Naod Tube

Naod Tube like like

ሰበር!በጎንደር የቦምብ ጥቃት!​በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ትላንት ምሽት የአርሴናል እና ፒኤስጂ የቻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ በፕሮጀክተር ሲተላለፍ በነበረበት ወቅት በተከሰተ የቦምብ...
05/31/2026

ሰበር!

በጎንደር የቦምብ ጥቃት!

​በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ትላንት ምሽት የአርሴናል እና ፒኤስጂ የቻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ በፕሮጀክተር ሲተላለፍ በነበረበት ወቅት በተከሰተ የቦምብ ፍንዳታ የተማሪዎች ህይወት ማለፉና በርካቶች መጎዳታቸው ታውቋል።

​ፍንዳታው የተከሰተው የመጀመሪያው አርባ አምስት ደቂቃ ሊጠናቀቅ ሲል ሲሆን፣ በአዳራሹ ውስጥ በነበረው ከፍተኛ መጨናነቅ ምክንያት በተፈጠረ መረጋገጥም ተጨማሪ ጉዳት ደርሷል።

​የተማሪዎች ህብረት አመራሮች እና የከተማው ነዋሪዎች እንደገለጹት፣ በጥቃቱ የሁለት ወይም የሶስት ተማሪዎች ህይወት አልፏል።

የሟቾች አስክሬን ዛሬ ጠዋት ወደ ቤተሰቦቻቸው የተሸኘ ሲሆን፣ ከ30 በላይ የሚሆኑ የቆሰሉ ተማሪዎች በካምፓሱ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል።

​አሁን ላይ ፖሊስ በካምፓሱ ገብቶ የፍንዳታውን መንስኤ እያጣራ ሲሆን፣ በካምፓሱ ውስጥ የሀዘን ድባብ ሰፍኖ ይገኛል።

ሰበር ዜናዲያቆን ዳንኤል ክብረት ከስልጣን ተነሱ!የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ እና የቅርብ ሰው ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ከስልጣን መነሳታቸውን መሰረት ሚዲያ ዘግቧል። ዲያቆን ዳንኤል የፋና ብሮድ...
05/27/2026

ሰበር ዜና

ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ከስልጣን ተነሱ!

የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ እና የቅርብ ሰው ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ከስልጣን መነሳታቸውን መሰረት ሚዲያ ዘግቧል። ዲያቆን ዳንኤል የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የቦርድ ሰብሳቢ የነበሩ ሲሆን፤ ከተቋሙ ሰራተኞች በተነሳባቸው ቅሬታ ምክንያት ከቦርድ ሰብሳቢነታቸው ተነስተዋል ሲል የዜና ጣብያው ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል። በምትካቸውም የኮሙኒኬሽን ሚኒስትሯ ወይዘሯ እናትአለም መለስ ተተክተዋል። ይህን የስልጣን ሽግሽግ በተመለከተ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽንም ሆነ ከመንግሥት በኩል የተባለ ነገር የለም።

የጀነራሉ እገታ እና ያሉበት መታወቅ!ጀነራሉ መታገታቸው ተረጋገጠ፡፡ አንድ ወር ለሚሆን ጊዜ ከአደባባይ የጠፉት ጀነራሉ፤ መታገታቸውን የፈረንሳዩ ጋዜጣ ይፋ አድርጓል፡፡ ጀነራሉ ወደ አዲስአበባ...
05/27/2026

የጀነራሉ እገታ እና ያሉበት መታወቅ!

ጀነራሉ መታገታቸው ተረጋገጠ፡፡ አንድ ወር ለሚሆን ጊዜ ከአደባባይ የጠፉት ጀነራሉ፤ መታገታቸውን የፈረንሳዩ ጋዜጣ ይፋ አድርጓል፡፡ ጀነራሉ ወደ አዲስአበባ እንዳይጓዙ እና ለፌዴራል መንግስት ባለስልጣናት ጋር እንዳይገናኙ በሚል ነው የታገቱት ተብሏል፡፡

ጀነራሉ ታግተዋል፡፡ የተረጋገጠ መረጃ ነው፡፡ ህውሃት ከአንድር ወር በፊት ደብረጽዮን ገብረሚካኤልን ፕሬዝዳንት አድርጎ ጀነራል ታደሰ ላይ መፈንቅለ መንግስት ካከናወነ በኋላ፤ ጀነራሉ ጠፍተው ከርመዋል፡፡ ከዚህ የመፈንቅለ አስተዳደር በኋላ በአደባባይ ያልታዩት ጀነራል ታደሰ፤ የት ጠፉ በሚልም ብዙ ሲጠየቅ ነበር፡፡ ለዚህ ጥያቄ መልስ የሚሆን መረጃ ዛሬ ይፋ ሆኗል፡፡

