Ermiyas Girma

Ermiyas Girma "እኔ ታናሽና የተናቅሁ ነኝ ትእዛዛትህን ግን አልረሳሁም"
መዝ:- 118 - 141
(1)

👉"ለልጅ ልጅ ሁሉ ስምሽን ያሳስባሉ"             መዝ. 44 (45)፥17👉ሐምሌ 15 ቀን የሶርያው ቅዱስ እኤፍሬም የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው። #የቅዱስ  #ኤፍሬምን  #ውዳሴ  #ማርያም ...
07/21/2025

👉"ለልጅ ልጅ ሁሉ ስምሽን ያሳስባሉ"
መዝ. 44 (45)፥17

👉ሐምሌ 15 ቀን የሶርያው ቅዱስ እኤፍሬም የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው።

#የቅዱስ #ኤፍሬምን #ውዳሴ #ማርያም #መጸለይ #ያለው #ቃል #ኪዳን

" . . . ይህን ተናግሮ ሲፈጽም እንደቀደመው ዝም ብላው አትሄድም ውዳሴዬን ከቅዳሴዬ አንድ አድርጎ ያነበበ የተረጎመ የሰማ ያሰማ አንተ ከገባህበት ውሳጤ መንጦላዕት አስገባዋለሁ ብላ ተስፋውን ነግራው ቃል ኪዳኑን ሰጥታው በያዘችው መስቀለ ብርሃን ባርካው ሰማየ ሰማያት ታርጋለች። እርሱም ተባርኮ እጅ ነሥቶ ከመካነ ግብሩ ይቀመጣል።"

ምንጭ፦
ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ፣ ዘእሑድ፣ መጋቤ ሐዲስ ደምፀ አንበርብር፣ ገጽ 194-195፣ 2007ዓ.ም

👉"በኋላዋ ደናግሉን ለንጉሥ ይወስዳሉ፥ ባልንጀሮችዋንም ወደ አንተ ያቀርባሉ፤ በደስታና በሐሴት ይወስዱአቸዋል፥ ወደ ንጉሥ እልፍኝም ያስገቡአቸዋል። በአባቶችሽ ፋንታ ልጆች ተወለዱልሽ፥ በምድርም ሁሉ ላይ ገዥዎች አድርገሽ ትሾሚያቸዋለሽ። ለልጅ ልጅ ሁሉ ስምሽን ያሳስባሉ" መዝ. 44(45)፥14-17

‎"በዚህ ዘመን ለቤተ ክርስቲያን ከሚያስፈልጓት ማኅበራት ቀዳሚው ማኅበረ ቅዱሳን  ነው።"  ብፁዕ አቡነ በርናባስ ሐምሌ ፲፬/፳፻፲፯ ዓ.ም‎በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰን...
07/21/2025

‎"በዚህ ዘመን ለቤተ ክርስቲያን ከሚያስፈልጓት ማኅበራት ቀዳሚው ማኅበረ ቅዱሳን ነው።" ብፁዕ አቡነ በርናባስ

ሐምሌ ፲፬/፳፻፲፯ ዓ.ም

‎በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የሰቆጣ ማእከል 18ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ለተከታታይ ሁለት ቀናት አካሂዷል።

‎በጉባኤው የተገኙት የዋግ ኽምራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብፁዕ አቡነ በርናባስ እንደገለጹት ማኅበረ ቅዱሳን የተዘጉ አቢያተ ክርስቲያናትን በመክፈት፣አዳዲስ አማንያንን ወንጌል በማስተማርና በማስጠመቅ ፣ጉባኤ ቤቶችን በመደገፍ በኩል የሠሩት ሥራ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።

‎ብፁዕነታቸው አክለውም ዘመኑ ክርስትያኖች የሚፈተኑበት፣ቤተ ክርስቲያን የውጭና የውስጥ ጠላቶች በበዙባት በዚህ ዘመን ለቤተ ክርስቲያን ከሚያስፈልጓት ማኅበራት ቀዳሚው ማኅበረ ቅዱሳን ነው ብለዋል።

‎በጠቅላላ ጉባኤው ተገኝተው የዋናውን ማእከል መልእክት ያስተላለፉት ዲ/ን መንግሥት በበኩላቸው ማኅበሩ የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳት፣የገጠሪቷን አብያተ ክርስትያናት በመደገፍ፣የጉባኤ ቤቶችን በማጠናከር እና ማኅበሩን ዓለም ዓቀፋዊ ለማድረግ የተሠሩ ሥራዎች የሚበረታቱ እንደሆነ ገልጸቷል።

