Fetam Media Network-FMN

Fetam Media Network-FMN Show new sides to the peoples

የኢትዮጵያን ስም በሰበብ በአስባቡ መጥራት የሚወደው ጋሽ ትራምፕ  "...ኢትዮጵያ በናይል ወንዝ ላይ እየገደበች በነበረው  ግዙፍ  ግድብ ምክንያት ኢትዮጵያና ግብፅ ሊገቡበት የነበረውን ትልቅ...
06/16/2025

የኢትዮጵያን ስም በሰበብ በአስባቡ መጥራት የሚወደው ጋሽ ትራምፕ
"...ኢትዮጵያ በናይል ወንዝ ላይ እየገደበች በነበረው ግዙፍ ግድብ ምክንያት ኢትዮጵያና ግብፅ ሊገቡበት የነበረውን ትልቅ ጦርነት እኔ ጣልቃ በመግባት አስቀርቼዋለሁ... ልክ ኢሄን እንዳሳካሁት ሁሉ የኢራንና እስራኤልንም ጦርነት አስቀራለሁ " ሲል ሳያፍር ተናግሯል !

በማደራደር ሰበብ የኢትዮጵያን እጅ ለመጠምዘዝ ሞክሮ ሳይችል ሲቀር ግብፅ ግድቡን ታፈነዳዋለች እስከማለት ፀባጫሪ ለግብፆች" ግድቡን ምቱት" አይነት ንግግር በአደባባይ እስከ መናገር ደረጃ የደረሰበትን ግዜ መቼስ ኢትዮጵያዊያን አይረሱም ።

የሆነው ሆነና በብዙ ተነግሮ ማያልቅ መስዕዋትነት እነሆ ኢትዮጵያ ታላቁን የአፍሪካ ግዙፍና ታሪካዊ ግድብ ልታስመርቅ ሽርጉድ ማለት ጀምራለችና ክሬዱቱን ለመውሰድ መሞከሩ ከማናደድ ይልቅ የሚያስቅ ፣ የኢትዮጵያዊያንንም አይበገሬነት ያረጋገጠ ተደርጎ ይወሰዳል ።

FMN

ሰበር ዜና!ሰበር ዜናበአማራ ክልል ጎንደር ዙሪያ አንድ ሄሊኮፕተር መውደቁን ከቦታው የደረሰን መረጃ ያሳያል። ሄሊኮፕተር የወደቀው በምን ምክንያት እንደሆነ የተረጋገጠ መረጃ የለም። መረጃውን ...
06/16/2025

ሰበር ዜና!
ሰበር ዜና
በአማራ ክልል ጎንደር ዙሪያ አንድ ሄሊኮፕተር መውደቁን ከቦታው የደረሰን መረጃ ያሳያል። ሄሊኮፕተር የወደቀው በምን ምክንያት እንደሆነ የተረጋገጠ መረጃ የለም። መረጃውን እያጣራን ነው።

የፈጣሪ ያለህ!! ይህ ሼህ የሚደንቅ መሪ ነው።ምሽቱን የኢራኑ ሼህ አያቶላ በሰጡት መግለጫ ትላንት ማታ ወደ እስራ^ኤል የላክናቸዉ ሚሳ^ኤሎች የሙከራ ስርጭቶች ናቸዉ ወደ ጦር°•ነት የምንገባዉ...
06/15/2025

የፈጣሪ ያለህ!! ይህ ሼህ የሚደንቅ መሪ ነው።
ምሽቱን የኢራኑ ሼህ አያቶላ በሰጡት መግለጫ ትላንት ማታ ወደ እስራ^ኤል የላክናቸዉ ሚሳ^ኤሎች የሙከራ ስርጭቶች ናቸዉ ወደ ጦር°•ነት የምንገባዉ ዛሬ ለሊት ነዉ።
ህዝባችንም አደባባይ ወጥቶ እስራ^ኤልን እንድናጠቃ አጥብቆ ጠይቆናል።
እስ^ራኤልን ከትላንቱ ጥፋት ዛሬ 20 እጥፍ አድርገን እንልክላታለን ለዚህም ይሆን ዘንድ 2000 ሺህ ሚሳ°•ኤሎች ዝግጁ ሆነዋል ብለዋል።

