Gishen Media / ግሸን ሚዲያ

Gishen Media / ግሸን ሚዲያ "ለሃገራችን እንደዜጋ ለቤተ ክርስቲያናችን እንደልጅነታችን እናገለግላለን"
(2)

የእሑድ ድርሳነ ኪዳነ ምሕረት (በአማርኛና በልሳነ እንግሊዝ)አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም በእግዚአብሔር አንድነት  #በሰንበተ  #ክርስቲያን ( #እሑድ)  #ቀን  ...
10/26/2025

የእሑድ ድርሳነ ኪዳነ ምሕረት (በአማርኛና በልሳነ እንግሊዝ)

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም በእግዚአብሔር አንድነት #በሰንበተ #ክርስቲያን ( #እሑድ) #ቀን #የሚነበብ #የኪዳነ #ምሕረት #ድርሳን #ይህ #ነው።

መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ለእናቱ መልሶ “ለሚወዱሽ ሰዎች ሁሉ መሸጋገሪያ ሁኝ አላት። በአንቺ መሰላልነት ከምድር ወደ ሰማይ ያርጋሉ እኔም ከምድር ከፍ ከፍ ያልሁ እንደሆነ ሁሉን ወደ እኔ እስባለሁ ብዬ በወንጌል ለሐዋርያት እንደተናገርሁኝ። (ዮሐ. 12፥32)

የምስበው በምንድን ነው? የቸርነቴ መሰላል አንቺ አይደለሽም? አባቴ የመረጣቸውን ሁሉ በአንቺ ወደ እኔ አቀርባለሁ።”

መድኃኒታችን ክርስቶስ ለእናቱ ለማርያም እንደዚህ አላት።

እኛስ ለወደደን ፈጣሪያችን ምን ዋጋ እንከፍለዋለን? ቸር እናትን ይቅር ባይ ንግሥትን ለአስገኘልን ምን እንከፍለዋለን? ፊትዋ ከፀሐይና ከሰማይ ከዋክብት ይልቅ የሚያበራ፣ ከበረድ ከወተት ንጹሕ የሆነች፣ ነገሥታቱ ቤት ካለው የተክል ቦታ ዕፅዋት ይልቅ መዓዛዋ የሚያውድ፣ ከመላእክት ይልቅ ኅሊናዋ ንጽሕ የሚሆን፣ ክርስቶስን በሥጋ የጸነሰች፣ ከልዑላኑ ከነቢያት ከሐዋርያት የበለጠች ከክቡራን ይልቅ የከበረች የነቢያትና የዳዊት ልጅ ይህች ድንግል ናት። የሴቶች ሁሉ መመኪያ የምእመናንም ሁሉ ክብራቸው ይህች ናት።

ስለዚህም “ለአከበራት ለአነጻት ለአብ፣ ከእርሷ ተወልዶ ሰው ለሆነ ለወልድ፣ ከሥጋና ከነፍሷም ላልተለየ ለመንፈስ ቅዱስ ክብር ምስጋና ስግደት ይገባል” እንላለን። ለዘለዓለሙ አሜን።

መድኃኒታችን ለእናቱ እንዲህ አላት “የቃል ኪዳንሽን መጽሐፍ የጻፈው ያጻፈው፣ አንብቦ የተረጎመ፣ ቃሉን ሰምቶ በልቡ የጠበቀ ሰው ሁሉ ከአንቺ ዋጋቸውን ያገኛሉ። ከእኔና ከአንቺም ጋር በአንድነት ይኖራል፤ ለዘለዓለሙ አሜን።”

👉 "አምላክህ እግዚአብሔር እርሱ አምላክ እንደ ሆነ፥ ለሚወድዱትም ትእዛዙንም ለሚጠብቁ ቃል ኪዳኑንና ምሕረቱን እስከ ሺህ ትውልድ ድረስ የሚጠብቅ የታመነ አምላክ እንደ ሆነ እወቅ" - ዘዳ. 7፥9

- - - - - - - -

In the Name of the Father, and of the Son, and of the Holy Spirit, the one God.
This is the reading for the Queenship of Mary (the Covenant of Mercy / Kidane Mehret) for the Sabbath of Christians, the Lord’s Day (Sunday).

And our Savior Jesus Christ spake unto His Mother, saying:
“Be thou a crossing for all the people that love thee. By thy being a ladder shall they be taken up from earth unto heaven, even as I have spoken in the Gospel: ‘And I, if I be lifted up from the earth, will draw all men unto Me’ (John 12:32).

With what do I draw? Art thou not the ladder of My mercy? Through thee do I draw nigh unto Me those whom My Father hath elected.”
That He said unto His Mother, Mary.
And what shall we render unto our Creator Who hath loved us? What shall we offer unto Him Who hath given unto us a gracious Mother and a merciful Queen? Behold, this is the Virgin whose countenance shineth brighter than the sun and the stars of heaven; who is purer than snow and milk; whose fragrance surpasseth the sweetness of the gardens in the palaces of kings; whose conscience is more spotless than the angels; who conceived Christ in the flesh; who is more glorious than the exalted prophets and apostles; who is more honorable than the honored; and who is the daughter of the prophets and of David. This is she who is the pride of all women and the glory of all the faithful.

Wherefore we say:
“Glory, praise, and prostration be unto the Father—Who hath honored and made her immaculate;
unto the Son—Who became man and was born of her;
and unto the Holy Spirit—Who departed not from her body nor her soul, world without end. Amen.”

And our Savior spake again unto His Mother, saying:
“Whosoever shall write the book of thy covenant, or cause it to be written, or read and translate it, or lay up its words within his heart after hearing them, he shall receive his reward of thee. He shall dwell with Me and with thee, forever and ever. Amen.”

