Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ

Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ is an Ethiopian entertainment and news website launched in March 2016. The official page of tobiatube247.com

😂😂😂🤣🤣🤣🤣
06/05/2025

😂😂😂🤣🤣🤣🤣

የማክሮ- ኢኮኖሚ ማሻሻያ አድርገናል ከተባለ ጊዜ ጀምሮ ... የተገኙ ትሩፋቶች 👉 ኢትዮ-ቴሌኮም ከፍተኛ የታሪፍ ማሻሻያ ጭማሪ አደረገ👉 መብራት ሃይል ሶስት እጥፍ የዋጋ ጭማሪ አደረገ👉 የውሃ...
05/31/2025

የማክሮ- ኢኮኖሚ ማሻሻያ አድርገናል ከተባለ ጊዜ ጀምሮ ... የተገኙ ትሩፋቶች

👉 ኢትዮ-ቴሌኮም ከፍተኛ የታሪፍ ማሻሻያ ጭማሪ አደረገ
👉 መብራት ሃይል ሶስት እጥፍ የዋጋ ጭማሪ አደረገ
👉 የውሃ አገልግሎት የክፍያ ታሪፉን እላይ ሰቀለው

👉 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለአገልግሎት ተጨማሪ እሴት ታክስ ማስከፈል ጀመረ

👉 ነዳጅ በሊትር በየ 3 ወሩ ከአስር ብር በላይ ይጨምራል

👉 የትኛውም የመንግስት አገልግሎቶች እንደ ቀልድ የሚጨምሩት ክፍያ የማይቀመስ ሆነ

👉 መሰረታዊ የፍጆታ ሸቀጦች ሆነ የትኛውም ምርት በየቀኑ የዋጋ ተመናቸው ከፍ እያለ አስቸገረ .

👉 ከውጭ የሚገቡ ምርቶች በየወሩ ከእጥፍ በላይ ይጨምራሉ

👉 አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የሰው ኪስ መግባት እስኪቀራቸው ድረስ ህብረተሰቡን አማረሩ

👉 መንግስት በታክስ ሀንግ መስራት ጀመረ ... ወዘተረፈ እንዲሁም መጪው ሐምሌ ላይ ሌላ የምስራች ሊያበስሩን ጉድ ጉድ እያሉ ነው

👉 ነገር ግን የሰራተኛው ደሞዝ ባለበት ደርቋል። ደሞዝ ቢጨመርም እንኳን ለአንድ ቀን ምሳ የማትበቃ 700 ብር ጠብ ትደረጋለች

👉 የገንዘባችን የመግዛት አቅም ደግሞ ተመናምኖ እርቃኑን ቀርቷል።

👉 ህዝቡ በተአምርና በአስማት ሌላውን ነገር ትቶ ትንፋሹን ለማስቀጠል ብቻ ህይወቱን ይገፋል።

👉 በጎን በኩል ደግሞ ሚዲያው ፣ ካድሬው ፣ የገፅታ ግንባታ ባለሞያው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ መላው አለም እየተደመመበት እንደሆነ ይነግሩናል። አስፓልት ፣ መብራት ፣ ውሀ የጠገበ ዘንባባ በባዶ ሆዶችሁ እያያችሁ ተደመሙ ይሉናል።

እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ያለበት የውጭ ዕዳ መጠን 575.6 ዶላር መድረሱን፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ አሶሴሽን ባወጣው ሪፖርት ገለጸ፡፡አሶሴሽኑ የአገሪቱን ከ2021 እስከ 2023 የኢኮኖሚ አፈጻጸ...
05/25/2025

እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ያለበት የውጭ ዕዳ መጠን 575.6 ዶላር መድረሱን፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ አሶሴሽን ባወጣው ሪፖርት ገለጸ፡፡

አሶሴሽኑ የአገሪቱን ከ2021 እስከ 2023 የኢኮኖሚ አፈጻጸም አስመልክቶ ግንቦት 14 ቀን 2017 ዓ.ም. ባወጣው ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. እስከ 2023 ድረስ ያለባት የብድርመጠን 62.5 ቢሊዮን ዶላር መድረሱንና እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊም የተጠቀሰው መጠን የውጭ ዕዳ እንዳለበት ጠቁሟል፡፡

