Bbc Agew

Bbc Agew የአገው ህዝብ አፍ፣አይንና ጆሮ

ኢትዮጵያ በ5 ቢሊየን ፓውንድ "ሜጋ ኤርፖርት ሲቲ" በመገንባት ላይ ትገኛለች። ተጠናቆ ስራ ሲጀምርም በአፍሪካ ግዙፉና በአለም ካሉ እጅግ ቢዚ ኤርፖርቶች አንዱ ይሆናል። ከአዲስ አበባ በ25 ...
12/01/2024

ኢትዮጵያ በ5 ቢሊየን ፓውንድ "ሜጋ ኤርፖርት ሲቲ" በመገንባት ላይ ትገኛለች። ተጠናቆ ስራ ሲጀምርም በአፍሪካ ግዙፉና በአለም ካሉ እጅግ ቢዚ ኤርፖርቶች አንዱ ይሆናል።

ከአዲስ አበባ በ25 ማይል ርቀት ላይ በቢሾፍቱ አቅራቢያ የሚገነባው አዲሱ ኤርፖርት በ2029 ሲጠናቀቅ በአመት እስከ 110 ሚሊዮን መንገደኞችን ያስተናግዳል። ተርሚናል እና አራት ማኮብኮቢያ/ማረፊያ ራንዌዮች ይኖሩታል።

ከባህር ጠለል በላይ 2,334 ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው የአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ ኢትዮጵያ የዓለም አቀፋዊ የአቪዬሽን ማዕከልነቷን እያረጋገጠ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ መጨናነቅ ገጥሞታል።

የሚገነባው "የሜጋ ኤርፖርት ከተማ" ይህን ችግር ከማቃለል ባለፈ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ያሳድጋል፣ ሀገሪቱን በአለም አቀፍ ንግድና ቱሪዝም ዋና ተዋናይነት ያስቀምጣል። አዲሱ ተቋም እንደ ዱባይ እና ሄትሮው ያሉ አለምአቀፍ አየር ማረፊያዎችን ለመወዳደር ያለመ ነው።

በአዊ ብሄ/አስ በህገወጥ መንገድ ነዳጅ የሚያሸሹ፤ ነዳጅ እያለ የለም ብለው የሚዘጉ ማደያዎች የነዳጅ አቅርቦት ስጋት መሆናቸው  ተገለፀ።የአዊ ብሄ/አስ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ በበኩሉ በ...
11/30/2024

በአዊ ብሄ/አስ በህገወጥ መንገድ ነዳጅ የሚያሸሹ፤ ነዳጅ እያለ የለም ብለው የሚዘጉ ማደያዎች የነዳጅ አቅርቦት ስጋት መሆናቸው ተገለፀ።

የአዊ ብሄ/አስ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ በበኩሉ በዘርፉ የሚስተዋለው ህገወጥነት ለማስተካከል እየሰራሁ ነኝ ብሏል።

ከቅርብ አመታት ወዲህ በሀገራችን የነዳጅ አቅርቦቱ ከአለም አቀፍ ሁኔታው ጋር በተያያዘ እጥረት ማጋጠሙ ይታወቃል።

ይህንን አለም አቀፍ ሁኔታውንና የሀገሪቱን ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት በማድረግ ደግሞ ለጥረቱና ለዋጋ ንረቱ እንዲባባስ በር ከፍቷል።

በተለይም በማደያዎች ተሸከርካሪ፣ የነዳጅ መያዣ ጀሪካኖችና የበርሜሮች ረጃጅም ሰልፎችን ማየት የዕለት ተዕለት ክስተት ሆኗል።

ነገር ግን አለም አቀፍ ሁኔታውና መሬት ላይ ያለው የነዳጅ አቅርቦትና ሽያጭ እውነታ ምን ይመስላል ብለን በአዊ ብሄ/አስ በሚገኙ ማደያዎች እንዲሁም በንግድና ትራንስፖርት ዘርፉና የሚመለከታቸውን አካላት ለመዳሰስ ሞክረናል።

