Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ

Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ is an Ethiopian entertainment and news website launched in March 2016. The official page of tobiatube247.com
(1)

ኢትዮጵያ የኬንያን የመብራት ፈረቃ ማስቀረቷ ተዘገበ፡፡ የኬንያው ካፒታል ኤፍኤም እንደዘገበው ኬንያ ከውጭ ከምትገዛው የኤሌክትሪክ ሀይል ውስጥ ቀዳሚዋ አቅራቢ አገር ኢትዮጵያ ሆናለች፡፡ በጁን...
10/01/2025

ኢትዮጵያ የኬንያን የመብራት ፈረቃ ማስቀረቷ ተዘገበ፡፡
የኬንያው ካፒታል ኤፍኤም እንደዘገበው ኬንያ ከውጭ ከምትገዛው የኤሌክትሪክ ሀይል ውስጥ ቀዳሚዋ አቅራቢ አገር ኢትዮጵያ ሆናለች፡፡

በጁን ወር 2025 ባለው መረጃ መሰረት አገሪቱ ከውጭ ከገዛችው የኤሌክትሪክ ሀይል 83 ፐርሰንቱ ከኢትዮጵያ መሆኑን ያስረዳው ዘገባው፣ በዚህ አመት ከኢትዮጵያ የተገዛው ሀይል 1274 ጊጋ ዋት ሀወር መሆኑን ጠቅሷል፡፡ በዚሁ ጊዜ ከኡጋንዳ 225 ጊጋ ዋት ሀወርና ከታንዛኒያ ደግሞ 33 ጊጋ ዋት ሀወር መብራት መግዛቷን ያስታወቀው ዘገባው ጨምሮም በዚህ አመት ኬንያ ከውጭ የገዛችው የኤሌክትሪክ ሀይል በ27 ፐርሰንት መጨመሩን አስታውቋል፡፡

ይህ የሆነው ደግሞ በኢትዮጵያና ኬንያ መካከል የኤሌክትሪክ ግዢ ስምምነት ተግባራዊ መሆን በመጀመሩ ነው ብሏል፡፡ የኬንያ የሀይልና ፔትሮሊየም ተቆጣጣሪ ባለስልጣን ለዜና አውታሩ በሰጠው መግለጫ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል መግዛት መቻሉ ወጪ ለመቆጠብም እንደረዳው አስረድቷል፡፡ በዚህም በአመት 10 ሚሊዮን ዶላር ያህል ወጪ እንደሚያድንም ገልጿል፡፡

በሌላ በኩል ቢዝነስ ዴይሊ አፍሪካ የተሰኘው የኬንያ ጋዜጣ እንደዘገበው አገሪቱ በሀይል እጥረት ከፍተኛ አደጋ ውስጥ በገባችበት ወቅት ከኢትዮጵያ መፍትሄ አግኝታለች፡፡ በዘገባው በኬንያ ውስጥ የመብራት ፈረቃ የነበረ ከመሆኑም በላይ በአንዳንድ አካባቢዎች ለተወሰኑ ቀናት ጨለማ ለመሆን የሚገደዱበት ጊዜም ነበረ፡፡ ‹‹የኬንያን የመብራት ፈረቃ ኢትዮጵያ አስቀርታለች›› ያለው ዘገባው በህዳሴው ግድብ ምርቃት ላይ የኬንያው ፕሬዝደንት ዊልያም ሩቶ የክብር እንግዳ በመሆን መገኘታቸውን አውስቷል፡፡

ባለፈው ሰኔ ወር ኬንያ 200 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሀይል ከኢትዮጵያ ለመግዛት በምትችልበት ሁኔታ ላይ ስምምነት ማድረጓን ጠቅሶም ከህዳሴው ግድብ መጠናቀቅ በኋላ ተጨማሪ 200 ሜጋ ዋት ለመግዛት ጥያቄ ማቅረቧንም አስታውቋል፡፡
(Zehabesha)

09/30/2025

"Quantum English" 😂😂 AI እንኳን መፍታት ያልቻለው እንግሊዝኛ 😂😂 ትርጉሙን ለነገረን ሽልማት አለው

በሰሜን ወሎ ጤና ጣቢያ ላይ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት አራት ሰላማዊ ሰዎች ሲገደሉ 10 ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን የዓይን እማኞች ተናገሩ (BBC Amharic)በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ጉባላ...
09/30/2025

