Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ

Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ is an Ethiopian entertainment and news website launched in March 2016. The official page of tobiatube247.com
(1)

08/08/2025

😥😥 ያን ፈገግታና መልካምነት ነጠቁት 😥😥

08/02/2025

ሰበር መረጃ - The legendary ተወዳጁ ድምፃዊ ቴዎድሮስ ታደሰ በአዲስ አልበም ሊመጣ ነው!!!

ለምግብ እጥረት ከተጋለጡ አገሮች ኢትዮጵያ አምስተኛ ደረጃ መያዟን የተመድ ሪፖርት አመላከተ‹‹ኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍ የምግብ ሥርዓት ፍኖተ ካርታ አዘጋጅታለች›› - ጠ/ሚ ዓብይ አህመድ (ዶ/ር...
07/30/2025

ለምግብ እጥረት ከተጋለጡ አገሮች ኢትዮጵያ አምስተኛ ደረጃ መያዟን የተመድ ሪፖርት አመላከተ

‹‹ኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍ የምግብ ሥርዓት ፍኖተ ካርታ አዘጋጅታለች›› - ጠ/ሚ ዓብይ አህመድ (ዶ/ር)

ኢትዮጵያ ለምግብ እጥረት የተጋለጡ በርካታ ሰዎች ካሉባቸው አገሮች አምስተኛ ደረጃን መያዟ፣ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ሪፖርት ተመላከተ።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የምግብና የእርሻ ድርጅት (ፋኦ)፣ የዓለም አቀፍ ፈንድ ለግብርና ዕድገት፣ የተባበሩት መንግሥታት የሕፃናት ፈንድ፣ የዓለም የምግብ ፕሮራምና የዓለም የጤና ድርጅት ሐምሌ 22 ቀን 2017 ዓ.ም. የዓለም የምግብና አመጋገብ ሥርዓትን የተመለከተ ሪፖርት ይፋ አድርገዋል።

ሪፖርቱ እ.ኤ.አ. በ2025 በዓለም 295 ሚሊዮን ሰዎች በከፋ የምግብ ዕጦት እንደተጋረጠባቸውና ከፍተኛ የምግብ ችግርካለባቸው አገሮች መካከል፣ ኢትዮጵያ ናይጄሪያ፣ ሱዳን፣ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎንና ባንግላዴሽን ተከትላ በአምስተኛ ደረጃ ተቀምጣለች ብሏል። ከእነዚህ አገሮች በተጨማሪ ደቡብ ሱዳን፣ ሶሪያ፣ የመን፣ አፍጋኒስታንና ሄይቲ ለከፋ የምግብ ዕጦት የተጋለጡ ተብለው በሪፖርቱ ተካተዋል፡፡

በአገሮች እየተባባሱ በመጡ ሰብዓዊ ቀውሶችና እየጨመረ ባለው ከፍተኛ የምግብ እጥረት ምክንያት፣ በቂ ምግብ የማግኘ-መብት አደጋ ውስጥ መውደቁን በሪፖርቱ ተጠቁሟል፡፡

በሴፍቲኔት ፕሮግራም የሚፈጸም የጥሬ ገንዘብ ሥርጭት ኢትዮጵያ ላይ የዋጋ ንረት እንዲያሻቅብና በድህነት ውስጥ የሚኖረውን ዜጋ የመግዛት አቅም ማዳከሙን፣ ጥሬ ገንዘብ ከማስተላለፍ ቀጥታ የምግብ ዕርዳታ ማቅረብ ውጤታማ የሚባል አማራጭ እንደሆነ በተመድ ሪፖርት ተመላክቷል፡፡
(ሪፓርተር)

መንግሥት ከተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ 13.9 ቢሊዮን ብር መበደሩ ተነገረ የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ ባለፉት ሁለት ዓመታት በግምጃ ቤት ሰነድ ኢንቨስትመንት 13.9 ቢሊዮን ብ...
07/27/2025

መንግሥት ከተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ 13.9 ቢሊዮን ብር መበደሩ ተነገረ

የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ ባለፉት ሁለት ዓመታት በግምጃ ቤት ሰነድ ኢንቨስትመንት 13.9 ቢሊዮን ብር ለመንግሥት ማበደሩን አስታወቀ፡፡
የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ በየሁለት ሳምንቱ በሚወጣ ጨረታ በመሳተፍና የመንግሥት ግምጃ ቤት ሰነድ (Treasury Bill) በመግዛት 13.9 ቢሊዮን ብር ለመንግሥት ማበደሩን፣ የፈንዱ የኦፕሬሽን ሥራ ክፍል ዳይሬክተር አቶ መርጋ ዋቅወያ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
ፈንዱ የሚሰበሰበውን ዓረቦን ኢንቨስት ሲያደርግ ሁለት ጉዳዮችን ትኩረት እንደሚያደርግና ገንዘቡ መመለስ መቻሉ ቀዳሚው መሆኑን፣ በዚህም ብድር ያለ መመለስ ዕድሉ ዜሮ መሆን ስላለበት በግምጃ ቤት ሰነድ መልክ ለመንግሥት የሚያበድረው እንደሚሆን አስታውቀዋል፡፡
እስካሁን 1.24 ቢሊዮን ብር በሙዳራባ፣ እንዲሁም 13.9 ቢሊዮን ብር በግምጃ ቤት ሰነድ፣ በአጠቃላይ 15.14 ቢሊዮን ብር ኢንቨስት መደረጉን አስረድተዋል፡፡
ሌላው ብድሩ በጥሬ ገንዘብ የሚገኝ መሆኑን ማረጋገጥ እንደሚገባ፣ ለዚህም ምክንያቱ በአባል የፋይናንስ ተቋማት ጉዳት መድረሱ እንደተረጋገጠ ገንዘቡ ሲያስፈልግ በጥሬ ገንዘብ ሊገኝ የሚችል መሆን ስላለበት መሆኑን አክለዋል፡፡

የአገሪቱን የፋይናንስ ጤናማነት የማረጋገጥ ኃላፊነት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ቢሆንም፣ ፈንዱ ለዚህ ዓላማ አስተዋጽኦ ለማድረግ መቋቋሙን የገለጹት ዳይሬክተሩ፣ ይህም ገንዘብ አስቀማጩ በባንኮች ወይም በማይክሮ ፋይናንስ ያስቀመጠው ገንዘብ ኢንሹራንስ እንዲኖረው በማድረግ አመኔታ መፍጠርና የፋይናንስ ዘርፉን ማረጋጋት መሆኑን አብራርተዋል፡፡

በዚህም ባለፉት ሁለት ዓመታት ከተለያዩ ተቋማት ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችለውን ስምምነት መፈራረሙን፣ ከእነዚህ ውስጥም ፈንዱ የገንዘብ እጥረት ሲያጋጥመው ከገንዘብ ሚኒስቴር የመጠባበቂያ ገንዘብ ማግኘት ስላለበት ለዚህ የሚረዳ ስምምነት እንደተፈራረመ ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም በባንኮች ወይም በማይክሮ ፋይናንሶች ችግርሲፈጠር ፈንዱን በመወከል የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለገንዘብ አስቀማጮች ገንዘባቸውን መክፈል የሚያስችል ስምምነት መፈረሙን ገልጸዋል።

ፈንዱ ከተሰበሰበ በኋላ እንዴት ኢንቨስት ማድረግ እንደሚችል በግልጽ የሚያስቀምጥ መመርያ እንዳልነበረ፣ ባለፈው ዓመትም መመርያውን የማዘጋጀት ሥራ መከናወኑን አቶ መርጋ አስረድተዋል፡፡

