Naod Tube

Naod Tube like like

 ‼️ላለፉት አምስት አስርት አመታት ትግራይን በጦርነት አዙሪት ውስጥ ሲያተራምስ የቆየው ህወሀት አሁን ደግሞ “ትግራይ ላይ ብሄራዊ ስጋት ተጋርጧል” በሚል የጦርነት ቅስቀሳ ሰነድ እያዘጋጀ ስ...
12/28/2025

‼️

ላለፉት አምስት አስርት አመታት ትግራይን በጦርነት አዙሪት ውስጥ ሲያተራምስ የቆየው ህወሀት አሁን ደግሞ “ትግራይ ላይ ብሄራዊ ስጋት ተጋርጧል” በሚል የጦርነት ቅስቀሳ ሰነድ እያዘጋጀ ስለመሆኑ ከቡድኑ ሾልኮ የወጡ መረጃዎች እያሳዩ ነው፡፡

ሰነዱ በእነ ጄ/ል ምግበይ ሃይለ እና ጄ/ል ፍሰሃ ማንጁስ አማካኝነት የተዘጋጀ ስለመሆኑ ምንጮች ያረጋገጡ ሲሆን አሁን የማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝም ታውቋል።

በሰነዱ ላይ ቡድኑ እያደረገ ለሚገኘው የጦርነት ዝግጅት ስጋት ይሆኑብኛል የሚላቸውን የታጣቂ አመራሮች እንዴት እንደሚያስወግዳቸው እንዲሁም ታጣቂ ቡድኑ ያጣውን ህዝባዊ አመኔታ በመመለስ ህዝቡን እንዴት ለጦርነት ማዘጋጀት እንደሚችል የሚያትት መሆኑም ታውቋ፡፡

የትግራይ ክልል አሁናዊ የፀጥታ ሁኔታ 👉 በትግራይ ክልል የሚገኙ ነጋዴዎች “የፌዴራል መንግስት ውሳኔ በስራችን ላይ ጫና ፈጥሮብናል” በሚል በታህሳስ 21/2018 ዓ.ም ክልል አቀፍ ሰላማዊ ሰ...
12/27/2025

የትግራይ ክልል አሁናዊ የፀጥታ ሁኔታ

👉 በትግራይ ክልል የሚገኙ ነጋዴዎች “የፌዴራል መንግስት ውሳኔ በስራችን ላይ ጫና ፈጥሮብናል” በሚል በታህሳስ 21/2018 ዓ.ም ክልል አቀፍ ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ በየወረዳዎች ቅስቀሳ እና ዝግጅት እየተደረገ ነው ፤

👉 የታጣቂ ቡድኑ ከፍተኛ አመራሮች “ትግራይ የብሄራዊ ህልውና ስጋት” ተጋርጦባታል የሚል መነሻ ያለው በፅንፈኛው ቡድን የፖለቲካ እና ወታደራዊ ዶክትሪን ላይ ያተኮረ ስትራቴጂክ እቅድ ትንተና ሰነድ ዝግጅት እያስቀጠሉ ነው ፤

👉 የአርሚ 11 እና 17 ታጣቂ አመራሮች የዋልድባ አካባቢ የሽፍታ እና ሚሊሻ ታጣቂዎችን በማይተክሊት፣ ማይፀብሪ ዙሪያ እና ተከዜ ወንዝ ዳርቻ አካባቢዎች በማሰማራት የሀራ መሬት ታጣቂ እና የመከላከያ ሰራዊት ስምሪት ላይ የሚያደርጉትን ክትትል አስቀጥለዋል::

👉 የምዕራብ ግንባር አዛዥ ጀ/ል ምግበይ ሃይለ ከታህሳስ 14-16/2018 ዓ.ም በሽሬ ከተማ ባካሄደው የግንባሩ ከፍተኛ የታጣቂ አመራሮች ስብሰባ ላይ የፅንፈኛው የህወሃት ቡድንን ፍላጎት የሚቃረን ሀሳብ ያነሱ የታጣቂ አመራሮች ላይ ጥብቅ ክትትል እና እርምጃ እንዲወሰድ ትእዛዝ እየሰጠ ነው።

