Naod Tube

Naod Tube like like

ሰበር ሞንጆሪኖ ተመታ ሆስፒታል መግባቷ ታወቀ!የህወሃት ቡድን ቁልፍ አመራር የሆነችው ሞንጆሪኖ በከባድ ሁኔታ ተመታለች ተብሏል። ሞንጆሪኖ በአሁኑ ሰኣት በመቀሌ ከተማ (ቀበሌ 18 / አዲሃቂ ...
09/03/2026

ሰበር

ሞንጆሪኖ ተመታ ሆስፒታል መግባቷ ታወቀ!

የህወሃት ቡድን ቁልፍ አመራር የሆነችው ሞንጆሪኖ በከባድ ሁኔታ ተመታለች ተብሏል። ሞንጆሪኖ በአሁኑ ሰኣት በመቀሌ ከተማ (ቀበሌ 18 / አዲሃቂ ክፍለ ከተማ) በሚገኘው ‘አልላ’ የግል ሆስፒታል መግባቷ ታውቋል።

የሆስፒታሉ 2ኛ ብሎክ በከፍተኛ ሁኔታ በታጠቁ በህወሃት ሃይሎች ተከቦ የሚገኝ ሲሆን፣ ማንኛውም ሰው ወደ ስፍራው እንዳይጠጋ ተከልክሏል።

በመቀሌ እና በዙሪያዋ ያሉ የውስጥ መረጃ ምንጮቻችን እንደጠቆሙት፣ የጥፋት ቡድኑ ከፍተኛ ውጥረት እና የሞራል ውድቀት ውስጥ እንደሚገኝ ታውቋል።

አዲስ አበባ ገብቷል‼️በፋኖ ትግል ውስጥ ትልቅ አመራር የነበረው በተለይም የጎጃም ፋኖ ቃል አቀባይ በመሆን ለብዙ ጊዜ ትግሉን ሲመራ የቆየው ማርሸት ፀሀዩ ትናንት ነሐሴ 24/2018 ዓ.ም 1...
08/31/2026

አዲስ አበባ ገብቷል‼️
በፋኖ ትግል ውስጥ ትልቅ አመራር የነበረው በተለይም የጎጃም ፋኖ ቃል አቀባይ በመሆን ለብዙ ጊዜ ትግሉን ሲመራ የቆየው ማርሸት ፀሀዩ ትናንት ነሐሴ 24/2018 ዓ.ም 10:00 አካባቢ በቁጥጥር ስር ውሎ በሄሊኮፕተር አዲስ አበባ መግባቱ ተረጋግጧል። ማርሸት ከትግል አጋራቹ ጋር ባለመስማማት በቅርቡ ከፍተኛ ድብደባ ተፈፅሞበት በድብቅ ቦታ ህክምና ሲደረግለት ነበር የቆየው።

ሰበር ዜናበራያ አዘቦ የድሮን ድብደባ ተፈጸመ!ከደቂቃዎች በፊት በራያ አዘቦ ተከታታይ የድሮን ጥቃት መፈጸሙን ምንጮች አረጋግጠዋል። ጥቃቱ በሕወሓት ወታደራዊ ካምፖች ላይ ያነጣጠረ ነው ተብሏል...
08/24/2026

ሰበር ዜና

በራያ አዘቦ የድሮን ድብደባ ተፈጸመ!

ከደቂቃዎች በፊት በራያ አዘቦ ተከታታይ የድሮን ጥቃት መፈጸሙን ምንጮች አረጋግጠዋል። ጥቃቱ በሕወሓት ወታደራዊ ካምፖች ላይ ያነጣጠረ ነው ተብሏል።

08/21/2026

‼️ ፅምዶ

ደብረፅዮን ጨምሮ አራት የፖለቲካ አመራሮች ጀነራል ፍስሃ ማንጁስና ጀነራል ወዲ መድህን ጨምሮ ስድስት የTDF አመራሮች ዘመነ ካሴና ጀነራል ተፈራ ማሞን ጨምሮ አራት የፋኖ አመራሮች ትላንት ኤርትራ ገብቷል።

ቀጣይ ምን ይሆናል የሻቢያንም የህወሃትንም የፋኖንንም መጨረሻ እናየዋለን::

ምፅዋ በካርጎ አውሮፕላኖች ተጨናንቋል‼️ሱዳን ከባባድ መሣሪያዎችን በኤርትራ ምፅዋ እያራገፈች ነው‼️ጀነራል አል_ቡርሃን ከባባድ መሣሪያዎችን በኤርትራ ምፅዋ አውሮፕላን ማረፊያ በብዛት  እያራ...
08/15/2026