ባለፉት ሁለት ዓመታት 13.85 ቢሊዮን ብር መሰብሰብ መቻሉን፣ ይህም መነሻ ዓረቦንና ዓመታዊ ዓረቦን በሚሉ ሁለት መንገዶች እንደሚሰበሰብ አስረድተዋል፡፡ የመጀመሪያው መነሻ ዓረቦን የፈንዱን የኦፕሬሽን ወጪ ለመሸፈን የሚውል መሆኑን፣ አሰባሰቡም ከእያንዳንዱ አባል የፋይናንስ ተቋም ካለው ተቀማጭ ገንዘብ ዐ.04 በመቶ እንደሆነ ገልጸዋል። ከዚህም በአጠቃላይ 850 ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ እንደነበርና ይህንንም በአንድ ጊዜ ለመሰብሰብ አባል የፋይናንስ ተቋማት በአንድ ጊዜ ለመክፈል ይከብዳቸዋል በሚል በሦስት ዓመታት እንዲከፍሉ መደረጉን፣ በአሁኑ ወቅትም ተሰብስቦ እየተጠናቀቀ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡

ሌላው ዓመታዊ ዓረቦን የፋይናንስ ተቋማቱ ከተቀማጭ ገንዘባቸው ዐ.3 በመቶ በየዓመቱ የሚከፍሉበት ሲሆን፣ አሰባሰቡም በየሩብ ዓመቱ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

‹‹ፈንዱ የሚሰበስበው ዓመታዊ ዓረቦን በገቢ መልኩ የሚመዘገብ በመሆኑ የገቢ ግብርታክስ ይጣልበታል የሚል ፍራቻ ስለነበር፣ ታክስ ከተደረገ ደግሞ አቅሙን ሊገነባ አይችልም የሚል ሥጋት ነበረብን፡፡ ነገር ግን የገንዘብ ሚኒስቴር ባሻሻለው የገቢ ግብርአዋጅ ከገቢ ግብር ነፃ እንዲሆን ተደርጓል፤›› ብለዋል፡፡

ተቋሙ ለትርፍ ያልተቋቋመ በመሆኑ የገቢ ግብር ሊከፍል አይገባም ያሉት ዳይሬክተሩ፣ የሌሎች አገሮች ተሞክሮም የሚያሳየው ከዚህ ነፃ መደረጉ ተገቢ እንደሆነ ነው ሲሉ አስረድተዋል፡፡
(ሪፓርተር)

ኢትዮጵያ በከፍተኛ ደረጃ ከአይኤምኤፍ ከተበደሩ 10 የአፍሪካ ሀገራት ተርታ መመደቧ ተጠቆመአለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) በከፍተኛ ደረጃ ብድር ከሰጣቸው 10 የአፍሪካ ሀገራት...
07/23/2025

ኢትዮጵያ በከፍተኛ ደረጃ ከአይኤምኤፍ ከተበደሩ 10 የአፍሪካ ሀገራት ተርታ መመደቧ ተጠቆመ

አለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) በከፍተኛ ደረጃ ብድር ከሰጣቸው 10 የአፍሪካ ሀገራት መካከል አንዷ ኢትዮጵያ መሆኗ ተገለጸ። በተያዘው አመት 2017 ዓ.ም ሐምሌ ወር ላይ ኢትዮጵያ ተጨማሪ ብድር ከአይኤምኤፍ እንደምታገኝም ተጠቁሟል።

እንደ አፍሪካን ቢዝነስ ኢንሳይደር ዘገባ የኢትዮጵያ አጠቃላይ የአይኤምኤፍ ብድር እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ አንድ ነጥብ 6 ቢሊየን ዶላር ተጠግቷል፤ ከአፍሪካ በሰባተኛ ደረጃ ተቀምጣለች።

ኢትዮጵያን ጨምሮ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት አለምአቀፉ የገንዘብ ተቋም ብድር እያገኙ ያሉት በውጭ ምንዛሬ እጥረት ሳቢያ መተንፈስ ያቃተውን ኢኮኖሚያቸውን ትንፋሽ እንዲቀጥል ለማድረግ ነው በሚል መሆኑን የጠቆመው አፍሪካን ቢዝነስ ኢንሳይደር ድረገጽ ይሁን እንጂ ከፍተኛ የአይኤምኤፍ ዕዳ የረዥም ጊዜ መዘዞች ይዞ በመምጣት በአህጉሪቱ ላይ ስጋት እየፈጠረ ይገኛል ሲል አመላክቷል።