12/26/2025

የሻብያ ጦር ትንኮሳ በቡሬ

የኤርትራ ጦር ድንበር ተሻግሮ በቡሬ ድንበር ትንኮሳ እየፈጸመ መሆኑን የሚገልጽ መረጃ ከስፍራው ወጥቷል፡፡ ጦሩ ወደ አፋር ክልል በመግባት ትንኮሳ እያደረገ ነው ተብሏል፡፡

ሻብያ አላርፍ ብሏል፡፡ በአፈቀላጤው አቶ የማነ በኩል እኛ የምንፈልገው ሰላም ነው ቢልም፤ በተግባር ግን ጸብ አጫሪ ድርጊቱን ቀጥሎበታል፡፡ ዛሬ በወጣ መረጃም የሻብያው ጦር በአፋር ግዛት ተሻግሮ በመግባት ትንኮሳ እየፈጸመ እንደሆነ አረጋግጧል፡፡ የኤርትራ ጦር ወደ አፋር ክልል ድንበር አካባቢዎች ሰርጎ በመግባት ወታደራዊ ትንኮሳ እየፈጸመ መሆኑን አዲስ ሪፖርተር ድህረ ገጽ ዘግቧል። ዜናው ሕውሓት “ትዕግስቴ አልቋል” በማለት መግለጫ ከማሰራጨቱ ጋር የተናበበ እንደሆነ ተመልቷል።

የሻብያ ጦር ወደ ኢትዮጵያ ግዛት ዘልቆ ትንኮሳ እፈጸመባቸው ካሉ አካባቢዎች መሀል ቡሬ፣ ደናክል፣ ጋረቦ እና አዋላ ይጠቀሳሉ፡፡ ዘገባው እንዳለው፣ በተለይም በቡሬ አፋር ድንበር አቅጣጫ የኤርትራ ጦር ከፍተኛ ወታደራዊ ንቅናቄ እያደረገ ነው ብሏል፡፡ የኤርትራ ወታደሮች በአካባቢው ሰላማዊ የአፋር ዜጎችን በማዋከብና የክልሉን ድንበር ለመዳፈር ሙከራ ማድረጉን ተከትሎ ክልሉ ድርጊት በአስቸኳይ ካልቆመ ራሱን ለመከላከል አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስድ እንዲሁም የፌዴራል መንግስት ጉዳዩን በቅርበት እንዲከታተል በአሰራሩ አግባብ ጥሪ ማቅረቡ ተሰምቷል።

ሰበር ጀነራሉ ብልጽግናን ጠላት ሲሉ ፈረጁጨዋታው አብቅቷል፤ ጦርነቱ ቀርቧል ሲሉ ጀነራሉ ተናገሩ፡፡ ብልጽግናን ጠላት ሲሉ የገለጹት የትግራዩ ጀነራል፤ ተፈናቃዮችን ይዘን በኃይል እንገባለን ሲ...
12/25/2025

ሰበር

ጀነራሉ ብልጽግናን ጠላት ሲሉ ፈረጁ

ጨዋታው አብቅቷል፤ ጦርነቱ ቀርቧል ሲሉ ጀነራሉ ተናገሩ፡፡ ብልጽግናን ጠላት ሲሉ የገለጹት የትግራዩ ጀነራል፤ ተፈናቃዮችን ይዘን በኃይል እንገባለን ሲሉ ጠንካራ አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ እያሸበሩን ነው ያሏቸውን አካላት ደግሞ እጃቸው ይቆረጣል በሚል ዝተዋል፡፡

በራያ ግንባር የተሰማራውን የህወሓት ኃይል የሚመሩት ጀነራል ዩሀንስ ወልደ ጊዮርጊስ ወይም በቅጽል ስማቸው ጆን መዲድ ጨዋታው አብቅቷል፣ ጦርነቱም ተቃርቧል ብለዋል፡፡ ጀነራሉ እንደተለመደው ብልጽግና ፓርቲን በጠላትነት ፈርጀው የፕሪቶሪያውን ስምምነት መዘባበቻ እንዲሆን አድርጓል በማለት ወንጅለዋል፡፡ ጀነራሉ ይሁን ያሉት ከሰሞኑ መነጋገሪያ ስለሆነው የትግራይ ተፈናቃዮች ረሀብ ጉዳይ በማይጨው ከተማ በተደረገ ስብሰባ ላይ ነው፡፡

