Naod Tube

Naod Tube like like

(Naod Tube) የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ስለኢትዮጵያ ጉዳይ ከአስመራ ቤተመንግስት ከተናገሩ ከሁለት ቀን በኋላ፣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ከየትኛውም አቅጣጫ የሚሰነዘርበት...
07/22/2025

(Naod Tube) የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ስለኢትዮጵያ ጉዳይ ከአስመራ ቤተመንግስት ከተናገሩ ከሁለት ቀን በኋላ፣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ከየትኛውም አቅጣጫ የሚሰነዘርበትን ትንኮሳ ለመመከት በሚያስችል አስተማማኝ ቁመና ላይ እንደሚገኝ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በጅማ በነበረ ወታደራዊ ስነ ስርዓት ላይ ተናገሩ።

ጠቅላይ ኢታማዦር ሹሙ፣ የሠራዊቱ ዋነኛ ተልዕኮ የሀገርን ሉዓላዊነት ማስከበር መሆኑን አስታውሰው፣ ይህንን ኃላፊነቱን ለመወጣትም ከምንጊዜውም በላይ ዝግጁ ነው ብለዋል። "ኢትዮጵያዊያን የጀግንነትና የአይበገሬነት ስነ-ልቦና ያለን ህዝቦች መሆናችንን ዓለም የሚያውቀው ሀቅ ነው" ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ፣ ሠራዊቱ የሀገርን ክብር ጠብቆ ለማቆየት ዛሬም እንደትናንቱ ጽኑ አቋም እንዳለው ገልጸዋል።

ጅማ፣ ኢትዮጵያ::

“የደበቃችሁትን መድፍና ታንክ አስረክቡ!” ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ለህወሃት አመራሮች  “ተዉ እያልናችሁ ነው፡፡” ሲሉ  ማስጠንቀቂያ አስተላልፈዋል፡፡ኢታማዦር ሹሙ በመልዕክታቸው  “የህወሀት መ...
07/21/2025

“የደበቃችሁትን መድፍና ታንክ አስረክቡ!”

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ለህወሃት አመራሮች “ተዉ እያልናችሁ ነው፡፡” ሲሉ ማስጠንቀቂያ አስተላልፈዋል፡፡

ኢታማዦር ሹሙ በመልዕክታቸው “የህወሀት መሪዎች ተዉ እየተባላችሁ ነው፡፡ በፓርላማም ተነግሯችኋል - ይቅርባችሁ ተብላችኋል፡፡ ያለፈው ኢትዮጵያንም ህወሀትንም ጎድቷል ተብላችሁዋል” ብለዋል፡፡

"...ያኔ ተዉ እያልናችሁ ሰሜን እዝን መታችሁ - ከዛ መከራ ወረደ፣ ተው እያልን ትግራይን ለቀንላችሁ ወጥተን ተከትላችሁ መጣችሁ - መከራ ወረደባችሁ፡፡ ከሰሜን ሸዋ ትግራይ ከገባችሁ በኋላ - ይበቃል አሁን ወደ ድርድር ተመለሱ አልናችሁ አሻፈረኝ ብላችሁ - 12 አርሚ ገንብታችሁ እንደገና ሶስተኛ ዙር ስህተት ሰራችሁ፡፡..." ሲሉም ነው የገለጹት፡፡

"...አሁን ላይ ኢትዮጵያ ውስጥ መድፍና ታንክ የታጠቀ ክልል የለም!"" ያሉት ፊልድ ማርሻሉ "ታንኩ እና መድፉን፣ አየር መቃወሚያውን አስረክቡ!" ሲሉ በማስጠንቀቅ - “ባለፈው ያስረከባችሁት አለ፡፡ ይሄንን ግን ደብቃችሁት ነበር - አሁን ብቅ ብቅ ማድረግ ጀምራችኋል..." ሲሉም ነው የተደመጡት፡፡

ኤርትራ ተኮሰች‼️❓ኤርትራ  #ከአሰብ ወደብ 80 ኪሎ ሜትር  #ርቀት ላይ በምትገኘው  #በአፋር ቡሬ የኢትዮጵያ ክፍል   ዛሬ ማምሻውን መተኮሱ ተዘግቧል።
07/16/2025

