Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ

Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ is an Ethiopian entertainment and news website launched in March 2016. The official page of tobiatube247.com
(3)

የ 30% የነዳጅ ግብር ተግባራዊ ሊደረግ ነው!!በነዳጅ ምርቶች ላይ የተጣለዉ አጠቃላይ ግብር በቀጣይ ወር ተግባራዊ እንደሚሆን ተገለፀ የኢትዮጵያ መንግሥት ለረጅም ጊዜ የዘለቀውን የነዳጅ ድጎ...
11/17/2025

የ 30% የነዳጅ ግብር ተግባራዊ ሊደረግ ነው!!

በነዳጅ ምርቶች ላይ የተጣለዉ አጠቃላይ ግብር በቀጣይ ወር ተግባራዊ እንደሚሆን ተገለፀ

የኢትዮጵያ መንግሥት ለረጅም ጊዜ የዘለቀውን የነዳጅ ድጎማ ቀስ በቀስ ለማስወገድ ከሚወስዳቸው ሰፋፊ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች አንዱ የሆነው አዲስ የግብር አወቃቀር ከሚቀጥለው ወር ጀምሮ ተግባራዊ ሊሆን ነው።

ይህ አዲስ እርምጃ በነዳጅ ምርቶች ላይ 15% ተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) እና 15% ኤክሳይዝ ቀረጥን ያካተተ አጠቃላይ 30% ታክስ መጣል ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ከአንድ ወር በኋላ ታክሱን መሰብሰብ ይጀምራል።

በአዲሱ መመሪያ መሠረት፣ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅቱ የተሰበሰበውን ግብር በሙሉ ለገቢዎች ሚኒስቴር ማስገባት ግዴታው ሲሆን፣ መንግሥት በዚህም እስከ ታኅሣሥ 2018 ዓ.ም. ድረስ ለቤንዚንና ናፍጣ መሸጫ ዋጋዎች ሁሉንም ህጋዊ የግብር መጠን ጨምሮ ሙሉ ወጪን የመሸፈን ግብ ላይ ለመድረስ አቅዷል።

​የገንዘብ ሚኒስቴር ከአዲሱ በጀት ዓመት ጀምሮ በነዳጅ ምርቶች ላይ አጠቃላይ 30 በመቶ ግብር ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ሊያደርግ ማቀዱን ካፒታል ጋዜጣ ከሁለት ወራት በፊት መዘገቡ ይታወሳል።

ሚኒስትሩ መስከረም 2018 ዓ.ም. አጋማሽ ላይ ባቀረቡት አጠቃላይ የዜጎች በጀት ዉስጥ፣ በተያዘው በጀት ዓመት ተግባራዊ የሚደረጉ የግብር አይነቶችን በዝርዝር አስቀምጠው ነበር።
(ካፒታል)

ገንዘብ ሚኒስቴር በ2016 ዓ.ም ህግን ባልተከተለ መንገድ 15.1 ቢሊየን ብር ከተለያዩ ተቋማት ሰበሰበ።የገንዘብ ሚኒስቴር ከ15 ቢሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ከበጀት ዕቅድ ውጪ መሰብሰብን በኦ...
11/16/2025

ገንዘብ ሚኒስቴር በ2016 ዓ.ም ህግን ባልተከተለ መንገድ 15.1 ቢሊየን ብር ከተለያዩ ተቋማት ሰበሰበ።

የገንዘብ ሚኒስቴር ከ15 ቢሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ከበጀት ዕቅድ ውጪ መሰብሰብን በኦዲት ተገለፀ

የገንዘብ ሚኒስቴር በ2016 በጀት ዓመት ከፍተኛ መጠን ያለው የመንግሥት ገንዘብ ከበጀት ዕቅድ ውጪ ሰብስቦ መገኘቱን በፌደራል ዋና ኦዲተር ይፋ ባደረገዉ የተጠቃለለ ገቢና ወጪ የሂሳብ ኦዲት ሪፖርት ላይ አመለከተ።

