Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ

Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ is an Ethiopian entertainment and news website launched in March 2016. The official page of tobiatube247.com
(3)

01/04/2026

ከተሸለሙ አይቀር እንዲህ ነው 😀😀😀
በቴሌ ጨዋታዎች አንድ ግለሰብ የመኪና ሽልማት ይደርሰውና ሽልማቱን ለመቀበል ወደ ቴሌ ከባለቤቱ ጋር ያቀናል ታዲያ በዕለቱ ሌላ ሽልማት የማውጣት ስነስርዓት ነበር እና እጣው ሲወጣ ለማን ቢወጣ ጥሩ ነው ለባለቤቱ 😀😀😀
የጅማዎቹ ጥንዶች የ 2 መኪና ባለቤት የሆኑበት አጋጣሚ 😂😂😂

የቬንዚዌላ መከላከያ ሚኒስቴር በመላ አገሪቱ የጦር ኃይሉ እንደሚሰማራ አስታወቁ።ቭላድሚር ፓድሪኖ ሎፔዝ በቪዲዮ ባስተላላፉት መልዕክት ቬንዚዌላ አይታ የማታውቀው “አስከፊ ጥቃት” ገጥሟታል፤ በ...
01/03/2026

የቬንዚዌላ መከላከያ ሚኒስቴር በመላ አገሪቱ የጦር ኃይሉ እንደሚሰማራ አስታወቁ።

ቭላድሚር ፓድሪኖ ሎፔዝ በቪዲዮ ባስተላላፉት መልዕክት ቬንዚዌላ አይታ የማታውቀው “አስከፊ ጥቃት” ገጥሟታል፤ በ“ማዱሮ ትዕዛዝ” የጦር ኃይሉ በመላ አገሪቱ ይሰማራል ብለዋል።
“አጥቅተውናል ነገር ግን እንድንበረከክ ግን አያደርጉንም” ሲሉ የመከላከያ ሚኒስትሩ ጨምረው ተናግረዋል።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት በቬንዚዌላ ወታደራዊ የጦር ካምፖች ላይ ጥቃት መሰንዘራቸውን እና የአገሪቱን ፕሬዚዳንት ከእነባለቤታቸው በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን ተናግረዋል።
ፕሬዚዳንቱ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ ማዱሮ እና ባለቤታቸው በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ ከአገር አንዲወጡ ተደርገዋል ብለዋል።

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዋሽንግተን “ቬንዙዌላ ላይ ሰፊ ጥቃት” መፈፀሟን እና መሪውን ፕሬዝዳንት ኒኮላስ ማዱሮን እና ባለቤታቸውን መያዟን አስታወቁ።
ትራምፕ በትሩዝ ማኅበራዊ የትስስር ገጻቸው “ዩናይትድ ስቴትስ ውጤታማ የሆነ ሰፊ ጥቃት በቬንዙዌላ እና በመሪዋ ላይ ፈፅማለች። ፕሬዝዳንት ኒኮላስ ማዱሮ ከባለቤታቸው ጋር ተይዘው ከአገሪ ውጭ እንዲወጡ ተደርጓል” ብለዋል።
ትራምፕ ፕሬዝዳንቱ እንዴት እንደተያዙ ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

“ተልዕኮው በአሜሪካ የህግ ማስከበር መሰረት ተካሂዷል። ዝርዝሮች መውጣታቸውን ይቀጥላሉ. . . በማለት በመኖሪያ ቤታቸው መግለጫ እንደሚሰጡ ጠቅመዋል።
የቬንዙዌላ መንግሥት እስካሁን የፕሬዝዳንቱን መያዝ በሚመለከት ማረጋገጫ አልሰጠም።
ቅዳሜ ጠዋት ከቬንዙዌላ ዋና ከተማ ጭስ ሲወጣ ከታየ በኋላ የአሜሪካ ባለሥልጣናት በከተማዋ በሚገኙ ወታደራዊ ሠፈሮች ላይ ጥቃት እንዲሰነዘር ትዕዛዝ እንደተሰጠ አረጋግጠዋል።