ኤርትራ ተኮሰች‼️❓
ኤርትራ #ከአሰብ ወደብ 80 ኪሎ ሜትር #ርቀት ላይ በምትገኘው #በአፋር ቡሬ የኢትዮጵያ ክፍል ዛሬ ማምሻውን መተኮሱ ተዘግቧል።

07/16/2025

መቀሌ‼️
ዛሬ ምሽት 12:00 ላይ ከአዲስ አበባ ተነስቶ ወደ መቀሌ ሲያመራ የነበረ አውሮፕላን ከምሽቱ 2:00 ላይ አሉላ አባነጋ ኤርፖርት እንዳረፈ ድንገተኛ የመንሸራተት አደጋ አጋጥሞት ከአጥር ውጪ ወጥቶ ጭቃ ውስጥ መውደቁን ምንጮቻችን ገልፀዋል።

ለሽብር ተልዕኮ የተመለመሉ 82 የአይ ኤስ አባላት በቁጥጥር ስር ዋሉአዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ለሽብር ተልዕኮ የተመለመሉ 82 የአይ ኤስ አባላት በቁጥጥር ስር ዋሉ መዋ...
07/15/2025

ለሽብር ተልዕኮ የተመለመሉ 82 የአይ ኤስ አባላት በቁጥጥር ስር ዋሉ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ለሽብር ተልዕኮ የተመለመሉ 82 የአይ ኤስ አባላት በቁጥጥር ስር ዋሉ መዋላቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ፡፡

አገልግሎቱ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን በላከው መግለጫ እንዳመለከተው፥ በፑንትላንድ የሚንቀሳቀሰው የአይ ኤስ የሶማሊያ ክንፍ በተለያዩ ሀገራት እንዲሁም በኢትዮጵያ ለመስፋፋትና የሽብር ቡድኑን ሴሎች ለመመስረት የሚያደርገውን ጥረት በተመለከተ የመረጃ ስምሪትና ጥናት ሲደረግ ቆይቷል፡፡

በተለይም በኢትዮጵያ የሽብር መረብ ለመዘርጋት የሚያደርገውን ሙከራ በተመለከተ ከጅምሩ በመረጃና በማስረጃ ተደግፎ ጥብቅ ክትትል ሲያደርግ መቆየቱንም አገልግሎት መስሪያ ቤቱ ገልጿል፡፡

የሥጋት ደረጃውን በተመለከተ በየጊዜው ባከናወናቸው ግምገማዎች ተጋላጭነትን የሚያስከትሉና ወደ ብሔራዊ ደኅንነት ሥጋት የሚያድጉ ተጨባጭ ግኝቶች መለየታቸውንም ጠቁሟል፡፡

የተከናወነውን ተጨባጭ መረጃና ማስረጃ የማጠናቀር ሂደት ተከትሎ የሽብር ቡድኑ በፑንትላንድ አሰልጥኖ ወደ ተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ያሰማራቸው 82 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከፌዴራል ፖሊስና ከክልል የጸጥታ አካላት ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

ከቡድኑ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያላቸውና ሁለንተናዊ ድጋፍ ሲያደርጉ የነበሩ ተጠርጣሪዎች መካተታቸውን የጠቀሰው መግለጫው፥ በተለይ በዓለምአቀፍ የሽብር ቡድኑ በመረጃ ክንፍ የተደራጁ እንዲሁም በፋይናንስና በሎጀስቲክ እገዛ ሲያደርጉ የነበሩ ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን አመልክቷል፡፡

የሽብር ቡድኑ የጥፋት ተልዕኮውን ለማስፋፋትና ምልመላ ለማከናወን የሃይማኖት ተቋማትንና ሃይማኖትን እንደ ሽፋን እንደሚጠቀምም ነው አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ በመግለጫ ያመለከተው፡፡

የሕዝብን አንድነትና ተከባብሮ የመኖር እሴት የሚሸረሽሩ ብሎም ለአመጽና ሁከት የሚያነሳሱ አስተምህሮዎችን ለማስፋፋት ሙከራ ሲደረግ እንደነበር በተጨባጭ ማስረጃ መረጋገጡንም አስታውቋል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ በአዲስ አበባ፣ በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ፣ አዳማ፣ ሃሮማያ፣ ሻሸመኔ፣ ባሌ፣ጅማና ሻኪሶ ከተማ ዙሪያ እንዲሁም በአማራ ክልል ከሚሴ አካባቢ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጤ ዞንና ሃላባ ቁሊቶ ከተማ፤ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማና በሐረሪ ክልል በቁጥጥር ውለዋል፡፡