አንዳፍታ ሚዲያ በተመለከተው እና የሕውሓት ልሳን በሆነው ዎይን ድህረገጽ ላይ በተሰራጨው የጀነራሉ ንግግር እንደተመላከተው፣ “በጠላቶቻችን በኩል የፕሪቶሪያ ስምምነት መዘባበቻ ሆኗል፤ ጨዋታው አብቅቷል” በማለት ተደምጠዋል። ከተፈናቃዮች ጋር በተያያዘ “እኛ እንደ ሠራዊት ማንኛውንም እርዳታ ጭነን ሳይሆን የምንመጣው፣ እናንተን ጭነን ነው ወደ ቤታችሁ የምንመልሳችሁ” ሲሉም አክለዋል፡፡ እንደ ጀነራሉ ገለጻ ተፈናቃዮችን በኃይል ወደ ወልቃይት ወይም ምእራብ ትግራይ የመመለስ ጉዳይ በሁኑ ወቅት በህወሓት አመራር እየታሰበበት ያሉ ጉዳይ ነው፡፡ ጀነራል ታደሰ ወረደ ከትናንት በስትያ በሰጡት መግለጫ ተፈናቃዮች ካልተመለሱ ጦርነት ማስቀረት አይቻልም ማለታቸውን ዘግበን ነበር፡፡

ጀነራል ዩሀንስ ወልደጊዮርጊስ አክለውም አንድ እግራቸውን ውጪ አድርገው በትግራይ ክልል አመጽ ለመፍጠር የሚሞከሩ አካላትን እጅ እንቆርጣለን የሚል ማስጠንቀቂያ አሰምተዋል፡፡ አፋር ክልል ተቀምጠው ትግራይን መረበሽ የሚልጉ ያሏቸውን ኃይሎችን በሽምግልና የማይገቡ ከሆነ እርምጃ እንደሚወሰድባቸው አስጠንቅቀዋል፡፡

የትግራይ ሕዝብ በረሀብ አለንጋ እየተገረፈ ቢሆንም ሕወሓት አሁንም የጦር ድቤ ድለቃውን ተያይዞታል።

"እኛ ከወንድሞቻችን ኢትዮጵያዊያን ጋር ምንም አይነት ችግር የለብንም" ሲሉ የግብፁ ፕሬዝደንት ተናገሩ፡፡   | በካይሮ የአፍሪካ ሩሲያ የትብብር ፎረም መካሄድ መጀመሩን ትላንት በዘሀበሻ መዘ...
12/21/2025

"እኛ ከወንድሞቻችን ኢትዮጵያዊያን ጋር ምንም አይነት ችግር የለብንም" ሲሉ የግብፁ ፕሬዝደንት ተናገሩ፡፡

| በካይሮ የአፍሪካ ሩሲያ የትብብር ፎረም መካሄድ መጀመሩን ትላንት በዘሀበሻ መዘገባችን ይታወሳል፡፡

በዚህ ስብሰባ ላይ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጄይ ላቭሮቭና በርካታ የሩሲያ ዲፕሎማቶች የተገኙ ሲሆን የ50 የአፍሪካ አገራት ሚኒስትሮችም ተሳታፊ መሆናቸውን ገልፀን ነበር፡፡ ይህ ፎረም ዛሬም ቀጥሎ ሲቀጥል የግብፁ ፕሬዝደንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ ተገኝተው ለተሳታፊዎች ንግግር አድርገዋል፡፡

በዚህ ንግግራቸው ላይ ስለኢትዮጵያም አንስተው ነበር፡፡ አል ሲሲ ሲናገሩ ‹‹ግብፅ ከኢትዮጵያዊያን ወንድሞቿ ጋር ምንም አይነት ችግር የለባትም፡፡ እንዲሁም ከኢትዮጵያዊያን ጋር ግጭት ውስጥ መግባትም ሆነ ጥላቻ ማስፈን አትሻም›› ብለዋል፡፡

ጨምረውም ‹‹የግብፅ ዋነኛ ጥያቄ በአባይ ወንዝ ላይ ያላት የውሀ መብቷ እንዳይጎዳ ብቻ ነው፡፡ ይህንን መብቷን ለማስጠበቅ ደግሞ በህዳሴው ግድብ ላይ ህጋዊና አሳሪ ስምምነት ላይ መድረስ አስፈላጊ ነው፡፡ ስምምነቱ ለሁሉም አካላት ዋስትና የሚሰጥ ይሆናል›› በማለት ገልፀዋል፡፡