‎በመጨረሻም ለተከታታይ ሁለት ቀናት ሲካሄድ የነበረው 18ኛው ጠቅላላ ጉባኤ በ2018 ዓ.ም የሚከወኑ የሥራ ዕቅዶችን ተወያይቶ በማጽደቅና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ጠቅላላ ጉባኤው ተጠናቋል።
👇👇👇👇👇👇👇
የማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ሚዲያ አውታሮች ይቀላቀሉ
ቴሌግራም፡- http://t.me/mkpublicrelation
የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት፡- http://www.facebook.com/eotcmkidusan/
ድረገጽ፡- http://www.eotcmk.org
ዩ ቲዩብ፡- http://www.youtube.com/user/EOTCMK
:- https://www.youtube.com/@-zemawetibebzmk7905

ወንድሜ ዘማሪ አቤል ተስፋዬ እንኳን ለዚህ ታላቅ የደሥታህ ቀን አደረሰህ ትዳራችሁን እመ አምላክ ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም ትባርክ.! "ሚስት ያገኘ በረከትን አገኘ ከእግዚአብሔርም ሞገስ...
07/20/2025

ወንድሜ ዘማሪ አቤል ተስፋዬ እንኳን ለዚህ ታላቅ የደሥታህ ቀን አደረሰህ
ትዳራችሁን እመ አምላክ ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም ትባርክ.!
"ሚስት ያገኘ በረከትን አገኘ ከእግዚአብሔርም ሞገስን ይቀበላል"
ምሳሌ:- ፲፰ - ፳፪

 #ከድርሳነ  #ሚካኤል  #ዘሐምሌ 👉"ቅዱስ ጠባቂ"        ዳን. 4፥13በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አምነን በባሕርይ በህልውና ባገዛዝ አንድ አምላክ ብለን   ቀን  #የቅዱስ  #ሚ...
07/18/2025

#ከድርሳነ #ሚካኤል #ዘሐምሌ

👉"ቅዱስ ጠባቂ"
ዳን. 4፥13

በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አምነን በባሕርይ በህልውና ባገዛዝ አንድ አምላክ ብለን ቀን #የቅዱስ #ሚካኤል የመታሰቢያው በዓል ዕለት #የሚጸለየውንና #የሚነበበውን #ድርሳን እንናገራለን።

በዚህም ቀን እግዚአብሔር የፋርስ ንጉሥ ወደሚሆን ወደ ሰናክሬም ከተማ ልኮት ስለ ነበር ኢየሩሳሌምን በከበባት ጊዜ ከሠራዊቱ መካከል መቶ ሰማንያ አምስት ሺህ ሰው ፈጀበት።

ሰናክሬምም በንጉሡ በሕዝቅያስ በአምላኩ በእግዚአብሔር ላይ ዛሬ ከእጄ ማነው የሚያድናችሁ በማለት የስድብና የዘለፋ ደብዳቤ ላከ።

የይሁዳ ንጉሥ ሕዝቅያስም በሱ ላይና በፈጣሪው በእግዚአብሔር ላይ የተሠነዘረውን ይህን የእብሪት አነጋገር በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ ከኃዘኑም የተነሣ ማቅ ለበሰ ሕዝቡንና ሀገሩ ኢየሩሳሌምን ያድን ዘንድ ወደ ቤተ እግዚአብሔር ገብቶ እየወደቀ እየተነሣ ይጸልይና እግዚአብሔርን ይለምን ጀመር። እግዚአብሔርም ልመናውንና ጸሎቱን ተቀብሎ የመላእክት አለቃ የሚሆን ቅዱስ ሚካኤልን የፋርስ ንጉሥ የሚሆን ወደ ሰናክሬም ከተማ ላከው። ከዚያም ኢየሩሳሌምንና የይሁዳን ሰዎች አዳናቸው።

ስለዚህ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት እንደ ዛሬው ሁሉ የቅዱስ ሚካኤል በዓል በየወሩ እንድናከብር አዘዙን። ልመናው አማላጅነቱ ከኛ አይለየን እስከ ዘለዓለሙ አሜን።