በእንጅባራ ከተማ የባጃጅና የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ተጠቃሚዎች በሰጡት አስተያየት በነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ምክንያት ከትርፍ በላይ እንደሚጭኑ እና ከታሪፍ በላይ እንደሚያስከፍሉ የተናገሩ ሲሆን አሁን ላይ በተለይም የባጃጅ ክፍያ በእጥፍ እንደጨመረ ቅሬታቸውን አቅረበዋል ።

"በትራንስፖርት ዘርፉ ህግ ይከበርልን " የሚሉት ነዋሪዎቹ መንግስት ለዚህ ዘርፍ ትኩረት በመስጠት የማስተካከል ስራ እንዲሰራም በአፅንኦት ጠይቀዋል።

በእንጅባራ ከተማ ያነጋገርናቸው የተሽከርካሪ ሹፌሮች በበኩላቸው አሁን አሁን እየተለመደ የመጣው በህገወጥ መንገድ ነዳጅ የሚያሸሹ፤ ነዳጅ እያለ የለም ብለው የሚዘጉ ማደያዎች የነዳጅ አቅርቦት ስጋት ሁነዋል።"በዚህም ምክንያት በተተመነው የነዳጅ ዋጋ ሳይሆን ከፍተኛ ጭማሪ ባለው (በጥቁር ገበያ ) እንድንገዛ እንገደዳለን" ነው ያሉት።በትራንስፖርት እንቅስቃሴ ላይም የራሱ የሆነ አሉታዊ ተፅዕኖ ከማሳረፉ በተጨማሪ ነዳጅ ወደ ጥቁር ገበያ በሚዘዋወርበት ወቅት ለተሸከርካሪው ጤንነት ላይ ጉዳት እንደሚያደርስም ነው ያረጋገጡት ።

የአዊ ብሄ/አስ ንግድ መምሪያ ሀላፊ አቶ ያረጋል ያየህ ፥ በብሄረሰቡ አስተዳደሩ 33 የሚሆኑ ማደያዎች እንዳሉ ተናግረዋል ። የሚስተዋለውን የነዳጅ ስርጭት ችግር ከማደያ ባለቤቶች ጋር በመነጋገር ለመፍታት ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል።እንደ ሀላፊው ገለፃ በብሄረሰብ አስተዳደሩ የቤንዚን እንጂ የናፍጣ እጥረት እንደሌለም አረጋግጠዋል ።ይሁን እንጂ በቁጥጥር ማነስ በየወረዳዎችና በከተሞች የነዳጅ ርክክብ ችግር በንግድ ተቋሙ ዘንድ መኖሩን እንደ ምክንያት አንስተዋል።

እንደ ሀላፊው ገለፃ ተቋሙ በቅረቡ ጥናት አድርጊያለሁ ባላቸው ማደያዎች የከፋ ችግር እንዳላጋጠመ እና አልፎ አልፎ ህገወጥነት የሚስተዋል መሆኑን ጠቁመዋል።የፀጥታው ችግር ለዚህ ዘርፍ አባባሽ ምክንያቶች እንደሆኑም ነው የገለፁት። እንደ ሀገር ቤንዚን እጥረቱ በረጅም ጊዜ የሚመጣ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የተፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል ።

ማደያዎች ከተፈቀደላቸው ውጭ በጀሪካ፣በበርሜልና በመሳሰሉት ዕቃዎች ሲሸጡ ከተገኙ ህገወጥ እንደሆኑ የሚገልፁት አቶ ያረጋል በቅርቡም ይሄን ሲፈፅሙ የተገኙ 5 ማደያዎች ላይ ማስጠንቂያ የተሰጣቸው ሲሆን በዚህ ሂደት የተወረሰ (17ሽህ ሊትር ነዳጅ) በቁጥጥር ስር መዋሉን አስታውቀዋል።

