Gishen Media / ግሸን ሚዲያ

Gishen Media / ግሸን ሚዲያ "ለሃገራችን እንደዜጋ ለቤተ ክርስቲያናችን እንደልጅነታችን እናገለግላለን"
(3)

👉"ሰው እናታችን ጽዮን ይላል" መዝ. 86 (87)፥5 👉"እኛ ደግሞ ለእናንተ እንደምንሆን ጌታ እርስ በእርሳችሁ ያላችሁን ለሁሉም የሚሆን ፍቅራችሁን ያብዛ ይጨምርም" 1ኛ ተሰ. 3፥13 👉"A...
12/13/2025

👉"ሰው እናታችን ጽዮን ይላል" መዝ. 86 (87)፥5

👉"እኛ ደግሞ ለእናንተ እንደምንሆን ጌታ እርስ በእርሳችሁ ያላችሁን ለሁሉም የሚሆን ፍቅራችሁን ያብዛ ይጨምርም" 1ኛ ተሰ. 3፥13

👉"A man shall say, Sion is my mother" Ps. 87:5 (LXX)

👉"And the Lord make you to increase and abound in love one toward another, and toward all men, even as we do toward you" 1Thess. 3:12 (KJV)

ታኅሣሥ 4 - የመጀመሪያው ሐዋርያ ቅዱስ እንድርያስ በምስክርነት (በሰማዕትነት) ዐረፈ። በረከቱ ይደርብን!👉"በብዙ ክብርም ደግሞ አከበሩን" ሐዋ. 28፥10 👉"Who also honoured u...
12/13/2025

ታኅሣሥ 4 - የመጀመሪያው ሐዋርያ ቅዱስ እንድርያስ በምስክርነት (በሰማዕትነት) ዐረፈ።

በረከቱ ይደርብን!

👉"በብዙ ክብርም ደግሞ አከበሩን" ሐዋ. 28፥10

👉"Who also honoured us with many honours" Acts 28:10

Stop the killing and the cover-up of the massacre of Orthodox Tewahedo Christians in Ethiopia! Between October 24 and No...
12/12/2025

Stop the killing and the cover-up of the massacre of Orthodox Tewahedo Christians in Ethiopia! Between October 24 and November 27, 2025, more than 51 were killed in Oromia (the majority of which were in Arsi)—and thousands more over the past eight years nationwide.

The number of killed in just over 30 days has reached 51 after eleven more Orthodox Christians that were abducted were killed at Mechetu Bebekesa locality of Enqolo Wabe district in Arsi Zone of Oromia Regional State on Thursday, November 27, 2025.

(Image shows Lijalem Sentayehu, an Orthodox child that was abducted and killed from Digelu Locality of Sole Guna District, on November of 2024, in Arsi Zone, Oromia.)

ታኅሣሥ 3 - የአቡነ ዜና ማርቆስ ዘደብረ ብሥራት ዘምሁር ኢየሱስ ዕረፍታቸው ነው። ጻድቁ ከአባታቸው ቀሲስ ዮሐንስ እና ከእናታቸው ማርያም ዘመዳ በቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ ብሥራት በጽላልሽ ዞ...
12/12/2025

ታኅሣሥ 3 - የአቡነ ዜና ማርቆስ ዘደብረ ብሥራት ዘምሁር ኢየሱስ ዕረፍታቸው ነው። ጻድቁ ከአባታቸው ቀሲስ ዮሐንስ እና ከእናታቸው ማርያም ዘመዳ በቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ ብሥራት በጽላልሽ ዞረሬ ቡልጋ በኢቲሳ ቅዱስ ሚካኤል አጥቢያ (ሰሜን ሸዋ) ተወልደዋል፤ ስማቸውንም ያወጣላቸው ወንጌላዊው ነው። በቅዱሳን ሊቃነ መላእክትም ይጠበቁ የነበሩት ጻድቁ በተአምራት የታጀበው ጥምቀታቸው የተከናወነው በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በአረጋዊ አጎታቸው በቀሲስ እንድርያስ ነበር።