👉"Know therefore that the Lord thy God, he is God, the faithful God, which keepeth covenant and mercy with them that love him and keep his commandments to a thousand generations" Deut. 7:9

ምንጭ/Source:
ድርሳነ ኪዳነ ምሕረት፣ ቁጥር 1 – 8፣ ገጽ 130 – 131፣ 2001 ዓ.ም
Homily of the Covenant, no. 1-8, pages 130-131, 2001 E.C (Geez-Amharic)

10/25/2025
ለአቡነ አረጋዊ የተሰጣቸው ቃል ኪዳን (በአማርኛና በልሳነ እንግሊዝ) 👉"ለሚያምን ሁሉ ይቻላል" ማር. 9፥23 "ጌታችን በመንፈቀ ሌሊት ተገልጾ ቃል ኪዳን ሰጠው ዳግመኛም ጸሎትህ እነሆ በኔ ...
10/23/2025

ለአቡነ አረጋዊ የተሰጣቸው ቃል ኪዳን (በአማርኛና በልሳነ እንግሊዝ)

👉"ለሚያምን ሁሉ ይቻላል" ማር. 9፥23

"ጌታችን በመንፈቀ ሌሊት ተገልጾ ቃል ኪዳን ሰጠው ዳግመኛም ጸሎትህ እነሆ በኔ ዘንድ ደርሶ ተሰምቷል።

ስለዚህም ከድካም ወደዕረፍት ከኀዘን ደስታ ወዳለበት ከኃሣር ወደክብር በታላቅ ደስታ እወስድህ ዘንድ ወደአንተ መጥቻለሁ አለው።

የዚህን የሀላፊውን ዓለም ክብር ስለናቅህ በመንግስተ ሰማያት የማያልፈውን የማይጠፋውን ክብር አቀዳጅሃለሁ።

በዚህ ዓለም የሐሩን ልብስ የወርቅና የብሩን ጌጥ እንደናቅህ እኔ አይን ያላየውን ጆሮ ያልሰማውን በሰው ልቡና ያልታሰበውን አለብስሃለሁ አስጌጥሃለሁ።

ከትውልድ ሀገርህ ወጥተህ በባዕድ አገር ስለኖርክ እኔ ሰማያዊት ኢየሩሳሌምን እሰጥሃለሁ የሚያልፉ የሚፈርሱ የዚህን ዓለም ቤት ንብረት ስለናቅህ የማይፈርስ የማያልፍ የሕይወት ቤት እኔ እሰጥሃለሁ።

መታሰቢያህን ያደረገ በጸሎትህም የተማመነውን ሁሉ እኔ በመላእክት ፊት ሞገስን ባለሟልነትን እሰጠዋለሁ።

በእውነተኛ ሃይማኖት ሁኖ የገድልህን መጽሐፍ የጻፈ ያጻፈ የተረጎመ እኔ ስሙን በሕይወት መጽሐፍ እጽፈዋለሁ።

መታሰቢያህ በሚደረግበት ዕለት የራበውን ያጠገበ የጠማውን ያጠጣ እኔ የሕይወት እንጀራ አበላዋለሁ የሕይወት ጽዋም አጠጣዋለሁ።

በዓልህ በሚከበርበት ዕለት ለራበው ምሳውን ያበላ እኔ በምሳሐ ደብረ ጽዮን የምሳ ግብዣ አደርግለታለሁ።

በስምህ በተሠራው ቤተ መቅደስ ውስጥ የጸለየ የለመነ ፈጥኜ ጸሎቱን እሰማዋለሁ ልመናውንም እቀበለዋለሁ ቤተ ክርስቲያንህንም ለሠራ ዐሥራ ሁለት የብርሃን አዳራሽ አዘጋጅለታለሁ።

የገድልህን መጽሐፍ በመታመን በንጽሕና አድርጎ በቤቱ ያስቀመጠ ወረርሽኝ በሽታ ወይም ቸነፈር በቤቱ አይገባም ድንገተኛም የሰውና የእንስሳ ሞት አይደርስበትም የእህል ችግርም አይኖርበትም።

በጥቡዕ ልብ ሆኖ የገድልህን መጽሐፍ የሰማ ያለስንፍና በፍጹም መታመን የንባቡን ኃይለ ቃል የሰማ እኔ ለችግሩ ሁሉ ፈጥኜ እደርስለታለሁ።

ለቤተ ክርስቲያንህ መባ ያገባ ዕጣን ወይም ቅብዓ ሜሮን ወይም ዘይት የሰጠ እኔ በሰማያዊት መንግሥቴ አስገባዋለሁ።

ንጉሥም ቢሆን ለቤተ ክርስቲያንህ የሐር መጎናጸፊያ ቢሰጥ በዓልህ በሚከበርበት ዕለት ቢያከብር እኔ በመንግሥቴ አከብረዋለሁ በጠላቱም ላይ ድልን አቀዳጀዋለሁ ከመኳንንቱ ከመሳፍንቱ ጋር ሰላምን እሰጠዋለሁ በምድርም ላይ ዘመኑን ወይም ዕድሜውን አረዝምለታለሁ።

ከሁሉም ይልቅ የሞት ጥላ አያርፍብህም መልአከ ሞትም ሊያስደነግፅህ አይችልም እንደ ነቢያቶቼ ኤልያስና ሄኖክ ትሠወራለህ እንጂ።

በቡሩካን እጆችህ የቀበርካት እናትህ ዕድናንም በትንሣኤ ሕይወት እስካስነሣት ድረስ መቃብሯን አፍርሶ ሌላ ሰው እንዳይቀበርበት ወይም ለማንም እንዳይታይ እንደ እንበረም ልጅ እንደሙሴ መቃብር ይሰወራል።

