TGEthiopianBroadcasting

TGEthiopianBroadcasting TG Ethiopian Broadcasting, LLC is a media company based in Alexandria, Virginia (United States). TG

TG stands for the late Dr. Artist Tilahun Gessesse who is the King of Ethiopian music

07/30/2025

መታየት ያለበት!
በሼክ መሐመድ አላሙዲ ለሙዚቃው ንጉሥ ለዶ/ር አርቲስት ጥላሁን ገሠሠ የተገዛውን ቤት የጥላሁን ገሠሠ ቤተሰቦች ቤቱን ለቀው እንዲወጡ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከፈረደ በኋላ፣ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ደግሞ የራሱን ውስኔ አስተላልፏል...ይመልከቱ!
SHARE, LIKE, FOLLOW

እውነት እግዚአብሔር ነው እየተባለ ለምን ይዋሻል? ውሸትን እውነት ለማስመሰል ተብሎ የእግዚአብሔር አምላካችን ስም እየተጠራ ሲዋሽ አልበዛም እንዴ? አሁን የምንቆጣው እኛ ሳንሆን እግዚአብሔር ...
07/10/2025

እውነት እግዚአብሔር ነው እየተባለ ለምን ይዋሻል? ውሸትን እውነት ለማስመሰል ተብሎ የእግዚአብሔር አምላካችን ስም እየተጠራ ሲዋሽ አልበዛም እንዴ? አሁን የምንቆጣው እኛ ሳንሆን እግዚአብሔር ነው። እግዚአብሔር በስሙ ሲዋሽ ዝም ብሎ አያይም። የእግዚአብሔርን ስም እየጠሩ በውሸት ለሚምሉትም መጽሃፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል...

ኦሪት ዘሌዋውያን ምዕራፍ 19 ቁጥር 12 እንዲህ ይላል፡
“በስሜም በሐሰት አትማሉ፣ የአምላካችሁንም ስም አታርክሱ፣ እኔ እግዚአብሔር ነኝ”
Leviticus 19:12 (ESV)
“You shall not swear by my name falsely and so profane the name of your God: I am the Lord.
__________________________________________________________________
ኦሪት ዘጸአት ምዕራፍ 20 ቁጥር 7፡
“የእግዚአብሔርን፣ የአምላክህን ስም ከከንቱ አትጥራ፣ እግዚአብሔር በከንቱ የሚጠራውን ከበደል አያነጻውም።”
Exodus 20:7
“You shall not take the name of the Lord your God in vain, for the Lord will not hold him guiltless who takes his name in vain.
_____________________________________________________________________
ትንቢተ ዘካርያስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 4
“እኔ አስወጣዋለሁ ይላል፣ የሠራዊት ጌታ፣ እግዚአብሔር ወደሚሰርቀውም ቤት፣ በሐሰትም በስሜ ወደሚምለው ቤት ይገባል፣ በቤትም ውስጥ ይኖራል፣ እርሱንም፣ እንጨቱንና፣ ድንጋዩን ይበላል።
Zechariah 5:4
“I will send it out, declares the Lord of hosts, and it shall enter the house of the thief, and the house of him who swears falsely by my name. And it shall remain in his house and consume it, both timber and stones.”
______________________________________________________________________
ኦሪት ዘዳግም ምዕራፍ 5 ቁጥር 11
የእግዚአብሔርን የአምላክህን ስም በከንቱ አትጥራ፣ እግዚአብሔር ስሙን በከንቱ የሚጠራውን ከበደል አያነጻውምና.”
Deuteronomy 5:11 (NIV) (Third Commandment)
“You shall not misuse the name of the Lord your God, for the Lord will not hold anyone guiltless who misuses his name.”
_______________________________________________________________________፟
በእግዚአብሔር ስም እየማሉ የሚናገሩትን ውሸት እውነት ለማስመሰል መሞከር ትልቅ ኃጢያትና እግዚአብሔርን የሚያስቀይም አጸያፊ ተግባር ነው። እስከአሁን ዝም ብለን ነበር፣ ነገር ግን እየተደጋገመ በእግዚአብሔር እየተማለ ሲዋሽ ግን ዝም አንልም፣ በዝርዝር እንመለስበታለን፣ ጠብቁን!! እስከዛው ድረስ LIKE AND FOLLOW US

