12/05/2025
ኅዳር 26 ዕረፍታቸው ነው! በረከታቸው ይደርብን!
👉“የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች” ያዕ. 5፥16
ለአቡነ ሀብተ ማርያም የተሰጣቸው ቃል ኪዳን (በአማርኛና በልሳነ እንግሊዝ)
“. . . እኔ የሰጠሁህን ቃል ኪዳን ተስፋ አድርጎ መጽሐፈ ገድልህን ለሚጽፈው የሚጽፈውን ድኅነት በሚገኝበት ስሙን በመንግሥተ ሰማያት በእውነት እጽፋለሁ፤ ሥጋህም ከተቀበረበት ቦታ በወዲህና በወዲያ ተከታትመው የሥጋዊ ደማዊ ሰው ጸሎት ሁሉ ወደኔ እንዲያሳርጉ መላእክተ ብርሃንን አዛለሁ።
በዚያ የተደረገውን ይዞ አንተን ያከበረውን አከብረዋለሁ፣ አንተን የወደደ እኔንም መውደዱ ነውና።
የሰጠኹህን ቃል ኪዳን አስቦ ለቤተ ክርስቲያንህ ቅብን፣ ዘይትን፣ ወይንን፣ ዕጣንን፣ ኅብስትን እስከ ቀዝቃዛ ውኃ ድረስ በአንተ ስም መባዓ የሰጠውን ሰው የወደደውን ሁሉ አደርግለታለሁ፥ በመንግሥተ ሰማያትም ከወዳጆቹ ከቅዱሳን ጋራ ደስ አሰኘዋለሁ።
ትሩፋትህን የሚናገር መጽሐፍህን የሚያነብ፣ ወዲያና ወዲህ ሳይል በማድነቅ መጽሐፈ ገድልህን የሚሰማ በግልጥ ካንተ ጋር መንግሥተ ሰማያት እንዲገባ አደርገዋለሁ።
ኃጥእ ሰው ሁሉ በሃይማኖት አምኖ ‘አቤቱ የአባታችን የአቡነ ሀብተ ማርያም ፈጣሪ ኃጢአቴን ይቅር በለኝ’ ብሎ ያንተን ስም ጠርቶ ቢለምነኝ ኃጢአቱን አስተሠርይለታለሁ አንተ ስለወደድኸኝ ንጹሕ ማደሪያ ስለሆንከኝ። . . .”
ምንጭ፦
ገድለ አቡነ ሀብተ ማርያም (ግእዝ አማርኛ)፣ ቅዳሜ የሚነበብ፣ ምዕራፍ 14፣ ቁጥር 5-9፣ ገጽ 151፣ 2001 ዓ.ም
👉"አምላክህ እግዚአብሔር እርሱ አምላክ እንደ ሆነ፥ ለሚወድዱትም ትእዛዙንም ለሚጠብቁ ቃል ኪዳኑንና ምሕረቱን እስከ ሺህ ትውልድ ድረስ የሚጠብቅ የታመነ አምላክ እንደ ሆነ እወቅ" ዘዳ. 7፥9
👉"ጻድቃንንም የሚጠሉ ይጸጸታሉ" መዝ. 33 (34)፥21
👉"የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው" ምሳ. 10፥7
👉" እግዚአብሔር ጻድቃንን ይወድዳል" መዝ. 145(146)፥8
👉"የጻድቃንን ማደሪያቸውንና የቅዱሳንን ማረፊያቸውን አየሁ። በዚያም ዐይኖቼ ከመላእክት ጋራ ማደሪያቸውን፥ ከቅዱሳንም ጋር ማረፊያቸውን አዩ። ስለ ሰው ልጆች ይለምናሉ፥ ይማልዳሉ፥ ይጸልያሉም።" መጽሐፈ ሄኖክ 9፥21-23
👉"ለሚያምን ሁሉ ይቻላል" ማር. 9፥23
- - - - - - - - - - - - - - - -
Covenant Given to Abune Habte Maryam
👉” The effectual fervent prayer of a righteous man availeth much” Jas. 5:16
“I shall verily inscribe within the heavenly kingdom—where salvation hath her dwelling—the name of him who, trusting in the covenant I bestowed upon thee, doth set down thine account. And I shall charge angels of light to encamp both here and there about the place where thy body lieth entombed, that they may bear aloft the prayers of mortal men—creatures of flesh and blood—before Mine own presence.
And remembering what befell in that holy place, whosoever doth honor thee, him shall I likewise honor; for whoso loveth thee loveth Me also.
To the one who, pondering the covenant I granted unto thee, bringeth oil, ointment, wine, incense, bread, or even cold water as an offering in thy name, I shall fulfill all his desires and make him rejoice with his beloved—the saints—in My heavenly kingdom.
He that readeth thy deeds, declaring thy virtue, and he that hearkeneth in wonder to thine accounts and wandereth not in mind nor body, him shall I cause to enter heaven with thee unhindered.
Forasmuch as thou hast loved Me and become My pure abode—if a sinner believeth and crieth, ‘O God of Abune Habte Maryam, forgive my sins,’ invoking thy name as he entreateth Me—I shall pardon him.”
Source:
The Hagiography of Abune Habte Maryam (Ge'ez-Amharic), Saturday' Reading, Chapter 14, No. 5-9, Page 151, 2001 E.C
👉"Know therefore that the Lord thy God, he is God, the faithful God, which keepeth covenant and mercy with them that love him and keep his commandments to a thousand generations" Deut. 7:9
👉"they that hate the righteous shall be desolate" Ps. 34:21
👉"The memory of the just is blessed" Prov. 10:7
👉"the Lord loveth the righteous" Ps. 145:8
👉"I saw the dwelling place of the righteous and the resting place of the saints. There, my eyes beheld their dwelling with the angels and their resting place with the saints. They entreat for the children of men, they intercede for them, and they pray for them." Enoch 9:21-23
👉"all things are possible to him that believeth" Mark 9:23