Click Dessie

Click Dessie Make Wollo Great Again

ቢሊዬ❤ ከረጅም ጊዜ በኋላ ዛሬ አየሁሽአሁን ምን ማለት እንዳለብኝ ባላውቅም በዚች ቅጽበት የሚሰማኝን ስሜት ግን መናገር እፈልጋለሁ። ገና በመጀመሪያ እንዳየሁሽ ልቤ ስንጥቅ ሲል የነበረኝን ስ...
08/21/2023

ቢሊዬ❤ ከረጅም ጊዜ በኋላ ዛሬ አየሁሽ
አሁን ምን ማለት እንዳለብኝ ባላውቅም በዚች ቅጽበት የሚሰማኝን ስሜት ግን መናገር እፈልጋለሁ። ገና በመጀመሪያ እንዳየሁሽ ልቤ ስንጥቅ ሲል የነበረኝን ስሜት መቼም በሕይወት እያለሁ አልረሳውም። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ የምታደርጊውንና የምትናገሪውን በሙሉ በስስት እከተላለሁ አዳምጣለሁ። ምንም እንኳን ለአንቺ ያለኝን ስሜት ለመግለፅ ትክክለኛ ቦታ ባላገኝም አንቺን ባሰብኩ ጊዜ የሚሰማኝ ስሜት ልዩ በመሆኑ በተደጋጋሚ አስብሻለሁ፤ በቃ ደስ ይለኛላ። ቢሊ 😍 በሁሉም ነገሮችሽ እንደማፈቅርሽ ግን እንደዚህ በአደባባይ ላሳውቅሺ እፈልጋለሁ።

07/22/2023

lmkkl

06/07/2023

በዘመነ ካሴ ላይ የተፈጸመውን ተደጋጋሚ “የአጋንንት ጥቃት” ማክሸፉን የጎጃም ፀረ-ድግምት ብርጌድ አስታወቀ 😂

Getnet Almaw Tiruneh - ጌትነት አልማው ጥሩነህ

የጠላት ወገን በዘመነ ካሴ ላይ በተደጋጋሚ የሰነዘረውን የአጋንንት ጥቃት በአስተማማኝ ሁኔታ ማክሸፉን የጎጃም ፀረ-ድግምት ብርጌድ (ጎፀድ) አስታውቋል !!

የብርጌዱ አዛዥና የአለም ፀረ-ድግምት የበላይ አዛዥ አቶ ደምለው ቅደድ ከጎጃም ጎረቤት ለተውጣጡና #ዋጃጋንት የሚገኘውን የጎጃም ፀረ-ድግምት (ጎፀድ) በመጎብኘት ላይ ለሚገኙ ከፍተኛ የድግምት ባለሙያዎች በዛሬው ቀን እንደገለጹት ብርጌዱ በዘመነ ካሴ ላይ በተደጋጋሚ የተቃጣውን የአጋንንት ጥቃት በአስተማማኝ ብቃት ማክሸፉን ገልጸው በአሁኑ ሰዓት ብርጌዱ “በአንደርብ መምታት፣ ጥላ ወጊ፣ በድግምት ማፍዘዝ፣ የጠላትን ልብ ማራራት” በሚል የተለዩ አራት የሚሆኑ ፕሮጀክቶችን ከፍተኛ ሃብትና ባለሙያ መድቦ እያበለጸገ መሆኑን ገልጸዋል... 😂

የጎጃም ፀረ-ድግምት ብርጌድ የበላይ አዛዥ የሆኑት አቶ ደምለው ቅደድ ከጎጃም ጎረቤት ለተውጣጡና ማዕከሉን በመጎብኘት ላይ ለሚገኙ ከፍተኛ የድግምት ባለሙያዎች “ጎረቤት ክፍለ ሃገራት መሰል ፀረ-ድግምት ማዕከላት ሲያደራጁ የማዕከሉ ድጋፍ እንደማይለያቸው” ገልጸው ማዕከሉ በአሁኑ ሰዓት ከኢራን፣ ሶሪያ፣ የመን፣ ራሽያና ቱርክ ጋር በጋራ ለመስራት ውል ማሰሩን ገልጸውላቸዋል..



አሳፍራችሁን ያልሞትነውን ሰዎች እንዲህ በሳቅ ግደሉን እንጂ !... 😂...😂...😂

ደሴ ውስጥ ብቻ ከ100 ሚሊየን ብር በላይ የዘረፈው የወያኔ አርሚ 31  ገመና በአንድ አባሉ ሲጋለጥ ......👉-ዘረፋው ከከፍተኛ አመራሮች የተላለፈ ትዕዛዝ መሆኑን የአርሚው አዛዦች ሲያብራ...
05/15/2023

ደሴ ውስጥ ብቻ ከ100 ሚሊየን ብር በላይ የዘረፈው የወያኔ አርሚ 31 ገመና በአንድ አባሉ ሲጋለጥ ......