ይህቺን ቤተ መቅደስህንም ታላቅና የተከበረች አደርጋታለሁ የበቁ የደጋግ ነገሥታትና ጳጳሳት የመቃብራቸው ወይም የማረፊያቸው ቦታ ትሆናለች።

ጌታችንም ይህን ቃል ኪዳን በሰጠው ጊዜ ክቡር አባታችን አቡነ አረጋዊ ጌታችንን አቤቱ በፊትህ ሞገስ አግኝቼስ ከሆነ እናገር ዘንድ ይፈቀድልኝ አለው።

ጌታም ወዳጄ አረጋዊ ሆይ ፈቅጄልሃለሁ ተናገር ከኔ የምትፈልገውንም ሁሉ ጠይቅ ወይም ለምን አለው።

ከዚያም አባታችን አቡነ አረጋዊ ይህን ሁሉ ለሰጠኸኝ እስከ ዘላለሙ ድረስ ስምህ የተመሰገነ የጌትነትህም ክብር የተባረከ ነው ብሎ አመሰገነ።

አሁንም ጌታ ሆይ መታሰቢያየን ያደረገ የገድሌን መጽሐፍ የጻፈ በጸሎቴ የተማመነ እስከ ስንት ትውልድ ድረስ ትምርልኛለህ አለው።

መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እስከ ዐሥራ አምስት ትውልድ ድረስ እምርልሃለሁ አለው።

አባታችን አቡነ አረጋዊም አቤቱ ይህች ቦታ የነገሥታት የጳጳሳት የክቡራን መኳንንትና መሳፍንት ብቻ መቀበሪያ ሁና አትቅር ነገር ግን ለተገፉ ለነዳያን አባት እናት ለሞቱባቸው ለዕውራንና ለሐንካሳን መጠጊያ ትሆን ዘንድ ማንኛውም ግለሰብ ይቀበርባት እንጂ እኔ በዚች አገር እንግዳና ስደተኛ ነኝና አለው።

መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም የተመሰገንህ አረጋዊ እንደ ቃልህ ይደረግልህ አለው።

አባታችን አቡነ አረጋዊም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አቤቱ ከሩቅ ወይም ከቅርብ መጥተው ንስሐ ሳይገቡና በድንገተኛ ሞተው በዚች በአፀደ ቤተ ክርስቲያኔ የተቀበሩትን ሁሉ ኃጢአታቸውን ይቅር በላቸው አለ።

መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እንኳንስ በተራራው ጫፍ ላይ የተቀበረ ይቅርና ከተራራው ሥር እንኳ ቢሆን ይልቁንም በስምህ የተሰየመ ቤተ ክርስቲያን ሁሉ በዚያ የተቀበረው ኃጢአቱ ይሠረይለታል እነዚህንም ሁሉ ዓሥራት አድርጌ ሰጠሁህ አለው።

አባታችን አቡነ አረጋዊም አቤቱ ይህችን ቤተ መቅደስና በውስጡዋም የሚኖሩትን ባርክ አለው።

መድኃኒታችንም ይህች ቤተ መቅደስህ የተባረከች የተቀደሰች ትሁን በውስጧም ሰው አይታጣ መብራቷ አይጥፋ ሥጋዬና ደሜ በውስጧ በተዘጋጀ ጊዜ ልምላሜ ሙቀት ያልተለየው የሠመረ በፊቴም ተቀባይነት ያለው ይሁን አለው።

አባታችን አቡነ አረጋዊም መልሶ አቤቱ ይህችን መንፈሳዊ ማኅበር ልጆቼንና ቅዱሳኖቼንም ሁሉ ባርክ አለው።

ይህች ማኅበር የተባረከች ትሁን የችግረኞች መጠጊያ የተራቡ የሚጠግቡባት የታረዙ የሚለብሱባት ወይም ለተራቡት ምግብ ለተራቆቱት ልብስ ትሁን አለው።

እሊህ ቅዱሳን ልጆችህም እልፍ አእላፋት ይሁኑ እንደባህር አሸዋ እንደሰማይ ከዋክብትም ትውልዱ ነገዱ እንደተስፋፋ ዘሩም እንደበዛ እንደ ያዕቆብ ልጆች የበዙ ይሁኑ።

ድንገተኛ በሽታ መቅሠፍት ሰውነትን የሚያዝግ የሚያጠወልግ ሕማም ወደነሱ አይቀርብም።

አባታችን አቡነ አረጋዊ አቤቱ ይህችን የማድርባትን በአቴንና ከአንተም ጋር ቆሜ ቃል ኪዳን የተቀበልኩባትን ቦታ ባርክ።

ይልቁንም ይህቺ እግርህ ከቆመባት መሬት አፈሯን ወስደው በመቀባት መድኃኒት ትሆናቸውና ወይም ከሕመማቸው ይፈወሱ ዘንድ ባርካት አክብራትም።

ሕመም ያለበት ቢኖር ፈጥኖ ይወገድለት በፍጹም መታመን በአንገቱ ላይ እምነቱን ቢአሥር ከክፉ ደዌ ከሚያንቀጠቅጥ ወይም ከሚያንዘፈዝፍ በሽታ ይድን ዘንድ መሬቱን ወይም እምነቱን በተቀባ ጊዜ በሱ ላይ ድንቅ ድንቅ ተአምር ተፈጽሞ ከሕመሙ ነፃ ይሆን ዘንድ ፈቃድህ ይሁን በማለት አባታችን አቡነ አረጋዊ ለመነ።

ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ይሁን ይደረግልህ በማለት በማይታበል ቃሉ ቃል ኪዳን ገባለት።"

+++አሜን+++

ምንጭ፦
ገድለ አቡነ አረጋዊ፤ ዘሰኔ፤ ምዕራፍ 2፤ ከቁጥር 1 – 36፤ 1978 ዓ.ም

👉"ኢየሱስ፦ እስክመጣ ድረስ ይኖር ዘንድ ብወድስ ምን አግዶህ? አለው" ዮሐ. 21፥23

👉"ያመኑትንም እነዚህ ምልክቶች ይከተሉአቸዋል፤ በስሜ አጋንንትን ያወጣሉ፤ በአዲስ ቋንቋ ይናገራሉ፤ እባቦችን ይይዛሉ። የሚገድልም ነገር ቢጠጡ አይጎዳቸውም፤ እጃቸውን በድውዮች ላይ ይጭናሉ እነርሱም ይድናሉ።" ማር. 16፥17-18

👉"በእባብ ላይ ትጫማለህ" መዝ. 90 (91)፥13

👉"የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው" ምሳ. 10፥7

👉"ጻድቃንንም የሚጠሉ ይጸጸታሉ" መዝ. 33 (34)፥21

👉" እግዚአብሔር ጻድቃንን ይወድዳል" መዝ. 145(146)፥8

👉"አምላክህ እግዚአብሔር እርሱ አምላክ እንደ ሆነ፥ ለሚወድዱትም ትእዛዙንም ለሚጠብቁ ቃል ኪዳኑንና ምሕረቱን እስከ ሺህ ትውልድ ድረስ የሚጠብቅ የታመነ አምላክ እንደ ሆነ እወቅ" ዘዳ. 7፥9

👉"የጻድቃንን ማደሪያቸውንና የቅዱሳንን ማረፊያቸውን አየሁ። በዚያም ዐይኖቼ ከመላእክት ጋራ ማደሪያቸውን፥ ከቅዱሳንም ጋር ማረፊያቸውን አዩ። ስለ ሰው ልጆች ይለምናሉ፥ ይማልዳሉ፥ ይጸልያሉም።" መጽሐፈ ሄኖክ 9፥21-23

- - - - - - - - - - - - - - - - - - - - - - - -

The Covenant Given unto Abune Aregawi:

👉"all things are possible to him that believeth" Mark 9:23

Our Lord appeared unto him at midnight and bestowed upon him a covenant, saying:
“Thy prayer hath ascended unto Me, and I have hearkened unto thy supplication.

Wherefore am I come to take thee from weariness unto rest, from sorrow unto joy, and from affliction unto honor and exceeding gladness.

Because thou hast forsaken the glory of this temporal and fleeting world, I shall endue thee with honor that fadeth not, nor is momentary, in My heavenly kingdom.

Forasmuch as thou hast renounced raiment of silk, and jewels of gold and silver, I shall clothe and adorn thee with that which eye hath not seen, nor ear heard, neither hath it entered into the heart of man.

Because thou hast left the land of thy nativity and sojourned in a strange country, I shall give unto thee the Heavenly Jerusalem. And because thou hast forsaken thine house and the treasures of this passing world, I shall grant unto thee a habitation of life, incorruptible and imperishable.

Whosoever shall commemorate thee, and believe in thine intercession, I shall grant him favor before Mine angels, and give unto him ministry.

The name of him that writeth thy hagiography or account in true faith, or causeth it to be written, or translateth it, shall I inscribe in the Book of Life.

He that feedeth the hungry or giveth drink unto the thirsty upon thy feast day shall partake of the Bread of Life and drink from the Chalice of Life.

I shall prepare a banquet upon Mount Zion for him that feedeth the poor upon thy feast day.

Whoso prayeth in the church builded in thy name, I shall hear him speedily and accept his supplication. And for him that buildeth thy church, I shall prepare twelve halls of light.

Whoso keepeth thy sacred history in his dwelling faithfully and reverently, no sickness nor pestilence shall enter therein; neither sudden death of man nor beast shall befall him, neither shall his fruits fail.

He that hearkeneth diligently unto thy acts and unto the verses of the readings with faith, I shall be swift to deliver him from all his troubles.

If any offer unto thy church oblations, incense, myrrh, or oil, I shall cause him to enter into My heavenly kingdom.

If a king bestow vestments upon thy church and celebrateth thy feast, I shall honor him in My kingdom, give him victory over his enemies, grant him peace with princes and captains, and prolong his days upon the earth.

Above all, thou shalt not be touched by the shadow of death; neither shall the angel of death affright thee. For thou shalt be taken up, and hidden, even as My prophets Elias and Enoch.

And until the Resurrection of the Dead, thy mother Edna, whom thou didst bury with thine holy hands, her sepulchre shall not be destroyed that another may be laid therein, but shall be hidden, even as the tomb of Moses, son of Amram.

And I shall make thy church exalted and much honored; it shall become the resting place of righteous and perfect emperors and bishops.’

When our Lord had delivered unto him this covenant, our venerable father Abune Aregawi besought Him, saying,
‘O Lord, if I have found grace in Thy sight, suffer me to speak before Thee.’

And the Lord said unto him,
‘My beloved Aregawi, I have granted thee license. Speak; ask all that thou desirest of Me, and make thy supplication.’

Then our father gave thanks, saying,
‘Blessed be Thy name, O Lord, who hast granted me all things for ever; and blessed be the glory of Thy dominion.’

