Bbc Agew

Bbc Agew የአገው ህዝብ አፍ፣አይንና ጆሮ

በህግ አምላክ ቢባሉም የማይመለሱ ናቸውስብስባቸው የሚገርም ነው
07/19/2025

በህግ አምላክ ቢባሉም የማይመለሱ ናቸው
ስብስባቸው የሚገርም ነው

#በቅርብ ቀን
የእንጅባራ ከተማ አስተዳደር ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት አንዳንድ ሰራተኞችና አመራሩ(ኃላፊው) በምን አይነት የሙስና ቅሌት ውስጥ እንዳሉ በማጣራት ላይ ነን በከፊል መረጃዎች ደርሰውናል። የበለጠ ከእናንተ በሚደርሰን መረጃ አጠናክረን በቅርብ ቀን በይፋ እናሰጣዋለን።
"አፍንጫ ሲመታ..."

07/05/2025
እስቲ ጎልጉሉ
06/18/2025

እስቲ ጎልጉሉ

ስለ እንጅባራ ከተማ ተቀዳሚ ም/ከንቲባ አቶ ለምን ከክልል ገቢዎች ወደ እንጅባራ ከንቲባነት መጡ?
በቅርብ ቀን ይጠብቁን🖋️
ያለዎትን መረጃ በውስጥ መስመር ያጋሩን

04/27/2025

“50 ሰሪ፣50 ደንጓሪ ፣50 አነዋሪ”           ያላጣው ያለፉት 7 የፈተናና                የስኬት ዓመታት !አጼ ቴዎድሮስ ወይብላ ማሪያምን በፍጥነት ለማሰራትና  ሁሉም ህዝብ...
04/03/2025

“50 ሰሪ፣50 ደንጓሪ ፣50 አነዋሪ”
ያላጣው ያለፉት 7 የፈተናና
የስኬት ዓመታት !

አጼ ቴዎድሮስ ወይብላ ማሪያምን በፍጥነት ለማሰራትና ሁሉም ህዝብ እንዲሳተፍ ፈለጉ፡፡ ሊቃውንቶቹ እንዲህ ከሆነ በፍጥነትም ሆነ በጥራት አይሰራም አሉና ፣ 50 ሰሪ እንጨትና ጡብናውን በአግባቡ የሚያዘጋጅና የሚሰራ ፣ 50 ደንጓሪ የሚሰራ የሚመስል አስመሳይ ፣ 50ው ደግሞ ይህ እንዲህ ቢሆን ይህ ደግሞ እንዲያ እየያለ የሚተች አነዋሪ ካለ ይበቃል ብለው በማማከር ቤተ ክርስቲያኗ በፍጥነትና በጥራት እንደተሰራች የሚነግረን አፈታሪክ (Legend) አለ፡፡

ይህ ሀገራችን አሁን ለገጠማት ችግርና ላጋጠማት እድል ጥሩ ማሳያ ነው ፡፡ ሀገራችን በለውጥ ፈላጊው ህዝብ ተሳትፎና ለውጡን በቆራጥነት በሚመሩ መሪዎች አማካኝነት ቀላል የማይባሉ ድሎች የተገኙ 7 ዓመታትን አሳልፋለች።

ለውጡን ለመንጠቅና ለውጡን ማስቀጠል በሚፈልጉ ኃይሎች መካከል በሚደረግ ትግል ብዙ ተፈትናለች ፡፡ያልተፈተነ አያልፍም እንዲሉ በሰላሙ ጊዜ ከሆነው በላይ እነዚህን ፈተናን ወደ ድል ቀይራ ዓለምን ያስደመመ ስኬት አስመዝግባለች ፤ችግር ባለባቸው ክልሎች የተመዘገቡ ልማቶችም ይሄ ችግር ባይኖር ብለው የሚያስቋጩ ሥራዎች ተሰርተዋል።

በየትም ሁሉ ሰሪ፣ሁሉም ደንጓሪ ሁሉም ደግሞ አነዋሪ ሆኖ የተሰራ ሀገር፣የተገኘ ሰላምና የተፈጠረ ዴሞክረሲ አልታየም፡፡
ሁላችንም የሚናችንን እንወጣ ፣ባላፉት ሰባት አመታት የልካችንን መወጣት አቅቶን የእልሀችንን ሚና ስንጫወት ለእኛ ስቃይ ለጠላቶቻችን ደግሞ ሲሳይ ሆነናልና።