በሰሜን ወሎ ጤና ጣቢያ ላይ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት አራት ሰላማዊ ሰዎች ሲገደሉ 10 ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን የዓይን እማኞች ተናገሩ (BBC Amharic)

በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ጉባላፍቶ ወረዳ ቅዳሜ መስከረም 17/2018 ዓ.ም. ጤና ጣቢያ ላይ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት ነፍሰ ጡር እናትን ጨምሮ የአራት "ሰላማዊ ሰዎች" ሕይወት ሲያልፍ 10 በላይ ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን የዓይን እማኞች እና የሕክምና ምንጮች ለቢቢሲ ተናገሩ።

ጥቃቱ ከዞኑ እና ከወረዳው ዋና ከተማ ወልዲያ 20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ሳንቃ በተባለች የክላስተር ከተማ በሚገኝ ጤና ጣቢያ ላይ ከቀኑ 06፡00 አካባቢ መፈፀሙን አራት የዓይን እማኞች እና የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል። የዞኑ አስተዳደር ስለጥቃቱ እና ስለደረሰው ጉዳት ለመናገር እንደማይችል ለቢቢሲ ተናግሯል።

በስፍራው የነበሩ የጤና ጣቢያው አንድ ባለሙያ መሣሪያው በዋናነት ፊት ለፊት በሆነው እና ታካሚዎች ተኝተው በሚታከሙበት "5 ቁጥር" በተባለው ክፍል ላይ ማረፉን ተናግረዋል። ከጥቃቱ እንደተረፉ የተናገሩት የጤና ጣቢያው ባልደረባ ጥቃቱ የደረሰበትን ቅፅበት ሲገልፁ "ምንም ራሴን አላውቅም፤ መሬት ተሰንጥቆ የዋጠን ነው የመሰለን። ከጎኔ የነበሩት ሲወድቁ እኔን እግዚአብሔር ነው የከለለኝ" ሲሉ እማኝነታቸውን ሰጥተዋል።

ፍንዳታውን ሰምተው በፍጥነት አካባቢው ላይ መድረሳቸውን የተናገሩ ሌላ የዓይን እማኝ ጤና ጣቢያው ውስጥ የነበረ የቤተሰብ አባላቸው ከጥቃቱ መትረፉን ገልፀው፤ ዘግናኝ ሁኔታ መመልከታቸውን ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ወከባ እና ተጨማሪ የጥቃት ስጋት በመፈጠሩ "በደመ-ነፍስ . . .የደማውም፤ የተመታውም እየተዛዘለ ነው የወጣው" ሲሉ ክስተቱን ተናግረዋል። የቆሰሉ ሰዎችን ማውጣታቸውን እና አስከሬን ማንሳታቸውን የተናገሩ ሌላ የዓይን እማኝ ደግሞ ለመግለፅ የሚከብድ ሁነት ማየታቸውን ተናግረዋል።

"ፍንጣሪው እንደ አሽዋ ነው፤ እንደ እሳት ነው የሚያቃጥለው" ያሉት በሕይወት የተረፉ የጤና ጣቢያው ባልደረባ፤ ጤና ጣቢያው ክፉኛ መጎዳቱን ሲገልፁ "ከ5 ቁጥር ጀምሮ እስከ 7 ቁጥር ድረስ የለም" ሲሉ የተቋሙ ክፍሎች መፈራረሳቸውን ገልፀዋል።

ቢቢሲ የተመለከተው እና በገለልተኛ አካል ማረጋገጥ ያልቻላቸውው ፎቶ ግራፎች እና ቪዲዮዎች ጤና ጣቢያው ላይ የደረሰውን ጉዳት ያሳያሉ።

የጤና ጣቢያው ባለሙያ "ዓይናችን እያየ" አራት ታካሚ እና አስታማሚዎች ሕይወታቸው አልፏል ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል። ሦስቱ ልጆቻቸውን ሲያስታምሙ የነበሩ ወላጆች መሆናቸውን ገልፀዋል።