አባት(ጎራው ደመላሽ): የ4ቀኗ የማርያም አራስ ህፃኑን ለኔ ሰጣ ሞተችብኝ😢 ቀናችንን በመልካም ነገር እንጀምረው ሼር በማድረግ እንተባበር ዛሬ በህይወቴ አይቼው የማላውቀው እጅግ ከባድና ፈታኝ...
06/15/2025

አባት(ጎራው ደመላሽ): የ4ቀኗ የማርያም አራስ ህፃኑን ለኔ ሰጣ ሞተችብኝ😢

ቀናችንን በመልካም ነገር እንጀምረው
ሼር በማድረግ እንተባበር

ዛሬ በህይወቴ አይቼው የማላውቀው እጅግ ከባድና ፈታኝ ችግር ገጥሞኛል። ባየሁትና በሰማሁት ነገር ቀኔ ጨልሞ እጅግ አስከፊ የስሜት መረበሽ ውስጥ እገኛለሁ። ነገሩ እንዲህ ነው።

ዛሬ በቅኖች ጥቆማ መተከል ዞን ዳንጉር ወረዳ ማንቡክ ከተማ 01 ቀበሌ ከአቶ ጎራው ደመላሽ ቤት ተገኝተናል። አቶ ጎራው የሚያስቀና ትዳር የነበራቸው፣ እንደፈለጉ ወጥተው ገብተው ሰርተው ለቤተሰቦቻቸው ሳቅ የሚገዙ ደግ ባለትዳር ነበሩ።

በአብሮነታቸው፣ በመቻቻላቸውና በፍቅራቸው ያልቀና የማንቡክ ከተማ ህዝብ አልነበረም። ሁለት ልጆችን ወልደው ያሳደጉ፣ በአካባቢው ማህበረሰብ የተከበሩም ነበሩ።

እንሆ ሶስተኛ ልጃቸውን በስስት ለማየት ቀን ተጠባበቁ። ቀኑ ደረሰና ግርማው የሚያበራ ወርቅ ህፃንን በሆስፒታል ወለዱ። አምላክንንም ከልብ አመሰገኑ። ሆኖም ከውልደት ጋር በተያያዘ ግን እናት ብዙ ደም ፈሰሳትና ታመመች። አገግማም በሁለተኛ ቀኗ ወጣች። እንሆ ከሆስፒታል ከወጣች በሁለተኛ ቀኗ፣ ከወለደች በአራተኛ ቀኗ እናታችን በድንገት በተኛችበት አረፈች።

አባት ተጨነቀ፣ ልጆቹ ተንጫጩ፣ ጎረቤት አለቀሰ፣ ድፍን የማንቡክ ህዝብ የደም ጎርፍ እንባን አፈሰሰ።
አቤት የፈጣሪ ስራ! ፈጣሪ ወዳጅን መንሳት? አባት ሀዘኑን ዋጥ አድርጎ፣ የቤቱን ገመና ሸፍኖ፣ የደም እንባ እያነባ፣ ቤተክርስቲያን የፍታት ስርዓቷን ከዕለት እስከ 80 አወጣ።

ህፃኑንም እያዘለ የ10 ወር አደረሰ።
ሶስቱ ህፃናት ለመብል እንጂ ለመስራት ያልደረሱ በመሆናቸው ያለውን ሀብትና ጥሪት እየሸጠ ቀለበ። ጓዳውና ኪሱ ተራቆተ። በአደባባይ ህፃኑን አዝሎ ለስራ ካሬታ ይዞ ወጣ። ግን ሰዎች ህፃን አሸክሞ ማዘዝ ሲከብዳቸው 5 እና 10 ብር እየሰጡት መሄድ ጀመሩ።

ያ ክንደ ብርቱና ጀግና የልጆቹን ሳቅ የሚመልስ አባት በልጆቹ እናት ድንገተኛ ሞት ሳያስበው ለልመና ተዳረገ። ህፃን አዝሎ ወንድ ልጅ ልመና እጅግ ደም ያስነባል! አዎ! ከሌለህ የለህማ! ምን አማራጭስ ይኖረዋል!