የብድር ጫናው እንዲበዛ ካደረጉ ምክንያቶች መሀል የመንግሥት ወጪ አስተዳደር አቅም ማነስ፣ የፕሮጀክቶች አፈጻጸም ደካማነት፣ ኢኮኖሚውን ሊደግፉ የሚችሉ ፕሮጀክቶችን አለማስፋት፣ የወጪ ንግድ መቀዛቀዝና የማምረት አቅም እየቀነሰ መምጣት ዋነኞቹ እንደሆኑ በሪፖርቱ ጠቅሷል።

በማኅበሩ ከፍተኛ የማክሮ ኢኮኖሚ ተመራማሪ ናስር የኑስ (ዶ/ር)፣ ከዚህ በፊት አገሪቱ ለተለያዩ ፕሮጀክቶች ከተለያዩ ተቋማትና አገሮች የተበደረቻቸው ብድሮች ውጤታማ አለመሆናቸው ዋነኛ የብድር ጫና ምክንያት መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡

ኢትዮጵያ የብድር መክፈያ ጊዜን በመደራደር እንዲራዘም ማድረጓ ጥሩ ቢሆንም፣ ሊከፈል የነበረውን ገንዘብ አሁንም ኢኮኖሚውን መደጎም በማይችሉ መንገዶች ወጪ ከተደረገ የዕዳ ጫናው ይጨምራል እንጂ ሊቀንስ እንደማይችልም ተመራማሪው ተናግረዋል፡፡

የመንግሥት ወጪ በተቀናጀና ኢኮኖሚውን በሚጠቅም መንገድ ካልተተገበረ ዕዳ መክፈል ከማይችሉ አገሮች መካከል እንድትመደብ ከማድረግ ባለፈ፣ ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ያልሆነች አገር እንድትሆን ያደርጋታልም ብለዋል፡፡

ከዚህ በፊት ከዓለም አቀፍ አበዳሪ ተቋማትና አገሮች የተገኙ ብድሮች ባደረሱት ጫና ምክንያት፣ መንግሥት በወጪ ቅነሳ ላይ መቆየቱ ለኢኮኖሚው መቀዛቀዝ ተጨማሪ ምክንያት እንደሆነም ተመራማሪው ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከወጪ ንግድ ከሚገኘው ገቢ ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ የብድር ጫና ካለባቸው አገሮች መካከል አንዷ የሚያደርጋት እንደሆነ፣ ከዓመታዊ ምርት ወይም ጂዲፒ አንፃር ደግሞ በአማካይ ላይ እንደሆነች በሪፖርቱ ተጠቅሷል፡፡

መንግሥት የገጠመውን የገንዘብ እጥረት ለመፍታት ከግብር የሚሰበስበውን መጠን በየዓመቱ እያሳደገ መሆኑን የተናገሩት ናስር (ዶ/ር) ጭማሪው ተቀጣሪና መደበኛ የሥራ መስኮችን ዒላማ ያደረገ በመሆኑ የዋጋ ግሽበትን ከማባባስ ባለፈ አገራዊ የኢኮኖሚ መረጋጋትን አላመጣም ብለዋል፡፡

በመሆኑም መንግሥት ለኢኮኖሚው ተጨማሪ አቅም የሚሆኑ ፕሮጀክቶችን ማስፋት፣ አዳዲስና ያልተለመዱ የግብር መሰብሰቢያ አማራጮችን በመፈለግ የዋጋ ግሽበትን በማያባብስ፣ ከተቋማት ጋር መናበብን መሠረት ባደረገ መንገድ እንዲተገበርም ተመራማሪው አሳስበዋል፡፡