የኦዲቱ ግኝት እንደሚያሳየው፣ ከተለያዩ ድርጅቶች የተሰበሰበው ብር ከ15.1 ቢሊዮን ብር በላይ በፋይናንስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 648/2001 ክፍል 5 አንቀጽ 20 ንዑስ አንቀጽ 20 መሠረት በበጀት ዕቅድ ውስጥ ሳይካተት ቀርቷል።

ይህ ድርጊት አዋጁን በቀጥታ የሚጣረስ ሲሆን፣ ዓመታዊ በጀት ሲዘጋጅ ሊሰበሰብ የሚችል ማንኛውም የመንግሥት ገንዘብ በዕቅድ መያዝ አለበት የሚለውን መሠረታዊ የሕግ መስፈርት ያልተከተለ መሆኑ ተገልጿል።

ምንጭ:- ካፒታል

11/14/2025
ተቋርጧል❗❗❗📡ኢትዮ_ሳት ከሳተላይት ችግር ጋር በተያያዘ ለጊዜው ተቋርጧል።ዲሻችሁን ወይም ቲቪያችሁን ምንም ሳትነካኩ በመጠበቅ የሳታላይት ችግሩ ሲቀረፍ በራሱ የሚመለሱ ይሆናል።
11/14/2025

ተቋርጧል❗❗❗
📡ኢትዮ_ሳት ከሳተላይት ችግር ጋር በተያያዘ ለጊዜው ተቋርጧል።
ዲሻችሁን ወይም ቲቪያችሁን ምንም ሳትነካኩ በመጠበቅ የሳታላይት ችግሩ ሲቀረፍ በራሱ የሚመለሱ ይሆናል።

በጥቅምት የምግብ ነክ ያልሆኑ እና የምግብ ነክ ዕቃዎች ዓመታዊ የዋጋ ግሽበት መጠኖች ጭማሪ አሳይተዋል።በሀገሪቱ የዋጋ ግሽበት ዙሪያ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ያወጣዉ መረጃዎች እንደ...
11/08/2025

በጥቅምት የምግብ ነክ ያልሆኑ እና የምግብ ነክ ዕቃዎች ዓመታዊ የዋጋ ግሽበት መጠኖች ጭማሪ አሳይተዋል።

በሀገሪቱ የዋጋ ግሽበት ዙሪያ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ያወጣዉ መረጃዎች እንደሚያሳየው፣ በጥቅምት ወር በ2018 የምግብ ነክ ያልሆኑ እና የምግብ ነክ ዕቃዎች ዓመታዊ የዋጋ ግሽበት መጠኖች ጭማሪ አሳይተዋል።

በተለይም፣ የምግብ ነክ ያልሆኑ ዕቃዎች የዋጋ ግሽበት መጠን ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ወደ 14.2 በመቶ ከፍ ብሏል። ይህ አሃዝ ከጥቅምት 2017 ዓ.ም የምግብ ነክ ያልሆነው የዋጋ ግሽበት መጠን 11.6% ጋር ሲነጻጸር፣ በእጅጉ የላቀ መሆኑን ለመረዳት ችሏል።

ይህ ጭማሪ በብዙ የኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ ባለሁለት አሃዝ የዋጋ ጭማሪ የታየበት ሲሆን፣ ከሁሉም በላይ ትራንስፖርት በ27.0% ማሻቀብ ተገልጿል።

ካፒታል ከተቋሙ ያገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ ሌሎች ዋና ዋና አስተዋጽዖ አድራጊዎች ዉስጥ ልዩ ልዩ ዕቃዎችና አገልግሎቶች 22.3 በመቶ ፣ የአልኮል መጠጦች እና ትምባሆ 14.6% ፣ የቤት ዕቃዎች 14.1% እንዲሁም መኖሪያ ቤት፣ ውሃ፣ ኤሌክትሪክ 12.4% ጭማሪ አሳይተዋል።

አገልግሎቱ ትናንት ባወጣው መረጃ እንደሚጠቁመው፣ የጥቅምት ወር 2018 ዓ.ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት 11.7 በመቶ ደርሷል። ይህም መስከረም ወር ተመዝግቦ ከነበረው 13.2 በመቶ ግሽበት አኳያ ቅናሽ ማሳየቱን ለመረዳት ተችሏል።