09/17/2024

"ህጋዊ ዘራፊዎች" ሳይቀጣጠል በቅጠል
============
💵 የእንጅባራ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት ባለሙያዎች ቀድመው ለነጋዴው የተጣለበትን የግብር መጠን በስልክ እና በሚቀርቧቸው ጓደኛቸቸው በኩል በመግለፅ እኛ እናስቀንስልሃለን በማለት ባለሙያዎች ከጋዴው ጋር በመደራደር እና ጉብ በመቀበል መንግስት ማግኘት የሚገባውን የግብር ገቢ በማስቀነስ የራሳቸውን ኪስ እያሳበጡ ያሉ አቤት የሚላቸው የጠፋ ሰራተኞች በዝተዋል።
በተመሳሳይ የሚገግዱት ንግድና የተጣለባቸው ግብር ከአቅም በላይ ሆኖባቸው ቅሬታ ቢያቀርቡም እኛ እናስ ቀንስላችኋን አልያ አትልፉ ተብሎ ተስፋ የቆርጦና የሚያለቅሱ ብዙዎች ናቸው።
ወዴት ወዴት ?
💵 የመሬት ይዞት አሰተዳደር ጽ/ቤት ያሉ ባለሙያዎች ከመሪት ካሳ ጋር ተያይዞ የሚሰሩ ባለሙያዎች እና ደላሎች('ብሮከሮች') አማካኝነት የኢንቨስትመንት ቦታዎችን እኛ እናስጨርስላችኋለን እያሉ ከባለሀብቱ ርብጣ ገንዘብ ተቀብለው መሬቱን እየቸበቸቡ ያሉ ቦጫቂዎችን ተው ሊባሉ ይገባል።
የዞኑም የከተማ አስተዳደሩም አመራሮች እራሳችሁን አንፅታችሁ ሌቦችን አፅዱ አልያ ግን የሚሆነው ሌላ ነው።

መስከን ወይስ መስከር? # # # # # # # # # # # # #መስክር ብዙ ነው ጉዳቱ፤ ማስቀየም መቀየም፣ መውደቅ መጣል፣ መድማት ማድማት፣ መሰበር መስበር፣ መሞት መግደል፣...መስከር በመጠ...
09/16/2024

መስከን ወይስ መስከር?
# # # # # # # # # # # # #
መስክር ብዙ ነው ጉዳቱ፤ ማስቀየም መቀየም፣ መውደቅ መጣል፣ መድማት ማድማት፣ መሰበር መስበር፣ መሞት መግደል፣...መስከር በመጠጥ ብቻ ሳይን በነገርም መስከር አለ። የነገር ስካር መብረጃ የለውም። አሁን ላይ በነገር አስክረው በአብሮነት እሴቶቻን ጥላሸት ለመቀባት የተነሱ የፅንፈኝነት አባዜ የተናወጣቸው ሆድ አደሮች አሉ። ህሊና ሳይሆን ገንዘብ/$ የገዛቸው።

እዚህም እዚም ክብሪት እየጫሩ ዳር ሆነው የሚሞቁ "የቁማርተኝች" ሲራ ያልገባቸው እሳቱን የሚያራግቡና እፍፍፍፍፍፍ የሚሉ "አክትቪስቶች" ጥቂቷን አብዝተው ትንሿን አግዝፈው ለእኩይ ተግባር ህዝብን "ተነስ" ባዮች የበዙባት ሀገር ሆናለች። "አክቲቪስቶች" እና ፓለቲከኞች ከባላንጣዎቻችን በሚሸጎጥላቸው $ እየሰከሩ ምስኪኑን ህዝብ በነገር እያስከሩ "wrong turn" ፊልሙ እየሰሩብን እንደሆነ ልንነቃ ይገባል።

መስከር ብዙ ነው መዘዙ፤ በእንዲህ ያለ ጊዜና ወቅት ከመስከር መስከን እውነተኛውን መንገድና ትክክለኛውን አቅጣጫ እንድናውቅ ይረዳናል።
ከስካራችን ስንወጣ ፀፀቱ እንዳይገለን ስክን በማለት ቅዝምዝሙን ዝቅ ብሎ ማለፍ ይበጃል።
Agew media Network /አገው ሚድያ ኔትወርክ
Awi Times
Awi communication
አዊ ብልጽግና ፓርቲ - Awi P.P.
አንከሻ ጓጉሳ ብልፅግና ፓርቲ