ግለሰቦቹን ለመያዝ በተደረገው ስምሪት በየአካባቢው የሚገኘው ኅብረተሰብ ከደኅንነትና ከጸጥታ አካላት ጋር በመተባበር ያሳየው ተሳትፎ በመልካም አርዓያነት የሚጠቀስ ነው ብሏል፡፡
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በመግለጫው እንዳስታወቀው፥ በቁጥጥር ስር ያልዋሉ የሽብር ቡድኑ አባላት ላይ የሚደረገው ክትትል ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡

ኅብረተሰቡም በየአካባቢው ሰላምን የሚያደፈርሱና ስጋት ሊፈጥሩ የሚችሉ አጠራጣሪ ሁኔታዎችን ሲመለከት አንደ ሁልጊዜው ለሚመለከታቸው የደኅንነትና የጸጥታ አካላት ጥቆማውን በማቅረብ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ አገልግሎቱ ጥሪ አቅርቧል፡፡

ከፕሌን አልወርድም ... ቲክቶከሩ ጆን ዳንኤል ከ 11 ወር የእስር ቆይታ በኃላ ከእስር መፈታቱ ተሰምቷልDes yilal
07/12/2025

ከፕሌን አልወርድም ...

ቲክቶከሩ ጆን ዳንኤል ከ 11 ወር የእስር ቆይታ በኃላ ከእስር መፈታቱ ተሰምቷል

Des yilal

07/12/2025

OMG !!

07/10/2025
13 ክፍለ ጦር ሰራዊት ቲዲኤፍን ከድቶ ሃራ መሬት የተባለውን ጸረ ህወሓት ታጣቂ ቡድን መቀላቀሉን አመራሮቹ ይፋ አደረጉ፡፡ ታጣቂ ቡድኑ ከመሸገበት አፋር ክልል ወጥቶ ትግራይ መግባቱንም ተናግ...
07/07/2025

13 ክፍለ ጦር ሰራዊት ቲዲኤፍን ከድቶ ሃራ መሬት የተባለውን ጸረ ህወሓት ታጣቂ ቡድን መቀላቀሉን አመራሮቹ ይፋ አደረጉ፡፡ ታጣቂ ቡድኑ ከመሸገበት አፋር ክልል ወጥቶ ትግራይ መግባቱንም ተናግሯል፡፡ በአንድ ቀን እስከ 20 የሚጠጉ የቲዲኤፍ ታጣቂዎች እየተቀላቀሉን ነው ያሉት አመራሮቹ፤ አስር የሚጠጉ ጀነራሎችም ቡድኑን እንደተቀላቀሉ ተናግረዋል፡፡ በሌላ በኩል ጀነራል ታደሰ ወረደ በእኛ በኩል ወደ ማዕከላዊ መንግስቱ ጥይት አንተኩስም ብለዋል፡፡

ትግራይ በአስፈሪ ፖለቲካዊ ሁነት ውስጥ ትገኛለች፡፡ የተከፋፈሉ የትግራይ ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ኃይሎች ለክልሉ ህዝብ አልፎም ለአገሪቱ ስጋትን ደቅነዋል፡፡ ወዲህ የደብረጽዮን እና ጌታቸው ቡድን ተሰንጥቆ የ4ኪሎ እና ሻብያ አጋፋሪ ሆኗል፡፡ ወዲያ ደግሞ የቲዲኤፍ ሰራዊት ለሁለት መከፈሉን ተከትሎ የትግራይ ሰራዊት የእርስ በርስ ውጊያ ለክልሉ ትልቅ ራስ ምታት ሆኗል፡፡

