10/23/2025
ለአቡነ አረጋዊ የተሰጣቸው ቃል ኪዳን (በአማርኛና በልሳነ እንግሊዝ)
👉"ለሚያምን ሁሉ ይቻላል" ማር. 9፥23
"ጌታችን በመንፈቀ ሌሊት ተገልጾ ቃል ኪዳን ሰጠው ዳግመኛም ጸሎትህ እነሆ በኔ ዘንድ ደርሶ ተሰምቷል።
ስለዚህም ከድካም ወደዕረፍት ከኀዘን ደስታ ወዳለበት ከኃሣር ወደክብር በታላቅ ደስታ እወስድህ ዘንድ ወደአንተ መጥቻለሁ አለው።
የዚህን የሀላፊውን ዓለም ክብር ስለናቅህ በመንግስተ ሰማያት የማያልፈውን የማይጠፋውን ክብር አቀዳጅሃለሁ።
በዚህ ዓለም የሐሩን ልብስ የወርቅና የብሩን ጌጥ እንደናቅህ እኔ አይን ያላየውን ጆሮ ያልሰማውን በሰው ልቡና ያልታሰበውን አለብስሃለሁ አስጌጥሃለሁ።
ከትውልድ ሀገርህ ወጥተህ በባዕድ አገር ስለኖርክ እኔ ሰማያዊት ኢየሩሳሌምን እሰጥሃለሁ የሚያልፉ የሚፈርሱ የዚህን ዓለም ቤት ንብረት ስለናቅህ የማይፈርስ የማያልፍ የሕይወት ቤት እኔ እሰጥሃለሁ።
መታሰቢያህን ያደረገ በጸሎትህም የተማመነውን ሁሉ እኔ በመላእክት ፊት ሞገስን ባለሟልነትን እሰጠዋለሁ።
በእውነተኛ ሃይማኖት ሁኖ የገድልህን መጽሐፍ የጻፈ ያጻፈ የተረጎመ እኔ ስሙን በሕይወት መጽሐፍ እጽፈዋለሁ።
መታሰቢያህ በሚደረግበት ዕለት የራበውን ያጠገበ የጠማውን ያጠጣ እኔ የሕይወት እንጀራ አበላዋለሁ የሕይወት ጽዋም አጠጣዋለሁ።
በዓልህ በሚከበርበት ዕለት ለራበው ምሳውን ያበላ እኔ በምሳሐ ደብረ ጽዮን የምሳ ግብዣ አደርግለታለሁ።
በስምህ በተሠራው ቤተ መቅደስ ውስጥ የጸለየ የለመነ ፈጥኜ ጸሎቱን እሰማዋለሁ ልመናውንም እቀበለዋለሁ ቤተ ክርስቲያንህንም ለሠራ ዐሥራ ሁለት የብርሃን አዳራሽ አዘጋጅለታለሁ።
የገድልህን መጽሐፍ በመታመን በንጽሕና አድርጎ በቤቱ ያስቀመጠ ወረርሽኝ በሽታ ወይም ቸነፈር በቤቱ አይገባም ድንገተኛም የሰውና የእንስሳ ሞት አይደርስበትም የእህል ችግርም አይኖርበትም።
በጥቡዕ ልብ ሆኖ የገድልህን መጽሐፍ የሰማ ያለስንፍና በፍጹም መታመን የንባቡን ኃይለ ቃል የሰማ እኔ ለችግሩ ሁሉ ፈጥኜ እደርስለታለሁ።
ለቤተ ክርስቲያንህ መባ ያገባ ዕጣን ወይም ቅብዓ ሜሮን ወይም ዘይት የሰጠ እኔ በሰማያዊት መንግሥቴ አስገባዋለሁ።
ንጉሥም ቢሆን ለቤተ ክርስቲያንህ የሐር መጎናጸፊያ ቢሰጥ በዓልህ በሚከበርበት ዕለት ቢያከብር እኔ በመንግሥቴ አከብረዋለሁ በጠላቱም ላይ ድልን አቀዳጀዋለሁ ከመኳንንቱ ከመሳፍንቱ ጋር ሰላምን እሰጠዋለሁ በምድርም ላይ ዘመኑን ወይም ዕድሜውን አረዝምለታለሁ።
ከሁሉም ይልቅ የሞት ጥላ አያርፍብህም መልአከ ሞትም ሊያስደነግፅህ አይችልም እንደ ነቢያቶቼ ኤልያስና ሄኖክ ትሠወራለህ እንጂ።
በቡሩካን እጆችህ የቀበርካት እናትህ ዕድናንም በትንሣኤ ሕይወት እስካስነሣት ድረስ መቃብሯን አፍርሶ ሌላ ሰው እንዳይቀበርበት ወይም ለማንም እንዳይታይ እንደ እንበረም ልጅ እንደሙሴ መቃብር ይሰወራል።
ይህቺን ቤተ መቅደስህንም ታላቅና የተከበረች አደርጋታለሁ የበቁ የደጋግ ነገሥታትና ጳጳሳት የመቃብራቸው ወይም የማረፊያቸው ቦታ ትሆናለች።
ጌታችንም ይህን ቃል ኪዳን በሰጠው ጊዜ ክቡር አባታችን አቡነ አረጋዊ ጌታችንን አቤቱ በፊትህ ሞገስ አግኝቼስ ከሆነ እናገር ዘንድ ይፈቀድልኝ አለው።
ጌታም ወዳጄ አረጋዊ ሆይ ፈቅጄልሃለሁ ተናገር ከኔ የምትፈልገውንም ሁሉ ጠይቅ ወይም ለምን አለው።
ከዚያም አባታችን አቡነ አረጋዊ ይህን ሁሉ ለሰጠኸኝ እስከ ዘላለሙ ድረስ ስምህ የተመሰገነ የጌትነትህም ክብር የተባረከ ነው ብሎ አመሰገነ።
