Faf Media-ፋፍ ሚዲያ

Faf Media-ፋፍ ሚዲያ የፋፍ ሚዲያ ቤተሰብ ስለሆኑ እናመሰግናለን!! Follow Faf Media and see the world through a lens of truth.!
(1)

ይሄንን ሿሿ መጽሐፍ አንብቡት!!!ለጥያቄዎቻችን መልስና ማብራሪያ ከሰጡን የአካባቢው ታዋቂ ሽማግሌዎችና የሃይማኖት መሪዎች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል? ተብሎ ስም ዝርዝራቸው የተጠቀሱ እነዚ...
07/24/2025

ይሄንን ሿሿ መጽሐፍ አንብቡት!!!

ለጥያቄዎቻችን መልስና ማብራሪያ ከሰጡን የአካባቢው ታዋቂ ሽማግሌዎችና የሃይማኖት መሪዎች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል?

ተብሎ ስም ዝርዝራቸው የተጠቀሱ
እነዚህን ሽማግሌዎችና የሃይማኖት መሪዎች
የት የት አካባቢ ሽማግሌዎችና የሃይማኖት መሪዎች
እንደሆኑ በቀስት ያደረግነባቸው ስሞችን ተመልከቱ!?
እንግዲህ እነዚህ የአካባቢው ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባት ሳይሆኑ ናቸው ተብሎ
የአዘርነት አካባቢ ሽማግሌና የሐይማኖት አባቶች ስልጤ ራሱን የቻለ ብሄር ሳይሆን ጉራጌ ነው
ብለው ምስክርነታቸውን ሰጡ ተብሎ የተፃፈ መጽሃፍ ነው።
እንዴት አይነት ሸዋ ሸዋ ሊሰሩት እንደነበረ እዩ?

ከዚህ ሿሿ ላወጡን ጀግኖች በህይወት ላሉ አባቶቻችን ረጅም እድሜ 🤲🏻
በህይወት ለሌሉት ደግሞ አላህ ጀነት ፍርዶሱን የወፍቃቸው 🤲🏻
በምን ሂሳብ ነው አንድ የውልቅጤ አካባቢ ሽማግሌ ለአዘርነት ወይም ለስልጤ ህዝብ መልስ ሰጪ የሚሆነው ?

በምን ሂሳብ ነው አንድ የጉመር አካባቢ ሽማግሌ ለአዘርነት ወይም ለስልጤ ህዝብ መልስ ሰጪ የሚሆነው ?

የኛ ቤት የፌስቡክ ነዋሪዎች የስልጤን ህዝብ እኔ ነኝ የምመራው የምትሉ የፌስቡክ አርበኞች ይሄንን መጽሐፍ አይታችሁት ይሁን? ይህንን መጽሐፍ ግዜ አግኝታችሁ አንብባችሁት ይሁን?ለማህበረሰባቹ ...
07/24/2025

የኛ ቤት የፌስቡክ ነዋሪዎች
የስልጤን ህዝብ እኔ ነኝ የምመራው የምትሉ
የፌስቡክ አርበኞች
ይሄንን መጽሐፍ አይታችሁት ይሁን?
ይህንን መጽሐፍ ግዜ አግኝታችሁ አንብባችሁት ይሁን?
ለማህበረሰባቹ ተቆርቋሪነታችሁን መጽሐፉን አንብባችሁ ምላሽ ሰጥታችሁ ይሁን?