በከተማ ከሚኖረው ማኅበረሰብ ውስጥም ከ25 በመቶ በላይ የሆኑ ሴቶች ሥራ አጥ ናቸው የተባለ ሲሆን፣ አገሪቱ ከ1993 ዓ.ም. ጀምሮ እየተገበረችው ያለው የሥነ ሕዝብ ፖሊሲ ከአሁኑ ወቅታዊ ሁኔታ ጋር ተመጋጋቢ እንዳልሆነም ተገልጿል፡፡

እ.ኤ.አ. ከ2020 ጀምሮ የኢትዮጵያ መንግሥት ተገማች አለመሆን፣ የሕዝብ እምነት ማጣት፣ መግባባት ላይ ያልተደረሰባቸው የልማት ሥራዎች መኖር፣ ግጭቶችና የውጭኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች መቀነስ የመንግሥትን አቅም እንዳዳከሙ አሶሴሽኑ በሪፖርቱ አመላክቷል።
(ሪፓርተር)

♦የታመመው ማነው?♦በስነ አእምሮ ሕክምና ዘንድ የሚታወቁ ሦስት የስነ አእምሮ በሽታ መገለጫዎች አሉ።፩- Hallucination፪- Illusion፫- Delusion የመጀመርያዎቹ ሁለቱ የተሳሳተ...
05/24/2025

♦የታመመው ማነው?♦
በስነ አእምሮ ሕክምና ዘንድ የሚታወቁ ሦስት የስነ አእምሮ በሽታ መገለጫዎች አሉ።
፩- Hallucination
፪- Illusion
፫- Delusion

የመጀመርያዎቹ ሁለቱ የተሳሳተ የሃሳብ አቀባበል/አረዳድ (Thought perception) ውጤት ሲሆን ፤ ሦስተኛው የተሳሳተ እምነት/ግንዛቤ (Thought content) ነው።

ከሌላው ሕመም በተለዬ
የስነ አእምሮ የጤና እክል ያለበትን ታካሚ ለማከም አስቸጋሪ የሚያደርገው ነገር ፤ ታማሚው መታመሙን አለማወቁ ነው።

በሽተኛው ፥ ሌሎች ሰዎች እንዲታከም ቢነግሩት እንኳን ፤ የታመሙት ሌሎች እንደሆኑ ያስባል/ያምናል። ስለዚህም በጊዜው አይታከምም። መድኃኒት ቢሰጠው በአግባቡ ለመውሰድ ፈቃደኛ አይሆንም።

ጥቂት ስለጠቀስናቸው ምልክቶች ለመነጋገር ያክል፦
♦Hallucination - የምንለው አንድ ሰው በእውነት የሌለን ነገር (Stimuli) እንዳለ አድርጎ ማዬት ፣ መስማት ፣ ማሽተት ፣ ማጣጣም ፣ መዳሰስ ነው።
ብዙ ምስሌዎችን ራሳችሁ አስባችሁ ድረሱበት።

♦Illusion - አንድ ሰው በነባራዊ ዓለም ያሉ ነገሮችን (Stimuli) የሚቀበልበት መንገድ ሲሳሳት ነው። ይህ ሰው እስክብሪቶ/Sthetoscope የያዘ ሰው መሳርያ የያዘ ሊመስለው ይችላል። የሚያለቅስ ፣ የተራበ ሰው ሲያይ የሚስቅ እና ደስተኛ የጠገበ መስሎ ይታየዋል። ምግብ ራበኝ የሚል ሰው ስልጣን ራበኝ የሚል ሊመስለው ይችላል።

♦Delusion - ይሄ ደግሞ አመክንዮ/ምክንያታዊነት ፥ ሊያሸንፉት የማይችሉ የሃሳብና የግንዛቤ ይዘት ተቃርኖ ነው። ይህም ብዙ አይነት ዘርፎች ያሉት ሲሆን የተለየ ሀይል/ውበት/አቅም አድርጎ ማሰብ/Delusion of Grandeur/, ሰዎች እየሰለሉት ፥ሊያጠቁት እየተከተሉት እንደሆነ ማሰብ /Paranoid Delusion/ ፣ ሌሎች ሳይነግሩኝ በሌሎች አእምሮ ውስጥ ያለውን ሃሳብ አውቃለሁ ማለት (Thought broadcasting) ፣ ሁሉንም ነገር ከራስ ጋር ማገናኘት (Ideas of reference) እንዲሁም Delusion of guilt ይገኙበታል።