የቬንዙዌላ መንግሥት ብሔራዊ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጇል። አሜሪካ ኒኮላስ ማዱሮ ዓለም አቀፍ አደገኛ ዕፅ አዘዋዋሪ ድርጅትን ይመራሉ የሚል ክስ ለረጅም ጊዜ ስታቀርብ ቆይታለች።
ዋሽንግተን ፕሬዝዳንቱን በቁጥጥር ስር ማዋል የሚያስችል መረጃ ለሚሰጡ ሰዎች የ50 ሚሊዮን ዶላር ጉርሻ አውጥታ ነበር።

Via bbc

01/03/2026

ማዱሮ ከተያዘ በኋላ ትራምፕ አሜሪካ 'ሀገሪቱን እንደምታስተዳድር' ተናገሩ

"ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ተገቢ እና አስተዋይነት የተሞላበት ሽግግር እስኪደረግ ድረስ አሜሪካ ቬንዙዌላን ታስተዳድራለች" - ትራምፕ

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ "የቬንዙዌላን ህዝብ ጥቅም ያላሰበ ሌላ ሰው ቬንዙዌላን እንዲቆጣጠር እድል አንወስድም" ብለዋል።

ሩሲያ አሜሪካ በቬንዙዌላ ላይ የሰነዘረችውን ጥቃት እና የማዱሮን መያዝ በፅኑ ተቃወመችየቬንዙዌላ የቅርብ የፖለቲካ አጋር የሆነችው ሩሲያ፣ አሜሪካ በቁጥጥር ስር ያዋለቻቸውን ፕሬዚዳንት ኒኮላስ...
01/03/2026

ሩሲያ አሜሪካ በቬንዙዌላ ላይ የሰነዘረችውን ጥቃት እና የማዱሮን መያዝ በፅኑ ተቃወመች

የቬንዙዌላ የቅርብ የፖለቲካ አጋር የሆነችው ሩሲያ፣ አሜሪካ በቁጥጥር ስር ያዋለቻቸውን ፕሬዚዳንት ኒኮላስ ማዱሮን እና ባለቤታቸውን በአስቸኳይ እንድትለቅ ጠየቀች።

የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በጉዳዩ ላይ ባወጣው መግለጫ፤ የአሜሪካን እርምጃ አጥብቆ ተቃውሟል።

"የቬንዙዌላው ፕሬዚዳንት ኒኮላስ ማዱሮ እና ባለቤታቸው በአሜሪካ ውስጥ በቁጥጥር ስር መሆናቸው መረጋገጡን ተከትሎ፣ የአሜሪካ አመራር የወሰደውን እርምጃ እንደገና እንዲያጤን አጥብቀን እናሳስባለን" ያለው ሚኒስቴሩ፤ አሜሪካ "በህጋዊ መንገድ የተመረጡትን የአንድ ሉዓላዊ ሀገር ፕሬዚዳንት እና ባለቤታቸውን በአስቸኳይ እንድትለቅ" ጥሪ አቅርቧል።

አሜሪካ ቅዳሜ ማለዳ በደቡብ አሜሪካዊቷ አገር ቬንዙዌላ ላይ ጥቃት ፈጽማ ፕሬዝዳንት ኒኮላስ ማዱሮን በቁጥጥር ሥር ማዋሏን ካሳወቀች በኋላ ክስ እንደመሠረተችባቸው ገለጸች።በፊትበአሜሪካ ጥርስ ...
01/03/2026

አሜሪካ ቅዳሜ ማለዳ በደቡብ አሜሪካዊቷ አገር ቬንዙዌላ ላይ ጥቃት ፈጽማ ፕሬዝዳንት ኒኮላስ ማዱሮን በቁጥጥር ሥር ማዋሏን ካሳወቀች በኋላ ክስ እንደመሠረተችባቸው ገለጸች።