ምፅዋ በካርጎ አውሮፕላኖች ተጨናንቋል‼️
ሱዳን ከባባድ መሣሪያዎችን በኤርትራ ምፅዋ እያራገፈች ነው‼️
ጀነራል አል_ቡርሃን ከባባድ መሣሪያዎችን በኤርትራ ምፅዋ አውሮፕላን ማረፊያ በብዛት እያራገፈ እንሚገኝ በሳተላይት ምስል ተረጋግጧል ።
ከሱዳን ተነስተው በምፅዋዋ አውሮፕላን ማረፊያ ያረፉ በርካታ የጭነት አውሮፕላኖች ከባባድ መሳሪያዎችን፣ ተወንጫፊ ሚሳይሎችንና ጥይት እያራገፉ መሆናቸውን የሳተላይት ምስሎች አሳይተዋል።
ከሱዳን በተጨማሪ ከቤላሩስ እንዲሁም ከኢራን የመጡ የጭነት አውሮፕላኖች ከሁለት ቀን በፊት ምፅዋ እንዳረፉ ከሳታላይት ምስሎች ለማየት ተችሏል።

ሰበር በብሉ ናይል ግዛት ከኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢ አዲስ ውጊያ ተቀሰቀሰ!ከአንድ ወር በፊት የሱዳን ጦር ስትራቴጂካዊቷን ኩርሙክን መቆጣጠሩ ይታወቃል፡፡ ጦሩ በወቅቱ ከተማዋን ሲቆጣጠር የፈጥ...
08/11/2026

ሰበር

በብሉ ናይል ግዛት ከኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢ አዲስ ውጊያ ተቀሰቀሰ!

ከአንድ ወር በፊት የሱዳን ጦር ስትራቴጂካዊቷን ኩርሙክን መቆጣጠሩ ይታወቃል፡፡ ጦሩ በወቅቱ ከተማዋን ሲቆጣጠር የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ታጣቂዎች ወደኋላ አፈግፍገው ነበር፡፡

ዛሬ በወጣ መረጃ፣ በሸረሪናው ውጊያ ተሳትፏል በሚል የተወነጀለው የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ በሱዳን ጦር ላይ አዲስ የመልሶ ማጥቃት ከፍቷል፡፡ ይህን ተከትሎ በአሁኑ ሰዓት ከባድ ውጊያ እየተደረገ ነው፡፡

በዚህ ቀጠና የሕወሓት የጦር አሃዶች ከአልቡርሃን ጎን ሆነው እንደሚዋጉ ይታወቃል፡፡

07/06/2026
 : የህወሓት የአፈሳ አስተባባሪ ተገ*ደለ!በሰሜን ምዕራብ ዞን መይሊ ቀበሌ ከሰሞኑ በውል የማይታወቅ ቁጥር ያለው ወጣት ያፈሰ ሲሆን አፈሳውን በዋናነት ሲያስተባብር የነበረ አንድ ግለሰብ አመ...
07/06/2026

: የህወሓት የአፈሳ አስተባባሪ ተገ*ደለ!

በሰሜን ምዕራብ ዞን መይሊ ቀበሌ ከሰሞኑ በውል የማይታወቅ ቁጥር ያለው ወጣት ያፈሰ ሲሆን አፈሳውን በዋናነት ሲያስተባብር የነበረ አንድ ግለሰብ አመሻሽቶ ወድ ቤቱ ሲመለስ በአካባቢው ወጣቶች ተገድሎ መገኘቱ ታውቋል።

የትግራይ ወጣት ህወሓት የሚባል የህዝብ ጠላ*ት ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ እያወገዘ እና እያገ*ደለው ይገኛል።

ይህ የሚያሳየው የትግራይ ህዝብ በህወሓት ላይ ያለውን ከፍተኛ ጥላቻ ነው። ከሰሞኑም ህወሓት በመቀሌ እና ዙሪያዋ እያደረገ የሚገኘው አፈሳ ላይ በህወሓት ላይ ድንጋይ እስከ መወርወር ደርሰዋል።

የዚህ የአፈሳ አስተባባሪው መገደል የሚያሳየው ያለፍልጎታቸው በመታፈሳቸው የተነሳ የተፈጠረ ግድያ መሆኑን ያሳያል። ህዝብን በግዳጅ ማንበርከክ ገና ዋጋ ያስከፍላል። የህዝብ ማዕበልን የሚያስቆም ምንም ሃይል የለም። በትጥቅ ህዝብ ከተነሳ ማስቆም አይቻልም። የትግራይ ህዝብ አሁን ያለበት ሁኔታ ከታጠቀ የህወሓት ሃይል ጋር መጋፈጥ ሆኗል።

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=122114168529280268&id=61588408056047&mibextid=WC7FNe
06/23/2026