07/23/2025
ተንኮሉ ሸይጣን ይቀናበታል። ሸይጣን ተጨማሪ የተንኮል ዕውቀት ቢሻ እርሱ ጋር ተጠግቶ የሚማር ይመስለናል። ክፋቱ አቻ አይገኝለትም። ቢችል ሁሉንም አጥፍቶ ብቻውን ቢቀር ደስተኛ ነው። ከዛሬ 4...
07/22/2025

ተንኮሉ ሸይጣን ይቀናበታል። ሸይጣን ተጨማሪ የተንኮል ዕውቀት ቢሻ እርሱ ጋር ተጠግቶ የሚማር ይመስለናል። ክፋቱ አቻ አይገኝለትም። ቢችል ሁሉንም አጥፍቶ ብቻውን ቢቀር ደስተኛ ነው። ከዛሬ 48 ሳምንታት በፊት ጥምብ እርኩሱን አውጥቶ ያጠለሸውን ታታሪ የካሜራና የሚዲያ ባለሙያ ለጥቅም ጊዜ አይኑን በጨው አሽቶ ሲያንቆለጳጵሰው ተመለከትን። በተገላቢጦሽ ፎቶዬ ከፊት አልተገናኘም በሚል ብቻ ስለ ሚዲያ ሕግ መጣስ እና የመንግስት ሚስጥር መበተን ንዝነዛ ከጀመረ ሁለተኛ ቀኑ ሞላ።

በቃ ጉዱን በደንብ ቢያይ.. Even the devil will paused and said, 'Damn, I thought I was the master of trickery!'"😎

አጅሬው ራሱን እንደ ነብይ ስልጤው ሙሴ ነኝ ለማለትም ይቃጣዋል። አንዴ የአለም አቀፉ የስልጤ ማህበረሰብ የበጎ አድራጎት ማህበር ሰብሳቢ፣ በሌላ ጊዜ የስልጤ የዩንቨርሲቲ ተማሪዎች ሰብሳቢ፣ ሲያሻውም ብቸኛ የስልጤ ህዝብ ተወካይ ተቆርቋሪ አድርጎም ይከሰታል። ወዲህ የስልጤ ሙህራን ምልክት አድርጎም ራሱን ይስላል። እንደ ስልጤ ማህበረሰብ ቻይነት ሆኖ ላይለያይ የተጋመደ በኢስላም ገመድ የተሳሰረ ሆኖበት ተፈተነ እንጂ ሊከፋፍለው ሊበታትነው በዛች ሚጢጢዬ አቅሙ ያልፈነቀለው ድንጋይ ያልቧጠጠው ተራራ የለም። የሚያውቅ ያውቀዋል!

ልብ በሉ ከስር በምስል አስደግፈን ያመጣነውን ብቻ መመልከት ምን ያህል ሰይጣን የሚቀናበት ቀጣፊ መሆኑን ተመልከቱ። የዞኑ መንግስት በዚህ ልክ በስሩ ያለ አንድ ቢሮ የመንግስትን ሚስጥር እያወጣ የሚሰጥ ከሆነ መንግስትነቱ ዬቱ ጋር ነው?

አይ አልቻልቡና ጉዱ አያልቅም ነገሩ ወዲህ ነው -ሲልከሰከስ ቀርጥፎ የጨረሰውን ቅቡልነት በጥላሸት ሚዲያ ኔትዎርክ በኩል ባይሳካ የወደቀበት ከተረሳ አመታት ያለፈውን የተማሪዎች ህብረት አቧራውን አራግፎ ወራቤ ከትሞ ነበር አሉ።

ፎቶዬ አወል ሰልፍ አልተገናኘም ብሎ ክስ ግን ዘመኑን አይመጥንም ለሰሚውም ይደብራል😊

✍️ቦርዱ የመራጮች ምዝገባ መጠናቀቁን በይፋ ካሳወቀ ከሁለት ቀናት በኋላ በሁለት ክልሎች ምዝገባውን አራዘመ✍️የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የ2017 ምርጫ አስፈጻሚ ቦርድ፤ ...
07/22/2025

✍️ቦርዱ የመራጮች ምዝገባ መጠናቀቁን በይፋ ካሳወቀ ከሁለት ቀናት በኋላ በሁለት ክልሎች ምዝገባውን አራዘመ

✍️የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የ2017 ምርጫ አስፈጻሚ ቦርድ፤ ሐምሌ 13/2017 የመራጭነት ምዝገባ መጠናቀቁን ካሳወቀ በኋላ በድጋሚ በሁለት ክልሎች አንድ ሣምንት የመመዝገቢያ ጊዜ ፈቅዷል።

