Ethio Beteseb Media

Ethio Beteseb Media ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ መንፈሳዊ እና ማኅበራዊ እንዲሁም ወቅታዊ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መረጃን የሚያደርስ ሚዲያ ነው ።
501(c)(3) Registered
(2)

✏  "ታቦተ ጽዮን" ሕዳር ጽዮን  √"ወቀጥቀጠቶ ለዳጎን ነፍሳተ ብዙኃን ማህጎሊ፣ የብዙዎችን ነፍሳት ያጠፋ ዳጎንን ሰባበረችው" ፡፡👉ታላቁ ኢትዮጵያዊው ሊቅ አባ ጽጌ ድንግል ሰቆቃወ ድንግል ...
11/29/2025

✏ "ታቦተ ጽዮን" ሕዳር ጽዮን

√"ወቀጥቀጠቶ ለዳጎን ነፍሳተ ብዙኃን ማህጎሊ፣
የብዙዎችን ነፍሳት ያጠፋ ዳጎንን ሰባበረችው" ፡፡

👉ታላቁ ኢትዮጵያዊው ሊቅ አባ ጽጌ ድንግል ሰቆቃወ ድንግል በተባለው ድርሰቱ ፦

👉ፍህም የተሸከመች የወርቅ ማዕጠንት🙏

√ድንግል ሆይ ቡሩክ ከቤተ መቅደስ ይዞሽ የወጣ እሳትነት ያለውን ፍህም የተሸከምሽ የወርቅ ማዕጠንት አንቺ ነሽ ። ፍህም የተባለውም ኃጢአትን የሚያስተሠርይና በደልን የሚደመስስ ነው፤ ይኸውም ካንቺ ሰው የሆነና ራሱን የተወደደ መስዋዕት አድርጎ ያሳረገ የእግዚአብሔር ቃል ነው ።√ (ቅዱስ ኤፍሬም)

👉እንኳን ለጽዮን ማርያም የተዋሕዶ ልጆች በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን 🙏

📍ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ

📝የዛሬው ልዩ ዝግጅት እኔ እና መምህር ሱራፌል ወንድሙ ቆይታ እናደርጋለን ፦👉ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ የተከፈተው የውስጥም የውጭም ዘመቻ ፣ ተባባሪዎቹ እነማን ናቸው ?...
11/28/2025

📝የዛሬው ልዩ ዝግጅት እኔ እና መምህር ሱራፌል ወንድሙ ቆይታ እናደርጋለን ፦

👉ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ የተከፈተው የውስጥም የውጭም ዘመቻ ፣ ተባባሪዎቹ እነማን ናቸው ?

👉ጳጳሳቱ ምን እያደረጉ ነው ?

👉በዘር በተሾሙት ጳጳስ እንዲነገር የተፈለገው ምንድን ነው ?
👉አሁን ቤተክርስቲያንን እየመራ ያለው ማን ነው ?

👉በታቦቱ ፊት የታየዉ ድፍረት ፣ ምን ታስቦ ነው ?

👉ዛሬም በአርሲ ኦርቶዶክሳውያን እየተገደሉ ነው ?

ብዙ ነገሮችን እናነሳለን አብራችሁን ቆዩ

📍ሼር ላይክ በማድረግ ለሌሎች እናድርስ

በታቦቱ ፊት የታየዉ ድፍረት // የጳጳሱ ማን አለብኝነት // የዘር ሹመት፣ በኑፉቄ ድፍረት # Ethiobetesebmedia

11/26/2025

ይህ እንዴት ይቻላል ? //
ከአሜሪካ ጉዞ ወደ ገዳም //
የገዳሙ በረከት ምን ይዞ መጣ ? //
ወጣቱ ከዚህ ምን ይማራል ?

📝ነገረ ዳንኤል 👉ያሁሉ ኦርቶዶክሳውያን የግፍ ግድያ  በአርሲ በኦሮምያ  ሲፈጸምበት ፣ እጁን አፉ ላይ የጫነው ዳንኤል ፣ ዛሬ ደግሞ በዚህ መልክ ተገልጧል ፣ 👉ዳንኤል ግን  ምን ሆኖ ነው የ...
11/26/2025

📝ነገረ ዳንኤል

👉ያሁሉ ኦርቶዶክሳውያን የግፍ ግድያ በአርሲ በኦሮምያ ሲፈጸምበት ፣ እጁን አፉ ላይ የጫነው ዳንኤል ፣ ዛሬ ደግሞ በዚህ መልክ ተገልጧል ፣

👉ዳንኤል ግን ምን ሆኖ ነው የሚል አይጠፋው ፣ ነገሩ ፓለቲካ እና ገንዘብ ቤት ሰርተው ነው ፣ ዕድሜ የሰጠው ገና ብዙ ያያል ፣

👉 እኛ ግን አጀንዳችን ዛሬም እየተገደሉ ስላሉ ፣ ስለሚታገቱት ንፁሀን ፣ በሀገራቸው እንደሁለተኛ ዜጋ የተቆጠሩ ኦርቶዶክሳውያን አሁንም የሰው ያለ ድረሱልን ይላሉ ፣ ድምፃችንን እናሰማ ፣ ወገን ።

