05/31/2026
ሰበር!
በጎንደር የቦምብ ጥቃት!
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ትላንት ምሽት የአርሴናል እና ፒኤስጂ የቻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ በፕሮጀክተር ሲተላለፍ በነበረበት ወቅት በተከሰተ የቦምብ ፍንዳታ የተማሪዎች ህይወት ማለፉና በርካቶች መጎዳታቸው ታውቋል።
ፍንዳታው የተከሰተው የመጀመሪያው አርባ አምስት ደቂቃ ሊጠናቀቅ ሲል ሲሆን፣ በአዳራሹ ውስጥ በነበረው ከፍተኛ መጨናነቅ ምክንያት በተፈጠረ መረጋገጥም ተጨማሪ ጉዳት ደርሷል።
የተማሪዎች ህብረት አመራሮች እና የከተማው ነዋሪዎች እንደገለጹት፣ በጥቃቱ የሁለት ወይም የሶስት ተማሪዎች ህይወት አልፏል።
የሟቾች አስክሬን ዛሬ ጠዋት ወደ ቤተሰቦቻቸው የተሸኘ ሲሆን፣ ከ30 በላይ የሚሆኑ የቆሰሉ ተማሪዎች በካምፓሱ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል።
አሁን ላይ ፖሊስ በካምፓሱ ገብቶ የፍንዳታውን መንስኤ እያጣራ ሲሆን፣ በካምፓሱ ውስጥ የሀዘን ድባብ ሰፍኖ ይገኛል።