And he continued, saying,
‘And now, O Lord, how many generations of him that keepeth my feast, writeth my history, and believeth in mine intercession wilt Thou forgive?’

And our Savior Jesus Christ answered and said,
‘For thy sake will I pardon fifteen generations of his seed.’

Then said our father,
‘O Lord, forasmuch as I was a stranger in this land, let not this place be only the resting of emperors, bishops, nobles, and rulers; but let it be a refuge for the poor and outcast, for orphans, the blind, and the maimed — yea, a sepulchre for all.’

And the Lord answered him,
‘Blessed Aregawi, even as thou hast spoken, so shall it be unto thee.’

Then our father Abune Aregawi said unto our Savior Jesus Christ,
‘O Lord, forgive all those who, unrepentant, come from far and near, die suddenly, and are buried within my church.’

And our Savior answered,
‘Not only those buried upon the mountain, but even they that rest at the foot thereof, yea, all that are buried in churches raised in thy name — their sins are forgiven. I have made them all thy portion and thine inheritance.’

And our father besought Him again, saying,
‘Bless, O Lord, all that abide within the church or monastery and dwell therein.’

And our Savior replied,
‘Let thy church and monastery be blessed and hallowed. Let it never be without inhabitants, neither let its light be extinguished. When My Body and Blood are offered within it, let it be acceptable and well-pleasing before Me.’

Then said our father,
‘Bless, O Lord, this spiritual assembly of my children and of all my holy ones.’

And the Lord said,
‘Blessed be this congregation. Let it be a refuge for the destitute, a place where the hungry are filled, the thirsty refreshed, and the naked clothed.
Let thy holy children be multiplied — thousands upon thousands — even as the sand of the sea and the stars of heaven, as was Jacob whose seed became exceeding many.
Neither let sudden sickness, nor pestilence, nor the wasting disease draw nigh unto them.’

Then our father Abune Aregawi entreated Him, saying,
‘O Lord, bless this my cell, and this place wherein I have received Thy covenant. Grant that it may become a spiritual medicine unto all that take of the earth whereon Thou standest, that they may be healed miraculously. Bless it, and glorify it.’
‘If any be sick, let his malady be swiftly taken away. Let it be Thy will that if he bindeth upon his neck the holy earth, let him be delivered from grievous disease, trembling, and palsy; and if he anoint himself therewith, let great wonders of healing be wrought upon him.’

And our Lord, God, and Savior Jesus Christ made covenant with him, saying,
‘So be it, even as thou hast spoken.’”

+++Amen+++

Source:
Hagiography of Abune Aregawi, Reading of Senne, Chapter 2, no. 1-36, 1978 Ethiopian Calendar (Geez-Amharic)

👉"If I will that he tarry till I come, what is that to thee?" John 21:23

👉"And these signs shall follow them that believe; In my name shall they cast out devils; they shall speak with new tongues; They shall take up serpents; and if they drink any deadly thing, it shall not hurt them; they shall lay hands on the sick, and they shall recover." Mark 16:17

👉"Thou shalt tread upon . . . adder" Ps. 91:13

👉"The memory of the just is blessed" Prov. 10:7

👉"they that hate the righteous shall be desolate" Ps. 34:21

👉"the Lord loveth the righteous" Ps. 145:8

👉"Know therefore that the Lord thy God, he is God, the faithful God, which keepeth covenant and mercy with them that love him and keep his commandments to a thousand generations" Deut. 7:9

👉"I saw the dwelling place of the righteous and the resting place of the saints. There, my eyes beheld their dwelling with the angels and their resting place with the saints. They entreat for the children of men, they intercede for them, and they pray for them." Enoch 9:21-23

ድርሳነ ሚካኤል ዘጥቅምት (በአማርኛና በልሳነ እንግሊዝ) 👉"ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል" ዳን. 12፥1በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አምነን በስም በአካል በግብር ሦ...
10/21/2025

ድርሳነ ሚካኤል ዘጥቅምት (በአማርኛና በልሳነ እንግሊዝ)

👉"ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል" ዳን. 12፥1

በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አምነን በስም በአካል በግብር ሦስት ብንል በባሕርይ በህልውና በአገዛዝ አንድ አምላክ በማለት እያመን #ጥቅምት #በባተ #በዓሥራ #ሁለት #ቀን ንዑድ ክቡር የሚሆን የመላእክት አለቃ #የቅዱስ #ሚካኤል #በዓል #የሚከበርበት #ቀን መሆኑን እንናገራለን።

በዛሬው ቀን እግዚአብሔር ነቢዩ ሳሙኤልን በቤተ መቅደስ ሣለ በቂስ ልጅ በሳኦል ፋንታ በእስራኤል ላይ ዳዊትን ቀብቶ ያነግሠው ዘንድ በቤተ ልሔም የሚኖር የዳዊት አባት ወደ እሴይ ቤት ልኮታልና።

ያን ጊዜም ነቢዩ ሳሙኤል ነገሥታቱ ተቀብተው የሚነግሡበትን ቅብዐ መንግሥት ይዞ ወደ እሴይ ዘንድ በደረሰ ጊዜ ልጆችህን ሁሉ አቅርብልኝ ከልጆችህ መካከል ቅብዐ መንግሥት ቀብቼ በእስራኤል ላይ አነግሠው ዘንድ የእግዚአብሔር መልአክ አዞኛልና አለው።