👉-ዘረፋው ከከፍተኛ አመራሮች የተላለፈ ትዕዛዝ መሆኑን የአርሚው አዛዦች ሲያብራሩ
"አርሚ 31 ከባንኮች የተገኘውን ብር በሙሉ ሰብስቦ ለትግራይ መንግስት እንዲያስረክብ ተልዕኮ ተሰጥቶታል" አሉ።
👉- ከዛ በኋላ ዘረፋውን የሚያስፈፅሙ የሰራዊቱ አባላት ተመለመሉ
-በሌ/ኮ ገ/ስላሴ ገ/መድህን ከሚመራው የአርሚው የመሃንዲስ አባላት
እና ...
-በሌ/ኮ ጨርቆስ ከሚመራው የአርሚው የስለላ አባላት ሰዎች ተመለመሉ። ስራውን ከህዝብ ዕይታ ውጪ ሆኖና ምስጢራዊነቱ በተጠበቀ ሁኔታ እንዲፈፀምም ትዕዛዝ ተሰጣቸው ።

👉- እነዚህ የጦሩ አባላት ከምሽቱ 1 ሰዓት ጀምሮ ጄኔሬተሮችንና ግራይንደሮችን ተሸክመው ይሰማራሉ።ካዝናዎችን ሲሰብሩ ያድራሉ ።
👉 -ካዝናዎችን እየሰበሩ የሰበሰቡትን ብር በመኪና እየጫኑ ኮ/ል ገ/ብረስላሴ ይዞት ወደነበረው ቤት ( መጠለያ ) ይወስዱታል።
👉የፋይናንስ ሃላፊው ገብረሃንስ ጧት ጧት ወደ ቤቱ እየመጣ ብሩን ይቆጥራል
👉 በመጨረሻም ስራው ሲጠናቀቅ በዘረፋው የተሳተፉት ለያንዳንዳቸው 7 ሺ ብር ተሰጥቷቸዋል።
👉- በዘረፋ የተሰበሰበው ከ100 ሚሊየን ብር በላይ በኩንታሎች እየተሞላ ወደ መቀሌ ተወሰደ።
ኮ/ል ገ/ስላሴ ፣የፋይናንስ ሃላፊው ገብረዮሃንስ እና የኮ/ል ገ/ስላሴ መጋቢ የነበረችው ዳናይት አብረው ወደ መቀሌ የተጓዙት ሰዎች ናቸው።
👉 ብሩ መቀሌ ውስጥ ላጪ በተባለው ሰፈር ካለው የገብረዮሃንስ ቤት ውስጥ ተራገፈ።

በዚህ ዘረፋ ላይ የተሳተፉ ከፍተኛ የአርሚው አመራሮች
1-ብ/ጄነራል ዘነበ ክፍሉ- የአርሚ 31 አዛዥ
2-ገዛኸኝ - የአርሚው ኮሚሳር (አሁን የትግራይ ፖሊስ ም/ኮሚሽነር ሆኗል )
3-ኮ/ል ፍሰሃ ፅዮን - የአርሚው ሎጂስቲክስ
4- ሌ/ኮ ገብረስላሴ ገብረመድህን - የአርሚው የመሃንዲስ ሃላፊ
5- ሌ/ኮ ጨርቆስ - የስለላ ሃላፊ
6-ገብረዮሃንስ - የፋይናንስ ሃላፊ
Asfaw Abreha

በነገራችን ላይ የኦሮሚያ ሙስሊሞች በኦሮሞ ፖለቲካ ላይ ካላቸው ውክልና ይልቅ የአማራ ክልል ሙስሊሞች በአማራ ፖለቲካ ውስጥ ያላቸው ውክልና ይበልጣል ። ይሄ በማስረጃ ሊረጋገጥ የሚችል ሀቅ ነ...
05/05/2023

በነገራችን ላይ የኦሮሚያ ሙስሊሞች በኦሮሞ ፖለቲካ ላይ ካላቸው ውክልና ይልቅ የአማራ ክልል ሙስሊሞች በአማራ ፖለቲካ ውስጥ ያላቸው ውክልና ይበልጣል ። ይሄ በማስረጃ ሊረጋገጥ የሚችል ሀቅ ነው ።