አሁንም ጌታ ሆይ መታሰቢያየን ያደረገ የገድሌን መጽሐፍ የጻፈ በጸሎቴ የተማመነ እስከ ስንት ትውልድ ድረስ ትምርልኛለህ አለው።
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እስከ ዐሥራ አምስት ትውልድ ድረስ እምርልሃለሁ አለው።
አባታችን አቡነ አረጋዊም አቤቱ ይህች ቦታ የነገሥታት የጳጳሳት የክቡራን መኳንንትና መሳፍንት ብቻ መቀበሪያ ሁና አትቅር ነገር ግን ለተገፉ ለነዳያን አባት እናት ለሞቱባቸው ለዕውራንና ለሐንካሳን መጠጊያ ትሆን ዘንድ ማንኛውም ግለሰብ ይቀበርባት እንጂ እኔ በዚች አገር እንግዳና ስደተኛ ነኝና አለው።
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም የተመሰገንህ አረጋዊ እንደ ቃልህ ይደረግልህ አለው።
አባታችን አቡነ አረጋዊም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አቤቱ ከሩቅ ወይም ከቅርብ መጥተው ንስሐ ሳይገቡና በድንገተኛ ሞተው በዚች በአፀደ ቤተ ክርስቲያኔ የተቀበሩትን ሁሉ ኃጢአታቸውን ይቅር በላቸው አለ።
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እንኳንስ በተራራው ጫፍ ላይ የተቀበረ ይቅርና ከተራራው ሥር እንኳ ቢሆን ይልቁንም በስምህ የተሰየመ ቤተ ክርስቲያን ሁሉ በዚያ የተቀበረው ኃጢአቱ ይሠረይለታል እነዚህንም ሁሉ ዓሥራት አድርጌ ሰጠሁህ አለው።
አባታችን አቡነ አረጋዊም አቤቱ ይህችን ቤተ መቅደስና በውስጡዋም የሚኖሩትን ባርክ አለው።
መድኃኒታችንም ይህች ቤተ መቅደስህ የተባረከች የተቀደሰች ትሁን በውስጧም ሰው አይታጣ መብራቷ አይጥፋ ሥጋዬና ደሜ በውስጧ በተዘጋጀ ጊዜ ልምላሜ ሙቀት ያልተለየው የሠመረ በፊቴም ተቀባይነት ያለው ይሁን አለው።
አባታችን አቡነ አረጋዊም መልሶ አቤቱ ይህችን መንፈሳዊ ማኅበር ልጆቼንና ቅዱሳኖቼንም ሁሉ ባርክ አለው።
ይህች ማኅበር የተባረከች ትሁን የችግረኞች መጠጊያ የተራቡ የሚጠግቡባት የታረዙ የሚለብሱባት ወይም ለተራቡት ምግብ ለተራቆቱት ልብስ ትሁን አለው።
እሊህ ቅዱሳን ልጆችህም እልፍ አእላፋት ይሁኑ እንደባህር አሸዋ እንደሰማይ ከዋክብትም ትውልዱ ነገዱ እንደተስፋፋ ዘሩም እንደበዛ እንደ ያዕቆብ ልጆች የበዙ ይሁኑ።
ድንገተኛ በሽታ መቅሠፍት ሰውነትን የሚያዝግ የሚያጠወልግ ሕማም ወደነሱ አይቀርብም።
አባታችን አቡነ አረጋዊ አቤቱ ይህችን የማድርባትን በአቴንና ከአንተም ጋር ቆሜ ቃል ኪዳን የተቀበልኩባትን ቦታ ባርክ።
ይልቁንም ይህቺ እግርህ ከቆመባት መሬት አፈሯን ወስደው በመቀባት መድኃኒት ትሆናቸውና ወይም ከሕመማቸው ይፈወሱ ዘንድ ባርካት አክብራትም።
ሕመም ያለበት ቢኖር ፈጥኖ ይወገድለት በፍጹም መታመን በአንገቱ ላይ እምነቱን ቢአሥር ከክፉ ደዌ ከሚያንቀጠቅጥ ወይም ከሚያንዘፈዝፍ በሽታ ይድን ዘንድ መሬቱን ወይም እምነቱን በተቀባ ጊዜ በሱ ላይ ድንቅ ድንቅ ተአምር ተፈጽሞ ከሕመሙ ነፃ ይሆን ዘንድ ፈቃድህ ይሁን በማለት አባታችን አቡነ አረጋዊ ለመነ።
ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ይሁን ይደረግልህ በማለት በማይታበል ቃሉ ቃል ኪዳን ገባለት።"
+++አሜን+++
ምንጭ፦
ገድለ አቡነ አረጋዊ፤ ዘሰኔ፤ ምዕራፍ 2፤ ከቁጥር 1 – 36፤ 1978 ዓ.ም
👉"ኢየሱስ፦ እስክመጣ ድረስ ይኖር ዘንድ ብወድስ ምን አግዶህ? አለው" ዮሐ. 21፥23
