Info Center

Info Center FELEG ETHIOPIA

የሙሉጌታ ከበደ ሥርአተ ቀብር ነገ ይፈጸማልየቀድሞው የቅዱስ ጊዮርጊስ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አምበልና አጥቂ ሙሉጌታ ከበደ (ወሎየው) ሥርአተ ቀብር ነገ ይፈጸማል። የአስከሬን የሽኝት ...
06/11/2025

የሙሉጌታ ከበደ ሥርአተ ቀብር ነገ ይፈጸማል

የቀድሞው የቅዱስ ጊዮርጊስ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አምበልና አጥቂ ሙሉጌታ ከበደ (ወሎየው) ሥርአተ ቀብር ነገ ይፈጸማል።

የአስከሬን የሽኝት ፕሮግራሙ ነገ ሰኔ 5 ቀን 2017 ዓ.ም 2:30 ጀምሮ በአዲስ አበባ ስታዲየም እንደሚደረግ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ አስታውቋል።

ስርአተ ቀብሩም ነገ ከቀኑ 7:00 ሠአት ኮልፌ በሚገኘው የሙስሊም መካነ መቃብር ይፈፀማል። ሙሉጌታ ከበደ ባደረበት ህመም ሳቢያ በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

http://t.me/felegethiopia

ሙሉጌታ ከበደ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ !የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና የቅዱስ ጊዮርጊስ አጥቂ ሙሉጌታ ከበደ (ወሎየው) ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱ ተሰምቷል።የሀገራችን የምንጊዜውም ...
06/11/2025

ሙሉጌታ ከበደ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ !

የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና የቅዱስ ጊዮርጊስ አጥቂ ሙሉጌታ ከበደ (ወሎየው) ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱ ተሰምቷል።

የሀገራችን የምንጊዜውም ምርጡ አጥቂ የሚባለው ሙሉጌታ ባጋጠመው ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል። ሙሉጌታ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና በቅዱስ ጊዮርጊስ ለበርካታ ዓመታት በስኬት በመጫወት የገዘፈ ስም ያለው ምርጡ አጥቂ ነበር።

http://t.me/felegethiopia

.   人  ✨* 。 • ˚* ˚ 🌙  ( ___)   *    ኢድ *   ✨  ┃口┃ ** አልአድሃ (አረፋ)✨  ┃口┃✨                  * *˛•  ┃口┃✨ 。* ✨ 。•˛˚˛*   ┃口┃ •...
06/05/2025

. 人 ✨* 。 • ˚* ˚ 🌙
( ___) * ኢድ * ✨
┃口┃ ** አልአድሃ (አረፋ)✨
┃口┃✨ * *˛•
┃口┃✨ 。* ✨ 。•˛˚˛*
┃口┃ •˛˚˛* 人 •˛˚ *
┃口┃ .-:'''"''"'':-. ✨
┃口┃ (_(_(_()_)_)_)
┃口┃_┃∩∩∩∩∩∩┃
┃口┃_┃∩∩∩∩∩∩┃
三_三三三三三

ለእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለኢድ አል አደሀ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

በዓሉ የደስታ የአንድነት የመተሳሰብና የመተዛዘን እንዲሆንልን ከልብ እንመኛለን!

መልካም በዓል ይሁንላችሁ!

ቴሌግራም ላይ ቤተሰብ ይሁኑ
https://t.me/felegethiopia

ኢንተር ሚላን ከፒ ኤስ ጂ ተጠባቂው የቻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜተጠባቂው የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ ምሽት 4 ሠአት በጀርመን ሙኒክ አሊያዝ አሬና ስታዲየም ይካሄዳል። ከፈረንጆቹ 199...
05/31/2025