ፕሬዝደንት አል ሲሲ ንግግራቸውን ሲቀጥሉም ‹‹የግብፅ ፖሊሲ ወጥነት ያለውና በየትኛውም አገር ውስጣዊ ጉዳይ ላይ ያለመግባት ላይ የተመሰረተ ነው፡፡ በሌሎች አገራት ውስጥ መተራመስ እንዲፈጠር የሚያደርግ ፖሊሲም የላትም፡፡

ምንም እንኳ እኛ ከኢትዮጵያ ጋር አለመግባባት ቢኖረንም ፈፅሞ ለኢትዮጵያ ስጋት የሚሆን ነገር ፈጥረን አናውቅም›› በማለት ገልፀው ግብፅ ማንኛውም አለመግባባት በውይይትና በፖለቲካዊ መፍትሄ እንጂ በግጭት ወይንም በሀይል ይፈታል የሚል እምነት እንደሌላት አስታውቀዋል፡፡

ጌራ ወርቅ ዘመነ ላይ ተኮሰበት!!ጌራወርቅ ወርቁ ማለት የፋኖ ታጣቂዎች ዘንድ ትልቅ የሆነ አክብሮት የሚሰጠው እና የሚወደድ ሰው ነው።ለዚህ ደግሞ ዋናው ምክንያት ጌራወርቅ ሁሌም ቢሆን ጥፋት ...
12/21/2025

ጌራ ወርቅ ዘመነ ላይ ተኮሰበት!!

ጌራወርቅ ወርቁ ማለት የፋኖ ታጣቂዎች ዘንድ ትልቅ የሆነ አክብሮት የሚሰጠው እና የሚወደድ ሰው ነው።ለዚህ ደግሞ ዋናው ምክንያት ጌራወርቅ ሁሌም ቢሆን ጥፋት ሲኖር ፊት ለፊት ተናግሮ ነገሩ እንዲስተካከል የሚሞክር እውነተኛ ሰው ስለሆነ ነው።

ታዲያ ጌራወርቅ የጎጃም ፋኖ በነዘመነ ካሴ ትዕዛዝ ከዚህ በፊት የተሰሩ ለአይን እና ጆሮ የሚዘገንኑ ድርጊቶችን አበክሮ ሲቃወም የነበረ ሰው ነው።በተለይ የተማረ ሰው ጎጃም ውስጥ መኖር የለበትም ብለው እነ ዘመነ ትምህርት ቤት ሲያወድሙ፣መምህር እና ተማሪ በቁም አቃጥለው ሲገሉ ተቃውሟል።

ከዚህ በተጨማሪም የቤተ ክርስቲያን ፅላት በነዘመነ ተዘርፎ ሲሸት፣ሴቶች ሲደፈሩ፣የጎጃም አርሶ አደር ላቡን አፍሶ ያገኘውን እህል እና ከብት ሲዘርፍትም ጌራወርቅ ይህ ድርጊት መቆም አለበት በማለት እነ ዘመነን ሲቃወም ቆይቷል።

ታዲያ አሁን ላይ ጎጃም ውስጥ በነዘመነ አማካኝነት የሚደረገው ሀጢያት እየባሰበት በመሄዱ ይህ ደግሞ እንዲቆም በማሰብ ጌራወርቅ ዘመነ ላይ ተኩሶበታል።በዚህም ከዉልደት እስከ እድገት የድንቁርና ጡጦ ሲጠባ ያደገ ዘመነ ካሴ መሪ ሊሆን አይችልም፤ በድንገት እና በአጋጣሚ የተረገመች ወንበር ላይ ቢቀመጥ አጥፍቶ እና አበላሽቶ መጥፎ ታሪክ እየፃፈ ነው ሲል ጌራወርቅ ዘመነ ላይ በብዕሩ በመተኮስ ጎጃም ውስጥ ፋኖ እያደረገ ያለውን ሀጢያት መቆም እንዳለበት አሳውቋል።

Address

Houston, TX
0000

Telephone

+251948830777

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Naod Tube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Naod Tube:

Share