ክብርና ጽናት ለአርቲስት አያሌው መስፍንና ለቤተሰቦቹአርቲስት አያሌው መስፍን ምንግዜም የምናከብረው የምንወደው ታላቅ አርቲስት ነው። ወ/ሮ ሄለንም እጅግ በጣም የምናከብራት ታላቅ ሰው ነበረች...
07/01/2025

ክብርና ጽናት ለአርቲስት አያሌው መስፍንና ለቤተሰቦቹ
አርቲስት አያሌው መስፍን ምንግዜም የምናከብረው የምንወደው ታላቅ አርቲስት ነው።
ወ/ሮ ሄለንም እጅግ በጣም የምናከብራት ታላቅ ሰው ነበረች። በአርቲስት አያሌ መስፍን ባለቤት በወ/ሮ ሄለን አስፋው እልፈት የተሰማን ሀዘን እጅግ በጣም ጥልቅ ነው። ለአርቲስት አያሌው መስፍን፣ ለልጆቹ፣ ለቤተሰቦቹ እግዚአብሔር ጽናቱን ይስጥልን።

የወ/ሮ ሄለን አስፋውም ሥርዓተ ፀሎተ ፍትሃት ሐሙስ፣ Thursday, July 3, 2025, ከ9፡30 A.M. እስከ 12:00 P.M. ድረስ በዳግማዊ ግሸን ቤተክርስትያን (16250 E. Colfax Ave, Aurora, CO 80011 ) ከተከናወነ በኋላ ስርዓተ ቀብሩ ደግሞ በOlinger Hampden Morutuary, 8600 E Hampden, Denver, CO 80231 ይከናወናል። በቦታውም በመገኘት ለሀገራችን ታላቅ አስተዋጽኦ ያደረገውን አርቲስት አያሌው መስፍንና ቤተሰቡን እናጽናና።

የጋዜጠኛ ንጉሴ ወልደማርያም ስርዓተ ቀብርጋዜጠኛ ንጉሴ ወልደማርያም ከእናቱ ከወይዘሮ ፈለቀች እና ከአባቱ መምሬ ወልደማርያም ህዳር 2 ቀን 1948 ዓ.ም. (November 12, 1955)  በ...
07/01/2025

የጋዜጠኛ ንጉሴ ወልደማርያም ስርዓተ ቀብር
ጋዜጠኛ ንጉሴ ወልደማርያም ከእናቱ ከወይዘሮ ፈለቀች እና ከአባቱ መምሬ ወልደማርያም ህዳር 2 ቀን 1948 ዓ.ም. (November 12, 1955) በአዲስ አበባ ባእታ ማርያም አካባቢ ተወለደ። ንጉሴ ወልደማርያም የአንደኛ እና የሁለተኛ ትምህርቱን በአዲስ አበባ ትምህርት ቤቶች በማድረግ አጠናቋል። ከዝያም በያሬድ ሙዚቃ ቤት ትምህርቱን ተከታትሎ አጠናቋል። በማስታወቂያ ሚንስቴር በዜና ክፍል እና በተለያዩ ቦታዎችም ሰርቷል። ጋዜጠኛ ንጉሴ ወልደማርያም በእድገት በህብረት ዘመቻ በነበረበት ግዜ መሄዴ ነው ዘመቻን እና በወሎ ረሀብ በድርቁ ግዜ ወሎ ተርቦ እንደዝያ ሲያልቅ የሚለውን ዜማ በግዜው የተጫወተ፣ የብዙ ባለሙያ ባለቤት ነበር። ከዝያም ወደ ዋሽንግተን ዲሲ ከመጣም በኋላ፣ ከጓደኞቹ ጋር የአንድ ኢትዮጵያ ሬድዬ በመመስረት እና በኋላም በግሉ የሀገር ፍቅር ሬድዮን መስርቶ ሬዲዮኑን እስካቆመበት ድረስ ለሚወዱትም፣ለሚጠሉትም በየሳምንቱ በጉጉት እየተጠበቁ ለህዝቡ ያገለገለ ታዋቂ ጋዜጠኛ ነበር።
በዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ ሀገር ፍቅር ሬዲዮን በመክፈት ለብዙ ጊዜ በጋዜጠኛነት ሲያገለግል የነበረው ጋዜጠኛ ንጉሤ ወልደማርያም ባደረበት ሕመም ምክንያት በሕክምና ሲረዳ ከቆየ በኋላ ሰኔ 20፣ 2017 ዓ.ም. (June 27, 2025) በተወለደ በ69 ዓመቱ ከዚህ ዓለም አርፏል። ጋዜጠኛ ንጉሴ ባለትዳር እና የ2 ልጆች አባት ነበረ።