✍️ቦርዱ ዛሬ ማክሰኞ ሐምሌ 15/2017 ምሽት ባወጣው መግለጫ እንዳሳወቀው፣ ምዝገባው የተራዘመው በአማራ እና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ነው።

✍️በክልሎቹ የመጅሊስ ምርጫ ምዝገባ ሂደቱን ከነገ ረቡዕ ሐምሌ 16 እስከ ረቡዕ ሐምሌ 23/2017 ለማስቀጠል የወሰነው በሦስት ምክንያቶች መሆኑን ገልጿል። እነዚህ ምክንያቶች በክልሉ በነበረው የምርጫ አስፈጻሚ ቦርድ አለመግባባት ምዝገባ የተቋረጠ መሆኑ፣ የቁሳቁስ ሥርጭት በጊዜ ባለመዳረሱ እና በዚህ ሳቢያ የሥልጠናና የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራ በወቅቱ አለመሰጠቱ ናቸው።

✍️ችግሮቹ እንደተፈቱ የጠቆመው ቦርዱ፣ ከነገ ጧት 12 ሰዓት ጀምሮ የማኑዋል እና የኦንላይን የምዝገባ ስልቶች እንዲቀጥል ውሳኔ ማሳለፉን አስታውቋል። በዚህም ምዝገባውን ያልጀመሩ አካባቢዎች እንዲጀምሩ እና ምዝገባውን ጀምረው በተለያየ ምክንያት ያቋረጡ አካባቢዎች ይቀጥላሉ ብሏል።

✍️የምርጫ አስፈጻሚ ቦርዱ የምዝገባውን መጠናቀቅ ባሳወቀበት ቀዳሚ መግለጫ፣ ለአንድ ወር በቆየው ሒደት የተመዘገበውን የመራጮች ቁጥር ይፋ አላደረገም።

07/22/2025

የጥቅም ትስስሩ ኬት እስኬት.....

 ::ሐሰተኛ መረጃ ማሰራጨት በህግ የሚያስጠይቅ ነው::በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ሲሰራጭ የነበረው የአንዲት ግለሰብ አቤቱታ ሐሰተኛ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ በድጋሚ አረ...
07/22/2025

::

ሐሰተኛ መረጃ ማሰራጨት
በህግ የሚያስጠይቅ ነው::

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ሲሰራጭ የነበረው የአንዲት ግለሰብ አቤቱታ ሐሰተኛ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ በድጋሚ አረጋግጧል!

ከዚህ ቀደም ወ/ሮ ሰርካለም አስራት ነሐሴ 19 ቀን 2016 ዓ/ም በልጇ ላይ የግብረ ሰዶም ጥቃት እንደተፈፀመበት እና በእሷ ላይም ጥቃት ሊፈፀምባት እንደሆነ ለለሚኩራ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ማመልከታቸው ይታወሳል።

* በወንጀሉ የተጠረጠረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ።

* ጥቃት ደርሶበታል የተባለው ህፃን ወደ አበበች ጎበና መታሰቢያ ሆስፒታል ተላከ።

* ተጨማሪ ምርመራ ለማድረግ ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ተልኮ፣ በህፃኑ ላይ ምንም አይነት የግብረ ሰዶም ጥቃት እንዳልተፈፀመበት በህክምና ማስረጃ ተረጋገጠ።

የለሚኩራ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የወንጀልና ትራፊክ አደጋ ምርመራ ኃላፊ ኮማንደር መስፍን በላቸው ይህን መረጃ አረጋግጠዋል።

ጥር 19 ቀን 2017 ዓ/ም ግለሰቧ ተመሳሳይ አቤቱታ በድጋሚ ማቅረቧን ተከትሎ ፖሊስ ተጨማሪ ምርመራ አድርጓል። ታዳጊው ለሁለተኛ ጊዜ ሆስፒታል ተልኮ ተመርምሮ ጥቃቱ እንዳልተፈፀመበት እንደገና ተረጋግጧል።