ምንጭ፦
ድርሳነ ሚካኤል ዘሐምሌ 47-50/2ኛ ነገ. 19

መድኃኔ ዓለም  #ዐርብ
07/17/2025

መድኃኔ ዓለም

#ዐርብ

👉"የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው" ምሳ. 10፥7"በዚህች ቀን [ሐምሌ 10] ናትናኤል የተባለው ቅዱስ ሐዋርያ ስምዖን ቀለዮጳ በሰማዕትነት አረፈ"  ስንክሳር ዘሐምሌ 10👉"ኢየሱስ ናትናኤልን...
07/16/2025

👉"የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው" ምሳ. 10፥7

"በዚህች ቀን [ሐምሌ 10] ናትናኤል የተባለው ቅዱስ ሐዋርያ ስምዖን ቀለዮጳ በሰማዕትነት አረፈ" ስንክሳር ዘሐምሌ 10

👉"ኢየሱስ ናትናኤልን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ ስለ እርሱ፦ ተንኰል የሌለበት በእውነት የእስራኤል ሰው እነሆ አለ" ዮሐ. 1፥48

👉"ደቀ መዛሙርቱን ጠራ፥ ከእነርሱም አሥራ ሁለት መረጠ ደግሞም ሐዋርያት ብሎ ሰየማቸው" ሉቃ. 6፥13

👉"እግዚአብሔር የመረጣቸውን ማን ይከሳቸዋል?" ሮሜ 8፥33

👉"አስቀድሞም የወሰናቸውን እነዚህን ደግሞ ጠራቸው፤ የጠራቸውንም እነዚህን ደግሞ አጸደቃቸው፤ ያጸደቃቸውንም እነዚህን ደግሞ አከበራቸው" ሮሜ 8፥30

👉"ክብር ለሚገባው ክብርን ስጡ" ሮሜ. 13፥7

👉"በብዙ ክብርም ደግሞ አከበሩን" ሐዋ. 28፥10

ለአበው ወዳጆች የተላለፈ ጥሪ። https://youtu.be/dr9KCX0mlFo?si=sftoPjd1hyM37neiየኢትዮጵያ ሊቃውንት በሀገራችን ኢትዮጵያ እንዲሁም በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲ...
07/15/2025

ለአበው ወዳጆች የተላለፈ ጥሪ። https://youtu.be/dr9KCX0mlFo?si=sftoPjd1hyM37nei
የኢትዮጵያ ሊቃውንት በሀገራችን ኢትዮጵያ እንዲሁም በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ግንባታ አሻራቸው ከመሠረቱ እስከ ጉልላቱ ጉልቶ ይታያል። ታሪካቸውን ግን ትውልዱ አያውቀውም። እንዲያውም በደምሳሳው #አበው ተብለው ይታለፋሉ። ስለዚህ በአበውና በውሉድ መካከል ያለውን ርቀት ለማቀራረብ
በሚል ርእስ ታሪካቸውን #በመስታዋት ሚዲያ ማቅረብ ጀምሬአለሁ። ነገር ግን ሚዲያው በሚገባው መጠን ስላላደገ ባሰብኩት መጠን እየታየ አይደለም። ይህ መልእክት የደረሳችሁ ሁሉ #መስታዋት ሚዲያን በማሳደግ የበኩላችሁን አስተዋጽኦ እንድታደርጉ #በሊቃውንቱ ስም እጠይቃለሁ።
#ሚዲያው የሚያቀርበው ዜና አበውን ብቻ አይደለም። ሌሎች ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶችንም እናገኝበታለን።
#መስታዋት መልካም ነው ከመስታዋት ፊት ስንቆም ራሳችንን እናያለን።


በመ/ር ኀይለ ማርያም ዘውዱ (ዘቦሩ ሜዳ)
ሐምሌ 8/2017 ዓ.ም

Hailemariam Zewdu

👉"ከእንግዲህ ወዲህ በጌታ የሚሞቱ ሙታን ብፁዓን ናቸው" ራእይ. 14፥13👉"በዚህችም ዕለት [ሐምሌ 8] በምዕራባዊ በረሀ የሚኖር ታላቅና ክቡር አባት የሆነው የአባ ኪሮስ የዕረፍቱ መታሰቢያ ...
07/14/2025

