01/11/2024
የዛሬ ወር አከባቢ ዶ/ር ማሙሻ ፋንታ ጂም ስፖርት እየሰራ ተዝለፍልፎ ወደቀ የሚል ወሬ ሰምቼ ነበረ።ህመሙ ከልብ ጋር የተገናኘና ትንሽ ከበድ ያለ ስለሆነ ወሬውን የሰማ ሰው እግዚአብሔር እንዲፈውሰው ለወንድማችን እየፀለየለት ነበረ።
እግዚአብሔር ይመስገን ወንድም ማሙሻ አሁን ላይ ወደ ቀድሞ ጤንነቱን በመመለሱ የተነሳ የፊታችን ቅዳሜ ጥር 4 የምስጋና ፕሮግራም አዝጋጅቷል።የምትችሉ እግዚአብሔርን አንድ ላይ እናመስግን ስለ አለ በእለቱ ተገኝታችሁ ደስታውን ተካፈሉለት።ወንድማችን ማሙሻ የምታመልከው አምላክ እንኳን አዳነክ።በቀሪ ዘመንህ ጌታ ኢየሱስ ረጅም እድሜና ጤና ይስጥህ።