Agew media Network Agew media Network /አገው ሚድያ ኔትወርክAgew media Network /አገው ሚድያ ኔትወርክ ሚድያ ኔትወርክAwi Timesአዊ ብልጽግና ፓርቲአዊ ብ...
08/31/2024

Agew media Network Agew media Network /አገው ሚድያ ኔትወርክAgew media Network /አገው ሚድያ ኔትወርክ ሚድያ ኔትወርክAwi Timesአዊ ብልጽግና ፓርቲአዊ ብልጽግና ፓርቲ - Awi P.P.Awi አዊ ብልጽግና ፓርቲ - Awi P.P.አዊ ብልጽግና ፓርቲ - Awi P.P.Awi communication

ከፌስ ቡክና ከአዳራሽ ወሬ እንውጣ ከእንጅባራ ከተማ በ3 እና 5 ኪ.ሎ ሜትር ርቀት ላይ ፋኖ እያስተዳደር አዊ ነፃ ነው ማለት ይብዳል። በተለምዶ አሮጌው እንጅባራ ላይ ያሉ ህፃናት ተመዝግብው...
08/28/2024

ከፌስ ቡክና ከአዳራሽ ወሬ እንውጣ

ከእንጅባራ ከተማ በ3 እና 5 ኪ.ሎ ሜትር ርቀት ላይ ፋኖ እያስተዳደር አዊ ነፃ ነው ማለት ይብዳል። በተለምዶ አሮጌው እንጅባራ ላይ ያሉ ህፃናት ተመዝግብው ትምህርት ካልጀመሩ ምኑ ነፃ ነው ማለት ይቻላል።
ደግሞስ ከአንድ መቶ በላይ የሚሆኑ የዞኑ ቀበሌዎች በፋኖ ታጣቂ ስር ሆኖው እያሉ ነፃ ነው ማለት ይቻላል?
Bbc AgewAwi communicationAgew media Network /አገው ሚድያ ኔትወርክAgew media Network /አገው ሚድያ ኔትወርክAwi Timesየዶክተር አብይ አህመድ ደጋፊዎች በአማራ/Dr. Abiy supporters in Amharaየዶክተር አብይ አህመድ ደጋፊዎች በአማራ/Dr. Abiy supporters in Amharaየዶክተር አብይ አህመድ ደጋፊዎች በአማራ/Dr. Abiy supporters in Amharaየዶክተር አብይ አህመድ ደጋፊዎች በአማራ/Dr. Abiy supporters in AmharaAwi communicationአዊ ብልጽግና ፓርቲአዊ ብልጽግና ፓርቲ - Awi P.P.አዊ ብልጽግና ፓርቲ - Awi P.P.አዊ ብልጽግና ፓርቲ - Awi P.P.ዘአገው አዊAGEW TVአገው ቲቪአንከሻ ጓጉሳ ብልፅግና ፓርቲJan Timesዝኩናጉ ዝኩናጉ

የአገው ክልልነት ጥያቄ===========ክልልነት በህገ-መንግስት ወይስ በፒቲሽን?አካሄዱን በውል መረዳት ተገቢ ነው። "አገው ያፏጨውን ሳይዘፍን አይቀርም" እውነት ነው። የሚገርመው የአገው ህ...
08/26/2024