በከባቢያቸው የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ከተማሩ በኋላ በ8ት ዓመታቸው ድቁና ተቀብለዋል። እድሜያቸው ሲደርስ ማርያም ክብራ ከተባለች ከባለጠጎች ወገን ከሆነች ልጅ ጋር ቢያጋቧቸውም ሁለቱም ምናኔን ፈላጂዎች በመሆናቸው ጫጉላ ቤታቸውን ስለክርስቶስ ፍቅር ይህ ዓለምም ኃላፊ ስለሆነ ትተው በመላእክት (በቅዱስ ሩፋኤልና ቅዱስ ዑራኤል) መሪነት ወደ በረሃ (ወደ ምሁር) ወደ አባ ማማስ ቤተ ደናግል ገዳም ተጉዘዋል። በዚያም ማርያም ክብራ በቤተ ደናግል ለ7ት ዓመታት ተጋድላ 3ት አክሊላትን ተቀብላ ጥር 21 ዐርፋ በሁለት አናብስት ማረፊያዋ ተቆፍሮ ሥጋዋ ተቀብሯል። አቡነ ዜና ማርቆስ እንደ ቅዱስ ፊልጶስ ተነጥቀው ግብፅ ከአቡነ ብንያሚን ለሐዋርያዊ አገልግሎት ክህነትን ተቀብለዋል ብዙዎችንም ከጣዖት አምልኮ መልሰው አጥምቀዋል።

ኋላ በመንዝ ከአባ ገብረ ናዝራዊ እጅ መንኩሰው በወግዳ ባለች ዋሻ በተጋድሎ ይኖሩ ሳለ የአጎታችው ልጅ አቡነ ተክለ ሃይማኖት (ወልደ ጸጋ ዘአብ) ወደ ግራርያ እስኪሄዱ ድረስ አብረው በደብረ ብሥራት በተጋድሎ ኖረዋል። ጻድቁ ሰፊ ሐዋርያዊ አገልግሎት የነበራቸው ሲሆን በሸዋ፣ በአዳል (አፋር)፣ በጉራጌ (ምሁርና ከባቢው) አስተምረዋል። የማኅሌተ ጽጌው ደራሲ አባ ጽጌ ድንግል (ጽጌ ብርሃን) ከይሁዲነት ከመለሷቸው ልጆቻቸው መካከል ይጠቀሳሉ። ዝቋላ፣ አክሱም፣ ዋልድባ፣ አድዋ፣ ስሜን ቅዱስ ያሬድ፣ ላሊበላ፣ ይምርሐነ ክርስቶስ፣ ጣና (ጻና)፣ ሐይቅ እስጢፋኖስ እና ጎጃም የረገጧቸው ቦታዎች ናቸው። በነዚህም አንድም ከቅዱሳን በረከት ተቀብለዋል አንድም በሐዋርያዊ አገልግሎት ሺዎችን ከጣዖት አምልኮ መልሰዋል ሰማዕታት እስከመሆን ድረስ የደረሱ ቅዱሳንን በመንፈስ ወልደዋል እሳቸውም ብዙ መከራ ተቀብለዋል።

ጻድቁ አንበሶችና ነብሮች ይከተሏቸው የነበሩ ሰይጣንን የገዘቱ ድንቅ አድራጊ ሲሆኑ እንደጌታችን ለአማንያን እንደሰጠውም ቃል ኪዳን እንጀራ አበርክተዋል ሺዎችን መግበዋል ፀሐይን እንደ ኢያሱ ወልደ ነዌ አቁመዋል እንደ ሙሴ መሬት ታዛቸው ተከፍታ ተጻራሪያቸውን ውጣላቸዋለች እንዲሁም ሙታን ተነሥተውላቸዋል። ጌታችን እመቤታችን ቅዱሳኑ ሁሉ የመንፈስ ልጆቻቸውም በተገኙበት ቃል ኪዳን ተቀብለው በዚህች ቀን (በዕለተ ዐርብ) በ140 ዓመታቸው ዕረፍታቸው ሆኗል።

ጻድቁ በስማቸው ከሚታወቁት ገዳማት መካከል ሥጋቸው ያረፈበት ደብረ ብሥራት በሰሜን ሸዋ በሞረትና ጅሩ ወረዳ በእንጠራ ቀበሌ ከእነዋሪ በስተ ምዕራብ ከ13 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኘው አንዱ ሲሆን ሌላኛው ገዳማቸው [ቀደም ብሎ በ9ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ቢመሠረትም] ምሁር ኢየሱስ (ይምቦል ኢየሱስ) ከአዲስ አበባ በደቡብ ምዕራብ አቅጣጫ 200 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በጉራጌ ዞን ከወልቂጤ ከተማ 55 ኪ.ሜ ርቆ ይገኛል። ከገዳማቶቻቸው ፍሬዎች መካከል በኢየሩሳሌም በአረብኛም በዕብራይስጥም ስለተዋሕዶ ሃይማኖታቸው የተከራከሩት ድልም የነሡት አባ በኃይለ ማርያም ዘደብረ ብሥራት ይጠቀሳሉ። የጻድቁ በረከታቸው ይደርብን።