ወገን ሁሉንም ሽጦ በአንድ ሜትር ሸራ፣ ተደራርቦ በተሰፋ ኩንታል ያስተኛቸዋል። ሲያገኝ በቆሎ እንጀራ ያስፈጫል። ሲያጣም የወፍጮ ጥራጊ አንጠርጥሮ ቂጣ በመጋገር ይመግባል።

ይበቃኛል! ምኑስ ሌላውማ ይነገራል ወገን? ወገን ስለፈጣሪ ድረሱለት! አባትን ከለቅሶና ከሀዘን፣ ልጆችን ከርሃብ በአስቸኳይ እንታደግ።

ለእርዳታ የሚሆን የባንክ አካውንት በራሳቸው ስም
CBE 1000267318925 ጎራው ደመላሽ
ስልካቸው:-
0924452039 ጎራው ደመላሽ

(በአካል ሁሉንም የሚያስተባብሩት
Mitiku Essayas ናቸው)

ሼር... ሼር... ሼር...
ለቅኖች አድርሱልኝ!

Via ሚትኩ እሳያስ
ከመተከል

🙏🙏🙏

🌴🌴🌴

   ➫ አገሩን ኢራንን አሳልፎ የሸጠ  አጋድሞ ያረ_ዳት  ጀነራል‼️አንዳንዴ አለምን ጉድ ያስባሉ ለማመን ሁሉ የሚቸግሩ የክህደት ታሪኮች ይደመጣሉ …አገራቸውን አጋድመው የሚያርዱ ዜጎች ይፈጠ...
06/15/2025

➫ አገሩን ኢራንን አሳልፎ የሸጠ አጋድሞ ያረ_ዳት ጀነራል‼️
አንዳንዴ አለምን ጉድ ያስባሉ ለማመን ሁሉ የሚቸግሩ የክህደት ታሪኮች ይደመጣሉ …አገራቸውን አጋድመው የሚያርዱ ዜጎች ይፈጠራሉ። የሆዳቸው እንጂ የአገራቸው ጉዳይ ፈጽሞ የማያሳስባቸው ሰው መሳዮች ይፈጠራሉ። በቃላት መግለጽ በማይቻል ደረጃ የአገራቸውን አንገት በዱልዱም ቢላዋ ካረዱት መካከል ኢራናዊው ብርጋዴር ጀነራል ኢስማኤል ቃኒ ተጠቃሽ ነው።
የኢራን ፕሬዚዳንት መሐመድ አህመዲ ነጃድ ከስልጣን ከወረዱ በኋላ በአንድ የቱርክ ቴሌቭዥን ጣቢያ የአረብኛ ፕሮግራም አንድ ጥያቄ ቀረበላቸው። ኢራን "የሞሳድን መረብ መበጣጠስ ያልቻለችበት ምክንያት ምንድነው?" የሚል።

ተስፋ በቆረጠ ስሜት 'በፕሬዝዳንትነት ዘመኔ ለመበጣጠስ ቁርጠኝነቱ ነበረኝ፤ እናም በጣም ጥቂት ቁልፍ ታማኝ ሰዎች የተካተቱበት ኮሜቴ አዋቅሬ ነበር። ሆኖም ውጤቱ የምጠብቀው አልነበረም። አሁን መለስ ብዬ ስገመግም የኮሚቴው ሰብሳቢ ያደረግኩት ሰው የሞሳድ አባል ይመስለኛል' በማለት መለሱ።

ንግግራቸው አስቂኝ ቀልድ ተደርጎ ነበር የተወሰደው። ኢራንም ከቁብ አልቆጠረችውም። ምክንያቱም የኮሚቴ ሰብሳቢ አድርገውት የነበረው በኢራን እስልምና አብዮታዊ ጥበቃ ቡድን (IRGC) ስር የተደራጀው አል-ቁድስ (Quds Force) ልዩ ክፍል ምክትል አዛዥን ነበር። ኢራን በእሳት የተፈተኑ ወርቆች ከምትላቸው የጦር መሪዎቿ አንዱ ብርጋዴር ጀነራል ኢስማኤል ቃኒ ነበር።

አህመዲ ነጃድ ቃለ ምልልሱን በሚሰጡበት ወቅት ደግሞ ብርጋዴር ጀነራል ኢስማኤል ቃኒ አሜሪካ ኢራቅ በድሮን ጥቃት የገደለቻቸውን ጀኔራል ሱሌማኒ ተክተው የአል ቁድስ ዋና አዛዥ ሆኖ ነበር (እኤአ ጥር 2020 አካባቢ ማለት ነው)። በዚህ ደረጃ የሚገኝን ቁልፍ የአገሪቱ ወታደራዊ አዛዥ መጠርጠር የማይታሰብ ነበር።