እነዚህ ከስነ አእምሮ ጤና መታወክ መገለጫዎች ውስጥ ተጠቃሾች ናቸው።
እነዚህ ምልክቶች ያሉበት ሰው ፥ ጤናው እስኪመለስ ድረስ የስነ አእምሮ ሕክምና ማግኘት እንዲሁም የቅርብ ክትትል ያስፈልገዋል። በዚህ አረዳድ እና ግንዛቤ ውስጥ ሁኖ ሥራን በተገቢ ሁኔታ ማከናወን አይቻልም።

ያልሆነው የሆነ የሚመስለው (Hallucination)፣ የሆነውን ነገር በትክክል መተርጎም ካልቻለ(Illusion) ፣ ስለ ነገሮች ያለው እሳቤ እና እምነት ከእውነት የሚቃረን ሁኔ ከተገኘ (Delusion) ፤ ሕክምና ሳያገኙ ሥራንና ሌላን ሰው መምራት ቀርቶ ራስን መምራት አይቻልም።

በሃገራች እየሆነ ያለው ይሄው ነው።
የማይታይ ስዕል እየታየን ፣ ያልተነገረ ቃል እያደመጥን ፣ እያሸተትን ፤ በምናብ ዓለም እንኖራለን ፤ የፈጠራ ታሪክ እያወራን ከራሳችን ተጣልተን ፥ ሌሎችን እናጣላለን ፤ ፈርተን/ተሸብረን ፥ ሌሎችን እናሸብራለን።

የሚያውቁት እና የራስ የሆነን ጥያቄ ፥ እንደማያውቁት ሁኖ መገኘት።
የሚያውቁት እና ለዘመናት መፍትሔ ያላመጣን የጥያቄ መንገድ ፥ መፍትሔ የሚያመጣ ትክክለኛ መንገድ ነው ብሎ መሞገት።

የህዝብ ዓይን እና ጆሮ ነን ብለው የሚለፍፉ ሚዲያዎች ፥ የህዝቡ ዓይን ከሚያየው የህዝቡ ጆሮ ከሚሰማው በተቃራኒው ይዘግባሉ ይናገራሉ።
ብዙ ሆስፒታሎች በከፊል ተዘግተው (ሕክምና አገልግሎት መስጠት አቁመው) ፥ ብዙ ታካሚዎች እየተጉላሉ ፥ እንላለን።

የገንዘብን የመግዛት አቅም ሦስት እጥፍ (300%) ቀንሶ ፥ የ10% የደመወዝ ጭማሪ የማድረግ ሽሙጥ። (ይሄ በ290% ደመወዝ ተቀነሰ እንጅ ፥ ደመወዝ አልተጨማረም። ብር አይበላም ፤ ዓላማው መግዛት ነው።)

ይሄስ - ወዳጅ ለመምሰል መሞከር ነው።

ከድህነት ወለል በታች ቁልቁል እየወረድን ፥ በዕድገት ጎዳና ላይ እንደሆንን እናስባለን ፥ እንናገራለን።

በጽኑ ርሀብ የሚገረፍ ህዝብ ይዘን ፤ በልማት ጎዳና ላይ እንደሆንን ይሰማናል ፥ እንናገራለን ፤ ገፅታ ለመገንባት እንታትራለን።
እርዳታ እየለመንን ፥ እርዳታ እንሰጣለን።
ሰውን ከሰውነት ተራ እያወጣን ፣ እያፈረስን ፣ እያስራብን ፣ እያፈናቀልን ፣ እያራቆትን ፤ መንገድ በማስዋብ እና ኮሪደር በማልማት ሥራ ተጠምደናል።

በሃገራችን/ስለሀገራችን
ህዝቡ ዕለት ከዕለት እያጋጠመው እና እየተናገረው የሚገኘው ድምፅ ፤ የህዝብ መሪዎች ከሚሰሙት ፣ ከሚገነዘቡት ፍፁም የተለየ ሲሆን ይስተዋላል።

ችግሩ የመጣው
አውቆ የተኛ ቢቀሰቅሱት አይሰማም አይነት (Malingering) - አውቆ አበደነት ፤ ወይስ እንደታመሙ ከማያውቁበት የጤና ችግር (Hallucination ፣ Dellusion and Illusion?)