ሁለት የዓይን እማኞችም በጥቃቱ ሦስት ሰዎች ወዲያው ሕይወታቸው ማለፉን መመልከታቸውን ገልፀው፤ ሟቾቹ "ልጆቻቸውን ሲያስታምሙ" የነበሩ እናት እና አባት እንዲሁም ወደ ሕክምና ከሄዱ በኋላ ሕይወታቸው ያለፉ ለሁለት ወራት በጤና ጣቢያው ተኝቶ እየታከመ የነበረ የአንድ ታካሚ አባት መሆናቸውን ተናግረዋል።

የጤና ባለሙያው አራተኛዋ ሟች ለመገላገል ጤና ጣቢያ የመጣች ነፍሰ ጡር ሴት መሆኗን ለቢቢሲ ተናግረዋል።

"ማዋለጃ ክፍል ላይ የሞተች እናት አለች። አንዷ [ነፍሰ ጡር] ወልዳ ነበር፤ አንደኛዋ እየወለደች እያለች ነው የሞተችው። አሁን ስንሰማ አዋላጅ ነርሱም እጁን ተመትቷል" ብለዋል።

በጥቃቱ የጤና ባለሙያ ልጅ የሆነች የስድስት ዓመት ሕፃንን ጨምሮ ከ10 በላይ ሰዎች መቁሰላቸውንም እማኞች ተናግረዋል።

ከእነዚህም መካከል ስምንት የሚሆኑት ቁስለኞች የጤና ጣቢያው ባለሙያዎች መሆናቸውን ገልፀው፤ ከሁለት ቀናት በኋላ ሰኞ ዕለት መንገድ ሲከፈት ቁስለኞች ወደ ወልዲያ ሆስፒታል መወሰዳቸውን ተናግረዋል።

የጤና ጣቢያውን የጽዳት ሠራተኛ ጨምሮ ስድስት ሰዎች ለሕክምና ወልዲያ ሆስፒታል መግባታቸውን እና ከባድ ጉዳት ያጋጠማቸው ሦስቱ ቁስለኞች ቀዶ ሕክምና እንደተደረገላቸው የቢቢሲ ምንጮች ተናግረዋል።

(BBC Amharic)

በውስጥ መስመር የደረሰን ከንግድ ባንክ 700 ብር ወደ አቢሲንያ ልኬ 60 ብር ቆረጠብኝ ይህ ተገቢ ነወ ወይ ይለናል
09/30/2025

በውስጥ መስመር የደረሰን ከንግድ ባንክ 700 ብር ወደ አቢሲንያ ልኬ 60 ብር ቆረጠብኝ ይህ ተገቢ ነወ ወይ ይለናል

በነዳጅ ምርቶች ላይ አጠቃላይ የ30 በመቶ ግብር በተያዘው በጀት ዓመት ተግባራዊ መደረግ ይጀምራሉ ተባለ​ የገንዘብ ሚኒስቴር ከ2018 የበጀት ዓመት ጀምሮ በነዳጅ ምርቶች ላይ አጠቃላይ 30 ...
09/29/2025

በነዳጅ ምርቶች ላይ አጠቃላይ የ30 በመቶ ግብር በተያዘው በጀት ዓመት ተግባራዊ መደረግ ይጀምራሉ ተባለ

​ የገንዘብ ሚኒስቴር ከ2018 የበጀት ዓመት ጀምሮ በነዳጅ ምርቶች ላይ አጠቃላይ 30 በመቶ ግብር ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ እንደሚያደርግ ማረጋገጡ ተሰማ። ይህ አዲስ ግብር 15 በመቶ የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) እና 15 በመቶ የኤክሳይዝ ቀረጥን የሚያካትት መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል።

ይህ እርምጃ በአገሪቱ የፋይናንስ ፖሊሲ ላይ ከፍተኛ ለውጥ የሚያመጣ መሆኑና የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ አንዱ አካል እንደሆነ ተመላክቷል።

​ሚኒስትሩ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ ባቀረቡት አጠቃላይ የዜጎች በጀት ዉስጥ፣ በተያዘው በጀት ዓመት ተግባራዊ የሚደረጉ የግብር አይነቶችን በዝርዝር አስቀምጠዋል።

