Gishen Media / ግሸን ሚዲያ

Gishen Media / ግሸን ሚዲያ "ለሃገራችን እንደዜጋ ለቤተ ክርስቲያናችን እንደልጅነታችን እናገለግላለን"

07/10/2025

ዋልድባ አብረንታንት መድኃኔ ዓለም ገዳም ዘቤተ አቡነ ሚናስ ማኅበር

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ -1000064118742 ወይም 1000018796779

ይኽንን ታለቅ ገዳም የቅዱሳን ሥፍራ ከላይ ባለው ባንክ አካውንት ከኢትዮጵያም እንዲሁም ከየትኛውም የዓለም ክፍል ሆናችሁ መደገፍ እና በረከት መቀበል ይገባል።

ለበለጠ መረጃ:-0925060505 / 0954030404

ሙሉ ቪዲዮው እጅግ በጣም ልብን የሚማርክ እጅግ አስተማሪ ነው በኮሜንት መስጫ ሳጥን ላይ ይገኛል👇

ሸር በማድረግ ለምዕመናን እንዲደርስ አግዙ አገልግሉም አደራ🙏

እነርሱ ማርያም አታማልድም ፤አትራዳም ፤ሞታለች ጸሎትም አትሰማም። መታሰቢያዋ ተረስቷል። ክብሯም ከእኛ እንደ አንዳችን ነው ይሉናል። እርሷ ደግሞ እንዲህ በስውር የነገርናትን እንዲህ በግልጥ ...
07/09/2025

እነርሱ ማርያም አታማልድም ፤አትራዳም ፤ሞታለች ጸሎትም አትሰማም። መታሰቢያዋ ተረስቷል። ክብሯም ከእኛ እንደ አንዳችን ነው ይሉናል።

እርሷ ደግሞ እንዲህ በስውር የነገርናትን እንዲህ በግልጥ መልሳልን ክራንች አስጥላ እያዘለለችን ታስገርምናለች። ፍቅር እና ርህራሄዋን የቀመሰ በደንብ ያወራላታል።

ማርያም

ስውሯ ማርያም።

Kune Demelash kassaye -Arba Minch

የዘማሪት አዜብ ከበደ ፌስቡክ አካውንትን በመጥለፍ በስሟም ከተለያዩ ሰዎች ገንዘብ በመጠየቅ ላይ ናቸው እና የተወደዳችሁ የእህታችን ወዳጅ ዘመድ የሆናችሁ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንድታደርጉ ዘማ...
07/09/2025

የዘማሪት አዜብ ከበደ ፌስቡክ አካውንትን በመጥለፍ በስሟም ከተለያዩ ሰዎች ገንዘብ በመጠየቅ ላይ ናቸው እና የተወደዳችሁ የእህታችን ወዳጅ ዘመድ የሆናችሁ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንድታደርጉ ዘማሪት አዜብ ጠይቃለች

ዘማሪት አዜብ ቀና ልብ ያላት ጥሩ አገልጋይ እህቶቻችን እንደሆነች ይታወቃል አገልሎትሽን እግዚአብሔር ይባርክ ..!!

“አቤቱ ድውይ ነኝና ፈውሰኝ” መዝ ፮፥፪በሚል መሪ ቃል ፈውስ መንፈሳዊ ዘጣና ቅዱስ ቂርቆስ በአይነቱ ልዩ የሆነ አጠቃላይ ሆስፒታል ለመገንባት ተነስተናል።   እርሶም ለዚህ ፕሮጀክት ከታች በ...
07/09/2025

“አቤቱ ድውይ ነኝና ፈውሰኝ” መዝ ፮፥፪
በሚል መሪ ቃል
ፈውስ መንፈሳዊ ዘጣና ቅዱስ ቂርቆስ
በአይነቱ ልዩ የሆነ አጠቃላይ ሆስፒታል ለመገንባት ተነስተናል። እርሶም ለዚህ ፕሮጀክት ከታች በተቀመጡት የባንክ አማራጮች አበርክቶ በማድረግ አሻራዎትን ያሳርፉ።

ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአባቶች እና የእናቶች አንድነት ገዳም የአራቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ምሥክር ጉባኤ ቤት

TANA KIDUS KIRKOS YE-ABATOCH ENA YE-ENATOCH ANDNET GEDAM YE-ARATU GUBAYAT METSAHIFT MISKIR GUBAE BET

1000680619488 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
219553568 አቢሲኒያ ባንክ
2011111181981013 አባይ ባንክ
0068829811701 አሐዱ ባንክ
5020827358011 ዳሸን ባንክ

ለበለጠ መረጃ በስልከ ቁጥር
+251 982333444
+251 983333444
+251 984333444 ይደውሉ።

07/09/2025

"የእግዚአብሔር ፈቃዱ ንጹሕ እንድንሆን ነው"
-ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን

"አደራ አለብኝ"ዓለም አቀፍ የግቢ ጉባኤ ምሩቃን ኅብረት ጉባኤመምህር መዝገበ ቃልወር በገባ የመጀመሪያው ረቡዕ በግቢ ጉባኤያት ምሩቃን ዓለም አቀፍ ኅብረት የቴሌግራም ቻናል ሐምሌ 2,2017ዓ...
07/09/2025

"አደራ አለብኝ"
ዓለም አቀፍ የግቢ ጉባኤ ምሩቃን ኅብረት ጉባኤ

መምህር መዝገበ ቃል

ወር በገባ የመጀመሪያው ረቡዕ በግቢ ጉባኤያት ምሩቃን ዓለም አቀፍ ኅብረት የቴሌግራም ቻናል

ሐምሌ 2,2017ዓ.ም
ምሽት ከ2:00 - 3:00

ማኅበረ ቅዱሳን

ቴሌግራም ሊንክ 👇
http//t.me/gibigubayat_mirukan_hibret

በኦርቶዶክሳዊት እምነት ያመኑ 55 ነፍሳት ተጠምቀው ልጅነትን አገኙ ።*** በኧሌ  ዞን  በሚገኘው የጉማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በቃርቃርቴ ስብከተ ኬላ  55  የሌላ ቤተእምነት ሰዎ...
07/08/2025

በኦርቶዶክሳዊት እምነት ያመኑ 55 ነፍሳት ተጠምቀው ልጅነትን አገኙ ።
***

በኧሌ ዞን በሚገኘው የጉማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በቃርቃርቴ ስብከተ ኬላ 55 የሌላ ቤተእምነት ሰዎች አምነው እና ምስጢራትን ተፈጽሞላቸእ የሥላሴ ልጅነትን አግኝተው ኦርቶዶክሳዊ ሆነዋል።

አብ የመረጣቸው ወልድ የወዳደቸው መንፈስቅዱስ ህይወት የሆናቸው 55 ነፍሳት ከአሕዛብነት ወደ ልጅነት መጥተዋል።

እግዚአብሔር ይመስገን !!!

ምንጭ:- Abo media - አቦ ሚዲያ

ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ  #ለመጥምቀ  #መለኮት  #ቅዱስ  #ዮሐንስ  #የሰጠው  #ቃል  #ኪዳን“ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ወዳጄ ዮሐንስ ...
07/07/2025

ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ #ለመጥምቀ #መለኮት #ቅዱስ #ዮሐንስ #የሰጠው #ቃል #ኪዳን

“ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ወዳጄ ዮሐንስ ሆይ የሰጠሁህን ቃል ኪዳን ታምኖ በስምህም ተማፅኖ በቤተ ክርስቲያን በበዓልህ ቀን የጸለየ መታሰቢያህንም ያደረገ በስምህም የለመነ ነፍሱ ከሥጋው በተለየች ጊዜ ባሕረ እሳትን አሻግረዋለሁ መንግሥተ ሰማያትንም ከፍቼ መላእክትም ቢሆኑ ያላዩት ደስታ ያለበት እረፍትም ያለበት ሥፍራን አወርሰዋለሁ። የብርሃን ልብስን አለብሰዋለሁ የብርሃን ዘውድም አቀዳጀዋለሁ። እስከ ሃምሳ አምስት ትውልድ ድረስ እምርለታለሁ።

በስምህም የተራበን ያበላ የተጠማንም ያጠጣውን እኔ ከሕይወት ምግብ አጠግበዋለሁ ከኤዶም ገነት ከሚፈስ ከማርና ከስኳር ይልቅ የሚጣፍጥ ከወተትም የነጣ የሕይወት መጠጥን አጠጣዋለሁ። በስምህ ለድሆች ከሚበላው ከሚጠጣው ከፍሎ ስላጠጣም በምግባር በሃይማኖት ጸንቶ ቅዱስ ሥጋዬን ክቡር ደሜን ይቀበል ዘንድ አዘጋጀዋለሁ። ማደሪያዬ ቤተ ክርስቲያንንም በስምህ ያነጸውን እኔ በመንግሥተ ሰማያት ሰባ ሰባት አዳራሽን አንጽለታለሁ እስከ ሃምሳ አምስት ትውልደ ዘርኡ ድረስ እምርለታለሁ።

ወደመንፈሳዊ ወደሥጋዊ ግብሩ ሲያልፍ ቤተ ክርስቲያንህም ቢሆን ደጃፉንም ቢሆን የተሳለመውን ሰው እኔ ወደ ዙፋኔ አቀርበዋለሁ። በክብርም ከፍ ከፍ አደርገዋለሁ። በቤተ ክርስቲያንህ የተቀበረውንም በኢየሩሳሌም መቃብሬ እንደተቀበረ አደርግለታለሁ። ዓይን ያላየውን ጆሮ ያልሰማውን በሰው ያልታሰበውን ጸጋና ክብርም እሰጠዋለሁ እስከ ሃምሳ አምስት ትውልድ ድረስም እምርለታለሁ።

ማደሪያዬ የሚሆን ቤተ ክርስቲያንህ በስምህ በታነጸበት ስምህ በተጠራበት መታሰቢያህ በተደረገበት የተአምርህ ዜና በሚነገርበት ገድልህም በሚተረጎምበት እኔ በዚያ እኖራለሁ። ገድልህና ተአምርህ በሚነገርበት በዚያም ርኩሳን መናፍስት ይርቁ ዘንድ እልፍ አዕላፍ መላእክትን አዛለሁ አጋንንትንም እስከሰማኒያ ቀን ጎዳና አርቃቸዋለሁ። ከሩቅም ከቅርብም ወደ ቤተ ክርስቲያንህ የመጡትንም ወደ ቅድስት ኢየሩሳሌም መቃብሬ እንዲሄዱ አደርጋቸዋለሁ። ክብርንም አበዛላቸዋለሁ። ትውልዳቸውንም እስከ ሃምሳ አምስት ድረስ እምርላቸዋለሁ።

ወደ ቤተ ክርስቲያንህ ይሔድ ዘንድ ወዶ በበሽታም ቢሆን በእርጅናም ቢሆን የቀረውንም ከደጅህ ደርሶ እንደተሳለመ አደርግለታለሁ ክብሩንም ከተሳለሙት ጋር አደርጋለሁ። በዕለተ በዓልህም በእግሩ እያሸበሸበ በእጁም እያጨበጨበ በጽናጽል በከበሮ የሚያገለግለውንም እኔ ከጣእሙ ብዛት የተነሳ አጥንትን የሚያለመልም ምስጋናን አሰማዋለሁ። ስለስምህ በሽተኛን የጎበኘ ያዘነውን ያረጋጋ በአገልጋዮቼ በቅዱሳን አጠገብ አሳርፈዋለሁ። መጽሐፈ ገድልህንም የጻፈ ያጻፈ የሰማ ያነበበ የተረጎመ ያስተረጎመውን የተሳለመውንም ሁሉ እኔ ስሙን በሕይወት መጽሐፍ እጽፋለሁ ትውልዱንም እስከ ሃምሳ አምስት ትውልድ ድረስ እምርለታለሁ።