Addis Standard

" መኖር ከማይችል ሰው ግብር አትሰበስብም ፤ በልቶ ከማያድር ሰው ግብር አትሰበስብም ! " - አቶ ካሳሁን ፎሎ" እንደ ሀገር ግብር መሰብሰብ አለበት ልማትም መቀጠል አለበት ፤ የሰው ህይወት...
07/16/2025

" መኖር ከማይችል ሰው ግብር አትሰበስብም ፤ በልቶ ከማያድር ሰው ግብር አትሰበስብም ! " - አቶ ካሳሁን ፎሎ

" እንደ ሀገር ግብር መሰብሰብ አለበት ልማትም መቀጠል አለበት ፤ የሰው ህይወትም መቀጠል አለበት ፤ ሰው እየተራበ መስራት አይችልም ምርታማ መሆን አይችልም ! "

የኢትዮጵያ የሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ዋና ፕሬዘዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ስለ ገቢ ግብር አዋጁ ምን አሉ ?

" የደመወዝ ገቢ ግብር ከዚህ በፊት መነሻው 600 ብር ነው፤ አሁን በረቂቁ የቀረበው 2,000 ሆኖ ነው።

በመሰረቱ 600 በሆነበት ሰዓት አንደኛ ገንዘብ የመግዛት አቅሙ ትልቅ በመሆኑ ፣ 1 ዶላርም 20 ብር ነበር ያኔ የዛሬ 10 ዓመት አካባቢ ነው ይሄ ነገር የተሻሻለው ፤ ሁለተኛ የመንግሥት ሰራተኞች መነሻ ደመወዝ 600 ነበር ያኔ 600 ለአንድ ሰው ለአንድ ወር ቢያንስ ምግብ መብላት ብቻ ይበቃዋል በሚል ታሳቢ አማካይ ተወስዶ ነው 600 የተባለው።

አሁን ግን 300% ፣ 200% ጨመርን (ማለትም 2000 ብር አደረግን) እሱ አይደለም ዋናው መነሻው ስንት ነው አሁን ? በአጭሩ ፤ እንኳን የኑሮ ውድነቱን ታሳቢ ያደረገ መንግሥት እራሱ ሰራተኛው በ600 ብር ሊያኖረው አይችልም ፤ የኑሮ ውድነቱ ከሚታሰበው በላይ በተለይም በሪፎርሙ መንግሥት በይፋ ያረጋገጠው ታችኛው የሰራተኛ ክፍል ጎድቶታል፤ ' ሊቋቋመው አይችልም ' በሚል መነሻ ደመወዙን ከፍ አድርጓል ፤ መነሻ ደመወዝን ከፍ ሲያደርግ ይሄን ታሳቢ አድርጓል።

አሁንም ቢሆን እነዚህ ሰዎች መኖር ከማይችል ሰው ግብር አትሰበስብም ፤ በልቶ ከማያድር ሰው ግብር አትሰበስብም። በቀን 2.15 ዶላር የሚያገኝ ሰው ድሃ ነው ከዚያ በታች የሚያገኝ በሙሉ ድሃ ነው ፤ እኛ ደግሞ እዛ ሁሉ አልደረስንም።

እኛ እያቀረብን ያለነው ሃሳብ 8,324 መነሻ ይሁን ነው። እንኳን የኛ ሀሳብ የመንግሥት እራሱ ያስቀመጠው መነሻ ላይ እንኳን አልደረሰም።

ሌላው በፊት የግብር ምጣኔው ከ0 ጀምሮ 10% ፣ 15% ፣ 20% ፣ 25% ፣ 30% ፣ 35% ይቀጥል ነበር አሁን 10%ን ከመሃል አወጡና ከ0 ጀምረው ቀጥታ 15% ነው የገቡት። አሁን ቀጥታ ከ15 ከከፍተኛው ነው ሲጀምር የጀመሩት። ይሄ ትክክል አይደለም።