ታማኙ የፈረንሳይ ጋዜጣ አፍሪካን ኢንተለጀንስ ስለ ጉዳዩ ሰማሁት ያለውን መረጃ ምንጮቹን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል፡፡ ጀነራል ታደሰ ወረደ ከመቀሌ እንዳይወጡ እና እንዳይንቀሳቀሱ ታግተው እንደሚገኙ አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡ ‹‹ጀነራሉ ወደ አዲስአበባ እንዳይጓዙ በዚያም ከፌዴራል ባለስልጣናት ጋር እንዳይገናኙ በሚል በህውሃት ቁጥጥር ስር ናቸው›› በማለት ዘግቧል፡፡

የአፍሪካን ኢንተለጀንስ ዘገባ እንደሚያመላክተው፣ ይህ እገዳ የተጣለው በጀነራል ፃድቃን ገብረትንሳኤ እና ጌታቸው ረዳ አሰባሳቢነት ባለፈው ሳምንት በአዲስአበባ ምክርቤት መመስረቱን ተከትሎ ነው፡፡ የእነ ጀነራል ፃድቃን የአዲስአበባው ምክርቤት ሕውሓትን ባጭር ጊዜ አስወግዶ ክልሉን ለመቆጣጠር አቅዷል፡፡ ህውሓት ጀነራል ታደሰ ወደ አዲስአበባ ኮብልለው ከአዲሱ ምክርቤት ጋር እዳይቀላቀሉ በሚል ነው ጀነራል ታደሰን የቁም እስረኛ ያደረጋቸው ብሏል ዘገባው፡፡ ጀነራሉ ብዙ ሚስጥር የሚያውቁ እና ህውሃት አደጋ ላይ ሊጥሉ የሚችሉ ሰው በመሆናቸው እንደሆነ ጋዜጣው አብራርቷል፡፡

ከአፍሪካን ኢንተለጀንስ መረጃ መረዳት እንደተቻለው ህውሓት ጀነራሉን ለማገት የወሰነው በሁለት አበይት ምክንያቶች ናቸው፡፡ አንደኛው ጀነራሉ የእነፃድቃንን ምክርቤት እንዳይቀላቀሉ በሚል ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ ጀነራሉ እጅ ላይ በርካታ የሕውሓት ሚስጥሮች በመኖራቸው ነው፡፡

ሰበር ዜናአሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የነበረውን የጦር መሳሪያ ገደብ አነሳችዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ተጥሎ የነበረውን የጦር መሳሪያ ገደብ እና ከደህንነት ዘርፍ ጋር የተያያዙ እገ...
05/12/2026

ሰበር ዜና

አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የነበረውን የጦር መሳሪያ ገደብ አነሳች

ዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ተጥሎ የነበረውን የጦር መሳሪያ ገደብ እና ከደህንነት ዘርፍ ጋር የተያያዙ እገዳዎችን ማንሳቷ ተሰምቷል። ይህ እርምጃ በሁለቱ ሀገራት መካከል የነበረውን የዲፕሎማሲ ግንኙነት ወደ ተሻለ ደረጃ ለማምጣት የተወሰደ መሆኑ ተገልጿል።

አሜሪካ እገዳውን የጣለችው በ2021 በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሄደው የትግራይ ጦርነት ወቅት ነበር። በወቅቱ ዋሽንግተን በጦርነቱ ዙሪያ በተነሱ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እና የሰብዓዊ ቀውስ ምክንያት የጦር መሳሪያ ሽያጭን እና የደህንነት ትብብርን ገድባ ነበር።

አሁን ግን የአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ያለው የፀጥታ ሁኔታ፣ የቀይ ባሕር የንግድ መስመር ጠቀሜታ እና የኢትዮጵያ በቀጠናው ያላት ስትራቴጂካዊ ሚና አሜሪካን አዲስ ውሳኔ እንድትወስድ እንዳደረጋት ተንታኞች ይናገራሉ።