👉"ያመኑትንም እነዚህ ምልክቶች ይከተሉአቸዋል፤ በስሜ አጋንንትን ያወጣሉ፤ በአዲስ ቋንቋ ይናገራሉ፤ እባቦችን ይይዛሉ። የሚገድልም ነገር ቢጠጡ አይጎዳቸውም፤ እጃቸውን በድውዮች ላይ ይጭናሉ እነርሱም ይድናሉ።" ማር. 16፥17-18
👉"በእባብ ላይ ትጫማለህ" መዝ. 90 (91)፥13
👉"የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው" ምሳ. 10፥7
👉"ጻድቃንንም የሚጠሉ ይጸጸታሉ" መዝ. 33 (34)፥21
👉" እግዚአብሔር ጻድቃንን ይወድዳል" መዝ. 145(146)፥8
👉"አምላክህ እግዚአብሔር እርሱ አምላክ እንደ ሆነ፥ ለሚወድዱትም ትእዛዙንም ለሚጠብቁ ቃል ኪዳኑንና ምሕረቱን እስከ ሺህ ትውልድ ድረስ የሚጠብቅ የታመነ አምላክ እንደ ሆነ እወቅ" ዘዳ. 7፥9
👉"የጻድቃንን ማደሪያቸውንና የቅዱሳንን ማረፊያቸውን አየሁ። በዚያም ዐይኖቼ ከመላእክት ጋራ ማደሪያቸውን፥ ከቅዱሳንም ጋር ማረፊያቸውን አዩ። ስለ ሰው ልጆች ይለምናሉ፥ ይማልዳሉ፥ ይጸልያሉም።" መጽሐፈ ሄኖክ 9፥21-23
- - - - - - - - - - - - - - - - - - - - - - - -
The Covenant Given unto Abune Aregawi:
👉"all things are possible to him that believeth" Mark 9:23
Our Lord appeared unto him at midnight and bestowed upon him a covenant, saying:
“Thy prayer hath ascended unto Me, and I have hearkened unto thy supplication.
Wherefore am I come to take thee from weariness unto rest, from sorrow unto joy, and from affliction unto honor and exceeding gladness.
Because thou hast forsaken the glory of this temporal and fleeting world, I shall endue thee with honor that fadeth not, nor is momentary, in My heavenly kingdom.
Forasmuch as thou hast renounced raiment of silk, and jewels of gold and silver, I shall clothe and adorn thee with that which eye hath not seen, nor ear heard, neither hath it entered into the heart of man.
Because thou hast left the land of thy nativity and sojourned in a strange country, I shall give unto thee the Heavenly Jerusalem. And because thou hast forsaken thine house and the treasures of this passing world, I shall grant unto thee a habitation of life, incorruptible and imperishable.
Whosoever shall commemorate thee, and believe in thine intercession, I shall grant him favor before Mine angels, and give unto him ministry.
The name of him that writeth thy hagiography or account in true faith, or causeth it to be written, or translateth it, shall I inscribe in the Book of Life.