ያውም በየመድረኩ አሜሪካ እና እስራኤልን የሚጠላና የሚያብጠለጥል፣ በሁለቱ አገራት ጥብቅ ማዕቀብ የተጣለበት፤ ሁል ጊዜ ለግድያ የሚዛትበት . . . ማንና እንዴት ይጠርጥረው? ኢራን አሁን በምርመራ እንዳረጋገጠችው ደግሞ ጀኔራል ሱሌማኒ በኢራቅ ባግዳድ የተገደሉት ቃኒ በሰጠው መረጃ ነበር።
ነገሮች በዛው ቀጠሉ፤ ኢራን አዳዲስ የመሬት ውስጥ ኑክሊየር ማብሊያዎችን ብትሰራም እንዳሰበችው መደበቅ አልቻለችም። ገና ሰርታ ሳትጨርስ መረጃው እስራኤል እጅ ይደርሳል። በስፍራው የሚሰሩ ሳይንቲስቶች ማንነት፣ አድራሽና እንቅስቃሴ ሁሉ ሞሳድ እጅ መግባቱን ቀጠለ። እስራኤል የፈለገችውን የኑክሊየር ሳይንቲስቲ በጠራራ ፀሃይ ያውም በአገሪቱ ዋና ከተማ መቅጠፍ ቀጠለች።

የአሁኑ ይባስ እንዲሉ የአገሪቱ አምስት ቁንጮ ባለስልጣናት ብቻ የሚያውቁት የኢራን የኑክሊየር ሙሉ ሚስጥራዊ ሰነድ በእስራኤል እጅ ገባ። ጠቅላይ ሚንስትር ኔታንያሁም ጋዜጠኞችን ሰብስበው የኑክሊየር ሰነዱን በስክሪን እየገለጡ ማብራሪያና መግለጫ ሰጡ። ሆኖም ማንም ማንንም መጠርጠር የሚችልበት አንዳችም ክፍተት አልነበረም።

ይባስ ብሎም የሀማሱ መሪ እስማኤል ሀኒያ በሄሊኮፕተር አደጋ የሞቱት የኢራን ፕሬዝዳንት ቀብር ላይ ለመገኘት ወደቴህራን ባቀኑበት ወቅት ወደ ማረፊያ ክፍላቸው አስቀድሞ በገባ ቦንብ ተቀጠፉ። ከዚህ ሁሉ ጀርባ የኢራን ሁነኛ ባለስልጣን ጀነራል #ቃኒ ቢኖርም ማን ይጠርጥረው❓በምን ፍንጭ❓

በታሪክ ለእስራኤል ፈተና ከሆኑት የታጣቂ ቡድን መሪዎች መካከል የሂዝቦላ መሪው ሀሰን ናስራላህ ይጠቀሳል። የማይጨበጠው ናስረላህ ከሞሳድና ከዓለም ተሰውሮ የሚኖር የእስራኤል ራስ ምታት ነበር። ለዓመታት ለመግደል ያደረገችው ጥረት ሀሉ አልተሳካላትም።

የዓለም የክለቦች እግር ኳስ ውድድር ነገ ይጀመራል  | የእግር ኳስ ቤተሰቦች በጉጉት የሚጠብቁትና ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው የዓለም የክለቦች እግር ኳስ ውድድር በነገው ዕለት ይጀመራል።በውድ...
06/14/2025

የዓለም የክለቦች እግር ኳስ ውድድር ነገ ይጀመራል

| የእግር ኳስ ቤተሰቦች በጉጉት የሚጠብቁትና ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው የዓለም የክለቦች እግር ኳስ ውድድር በነገው ዕለት ይጀመራል።

በውድድሩ ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚወከሉ 32 ክለቦች በአሜሪካ ከትመዋል።

ነገ ውድድሩ ሲጀመር የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ አሸናፊው ፒ ኤስ ጂ ከአትሌቲኮ ማድሪድ ጋር 4 ሠአት ይገናኛል።

ከእኩለ ሌሊት በኋላ 9 ሠአት ላይ ደግሞ የግብጹ አል ሂላል ከአሜሪካው ኢንተር ሚያሚ ጋር ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