የአገው ክልልነት ጥያቄ
===========
ክልልነት በህገ-መንግስት ወይስ በፒቲሽን?
አካሄዱን በውል መረዳት ተገቢ ነው። "አገው ያፏጨውን ሳይዘፍን አይቀርም" እውነት ነው። የሚገርመው የአገው ህዝብ ሰፊ ነው። በክልሉ ሁሉንም አይነት ምርቶች የሚያመርት። አራቱም የአየር ንብረት ዓይነቶች ያሉበት ዞን። ህግ/መንግስት አክባሪ ታሪክ ሰሪም ዘካሪም ህዝብ ነው። ክልሉ በጀት ሲመድብ ብሔረሰብ ዞን በሚል ተልካሻ ምክንያት በሌሎች ዞኖች ሰሌት የማይምድብ ከሆነነና እንደ ዳረጎት ብጥስ አድርጎ የሚጣልለት ከሆነ ፒቴሽን ሳይሆን የዞኑ ምክር ቤት ጥያቄውን ማንሳት ግድ ይለዋል።
Awi communicationBbc AgewAgew media Network /አገው ሚድያ ኔትወርክAgew media Network /አገው ሚድያ ኔትወርክAwi Timesአዊ ብልጽግና ፓርቲአዊ ብልጽግና ፓርቲ - Awi P.P.አዊ ብልጽግና ፓርቲ - Awi P.P.አዊ ብልጽግና ፓርቲ - Awi P.P.Awi communicationየዶክተር አብይ አህመድ ደጋፊዎች በአማራ/Dr. Abiy supporters in Amharaየዶክተር አብይ አህመድ ደጋፊዎች በአማራ/Dr. Abiy supporters in Amharaየዶክተር አብይ አህመድ ደጋፊዎች በአማራ/Dr. Abiy supporters in Amharaየዶክተር አብይ አህመድ ደጋፊዎች በአማራ/Dr. Abiy supporters in Amharaዘአገው አዊ

አሁን የጭቃኔ ጥግ ላይ ደርሰናል።"ነግ በኔ" የሚለው ብሒል ተቀብሯል። በየትኛውም ሁናቴ ብንሆን እንዴት እንዲህ ያለ ጭቃኔ እንፈጽማለን?በአንድ ወቅት በእድልና በአጋጣማ ጠቅላይ ሚኒስትርአስተ...
08/26/2024

አሁን የጭቃኔ ጥግ ላይ ደርሰናል።
"ነግ በኔ" የሚለው ብሒል ተቀብሯል። በየትኛውም ሁናቴ ብንሆን እንዴት እንዲህ ያለ ጭቃኔ እንፈጽማለን?
በአንድ ወቅት በእድልና በአጋጣማ
ጠቅላይ ሚኒስትር
አስተዳዳሪ
ከንቲባ
ወዘተ ልትሆን ትችላለህ። ነገር ግን ከሰፊው ህዝብ የሚስርቅህ ተግባር መፈፀም ተገቢ አይደለም። ነገ የሰፊው ህዝብ አባል መሆንህን መረሳት የለብህምና።
የሚገርመው የአስተዳዳሪ ጋርድ መሆን እራሳቸውን እንደ ንጉስ የሚቆጠሩ ብርካታ ናቸው። በአንድ ወቅት የአዊ ዞን አስተዳዳሪ የነበረው የአቶ እንግዳ ዳኛው ጠባቂዎች(ጋርድዶች) ከነበሩት መካከል አንድ ሽፍታ ሆኖ በወጣቶች ላይ እያደረሰ ያለው ግፍ ስናይ በእጅጉ አዝነናል።
ይህ ሰውና ግብረ አበሮቹ ተይዘው ተገቢውን እርጃ እንዲያገኙ ማድረግ የሁሉ ሰው ድርሻ ነው።
video 2 ይመልከቱ
Bbc Agew
Agew media Network /አገው ሚድያ ኔትወርክ
Awi communication
የዶክተር አብይ አህመድ ደጋፊዎች በአማራ/Dr. Abiy supporters in Amhara
Awi TimesAwi communicationnአዊ ብልጽግና ፓርቲ - Awi P.P.