‹ህወሓትን በትጥቅ እጥላለሁ› በሚል በአፋር የመሸገው ሀራ መሬት ወይምት ትግራይ ፒስ ፎርስ አዳዲስ ቀወታደራዊ እንቅስቃሴዎችን እያደረገ ይገኛል፡፡ የታጣቂ ቡድኑ ሁለት አመራሮች ከሰሞኑ በሰጡት አንድ ቃለመጠይቅ 13 የሚሆን ክፍለጦር ቲዲኤፍን ከድቶ እንደተቀላቀላቸው አሳወቅቀዋል፡፡ ሻለቃ አዲስ ወልደገብርኤል እና ሻለቃ እዮብ ሙሉወርቅ የተባሉት የቡድኑ አመራሮች በሰጡት አዲስ ቃለመጠይቅ፣ በሰሜኑ ጦርነት ወቅት በሕወሓት አሳሳችነት በጦርነቱ ተሳትፈናል በሚል በጸጸት ተናግረዋል፡፡ ‹‹ከጦርነቱ በኋላ እኛ ከጫካ ወደ ከተማ ስንገባ እነሱ ወደ ዝርፊያ ገቡ›› በማለት የሐውወሓት የጦር መኮንኖችን ዘልፈዋል፡፡

ህወሓት ስልጣኑን ለወጣት አላስረክብም በማለቱ ነው ለትግል የወጣንው ሲሉ የሚቀጥሉት የታጣቂ ቡድኑ አመራሮች፤ በወታደራዊም በፖለቲካውም መስክ መደራጀታቸውን ገልጸዋል፡፡ ሆኖም የጌታቸው ረዳ ስምረት ፓርቲ የታጣቂ ቡድኑ ፖለቲካዊ ክንፍ እንዳልሆነ አስረግጠዋል፡፡

ሻለቃዎቹ ከስምረት ፓርቲ ጋር ግንኙነት እንደሌላቸው ቢናገሩም፤ የስምረት ፓርቲ አመራሮች ግን የቡድኑ የትግል ምክንያት እንደሚደግፉ በአደባባይ በተደጋጋመ ገልጸዋል፡፡ አንዳነድ የፓርቲው አመራሮችም የቡድኑን ወታደራዊ እንቅስቃሴ በማኅበራዊ ገፃቸው እየተከታተሉ ሲያሰራጩ ይታያል፡፡ የሃራ መሬት ታጣቂ አመራሮች ግን ባሁኑ ወቅት ከስምረት ጋር ግንኙነት እንደሌለው ነው ያሳወቀው፡፡

በርካታ የቲዲኤፍ ወታደሮች ከነመሳሪያቸው ቡድኑን እየተቀላቀሉ ነው ያሉም ሲሆን፤ ባሁኑ ወቅት 13 የሚሆን ክፍለጦር በማይጸብሪ እና በአፋር ክልል ግዛት ማደራጀታቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡ ‹መቀሌን መቆጣጠር ግባችን ነው› የሚለው ቡድኑ፤ 10 የሚሆኑ ጀነራሎች ቡድኑን እንደተቀላቀሉም ይገልጻሉ፡፡ ባኑኑ ወቅት ታጣቂ ቡድኑን ማን እየመራ ነው በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱም፣ ‹‹ባኑኑ ወቅት ጀነራል ወዲ አንጥሩ ታጣቂ ቡድኑን እመሩ ነው፤ የሌሎች አመራሮችን ስም በጊዜው ይፋ እናደርጋለን›› በማለት አብራርተዋል፡፡ ታጣቂ ቡድኑን በመምራት ረገድ ግን ጀነራል ፃድቃን ገብረትንሳኤ እንደሌሉበት ይታወቅልን ብለዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ጀነራል ታደሰ ወረደ በእኛ በኩል ወደ ማዕከላዊ መንግስቱ ጥይት አንተኩስም ብለዋል፡፡ አብይ በሰሞነኛው የፓርላማ ማብራሪያቸው የትግራይ ኃይሎች ለጦርነት እየተጋጁ መሆኑን በመግለጽ ሽማግሌዎች አስቸኳይ አማላጅነት መላካቸው ይታወሳል፡፡ ይህንኑ ተከትሎ የትግራይ ኃይሎች ሕጋዊ ሰውነቱን ካጣው ህወሓት እሰከ ጊዜያዊ አስዳደሩ ፕሬዝዳንት ጀነራል ታደሰ ወረዳ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የጦርነት ስጋት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

ጀነራሉ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ምላሽ “ከውጭ ገፍቶ ካልመጣ በትግራይ በኩል የሚጀመር ጦርነት የለም ብለዋል” ብለዋል፡፡ ጀነራሉ ይሄንያሉት በሰሞነኛው “ዘመቻ አሉላ አባ ነጋ” የተባለው የጦርነት ድል ዝክርና በአስከሬን ማሳረፍ ፕሮግራም ላይ ሲሆን፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩን የጦርነት ስጋት አጣጥለዋል፡፡