እንዲሁም የጀርመኑ ሻምፒዮን ባየርን ሙኒክ ከኒውዚላንዱ ኦክላንድ ሲቲ ጋር በተመሳሳይ ሠአት ይጫወታል።

በውድድሩ ክለቦች በየአህጉራቸው ያስመዘገቡት ውጤት እና በቻምፒየንስ ሊግ ተሳታፊ የነበሩ ቡድኖች ቀደም ባሉት ዓመታት ያስመዘገቡት ውጤት ታይቶ ተሳታፊ ሆነዋል።

የውድድሩ አሸናፊ የሆነ ክለብ በውድድሩ እያንዳንዱ ጨዋታን ጨምሮ አጠቃላይ 125 ሚሊየን ዶላር ያገኛል።

ከውድድሩ ፅንሰ ሃሳብ ጀምሮ በበርካታ ተጫዋቾች እና የክለብ አመራሮች ተቃውሞ የገጠመው ይህ የክለቦች ውድድር ለቀጣይ 28 ቀናት ይቆያል።

የፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ መልዕክት "ሁሉም ነገር ከመጥፋቱ በፊት ኢራን ስምምነት ማድረግ አለባት፤ 'በአንድ ወቅት የኢራን ኢምፓየር ነበረ' አንዳይባል ታድርግ" ብለዋል። ኢራን ወደ ስምምነ...
06/14/2025

የፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ መልዕክት

"ሁሉም ነገር ከመጥፋቱ በፊት ኢራን ስምምነት ማድረግ አለባት፤ 'በአንድ ወቅት የኢራን ኢምፓየር ነበረ' አንዳይባል ታድርግ" ብለዋል። ኢራን ወደ ስምምነት እንድትመጣ በተደጋጋሚ ዕድል ሰጥቻታለሁ ከሚያውቁት በእጅጉን መጥፎ የሆነ ነገር ሊያጋጥማቸው እንደሚችል ነግሬያቸዋለሁ አሜሪካ በአለም ላይ ያሉ ዘመናዊ የሆኑ የጦር መሳሪያዎችን በሙሉ ሰርታለች በማለት እስራኤል እነዚህ የጦር መሳሪያዎች በብዛት እንዳላት እንደዚሁም ተጨማሪ መሳሪያዎች ገና እንደምትጨምር እና እንዴት መጠቀም እንዳለባቸው እንደሚያውቁም ነግሬያቸው ነበር ብለዋል።

ፕሬዚዳንት ትራምፕ አክለውም ከዚህ የከፋ ነገር ሊፈጠር ይችላል ብለው በፃፉበት ፅሁፋቸው ብዙ ውድመቶችን እና ሞቶችን አይተናል፤ ወደ ስምምነት ለመምጣት ግን አሁንም አልረፈደም ሁሉም ነገር ከመጥፋቱ በፊት ኢራን ስምምነት ማድረግ አለባት፤ 'በአንድ ወቅት የኢራን ኢምፓየር ነበረ' አንዳይባል ታድርግ" ሲሉ በጹሑፋቸውን ያቀረቡት ፕረዚዳንቱ ከዚህ በኋላ ሞት ይብቃ ነበር ያሉት።

እስራኤል "በኢራን ሉዓላዊነት፣ ደህንነት እና የግዛት አንድነት ላይ ጥሰት እየፈጸመች ነው”/  ቻይና /በኢራን ጥያቄ መሰረት የቅዳሜ፣ ሰኔ 7/ 2017 ዓ.ምበተጠራው በተባበሩት መንግሥታት የ...
06/14/2025

እስራኤል "በኢራን ሉዓላዊነት፣ ደህንነት እና የግዛት አንድነት ላይ ጥሰት እየፈጸመች ነው”/ ቻይና /

በኢራን ጥያቄ መሰረት የቅዳሜ፣ ሰኔ 7/ 2017 ዓ.ም
በተጠራው በተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ ላይ ቻይና የእስራኤልን ጥቃት
በተወካይዋ ፉ ኮንግ በኩል ማዉገዟ ተዘግቧል ።

በዲፕሎማሲያዊ ድርድር ላይ ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ የቻይናን ጥልቅ ስጋት የገለፁት ሊ የሚመለከታቸው ሀገራት ሁኔታውን የበለጠ ሊያበላሹ የሚችሉ እርምጃዎችን እንዲያስወግዱ እና በመካከለኛው ምስራቅ ከኒውክሌር ጦር መሳሪያ ነፃ የሆነ ዞን እንዲመሰረት ድጋፍ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።