እሴይም ይህን ቃል ከሳሙኤል አንደበት በሰማ ጊዜ እሺ በጎ ብሎ ከዳዊት በስተቀር ልጆቹን በሙሉ አቀረበለት እሱ (ዳዊት) በእርሻው መካከል በጎቹን ይጠብቅ ነበርና።
ከዚያም በእሴይ ልጆች በያንዳንዳቸው ራስ ላይ ቅብዐ መንግሥቱን እያፈሰሰ ቀብቶ ሊያነግሥ ቢሞክር የእግዚአብሔር ፈቃድ ሳይሆን ስለቀረ ሳሙኤል እሴይን ከልጆችህ መካከል የቀረ የለምን ሲል ጠየቀው እሴይም ከወንድሞቹ ሁሉ የሚያንስ ታናሽ ብላቴና አለ እሱም በበጎች መሠማሪያ በጎችን ሲጠብቅ ይገኛል አለው።

ሳሙኤልም ፈጥነህ አምጣልኝ ስለ አለው ያን ጊዜውን ፈጥኖ አመጣለትና በእግዚአብሔር ስለ ተመረጠ ቅብዐ መንግሥቱን ቀብቶ በእስራኤል ላይ አነገሠው።

ዳግመኛም በዛሬው ዕለት እግዚአብሔር ቅዱስ ሚካኤልን ወደ ዳዊት ልኮት ኃይል ሰጥቶ እየተራዳው የራዐይታዊና የኢሎፍላዊ ወገን የሚሆን ጎልያድን ገድሎ የእስራኤልን ልጆች ከጠላታቸው እጅ ያዳነበት ቀን ነው።
ስለዚህም የቤተ ክርስቲያን መምህራን የቅዱስ ሚካኤልን በዓሉን በየወሩ እንድናከብርና መታሰቢያውንም እንድናደርግ አዘዙን (ሥርዓት ሠሩልን)።

ምንጭ፦
ድርሳነ ሚካኤል ዘጥቅምት 82-88/1ኛ ሳሙ. 16/17

👉"ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ" ዳን. 10፥13

👉"የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል" መዝ. 33 (34)፥7

👉"ሁለቱም መላእክት በመሸ ጊዜ ወደ ሰዶም ገቡ፤ ሎጥም በሰዶም በር ተቀምጦ ነበር። ሎጥም ባያቸው ጊዜ ሊቀበላቸው ተነሣ፤ ፊቱንም ደፍቶ ወደ ምድር ሰገደ፥ አላቸውም፦ ጌቶቼ ሆይ፥ ወደ ባሪያችሁ ቤት አቅኑ፥ ከዚያም እደሩ፥ እግራችሁንም ታጠቡ፤ ነገ ማልዳችሁም መንገዳችሁን ትሄዳላችሁ። እነርሱም፦ በአደባባዩ እናድራለን እንጂ፥ አይሆንም አሉት። እጅግም ዘበዘባቸው፤ ወደ እርሱም አቀኑ፥ ወደ ቤቱም ገቡ፤ ማዕድ አቀረበላቸው፥ ቂጣንም ጋገረ እነርሱም በሉ።" ዘፍ. 19፥1-3

Tekemt's Encomium of the Archangel Saint Michael

👉"And at that time shall Michael stand up, the great prince which standeth for the children of thy people" Dan. 12:1

In the Name of the Father, and of the Son, and of the Holy Spirit. Believing in God, Who is one in essence, being, and dominion – albeit we confess Him thrice in name, in person, and in hypostatic attributes—do proclaim that upon the twelfth day of Tekemt (which is the two and twentieth of October) falleth the Feast of Saint Michael, the honored and most glorious Archangel.

Upon this blessed day, the Lord God sent forth Samuel the Prophet, whilst he ministered within the Temple, unto the house of Jesse, the father of David, who abode in Bethlehem, that he might anoint his son to reign in the stead of Saul, the son of Kish.

And when Samuel, bearing the holy oil of anointing, wherewith kings were consecrated to rule, came unto Jesse, he spake unto him, saying, “Bring forth thy sons, that I may anoint one among them to govern Israel, according to the commandment of the Angel of the Lord.”

Then Jesse, hearing these words, did obey, and brought forth all his sons, save only David, the youngest, who kept the sheep in the field.

Yet when Samuel lifted up the horn of oil to pour upon them, the Spirit of the Lord withheld him, for it was not His divine will. Then said Samuel unto Jesse, “Are here all thy children?” And Jesse made answer, saying, “There remaineth yet the youngest, who keepeth watch over the flock.”

Then spake Samuel, “Bring him hither with haste.” And when David was brought before him, forasmuch as God had chosen him, Samuel anointed him with oil, and made him king over Israel.

Also, on this day did God send Saint Michael to help David; and by his aid did David slay Goliath, the Philistine of Gath, and deliver the children of Israel from the hands of their enemies.

Wherefore, the holy teachers of the Church have decreed that we observe the Feast of Saint Michael each month, and hold his commemoration.