እንደ ተቋሙ ከሆነ በወሩ የምግብ ነክ ዕቃዎች 10.2 በመቶ እንዲሁም ምግብ ነክ ያልሆኑ እቃዎች ደግሞ 14.2 በመቶ ሆነው ተመዝግበዋል

ከወር እስከ ወር ያለው የዋጋ ግሽበት ባለፈው ወር ከነበረበት 3.6% ወደ 2.3% የወረደ ጭማሪ ያስመዘገበ ሲሆን፣ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በቁልፍ ዘርፎች መጠነኛ የዋጋ ለዉጦችን አሳይቷል

(Capital Ethiopia)

ሕጋዊ ወራሽ የሆኑ ግለሰቦች ስም ለማዞር በካሬ እስከ 12 ሺህ ብር እየተጠየቁ መሆኑን ተናገሩ
11/07/2025

ሕጋዊ ወራሽ የሆኑ ግለሰቦች ስም ለማዞር በካሬ እስከ 12 ሺህ ብር እየተጠየቁ መሆኑን ተናገሩ

Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.

ይኼንን ጽሑፍ ቁጭ ብለህ እያነበብህ ያለኸው በዚህ ሰዓት ምሥራቅ አርሲ ገጠር ውስጥ ስላልተገኘህ ብቻ ነው:: በዚህች ቅጽበት በሥጋት ውስጥ ሆነው "ከአሁን አሁን ምን ይመጣብን ይሆን?" እያሉ...
11/04/2025

ይኼንን ጽሑፍ ቁጭ ብለህ እያነበብህ ያለኸው በዚህ ሰዓት ምሥራቅ አርሲ ገጠር ውስጥ ስላልተገኘህ ብቻ ነው:: በዚህች ቅጽበት በሥጋት ውስጥ ሆነው "ከአሁን አሁን ምን ይመጣብን ይሆን?" እያሉ ያሉ የኦሮሚያ ምእመናን ቁጥራቸው ብዙ ነው:: ከቀናት በፊት የተገደሉትን ተናግረን ሳናበቃ አሁን ደግሞ ሌላ ቦታ አምስት እንደተገደሉ እየሰማን ነው::

ሰሞኑን ከሁለት ሺህ ዓመታት በፊት ሔሮድስ ስላሳደዳት እመቤታችን "ሰቆቃወ ድንግል" እያልን እያዘንን ነው:: ከሰይፍ ልጅዋን ማስጣል ያልቻለች የአርሲዋን እናትስ እንዴት ዝም እንበላት? ይህንን የማያቆም ሞት ዜና ሰምተን ወደ ጉሮሮአችን የሚወርድ ምግብና መጠጥ የምንተኛውም እንቅልፍ የለም:: የእነርሱ ሞት የእኛ ሞት ነው:: የእነርሱ መቁሰል የእኛ ቁስል ነው:: የቦታ ለውጥ እንጂ በእነርሱ የደረሰው በእኛም ሊደርስ ይችላል::

ቤተ ክርስቲያን ምሕላ እንድታውጅ ፣ ለተሠዉት ተገቢውን ክብር እና ጸሎተ ፍትሐት እንድታደርግ እንጠብቃለን:: ቤተ ክርስቲያን በየትኛውም ቦታ የንጹሐን ደም ዳግመኛ እንዳይፈስስ እንደ ራሔል ዕንባዋን የምትረጭበት ጊዜ አሁን ነው::

የቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ትኩረት ያልሠጠውን ችግር ሌላ አካል ሊጨነቅበት አይችልም:: ስለዚህ ቤተ ክርስቲያን በአስተዳደራዊ መዋቅርዋ መንግሥት ተገቢውን እርምጃ እንዲወስድ በሙሉ ትኩረት የምትሠራበት ጊዜም አሁን ነው:: ቅዱስ ሲኖዶስ በዚህ ዓይነት ጊዜ የሚያሳየው ምላሽ ከሌለ ሌላ ቀን ቢጣራ የማይሰማውን ቤተ ክርስቲያን አልባ ክርስቲያን በራሱ ላይ ይፈጥራል:: ሐዋርያዊትዋ ቤተ ክርስቲያንም በክህነት የማትመራ የመሆን አደጋ ይገጥማታል:: ክህነት ከሌለ ደግሞ ቤተ ክርስቲያንም ምሥጢራትም የሉም::