በፊትበአሜሪካ ጥርስ ውስጥ ስለገባችው ቬንዙዌላ አንዳንድ እውነታዎች:-

ፕሬዝዳንት ትራምፕ አሜሪካ በቬንዙዌላ ላይ ከፍተኛ ጥቃት ከፈጸመች በኋላ የአገሪቱን ፕሬዝዳንት ኒኮላስ ማዱሮን በቁጥጥር ሥር አውላለች ብለዋል።
በአውሮፓውኑ 1989 የፓናማ ወታደራዊ መሪ የነበሩትን ማኑኤል ኑሬጋን ከሥልጣን ካባረረችበት ወረራ ወዲህ ቀጥተኛ ጣልቃ ገብነትን ላቲን አሜሪካ ውስጥ ፈጽማ አታውቅም ነበር።

ትራምፕ እንዳሉት ፕሬዝዳንት ማዱሮን ከሥልጣን ካስወገዱ በአስተደዳራቸው ውስጥ በቬንዙዌላ የመንግሥት ለውጥ እንዲደረግ ሲወተውቱ ለነበሩ ነውጠኛ ባለሥልጣናት አስደሳች ድል ነው።

አሜሪካ ኒኮላስ ማዱሮ ወንጀለኛ የእጽ አዘዋዋሪ ድርጅትን ይመራሉ ስትል በተደጋጋሚ ብትከስም እሳቸው ግን ሲያስተባብሉ ነበር። በተጨማሪም ከፍተኛ መጭበርበር ተፈጽሞበታል በተባለው የ2024 ምርጫ ማሸነፋቸውን አሜሪካ አትቀበልም።

በቬንዙዌላ ባለሥልጣናት በኩልም አሜሪካ እንዲህ በጠላትነት ጠምዳ የያዘቻቸው በዓለም የተረጋገጠ ትልቁን የነዳጅ ክምችቷን ለመቆጣጠር በመፈለግ ነው በማለት ይከስሳሉ።

ቬንዙዌላ አንዳንድ እውነታዎች:-
በደቡብ አሜሪካ ሰሜናዊ የውቅያኖስ ዳርቻ ላይ የምትገኘው ቬንዙዌላ ከካሪቢያን ባሕር ጋር ረጅም የባሕር ዳርቻን ትጎራበታለች፡፡

በስተ ምዕራብ ከኮሎምቢያ፣ በደቡብ ከብራዚል እና በምሥራቅ ከጉያና ጋር ድንበር ትጋራለች።

የሕዝብ ብዛት
ቬንዙዌላ ወደ 28 ሚሊዮን የሚጠጋ ሕዝብ ያላት ሲሆን፣ አብዛኛው ሕዝቧ በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል ውስጥ ይኖራል።

አምሰት ሚሊዮን የሚሆነው ሕዝቧ በዋና ከተማዋ ካራካስ ውስጥ ወይም በዙሪያዋ ይገኛል።

የተፈጥሮ ሀብት
ቬንዙዌላ በዓለም ትልቁ የተረጋገጠ የነዳጅ ዘይት ክምችት፣ ከፍተኛ መጠን ያለው የድንጋይ ከሰል፣ ባክሳይት እና ወርቅ ያላት አገር ናት፡፡

ትላልቆቹ የነዳጅ ጉድጓዶች የሚገኙት በሰሜን ምዕራብ ማራካይቦ እና ኦሪኖኮ በተባሉት አካባቢዎች ነው፡፡

ተፈጥሮ
የአንዲሰ ተራራ ቬንዙዌላ ከኮሎምቢያ ጋር ከምትዋሰንበት ድንበር ተነሰቶ አስከ ሰሜናዊ የባሕር ዳርቻዋ ድረስ ተዘርግቷል።

ከብራዚል የሚነሳው የአማዞን ጥቅጥቅ ደን ደቡባዊውን የቬንዙዌላ ክፍልን ይሸፍናል።
ፖለቲካ
ከአውሮፓውያኑ 2013 ጀምሮ አገሪቱን ሲመሩ የቆዩት ኒኮላስ ማዱሮ ናቸው::