አክለዉም ቻይና በኢራን የኒውክሌር ጉዳይ ዙሪያ የሚደረጉ ፖለቲካዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች በኃላፊነት፣ በተጨባጭ እና በገለልተኛ መንገድ መደገፏን እንደምትቀጥል፣ አለም አቀፍ የኒውክሌር መስፋፋትን የመከላከል ዘዴን በጥብቅ እንደምትጠብቅ እና በመካከለኛው ምስራቅ ሰላምና መረጋጋትን እንደምታስጠብቅም ተናግረዋል።

በስብሰባው ላይ በርካታ የIAEA አባል ሀገራት አግባብነት ያለው ሁኔታ እንዳሳሰባቸው የገለፁ ሲሆን በርካታ ታዳጊ ሀገራት እስራኤል በኢራን የኒውክሌር መስሪያ ቤቶች ላይ የምታደርሰውን ጥቃት አጥብቀው አውግዘዋል።

በIAEA አጠቃላይ ጉባኤ የጸደቁትን በርካታ የውሳኔ ሃሳቦች በመጥቀስ በሰላማዊ የኒውክሌር መስሪያ ቤቶች ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶች ወይም ዛቻዎች የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቻርተርን፣ የአለም አቀፍ ህግን እና የIAEA ህጉን የሚጥሱ በመሆናቸው በኒውክሌር ደህንነት፣ በኑክሌር ደህንነት፣ በቀጣናዊ እና በአለም አቀፍ ሰላም እና ደህንነት ላይ ከፍተኛ ስጋት እየፈጠረ መሆኑን ጠቁመዋል። ፓርቲዎቹ የኢራንን የኒውክሌር ጉዳይ ለመፍታት ፖለቲካዊ እና ዲፕሎማሲያዊ አካሄዶች ትክክለኛ አማራጭ መሆናቸውን ጠቁመው አለም አቀፉ ማህበረሰብ ጥረቱን እንዲቀጥል ጠይቀዋል ሲል ዢንዋ ዘግቧል።

በስብሰባው ላይ የ IAEA ዋና ዳይሬክተር ራፋኤል ግሮስሲ አጽንኦት ሰጥተው እንደተናገሩት የኒውክሌር መስሪያ ቤቶች በማንኛውም ሁኔታ ጥቃት ሊደርስባቸው አይገባም ምክንያቱም ሰዎችን እና አካባቢን ሊጎዳ ይችላል. "እንዲህ ያሉት ጥቃቶች ለኒውክሌር ደህንነት፣ ደህንነት እና ጥበቃ እንዲሁም ለክልላዊ እና አለም አቀፋዊ ሰላም እና ደህንነት ከፍተኛ አንድምታ አላቸው" ሲል ግሮሲ ተናግሯል። ያለዉ ግሎባል ታይምስ ነዉ ።

በ  #እስራኤልና  #ኢራን ጦርነት የአብዛኛው  #ኢትዮጵያውያን ድጋፍ  #እምነትን መሠረት ያደረገ ነው።1. እስራኤልን የሚደግፈው የክርስትና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያዊብዙ የኢትዮጵያ የክርስት...
06/14/2025

በ #እስራኤልና #ኢራን ጦርነት የአብዛኛው #ኢትዮጵያውያን ድጋፍ #እምነትን መሠረት ያደረገ ነው።

1. እስራኤልን የሚደግፈው የክርስትና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያዊ

ብዙ የኢትዮጵያ የክርስትና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያዊ እስራኤልን የሚደግፈው “የክርስቲያን ወይም ክርስቶስ የተወለደባት ሐገር ናት” በሚል ነው። ነገር ግን አብዛኛው የክርስትና እምነት መነሻና የታሪኩ ሂደት የተፈጸመው እስራኤል ውስጥ ቢሆንም ክርስቶስ የተወለደው ግን በአሁኗ የፍልስጤም ግዛት ቤተልሔም ከተማ ነው።

እስራኤል የአብዛኛው የአይሁድ ምድር እንጅ የክርስቲያን አይደለችም። ካልተሳሳትኩ (ክርስቲያኖች 1.8%/ 1.6) ናቸው። እስራኤላውያንም ሆነ መንግስቷ ራሳቸውን "The Land of Jewish" ነው የሚሉት። ብዙ ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች እስራኤልን የሚደግፉት የክርስቲያን ሐገር ወይም ለኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች የደም ንክኪ አላቸው በሚል ነው።

እውነታው ግን ይኼ አይደለም። ማንኛውም ሐገር ቅድሚያ የሚሰጠው ለራሱ ሉዓላዊ ሐገርና ጥቅም ነው። እምነት የፖለቲካ ማስፈጸሚያ ሽፋን እንጅ pillar አይደለም። ብዙ ኢትዮጵያዊ ክርስቲያን እስራኤል ዘላለማዊ የኢትዮጵያ ወዳጅ የምትመስለው አለ። አይደለም!!