ኢንተር ሚላን ከፒ ኤስ ጂ ተጠባቂው የቻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ

ተጠባቂው የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ ምሽት 4 ሠአት በጀርመን ሙኒክ አሊያዝ አሬና ስታዲየም ይካሄዳል። ከፈረንጆቹ 1993 በኋላ የጣሊያን እና የፈረንሳይ ክለቦችን በፍፃሜ የሚያገናኘው ጨዋታ ኢንተር ሚላንን ከፒ ኤስ ጂ ያፋጥጣል።

ሁለቱም ቡድኖች ወደ ፍፃሜ ባደረጉት ጉዞ ጠንካራ ቡድኖችን ያሸነፉ ሲሆን፥ ኢንተር ሚላን በሩብ ፍፃሜው ባየርን ሙኒክን እንዲሁም በግማሽ ፍፃሜው ባርሴሎናን በማሸነፍ ለሙኒኩ ፍፃሜ የደርሷል። ኢንተር ሚላን ባለ ትልቅ ጆሮውን ዋንጫ ከዚህ ቀደም ሦስት ጊዜ ያነሳ ሲሆን፥ በቅርብ ጊዜ ለፍፃሜ ደርሶ በማንቼስተር ሲቲ መሸነፉ አይዘነጋም።

ፒ ኤስ ጂ በበኩሉ በጥሎ ማለፉ ሊቨርፑልን፣ በሩብ ፍፃሜው አስቶንቪላን እንዲሁም በግማሽ ፍፃሜው አርሰናልን በማሸነፍ ለፍፃሜ መድረሱ ይታወሳል።ፒ ኤስ ጂ ይህን ውድድር አሳክቶ የማያውቅ ሲሆን፥ የክለቡ ባለቤቶችም ይህን ውድድር ማሸነፍ ዋነኛ አላማቸው መሆኑን ይገልጻሉ።

የምሽቱን ፍፃሜ ሮማኒያዊው አርቢትር ኢስትቫን ኮቫክስ በመሀል ዳኝነት የሚመሩት ሲሆን፥ ከዚህ ቀደም ሁለት ጊዜ የፈረንሳዩ ክለብ በቻምፒየንስ ሊጉ ያደረጋቸውን ጨዋታዎች መርተው ሁለቱንም ፒ ኤስ ጂ ማሸነፉ የሚታወስ ነው። በተመሳሳይ መልኩ ኢንተር ሚላን የተጫወተባቸውን ሦስት ጨዋታዎች በመሃል ዳኝነት መርተው በሁለቱ አሸንፎ በአንዱ አቻ ወጥቷል።

ሁለቱ ቡድኖች በነበራቸው የቅርብ ጊዜ የእርስ በእርስ ግንኙነት አምሥት ጊዜ ተጫውተው ፒ ኤስ ጂ 3 እንዲሁም ኢንተር ሚላን 2 ጊዜ አሸንፈዋል። በሊግ ውድድር ፒ ኤስ ጂ የፈረንሳይ ሻምፒዮን ሲሆን ኢንተር ሚላን በውድድሩ የመጨረሻ ሳምንታት በጣላቸው ነጥቦች በናፖሊ የስኩዴቶውን ዋንጫ መነጠቁ አይዘነጋም።

በምሽቱ ጨዋታ ሁለቱም ክለቦች በርካታ የጎል ዕድሎችን የሚያመክኑ ግብ ጠባቂዎች ባለቤት ሲሆን፥ የኢንተር ሚላኑ ያን ሶመር በርካታ ያለቀላቸውን ኳሶች በማዳን በዘንድሮው ውድድር ቀዳሚው ነው። የባቫሪያኑ ክለብ ባየር ሙኒክ ስታዲየም አሊያንዝ አሬና በቻምፒየንስ ሊጉ ሻምፒዮን ሆነው የማያውቁ አዳዲስ ክለቦች የሻምፒዮንነት ዘውድ የሚደፉበት ስታዲየም ሲሆን፥ ይህ የታሪክ አጋጣሚ ዛሬ ምሽት ፒ ኤስ ጂን ሻምፒዮን አድርጎ ታሪኩን ያስቀጥላል ወይስ ኢንተር ለአራተኛ ጊዜ ሻምፒዮን ይሆናል?።