እየተወራላት የምንሰማት ኢትዮጵያ ሕዝቡ ከሚያውቃት ኢትዮጵያ ትለያለች።
ምናባዊ ዓለም
ወይስ ሌላ ሕዝቡ የማያውቃት ኢትዮጵያ ትኖር ይሆን እንጃ !

መሪዎች ስለራሱ እና ሚመሩት ህዝብ የሚናገሩት እና ተመሪው ሕዝብ ስለ ራሱ እና ስለመሪዎች የሚናገሩት በብዙው ይቃረናል።

እንደ ሃገር
ወይ እኛ ተመሪዎች (ሕዝብ) ታመናል !

ወይ መሪዎች ታምመውብናል !

እግዚአብሔር ምሕረቱን ይላክልን።

ዶ/ር ዮሴፍ

Good News!!ዶ/ር ሳሚ ዛሬ ከመሼ ከእስር መፈታቱን ሰምተናል። እንኳን ለቤትህ አበቃህ!!ሌሎችም የታሰሩ የጤና ባለሞያዎች እንዲፈቱ እንጠይቃለን!!via የሐኪሞች ድምፅ
05/23/2025

Good News!!
ዶ/ር ሳሚ ዛሬ ከመሼ ከእስር መፈታቱን ሰምተናል። እንኳን ለቤትህ አበቃህ!!

ሌሎችም የታሰሩ የጤና ባለሞያዎች እንዲፈቱ እንጠይቃለን!!
via የሐኪሞች ድምፅ

'ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ጠፈር ለሚያደርጉት ጉዞ 55 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ይደርግበታልመሠረት ሚድያ ከሀገር ውስጥ እንዲሁም በዋናነት በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ከሚገኙ ምንጮቹ ለበ...
05/22/2025

'ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ጠፈር ለሚያደርጉት ጉዞ 55 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ይደርግበታል
መሠረት ሚድያ ከሀገር ውስጥ እንዲሁም በዋናነት በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ከሚገኙ ምንጮቹ ለበርካታ ቀናት ሲያሰባስበው የነበረው መረጃ እንደሚጠቁመው በአለም ታሪክ ለመጀመርያ ግዜ የአንድ የሀገር መሪ ወደ ጠፈር ሊጓዝ ሰፊ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው፣ መንገደኛውም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ናቸው።

በኤምሬቶች የሚገኙ ምንጮቻችን እንዳረጋገጡልን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ጠፈር የመጓዛቸው አላማ በርካታ ግቦችን አካቷል፣ ከእነዚህም መሀል የሰላም እና የአንድነት መልዕክት ለአለም ብሎም ለኢትዮጵያውያን ማስተላለፍ እንዲሁም ወጣቶች ወደ ቴክኖሎጂው ዘርፍ እንዲሳቡ እና እንዲነሳሱ ለማድሩግ ታስቧል።

"ውይይቱ በኢትዮጵያ መንግስት እንዲሁም በተባበሩት ኤምሬቶች በኩል በስፋት ንግግር እየተደረገበት ነው" ያሉት አንዱ በዱባይ የሚገኝ የመረጃ ምንጭ በተለይ ከጠፈር ላይ ሆኖ ለአለም ህዝብ መልዕክት ማስተላለፍ የእቅዱ ዋና ግብ ነው ብለዋል።

'Project X' የሚል ስም ተሰጥቶት እየተሰራበት እንደሆነ የሚነገርለት ይህ የጠፈር ጉዞ ወጪው በተባበሩት ኤምሬቶች የሚሸፈን መሆኑን አንድ ሌላ እዛው ዱባይ የሚገኝ ምንጭ ለሚድያችን ተናግሯል።