ኦርቶዶክሳውያን ምእመናንም ይህንን ጊዜ ለመካሰስ ፣ አባቶችን ለመሳደብ ፣ አንዱ ሌላውን ለማስጠቆርና ለመናቆር ሳይሆን ለጸሎት ለምሕላና ለሰብአዊ ሥራና መሬት ላይ ቢወርዱ ችግሮችን የሚፈቱ ዘላቂ መፍትሔዎች ላይ በትብብር ለመሥራት ምክንያት ብናደርገው የተሻለ ነገር ማምጣት እንችላለን::

የሌላ እምነት ተከታዮች ሆነው ይህ በኦርቶዶክሳውያን ላይ ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያውያን ላይ የተቃጣ ጥቃት ብለው ጉዳዩን በተቋምም በግልም ያወገዙ ሰዎችን እናከብራለን:: "ይበላችሁ" ብለው የተሳለቁትን እና በክፉ ቀን ክፋታቸውን ላሳዩን ደግሞ እውነተኛ ማንነታቸውን ስላሳዩን እያመሰገንን "አቤቱ፥ በኢየሩሳሌም ቀን የኤዶምን ልጆች አስብ፦ “እስከ መሠረትዋ ድረስ አፍርሱ አፍርሱ፡” ያሉአትን" ብለን ለሰማያዊው ዳኛ ሠጥተናቸዋል:: መዝ. 137:7

ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ




ኢትዮጵያ በሕግ የበላይነት መከበር ከ143 አገሮች 132ኛ ደረጃ መያዟ በሪፖርት ተመላከተ በዓለም አቀፍ ደረጃ የአገሮችን የሕግ ሥርዓትና የሕግ የበላይነትን ቁመና በመገምገም በየዓመቱ ሪፖርት...
11/03/2025

ኢትዮጵያ በሕግ የበላይነት መከበር ከ143 አገሮች 132ኛ ደረጃ መያዟ በሪፖርት ተመላከተ

በዓለም አቀፍ ደረጃ የአገሮችን የሕግ ሥርዓትና የሕግ የበላይነትን ቁመና በመገምገም በየዓመቱ ሪፖርት ይፋ የሚያደርገው ዓለም አቀፍ የፍትሕ ፕሮጀክት (WJP) የተሰኘው ድርጅት፣ ኢትዮጵያን በሕግ የበላይነት ከ143 አገሮች 132ኛ ደረጃ ላይ መሆኗን አስታወቀ፡፡

በተባበሩት መንግሥታት ድርጅትና በሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችና በአገሮች የሚደገፈውና ከ20 በላይ አገሮችን በአባልነት ያቀፈው ድርጅቱ፣ እ.ኤ.አ. የ2025 ዓመታዊ የ143 አገሮች የፍትሕ ሥርዓትና የሕግ የበላይነት መከበር ቁመናን የተመለከተ ሪፖርቱን ጥቅምት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል፡፡

ሪፖርቱ ኢትዮጵያን እ.ኤ.አ. በ2024 በዓለም ከ142 አገሮች 130ኛ፣ እንዲሁም ከአፍሪካ ከ34 አገሮች 30ኛ ደረጃን ይዛ እንደነበር፣ በተያዘው ዓመት እ.ኤ.አ. 2025 ከ143 የዓለም አገሮች 132ኛ እንዲሁም ከ34 የአፍሪካ አገሮች ደግሞ 30ኛ ደረጃ ላይ አስቀምጧታል፡፡

ለደረጃው ማሽቆልቆል እንደ ምክንያት የቀረበው፣ የፍርድ ቤቶች ነፃነት ማጣትና የሲቪክ ምኅዳሩ መውረድ የዴሞክራሲ ሥርዓቱን እያጠበበው መሆኑ ነው ተብሏል፡፡