35% ከየት ጀመረ 14,100 በላይ የሚያገኝ ሰው 35% ግብር ይከፍላል ፤ 35% ከሰራተኛ በአሁኑ የኑሮ ውድነት 15% በእያንዳንዱ በምግብ ዋጋም፣ በሚገዛው እቃም 15% ይጨምራል ይሄ ሲደመር 50% ይመጣል፤ 7% የጡረታ አለ ጡረታ የሚያገኘው ከ60 ዓመት በኃላ አሁን ግን 57% ከደመወዙ ላይ ይሄዳል በቀረችው 43% ፦
- ልጆች ያስተምራል
- ምግብ ይበላል
- ልብስ ይገዛል
- ቤት ይከራያል ምንድነው የሚያደርገው ?

ይሄና ይሄ ብቻ ስላልሆነ ነው ዝም ያልን እንጂ ይሄም ከፍ ብሎ እኮ ይበቃል ማለት አይደለም።

ግን እንደ ሀገር ግብር መሰብሰብ አለበት ልማትም መቀጠል አለበት ፤ የሰው ህይወትም መቀጠል አለበት ፤ ሰው እየተራበ መስራት አይችልም ምርታማ መሆን አይችልም። "

(tikvahethiopia)

የኤሌክትሪክ ፍጆታ ክፍያ"ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍጆታ ሂሳብዎን" እንዴት እንደሚያሰሉና ለምን ምን ጉዳዮች እንደሚከፍሉ ያውቃሉ? ለአጠቃቀም እንዲረዳዎ በቀላሉ በቀጣይ በተቀመጠው አሰራር ...
07/15/2025

የኤሌክትሪክ ፍጆታ ክፍያ
"ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍጆታ ሂሳብዎን" እንዴት እንደሚያሰሉና ለምን ምን ጉዳዮች እንደሚከፍሉ ያውቃሉ? ለአጠቃቀም እንዲረዳዎ በቀላሉ በቀጣይ በተቀመጠው አሰራር መሰረት በማስላት ወጪዎን ይወቁ!

👉 አንድ "የመኖሪያ ቤት ደንበኛ" ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ ሲከፍል የአገልግሎት ክፍያ፣ የተቆጣጣሪ ባለስልጣን ቀረጥ፣ ተጨማሪ እሴት ታክስ፣ ለኢቲቪ የሚከፈል የአገልግሎት ክፍያ እና የአገልግሎት ክፍያ ተጨማሪ እሴት ታክስ አብሮ ይይዛል፡፡ አሠራሩም ደንበኞች በወር ውስጥ የተጠቀሙት የኃይል ፍጆታ ሲባዛ ወቅታዊ የአንድ ኪዋሰ ታሪፍ ማባዣ እና ከላይ የተዘረዘሩትን ክፍያዎችን የሚያጠቃልል ይሆናል፡፡

✅ ለምሳሌ በዚህ በሐምሌ ወር ከ301 እስከ 400 ኪዋሰ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚጠቀም አንድ ''የድህረ-ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኛ'' የአንድ ኪዋሰ ወቅታዊ የታሪፍ ማባዣ መጠን 4.4898 ብር ነው።

✅ በዚህ መሰረት ደንበኛችን በሐምሌ ወር ውስጥ 350 ኪዋሰ ተጠቅመዋል ብለን ብናስብ፡-

☑️ ወርሃዊ የኃይል ፍጆታ ▶️ 350 ኪ.ዋ.ሰ*4.4898 ብር (ወቅታዊ የታሪፍ ማባዣ) 🟰 1,571.43 ብር፣

☑️ ተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ ክፍያ ▶️ (ወርሃዊ የኃይል ፍጆታ በኪዋሰ*15%) ፤ ይህ ማለት 1,571.43*15% 🟰 235.7145 ብር፣

☑️ የአገልግሎት ክፍያ /ከ50 ኪ.ዋ.ሰ በላይ ፍጆታ ለሚጠቀሙ ደንበኞች/ 🟰 46.75 ብር፣

☑️ የአገልግሎት ክፍያ ተጨማሪ እሴት ታክስ ▶️ የአገልግሎት ክፍያ*15% ይህም ማለት 46.75 ብር *15% 🟰 7.0125 ብር፣