👉"ከእንግዲህ ወዲህ በጌታ የሚሞቱ ሙታን ብፁዓን ናቸው" ራእይ. 14፥13

👉"በዚህችም ዕለት [ሐምሌ 8] በምዕራባዊ በረሀ የሚኖር ታላቅና ክቡር አባት የሆነው የአባ ኪሮስ የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው።" ስንክሳር ዘሐምሌ 8፥74

#ጌታችን #አምላካችንና #መድኃኒታችን #ኢየሱስ #ክርስቶስ #ለአባ #ኪሮስ #የገባው #ቃል #ኪዳን #ይህ #ነው፦
“እውነት እልሀለሁ ስምህን በገሃድ አባ ኪሮስ ብሎ የጠራ ብቻ ሳይሆን በሕልሙም ስምህን አባ ኪሮስ ብሎ የጠራውን ሁሉ ኃጢአቱን ይቅር እለዋለሁ። ከአንተ ጋር ያለምርምር ወደ መንግስተ ሰማያት ይግባ አለው። ዳግመኛም አባ ኪሮስ ከፈጣሪህ አሳስበኝ የሚልህን እኔም ፈጥኜ ይቅር እለዋለሁ። ዳግመኛም መታሰቢያህን ሊያደርግ አስቦ ሳይሆንለት ቢቀር ኃጢአቱን ይቅር እለዋለሁ። ያለወቀሳ ከአንተ ጋር ወደ መንግስተ ሰማያት ይግባ። የገድልህን መጽሐፍ የጻፈውን ያጻፈውን ሰው ሁሉ እኔም ስሙን በመንግስተ ሰማያት በሕይወት መጽሐፍ እጽፈዋለሁ።”

ምንጭ፦
ገድለ አቡነ ኪሮስ፤ ገጽ 54 – 55 ቁጥር 15 – 18፤ 2002 ዓ.ም.

👉"የጻድቅ መታሰቢያ ለዘላለም ይኖራል" መዝ. 111 (112)፥6

👉"እግዚአብሔር ሰንበቴን ስለሚጠብቁ ደስ የሚያሰኘኝንም ነገር ስለሚመርጡ ቃል ኪዳኔንም ስለሚይዙ ጃንደረቦች እንዲህ ይላልና፦ በቤቴና በቅጥሬ ውስጥ ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች ይልቅ የሚበልጥ መታሰቢያና ስም እሰጣቸዋለሁ፤ የማይጠፋም የዘላለም ስም እሰጣቸዋለሁ። ያገለግሉት ዘንድ የእግዚአብሔርንም ስም ይወድዱ ዘንድ ባሪያዎቹም ይሆኑ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር የሚጠጉትንም መጻተኞች፥ እንዳያረክሱት ሰንበትን የሚጠብቁትን ቃል ኪዳኔንም የሚይዙትን ሁሉ፥ ወደ ተቀደሰ ተራራዬ አመጣቸዋለሁ፥ በጸሎቴም ቤት ደስ አሰኛቸዋለሁ፤ ቤቴ ለአሕዛብ ሁሉ የሚሆን የጸሎት ቤት ይባላልና የሚቃጠለውን መሥዋዕታቸውንና ሌላ መሥዋዕታቸውን በመሠዊያዬ ላይ እቀበላለሁ።" - ኢሳ. 56፥4-7

✨ጸሎቱ ወበረከቱ ለአቡነ ኪሮስ የሃሉ ምስሌነ

✨የአባታችን የአቡነ ኪሮስ ጸሎቱና በረከቱ ከሁላችን ጋር ይሁን

07/14/2025

"አንዲህ አድርገን እንጸልይ"
-ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ

👉"የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው" ምሳ. 10፥7👉አባ ጎዮርጊስ ዘጋሥጫ በቅዱስ ዑራኤል ብሥራት ከተጸነሱ በኋላ ሐምሌ ፯[7] ቀን ተወለዱ በ60 ዓመታቸውም ዕረፍታቸውም ሐምሌ ፯[7] ቀን ሆ...
07/13/2025

👉"የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው" ምሳ. 10፥7

👉አባ ጎዮርጊስ ዘጋሥጫ በቅዱስ ዑራኤል ብሥራት ከተጸነሱ በኋላ ሐምሌ ፯[7] ቀን ተወለዱ በ60 ዓመታቸውም ዕረፍታቸውም ሐምሌ ፯[7] ቀን ሆነ።