👉"የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው" ምሳ. 10፥7

 #ዐርብ
12/12/2025

#ዐርብ

👉"በዚህችም ቀን [ታኅሣሥ 3] የሊቀ መላእክት  #ፋኑኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን፤ እኛንም በፋኑኤል አማላጅነት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አ...
12/12/2025

👉"በዚህችም ቀን [ታኅሣሥ 3] የሊቀ መላእክት #ፋኑኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን፤ እኛንም በፋኑኤል አማላጅነት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን።" - ስንክሳር ዘታኅሣሥ 3 ቁጥር 13-14

👉"አራቱ መላእክትን አየሁ። ስማቸውንም አወቅሁ፥ ስማቸውንም የነገረኝ ከኔ ጋራ የመጣ መልአኩ ነው። የተሠወረውንም ሁሉ ገለጠልኝ በክብር ባለቤት ጌታም ፊት ሲያመሰግኑ የነዚያን የአራቱን መላእክት ቃል ሰማሁ አለ። . . . ሰይጣናትን አስወጥቶ ሲሰዳቸው አራተኛውንም ቃል ሰማሁ። በዚህ ዓለም የሚኖሩ ሰዎችን ያጣሏቸው ዘንድ ወደ መላእክት ጌታ እንዲገቡ አይተዋቸውም። . . .ከዚህም በኋላ ከኔ ጋራ የሚኖር ፍቅር አንድነት ያለው መላኩን ጠየቅሁት የተሠወረውንም ሁሉ የገለጠልኝ እሱ ነው። ፊታቸውን ያየሁት ቃላቸውንም የሰማኋቸው እኔም የቆጠርኋቸው እኒህ አራቱ እነማናቸው ብዬ ጠየቅሁት። እሱም፦ . . . አራተኛውም የዘላለም ሕይወት የሚወርሱ ሰዎች ተስፋ ሊሆን ንስሐ በሚገቡ ሰዎች ላይ የተሾመ ፋኑኤል ነው አለኝ።"
- መጽሐፈ ሄኖክ 10፥2-15

👉"ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ ስላላቸው ለማገዝ የሚላኩ የሚያገለግሉም መናፍስት አይደሉምን?" - ዕብ. 1፥14

የሊቀ መላእክት ቅዱስ ፋኑኤል በረከቱ ይደርብን ምልጃው ጥበቃው አይለየን!

👉"ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ፤ ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና።" መዝ. 44 (45)፥10-11 "እንዲሁም መዝሙረኛው ሀቅ ስለሆነ...
12/12/2025

👉"ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ፤ ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና።" መዝ. 44 (45)፥10-11

"እንዲሁም መዝሙረኛው ሀቅ ስለሆነው ከድንግል ሰለመወለዱ ዝም አላለም፥በጭራሽ፤ በዚያው እየጠቀስነው በነበረው በመዝሙር 44 (45) ውስጥ ወዲያው ያሰምርበታል። 'ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ፤ ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና' (ቁ. 10-11)በማለት። ይህ ታዲያ ገብርኤል 'ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው' (ሉቃ. 1፥28) በማለት ከተናገረው ጋር አንድ አይደለምን? መዝሙረኛው እርሱን ቅቡዕ ማለትም መሲሕ ወይም ክርስቶስ ካለ በኋላ (መዝ. 44(45)፥7) 'ልጄ ሆይ፥ ስሚ' በማለት የሥጋ ልደቱን ያውጃል። ልዩነቱ ገብርኤል ማርያምን በቅጽል መጥራቱ ብቻ እንደሆነ እይ፤ ምክንያቱም መልአኩ ከእርሷ በዘር ይለያልና (መልአኩ ሰማያዊ ነውና)። ነገር ግን ዳዊት በተገባ የራሱ ሴት ልጅ (ልጄ) እያለ ይጠራታል ምክንያቱም ከእርሱ ነውና እርሷ የምትገኘው።" - ቅዱስ አትናቴዎስ ዘእስክንድርያ፣ የመዝሙረ ዳዊትን ጥቅምና ትርጓሜ ለዲያቆኑ ለማርሴሊነስ ለማስረዳት በጻፈው ደብዳቤው 6ኛው አንቀጽ