የስርዓተ ፀሎት ፍትሃት ማክሰኞ፣ Tuesday, July 1, 2025, ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት (8:00 A.M.) ጀምሮ በርእሰ አድባራት ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን (1350 Buchanan St, NW, Washington DC) ከተደረገለት በኋላ ሥርዓተ ቀብሩ በ13472 Poplar Hill Rd, Waldorf, MD 20601 በሚገኘው በHeritage Memorial Cemetery, ይፈፀማል።
በጋዜጠኛ ንጉሤ ወልደማርያም ሞት የተሰማን ሀዘን እጅግ በጣም ጥልቅ ነው።
እግዚአብሔር ለቤተሰቦቹ፣ ለጓደኞቹና ለአፍቃሪዎቹ ጽናቱን ይስጥልን። ነፍሱን ይማርልን፣ በገነትም ያኑርልን!!!

ጋዜጠኛ ንጉሤ ወልደማርያም አረፈበዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ ሀገር ፍቅር ሬዲዮን በመክፈት ለብዙ ጊዜ በጋዜጠኝነት ሲያገለግል የነበረው ጋዜጠኛ ንጉሤ ወልደማርያም ባደረበት ሕመም ምክንያት በሕክም...
06/27/2025

ጋዜጠኛ ንጉሤ ወልደማርያም አረፈ
በዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ ሀገር ፍቅር ሬዲዮን በመክፈት ለብዙ ጊዜ በጋዜጠኝነት ሲያገለግል የነበረው ጋዜጠኛ ንጉሤ ወልደማርያም ባደረበት ሕመም ምክንያት በሕክምና ሲረዳ ከቆየ በኋላ ከዚህ አለም በሞት ተለይቶአል።
በጋዜጠኛ ንጉሤ ወልደማርያም ሞት የተሰማን ሀዘን እጅግ በጣም ጥልቅ ነው።
እግዚአብሔር ለቤተሰቦቹ፣ ለጓደኞቹና ለአፍቃሪዎቹ ጽናቱን ይስጥልን። ነፍሱን ይማርልን፣ በገነትም ያኑርልን

የሮማን ካቶሊክ ቤተክርስትያን ጳጳስ ፣ ፖፕ ፍራንሲስ በተወለዱ በ88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።
04/21/2025

የሮማን ካቶሊክ ቤተክርስትያን ጳጳስ ፣ ፖፕ ፍራንሲስ በተወለዱ በ88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።

አርቲስት ሰሎሞን ተካልኝ በድንገት አረፈአርቲስት ሰለሞን ተካልኝ ታመመ ሳይባል በድንገት ማረፉ ዛሬ ተሰምቷል። ሞት ከእግዚአብሔር ነውና በአሁኑ ወቅት ፖለቲካውን ወደኋላ ትተን በአርቲስት ሰለ...
04/21/2025

አርቲስት ሰሎሞን ተካልኝ በድንገት አረፈ
አርቲስት ሰለሞን ተካልኝ ታመመ ሳይባል በድንገት ማረፉ ዛሬ ተሰምቷል። ሞት ከእግዚአብሔር ነውና በአሁኑ ወቅት ፖለቲካውን ወደኋላ ትተን በአርቲስት ሰለሞን ተካልኝ የተሰማንን ሀዘን እንግለጽ። አርቲስት ሰለሞን ተካልኝ ከሞተ በኋላ አሁንም ያለፈውን ቁርሾ ይዛችሁ መጥፎ የምትናገሩ እግዚአብሔር አይወደውምና ከዚህ መጥፎ ድርጊታችሁ ተቆጠቡ። እግዚአብሔር ነፍስ ይማር፣ በገነትም ያኑርልን።

