥ የዞኑ መንግስትና የስራ አመራር ቦርዱ የሚጠበቅበትን እንደሚወጣ አቶ ዘይኔ ተናግረዋል።

የዞኑ ህዝብ የጤናውን ዘርፍ ለማገዝ ካለው ቁርጠኝነት መነሻ በ2017 ብቻ ከ3 መቶ 50 ሚሊየን ብር በላይ በማህበረሰብ ተሳትፎ ለጤና ልማት ስራ መዋሉን አቶ ዘይኔ አስታውቀዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ሀላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ ወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በክልል ደረጃ የጤና አገልግሎት ማሰላጫና የተሞክሮ ማዕከል መሆኑን ገልጸዋል።

በክልል ደረጃ የሆስፒታሉን ጉድለቶች በመፍታትና ውጤታማ ተሞክሮዎቹን ወደ ሁሉም ተቋማት በማስፋት ለተሻለ ውጤት እንደሚሰራ አቶ ሳሙኤል አንስተዋል።

የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ካሊድ ሸረፋ ሆስፒታሉ ያለፉትን ዓመታት ውጤቶች በመገምገምና ጉድለቶችን በመለየት በሚቀጥሉት ጥቂት ዓመታት የምስራቅ አፍሪካ የጤናው ዘርፍ የልህቀት ማዕከል ለመሆን በትጋት እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

የተያዙ ግቦች እንዲሳኩ የጤና ዘርፍ ባለድርሻ አካላትና አጠቃላዩ ማህበረሰብ እገዛና ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥል ዶ/ር ኻሊድ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ብሶት የወለደው ሻይድ መጽሐፍ ሊመረቅ መቃረቡን  ስንነግራችሁ በታላቅ ደስታ ነው!!!
10/05/2025

ብሶት የወለደው ሻይድ መጽሐፍ ሊመረቅ መቃረቡን ስንነግራችሁ በታላቅ ደስታ ነው!!!

ኢናሊላሂ ወኢና ኢለሂ ረጂኡን!እኛ የአላህ ነን ወደ እሱም ተመላሾች! ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ!በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን መካነ ሰላም ከተማ ...
10/04/2025

ኢናሊላሂ ወኢና ኢለሂ ረጂኡን!
እኛ የአላህ ነን ወደ እሱም ተመላሾች!

ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ!

በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን መካነ ሰላም ከተማ መስከረም 23፣2018 ዓ.ል በመስጂድ ኑር በኢሻ ሰላት ወቅት ወደ መስጂድ የታጠቁ ኃይሎች በመግባት ሃይማኖታዊ ግዴታቸውን በመወጣት ላይ በነበሩ ፦
1 የመስጂድ ዋና ኢማምና የወረዳው መጅሊስ ም/ሰብሳቢ
2 የመስጂድ አመራሮች
3 የመስጂድ ኻዲሞችን አሰቃቂ እና አረመኔያዊ በሆነ ሁኔታ መግደላቸውን የክልሉ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት አረጋግጦልናል።

እነሱም ሸሂድ ሆነዋል አላህ ጀነተል ፍርዶስ ይወፍቃቸው ።

ጠቅላይ ምክርቤቱ የእምነት ተቋማት የተከበሩ ቦታዎች በመሆናቸው ሊጠበቁ እንጅ እንዲህ አይነት አፀያፊ ተግባር የሚፈፀምባቸው መሆን የለባቸውምና ድርጊቱን በፅኑ ያወግዛል።

መላው የሃይማኖት ተቋማትም በእምነት ቦታዎች የሚደረጉ ትንኮሳዎች እና በእምነት ተከታዮች ላይ የተቃጣ መሰል የጅምላ ግድያ
ሊያወግዙና ሊያስቆሙ ይገባል።

ህዝበ ሙስሊሙ ይህንን በሀይማኖት ተቋማት ላይ የተቃጣ አደጋ ለመከላከል መረጃ በመለዋወጥ የሃይማኖት ተቋማትንና አካባቢውን እንዲጠብቅ ጠቅላይ ምክርቤቱ ጥሪውን ያስተላልፋል።

ብዝሃ ሀይማኖት ባለባት ሀገራችን በተለያየ እምነት ውስጥ ያሉ ህዝቦች ለዘመናት ያቆዩተን ሰላማዊ እና መልካም መስተጋብር ሆን ተብሎ ለመናድና ማባሪያ ያጣ ቀውስ ውስጥ እንድንገባ የሚፈልጉ አካላት የፈፀሙት መሆኑን ጠቅላይ ምክርቤቱ ይገነዘባል።

በመጨረሻም ሁሉም ሃይማኖት ተቋማትና መሪዎች ይህ ጉዳይ አብሮ የመኖር እሴት እንዳይሸረሽር ብሎም እንዳያጠፋ ድርጊቱን እንድታወግዙ እንዲሁም በፅኑ እንድትቃወሙ እየጠየቅን መንግስትም ይህንን ተግባር በእምነት ቦታዎችና አባቶች ላይ የፈፀሙት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንዲወስድ እንጠይቃለን።

መስከረም 24፣2018 ዓ.ል
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርቤት

10/04/2025

መካነሰላም

10/04/2025

#ኢሬቻ

10/04/2025

የመካነ ሰላም ህዝበ ሙስሊም በነቂስ በመውጣት በግፍ የተገደሉ መሪዎቹን የጀናዛ ሽኝት እያደረገ ይገኛል። አሏህ ለሟቾች የሸሂድነት ማዕረግ ያጎናፅፋቸው። አሚን

Address

American Fork, UT

Telephone

+97433401028

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Faf Media-ፋፍ ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share