ለመዳሰስ የሞከርናቸው ፅሁፎች እንደሚጠቁሙት ወደ ጠፈር የሚደረግ ጉዞ ለአንድ ሰው ከትንሹ 250 ሺህ ዶላር እስከ ከፍተኛው 55 ሚልዮን ዶላር ሊደርስ እንደሚችል ይጠቁማሉ።

ለምሳሌ 'Blue Origin' እና 'Virgin Galactic' የተባሉት መንኩራኩሮች ከንፍቀ ክበብ በታች ለሚደረግ እና ርካሽ የተባለ ጉዞ ከ200 ሺህ ዶላር እስከ 400 ሺህ ዶላር ያስከፍላሉ፣ ራቅ ያሉ እና ከንፍቀ ክበብ ውጪ የሚደረጉ የጠፈር በረራዎችን የሚያከናውኑት እንደ 'Space X' ያሉ ሮኬቶች ደግሞ በአንድ ሰው እስከ 55 ሚልዮን ዶላር (7.3 ቢልዮን ብር) እንደሚያስከፍሉ ታውቋል።

ጠ/ሚር አብይ ሊጓዙ እቅድ የያዙት ከንፍቀ ክበብ ውጪ ወደ አለም አቀፉ የጠፈር ማዕከል (International Space Station) እንደሆነ ታውቋል፣ ወጪውም ከላይ እንደተጠቀሰው በአንድ ሰው እስከ 55 ሚልዮን ዶላር እንደሚደርስ እና በኤምሬቶች እንደሚሸፈን ታውቋል።

ትራኦሬ የእርሻ መሳሪያዎች በነፃ ለገበሬዎች  አበረከተ!!ትራኦሬ ከ104 ቢሊዮን FCFA ገንዘብ ወጭ በማድረግ  ለገበሬዎች  ስጦታ አበረከተ !የቡርኪናፋሶ ፕሬዝዳንት ርዕሰ መስተዳድር ካፒቴን...
05/22/2025

ትራኦሬ የእርሻ መሳሪያዎች በነፃ ለገበሬዎች አበረከተ!!

ትራኦሬ ከ104 ቢሊዮን FCFA ገንዘብ ወጭ በማድረግ ለገበሬዎች ስጦታ አበረከተ !

የቡርኪናፋሶ ፕሬዝዳንት ርዕሰ መስተዳድር ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ ዛሬ ሀሙስ ማለዳ ላይ በገጠር ለሚገኙ ለአርሶአደሮች እና አርብቶ አደሮች የጭነት መኪናዎች፣ የሞተር ሳይክሎች ፣ትራክተሮች ፣ ክሬሸርስ
የእንስሳት መድኃኒት ፣ የሞተር ፓምፖች የማዕድን ማዳበሪያና ሌሎችም ግብአቶች ለገበሬዎች ማበርከታቸዉ ነዉ የተነገረው ።

ቡርኪናፋሶ ለጀመረችው በምግብ ራስን መቻል ዘመቻ ለማሳካት የገጠሩን ማህበረሰብ መደገፍና ማገዝ እንደሚያስፈልግ የገለፁት ኢብራሂም ትራኦሬ
2025-2026 ሀገሪቱን የምግብ ሉዓላዊነት ለማምጣት
608 ትራክተሮች ፣ 1102 የሞተር ማረሻ፣ 17 የጭነት መኪናዎች፣ ኮምባይነሮች፣ 150 ክሬሸርስ ማቀናበርያ የእፅዋት ዘር መኖ እና ሌሎች ቁሳቁሶች ለገበሬዎች አበርክተዋል ።
እነዚህ ቁሳቁሶች ለገበሬዎቹ በነፃ የቀረቡ ሲሆን ይህም በቅርብ ጊዜ ውስጥ የምግብ እራስን መቻልን ለማሳካት ነው” ሲሉ ገልፀዋል ።