ዶ/ር ወገኔ አሰፋ፣ በአበበች ጎበና ሆስፒታል የተቀናጀ የሴቶችና ህፃናት ህክምና ክፍል የህክምና ባለሙያ፣ ህፃኑ ሁለት ጊዜ መመርመሩን እና ምንም አይነት ጉዳት እንዳልደረሰበት አስረድተዋል።

የህክምና ታሪክ እና የህግ ሂደት

ፖሊስ ባደረገው ማጣራት፣ ግለሰቧ እና የ12 ዓመት ልጇ በኤካ ኮተቤ አጠቃላይ ሆስፒታል የአእምሮ ህክምና ሲከታተሉ እንደነበር እና ህክምናውን ሳይጨርሱ እንዳቋረጡ በማስረጃ አረጋግጧል።

በግለሰቧ አቤቱታ ወንጀሉን ፈፅሟል ተብሎ የተከሰሰው አቶ ተወልደ ከበደም፣ ጉዳዩን ለማጣራት ለአምስት ቀናት ታስሮ የነበረ ሲሆን፣ የህክምና ውጤቱን ተከትሎ በዋስ ተለቋል።

ግለሰቧ አሁንም ድረስ ፍትህ እንዳላገኘች በመግለፅ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ሐሰተኛ መረጃዎችን እያሰራጨች ትገኛለች። ፖሊስ፣ መረጃውን ከአንድ ወገን ብቻ በመስማት የሚያስተጋቡ ህገ-ወጥ ግለሰቦችም መኖራቸውን ገልጾ፣ በህግ አግባብ ተገቢውን እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል።
አዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስጠንቅቋል፡-

ባልተረጋገጠ መረጃ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች የሚሰራጨው የግለሰቧ አቤቱታ ሐሰተኛ መሆኑን በድጋሚ እያስታወቅን፣

ሐሰተኛ መረጃ ማሰራጨት በህግ የሚያስጠይቅ በተለይም በሰዎች ማህበራዊ ህይወት ላይ ጭምር ከፍተኛ ጫና የሚያሳድርና የህግ ተጠያቂነትን የሚያስከትል በመሆኑ ግለሰቦችም ሆኑ ተቋማት ተገቢውን ጥንቃቄ ሊያደርጉ ይገባል!"

እባክዎን መረጃዎችን ከታማኝ ምንጮች ብቻ ይቀበሉ እና ሀሰተኛ መረጃዎችን ከማጋራት ይቆጠቡ!

Via አዲስ አበባ ፖሊስ

በበጀት ዓመቱ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የታቀዱ እቅዶችን በቅንጅት ለመስራት በተደረገው ጥረት ተስፋ ሰጪ ዉጤት ተመዝግቧል፦ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር):::::::::::...
07/22/2025

በበጀት ዓመቱ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የታቀዱ እቅዶችን በቅንጅት ለመስራት በተደረገው ጥረት ተስፋ ሰጪ ዉጤት ተመዝግቧል፦ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር)
:::::::::::::::::::::::::::::::::::::::

" ከመስፈንጠር ከፍታ ወደ ላቀ እምርታ"በሚል መሪ ሀሳብ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በመንግስት እና በፓርቲ ትብብር የተከናወኑ አበይት ተግባራትን የገመገመና የ2018 ዕቅድ አቅጣጫዎች ላይ የመከረ የአመራር መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል።

በመድረኩ ከተረጅነት የመውጣት ጥረት፣ የስራ ዕድል ፈጠራ፣የገበያ ማረጋጋትና የኑሮ ውድነትን በመቀነስ ረገድና ሌሎች ጉዳዮችን በመዳሰስ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትና የተመዘገቡ ውጤቶችን በተመለከተ በስፋት ውይይት ተደርጓል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር)በመድረኩ ማጠቃለያ ባስቀመጡት አቅጣጫ እንዳሉት፦በበጀት ዓመቱ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የታቀዱ እቅዶችን በቅንጅት ለመስራት በተደረገው ጥረት ተስፋ ሰጪ ዉጤት ተመዝግቧል ብለዋል።

ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የኑሮ ዉድነትን ለማረጋጋትና የአርሶ አደሩን ኑሮ በማሻሻል ፡የስራ እድል ፈጠራ ችግር በመቅረፍና ረገድ ከፍተኛ ዉጤት ማስመዝገብ ተችሏል ብለዋል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ ከተሞችን በማዘመንና የከተማና የገጠር መንገድ ተደራሽነትን በማስፋት እየተደረገ ባለዉ ጥረት ተስፋ ሰጪ ዉጤት ስለመመዝገቡም ገልጸዋል።

በበጀት ዓመቱ የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች በትክክለኛ መንገድ ላይ ስለመሆኑ ጠቅሰዉ ፡-የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ በማስቀጠል የተሻለ ዉጤት ለማስመዝገብ አመራሩ በቅንጅት መስራት እንዳለበትም ገልፀዋል፡፡

በ2018 በጀት ዓመት ብልሹ አሰራርን በመታገል ፡ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቅረፍ ፍትሀዊና ቀልጣፋ አገልግሎት ለተገልጋዩ ለመስጠት ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም አክለዋል፡፡

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር) በበኩላቸው በ2017 የፓርቲ የዕቅድ አፈጻጸም ላይ ሰፋ ያለ ውይይት በማድረግ የነበሩ ስኬቶችን እና ጉድለቶችን ለይቶ በመገምገም 2017 የትጋትና የስኬት አመት መሆኑን ማረጋገጥ ችለናል ብለዋል።

በበጀት አመቱ ከክልል ማዕከል ጀምሮ በየደረጃው በሚሰጡ ተልዕኮዎች ተቀብሎ ከመፈጸምና ከማስፈጸም አኳያ የነበረው ቅንጅትና መናበብ በጥንካሬ የሚወሰድና የገዥ ትርክት ግንባታን ስርፀትን ያመላከተ ነው።

በአደረጃጀት በአስተሳሰብና በተግባር የተዋሀደ የተቀናጀ አመራርና አባል ስለመገንባቱም የተናገሩት ኃላፊው፤በተመሳሳይ የአሰራር ሰረዓቱ የተገነባ ፓርቲ፣የሚመራበት የአሰራርና አደረጃጀት መመሪያ እና ደንብን ከማስረጽ አኳያ አበረታች ስኬት መመዝገቡን ገልጸዋል።

በዚህም የተመዘገቡ ስኬቶችን የፓርቲያችንን ራዕይ ለማስቀጠልና ዕውን ለማድረግ እንጠቀምበታለን ዲላሞ (ዶ/ር) ከጉድለቱም መማር እንደሚገም ገልጸዋል።

አደረጃጀቶችን በመጠቀም በቅንጅት ህዝብን ተጠቃሚ ከማድረግ አንጻር በበጀት አመቱ በየደረጃው በርካታ ስራዎች ስለመሰራቱም አመልክተዋል።

አክለውም የአመለካከትና የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚታዩ የጥራት ችግሮች ስለመኖራቸው ገልጸው በቀጣይ ሁሉም ባለድርሻ በኃላፊነት ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች ከመስፈንጠር ከፍታ ወደ ላቀ እምርታ በሚደረገው ጉዞ በ2017 የተገኘውን ውጤት በማስቀጠል በቀጣይ በጀት ዓመትም የላቀ አፈፃፀም እንዲኖር የተቀናጀ ጥረት እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል።

ሀገራዊ የመጅሊስ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በማድረግ በኩል ህዝበ ሙስሊሙ ሚናውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ፡፡::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::የስ...
07/22/2025

ሀገራዊ የመጅሊስ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በማድረግ በኩል ህዝበ ሙስሊሙ ሚናውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ፡፡
::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::
የስልጤ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምርጫ አስፈጻሚ ቦርድ ከወረዳና ከተማ አስተዳደር የምርጫ አስፈጻሚ እና የመጅሊስ አመራር የ2017 ሀገራዊ የመጅሊስ ምርጫን አስመልክቶ በወራቤ ከተማ ውይይት አካሄደ፡፡