ዛሬ ምሽት የሚደረገውን ተጠባቂውን የቻምፒየንስ ሊግ ፍጻሜ ጨዋታ በቀላሉ በCRICFy TV Premium app መመልከት ትችላላችሁ። አፑን በሊንኩ በኩል ቴሌግራም ላይ አስቀምጠነዋል አፕዴት የሆነውን መርጣችሁ መጠቀም ትችላላችሁ።
👇👇👇

https://t.me/felegethiopia/26005
https://t.me/felegethiopia/26005
https://t.me/felegethiopia/26005

እባባችሁ እናንተ ደጋግ ኢትዮጵያውያን ሼር አድርጉለት 🙏ቴዎድሮስ ካሳሁን ተክሌ :- ወገኖቼ እንዴት ናችሁ እንደሚታወቀው እኔ በፋና ላምሮት ዝግጅት ላይ ስስራ ብዙ ጊዜ የመንፈስ ጭንቀት ይይዘ...
05/28/2025

እባባችሁ እናንተ ደጋግ ኢትዮጵያውያን ሼር አድርጉለት 🙏

ቴዎድሮስ ካሳሁን ተክሌ :- ወገኖቼ እንዴት ናችሁ እንደሚታወቀው እኔ በፋና ላምሮት ዝግጅት ላይ ስስራ ብዙ ጊዜ የመንፈስ ጭንቀት ይይዘኝ ነበር።

ብዙ ጊዜ ፕሮግራሞችን እያቋረጥኩኝ እወጣም ነበር።

ከዛ በኃላ ከጊዜ ወደ ጊዜ ይተወኛል ስል እየባሰብኝ ሄዶ ራሴን ላይ እርምጃዎችን እንደውስድ ያገፋፋኝ ጀመረ።

ነገር ግን ራሴንም የምወዳቸውን ልጆቼንም ልኑርላቸው ብዬ ፀበል ቦታ ፀበል እየተጠመቁኝ እገኛለሁ።

ትንሽም ሻል ብሎኛል።

ነገር ግን እኔ አሁን ላይ ስራም እየሰራው ስላልሆነ

* ለልጆቼ የቤት ክራይ፣
* የትምህርት ቤት ክፍያ እና አንዳንድ ነገር ስለተቸገርኩኝ እንድትረዱኝ ወደ እናንተ መጣሁ።

ያላችሁን ትንሽም ትልቅም ሳትሉ እርዱኝ።
ችግር ላይ ነኝ።"

1000298227707
TEWODROS KASAHUN TEKLE

አመስግናለሁ !

FELEG ETHIOPIA

ውድ ወዳጆቼበግሌ መፍትሔ ለማግኘት  ብዙ አማራጮችን ስሞክር ቆይቻለሁ። ልክ የዛሬ 15 ቀን ፣ ሐሙስ ዕለት ሕመሜን አደባባይ አውጥቼ ድጋፍ ከጠየኩ በኋላ ያገኘሁት በብሔር፣ በኃይማኖት እና በ...
05/28/2025

ውድ ወዳጆቼ
በግሌ መፍትሔ ለማግኘት ብዙ አማራጮችን ስሞክር ቆይቻለሁ። ልክ የዛሬ 15 ቀን ፣ ሐሙስ ዕለት ሕመሜን አደባባይ አውጥቼ ድጋፍ ከጠየኩ በኋላ ያገኘሁት በብሔር፣ በኃይማኖት እና በአካባቢ ያልተገደበ ፍቅር ገና ሳልታከም ሕመሜን ያስታገሰ ሆኖ አግኝቸዋለሁ። የተለያዩ የድጋፍ ጥያቄዎች በበዙበት እና የኑሮ ውድነቱን መቋቋም በከበደበት በዚህ ወቅት ሰዎች እያሳዩኝ ያለው ፍቅር ለመሸከም የሚከብድ ነው። በ15 ቀናት ውስጥ ከሚያስፈልገኝ 50 በመቶ ድጋፍ አግኝቻለሁ።