👉“እነሆም፥ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል” ሉቃ. 1፥48

👉"በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ" ዘፍ. 1፥1👉"በዚችም ቀን [ሐምሌ 7] ልዩ የሆኑ ሦስቱ አካላት በኦሪት መጽሐፍ እንደ ተጻፈ ወደ አብርሃም ቤት ገቡ ያቀረበላቸውንም ተመገ...
07/13/2025

👉"በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ" ዘፍ. 1፥1

👉"በዚችም ቀን [ሐምሌ 7] ልዩ የሆኑ ሦስቱ አካላት በኦሪት መጽሐፍ እንደ ተጻፈ ወደ አብርሃም ቤት ገቡ ያቀረበላቸውንም ተመገቡ የይስሐቅንም ልደት አበሠሩት ባረኩት አከበሩትም" - ስንክሳር ዘሐምሌ 7፥27

ኦሪት ዘፍጥረት 18

1 በቀትርም ጊዜ እርሱ በድንኳኑ ደጃፍ ተቀምጦ ሳለ እግዚአብሔር በመምሬ የአድባር ዛፍ ተገለጠለት።

2 ዓይኑንም አነሣና እነሆ፥ ሦስት ሰዎች በፊቱ ቆመው አየ፤ ባያቸውም ጊዜ ሊቀበላቸው ከድንኳኑ ደጃፍ ተነሥቶ ሮጠ፥ ወደ ምድርም ሰገደ፥እንዲህም አለ፦

3 አቤቱ፥ በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ እንደ ሆነ ባሪያህን አትለፈኝ ብዬ እለምናለሁ፤

4 ጥቂት ውኃ ይምጣላችሁ፥ እግራችሁን ታጠቡ፥ ከዚህችም ዛፍ በታች ዕረፉ፤

5 ቍራሽ እንጀራም ላምጣላችሁ፥ ልባችሁንም ደግፋ ከዚያም በኋላ ትሄዳላችሁ፤ ስለዚህ ወደ ባሪያችሁ መጥታችኋልና። እነርሱም፦ እንዳልህ አድርግ አሉት።

6 አብርሃምም ወደ ድንኳን ወደ ሣራ ዘንድ ፈጥኖ ገባና፦ ሦስት መስፈሪያ የተሰለቀ ዱቄት ፈጥነሽ አዘጋጂ፥ ለውሺውም፥ እንጎቻም አድርጊ አላት።

7 አብርሃምም ወደ ላሞቹ ሮጠ፥ እጅግ የሰባም ታናሽ ጥጃ ያዘና ለብላቴናው ሰጠው፥ ያዘጋጅም ዘንድ ተቻኰለ።

8 እርጎና ወተትም ያዘጋጀውንም ጥጃ አመጣ፥ በፊታቸውም አቀረበው፤ እርሱም ከዛፉ በታች በፊታቸው ቆሞ ነበር፥ እነርሱም በሉ።

9 እነርሱም፦ ሚስትህ ሣራ ወዴት ናት? አሉት። እርሱም፦ በድንኳኑ ውስጥ ናት አላቸው።

10 እርሱም፦ የዛሬ ዓመት እንደ ዛሬው ጊዜ ወደ አንተ በእውነት እመለሳለሁ፤ ሚስትህ ሣራም ልጅን ታገኛለች አለ። ሣራም በድንኳን ደጃፍ በስተ ኋላው ሳለች ይህንን ሰማች።

11 አብርሃምና ሣራም በዕድሜአቸው ሸምግለው ፈጽመው አርጅተው ነበር፤ በሴቶች የሚሆነውም ልማድ ከሣራ ተቋርጦ ነበር።

12 ሣራም በልብዋ እንዲህ ስትል ሳቀች፦ ካረጀሁ በኋላ በውኑ ፍትወት ይሆንልኛልን? ጌታዬም ፈጽሞ ሸምግሎአል።

13 እግዚአብሔርም አብርሃምን አለው፦ ካረጀሁ በኋላ በውኑ እወልዳለሁን? ስትል ሣራ ለምን ሳቀች?

14 በውኑ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር አለን? የዛሬ ዓመት እንደ ዛሬው ጊዜ ወደ አንተ እመለሳለሁ፤ ሣራም ልጅን ታገኛለች።

15 ሣራም ስለ ፈራች፦ አልሳቅሁም ስትል ካደች። እርሱም፦ አይደለም፥ ሳቅሽ እንጂ አላት።

16 ሰዎቹም ከዚያ ተነሥተው ወደ ሰዶም አቀኑ፤ አብርሃምም ሊሸኛቸው አብሮአቸው ሄደ።

17 እግዚአብሔርም አለ፦ እኔ የማደርገውን ከአብርሃም እሰውራለሁን?