ማዱሮ ከፍተኛ ማጭበርበር ተፈጽሞበታል በተባለው በ2024 በተካሄደው ምር ጫ ማሸነፋቸው ታውጇል።

(ቢቢሲ)

ህዝቤ: ኢትዮቴሌኮም እባካችሁ ኔትወርኩን አስተካክሉኢትዮቴሌኮም: ኸረ እንደውም ብር ጨምሩ
12/30/2025

ህዝቤ: ኢትዮቴሌኮም እባካችሁ ኔትወርኩን አስተካክሉ
ኢትዮቴሌኮም: ኸረ እንደውም ብር ጨምሩ

ሳፋሪኮም በዳታ ጥቅሎች ላይ እስከ 82% የዋጋ ጭማሪ ማድረጉን ተከትሎ ኢትዮ ቴሌኮም ምን አለ?ኢትዮ ቴሌኮም በተወሰኑ የአገልግሎት ጥቅሎች ላይ የ23 በመቶ አማካይ የዋጋ ጭማሪ ማድረጉን ዛሬ...
12/29/2025

ሳፋሪኮም በዳታ ጥቅሎች ላይ እስከ 82% የዋጋ ጭማሪ ማድረጉን ተከትሎ ኢትዮ ቴሌኮም ምን አለ?

ኢትዮ ቴሌኮም በተወሰኑ የአገልግሎት ጥቅሎች ላይ የ23 በመቶ አማካይ የዋጋ ጭማሪ ማድረጉን ዛሬ ሰኞ ታኅሳስ 20 በማኅበራዊ ትስስር ገጹ በኩል ባሠራጨው መረጃ አስታውቋል።

በዚህም መሠረት፣ በቴሌብር በኩል በ10 በመቶ ቅናሽ ሲገዛ የነበረው ጥቅል ወደ 20 በመቶ ከፍ እንዲል ማድረጉን ተቋሙ ገልጿል። በርካታ ደንበኞች የሚጠቀሙባቸው 38 የተለያዩ ጥቅሎች ላይ ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪ አለመደረጉን ያወሳው ኩባንያው፣ በተለይም ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች የሚጠቀሙባቸው የ1 ብር፣ የ2 ብር፣ የ5 ብር እና የ1 ሰዓት ጥቅሎች ባሉበት እንዲቀጥሉ መወሠኑን ገልጧል።

የታሪፍ ማሻሻያውን ማድረግ ያስፈለገው፣ በአሁኑ ወቅት ባለው የማክሮ ኢኮኖሚ ሁኔታ የሥራ ማስኬጃ እና የካፒታል ወጪዎቹ በመጨመራቸው፣ የአገልግሎት ጥራቱን በዘላቂነት ለማስጠበቅ አስፈላጊ ሆኖ ስላገኘው መሆኑን ተቋሙ ባሰራጨው መረጃ ጨምሮ ጠቅሷል።

የ"ሄሎ ታክሲ" ባለቤትና ስራ አስኪያጅ በቁጥጥር ስር ዋሉየነገን ኑሮ ለማሸነፍ፣ ከእለት ጉርሳቸው ቀንሰው፣ "የራሴን ታክሲ ይዤ ህይወቴን እቀይራለሁ" በሚል ተስፋ የሰነቁ 127 ንጹሃን ዜጎች...
12/29/2025

የ"ሄሎ ታክሲ" ባለቤትና ስራ አስኪያጅ በቁጥጥር ስር ዋሉ

የነገን ኑሮ ለማሸነፍ፣ ከእለት ጉርሳቸው ቀንሰው፣ "የራሴን ታክሲ ይዤ ህይወቴን እቀይራለሁ" በሚል ተስፋ የሰነቁ 127 ንጹሃን ዜጎች በከባድ የማታለል ወንጀል ሰለባ መሆናቸው ተሰማ። የአዲስ አበባ ፖሊስ ይህንኑ የብዙዎችን ቤት ያናጋ ወንጀል ፈጽመዋል የተባሉትን የ"ሄሎ ታክሲ" ባለቤት እና የስራ ኃላፊዎችን በቁጥጥር ስር አውሏል።