04/21/2025

እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው አደረሳችሁ! መልካም ፋሲካ
በሼክ መሐመድ አል አሙዲ ለታላቁ የሙዚቃው ንጉሥ ለዶ/ር አርቲስት ጥላሁን ገሠሠ የተሰጠው የቤት ጉዳይ... እንዴት በሙዚቃው ንጉስ ይጨከናል???????
ታላቁ የሙዚቃው ንጉሥ ዶ/ር አርቲስት ጥላሁን ገሠሠ የዛሬ 16 ዓመት (April 19, 2009) የፋሲካ ዕለት ነበር ከዚህ ዓለም የተለየን። ታዲያ ለኢትዮጵያ ሀገሩ እጅግ በጣም ትልቅ ስራ ሰርቶ ያለፈው ጥላሁን ገሠሠ በሕይወት የለም ተብሎ እንዴት በሱና በቤተሰቡ ላይ ይጨከናል? የሙዚቃው ንጉሥ ጥላሁን ገሠሠ ሼክ መሐመድ አል አሙዲ በገዛለት ቤት ውስጥ ከሚስቱና ከልጆቹ ጋር ከ25 ዓመታት በላይ እስከለተ ሞቱ ድረስ ኖሯል። ታዲያ ጥላሁን ገሠሠ ከሞተ በኋላ ቤቱን ለቃችሁ ውጡ በማለት በጥላሁን ገሠሠ ባለቤት ላይ በፍርድ ቤት ክስ ከቀረበ ቆየት ብሏል። ሼክ መሐመድ አል አሙዲም በዚህ ጉዳይ እንዲመስክሩ በፍርድ ቤት ተጠይቀው እኔ በዚህ ቤት ጉዳይ አያገባኝም ከከሳሽ ጋር ይጨርሱ ብለዋል ብለው በከሳሽ ጠበቃ በኩል ከሼክ መሐመድ አል አሙዲ የተጻፈ ደብዳቤ ነው ብለው አቀረቡ። ሼክ መሐመድ አል አሙዲ በሚወደውና በሚያከብረው በሙዚቃው ንጉሥ በጥላሁን ገሠሠ ላይ ጨክኖ ይሆን? ወይስ ከሼክ መሐመድ አል አሙዲ የተጻፈ ደብዳቤ ነው የተባለው የውሸት ይሆን? የፍርድ ቤቱ ውሳኔስ ምን ይመስል ነበር?

01/20/2025

የምስካየ ኅዙናን መድሃኔዓለም የኢ/ኦ/ተ ቤተክርስትያን በቅርቡ ተገዝቶ ከተመረቀ በኋላ በዚህ አዲስ ቤተ ክርስትያን የጥምቀት በዓል ለመጀመሪያ ጊዜ ተከብሮአል። ባህላችን ምን ግዜም ያምራል! ይመልከቱ

ወ/ሮ ዓመለወርቅ ተድላ እጅግ በጣም የተዋጣላቸው ሚስት፣ እናት፣ አያት፣ አክስት፣ እህትና አማች ነበሩ። ወ/ሮ ዓመለወርቅ ተድላ የ12  ልጆች እናትና የ23 ልጆች አያት ነበሩ። ወ/ሮ ዓመለወ...
11/12/2024

ወ/ሮ ዓመለወርቅ ተድላ እጅግ በጣም የተዋጣላቸው ሚስት፣ እናት፣ አያት፣ አክስት፣ እህትና አማች ነበሩ። ወ/ሮ ዓመለወርቅ ተድላ የ12 ልጆች እናትና የ23 ልጆች አያት ነበሩ። ወ/ሮ ዓመለወርቅ ተድላ ባደረባቸው ህመም ምክንያት በአሜሪካና በኢትዮጵያ ህክምና ሲያደርጉ ቆይተው ጥቅምት 28 ቀን 2017 ዓ.ም. በተወለዱ በ78 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። የቀብራቸውም ሥነ ሥርዓት እሁድ፣ ህዳር 1 ቀን 2017 ዓ.ም. አዲስ አበባ በአማኑኤል ቤተ ክርስትያን ተፈጽሞአል። እግዚአብሔር የእናታችንን የዓመለወርቅ ተድላን ነፍስ ይማርልን፣ በአፀደ ገነትም ያኑርልን።

ታዋቂው ጋዜጠኛ ዜና ነህ መኮንን አርፏል። እግዚአብሔር ነፍሱን ይማርልን፣ በገነትም ያኑርልን።
11/10/2024

ታዋቂው ጋዜጠኛ ዜና ነህ መኮንን አርፏል። እግዚአብሔር ነፍሱን ይማርልን፣ በገነትም ያኑርልን።

Address

PO Box 11061
Alexandria, VA
22312

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when TGEthiopianBroadcasting posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to TGEthiopianBroadcasting:

Share