18 አብርሃም በእውነት ታላቅና ብርቱ ሕዝብ ይሆናልና፥ የምድር አሕዛብም ሁሉ በእርሱ ይባረካሉና።

19 ጽድቅንና ፍርድን በማድረግ የእግዚአብሔርን መንገድ ይጠብቁ ዘንድ ልጆቹንና ከእርሱ በኋላ ቤቱን እንዲያዝዝ አውቃለሁና፤ ይህም እግዚአብሔር በአብርሃም ላይ የተናገረውን ነገር ሁሉ ያመጣ ዘንድ ነው።

20 እግዚአብሔርም አለ፦ የሰዶምና የገሞራ ጩኸት እጅግ በዝቶአልና፥ ኃጢአታቸውም እጅግ ከብዳለችና፥

21 እንግዲህስ ወደ እኔ እንደ መጣች እንደ ጩኸትዋ አድርገው እንደ ሆነ ወርጄ አያለሁ፤ እንዲሁም ባይሆን አውቃለሁ።

22 ሰዎቹም ከዚያ ፊታቸውን አቀኑ፥ ወደ ሰዶምም ሄዱ፤ አብርሃም ግን በእግዚአብሔር ፊት ገና ቆሞ ነበር።

23 አብርሃምም ቀረበ አለም፦ በውኑ ጻድቁን ከኃጢአተኛ ጋር ታጠፋለህን?

24 አምሳ ጻድቃን በከተማይቱ ውስጥ ቢገኙ በውኑ ሁሉን ታጠፋለህን? ከተማይቱንስ በእርስዋ ስለሚገኙ አምሳ ጻድቃን አትምርምን?

25 ይህ ከአንተ ይራቅ፤ ጻድቁን ከኃጢአተኛ ጋር ትገድል ዘንድ፥ ጻድቁም እንደ ኃጢአተኛ ይሆን ዘንድ፥ እንደዚህ ያለው አድራጎት ከአንተ ይራቅ። የምድር ሁሉ ፈራጅ በቅን ፍርድ አይፈርድምን?

26 እግዚአብሔርም፦ በሰዶም በከተማይቱ ውስጥ አምሳ ጻድቃን ባገኝ ስፍራውን ሁሉ ስለ እነርሱ እምራለሁ አለ።

27 አብርሃምም መለሰ አለም፦ እኔ አፈርና አመድ ስሆን ከጌታዬ ጋር እናገር ዘንድ እነሆ አንድ ጊዜ ጀመርሁ፤

28 ከአምሳው ጻድቃን አምስት ቢጐድሉ ከተማይቱን ሁሉ በአምስቱ ምክንያት ታጠፋለህን? ከዚያ አርባ አምስት ባገኝ አላጠፋትም አለ።

29 ደግሞም ተናገረው፥ እንዲህም አለ፦ ምናልባት ከዚያ አርባ ቢገኙሳ? እርሱም፦ ለአርባው ስል አላደርገውም አለ።

30 እርሱም፦ ጌታዬ አይቆጣ እኔም እናገራለሁ፤ ምናልባት ከዚያ ሠላሳ ቢገኙሳ? አለ። እርሱም፦ ከዚያ ሠላሳ ባገኝ አላጠፋም አለ።

31 ደግሞም፦ እነሆ፥ ከጌታዬ ጋር እናገር ዘንድ አንድ ጊዜ ጀመርሁ፤ ምናልባት ከዚያ ሀያ ቢገኙሳ? አለ። እርሱም፦ ከዚያ ሀያ ቢገኙ ስለ ሀያው አላደርገውም አለ።

32 እርሱም፦ እኔ ደግሞ አንድ ጊዜ ብቻ ብናገር ጌታዬ አይቆጣ፤ ምናልባት ከዚያ አሥር ቢገኙሳ? አለ። እርሱም፦ ስለ አሥሩ አላጠፋትም አለ።

33 እግዚአብሔርም ከአብርሃም ጋር ንግግሩን በጨረሰ ጊዜ ሄደ፤ አብርሃምም ወደ ስፍራው ተመለሰ።

Address

Lancaster, PA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ermiyas Girma posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ermiyas Girma:

Share