የታቀደውን ልማት ስንቃወም፣የተገኘውን ስኬት ብናጣጥል የሚጎዳው ትውልድ ነው።የእኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል ብሂል አለች የተባለችው እንስሳም አሁን ብትጠየቅ የምትደግመው አይመስልም።

ያለፉት 7 ዓመታት በፈተና የታጀበ ስኬት ኢተአማኒ ነው ።አሁን ፈተናው አብቅቶ ስኬቱ ልቆ ኦንዲቀጥል ችግራችንን በንግግር የመፍታትን ዘመንኛ መፍትሄ እንድንከተል ዝም ያሉ አዋቂ አንደበቶች ሁሉ መከፈት አለባቸው ። እንዲህ ከሆነ ብዙ እንሰራለን ብዙም እናያለን !

03/05/2025
ኢትዮጵያ በ5 ቢሊየን ፓውንድ "ሜጋ ኤርፖርት ሲቲ" በመገንባት ላይ ትገኛለች። ተጠናቆ ስራ ሲጀምርም በአፍሪካ ግዙፉና በአለም ካሉ እጅግ ቢዚ ኤርፖርቶች አንዱ ይሆናል። ከአዲስ አበባ በ25 ...
12/01/2024

ኢትዮጵያ በ5 ቢሊየን ፓውንድ "ሜጋ ኤርፖርት ሲቲ" በመገንባት ላይ ትገኛለች። ተጠናቆ ስራ ሲጀምርም በአፍሪካ ግዙፉና በአለም ካሉ እጅግ ቢዚ ኤርፖርቶች አንዱ ይሆናል።

ከአዲስ አበባ በ25 ማይል ርቀት ላይ በቢሾፍቱ አቅራቢያ የሚገነባው አዲሱ ኤርፖርት በ2029 ሲጠናቀቅ በአመት እስከ 110 ሚሊዮን መንገደኞችን ያስተናግዳል። ተርሚናል እና አራት ማኮብኮቢያ/ማረፊያ ራንዌዮች ይኖሩታል።

ከባህር ጠለል በላይ 2,334 ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው የአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ ኢትዮጵያ የዓለም አቀፋዊ የአቪዬሽን ማዕከልነቷን እያረጋገጠ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ መጨናነቅ ገጥሞታል።

የሚገነባው "የሜጋ ኤርፖርት ከተማ" ይህን ችግር ከማቃለል ባለፈ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ያሳድጋል፣ ሀገሪቱን በአለም አቀፍ ንግድና ቱሪዝም ዋና ተዋናይነት ያስቀምጣል። አዲሱ ተቋም እንደ ዱባይ እና ሄትሮው ያሉ አለምአቀፍ አየር ማረፊያዎችን ለመወዳደር ያለመ ነው።

በአዊ ብሄ/አስ በህገወጥ መንገድ ነዳጅ የሚያሸሹ፤ ነዳጅ እያለ የለም ብለው የሚዘጉ ማደያዎች የነዳጅ አቅርቦት ስጋት መሆናቸው  ተገለፀ።የአዊ ብሄ/አስ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ በበኩሉ በ...
11/30/2024

በአዊ ብሄ/አስ በህገወጥ መንገድ ነዳጅ የሚያሸሹ፤ ነዳጅ እያለ የለም ብለው የሚዘጉ ማደያዎች የነዳጅ አቅርቦት ስጋት መሆናቸው ተገለፀ።

የአዊ ብሄ/አስ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ በበኩሉ በዘርፉ የሚስተዋለው ህገወጥነት ለማስተካከል እየሰራሁ ነኝ ብሏል።

ከቅርብ አመታት ወዲህ በሀገራችን የነዳጅ አቅርቦቱ ከአለም አቀፍ ሁኔታው ጋር በተያያዘ እጥረት ማጋጠሙ ይታወቃል።

ይህንን አለም አቀፍ ሁኔታውንና የሀገሪቱን ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት በማድረግ ደግሞ ለጥረቱና ለዋጋ ንረቱ እንዲባባስ በር ከፍቷል።