He that feedeth the hungry or giveth drink unto the thirsty upon thy feast day shall partake of the Bread of Life and drink from the Chalice of Life.
I shall prepare a banquet upon Mount Zion for him that feedeth the poor upon thy feast day.
Whoso prayeth in the church builded in thy name, I shall hear him speedily and accept his supplication. And for him that buildeth thy church, I shall prepare twelve halls of light.
Whoso keepeth thy sacred history in his dwelling faithfully and reverently, no sickness nor pestilence shall enter therein; neither sudden death of man nor beast shall befall him, neither shall his fruits fail.
He that hearkeneth diligently unto thy acts and unto the verses of the readings with faith, I shall be swift to deliver him from all his troubles.
If any offer unto thy church oblations, incense, myrrh, or oil, I shall cause him to enter into My heavenly kingdom.
If a king bestow vestments upon thy church and celebrateth thy feast, I shall honor him in My kingdom, give him victory over his enemies, grant him peace with princes and captains, and prolong his days upon the earth.
Above all, thou shalt not be touched by the shadow of death; neither shall the angel of death affright thee. For thou shalt be taken up, and hidden, even as My prophets Elias and Enoch.
And until the Resurrection of the Dead, thy mother Edna, whom thou didst bury with thine holy hands, her sepulchre shall not be destroyed that another may be laid therein, but shall be hidden, even as the tomb of Moses, son of Amram.
And I shall make thy church exalted and much honored; it shall become the resting place of righteous and perfect emperors and bishops.’
When our Lord had delivered unto him this covenant, our venerable father Abune Aregawi besought Him, saying,
‘O Lord, if I have found grace in Thy sight, suffer me to speak before Thee.’