እ.ኤ.አ. በ2024 በሪፖርቱ መሠረት 57 በመቶ አገሮች ብቻ የሕግ የበላይነት ቁመናቸው አሽቆልቁሎ ነበር፡፡ በተያዘው ዓመት እ.ኤ.አ. 2025 ደግሞ 68 በመቶ የሚሆኑት አገሮች የሕግ የበላይነት ቁመናቸው ማሽቆልቆሉን አስታውቋል፡፡ የኢትዮጵያ የሕግ የበላይነት ቁመና ባለፈው ዓመት ከነበረው በ2.4 በመቶ መውረዱንም ጠቁሟል፡፡

ሩዋንዳ ከ143 አገሮች መካከል 39ኛ የተቀመጠች ሲሆን፣ ከአፍሪካ የመጀመሪያዋ የሕግ የበላይነት የተከበረባት አገርሆናለች፡፡ ናሚቢያና ሞሪሽየስ ደግሞ ሁለተኛና ሦስተኛ ደረጃን የያዙ የአፍሪካ አገሮች ሆነዋል፡፡ ካሜሩን፣ ዴሞክራቲክሪፐብሊክ ኮንጎና ሱዳን የሕግ የበላይነት ቁመናቸው በከፍተኛ ሁኔታ ያሽቆለቆለባቸው ተብለው ተመዝግበዋል፡፡

የሕግ የበላይነት ቁመናቸው እያሽቆለቆለ ነው ከተባሉት 16 አገሮች ኢትዮጵያ አንደኛዋ ስትሆን፣ በመንግሥት አካላት መካከል ያለው የእርስ በርስ የቁጥጥር ሥርዓት መዳከምና የመሠረታዊ መብቶች መጣስ ምክንያት መሆኑን ሪፖርቱ ያስረዳል፡፡

በዓለም 7ዐ በመቶ ከሚሆኑ የሲቪክ ምኅዳር ከጠበባቸው አገሮች መካከል የተመደበችው ኢትዮጵያ፣ ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ፣ የመሰብሰብና የመደራጀት፣ እንዲሁም የሲቪክ ተሳትፎ በእጅጉ ካሽቆለቆለባቸው አገሮች ውስጥ መሆኗን አመላክቷል፡፡

የሕግ ተርጓሚ አካላት በአስፈጻሚው አካል ተፅዕኖ ሥር እየወደቁ ነው የሚለው ሪፖርቱ፣ የጨመረ የፖለቲካ ጣልቃ ገብነት መኖሩንም አብራርቷል፡፡

ኢትዮጵያ በዓለም የፍትሐ ብሔር ክርክር ጉዳዮች 68 በመቶ ካሽቆለቆለባቸው አገሮች መካከል መሆኗን የሚያመለክተው ሪፖርቱ፣ ለረዥም ጊዜ የፍርድ ሒደቱ መጓተት፣ ውጤታማነቱ የማያስደስትና የመንግሥት ጣልቃ ገብነት መኖሩ ማሳያ ስለመሆኑ ያትታል፡፡

በዓለም አቀፍ ደረጃ ዴንማርክ፣ ስዊድን፣ ኖርዌይና ኒውዚላንድ ከፍተኛ የሕግ የበላይነት ያለባቸው ተብለው ሲመደቡ፣ ቬኔዙየላ፣ አፍጋኒስታን፣ ካምቦዲያ፣ ሀይቲና ኒካራጓ የሕግ የበላይነት በከፍተኛ ሁኔታ ያሽቆለቆለባቸው አገሮች ናቸው ተብለዋል፡፡
(ሪፓርተር)

" በአሁኑ ሰአት ከወጣቶች በዘለለ እድሜያቸው 12 እና 13 የሆኑ ህፃናት በስኳር በሽታ ኩላሊታቸው እንዳይሰራ እየሆነ ነው። ለዚህም ዋነኛ ምክንያቱ የስኳር እና የጨው ይዘት ያላቸው የታሸጉ ...
11/03/2025

" በአሁኑ ሰአት ከወጣቶች በዘለለ እድሜያቸው 12 እና 13 የሆኑ ህፃናት በስኳር በሽታ ኩላሊታቸው እንዳይሰራ እየሆነ ነው። ለዚህም ዋነኛ ምክንያቱ የስኳር እና የጨው ይዘት ያላቸው የታሸጉ ምግቦች ናቸው " - የኢትዮጵያ የኩላሊት ንቅለ ተከላ ማህበር