መረጃዉ የፋሶ ፕሬዝዳንት ኮሙኒኬሽን ዲፓርትመንት ነዉ

የኢትዮጵያ መንግስት እዳ 62.5 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ተገለፀ፡፡ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ማህበር ዛሬ ባወጣው ሪፖርት አገሪቱ ከፍተኛ የብድር ጫና ውስጥ መግባቷን አስታውቆ ለውጭ ገበያ ከሚቀርበው...
05/22/2025

የኢትዮጵያ መንግስት እዳ 62.5 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ተገለፀ፡፡
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ማህበር ዛሬ ባወጣው ሪፖርት አገሪቱ ከፍተኛ የብድር ጫና ውስጥ መግባቷን አስታውቆ ለውጭ ገበያ ከሚቀርበው የሚገኘው ገንዘብና መንግስት የሚሰበስበው ገቢ ለእዳ መክፈያ እየዋለ መሆኑን አስረድቷል፡፡

ማህበሩ በሪፖርቱ ‹‹ኢትዮጵያ በአንድ ወቅት ከአለም ፈጣን ኢኮኖሚ ካስመዘገቡ አገራት ተርታ ተሰልፋ ነበር›› ካለ በኋላ ካለፈው 10 አመት ወዲህ እድገቷ ማሽቆልቆሉን አስታውቋል፡፡ እየጨመረ የመጣው የዋጋ ንረት የዜጎችን ኑሮ ስጋት ውስጥ መክተቱን አስረድቶም ከዚህ መውጫ ያላቸውን ምክረ ሀሳቦች ለግሷል፡፡

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ማህበር አሁን ያለው የኢትዮጵያ እዳ 62.5 ቢሊዮን ዶላር የገለፀ ሲሆን ከወራት በፊት ይፋ የሆነው አንድ መረጃ ደግሞ እዳው 56.7 ቢሊዮን ዶላር መሆኑን አስታውቆ ነበር፡፡ በተመድ አማካኝነት ይፋ የሆነው ይህኛው መረጃ እንዳለው የኢትዮጵያ እዳ በተለያዩ መንገዶች የሚገለፅ ነው፡፡ ለምሳሌ ከአለም አቀፍና አህጉራዊ ድርጅቶች የተበደረችው መጠን 24 ቢሊዮን ዶላር ይደርሳል፡፡ ከተለያዩ አገራት የተበደረችው ደግሞ 9.5 ቢሊዮን እንደሚሆንና ከግለሰቦች ያለባት ብድር 17 ቢሊዮን ዶላር መሆኑን አስረድቷል፡፡
(ዘ-ሐበሻ ዜና)

ታዋቂው የቀዶ ህክምና ዶክተር ሳሙኤል ሀይሉ በመንግስት የጸጥታ ሃይሎች በትላንትናው ዕለት ታፍኖ መወሰዱን Ethiopia Health Forum አሳውቋል
05/21/2025

ታዋቂው የቀዶ ህክምና ዶክተር ሳሙኤል ሀይሉ በመንግስት የጸጥታ ሃይሎች በትላንትናው ዕለት ታፍኖ መወሰዱን Ethiopia Health Forum አሳውቋል

BBC Focus on Africa ቃለ መጠይቅ ስለ ኢትዮጲያ የጤና ባለሙያዎች የኑሮ ሁኔታ ለአለም አቀፍ ሚድያ የዶክተሮችን ድምፅ ያሰማችው Anatomic Pathologist ዶ/ር ማህሌት ጉሽ ...
05/20/2025

BBC Focus on Africa ቃለ መጠይቅ ስለ ኢትዮጲያ የጤና ባለሙያዎች የኑሮ ሁኔታ ለአለም አቀፍ ሚድያ የዶክተሮችን ድምፅ ያሰማችው Anatomic Pathologist ዶ/ር ማህሌት ጉሽ ገብረወልድ በፀጥታ ሀይሎች ታፍና ተወስዳለች።

ከቲክቶክ መንደር የተገኘ መልዕክት 😥😥😥
05/20/2025

ከቲክቶክ መንደር የተገኘ መልዕክት 😥😥😥

Address

Jersey City, NJ

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ:

Share