በተለይም በማደያዎች ተሸከርካሪ፣ የነዳጅ መያዣ ጀሪካኖችና የበርሜሮች ረጃጅም ሰልፎችን ማየት የዕለት ተዕለት ክስተት ሆኗል።

ነገር ግን አለም አቀፍ ሁኔታውና መሬት ላይ ያለው የነዳጅ አቅርቦትና ሽያጭ እውነታ ምን ይመስላል ብለን በአዊ ብሄ/አስ በሚገኙ ማደያዎች እንዲሁም በንግድና ትራንስፖርት ዘርፉና የሚመለከታቸውን አካላት ለመዳሰስ ሞክረናል።

በእንጅባራ ከተማ የባጃጅና የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ተጠቃሚዎች በሰጡት አስተያየት በነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ምክንያት ከትርፍ በላይ እንደሚጭኑ እና ከታሪፍ በላይ እንደሚያስከፍሉ የተናገሩ ሲሆን አሁን ላይ በተለይም የባጃጅ ክፍያ በእጥፍ እንደጨመረ ቅሬታቸውን አቅረበዋል ።

"በትራንስፖርት ዘርፉ ህግ ይከበርልን " የሚሉት ነዋሪዎቹ መንግስት ለዚህ ዘርፍ ትኩረት በመስጠት የማስተካከል ስራ እንዲሰራም በአፅንኦት ጠይቀዋል።

በእንጅባራ ከተማ ያነጋገርናቸው የተሽከርካሪ ሹፌሮች በበኩላቸው አሁን አሁን እየተለመደ የመጣው በህገወጥ መንገድ ነዳጅ የሚያሸሹ፤ ነዳጅ እያለ የለም ብለው የሚዘጉ ማደያዎች የነዳጅ አቅርቦት ስጋት ሁነዋል።"በዚህም ምክንያት በተተመነው የነዳጅ ዋጋ ሳይሆን ከፍተኛ ጭማሪ ባለው (በጥቁር ገበያ ) እንድንገዛ እንገደዳለን" ነው ያሉት።በትራንስፖርት እንቅስቃሴ ላይም የራሱ የሆነ አሉታዊ ተፅዕኖ ከማሳረፉ በተጨማሪ ነዳጅ ወደ ጥቁር ገበያ በሚዘዋወርበት ወቅት ለተሸከርካሪው ጤንነት ላይ ጉዳት እንደሚያደርስም ነው ያረጋገጡት ።

የአዊ ብሄ/አስ ንግድ መምሪያ ሀላፊ አቶ ያረጋል ያየህ ፥ በብሄረሰቡ አስተዳደሩ 33 የሚሆኑ ማደያዎች እንዳሉ ተናግረዋል ። የሚስተዋለውን የነዳጅ ስርጭት ችግር ከማደያ ባለቤቶች ጋር በመነጋገር ለመፍታት ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል።እንደ ሀላፊው ገለፃ በብሄረሰብ አስተዳደሩ የቤንዚን እንጂ የናፍጣ እጥረት እንደሌለም አረጋግጠዋል ።ይሁን እንጂ በቁጥጥር ማነስ በየወረዳዎችና በከተሞች የነዳጅ ርክክብ ችግር በንግድ ተቋሙ ዘንድ መኖሩን እንደ ምክንያት አንስተዋል።

እንደ ሀላፊው ገለፃ ተቋሙ በቅረቡ ጥናት አድርጊያለሁ ባላቸው ማደያዎች የከፋ ችግር እንዳላጋጠመ እና አልፎ አልፎ ህገወጥነት የሚስተዋል መሆኑን ጠቁመዋል።የፀጥታው ችግር ለዚህ ዘርፍ አባባሽ ምክንያቶች እንደሆኑም ነው የገለፁት። እንደ ሀገር ቤንዚን እጥረቱ በረጅም ጊዜ የሚመጣ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የተፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል ።

ማደያዎች ከተፈቀደላቸው ውጭ በጀሪካ፣በበርሜልና በመሳሰሉት ዕቃዎች ሲሸጡ ከተገኙ ህገወጥ እንደሆኑ የሚገልፁት አቶ ያረጋል በቅርቡም ይሄን ሲፈፅሙ የተገኙ 5 ማደያዎች ላይ ማስጠንቂያ የተሰጣቸው ሲሆን በዚህ ሂደት የተወረሰ (17ሽህ ሊትር ነዳጅ) በቁጥጥር ስር መዋሉን አስታውቀዋል።