የግብፁ ጠ/ሚ ሙስጠፋ ማድቡሊና ጠ/ሚ አብይ አህመድ  በብሪክስ ስብሰባ ላይ...    ምን ቢናገር ነው ? እንደዚህ ላሽ ያለው 😂
07/07/2025

የግብፁ ጠ/ሚ ሙስጠፋ ማድቡሊና ጠ/ሚ አብይ አህመድ በብሪክስ ስብሰባ ላይ... ምን ቢናገር ነው ? እንደዚህ ላሽ ያለው 😂

መፈንቅለ መንግስት በግብፅ መንግስት ላይ ተጠራ የጠ/ሚ አብይ አህመድ  የህዳሴው ግድብ ግንባታ መገባደድ ብስራትና  እሱን ተከትሎ ለነ ግብፅ "የደስታችን ተካፋይ ሁኑ" የሚለው  አሽሙራዊ ጥሪ...
07/06/2025

መፈንቅለ መንግስት በግብፅ መንግስት ላይ ተጠራ

የጠ/ሚ አብይ አህመድ የህዳሴው ግድብ ግንባታ መገባደድ ብስራትና እሱን ተከትሎ ለነ ግብፅ "የደስታችን ተካፋይ ሁኑ" የሚለው አሽሙራዊ ጥሪ ግብፃዊያንን እያሳበደ የሚገኝ ሲሆን በፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ ላይ ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሷል ፣ በአሁን ሰዓትም በርካታ የግብፅ ፖለቲከኞች የአልሲሲ መንግስት ላይ መፈንቅለ መንግስት እንዲደረግ ለህዝቡና ለጦር ሃይሉ ጥሪ የማድረግ ዘመቻ ውስጥ ገብተዋል።

ይህ የህዳሴው ግድብ መጠናቀቅ የአብዱል ፈታህ አልሲሲ መንግስት ላይ ትልቅ አደጋ ይዞ የመጣ ሲሆን የመፈንቅለ መንግስት የመካሄድ ሂደቶች የሚፈጠሩ ከሆነ ግብፅን ወደ 2011G.C የብጥብጥና የእርስ በእርስ ግጭት ዘመን ይመልሳታል የሚል ስጋቶች ተደምጠዋል።

ግብፅ ኢትዮጵያ እንዳትረጋጋ ለሺ ዘመናት ብዙ የግጭት የደም መፋሰስ ድግስ የደገሰች ቢሆንም አሁን ላይ ኢትዮጵያ አባይን ገድባ አጠናቃ የቧንቧውን ቁልፍ በእጇ አስገብታ ፤ የዘመናት የጂኦ ፖሊቲክሱን ወሳኝ ሃይል ተቆጣጥራው የሚገኝ ሲሆን ፣ በተቃራኒው በግብፅ ቤት ትልቅ በየትኛውም ሰዓት ሊፈነዳ የሚችል ውጥረት መፍጠር ጀምሯል።

ኢትዮጵያዊነት Ethiopiawinet

የብሪክስ መድረክ ዓለም አቀፋዊ ትብብርን በማሳደግ ረገድ ጠቃሚ ሆኖ ቀጥሏል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመ...
07/06/2025

የብሪክስ መድረክ ዓለም አቀፋዊ ትብብርን በማሳደግ ረገድ ጠቃሚ ሆኖ ቀጥሏል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የብሪክስ መድረክ የጋራ የልማት እና ዓለም አቀፋዊ ትብብርን በማሳደግ ረገድ ጠቃሚ ሆኖ ቀጥሏል አሉ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት÷ ከብሪክስ መሪዎች ጋር በሪዮ ዲ ጄኒሮ በዚህ ዓመቱ ጉባኤ ላይ ተገኝተናል ብለዋል።

የበለጠ እኩልነት እና ፍትኅ የሰፈነበት ዓለም ለማግኘት ትስስራችንን የበለጠ እናጠናክራለን በማለት ገልጸው፤ የብሪክስ መድረክ የጋራ የልማት እና ዓለም አቀፋዊ ትብብርን በማሳደግ ረገድ ጠቃሚ ሆኖ ቀጥሏል ነው ያሉት፡፡

Address

Forest Heights, MD

Telephone

+251948830777

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Naod Tube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Naod Tube:

Share