“አንተን ሳናሳክም አንተኛም” የሚሉ ጓደኞች፣ የሥራ ባልደረቦች እና ቤተሰቦች ስለሰጠኝ እግዚያብሔርን አመሰግነዋለሁ። ታክሜ፣ በሕይወት ቆይቼ ሁሉንም ቆሜ ለማመስገን እንዲረዳኝ እፀልያለሁ። እናንተም ፀልዩልኝ። ቀዶ ሕክምናው ተደርጎ ዕጢው ከወጣ በሕይወት የመቆየት ዕድሌ ከፍተኛ መሆኑን ሐኪሞቹ ነግረውኛል። ቀሪው 50 በመቶ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሞልቶ መታከም እንደምችል እንደሚረባረቡልኝ ሁሉም ቃል ገብተውልኛል። ብዙዎች በየኃይማኖታቸው እንደሚፀልዩልኝ የእምነት ቃላቸውን ሰጥተውኛል። ያረፍኩበት ቦታ ድረስ እምነትና ጸበል ያመጡልኝም አሉ። አሁን ላይ የሚያስፈልገው የሕክምና ገንዘብ ተሟልቶ፣ በወገኖቼ ጸሎት ታግዤ ፈውስ ላገኝ እንደምችል ተስፋ አለኝ!

ያጋጠመኝን የጤና ችግር ለወዳጆቼ፣ ዘመዶቼ፣ የሥራ ባልደረቦቼ እና ጎረቤቶቼ ሳልናገር የሸሸኩት በግሌ መፍትሔ ለማግኘት በማሰብ ነበር። በተለይ ዕጢው በቀዶ ሕክምና መውጣት እንዳለበት ከተነገረኝ ካለፈው ዓመት በኋላ ያልሞከርኩት ነገር አልነበረም።

በተፈጥሮዬ ግራኝ ስኾን ፣ ዕጢው የሚገኝበት ቦታ ደግሞ የግራኞችን ሰውነት እንቅስቃሴ በሚቆጣጠረው በቀኝ አንጎሌ ክፍል ነው። ይኽ ሁኔታም የቀዶ ሕክምና አማራጩን አስጊና አስፈሪ አድርጎብኛል። ምከንያቱም ቀዶ ሕክምናው የንግግር ክህሎቴን ሊያሳጣኝ እንደሚችል ስለተነገረኝ ነበር።

በሀገር ውስጥ በቅዱስ ያሬድ፣ በተክለኃይማኖት፣ በላንሴት በጥቁር አንበሳና በጳውሎስ ሆስፒታሎች ሕክምና ተከታትያለሁ። ተደጋጋሚ የMRI እና ሌሎች ምርመራዎችን አካሂጃለሁ። ጣሊያን ውስጥ በዚህ ሕክምና የተሳካ ውጤት አምጥተዋል የተባሉ ሐኪም ለሚገኙበት ሆስፒታል ተገቢው ክፍያ በመፈፀም የሕክምና ማስረጃዎቼን ልኬ ከባለሞያዎቹ ጋራ ሰፊ የቪዲዮ ውይይቶችን አድርጌያለሁ፡፡ በቅርቡም የMRI ውጤቴን አስቀድሜ ልኬ ወደአሚን አጠቃላይ ሆስፒታል በመጡ ቱርካዊ ኒውሮሰርጀን ምርመራ ተደርጎልኛል። በቪዲዮ ኮንፈረንስ የህንዳዊ ኒውሮሰርጀን ምክርም አግኝቻለሁ።