09/17/2024

"ህጋዊ ዘራፊዎች" ሳይቀጣጠል በቅጠል
============
💵 የእንጅባራ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት ባለሙያዎች ቀድመው ለነጋዴው የተጣለበትን የግብር መጠን በስልክ እና በሚቀርቧቸው ጓደኛቸቸው በኩል በመግለፅ እኛ እናስቀንስልሃለን በማለት ባለሙያዎች ከጋዴው ጋር በመደራደር እና ጉብ በመቀበል መንግስት ማግኘት የሚገባውን የግብር ገቢ በማስቀነስ የራሳቸውን ኪስ እያሳበጡ ያሉ አቤት የሚላቸው የጠፋ ሰራተኞች በዝተዋል።
በተመሳሳይ የሚገግዱት ንግድና የተጣለባቸው ግብር ከአቅም በላይ ሆኖባቸው ቅሬታ ቢያቀርቡም እኛ እናስ ቀንስላችኋን አልያ አትልፉ ተብሎ ተስፋ የቆርጦና የሚያለቅሱ ብዙዎች ናቸው።
ወዴት ወዴት ?
💵 የመሬት ይዞት አሰተዳደር ጽ/ቤት ያሉ ባለሙያዎች ከመሪት ካሳ ጋር ተያይዞ የሚሰሩ ባለሙያዎች እና ደላሎች('ብሮከሮች') አማካኝነት የኢንቨስትመንት ቦታዎችን እኛ እናስጨርስላችኋለን እያሉ ከባለሀብቱ ርብጣ ገንዘብ ተቀብለው መሬቱን እየቸበቸቡ ያሉ ቦጫቂዎችን ተው ሊባሉ ይገባል።
የዞኑም የከተማ አስተዳደሩም አመራሮች እራሳችሁን አንፅታችሁ ሌቦችን አፅዱ አልያ ግን የሚሆነው ሌላ ነው።

መስከን ወይስ መስከር? # # # # # # # # # # # # #መስክር ብዙ ነው ጉዳቱ፤ ማስቀየም መቀየም፣ መውደቅ መጣል፣ መድማት ማድማት፣ መሰበር መስበር፣ መሞት መግደል፣...መስከር በመጠ...
09/16/2024

መስከን ወይስ መስከር?
# # # # # # # # # # # # #
መስክር ብዙ ነው ጉዳቱ፤ ማስቀየም መቀየም፣ መውደቅ መጣል፣ መድማት ማድማት፣ መሰበር መስበር፣ መሞት መግደል፣...መስከር በመጠጥ ብቻ ሳይን በነገርም መስከር አለ። የነገር ስካር መብረጃ የለውም። አሁን ላይ በነገር አስክረው በአብሮነት እሴቶቻን ጥላሸት ለመቀባት የተነሱ የፅንፈኝነት አባዜ የተናወጣቸው ሆድ አደሮች አሉ። ህሊና ሳይሆን ገንዘብ/$ የገዛቸው።

እዚህም እዚም ክብሪት እየጫሩ ዳር ሆነው የሚሞቁ "የቁማርተኝች" ሲራ ያልገባቸው እሳቱን የሚያራግቡና እፍፍፍፍፍፍ የሚሉ "አክትቪስቶች" ጥቂቷን አብዝተው ትንሿን አግዝፈው ለእኩይ ተግባር ህዝብን "ተነስ" ባዮች የበዙባት ሀገር ሆናለች። "አክቲቪስቶች" እና ፓለቲከኞች ከባላንጣዎቻችን በሚሸጎጥላቸው $ እየሰከሩ ምስኪኑን ህዝብ በነገር እያስከሩ "wrong turn" ፊልሙ እየሰሩብን እንደሆነ ልንነቃ ይገባል።

መስከር ብዙ ነው መዘዙ፤ በእንዲህ ያለ ጊዜና ወቅት ከመስከር መስከን እውነተኛውን መንገድና ትክክለኛውን አቅጣጫ እንድናውቅ ይረዳናል።
ከስካራችን ስንወጣ ፀፀቱ እንዳይገለን ስክን በማለት ቅዝምዝሙን ዝቅ ብሎ ማለፍ ይበጃል።
Agew media Network /አገው ሚድያ ኔትወርክ
Awi Times
Awi communication
አዊ ብልጽግና ፓርቲ - Awi P.P.
አንከሻ ጓጉሳ ብልፅግና ፓርቲ