በከተማዋ እያደገ ከመጣው የትራንስፖርት ፍላጎት ጋር ተያይዞ፣ ዜጎች ህይወታቸውን ለማሻሻል የሚያደርጉትን ጥረት እንደ ምቹ አጋጣሚ የተጠቀሙት እነ አቶ ዳንኤል ዮሐንስ (የሄሎ ታክሲ ባለቤት)፣ ወ/ሪት እንግዳ የሺጥላ እና ግብረአበሮቻቸው፤ የዜጎችን ላብ እና ወዝ ለግል ጥቅማቸው ለማዋል ሲንቀሳቀሱ እንደነበር ፖሊስ አጋልጧል።

ተጠርጣሪዎቹ "በአነስተኛ ቅድመ ክፍያ የመኪና ባለቤት እናደርጋለን" የሚል ጣፋጭ ማስታወቂያ በመጠቀም፣ እያንዳንዱ ተጎጂ ከ130 ሺህ እስከ 350 ሺህ ብር እንዲከፍል አድርገዋል። ይህ ገንዘብ ለብዙዎቹ ተጎጂዎች የዓመታት የድካም ዋጋ፣ ምናልባትም ቋጥረው ያስቀመጡት የመጨረሻ ተስፋቸው ነበር። ሆኖም፣ ቃል የተገባው መኪና የለም፤ የተከፈለውም ገንዘብ በጥርጣሬ ውስጥ ወድቋል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ እንዳስታወቀው፣ እነዚህ ግለሰቦች ባልተገባ መንገድ ለመክበር በማሰብ የበርካታ ዜጎችን ህይወት አደጋ ላይ ጥለዋል። ፖሊስ አክሎም፣ "በአቋራጭ ለመክበር ከድሃው ዜጋ ጉሮሮ ላይ የሚነጥቁ አካላትን አንታገስም" ሲል አስጠንቅቋል።

በአሁኑ ወቅት አቶ ዳንኤል እና ተባባሪዎቻቸው በቁጥጥር ስር ውለው በከባድ የማታለል ወንጀል ምርመራ እየተጣራባቸው ይገኛል። ይህ ክስተት "ተስፋችንን አጨለሙብን" ብለው ለሚያነቡ 127 ቤተሰቦች ፍትህ የማግኘት ጅምር ተደርጎ ተወስዷል።
(Addis Ababa Police)

12/26/2025
እስራኤል ለሶማሊላንድ የሀገርነት እውቀና ሰጠችእስራኤል ለሶማሊላንድ ሪፐብሊክ ሙሉ የሀገርነት እውቅና መስጠቷን በይፋ አስታወቀች። ይህም ሶማሊላንድ ከአምስት አስርት ዓመታት በላይ ስታደርገው ...
12/26/2025

እስራኤል ለሶማሊላንድ የሀገርነት እውቀና ሰጠች

እስራኤል ለሶማሊላንድ ሪፐብሊክ ሙሉ የሀገርነት እውቅና መስጠቷን በይፋ አስታወቀች። ይህም ሶማሊላንድ ከአምስት አስርት ዓመታት በላይ ስታደርገው የነበረውን ዓለም አቀፍ እውቅና የማግኘት ጥረት ትልቅ ምዕራፍ ከፋች ሆኗል።

የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ሳር እንደገለፁት ፤ እስራኤል እና ሶማሊላንድ ሙሉ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ለመመስረት የሚያስችል ስምምነት መፈራረማቸውን ገልጸዋል።
ስምምነቱ በሁለቱ አገራት መካከል አምባሳደሮችን መሾም እና ኤምባሲዎችን መክፈትንም ያካትታል።