ብዙዎቹ እኔ ላለሁበት ሁኔታ ራሴን ሳልስት የሚካሄድ ቀዶ ሕክምና የተሻለ አማራጭ እንደሆነ ነግረውኛል። ሕክምናው በሀገር ውስጥ ያለ ቢሆንም በቀዶ ህክምናው ወቅት የspeech capability ክትትሉ ከማሽን ውጪ የሚካሄድ በመኾኑ ፍርሃቴ ከፍተኛ ኾነ። በዚህም የተለያዩ ሀገራትን አማራጮች ሳስስ ነበር። የጣልያኑ ሆስፒታል የተሻለ ሆኖ ያገኘሁት በቀዶ ህክምናው ወቅት በንግግር ችሎታዬ ላይም ሆነ በእጅና እግር እንቅስቃሴዬ ላይ እክል ቢፈጠር ወዲያውኑ የሚያሳውቅ ቴክኖሎጂ ያላቸው መሆኑና ዋጋቸውም ተመጣጣኝ በመሆኑ ነበር። ባለፉት ሁለት ዓመታት፣ የአንጎል ዕጢው ባስከተለብኝ ከፍተኛ ተጽእኖ ምክንያት የሥራ እንቅስቃሴዬ የተገደበ በመሆኑ፣ በአግባቡ አልሠራሁም። ጥሪቴም ተመናመነ፣ ያሰብኳቸውና የሞከርኳቸው ሌሎች አማራጮችም አልሳካ አሉ። በዚህም ምክኒያት ነበር የዛሬ ዓመት አይሆንም ብዬ የገፋሁትን ሌሎችን የማስቸገር መፍትሔ አሁን የተቀበልኩት። በዚህ ሁለት ሳምንት ያገኘሁትን ፍቅር፣ የተላከልኝን መልዕክት እና የተደወሉ ስልኮችን ብዛት ሳይ ግን ለድጋፉ ብቻ ሳይሆን የሰውን ፍቅር እንዳይበት እንኳን የድጋፍ ጥሪ ጥያቄን አቀረብኩ እንድል አደረገኝ።
አሁን ከእግዚያብሔር ጋራ ተስፋ ይታየኛል። ተስፋዬ እውን እንደሚሆን ደግሞ እምነት አለኝ። በሁለት ሳምንት ውስጥ በተስፋ እንድጠነክር ላደረጋችሁኝ ሁሉ እግዚያብሔር በሚያስፈልጋችሁ ይድረስላችሁ። Addis Chekol

➤GoFundme (ጎ ፈንድ ሚ)፡- https://shorturl.at/YHOSA
አዲስ ቸኮል አለነ
➤የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፡- 1000061095989
➤ዳሽን ባንክ:- 5009778150021
➤አቢሲኒያ:- 225994951
➤አዋሽ:- 013200542570900

Let’s Help Save the Life of Journalist Addis Chekol ! Addis Cheko… Selamawit Telahun needs your support for Save Addis Chekol: Urgent Brain Surgery Needed

20 ዓመታት ኮማ ውስጥ !ልዑል አል-ዋሊድ ቢን ካሊድ ቢን ታላል ከሳዑዲ ንጉሳውያን ቤተሰቦች የተገኘናየዘር ሐረጉ ከሳዑዲ መስራች ንጉስ አብዱላዚዝ የሚመዘዝ ነው። ልዑሉ በፈረንጆቹ 2005 በ...
05/28/2025

20 ዓመታት ኮማ ውስጥ !

ልዑል አል-ዋሊድ ቢን ካሊድ ቢን ታላል ከሳዑዲ ንጉሳውያን ቤተሰቦች የተገኘናየዘር ሐረጉ ከሳዑዲ መስራች ንጉስ አብዱላዚዝ የሚመዘዝ ነው። ልዑሉ በፈረንጆቹ 2005 በደረሰበት የመኪና አደጋ ሳቢያ ያለፉትን 20 ዓመታት በኮማ ውስጥ ይገኛል።