የኦሮሚያ ሙስሊሞች በአሁኑ ሰአት በኦሮሚያም ሆነ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ያላቸው ተሳትፎና ውክልና ከትግራይና ከጋምቤላ ቀጥሎ እጅግ ዝቅተኛው ነው ። በኦሮሚያ ብልፅግና ውስጥ ያላቸው ድርሻም ከሌላው ብልፅግና በጣም ያነሰ ነው ። በተቃዋሚው ፖለቲካ ዘርፍም ያላቸው እንቅስቃሴ ደካማ ነው ። ከጀዋር ሙሀመድ በሗላ በኦሮሚያ ውስጥ ተፅእኖ መፍጠር የሚያስችል ሙስሊም ፖለቲከኛና የፖለቲካ አመራር አለ ማለት ያስቸግራል ። ይህ ሁሉ የሚሆነው ከኦሮሚያ ክልል ህዝብ ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆነው ሙስሊሙ ሆኖ ሳለ ነው ።

የኦሮሚያ ሙስሊሞች በክልሉ ስራ አስፈፃሚ ውስጥ ያላቸው ድርሻ 20% እንኳ አይሆንም ።

በአንፃሩ የሙስሊሙ ቁጥር ከክርስቲያኑ አንፃር አናሳ የሆነበትን የአማራ ክልል ፖለቲካን ብናይ ሙስሊሞች በገዥውም ይሁን በተቃዋሚ ፓርቲ ውስጥ ጠንካራ ተሳትፎ አላቸው ። የአማራ ብልፅግና መሪው ሙስሊሙ ደመቀ መኮንን ጨምሮ በርካታ ፖለቲከኞች አሉ ።
አብንን እንኳ ብንመለከት በፓርቲው አመራር ደረጃ ጠንካራ ሙስሊሞች ያሉበት ፓርቲ ነው ።

የኦሮሚያ ክልል ግን ሙስሊሞችን እየሸነገለ ከፖለቲካ ተሳትፎ እያራቃቸው ይገኛል ። የሀረርጌ ፤ የባሌ ፤ የአርሲ ፤ የጅማ ፤ የቦረና ፤ የጉጂ ኦሮሞዎች ያላቸው የፖለቲካ ተሳትፎ እጅግ አናሳ ነው ። በተቃራኒው የኦሮሚያን ፖለቲካ በወለጋና በሸዋዎች ይዘወራል ። እነዚህ ደግሞ ሙስሊም ጠል ፖለቲከኞች የሚፈሩበት ቦታ ነው ።

ለኦሮሚያ ፕሮቴስታንት እና ዋቄፈታ የፖለቲካ መሪዎች ሙስሊሙ ኦሮሞ ከእምነቱ ይልቅ የብሔር ማንነቱ ላይ የበለጠ ትኩረት ማድረጉን እንደ ትልቅ አጋጣሚ በመውሰድ እየተጠቀሙት ይገኛሉ ።

ለሌሎች አናሳ ሙስሊሞች ጠበቃና ሚዛን መሆነ የነበረበት ሰፊው የኦሮሞ ሙስሊም ማህበረሰብ የክልሉን ፖለቲካ እንኳ መዘወር አቅቶት በኢስላም ጠል ፖለቲከኞች መገዛቱ የሚጎረብጥ ሀቅ ነው ።



ቴሌግራም
👉 t.me/Seidsocial

የከተማችን ማህበረሰብ ለፀጥታ ሀይሉ የሚሰጡትን መረጃ እና ጥቆማ ከዚህ በበለጠ ማጠናከር ይኖርበናል ሲል የደሴ ከተማ አሰተዳደር ፖሊሰ መምሪያ ማህብረሰብ አቀፍ የፖሊሰ አገልግሎት ዋ /ክፍል ...
05/05/2023

የከተማችን ማህበረሰብ ለፀጥታ ሀይሉ የሚሰጡትን መረጃ እና ጥቆማ ከዚህ በበለጠ ማጠናከር ይኖርበናል ሲል የደሴ ከተማ አሰተዳደር ፖሊሰ መምሪያ ማህብረሰብ አቀፍ የፖሊሰ አገልግሎት ዋ /ክፍል ገለፀ።

የደሴ ከተማ አሰተዳደር ፖሊሰ መምሪያ ማህብረሰብ አቀፍ የፖሊሰ አገልግሎት ዋ/ክፍል ሃላፊ ኮማንደር አበባዉ አሻግሬ እንደተናገሩ የከተማዋንዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ከምንጊዜውም በላይ በተለየ ትኩረት በመያዝ በየደረጃው ያለውን ማህብረሰብ በማሳተፍ እንደ አካባቢያችን ተጨባጭ ሁኔታ ህገወጥ ተግባራት የሚፈፅሙትን ግለሰቦች በመለየትና ከህዝብ በመነጠል የማህብረሰቡን ሰላም ማረጋግጥ ይኖርበናል።
የከተማችን ሰላም ለማሰጠበቅ ማህበረሰብ ለፀጥታ ሀይሎ መረጃ በመሠጠት ሰላማችንን መጠበቅ ይኖርበናል።