Source:
Tekemt's Encomium of the Archangel Saint Michael no. 82-88/ 1 Sam. 16/17

👉"Michael, one of the chief princes, came to help me" Dan. 10:13

👉"The angel of the Lord encampeth round about them that fear him, and delivereth them." Ps. 34:7

👉"And there came two angels to S***m at even; and Lot sat in the gate of S***m: and Lot seeing them rose up to meet them; and he bowed himself with his face toward the ground; And he said, Behold now, my lords, turn in, I pray you, into your servant's house, and tarry all night, and wash your feet, and ye shall rise up early, and go on your ways. And they said, Nay; but we will abide in the street all night. And he pressed upon them greatly; and they turned in unto him, and entered into his house; and he made them a feast, and did bake unleavened bread, and they did eat." Gen. 19:1-3

“ከአባቶቻችን ለልጆቻችን” በሚል መሪ ቃል ጥቅምት 16 ቀን 2018 ዓ.ም የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር እንደሚካሄድ ዛሬ ጥቅምት 11 ቀን 2018 ዓም በቦናንዛ አዲስ ሆቴል በተሰጠው ጋዜጣዊ...
10/21/2025

“ከአባቶቻችን ለልጆቻችን” በሚል መሪ ቃል ጥቅምት 16 ቀን 2018 ዓ.ም የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር እንደሚካሄድ ዛሬ ጥቅምት 11 ቀን 2018 ዓም በቦናንዛ አዲስ ሆቴል በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ተገለጸ።

በመግለጫው የደብረ ታቦር ደብረ ልዑላን መድኃኔ ዓለም የ፬ቱ ጉባኤያት መጻሕፍት ምስክር ጉባኤ ቤት የ72 ሚሊዮን ብር ፕሮጀክት ይፋ አድርጓል።

EOTCMK TV ጥቅምት 11 ቀን 2018 ዓ.ም

"በኦርቶዶክሳዊ ትውፊትና ትምህርት ዓለም አቀፍ በጎ ተጽዕኖበመፍጠር ትውልድ አሻጋሪ የልሕቀት ጉባኤ ቤት መሆን" የሚል ታላቅ ርዕይ ያለው ጉባኤ ቤቱ ይህ ርዕይ እውን እንዲሆን ዓለም አቀፍ መንፈሳዊ ትምህርት ማዕከል ግንባታ ለማጠናቀቅ አቅዷል።

የደብረ ታቦር ደብረ ልዑላን መድኃኔ ዓለም የ፬ቱ ጉባኤያት መጻሕፍት ምስክር ጉባኤ ቤት መምህር መምህረ መምህራን በጻሕ ዓለሙ ጥቅምት 16 ቀን 2018 ዓ.ም በግዮን ሆቴል ገቢ መሰብሰብ እንዳቀዱ ገልጸዋል።

በ1851 ዓ.ም በአጼ ቴዎድሮስ አማካኝነት በቅኔ እና መጻሕፍት ጉባኤው እንደተጀመረ ገልጸው በ2011 ዓ.ም አምስተኛ የወንበር መመህር ሁነው መመደባቸውን ተናግረዋል።

ከቦታዊ ታሪካውነት አንፃር እና ካሉ ነባራዊ ችግሮች ተነስተው የተለያዩ ፕሮጀክቶችን እንደቀረፁ ተናግረዋል።

የመጀመሪያው ፕሮጀክትም ከ300 በላይ የትርጓሜ ደቀ መዛሙርትን ማስተናገድ የሚችል መማሪያ፣ ቤተ መጻሕፍት እና ለተለያዩ አገልግሎት የሚውሉ አዳራሾች ያሉት ሲሆን ግንባታው ተጀምሯል ብለዋል።

ሁለተኛ ፕሮጀክትም ይህ ዓለም አቀፍ የትምህርት ማዕከል ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች ለሚመጡ ደቀመዛሙርት ነጻ የትምህርት እድል ይሰጣል፤ተማሪዎቹ ጥልቅ የሆነውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶቤተክርስቲያንን ትምህርትና ትውፊት ከምንጩ ቀስመውካጠናቀቁ በኋላ ወደየሀገራቸው ተመልሰውቤተክርስቲያንን በብቃት እንዲያገለግሉ ያግዛል፤ ከዚህ በፊት በአገር ውስጥ ከተለያዩ የዜማ ትምህርትቤቶች ተምረው ያስመሰከሩ ደቀመዛሙርት የወንጌልን ትምህርት በብቃትማስተማር እንዲችሉ ተጨማሪ የማብቂያ ትምህርት መስጠትና ሌሎች አገልግሎቶችን ይዟል።

በሦስተኛነትም ቋሚ የገቢ ምንጭ ማስገኛ ፕሮጀክቶች ናቸው።

21 የተለያዩ ቋንቋ ተናጋሪዎችን ጉባኤ ቤቱ ተቀብሎ በማስተማር ለአገልግሎት ማሰማራቱን ገልጸዋል።

የደቀ መዛሙርቱ በተለያዩ ጊዜያት በምግብ እጦት እና አካባቢው ብርዳማ በመሆኑ መቋቋም እያቃታቸው በበሽታ እየተጠቁ መሆናቸውንም ተናግረዋል።

በአሁኑ ሰዓት ከ80 በላይ ደቀ መዛሙርት የሚገኙ ሲሆን ከ200 ሺህ በላይ ወርሃዊ ወጭ ቢኖርም ከምእመናን እርዳታ ውጭ ምንም ገቢ አለመኖሩን በመግለጽ ጉባኤ ቤቱ ላለበት ችግር እና ላቀዳቸው ዘላቂ ፕሮጀክቶችን እንዲደግፉ ለምእመናን ጥሪ አቅርበዋል።

