
07/21/2025
👉"ለልጅ ልጅ ሁሉ ስምሽን ያሳስባሉ"
መዝ. 44 (45)፥17
👉ሐምሌ 15 ቀን የሶርያው ቅዱስ እኤፍሬም የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው።
#የቅዱስ #ኤፍሬምን #ውዳሴ #ማርያም #መጸለይ #ያለው #ቃል #ኪዳን
" . . . ይህን ተናግሮ ሲፈጽም እንደቀደመው ዝም ብላው አትሄድም ውዳሴዬን ከቅዳሴዬ አንድ አድርጎ ያነበበ የተረጎመ የሰማ ያሰማ አንተ ከገባህበት ውሳጤ መንጦላዕት አስገባዋለሁ ብላ ተስፋውን ነግራው ቃል ኪዳኑን ሰጥታው በያዘችው መስቀለ ብርሃን ባርካው ሰማየ ሰማያት ታርጋለች። እርሱም ተባርኮ እጅ ነሥቶ ከመካነ ግብሩ ይቀመጣል።"
ምንጭ፦
ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ፣ ዘእሑድ፣ መጋቤ ሐዲስ ደምፀ አንበርብር፣ ገጽ 194-195፣ 2007ዓ.ም
👉"በኋላዋ ደናግሉን ለንጉሥ ይወስዳሉ፥ ባልንጀሮችዋንም ወደ አንተ ያቀርባሉ፤ በደስታና በሐሴት ይወስዱአቸዋል፥ ወደ ንጉሥ እልፍኝም ያስገቡአቸዋል። በአባቶችሽ ፋንታ ልጆች ተወለዱልሽ፥ በምድርም ሁሉ ላይ ገዥዎች አድርገሽ ትሾሚያቸዋለሽ። ለልጅ ልጅ ሁሉ ስምሽን ያሳስባሉ" መዝ. 44(45)፥14-17