12/12/2025
👉"ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ፤ ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና።" መዝ. 44 (45)፥10-11
"እንዲሁም መዝሙረኛው ሀቅ ስለሆነው ከድንግል ሰለመወለዱ ዝም አላለም፥በጭራሽ፤ በዚያው እየጠቀስነው በነበረው በመዝሙር 44 (45) ውስጥ ወዲያው ያሰምርበታል። 'ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ፤ ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና' (ቁ. 10-11)በማለት። ይህ ታዲያ ገብርኤል 'ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው' (ሉቃ. 1፥28) በማለት ከተናገረው ጋር አንድ አይደለምን? መዝሙረኛው እርሱን ቅቡዕ ማለትም መሲሕ ወይም ክርስቶስ ካለ በኋላ (መዝ. 44(45)፥7) 'ልጄ ሆይ፥ ስሚ' በማለት የሥጋ ልደቱን ያውጃል። ልዩነቱ ገብርኤል ማርያምን በቅጽል መጥራቱ ብቻ እንደሆነ እይ፤ ምክንያቱም መልአኩ ከእርሷ በዘር ይለያልና (መልአኩ ሰማያዊ ነውና)። ነገር ግን ዳዊት በተገባ የራሱ ሴት ልጅ (ልጄ) እያለ ይጠራታል ምክንያቱም ከእርሱ ነውና እርሷ የምትገኘው።" - ቅዱስ አትናቴዎስ ዘእስክንድርያ፣ የመዝሙረ ዳዊትን ጥቅምና ትርጓሜ ለዲያቆኑ ለማርሴሊነስ ለማስረዳት በጻፈው ደብዳቤው 6ኛው አንቀጽ
👉"Hearken, O daughter, and consider, and incline thine ear; forget also thine own people, and thy father's house; So shall the king greatly desire thy beauty: for he is thy Lord; and worship thou him." Ps. 45:10-11
"Neither is the Psalmist silent about the fact that He should be born of a virgin - no, he underlines it straight away in 45, which we were quoting, but a moment since. "Harken, O daughter, he says, and see and incline thine ear, and forget thine own people and thy father’s house. For the King has desired thy beauty, and He is thy Lord." Is not this like what Gabriel said, "Hail, thou that art full of grace, the Lord is with thee?" [Lk 1:28] For the Psalmist, having called Him the Anointed One, that is Messiah or Christ, forthwith declares His human birth by saying, "Harken, O daughter", and see; the only difference being that Gabriel addresses Mary by an epithet, because he is of another race from her, while David fitly calls her his own daughter, because it was from him that she should spring." - St. Athanasius, Letter to (Deacon) Marcellinus on the Interpretation of the Psalms, 6th Paragraph