በመግለጫው የተገኙት የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ስዩማን ቀሲስ ምኅረት ሞላ ደቡብ ጎንደር የድጓ ምስክር ቤት የሆነው ቅድስት ቤተልሔም፣ የዙር አምባ የዝማሬ መዋስዕት ምስክር ቤት፣ ቅዱስ ያሬድ ለ3 ዓመታት ጉባኤ ዘርግቶ ያስተማረበት፣ ከ300 በላይ መጽሐፍት የጻፉት መምህር ኤስድሮስ የነበሩበት ሀገረ ስብከት ነው ብለዋል። የዚህ ታሪክ አካል የሆነው የደብረ ታቦር ደብረ ልዑላን መድኃኔ ዓለም የ፬ቱ ጉባኤያት መጻሕፍት ምስክር ጉባኤ ቤትም የቀደሙትን በመከተልና ታሪክ በማስቀጠል በስብከተ ወንጌል ከእግዚአብሔር ወቀሳ እንድንድን እየሠራ ያለ ነው። ተማሪዎቹ በመቃብር ቤት እስከመኖር በጤናም እጦት የሚያጋጥማቸውንም ችግር ተቋቁመው
እዚህ በመድረሳቸው ቋሚ ፕሮጀክቶች ለውጤት እንዲበቁ በሀገረ ስብከቱ ስም ጥሪ አቅርበዋል።

ጥቅምት 16 ቀን በግዮን ሆቴል በሚኖረው ገቢ አሰባሰብም ሊቃውንት እና ምእመናን እንደገኙ አደራ ብለዋል።

የማኅበረ ቅዱሳን የኤድቶሪያል ቦርድ አባል መልአከ ታቦር ኃይለ ኢየሱስ ፋንታሁን በበኩላቸው የተገናኘነው በአንድ አጥቢያ ጉዳይ ሳይሆን ስለሦስት ነገር ነው ብለዋል። ይኸውም የቅባት እና ጸጋ ትምህርትን በጉባኤ የተረታበት ቦታ በመሆኑ ታሪክን ማዘክር፣ የድጓ መምህራን መፍለቂያ እንደመሆኑ ይህንን ትምህርት እና መምህራንን ማስቀጠል እና የሀገርን አንድነት መጠበቅ ነው።

በመግለጫው የተገኙት መምህር ያረጋል አበጋዝ ጉባኤ ቤቶች ሲጠነክሩ ቤተ ክርስቲያነ‍እ ትጠነክራለች፤ እነሱ ላይ መሥራት የነገዋ ቤተ ክርስቲያን ላይ መሥራት ነው። ሌሎች ለምን ሠሩ ከምንል ክፉን የሚያርሙ እና ዘመኑን ዋጅተው ምእመናንን የሚያስተምሩ መምህራንን ማዘጋጀት አለብን። መምህር በጻሕ ዓለሙ ይህንን ተረድተው ይህን እድል ስለሰጡን ለእኛ እድልም በረከትም ነው በማለት ምእመናን መሳተፍ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

ሊቀ ሊቃውንት ቀለመወርቅ ቢራራ በበኩላቸው ብዙ ሥራው የተሠራ በመሆኑ የቀረውን ለመጨረስ ምእመናን መትጋት እንዳለባቸው መልእክት አስተላልፈዋል።፣

ምንጭ- ማኅበረ ቅዱሳን

10/19/2025

👉"እናትህ እነኋት" ዮሐ. 19፣27

👉"በዚያን ጊዜ የዘብዴዎስ ልጆች እናት . . . እየሰገደችና አንድ ነገር እየለመነች ወደ እርሱ ቀረበች። እርሱም፦ ምን ትፈልጊያለሽ? አላት" ማቴ. 20፥20-21

👉"የኢየሱስ እናት፦ 'የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም' አለችው።" ዮሐ. 2፥3

👉"ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች" መዝ. 44 (45)፥9

👉"Behold thy mother"John 19:27

👉"Then came to him the mother of Zebedee's children with her sons, worshipping him, and desiring a certain thing of him. And he said unto her, What wilt thou?" Matt.20:20-21

👉"the mother of Jesus saith unto him, They have no wine" John 2:3

👉"upon thy right hand did stand the queen in gold of Ophir" Ps. 45:9

በዚህችም ቀን (ጥቅምት 9) የደብረ ገሪዛኑ አቡነ መዝገበ ሥላሴ ዕረፍታቸው ይታሰባል። ጻድቁ ወንጌልን የሰበኩ ሙታንን ያነሡ ድውያንን የፈወሱ በጾም በጸሎት የኖሩ የ16ኛውና 17ኛው መቶ ክፍ...
10/19/2025

በዚህችም ቀን (ጥቅምት 9) የደብረ ገሪዛኑ አቡነ መዝገበ ሥላሴ ዕረፍታቸው ይታሰባል። ጻድቁ ወንጌልን የሰበኩ ሙታንን ያነሡ ድውያንን የፈወሱ በጾም በጸሎት የኖሩ የ16ኛውና 17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አባት ናቸው። ጉንዳጉንዶ ማርያምን ለ53 ዓመታት አስተዳድረዋል። እመቤታችን ብዙ ጊዜ የተገለጠችላቸው መላእክት የወደዷቸው የዕረፍታቸውን ጊዜ ቢያውቁ ከሰኔ ወደ ጥቅምት ያስቀየሩ ድንቅ አባት ናቸው።

👉"ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች" መዝ. 44 (45)፥9👉"upon thy right hand did stand the queen in gold of Ophir" Ps. 45:9እንበሌኪ ድንግል ለጽጌ መለኮት...
10/18/2025

👉"ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች" መዝ. 44 (45)፥9

👉"upon thy right hand did stand the queen in gold of Ophir" Ps. 45:9

እንበሌኪ ድንግል ለጽጌ መለኮት አባሉ
ኅድጊሰ አድኅኖተ ዓለም ኵሉ
አድኅኖ ነፍሶሙ እምኵነኔ ነቢያት ኢክህሉ።
- ማኅሌተ ጽጌ - ብፁዓን ኃጥአን (በከፊል)

 #ዐርብ
10/17/2025

#ዐርብ

Address

Lancaster, PA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gishen Media / ግሸን ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share