የአዊ ብሔ/አስተዳደር የ2016 በጀት አመት የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት ግምገማ እና የ2017 ዓ.ም ዕቅድ ኦረንቴሽን ማካሄድ ከተጀመረ 3ኛ ቀኑን አስቆጥሯል።እንጅባራ፦ ነሐሴ 13...
08/19/2024

የአዊ ብሔ/አስተዳደር የ2016 በጀት አመት የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት ግምገማ እና የ2017 ዓ.ም ዕቅድ ኦረንቴሽን ማካሄድ ከተጀመረ 3ኛ ቀኑን አስቆጥሯል።
እንጅባራ፦ ነሐሴ 13/2016 ዓ.ም

የአዊ ብሔ/አስተዳደር የ2016 በጀት ዓመት የተከናወኑ ዋና ዋና የልማት ተግባራት እና የመልካም አስተዳደር ተግባራት አፈፃፀም በጥልቀት ሲገመግም ሰንብቷሎ።
በነገው እለት ከየወረዳውና ከተ/አስተዳደሮች የመጡ አመራሮች በየመምሪያቸው ተገኝተው በየሴክተራቸው ሲገመግሙ ከዋሉ በኃሏ 10: ገመደማ ዘደ ዋናው መድረክ ይዘው እንደሚቀርቡ ይጠበቃል። በነገው እለትም ፍፃሜውን ያገኛል።
Agew media Network /አገው ሚድያ ኔትወርክ
Awi communication
Awi Times
ዝኩናጉ ዝኩናጉ
Bbc Agew

ከእንጅባራ ቻግኒ በሚጓዙ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ላይ የዝርፊያ ወንጀሎች ብቅ ብቅ እያሉ ስለሆነ ጥቅቃቂ ይደረግ።Agew media Network /አገው ሚድያ ኔትወርክBbc AgewBek...
08/18/2024

ከእንጅባራ ቻግኒ በሚጓዙ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ላይ የዝርፊያ ወንጀሎች ብቅ ብቅ እያሉ ስለሆነ ጥቅቃቂ ይደረግ።
Agew media Network /አገው ሚድያ ኔትወርክ
Bbc Agew
Beki Awahosu
Awi communication
ዝኩናጉ ዝኩናጉ
Awi Times

08/10/2024

ፅንፈኝነት መነሻውም መደራሸውም ራስ ወዳድናት ነው። ለፅንፈኛ እናትም፣ አባትም፣ ልጅም፣ ብሔርም፣ አገርም የለውም። ሁሉንም ለራሱ ብቻ ነው። ራሱ ጠግቦ የተረፈው ሌላው እንዲቀምሰው አይፈልግም። የፅንፈኛው ኃይል አሁን ቅማንትን በተሰካ መንገድ ዘር እንዳጠፋ የቀጣይ እቅዳቸው ደግሞ የጎጃም አገውን ማጥፋት እንደሆነ በመገምገም በራስሳቸው የፋይናንስና ፕሮፖጋንዳ ኃላፊያቸው በጌታቸው በጋሻው በኩል የዘር ጭፍጨፋ አዋጅ አውጀዋል ። አገው የራሱ ባህልና ታሪክ ያለው፣ በእኩልነትና በኢትዮጵያ አንድናት የሚያምንም፣ የሚቀበል የሚተገበርም ህዝብ ነው። መምራትንም መመራትንም ጠንቅቆ የሚያው ህዝብ ነው። እንደ ፅንፈኞች እኔ ብቻ ካልመራሁ ብሎ አይፈራገጥም። አሁን ፅንፈኛው በህዕቡ ሌለውን ብሔር በማጥፋት ራሱ ብቻ ለመኖር ያቀድው ዕቅድ በአደባባይ እየወጣ ነው። ሁሉም ኢትዮጵያዊና የአለም ህዝብ ፅንፈኛው አገውን ብቻ አጥፍቶ የማይቆም መሆኑን ተረድቶ በጋራ እንዲቆምና ፅንፈኝነት እንዲታገል እንጠይቃለን።

07/23/2024
ሰበር ዜና!በአማራ ፋኖ የሽዋ ዕዝ ዋና አዛዥ በመሆን ቡድኑን ሲመራ የነበረው  ኮሎኔል አስግድ መኮንን ለመንግስት ፀጥታ ሀይሎች ዛሬ እጁን ሰጥቷል፡፡  አመራሩ እጅን የሰጠው ገበየሁ ወንድማገ...
07/22/2024

ሰበር ዜና!