2. ኢራንን የሚደግፉ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች

ብዙ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ኢራንን የሚደግፉት የእስልምና ጠበቃ አድርገው ስለሚቆጥሯት ነው። እውነታው ግን እምነት የፖለቲካ ማስፈጸሚያ ሽፋን እንጅ መሠረቱ አይደለም። ኢራን ኢስላማዊ ሐገር ብትሆንም ከጥቅሟና ሉዓላዊነቷ ውጭ የማንንም ኢስላማዊ ሐገር የበላይነት አትፈልግም። ለምሳሌ፦ ኢራን ከእስልምና እምነት መፈጠሪያዋ ሳውዲ አረቢያ ጋር እሳትና ጭድ ናት።

ለምን ከተባለ አካባቢያዊና ቀጠናዊ የፖለቲካ አሰላለፍና የበላይነት ፍትጊያ ጉዳይ ነው። ኢራን የአብዛኛው ክርስቲያኗ ራሽያ ደጋፊ ስትሆን፣ ሳውዲ አረቢያ ደግሞ የአሜሪካ ደጋፊ ናት። የጥቅም ጉዳይ ነዋ! በእምነት ከተሄደማ ሳውዲ አረቢያና ኢራን የሱኒና የሽያ እስልምና ተከታዮች ናቸው።

የፖለቲካ አሰላለፉ በቀጠናው የበላይ ሆኖ ለመውጣት ስለሆነ እምነት ቦታ የለውም። የፖለቲካ ጉዳይ ሆኖ እንጂ የእምነት ጉዳይ ቢሆን አብዛኛው የኦርቶዶክስ ክርስትንና የዘር መመሳሰል ያለባቸው ራሽያና ዩክሬይን ባልተዋጉ ነበር።

ዞሮ ዞሮ በፖለቲካ ውስጥ እምነት የጥቅም ማስከበሪያ እንጅ ዋና ምክንያት አይደለም።
ከእምነት ውጪ ባለው ፖለቲካዊ ጥቅም ላይ እናተኩር!
Via Ethiopia

ኢራን ሚሳኤል ማስወንጨፏን ከቀጠለች “ቴህራን” ትቃጠላለች ሲሉ የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ አስጠነቀቁ።ሚኒስትሩ ከወታደራዊ ባለስልጣናት ጋር ባደረጉት ግምገማ ላይ በሰጡት አ...
06/14/2025

ኢራን ሚሳኤል ማስወንጨፏን ከቀጠለች “ቴህራን” ትቃጠላለች ሲሉ የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ አስጠነቀቁ።

ሚኒስትሩ ከወታደራዊ ባለስልጣናት ጋር ባደረጉት ግምገማ ላይ በሰጡት አስተያየት “የኢራኑ አምባገነን የኢራን ዜጎችን ወደ ታጋችነት እየቀየረ ነው። በተለይም የቴህራን ነዋሪዎች በእስራኤል ሲቪሎች ላይ ለደረሰው ጥቃት ከፍተኛ ዋጋ የሚከፍሉበት እውነታ እየፈጠረ ነው” ብለዋል።
https://bbc.in/4e3bNs5

ቻይና የአፍሪካ ሃገራትን ከቀረጥ ነፃ ተጠቃሚ አደረገች !ቤጂንግ ከኢስዋቲኒ በስተቀር በሁሉም የአፍሪካ ሀገራት የሚገኙ ምርቶች ላይ ታሪፍ ለማንሳትና ከአህጉሪቱ መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት፣...
06/14/2025

ቻይና የአፍሪካ ሃገራትን ከቀረጥ ነፃ ተጠቃሚ አደረገች !