​በዚህ መሰረት፣ ከነዳጅ ላይ ከሚጣለው አጠቃላይ 30% የኤክሳይዝ ታክስ እና የተጨማሪ እሴት ታክስ በተጨማሪ፣ የንብረት ታክስ ይገኙበታል። እንዲሁም አማራጭ አነስተኛ ታክስ እና የቅድመ ግብር ክፍያ በተመሳሳይ መልኩ በ2018 በጀት ዓመት ተግባራዊ ለማድረግ መታቀዱን ካፒታል ጋዜጣ ለመረዳት ችሏል።

​ነዳጅ በማዕከላዊነት የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ፣ የግብር ጭማሪው የዋጋ ግሽበቱ እንዲባባስ ያደርጋል የሚል ስጋት ሲከሰት እንደነበር ይታወሳል።

ምንጭ:- Capital Ethiopia

የባንኮች የማበደር ጣሪያ  ሙሉ ለሙሉ ሳይነሳ ከ18 ወደ 24 በመቶ  ከፍ እንዲል ተደረገየኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የባንኮች የብድር እድገት ሙሉ በሙሉ ሳይነሳ ከ18 በመቶ ወደ 24 በመቶ ከፍ...
09/29/2025

የባንኮች የማበደር ጣሪያ ሙሉ ለሙሉ ሳይነሳ ከ18 ወደ 24 በመቶ ከፍ እንዲል ተደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የባንኮች የብድር እድገት ሙሉ በሙሉ ሳይነሳ ከ18 በመቶ ወደ 24 በመቶ ከፍ እንዲል መወሰኑን የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ዛሬ መስከረም 19 ቀን 2018 ዓም አስታወቀ።

የብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ተመን(National Bank rate) አሁን ባለበት 15 በመቶ ሆኖ ባለበት እንዲቀጥል፣ ለሚሰጣቸው የተቀማጭ ሂሳብ አገልግሎት(Standing Deposite Facility) እና የብድር አገልግሎት(Standing Lending Facility) የሚከፈሉ የወለድ ተመኖች ባሉበት እንዲቀጥሉ፣ እንዲሁም ባንኮች የሚያስቀምጡት የግዴታ መጠባበቂያ ምጣኔ በነበረበት እንዲቀጥልም መወሰኑን ገልጿል።

የዋጋ ግሽበቱ በሚፈለገው ልክ እንዲሆን ለማስቻል እንዳስፈላጊነቱ ገበያ መር የሆኑ የፖሊሲ መሳሪያዎችን በተናጠልም ሆነ በቅንጅት በቀጣይነት የሚጠቀም መሆኑንና የገንዘብ ፖሊሲ መሳሪያዎች የብሔራዊ ባንክ የወለድ ተመን፣ከባንኮች ጋር የሚደረግ የገንዘብ ግብይት(Open Market Operations )ንና የውጭ ምንዛሪ ገበያ(Foreign Exchange Intervention )ባንኳች በብሔራዊ ባንክ የሚያስቀምጡት የግዴታ መጠባበቂያ ምጣኔ እንዲሆን መወሰኑንም አስታውቋል።

09/28/2025
'' ሰላም ነው ወይ? ''ተወዳጁ ድምፃዊ ወንዲ ማክ አዲስ የለቀቀውን ምርጥ ሙዚቃ ተጋበዙልን
09/21/2025

'' ሰላም ነው ወይ? ''
ተወዳጁ ድምፃዊ ወንዲ ማክ አዲስ የለቀቀውን ምርጥ ሙዚቃ ተጋበዙልን

Wendi Mak - 'ሰላም ነው ወይ?' | ወንዲ ማክ - 'Selam New Wey?' - New Ethiopian Music 2025 (Official Lyric Video) #ሰላምነውወይ ...

🤔🤔🤔
09/17/2025

🤔🤔🤔

የቅርንፉድ ውሀ አዘገጃጀት፣ ጥቅሞች፣ መጠን፣አጠቃቀምና መጠቀም የሌለባቸው ሰዎች
09/15/2025

የቅርንፉድ ውሀ አዘገጃጀት፣ ጥቅሞች፣ መጠን፣አጠቃቀምና መጠቀም የሌለባቸው ሰዎች

#ቅርንፉድ ውሀ አዘገጃጀት፣ተዓምራዊ ጥቅሞች፣መጠን፣አጠቃቀም፣ጉዳቱና መጠቀም የሌለባቸው ሰዎች| Cloves water uses and side effects"በቅንነት ላይክ እና...