Agew media Network Agew media Network /አገው ሚድያ ኔትወርክAgew media Network /አገው ሚድያ ኔትወርክ ሚድያ ኔትወርክAwi Timesአዊ ብልጽግና ፓርቲአዊ ብ...
08/31/2024

Agew media Network Agew media Network /አገው ሚድያ ኔትወርክAgew media Network /አገው ሚድያ ኔትወርክ ሚድያ ኔትወርክAwi Timesአዊ ብልጽግና ፓርቲአዊ ብልጽግና ፓርቲ - Awi P.P.Awi አዊ ብልጽግና ፓርቲ - Awi P.P.አዊ ብልጽግና ፓርቲ - Awi P.P.Awi communication

በሕገ-ወጥ መንገድ የጦር መሣሪያ በማዘዋወር ለፀረ ሰላም ኃይሎች ሊያቀብሉ የሞከሩ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የደቡብ ወሎ እና ደሴ ከተማ  ኮማንድ ፖስት አስታውቋል፡፡ ========...
04/02/2024

በሕገ-ወጥ መንገድ የጦር መሣሪያ በማዘዋወር ለፀረ ሰላም ኃይሎች ሊያቀብሉ የሞከሩ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የደቡብ ወሎ እና ደሴ ከተማ ኮማንድ ፖስት አስታውቋል፡፡
===============================
47 ሺህ ጥይትን ጨምሮ አራት ክላሽና አንድ ስናይፐር በሕገወጥ መንገድ ሲገበያዩ እና ሲያዘዋውሩ የነበሩ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የመከላከያ ሠራዊት አስታውቋል።

በሀገር መከላከያ ሠራዊት ኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ የ103ኛ ክፍለ ጦር 5ኛ ኮማንዶ ሪጅመንት ዋና አዛዥና የኮማንድ ፖስቱ አባል ሻምበል ታሪኩ ሻሜቦ እንደገለጹት፤ በሕገ ወጥ መንገድ የጦር መሣሪያ በማዘዋወር ላይ የተሳተፉ 42 ተጠርጣሪዎችን ከኅብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት መያዝ ተችሏል ብለዋል።

ለጽንፈኛ ኀይሎች ሊተላለፍ የነበረ 47 ሺህ ጥይት፣ አራት ክላሽና አንድ ስናይፐር ከነተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የገለጹት ሻምበል ታሪኩ፤ ከዚህ ባሻገር ለመሣሪያ ግዢ ሊውል የነበረ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብም በሠራዊቱ በቁጥጥር ስር ውሏል ብለዋል።

ተጠርጣሪዎች መሣሪያ በማዘዋወርና በመገበያየት ለፀረ ሰላም ኃይሉ በማቀበል ቀጣናውን የግጭት አካባቢ ሊያርጉ እንደነበሩ የገለጹት ሻምበል ታሪኩ፤ "ከኅብረተሰቡ ጋር በተደረገ ትብብር ሴራቸውን ማክሸፍ ተችሏል" ብለዋል፡፡

ሠራዊቱ በደቡብ ወሎ እና አካባቢው በጽንፈኞች ላይ እየወሰደ ያለውን ርምጃ አጠናክሮ መቀጠሉን የገለጹት ሻምበል ታሪኩ ሻሜቦ ኅብረተሰቡ አንድነቱንና ሰላሙን ጠብቆ ከሠራዊቱ ጎን መሰለፉን ተናግረዋል።
በቀጣይም በጽንፈኞች ላይ የሚወሰደው ርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው ያስታወቁት።

ሕገወጥ የጦር መሣሪያ ሲገዙና ሲደልሉ የተያዙት ተጠርጣሪዎችም በመከላከያ ሠራዊት በቁጥጥር ሥር ከዋልንበት ጊዜ ጀምሮ ምንም የደረሰብን ችግር የለም በሠራነውም ሥራ ተፀፅተናል ብለዋል።

Address

Chicago, IL

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bbc Agew posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share