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=122114168529280268&id=61588408056047&mibextid=WC7FNe

ክቡራትና ክቡራን የሶሮ 01 ምርጫ ክልል ነዋሪዎች፣ የተከበራችሁ ደጋፊዎቼ እና መላው የዲሞክራሲ ወዳጆች፤ በመጀመሪያ፣ ካለፈው 7ኛ ሀገራዊ የምርጫ ሂደት ጀምሮ ለእውነት፣ ለፍትሕ እና ለሕዝባችን ድምፅ መከበር ስትሉ ላሳያችሁት ጽናት፣ ትዕግሥትና ተስፋ ያልቆረጠ አንድነት ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።
​እኛ ወደዚህ የፖለቲካ ውድድር ስንገባ የሕዝባችንን እውነተኛ ፍላጎትና ድምፅ በቅንነት ለማገልገል እንጂ፣ የሕግ ጥሰቶችን እና ኢ-ዲሞክራሲያዊ አካሄዶችን ለማስተናገድ አይደለም። ካለፈው የምርጫ ሂደት ጋር ተያይዞ በሶሮ 01 የምርጫ ክልል የተፈጸሙት የሕግ ጥሰቶች የሕዝባችንን ነፃ ምርጫና ሉዓላዊነት የሚጋፉ ነበሩ። እኛም ይህንን ፍጹም ተቀባይነት የሌለው ድርጊት በሰላማዊና በሕጋዊ መንገድ ብቻ ለመታገል ቃል ገብተን ነበር።
​የተከበራችሁ ወገኖቼ፤ ዛሬ ያደረግነው ሕጋዊ ትግል እና ያቀረብነው አቤቱታ ፍሬ አፍርቷል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የቀረቡትን ክሶችና ማስረጃዎች በዝርዝር መርምሮ፣ በሶሮ 01 የምርጫ ክልል የተካሄደው ምርጫ የሕግ ጥሰት የተፈጸመበት መሆኑን በማረጋገጥ ምርጫው ተሰርዞ ድጋሚ ምርጫ እንዲካሄድ በ14/10/2018ዓ.ም የመጨረሻ ውሳኔውን አስተላልፏል።
​ይህ ውሳኔ የዶክተር ሀብታሙ ታምራት ብቻ ሳይሆን፣ የእናንተ የሶሮ 01 መራጮች የጽናት ውጤት ነው! ይህ ውሳኔ በሀገራችን የሕግ የበላይነትና የሕዝብ ድምፅ በቀልድ እንደማይታለፍ ያሳየ ትልቅ የዲሞክራሲ ድል ነው። ፍትሕ ዘግይታም ቢሆን መምጣቷን ያረጋገጠ ክስተት ነው።
​የተከበራችሁ የሶሮ 01 ነዋሪዎች፤
​አሁን ዋናው እና ወሳኙ ምዕራፍ ተጀምሯል። የምርጫ ቦርድ ድጋሚ ምርጫ እንዲደረግ መወሰኑ የሰጠን ትልቅ ዕድል ነው። ይህ ዕድል እውነተኛ ድምፃችንን ያለምንም ፍርሃትና ተፅዕኖ በካርዳችን የምናስመሰክርበት ወሳኝ ወቅት ነው።
​ስለሆነም፦ በቀጣይ በሚወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት፣ ሁላችንም በነቂስ ወጥተን የምርጫ ካርዳችንን በመያዝ ለድጋሚ ምርጫው እንድንዘጋጅ፤
​ይህ የድጋሚ ምርጫ ሂደት ፍጹም ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና የሕግ የበላይነት የተከበረበት እንዲሆን ሁላችንም እንደ ሁልጊዜው በንቃትና በጨዋነት እንድንጠብቅ፤ የጀመርነውን የለውጥና የልማት ጉዞ በድጋሚ ምርጫው ላይ በምናሳየው ጠንካራ ተሳትፎ እንድንደግም ጥሪዬን አቀርባለሁ።
​እውነት እና የሕዝብ ፍላጎት ሁልጊዜም ያሸንፋሉ! ፍትሕ ለሶሮ 01 ሕዝብ በምልዓት ትረጋገጣለች።
​ስለነበረን ጽናት ሁሉ እግዚአብሔር ያክብርልኝ!
ቀጣዩ ጊዜ የጋራ ድላችንን የምናበስርበት ይሆናል!

​ዶ/ር ሀብታሙ ታምራት ደሪሎ
የግል እጩ ተወዳዳሪ

Abiy Ahmed Ali
National Election Board of Ethiopia NEBE የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
Prosperity Party - ብልፅግና

06/22/2026

Address

Houston, TX
0000

Telephone

+251948830777

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Naod Tube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Naod Tube:

Shortcuts

Share