የአሜሪካ መንግሥት በተለይ “በአፍሪካ ቀንድ የሚፈጠሩ የፀጥታ ችግሮችን ለመቆጣጠር ከኢትዮጵያ ጋር ያለው ትብብር አስፈላጊ ነው” የሚል አቋም መያዙ ተጠቁሟል።

ድንበር ላይ ውጊያ ተቀስቅሷል‼️የሱዳኑ ጦርነት ወደ ኢትዮጵያ ድንበር እየተስፋፋ መሆኑን የሚያሳዩ መረጃዎች ወጥተዋል።የሱዳን መንግሥት በኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ ፈፀምኩት ባለው ጥቃት ሁለት...
05/10/2026

ድንበር ላይ ውጊያ ተቀስቅሷል‼️
የሱዳኑ ጦርነት ወደ ኢትዮጵያ ድንበር እየተስፋፋ መሆኑን የሚያሳዩ መረጃዎች ወጥተዋል።
የሱዳን መንግሥት በኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ ፈፀምኩት ባለው ጥቃት ሁለት የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር ካምፖችን ከጥቅም ውጪ ማድረጉን አሳውቋል።
የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦርም በርካታ የድሮን ጥቃት መፈፀሙን ገልጿል።
ለኢትዮጵያ ቅርብ በሆነው የሱዳን ብሉናይል ግዛት ከባድ ውጊያ እየተደረገ ይገኛል። ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ እና የሱዳን ጦር ስትራቴጂክ ስፍራዎችን ለመቆጣጠር እየተጋደሉ ነው።

በውጊያው SPLMO ተብሎ የሚጠራው የደቡብ ሱዳን አማጺ ከሄሜቲ ጦር ጋር ተሰልፏል።
በተጨማሪ ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ከአሶሳ በኩል ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ የሱዳን ምንጮች ዘግበዋል።
የሱዳን መንግሥት ከትናንት በስተያ ጀምሮ ወደ ኢትዮጵያ ድንበር ተጨማሪ ጦር እና መሳሪያ መላኩን መዘገባችን ይታወሳል።

ሌ/ጀ ታደሰ ወረደ ማስጠንቀቂያ ሰጡ‼️በትግራይ ክልላዊ መንግሥት ውስጥ ያለው የውስጥ የሥልጣን ሽኩቻ ወደ ከረረ ደረጃ መሸጋገሩን ተከትሎ፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት ሌተናል ጄነራል ታደ...
05/08/2026

ሌ/ጀ ታደሰ ወረደ ማስጠንቀቂያ ሰጡ‼️
በትግራይ ክልላዊ መንግሥት ውስጥ ያለው የውስጥ የሥልጣን ሽኩቻ ወደ ከረረ ደረጃ መሸጋገሩን ተከትሎ፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ የተቃውሞ መግለጫ አወጡ።

ዛሬ ሚያዝያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም "ተመርጠናል" የሚሉ አካላት በጸጥታ ኃይሎች ታጅበው በጊዜያዊ አስተዳደሩ የካቢኔ አዳራሽ ስብሰባ መጀመራቸውን ገልጸዋል። ድርጊቱ "የሥልጣን ወረራ" መሆኑን የጠቀሱት ጄነራሉ፣ ለሚከተለው ማንኛውም ዓይነት ቀውስ ተጠያቂው ይህ በጉልበት ሥልጣን ለመያዝ የሚንቀሳቀሰው አካል መሆኑን አስታውቀዋል።

በወንጀል ተፈላጊዎች (wanted)
05/08/2026

በወንጀል ተፈላጊዎች (wanted)

ልዩ መረጃ!‹‹ተዘጋጅተናል..›› ጀነራል አበባው ታደሰ በጦር ግንባር ታዩ! የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሰ በሰሜን ምእራብ ዕዝ ጉብኝት እያደረጉ መሆኑ ታው...
05/07/2026

ልዩ መረጃ!

‹‹ተዘጋጅተናል..›› ጀነራል አበባው ታደሰ በጦር ግንባር ታዩ!



የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሰ በሰሜን ምእራብ ዕዝ ጉብኝት እያደረጉ መሆኑ ታውቋል፡፡ ፊልድ ማርሻል ብርሓኑ ጁላ የላኩትን መልዕክትም ለሰራዊቱ ማድረሳቸውን አንዳፍታ ሚዲያ ከሰራዊቱ ድህረገጽ ተመልክቷል፡፡

በፌዴራል መንግስቱ እና በሕውሓት ኃይሎች መካከል ያለው ውጥረት ባየለበት በዚህን ወቅት፤ ጀነራሉ የሰራዊቱን የግዳጅ ዝግጁነት ለመመልከት በሰሜን ምእራብ ዕዝ ተገኝተዋል፡፡ ጀነራሉ በግንባር የሚገኙ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ የጦር ክፍሎችን ወታደራዊ ፣አካላዊና ስነ-ልቦናዊ ዝግጁነት ተዘዋውረው ተመልክተዋል የተባለ ሲሆን፤ እንዲህ የሚል መልዕክትም አስተላልፈዋል፡- ‹‹ዕዙ ከታሪካዊ ጠላቶቻችንም ይሁን ከባንዳዎች ሊሰነዘር የሚችል ጥቃትን መመከትና መደምሰስ በሚያስችለው የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል›› የሚል። ጀነራል አበባው ‹ባንዳ› ሲሉ የጠሯቸውን አካላት በስም ባይጠሩም፤ ከዚህ ቀደም በመከላከያ አመራሮች ‹ባንዳ› በሚል የሚጠራው በአካባቢው ያለው ኃይል ግን የፋኖ አማጺ ቡድን እንደሆነ ይታወቃል፡፡

ጀነራሉ በዚህ ንግግራቸው ቀጥለውም፣ የሰሜን ምእራብ እዝን፣ ‹‹የህወሃትን አገር የማፍረስ ተከታታይ ወረራ በመመከትና ሀገርን በማፅናት ትልቅ ሚና የነበረው ጠንካራ ዕዝ›› በማለት አሞካሽተውታል፡፡ ‹‹ሰሜን ምዕራብ ዕዝ በአማራ ክልል ግጭትና ሁከት ለመፍጠር በተንቀሳቀሰው የሀገር ውስጥ ባንዳ በሆነው ፅንፈኛው ቡድን ላይ ጠንካራ ምት በማሳረፍ ያሰበውን ኢትዮጵያን የማጥፋት ሴራ በማክሸፍ ፅንፈኛው ቅስሙ እንዲሰበር እና እጅ እንዲሰጥ በማድረግ ወገን የኮራበት፤ ጠላት ያፈረበትን ከፍተኛ ስራ የሰራ ዕዝ ነው›› ሲሉም አክለዋል፡፡

ጄኔራል አበባው ታደሠ ከሠራዊቱ ጋር በነበራቸው ቆይታ ‹‹ኢትዮጵያና ተቋሙ ይኮሩባችኋል›› ሲሉም የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላን መልዕክት አስተላልፈዋል።

05/05/2026

ዛሬ የኢትዮጵያ አየር ሃይል ጀቶችና ድሮውን በትግራይ ክልል ቅኝት ሲያደርጉ ነው የዋሉት:: ይህ በእንዲህ እንዳለ ትናት ምሽት ላይ የትግራይ ክልል ግዚያዊ አስተዳደር ቢሮ አካባቢ በፈነዳው ቦምብ ምክንያት ዛሬ ወደ ትግራይ ክልል ግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ታደሰ ወረደ ቢሮ የሚሄዱ መንገዶች ሙሉ በሙሉ ተዘግተው ነው የዋሉት::

NewsAlert ‼️በመቐለ ዛሬ ምሽት የቦምብ ፍንዳታ መድረሱን የከተማይቱ ፖሊስ አረጋገጠበትግራይ ክልል፣ መቐለ ከተማ፣ ዛሬ ምሽት ሁለት ሰዓት ገደማ የቦምብ ፍንዳታ መከሰቱን ታውቋል። ፍንዳ...
05/04/2026

NewsAlert ‼️በመቐለ ዛሬ ምሽት የቦምብ ፍንዳታ መድረሱን የከተማይቱ ፖሊስ አረጋገጠ

በትግራይ ክልል፣ መቐለ ከተማ፣ ዛሬ ምሽት ሁለት ሰዓት ገደማ የቦምብ ፍንዳታ መከሰቱን ታውቋል። ፍንዳታው የደረሰው በትግራይ ክልል ምክር ቤት እና በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት መካከል ባለ ቦታ ላይ እንደሆነ ተገልጿል:: በፍንዳታው እስካሁን በሰውና በንብረት ላይ ጉዳት እንደደረሰ አልታወቀም

Address

Houston, TX
0000

Telephone

+251948830777

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Naod Tube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Naod Tube:

Share