በአማራ ፋኖ የሽዋ ዕዝ ዋና አዛዥ በመሆን ቡድኑን ሲመራ የነበረው ኮሎኔል አስግድ መኮንን ለመንግስት ፀጥታ ሀይሎች ዛሬ እጁን ሰጥቷል፡፡ አመራሩ እጅን የሰጠው ገበየሁ ወንድማገኝ ከተባለ አጃቢው ጋር ኮምበልቻ ከተማ መሆኑ ታውቋል።

በሕገ-ወጥ መንገድ የጦር መሣሪያ በማዘዋወር ለፀረ ሰላም ኃይሎች ሊያቀብሉ የሞከሩ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የደቡብ ወሎ እና ደሴ ከተማ  ኮማንድ ፖስት አስታውቋል፡፡ ========...
04/02/2024

በሕገ-ወጥ መንገድ የጦር መሣሪያ በማዘዋወር ለፀረ ሰላም ኃይሎች ሊያቀብሉ የሞከሩ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የደቡብ ወሎ እና ደሴ ከተማ ኮማንድ ፖስት አስታውቋል፡፡
===============================
47 ሺህ ጥይትን ጨምሮ አራት ክላሽና አንድ ስናይፐር በሕገወጥ መንገድ ሲገበያዩ እና ሲያዘዋውሩ የነበሩ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የመከላከያ ሠራዊት አስታውቋል።

በሀገር መከላከያ ሠራዊት ኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ የ103ኛ ክፍለ ጦር 5ኛ ኮማንዶ ሪጅመንት ዋና አዛዥና የኮማንድ ፖስቱ አባል ሻምበል ታሪኩ ሻሜቦ እንደገለጹት፤ በሕገ ወጥ መንገድ የጦር መሣሪያ በማዘዋወር ላይ የተሳተፉ 42 ተጠርጣሪዎችን ከኅብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት መያዝ ተችሏል ብለዋል።

ለጽንፈኛ ኀይሎች ሊተላለፍ የነበረ 47 ሺህ ጥይት፣ አራት ክላሽና አንድ ስናይፐር ከነተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የገለጹት ሻምበል ታሪኩ፤ ከዚህ ባሻገር ለመሣሪያ ግዢ ሊውል የነበረ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብም በሠራዊቱ በቁጥጥር ስር ውሏል ብለዋል።

ተጠርጣሪዎች መሣሪያ በማዘዋወርና በመገበያየት ለፀረ ሰላም ኃይሉ በማቀበል ቀጣናውን የግጭት አካባቢ ሊያርጉ እንደነበሩ የገለጹት ሻምበል ታሪኩ፤ "ከኅብረተሰቡ ጋር በተደረገ ትብብር ሴራቸውን ማክሸፍ ተችሏል" ብለዋል፡፡

ሠራዊቱ በደቡብ ወሎ እና አካባቢው በጽንፈኞች ላይ እየወሰደ ያለውን ርምጃ አጠናክሮ መቀጠሉን የገለጹት ሻምበል ታሪኩ ሻሜቦ ኅብረተሰቡ አንድነቱንና ሰላሙን ጠብቆ ከሠራዊቱ ጎን መሰለፉን ተናግረዋል።
በቀጣይም በጽንፈኞች ላይ የሚወሰደው ርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው ያስታወቁት።

ሕገወጥ የጦር መሣሪያ ሲገዙና ሲደልሉ የተያዙት ተጠርጣሪዎችም በመከላከያ ሠራዊት በቁጥጥር ሥር ከዋልንበት ጊዜ ጀምሮ ምንም የደረሰብን ችግር የለም በሠራነውም ሥራ ተፀፅተናል ብለዋል።

Address

Chicago, IL

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bbc Agew posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share