And the Lord said unto him,
‘My beloved Aregawi, I have granted thee license. Speak; ask all that thou desirest of Me, and make thy supplication.’
Then our father gave thanks, saying,
‘Blessed be Thy name, O Lord, who hast granted me all things for ever; and blessed be the glory of Thy dominion.’
And he continued, saying,
‘And now, O Lord, how many generations of him that keepeth my feast, writeth my history, and believeth in mine intercession wilt Thou forgive?’
And our Savior Jesus Christ answered and said,
‘For thy sake will I pardon fifteen generations of his seed.’
Then said our father,
‘O Lord, forasmuch as I was a stranger in this land, let not this place be only the resting of emperors, bishops, nobles, and rulers; but let it be a refuge for the poor and outcast, for orphans, the blind, and the maimed — yea, a sepulchre for all.’
And the Lord answered him,
‘Blessed Aregawi, even as thou hast spoken, so shall it be unto thee.’
Then our father Abune Aregawi said unto our Savior Jesus Christ,
‘O Lord, forgive all those who, unrepentant, come from far and near, die suddenly, and are buried within my church.’
And our Savior answered,
‘Not only those buried upon the mountain, but even they that rest at the foot thereof, yea, all that are buried in churches raised in thy name — their sins are forgiven. I have made them all thy portion and thine inheritance.’
And our father besought Him again, saying,
‘Bless, O Lord, all that abide within the church or monastery and dwell therein.’
And our Savior replied,
‘Let thy church and monastery be blessed and hallowed. Let it never be without inhabitants, neither let its light be extinguished. When My Body and Blood are offered within it, let it be acceptable and well-pleasing before Me.’
Then said our father,
‘Bless, O Lord, this spiritual assembly of my children and of all my holy ones.’
And the Lord said,
‘Blessed be this congregation. Let it be a refuge for the destitute, a place where the hungry are filled, the thirsty refreshed, and the naked clothed.
Let thy holy children be multiplied — thousands upon thousands — even as the sand of the sea and the stars of heaven, as was Jacob whose seed became exceeding many.
Neither let sudden sickness, nor pestilence, nor the wasting disease draw nigh unto them.’
Then our father Abune Aregawi entreated Him, saying,
‘O Lord, bless this my cell, and this place wherein I have received Thy covenant. Grant that it may become a spiritual medicine unto all that take of the earth whereon Thou standest, that they may be healed miraculously. Bless it, and glorify it.’
‘If any be sick, let his malady be swiftly taken away. Let it be Thy will that if he bindeth upon his neck the holy earth, let him be delivered from grievous disease, trembling, and palsy; and if he anoint himself therewith, let great wonders of healing be wrought upon him.’
And our Lord, God, and Savior Jesus Christ made covenant with him, saying,
‘So be it, even as thou hast spoken.’”
+++Amen+++
Source:
Hagiography of Abune Aregawi, Reading of Senne, Chapter 2, no. 1-36, 1978 Ethiopian Calendar (Geez-Amharic)
👉"If I will that he tarry till I come, what is that to thee?" John 21:23
👉"And these signs shall follow them that believe; In my name shall they cast out devils; they shall speak with new tongues; They shall take up serpents; and if they drink any deadly thing, it shall not hurt them; they shall lay hands on the sick, and they shall recover." Mark 16:17
👉"Thou shalt tread upon . . . adder" Ps. 91:13
👉"The memory of the just is blessed" Prov. 10:7
👉"they that hate the righteous shall be desolate" Ps. 34:21
👉"the Lord loveth the righteous" Ps. 145:8
👉"Know therefore that the Lord thy God, he is God, the faithful God, which keepeth covenant and mercy with them that love him and keep his commandments to a thousand generations" Deut. 7:9
👉"I saw the dwelling place of the righteous and the resting place of the saints. There, my eyes beheld their dwelling with the angels and their resting place with the saints. They entreat for the children of men, they intercede for them, and they pray for them." Enoch 9:21-23