ተላላፊ ላልሆኑ በሽታዎች የሚያጋልጡ የታሸጉ ምግቦችን ለመቆጣጠር የሚያስችል አዋጅ ተዘጋጅቷል።

አዋጁ መዘጋጀቱን ተከትሎ ፦
- የተዋልዶ ጤና አገልግሎት ሰጭ ማህበራት ህብረት (CORHA)፣
- የኢትዮጵያ የልብ ማህበር፣
- የኢትዮጵያ የስኳር በሽታ ማህበር እና የኢትዮጵያ የኩላሊት ንቅለ ተከላ ማህበር በጋራ በመሆን ከቀናት በፊት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተው ነበር።

የኢትዮጵያ የኩላሊት ንቅለ ተከላ ማህበር ሰብሳቢ አቶ ቢኒያም አበራ " በአሁኑ ሰአት ከወጣቶች በዘለለ እድሜያቸው 12 እና 13 የሆኑ ህፃናት በስኳር በሽታ ኩላሊታቸው እንዳይሰራ እየሆነ ነው " ብለዋል።

" ለኩላሊት በሽታዎች ዋነኛ ምክንያቱ የስኳር እና የጨው ይዘት ያላቸው የታሸጉ ምግቦች ናቸው " ሲሉም ገልፀዋል።

አቶ ቢኒያም አበራ በዝርዝር ምን አሉ ?

" በማህበራችን ውስጥ አብዛኛው ኩላሊታቸው የተጎዱ ሰዎች ለኩላሊታቸው መጎዳት ዋነኛ ምክንያት የሆነው ደም ግፊት እና የስኳር በሽታዎች ናቸው። እነዚህ በሽታዎች ደግሞ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ከአመጋገብ ስርአት ጋር የተገናኙ ናቸው። ምክንያቱም የታሸጉ ምግቦች በአብዛኛው የስኳር እና የጨው ይዘት አላቸው።

በተለይ ደግሞ በፋብሪካ የሚቀነባበሩ ምግቦች በውስጣቸው በምግብ ማቀነባበር ስርአት ውስጥ የተጠራቀመ የስብ ክምችት አለ። ይህ የሚጨመር ስኳር ሰዎች በሚመገቡበት ጊዜ በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ሰውነት ውስጥ ከፍተኛ የስኳር መጠን እንዲገባ ያደርጋል። ይህ በሰውነታችን ውስጥ ያለውን የስኳር መጠን ያዛባዋል፤ በዚህም የስኳር በሽታ እንዲከሰት ያደርጋል። በምግብ ውስጥ የሚጨመር ንጥረ ነገር ደግሞ የደም ግፊትን ያመጣል። በመሆኑም ኩላሊት ስራውን በአግባቡ እንዳይሰራ ያዳክሙታል። በመጨረሻም ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ኩላሊት ስራውን እንዳይሰራ ያደርጋል።

እነዚህ ነገሮች በተናጠልም ሆነ በድምር በርካታ ቁጥር ያላቸውን ዜጎች እያጠቁ ያሉ ንጥረ ነገሮች ናቸው። ስለዚህ እነዚህን ንጥረ ነገሮች ወደ ዜጎች በሚመጡበት ጊዜ ቁጥጥር ሊደረግባቸው ይገባል።

በታሸጉ ምግቦች ሽፋን ላይ በውስጣቸው የያዙት ንጥረ ነገር በአይነት እና በመጠን ሊገለጽ እንዲሁም ሰዎች እነዚህን ሲመገቡ ሊደርስባቸው የሚችሉ ጉዳቶች በመሸፈኛቸው ላይ በጉልህ መቀመጥ አለባቸው።