አደጋው በእንግሊዝ ለንደን በወታደራዊ ኮሌጅ ትምህርቱን ለመከታተል ባቀናበት ወቅት የደረሰበት ሲሆን፥ ከባድና ውስብስብ የጭንቅላት አደጋ ነው። አደጋው ከደረሰበት ጊዜ ጀምሮ ኮማ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን፥ “በእንቅልፍ ውስጥ ያለው ልዑል” የሚል መጠሪያም ተሰጥቶታል።

የህክምና ባለሙያዎች አደጋው ከባድ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ‘ህይወቱን እናቋርጠው’ የሚል ጥያቄ ቢያቀርቡም ቤተሰቦቹ ግንበፈጣሪ ተስፋ አለን አንድ ቀን ይነቃል በሚል ሃሳቡን ተቃውመው የህክምና ክትትሉ ቀጥሏል። ወላጅ አባቱ ልዑል ካሊድ “በፈጣሪ ተስፋ አልቆርጥም ፤ የዓለም ህዝብም ጸሎት ያድርግልኝ” ብለዋል።

ቴሌግራም ላይ ቤተሰብ ይሁኑ
https://t.me/felegethiopia/



ማንቼስተር ዩናይትድ እና ቶተንሃም ሆትስፐርን ያገናኘው ተጠባቂው ዛሬ ምሽት የሚደረገውን የዩሮፓ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ ምሽት 4 ሠአት ላይ በስልኮ ይመልከቱ አፑን በሊንኩ በኩል አስቀምጠነዋል አ...
05/21/2025

ማንቼስተር ዩናይትድ እና ቶተንሃም ሆትስፐርን ያገናኘው ተጠባቂው ዛሬ ምሽት የሚደረገውን የዩሮፓ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ ምሽት 4 ሠአት ላይ በስልኮ ይመልከቱ አፑን በሊንኩ በኩል አስቀምጠነዋል አፕዴት የሆነውን መርጣችሁ መጠቀም ትችላላችሁ።
👇👇👇
https://t.me/felegsports/763
https://t.me/felegsports/764
https://t.me/felegsports/763


ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ በማሰባሰብ ተጠናቀቀ፡፡ከየካቲት 01 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በሰይፉ በኢቢኤስ እና በሰይፉ ሾው ዩቲዩብ ቻናል ላይ እየተደረገ በቆየው የቀጥታ ስርጭት የገቢ ማሰባሰብያ...
05/18/2025

ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ በማሰባሰብ ተጠናቀቀ፡፡

ከየካቲት 01 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በሰይፉ በኢቢኤስ እና በሰይፉ ሾው ዩቲዩብ ቻናል ላይ እየተደረገ በቆየው የቀጥታ ስርጭት የገቢ ማሰባሰብያ መርሃ ግብር ላይ የመጀመሪያው ዙር የገቢ ማሰባሰብ የቀጥታ ስርጭት ግቡን በማሳካት ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ በማሰባሰብ በይፋ ተጠናቀቀ፡፡

መቄዶንያ የአረጋዊያን እና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በአዲስ አበባ እያስገነባ ለሚገኘው የአረጋውያን መኖሪያና ዘመናዊ ሆስፒታል አጠቃላይ የፊኒሺንግ ስራውን ለማጠናቀቅ 5 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ በመግለፅ ከየካቲት 01 ቀን 2017 ጀምሮ የመጀመሪያ ዙር የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት 1 ቢሊየን ብር ለማሰባሰብ ዕቅድ በመያዝ በseifu on ebs እና በ Seifu Show ዩቱብ ቻናል ላይ በመጀመር ላለፉት ሶስት ወራት (90 ቀናት) በቆየው ገቢ ማሰባሰብ ፕሮግራም ላይ የታሰበውን እቅድ በማሳካት አጠቃላይ በገንዘብ እና በአይነት ከ 1 ቢሊየን ብር በላይ በማሰባሰብ በሰይፉ ዩቱዩብ ቻናል የተደረገው የመጀመሪያ ዙር የገቢ ማሰባሰብ ግንቦት 01 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ ተጠናቋል፡፡