በከተማች ወሰጥ በዚህ ሳምንት የተለያዩ የፀጥታ ሀይሎች ሚሊትሪ (አልባሳት) በመለበሰ ሰዎችን የሚያሰፈራሩ እና የሚያጭበረብሩ እንዳሉ በወሠጥ መሰመር ጥቆማ እየደረሰን ነዉ ።ሰልዚህም እንደዚህ አይነት ዉንጀልኞችን ለመያዝ እና ለመቆጣጠር የፀጥታ ሀይሉ ከወትሮዉ በተለየ መልኩ የ24ሰአት እሰታደ ባይ በመሆን እየሰራ እና እየተከታትል ነዉ። ማህበረሰብም በአካባቢዎ ይህንን አይነት ተግባር የሚፈፀም ካጋጠምዎት ወዲያዉኑ ለፀጥታ ሀይሉ ጥቆማ ማደርግ አልብዎት።

አሁንም ሰላም ወዳዱ ማህበረሰብ የፀጥታ ሀይሉ ደጋፍ እና ደጀንነቱን እያረጋገጠና እየደገፈ የከተማችንሰላምን ሰላም ለማስጠበቅ እየሰራ ነው፣ ይሰራልም። ማህበረሰቡ ትክክለኛ መረጃዎችንም ለፀጥታ አካሎቻችን ማድረሱን እንዲቀጥል ሲል ጥሪ አቀርቧል።

👉የተለያዩ መረጃዎችን መሰጠት ካሰፈልገዎት!!!
በደሴ ከተማ አሰተዳደር ፖሊሰ መምሪያ እና በ5ቱ ዋና ፖሊሰ ጣቢያ የመረጃ ሰልክ ቁጥሮች
1ኛ ፖሊሰ ጣቢያ ፦033 111 1107
የጣቢያ ሃላፊ ፦ 0920132011
2ኛ ፖሊሰ ጣቢያ ፦ 033 111 1601
የጣቢያ ሃላፊ ፦ 0914071024
3ኛ ፖሊሰ ጣቢያ፦ 033 111 1011
የጣቢያ ሃላፊ፦ 0914713766
4ኛ ፖሊሰ ጣቢያ፦ 033 111 5119
የጣቢያ ሃላፊ፦ 0910441992
5ኛ ፖሊሰ ጣቢያ፦033 312 3669
የጣቢያ ሃላፊ ፦ 0914600053
የፖሊሰ መምሪያወ ፦ 033 111 77 48
የመምሪያ ሃላፊ ፦ 0902209702
የዞን ማህ/አቀ/የፖሊሰ አገልግሎት ዋ/ክፍል ሃላፊ፦0912955818 ደዉልዉ መረጃ መሰጠት ይችላሉ።
ወንጀልን በጋራ እንከላከል!!!!

The Most Beautiful View Of  27 መድኋኒዓለም | ደሴ መድሀኒዓለም እና አካባቢውመልካም ቀን🥰 AHS Production
05/05/2023

The Most Beautiful View Of
27 መድኋኒዓለም | ደሴ መድሀኒዓለም እና አካባቢው
መልካም ቀን🥰 AHS Production

ወንድሞቻቸውን እንጂ "ጠላቴ" የሚሉትን ዋና ሃይል  ሲገድሉ ቀርቶ ሲያቆስሉ አይተን አናውቅም።  እራስን ማጥፋትና ማዋረድ የአማራ ህዝብ ታሪክና ማንነት እስኪመስል ድረስ ከትናንት እስከ ዛሬ ...
04/27/2023

ወንድሞቻቸውን እንጂ "ጠላቴ" የሚሉትን ዋና ሃይል ሲገድሉ ቀርቶ ሲያቆስሉ አይተን አናውቅም። እራስን ማጥፋትና ማዋረድ የአማራ ህዝብ ታሪክና ማንነት እስኪመስል ድረስ ከትናንት እስከ ዛሬ ድረስ ቤታቸውን በደም በማግማት ላይ ናቸው።

አቶ ግርማ ነብስህ በሰላም ትረፍ።

Address

California City, CA

Telephone

+12062587281

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Click Dessie posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share