(ዘ - ሐበሻ ዜና) ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅን አስመልክቶ ዛሬ በመስቀል አደባባይ ሲካሄድ በነበረው የደስታ ሰልፍ ላይ፣ ከባድ ዝናብን ለመጠለል በተፈጠረ መረጋገጥ ቢያንስ የአን...
09/14/2025

(ዘ - ሐበሻ ዜና) ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅን አስመልክቶ ዛሬ በመስቀል አደባባይ ሲካሄድ በነበረው የደስታ ሰልፍ ላይ፣ ከባድ ዝናብን ለመጠለል በተፈጠረ መረጋገጥ ቢያንስ የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ በበርካቶች ላይ ጉዳት መድረሱን ከስፍራው የደረሰን አስደንጋጭ ዜና ያመለክታል። ይህ አሳዛኝ ክስተት፣ ትላንት በተመሳሳይ ስፍራ መድረክ ተሰብሮ በርካታ ሰዎች የተጎዱበትን ሀዘን የደገመ ሆኗል።

በሺዎች የሚቆጠሩ ሰልፈኞች የህዳሴውን ግድብ በዝማሬና በጭፈራ እያከበሩ በነበረበት ወቅት፣ በድንገት የጣለው ከባድ ዝናብ ስነስርዓቱን አመሰቃቅሎታል።

የአይን እማኞች ከስፍራው ለዘሐበሻ እንደገለጹት፣ ህዝቡ ዝናቡን ለመጠለል በአቅራቢያው ወደሚገኙ ድንኳኖችና ህንጻዎች ለመግባት ሲሯሯጥ በተፈጠረ ከፍተኛ ግፊያና መረጋገጥ አደጋው ሊከሰት ችሏል።

ይህ የዛሬው አደጋ ይበልጥ አሳዛኝ የሚያደርገው፣ ገና የትላንቱ ቁስል ሳይደርቅ መከሰቱ ነው። ትላንት ለዚሁ የድጋፍ ሰልፍ ዝግጅት ሲደረግ የነበረ መድረክ ተሰብሮ በርካታ ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን መዘገባችን ይታወሳል።

በሁለት ተከታታይ ቀናት በአንድ ስፍራ ላይ እንዲህ አይነት አደጋዎች መከሰታቸው፣ በዝግጅቱ የደህንነት ጥንቃቄ ላይ ከፍተኛ ጥያቄዎችን እያስነሳ ነው።

በሀገር አቀፍ ደረጃ 8.4 በመቶ ተማሪዎች ብቻ 50% በላይ በማምጣት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን አልፈዋል። አጠቃላይ 48,929 ተማሪዎች አልፈዋል። በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12...
09/14/2025

በሀገር አቀፍ ደረጃ 8.4 በመቶ ተማሪዎች ብቻ 50% በላይ በማምጣት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን አልፈዋል።

አጠቃላይ 48,929 ተማሪዎች አልፈዋል።

በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና 1 ሺህ 249 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አለማሳለፋቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተናግረዋል።

ሚኒስትሩ የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ማጠናቀቂያን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ እንዳሉት 50 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን አሳልፈዋል።

12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ስንት ሆኖ ተመዘገበ?

በተፈጥሮ ሳይንስ 591

በማኅበራዊ ሳይንስ 579

የዘንድሮው 12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከፍተኛ ውጤት በተፈጥሮ ሳይንስ 591 ሆኖ ተመዝግቧል።

ውጤቱ የተመዘገበው ከዶዶላ ኢፈ ቦሩ ትምህርት ቤት መሆኑም ተመላክቷል።

በማኅበራዊ ሳይንስ የዘንድሮው ከፍተኛ ውጤት 579 ሲሆን፣ ይህም ከብሥራተ ገብርኤል ትምህርት ቤት የተገኘ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

በኦንላይን ከተፈተኑት 134 ሺህ 609 ተማሪዎች መካከል 29 ሺህ 239 ተማሪዎች አልፈዋል።

ይህም በወረቀት ከተፈተኑት ጋር ሲነጻጸር በጣም የተሻለ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

Address

Jersey City, NJ

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ:

Share