5. ለተቆጣጣሪ ባለስልጣን የሚከፈል ቀረጥ/ ▶️ (ወርሃዊ የኃይል ፍጆታ በኪዋሰ+የአገልግሎት ክፍያ)*0.5% ይህም ማለት (1,571.43 + 46.75)*0.5% 🟰 8.0909 ብር፣

6. ከ50 ኪ.ዋ.ሰ በላይ ለኢትጵያ ብሮድካስት ኮርፖሬሽን (ኢቲቪ) የሚከፈል 🟰 10 ብር፣

በመሆኑም ከላይ በተቀመጠው አሠራር መሰረት የደንበኛችን ወርሃዊ የኤሌክሪክ ፍጆታ ሂሳብ እንደሚከተለው ይሆናል፡

➡️ ወርሃዊ ፍጆታ (1571.43 ብር)
➡️ የተጨማሪ እሴት ታክስ (235.7145 ብር)
➡️ የአገልግሎት ክፍያ (46.75 ብር)
➡️ የአገልግሎት ክፍያ ተጨማሪ እሴት ታክስ (7.0125 ብር)
➡️ የተቆጣጣሪ ባለስልጣን የሚከፈል (8.0909 ብር)
➡️ ለኢቲቪ የሚከፈል የቴሌቪዥን አገልግሎት ክፍያ (10 ብር)
✅ ጠቅላላ ድምር 🟰1,878.9979 ብር (1 ሺህ 878 ብር 9979 ሳንቲም) ደንበኛው ይፈፅማል ማለት ነው፡፡

ይሔንን ማውጣት በሀሜት ያስቀጣል 😂😂😂
07/12/2025

ይሔንን ማውጣት በሀሜት ያስቀጣል 😂😂😂

አይ ባዴ ባዴሳ 😂😂😂 ጀለስ ግጥም ላይ ቀሽም የሆነው የደን ሀብታችን በመመናመኑ ነው 😂😂😂
07/02/2025

አይ ባዴ ባዴሳ 😂😂😂 ጀለስ ግጥም ላይ ቀሽም የሆነው የደን ሀብታችን በመመናመኑ ነው 😂😂😂

የአጎአ መታገድን ተከትሎ 18 የውጭ ኩባንያዎች ከኢትዮጵያ ለቀዉ መወጣታቸው ተገለፀየአፍሪካ የዕድገትና ዕድል ህግ (አጎአ) መታገዱን ተከትሎ ወደ 18 የሚጠጉ የውጭ ኩባንያዎች ኢትዮጵያን ለቀ...
06/29/2025

የአጎአ መታገድን ተከትሎ 18 የውጭ ኩባንያዎች ከኢትዮጵያ ለቀዉ መወጣታቸው ተገለፀ

የአፍሪካ የዕድገትና ዕድል ህግ (አጎአ) መታገዱን ተከትሎ ወደ 18 የሚጠጉ የውጭ ኩባንያዎች ኢትዮጵያን ለቀው መውጣታቸው በአፍሪካ ዲቨለፕመንት ባንክ ግሩፕ (AfDB) ይፋ በተደረገ አዲስ ሪፖርት ተገለጸ። ይህ ደግሞ የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ፓርኮች የ45 ሚሊዮን ዶላር ገቢ እንዲያጡ ምክንያት ሆኗል።

ባንኩ "Country Focus Report 2025 Ethiopia" በሚል ርዕስ ባወጣዉ ሰፊ የጥናት ግኝት መሰረት፣ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም በአጎአ በኩል ለብዙ ምርቶች ከቀረጥ ነጻ ወደ አሜሪካ ገበያ የመግባት ዕድል ነበራት። ይሁን እንጂ በጥር 2022 የAGOA መታገድ ቀደም ሲል የተቋቋሙ የገበያ ትስስሮችን እና የአቅርቦት ሰንሰለቶችን በእጅጉ ማቋረጡን ሪፖርቱ አስረድቷል።