ዕጣንና ዘቢብ ቅብዐ ሜሮንና መብራትን ንጹሕ ስንዴን የክህነት ልብስን መጎናጸፊያና መጋረጃን የሚሰጥ በበዓልህም ለምለም ሳርን በየወሩና በየዓመቱ በተወለድህበትም በወርኃ ሰኔ ሠላሳ ሰማዕትነትን በፈጸምህበት በወርኃ መስከረም ሁለት ቀን የከበረ ጸሎቱን እሰማዋለሁ ኃጢአቱንም ይቅር እለዋለሁ። እስከ ሃምሳ አምስት ድረስም ትውልዱን እምረዋለሁ።

ንዑድ ክቡር የሚሆን ሰማይና ምድርን በፈጠረ በፈጣሪው በእግዚአብሔር ዘንድም ክብሩ የላቀ ገባሬ ተአምር መጥምቅ ቅዱስ ዮሐንስ ይህን ሁሉ ቃል ኪዳን ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ በሰማ ጊዜ እጅግ ተደሰተ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ከቸር አባትህ ከማኅየዊ መንፈስ ቅዱስ ጋርም በአንድነት ለአንተ ምስጋና ይገባል ይህን ሁሉ የክብር ቃል ኪዳንን ሰጥተኸኛልና ብሎ ወድቆ ሰገደ።

ዳግመኛም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወዳጁ መጥምቅ ዮሐንስን ወዳጄ ዮሐንስ ሆይ እነግርህ ዘንድ ስማ ቤተ ክርስቲያንህ በታነጸበት ስምህም በተጠራበት መታሰቢያህም በተደረገበት ሥፍራ ሁሉ ረኃብና ጥም አባርና ቸነፈር የእንስሳ ሞት የሰው መቅሠፍት አይደርስም በዚያች ሀገር ፍጹም ተድላ ደስታ ይሆናል እንጂ። ልጅ ባይኖረው መካን ቢሆን የሃምሳ አምስት ትውልዱን ክብር ጨምሬ ለእርሱ እሰጣለሁ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንህ የታነጸችበትን ሥፍራም መንበረ መንግስቴ እንደተዘረጋባት ጽርሐ አርያም አደርጋታለሁ።”

ምንጭ ፦
የሐምሌ ገድለ ዮሐንስ መጥምቅ፤ ቁጥር 4 – 11፤ ገጽ 80 – 83፤ 1996 ዓ.ም

07/07/2025

"ዮሐንስ ማለት ፍስሓ ወሐሴት ፍቅር ወሰላም
ማለት ነው"

“ወብዙኃን ይትፌሥሑ በልደቱ፤ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል” (ሉቃ. ፩፥፲፬)

-ዲያቆን ዮርዳኖስ አበበ

07/06/2025

ምስጋና ይገባሃል ..!

07/04/2025

በ 90 ቀናት የሚተገበሩ ተግባራት
-በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን

እንዲህ አይነት ተግባራት ለቤተ ክርስቲያናችን እጅግ አስፈላጊ ናቸው በዚህ ፕሮጀክት እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እምችለውን አደርጋለሁ እናንተስ ?

የፈውስ መንፈሳዊ ዩቲዩብ ቻናል ሊንክ በኮመንት መስጫ ሳጥን ላይ ይገኛል ሰብስክራይብ በማድረግ ጉባኤ ቤቱን እንደግፍ ..!

Address

256 Kentshire Drive
Lancaster, PA
17603

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gishen Media / ግሸን ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share