ቤጂንግ ከኢስዋቲኒ በስተቀር በሁሉም የአፍሪካ ሀገራት የሚገኙ ምርቶች ላይ ታሪፍ ለማንሳትና ከአህጉሪቱ መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት፣ የፍጆታ ቁሳቁሶች ከቀረጥ ነፃ በዜሮ ታሪፍ እንደምታቀርብ ገለፀች ።

በማዕከላዊ ቻይና ሁናን ግዛት ዋና ከተማ ቻንግሻ "ቻይና እና አፍሪካ በጋራ ወደ ዘመናዊነት" በሚል መሪ ቃል 4,700 የሚጠጉ የቻይና እና የአፍሪካ ኩባንያዎች እንዲሁም ከ30,000 በላይ ተሳታፊዎች በተገኙበት አራተኛው የቻይና አፍሪካ የኢኮኖሚ እና የንግድ ትብብር መድረክ ላይ ነዉ ።

የቻይና አፍሪካ የኢኮኖሚና የንግድ ትብብር ብሉ ቡክ፡ የልማት ሪፖርት (2025) እንደ ኢንዱስትሪ፣ ግብርና፣ ቴሌኮሙኒኬሽን፣ ዲጂታል ኢኮኖሚ፣ አዲስ መሠረተ ልማት፣ አረንጓዴ ኢነርጂ እና የፋይናንሺያል አገልግሎቶች ባሉ ዘርፎች ትብብር መስፋፋቱን

ያለው ትብብር እየጨመረ መምጣቱ በቻይና እና በአፍሪካ መካከል ያለው የግብርና ንግድ ከጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት ወደ ተቀነባበሩ እቃዎች እየተሸጋገረ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን እነዚህ እድገቶች በአፍሪካ ለኢንዱስትሪያላይዜሽን መግፋት፣ በቻይና ኢኮኖሚ ማሻሻያ እና በቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ ቀጣይ ተጽእኖ የተፈጠሩ ናቸው ሲል አፍሪካ ኢኮኖሚና ንግድ ማስፋፊያ ምክር ቤት ኃላፊ Xu Xiangping ተናግረዋል ።

ቻይና እና አፍሪካ ትልቋ በማደግ ላይ ያሉ ሀገራት እና በታዳጊ ሀገራት ከፍተኛ መጠን ያለው አህጉር እንደመሆናቸው መጠን በደቡብ-ደቡብ ትብብር አዳዲስ ድንበሮችን በጋራ እየፈተሹ ነው ሲሉ የተገናገሩት ሚኒስትሩ ቻይና የአህጉሪቱን እድገትና ብልፅግና ማየት ምኞታቸዉ መሆኑን ገልፀዉ ከቻይና ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ላላቸው 53 የአፍሪካ ሀገራት ከቀረጥ ነፃ የዜሮ ታሪፍ ተጠቃሚ ይሆናሉ እንደ ኡጋንዳ እና ኢትዮጵያ ያሉ ከአሁን በፊት የዜሮ ታሪፍ ተጠቃሚ ለነበሩትም ለማራዘም ፈቃደኛ መሆኗን ተናግረዋል።

ቤጂንግ እንደ አንድ አካሏ የምታያትን ታይዋንን የምትደግፈው ኢስዋቲኒ ግን የዚህ እድለ ተጠቃሚ እንደማትሆን ገልፀዋል ።

አክለዉም "በአፍሪካ ያላደጉ ሀገራት ወደ ቻይና ለመላክ የበለጠ ምቹ ሁኔታዎችን ትሰጣለች" ብለዋል ።

ዘገባዉ የሲሲቲቪ ነዉ ።

ጦርነቱ ቀጥሏል!! እስራኤል በኢራን ዋና ከተማ በሚገኝ መኖሪያ ቤቶች ላይ በፈጸመችው ጥቃት 20 ህጻናትን ጨምሮ ወደ 60 የሚጠጉ ሰዎች መሞታቸውን የኢራን መንግስት ቲቪ ዘግቧል። (አልጀዚራ)
06/14/2025

ጦርነቱ ቀጥሏል!!

እስራኤል በኢራን ዋና ከተማ በሚገኝ መኖሪያ ቤቶች ላይ በፈጸመችው ጥቃት 20 ህጻናትን ጨምሮ ወደ 60 የሚጠጉ ሰዎች መሞታቸውን የኢራን መንግስት ቲቪ ዘግቧል። (አልጀዚራ)

Address

Atlanta, GA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Fetam Media Network-FMN posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share