ይህም ከኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ፓርኮች የሚላኩ ምርቶች በ2023 በ24% እንዲቀንሱ አድርጓል። በተለይም በሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ከ1,000 በላይ የሥራ ዕድሎች የተቋረጡ ሲሆን ለኢንዱስትሪ ፓርኮች በጠቅላላው 45 ሚሊዮን ዶላር የገቢ ኪሳራ አስከትሏል።

Via Capital

😞 😞 😞ዩጋንዳ ኢትዮጵያን በመብለጥ በአፍሪካ ቀዳሚ ቡና ላኪ ሀገር ሆናለች ሲል ማክሰኞ የወጣ ዘገባ አመልክቷል።የኡጋንዳ የግብርና፣ የእንስሳት ኢንዱስትሪ እና አሳ ሀብት ሚኒስቴር በዋና ከተ...
06/28/2025

😞 😞 😞
ዩጋንዳ ኢትዮጵያን በመብለጥ በአፍሪካ ቀዳሚ ቡና ላኪ ሀገር ሆናለች ሲል ማክሰኞ የወጣ ዘገባ አመልክቷል።

የኡጋንዳ የግብርና፣ የእንስሳት ኢንዱስትሪ እና አሳ ሀብት ሚኒስቴር በዋና ከተማዋ ካምፓላ በሰጠው መግለጫ ሀገሪቱ በግንቦት ወር 793,445 ባለ60 ኪሎ ግራም ከረጢት ቡና ወደ ውጭ በመላክ 243 ሚሊዮን ዶላር ገቢ አግኝታለች።

"የኡጋንዳ የቡና ኢንዱስትሪ ታሪካዊ ምዕራፍ ላይ ደርሷል። በግንቦት 2025 ዩጋንዳ በአፍሪካ ቀዳሚ ቡና ላኪ ሆና 47,606.7 ቶን በማስመዝገብ የኢትዮጵያ ቀደምት ስኬቶችን በልጧል" ብለዋል።

በፈረንጆቹ አቆጣጠር በግንቦት 2025 የኡጋንዳ ኤክስፓርት መጠን የኢትዮጵያን 43,481.02 ቶን በልጧል፣ ይህም በአህጉሪቱ የቡና ንግድ እንቅስቃሴ ላይ ወሳኝ ለውጥ አሳይቷል ሲሉ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

ሚኒስቴሩ የዘርፉን ልዩ እድገት የተሻሻለ የጥራት ደረጃዎች እና ጠንካራ የመንግስት ድጋፍ ስለነበረው ነው ብለዋል።

"በጠንካራ የጥራት ቁጥጥር፣ ሰፊ የገበሬ ማሰልጠኛ ፕሮግራሞች እና ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን ግብአቶች ተደራሽ በማድረግ የኡጋንዳ ቡና በላቀ ጥራት እና ልዩ ጣዕም መገለጫዎች በዓለም ገበያ ከፍተኛ ዋጋ ያለው ሆኗል" ሲል መግለጫው ገልጿል።

ሚኒስቴሩ በመጪዎቹ ወራት የምርት መጠን ይጨምራል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፥ በአሁኑ ወቅት ዋናው የመኸር ወቅት በቡና አብቃይ በሆኑ አካባቢዎች በመካሄድ ላይ ነው።

የኡጋንዳ ከፍተኛ የቡና ኤክስፖርት መዳረሻዎች ጣሊያን፣ ጀርመን፣ ስፔን፣ ሕንድ፣ ሱዳን፣ ቤልጂየም፣ ቻይና፣ አልጄሪያ፣ አሜሪካ እና ሞሮኮ ይገኙበታል።
ምንጭ:- The Independent

ያሳዝናል መምህር ደረጀ ነጋሽ በእስር ቤት ታመዉ ሆስፒታል ገብተዋል
06/27/2025

ያሳዝናል መምህር ደረጀ ነጋሽ በእስር ቤት ታመዉ ሆስፒታል ገብተዋል

Address

Jersey City, NJ

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ:

Share