ይህ ታሪካዊ ስምምነት ሶማሊላንድ እ.ኤ.አ. በ1991 ከሶማሊያ ተገንጥላ ነፃነቷን ካወጀች በኋላ በአንድ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አባል ሀገር እውቅና ስታገኝ የመጀመሪያዋ ያደርጋታል። ሶማሊላንድ የቀድሞው የብሪታንያ ጥበቃ ስር የነበረች ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በሰሜናዊ ሶማሊያ የሚገኘውን ሰሜን ምዕራባዊ ግዛት የምታስተዳድር ክልል ነች።

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ከሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት አብዲራህማን መሐመድ አብዱላሂ ጋር በቪዲዮ ባደረጉት ውይይት፤ አዲሱን ግንኙነት "ታሪካዊ እና ትልቅ ፋይዳ ያለው" ሲሉ ገልጸውታል።

ኔታንያሁ ፕሬዝዳንቱ በእስራኤል ጉብኝት እንዲያደርጉ የጋበዙ ሲሆን፣ ይህ አጋርነት በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለውን ትብብር ለማስፋፋት ትልቅ ዕድል መሆኑን ጠቁመዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሳር እንደገለጹት፤ ስምምነቱ የተደረሰው በሁለቱ መንግሥታት መካከል ለአንድ ዓመት ያህል ሲደረግ በነበረ ሰፊ ውይይት እና በኔታንያሁና በአብዱላሂ የጋራ ውሳኔ መሠረት ነው።

ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልእክት "በአገሮቻችን መካከል ያለውን ግንኙነት፣ የቀጣናውን መረጋጋት እና የኢኮኖሚ ብልጽግናን ለማሳደግ በጋራ እንሰራለን" ብለዋል።

በተጨማሪም ሳር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤታቸው በተለያዩ ዘርፎች ግንኙነቱን በአስቸኳይ ወደ ተቋማዊ አሰራር እንዲቀይር መመሪያ ሰጥተዋል።

ኢትዮጵያ ታህሳስ 2016 ዓ.ም. ከሶማሊላንድ ጋር የመግባቢያ ሰነድ መፈረሟ ይታወሳል። በወቅቱ ኢትዮጵያ ለባህር ኃይል የሚሆን የባህር በር ለማግኘት በምትኩ ለሶማሊላንድ እውቅና ለመስጠት ቃል ገብታ ነበር።

ሆኖም ይህ ስምምነት ከሶማሊያ መንግስት እና ከቀጠናው ሀገራት በገጠመው ከፍተኛ ተቃውሞ ሳቢያ ተግባራዊነቱ ተገትቶ ቆይቷል። አሁን እስራኤል የወሰደችው እርምጃ በአፍሪካ ቀንድ ያለውን የዲፕሎማሲ ሚዛን በእጅጉ ሊቀይረው እንደሚችል እየተገመተ ይገኛል።
(Via Capital)

12/25/2025

መስጠት ፀጋ ነው!

ሰብዐዊ እርዳታና ፓለቲካ ለተጋጨባቸው 😏😏😏''ተረጅዎች እንጂ እርዳታውን የሚያስተባብር አካል እረጂውን የመምረጥ መብት የለውም። ሲቀጥል በሠብአዊነት እይታ ጠላትህንም ቢሆን የማገዝ ወይም በጠ...
12/25/2025

ሰብዐዊ እርዳታና ፓለቲካ ለተጋጨባቸው 😏😏😏
''ተረጅዎች እንጂ እርዳታውን የሚያስተባብር አካል እረጂውን የመምረጥ መብት የለውም። ሲቀጥል በሠብአዊነት እይታ ጠላትህንም ቢሆን የማገዝ ወይም በጠላት እጅ መረዳት ስህተት ሊሆን አይችልም።''

Address

Jersey City, NJ

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ:

Share