በታሸጉ ምግቦች ላይ በቂ ቁጥጥርና ጥበቃ ሊደረግ ይገባል።

እነዚህ ምግቦች በማህበረሰባችን ላይ እያደረሱት ያለው ጉዳት እና ቀውስ ለመቀነስ ማህበራችን ይህ አዋጅ ቶሎ ተፈጻሚ እንዲሆን ይሰራል " ብለዋል።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የስነ ምግብ ህክምና ባለሙያ እና የኢትዮጵያ ስነ ምግብ ህክምና ባለሙያዎች ማህበር ተወካይ የሆኑት ዶ/ር ዘላለም ከበደ " ኢትዮጵያ በፋብሪካ በተቀነባበሩ እና ጤናማ ባልሆኑ ምግቦች ምክንያት ለሚደርሱ የጤና ጉዳቶች በየዓመቱ ከ31 ቢሊየን ብር በላይ ታወጣለች " ሲሉ ተናግረዋል።

አያይዘውም " በየስአቱ 25 ሰው ተላላፊ ባልሆኑ በሽታዎች ማለትም በስኳር፣ በኩላሊት፣ በጉበት እና በልብ እንዲሁም በደም ቧንቧ በሽታዎች ይሞታሉ፣ በአሁኑ ስአት የህመሙ ጫና ከ52 በመቶ በላይ ሆኗል " ነው ያሉት።

" የምግብ ጥራትን ማረጋገጥ ያስፈልጋል። ምክንያቱም በርካታ ሰዎች የታሸጉ ምግቦች ጥሩ እየመሰሏቸው ሲገዙ ይታያል። ይህ በጥናት መረጋገጥ አለበት። ማህበረሰቡ ባለው የግንዛቤ ክፍተት ምክንያት እየተጠቀመ እየተጎዳ ነው " ብለዋል።

" ማህበረሰቡ በአዋጁ መሰረት ክልከላ የሚደረግባቸው የስብ፣ የስኳር እና የጨው መጠናቸውን ያልጻፉ የታሸጉ ምግቦችን ሲያዩ ለሚመለከተው አካል ማሳወቅ አለባቸው። አዋጁ ቶሎ ወደ ተግባር ገብቶ ክፍተቶቹ እየታዩ መስተካከያ ሊደረግበት ይገባል " ሲሉ ገልጸዋል።

(Via ቲክቫህ ኢትዮጵያ)

2.7 ኪ.ግ የሚመዝነው የስማርትፎን መያዣ ማተር ኒውሮሳይንስ የተባለ ኩባንያ 2.7 ኪ.ግ የሚመዝን የስማርትፎን መያዣ ፈጥሯል ተባለ፡፡ይህም በጣም ከባድና ለመጠቀም አስቸጋሪ በመሆኑ የአብዛኞ...
10/31/2025

2.7 ኪ.ግ የሚመዝነው የስማርትፎን መያዣ

ማተር ኒውሮሳይንስ የተባለ ኩባንያ 2.7 ኪ.ግ የሚመዝን የስማርትፎን መያዣ ፈጥሯል ተባለ፡፡

ይህም በጣም ከባድና ለመጠቀም አስቸጋሪ በመሆኑ የአብዛኞቹን ሰዎች የስልክ አጠቃቀም ጊዜ በግማሽ ያህል ሊቀንስ ይገባልም የተባለለት ነው፡፡

የስማርትፎን መያዣዎች በአብዛኛው ቀላልና ለስላሳ ሆነው የተሰሩ ናቸው፣ ነገር ግን ማተር ኒውሮሳይንስ የተባለው ኩባንያ በተቃራኒው በመሄድ ምናልባትም ሊገኝ የሚችለውን ከባዱንና ግዙፉን የስልክ መያዣ ፈጥሯል።

ሰዎች በእጃቸው ያለውን ስልክ ለመጠቀም በተቻለ መጠን አስቸጋሪ ለማድረግ እጅግ በጣም የማይመች የስማርትፎን መያዣ ለመፍጠር የተቻላቸውን ያህል ሙከራ ማድረጋቸው ተገልጿል፡፡

በማይዝግ ብረት የተሰራው የስልክ መያዣ ክብደቱ 6 ፓውንድ (2.7 ኪ.ግ) ይመዝናል፣ በስልኩ ዙሪያ የሚጣበቁ ሁለት የተለያዩ ክፍሎችንም ያቀፈ ነው ተብሏል።

Address

Jersey City, NJ

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ:

Share