ይህ የገቢ ማሰባሰብ ፕሮግራም የተካሄደበት Seifu on EBS እና Seifu Show ዩቱዩብ ቻናል በቀጥታ ስርጭትና በማስታወቂያ ገቢ የተገኘ ብር 4,032,585.63 ለመቄዶኒያ ገቢ የተደረገ ሲሆን በመዝጊያ ስነ ስርዓት ላይ የተገኙት የመቄዶንያ የአረጋዊያን እና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል መስራች የክብር ዶክተር ቢኒያም በለጠ ላለፉት ሶስት ወራት ሲደረግ በቆየው ዝግጅት ላይ የተሳተፉትን በሙሉ በማመስገን ለዚህ ዝግጅት ዋናውን ሚና ሃላፊነት በመውሰድ የ1 ቢሊየን ብር ግብ እንዲሳካ ላደረገው ለሰይፉ ፋንታሁን ምስጋና በማቅረብ የምስጋና የምስክር ወረቀት የተበረከተ ሲሆን እንዲሁም በመቄዶኒያ በሚገኙ ተረጂዎች በእጅ ጥበብ የተሰራ ጋቢ ለሰይፉ ፋንታሁን እና ለአርቲስት ይገረም ደጀኔ ያለበሱ ሲሆን በአረጋውያኑ ምርቃት በመታጀብም በሰይፉ ፋንታሁን ምስል የተቀረፀ ምስለ ቅርፅ በስጦታ አበርክተዋል፡፡

በዚህ በሰይፉ በኢቢኤስ እና በሰይፉ ሾው ዩቲዩብ ቻናል በቀጥታ ስርጭት ላለፉት ሶስት ወራት በዘለቀው እና ለተመካቾች በደረሰ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀ ግብር ፣ ከተለያዩ የሀይማኖት ተቋማት የመጡ መምህራን፣ የኪነ ጥበብ ሰዎች ፤ የተለያዩ የመንግስት እና የግል ተቋማት ፤ ባንኮች እና የሚዲያ ባለሞያዎች መድረኩን በማድመቅ ልግስና በመስጠት እና ለጋሾችን በማበረታታት አብረውን ቆይተዋል። አሁንም በመቄዶንያ ዩቱዩብ ቻናል የቀጥታ ስርጭት የገቢ ማሰባሰቢያ እንደቀጠለ ነው።

ላለፉት ሶስት ወራት አብራችሁን ስለነበራችሁ ብርታት እና ልግስናችሁ ስላልተለየን እናመሰግናለን !

ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራም ላይ ቤተሰብ ይሁኑ https://t.me/felegethiopia/

05/18/2025

በወሎ አካባቢ ታዋቂ የነበረው ማሲንቆ ተጫዋች እንድሪስ ሃርቡ ከዚህ አለም በሞት ተለዬ።

እንድሪስ ሃርቡ ባደረበት ህመም ምክንያት ህክምና ሲከታተል ቆይቶ ግንቦት 9/2017 ዓ.ም ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል።

እንድሪስ ሃርቡ ከልጅነት እድሜው ጀምሮ በተለይ በወሎ አካባቢ በማሲንቆ ጨዋታው ይታወቃል።የበርካቶችን ሰርግ ሲያደምቅ ሰዎችን ሲያዝናና የኖረ ነበር። በ4ቱም ቅኝቶች የሚጫዎታቸው ዜማዎቹ ከሌሎች ተጨዋቾች በተለየ ታዋቂ አድርጎት ነበር ። ለቤተሰቡ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹና ለአድናቂዎቹ መፅናናትን እንመኛለን።(ኮምቦልቻ ኮሙኒኬሽን)

ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራም ላይ ቤተሰብ ይሁኑ https://t.me/felegethiopia/

Address

Atlanta, GA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Info Center posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Info Center:

Share