የስልጤ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምርጫ አስፈጻሚ ቦርድ ከወረዳና ከተማ አስተዳደር የምርጫ አስፈጻሚ እና የመጅሊስ አመራር ዛሬ በወራቤ ከተማ ባካሄደው የውይይት መድረኩ ላይ የ2017 ሀገራዊ የመጅሊስ ምርጫን አስመልክቶ የዞኑን የመራጭነት ምዝገባ ሂደት የተጠናቀቀበት አግባብ አፅንኦት ሰጥቶ ተመልክቷል፡፡

የግምገማ መድረኩን የስልጤ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምርጫ እፈጻሚ ሰብሳቢ የሆኑት ዶ/ር ከይረዲን ሁሴን ፣ምክትላቸዉ አቶ ሸምሴ ባሙድ እና የቦርዱ ፀኃፊ አቶ ነጃ ሰልማን በጋራ በመሆን መርተውታል፡፡

በዚሁ መነሻ በእስካሁኑ በየዘርፉ ማለትም በኡለሞች፣ ምሁራን፣ ወጣቶች፣ ሴቶች እና በሥራ ማህበረሰብ የተመዘገቡ መራጮች ከየመዋቅሩ ሪፖርት የቀረበ ሲሆን በእስካሁኑ የመራጭ ምዝገባ መመዝገብ ካለበት 89.36% የተመዘገበ መሆኑን ተገምግሟል፡፡

በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት የስልጤ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክርቤት ሰብሳቢ ሼህ አብዱረሂም አህመዲን የመጅልሱ ምርጫ 2017 ፍፁም ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ህዝበ ሙስሊሙ የድርሻውን ሊወጣ ይገባል ብለዋል፡፡

በመድረኩ ላይ የዕለቱ የክብር እንግዳና የስልጤ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ከድር አብደላ በበኩላቸው ምርጫዉ ሰላማዊ፣ አካታች እና ሁሉ አቀፍ እንዲሆን ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡

አቶ ከድር አክለውም የሙስሊሙን አንድነት ይበልጥ አሁን ካለበት ከፍ የሚያደርግ ተቋም ለመመስረት የሚችል መሆን እንዳለበትም መልክታቸዉን አስተላልፈዋል፡፡

በመጨረሻም የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች የምርጫ ማስፈጸሚያ መመሪያን አስመልክቶ የዞኑ የእስልምና ጉዳዮች ምርጫ አስፈጻሚ ፀኃፍ በሆኑት አቶ ነጃ ሰልማን በዝርዝር የቀረበ ሲሆን ከምዝገባ በኋላ ባሉ የምርጫ ሂደቶች በተለይም በእጩ ምልመላ፣ የመራጭ ድምጽ አሰጣጥ እና የኡለሞች አመራረጥን አስመልከቶ ለተሳታፊዎች ስልጠና ሰጥተዋል፡፡

"አስፈሪው ፊልም"አንቶኒዮየተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዛሬው ዕለት እንደተናገሩት የተመጣጠነ ምግብ እጥረት እጅግ እየተባባሰ መምጣቱን እና በጋዛ የሚገኘውን እያ...
07/22/2025

"አስፈሪው ፊልም"አንቶኒዮ

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዛሬው ዕለት እንደተናገሩት የተመጣጠነ ምግብ እጥረት እጅግ እየተባባሰ መምጣቱን እና በጋዛ የሚገኘውን እያንዳንዱን በር ረሃብ እያንኳኳ መሆኑን "አስፈሪ ፊልም" ሲሉ ገልፀውታል።

ጉቴሬዝ አክለውም በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ፊት"በአሁኑ ጊዜ በሰብአዊ መርሆዎች ላይ የተመሰረተ የሰብአዊ ስርዓት የመጨረሻ እስትንፋስ እያየን ነው።

