01/03/2026
የቬንዚዌላ መከላከያ ሚኒስቴር በመላ አገሪቱ የጦር ኃይሉ እንደሚሰማራ አስታወቁ።
ቭላድሚር ፓድሪኖ ሎፔዝ በቪዲዮ ባስተላላፉት መልዕክት ቬንዚዌላ አይታ የማታውቀው “አስከፊ ጥቃት” ገጥሟታል፤ በ“ማዱሮ ትዕዛዝ” የጦር ኃይሉ በመላ አገሪቱ ይሰማራል ብለዋል።
“አጥቅተውናል ነገር ግን እንድንበረከክ ግን አያደርጉንም” ሲሉ የመከላከያ ሚኒስትሩ ጨምረው ተናግረዋል።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት በቬንዚዌላ ወታደራዊ የጦር ካምፖች ላይ ጥቃት መሰንዘራቸውን እና የአገሪቱን ፕሬዚዳንት ከእነባለቤታቸው በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን ተናግረዋል።
ፕሬዚዳንቱ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ ማዱሮ እና ባለቤታቸው በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ ከአገር አንዲወጡ ተደርገዋል ብለዋል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዋሽንግተን “ቬንዙዌላ ላይ ሰፊ ጥቃት” መፈፀሟን እና መሪውን ፕሬዝዳንት ኒኮላስ ማዱሮን እና ባለቤታቸውን መያዟን አስታወቁ።
ትራምፕ በትሩዝ ማኅበራዊ የትስስር ገጻቸው “ዩናይትድ ስቴትስ ውጤታማ የሆነ ሰፊ ጥቃት በቬንዙዌላ እና በመሪዋ ላይ ፈፅማለች። ፕሬዝዳንት ኒኮላስ ማዱሮ ከባለቤታቸው ጋር ተይዘው ከአገሪ ውጭ እንዲወጡ ተደርጓል” ብለዋል።
ትራምፕ ፕሬዝዳንቱ እንዴት እንደተያዙ ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
“ተልዕኮው በአሜሪካ የህግ ማስከበር መሰረት ተካሂዷል። ዝርዝሮች መውጣታቸውን ይቀጥላሉ. . . በማለት በመኖሪያ ቤታቸው መግለጫ እንደሚሰጡ ጠቅመዋል።
የቬንዙዌላ መንግሥት እስካሁን የፕሬዝዳንቱን መያዝ በሚመለከት ማረጋገጫ አልሰጠም።
ቅዳሜ ጠዋት ከቬንዙዌላ ዋና ከተማ ጭስ ሲወጣ ከታየ በኋላ የአሜሪካ ባለሥልጣናት በከተማዋ በሚገኙ ወታደራዊ ሠፈሮች ላይ ጥቃት እንዲሰነዘር ትዕዛዝ እንደተሰጠ አረጋግጠዋል።
የቬንዙዌላ መንግሥት ብሔራዊ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጇል። አሜሪካ ኒኮላስ ማዱሮ ዓለም አቀፍ አደገኛ ዕፅ አዘዋዋሪ ድርጅትን ይመራሉ የሚል ክስ ለረጅም ጊዜ ስታቀርብ ቆይታለች።
ዋሽንግተን ፕሬዝዳንቱን በቁጥጥር ስር ማዋል የሚያስችል መረጃ ለሚሰጡ ሰዎች የ50 ሚሊዮን ዶላር ጉርሻ አውጥታ ነበር።
Via bbc