👉"Hearken, O daughter, and consider, and incline thine ear; forget also thine own people, and thy father's house; So shall the king greatly desire thy beauty: for he is thy Lord; and worship thou him." Ps. 45:10-11

"Neither is the Psalmist silent about the fact that He should be born of a virgin - no, he underlines it straight away in 45, which we were quoting, but a moment since. "Harken, O daughter, he says, and see and incline thine ear, and forget thine own people and thy father’s house. For the King has desired thy beauty, and He is thy Lord." Is not this like what Gabriel said, "Hail, thou that art full of grace, the Lord is with thee?" [Lk 1:28] For the Psalmist, having called Him the Anointed One, that is Messiah or Christ, forthwith declares His human birth by saying, "Harken, O daughter", and see; the only difference being that Gabriel addresses Mary by an epithet, because he is of another race from her, while David fitly calls her his own daughter, because it was from him that she should spring." - St. Athanasius, Letter to (Deacon) Marcellinus on the Interpretation of the Psalms, 6th Paragraph

Stop the killing and the cover-up of the massacre of Orthodox Tewahedo Christians in Ethiopia! Between October 24 and No...
12/11/2025

Stop the killing and the cover-up of the massacre of Orthodox Tewahedo Christians in Ethiopia! Between October 24 and November 27, 2025, more than 51 were killed in Oromia (the majority of which were in Arsi)—and thousands more over the past eight years nationwide.

The number of killed in just over 30 days has reached 51 after eleven more Orthodox Christians that were abducted were killed at Mechetu Bebekesa locality of Enqolo Wabe district in Arsi Zone of Oromia Regional State on Thursday, November 27, 2025.

(Image shows Priest Welde Iyesus Ayalew, the Administrator of the Church of Bika Debre Mewi Saint Michael, who was killed on September 26, 2024, with his wife and three sons (among which was a deacon) in Mojo Lume District of East Shewa Zone, Oromia.)

👉"ማርያም ሆይ፥ በእግዚአብሔር ፊት ጸጋ (ባለሟልነትን) አግኝተሻል" ሉቃ. 1፥30👉"አቤቱ፥ በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ እንደ ሆነ . . . እለምናለሁ" ዘፍ. 18፥3👉"የኢየሱስ እናት፦ 'የወይ...
12/10/2025

👉"ማርያም ሆይ፥ በእግዚአብሔር ፊት ጸጋ (ባለሟልነትን) አግኝተሻል" ሉቃ. 1፥30

👉"አቤቱ፥ በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ እንደ ሆነ . . . እለምናለሁ" ዘፍ. 18፥3

👉"የኢየሱስ እናት፦ 'የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም' አለችው።" ዮሐ. 2፥3

👉"Mary: for thou hast found favour with God" Luke 1:30

👉"My Lord, if now I have found favour in thy sight . . . I pray thee" Gen. 18:3

👉"the mother of Jesus saith unto him, They have no wine" John. 2:3

Stop the killing and the cover-up of the massacre of Orthodox Tewahedo Christians in Ethiopia! Between October 24 and No...
12/10/2025

Stop the killing and the cover-up of the massacre of Orthodox Tewahedo Christians in Ethiopia! Between October 24 and November 27, 2025, more than 51 were killed in Oromia (the majority of which were in Arsi)—and thousands more over the past eight years nationwide.

The number of killed in just over 30 days has reached 51 after eleven more Orthodox Christians that were abducted were killed at Mechetu Bebekesa locality of Enqolo Wabe district in Arsi Zone of Oromia Regional State on Thursday, November 27, 2025.

(Image shows Priest Tesfa Alemu, the Administrator of the Church of the Nativity of Christ in Angodecha(e) Locality, killed on June 4, 2025, with Mr. Kifle Gebre Kirstos and Mr. Begashaw Seyum in Jeju District of Arsi Zone, Oromia.)

Address

Lancaster, PA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gishen Media / ግሸን ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share