ይህ የአሰራር ሁኔታ እርዳታ ለመስጠት ሚያስፈልገው ቦታ እና ህይወትን ለማዳን የሚያስፈልገው ደህንነት ተነፍጎታል" በማለት ገልፀዋል።

#ዘገባው የነጋሽ መሀመድ ነው።

ባለፉት 3 ዓመታት አዲሱ መጅሊስ ለአንድነት ከተንቀሳቀሰው በላይ እነዚህ ሰዎች ሙስሊሙን ለመበታተን የተንቀሳቀሱት ይበልጣል!!! ከማን ጋር ወግነው ሙስሊሙን እያጠቁ እንደሆነ ተመለከቱ?
07/22/2025

ባለፉት 3 ዓመታት
አዲሱ መጅሊስ ለአንድነት
ከተንቀሳቀሰው በላይ
እነዚህ ሰዎች ሙስሊሙን ለመበታተን የተንቀሳቀሱት ይበልጣል!!!
ከማን ጋር ወግነው ሙስሊሙን እያጠቁ እንደሆነ ተመለከቱ?

ይሄ ነገር እውነት ከሆነ የኢትዮጵያ ሙስሊም ለሁለተኛ ጊዜ ከእንቅልፉ ሊናቃ ነው። ኡስታዝ አሕመዲን ጀበል መጅሊስ እንዳይገባ ታገደ‼️   ~~~~~~~~~~~  ኡስታዝ Ahmedin Jebel-አ...
07/21/2025

ይሄ ነገር እውነት ከሆነ የኢትዮጵያ ሙስሊም ለሁለተኛ ጊዜ ከእንቅልፉ ሊናቃ ነው።

ኡስታዝ አሕመዲን ጀበል መጅሊስ እንዳይገባ ታገደ‼️
~~~~~~~~~~~

ኡስታዝ Ahmedin Jebel-አሕመዲን ጀበል የፌዴራል መጅሊስ ቅጥር ግቢ እንዳይገባ መታገዱን ምንጮች ለሆራይዘን ሚዲያ ገለፁ::

በሁለቱ መሃከል የቆዬ መልካም ግንኙነት የነበረ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየሻከር መምጣቱን ጨምረው የገለፁት ምንጮች ፤ በተለይ ኡስታዝ አሕመዲን ጀበል “መጅሊስን ማን ይምራው? ሳንተፋፈር በግልጽ እንነጋገርበት‼️ በሚል ርዕስ በማኅበራዊ ትስስር ገፁ በፅሁፍ ያጋራው እና ከ ነጃሺ ቲቪ የጀማል አሕመድ ሾው ጋር የመጅሊስ ምርጫን አስመልክቶ በሁለት ክፍል የቀረበ ቃለ ምልልስ ግንኙነታቸውን የበለጠ የማይታረቅ አድሮታል ብለዋል::

ኡስታዝ አሕመዲን ጀበለ እስከ ቅርብ ግዜ የጠቅላይ ም/ቤቱ ፕሬዝደንት አማካሪ ሆኖ ሲሰራ እንደቆየ የሚታወቅ ሲሆን ፤ 'ፕሬዝዳንቱ ምክር አይቀበሉም❗ ብለው በገዛ ፍቃዳቸው ከአማካርነት ራሳቸውን ካገለሉ ጥቂት አማካሪዎችም አንዱ እንደነበረ ምንጮች ጨምረው ለሆራይዘን ገልፀዋል::

ፕሬዝዳንቱም የኡስታዝ አሕመዲንን የሚዲያ ዘመቻ ይገታልኛል ወይም ይመክትልኛል በሚል እራሱን "የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የጋራ ፎረም" የተሰኘ የሎቢ ቡድን ማደራጀታቸውንም ምንጮች ለሆራይዘን ሚዲያ ጨምረው ገልፀዋል::
ዘገባው @የሆራይዘን ሚድያ ነው

ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

Address

American Fork, UT

Telephone

+97433401028

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Faf Media-ፋፍ ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share