👉መንግስት ወንጀለኛ ብሎ የያዘውን በሕግ ፣ የመቅጣት ባለ ሙሉ መብት ነው ። በሳላ ቢላዋ አንገት እየቀላ ያለውን የመንግስት ክንፍ አንዳች ሳይሉ፣ በእጃችን በገባ ምርኮኛ ፣ ቪዲዬ ይዘናል ፣ ገና እንለቃለን እያሉ ግፍን መሸፈን እና ማድበስበስ ለሰው ይቻል ይሆናል ፣ ለምናምነው ጌታ ግን
ነገሩ ግልጥ ነው ።

👉 ነገሩ ግልጽ ነው ፣ እንዲህ አይነቱ አሰቃቂ ተግባር ነውር ጌጡ በሆኑ ፣ በማናቸውም ቡዱኖች እና ግለሰቦች ሲፈጸሙ እየታዩ ያሉት ዛሬ የተጀመረ አይደለም ፣ አሁን ትውልዱ ብዙ አሰቃቂ ድርጊቶችን በማየት ልቡ ደንድኗል ፣ ድርጊቱ ግን በማንኛውም ሁኔታ ፣ ማንም ይፈጽመው ማንም ❗ ይህን የአውሬነት ተግባር በጽኑ ሊዉገዝ ይገባል ።

📌መርጦ አልቃሽ ከመሆን ሁላችንንም ይሰውረን 🙏

📍ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ

📝የፋኖ ደጋፊ ተብለው ከቤተክርስቲያን ተባረሩ 👉የኔታ ተስፋ ማርያም ይባላሉ  አራት አይና ሊቅ የጎንደር ፊት ሚካኤል ከሰላሳ  ሁለት አመት  በላይ ያገለገሉ ፣ በርካታ ሊቃውንትን ያፈሩ ታላቅ...
11/26/2025

📝የፋኖ ደጋፊ ተብለው ከቤተክርስቲያን ተባረሩ

👉የኔታ ተስፋ ማርያም ይባላሉ አራት አይና ሊቅ የጎንደር ፊት ሚካኤል ከሰላሳ ሁለት አመት በላይ ያገለገሉ ፣ በርካታ ሊቃውንትን ያፈሩ ታላቅ አባት ናቸው።

👉 የድጓም መህምር፣ የሐድስ ኪዳን ፣ ትርጓሜ መህምር ናቸው ባህታዊ ሥጋ ባፋቸው ገብቶ አያውቅም መጠጥ ምን እንደሆነ አያውቁም የሚኖሩት መቃብር ቤት ነው

👉የቤተ ክርስቲያኑ መምህር እና አስተዳዳሪ ናቸው ፣ መነኩሴ ሆነው አንድ ቀን እንኳን እንደ መነኩሴ ቀሚስ ለብሰው ቆብ አጥልቀው ለሰው አይታዩም፦

👉 በሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ለሰው ልጅ በህይዎታቸው የሚያስተምሩ የሕይወት መምህር ጭምር ናቸው ፦

👉ታዲያ የማይከላዊ ጎንደር ሊቀ ጳጳስ አቡነ ዮሐንስ በውጭው ሲኖዶስ በአቡነ መርቆሬዎስ የተሾሙ ፣ሥራ አስኪያጃቸው አባ ዮሴፍ የብልጽግና የቁም ተጠሪ እና ካድሬ እንደሆኑ የመረጃ ምንጮቻችን ይናገራሉ ፣ ሊቀ ጳጳሱም ጉዳዩን በጥልቀት ሳይመረምሩ ፣ ከሥራ አስኪያጁ ጋር በመሆን ከቤተክርስቲያን እንዲወጡ የተደረገ ሲሆን ምክንያቱ ደግሞ፦

👉 የፋኖ ደገፊ ፣ ቤተክርስቲያኑን የፋኖ አደረጉ ተብለው ከቤተ ክርስቲያን በሰባት (7) ፖሊስ ተባረው በአሁኑ ጊዜ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጊቢ እንዳይገቡ ተደርገው አቤቱታ እንዳያቀርቡ በስቃይ በችግር ውስጥ እንደሚገኙ የመረጃ ምንጮቻችን መረጃውን አድርሰውናል ፦

🙏 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሊቃውንት ፣ ካህናት አገልጋዮች እና ምዕመናኑ በሙሉ ድምፅ ሊሆናቸው ይገባል ።

📍ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ

📝ተገድሎ የማያልቅ ሕዝብ ፣ ገድሎ የማይጠግብ አገዛዝ 👉በቀበሌው ሚሊሻ መሆናቸውን የገለፁ ግለሰብ ደግሞ በጥቃቱ ስለተገደሉ ሰዎች ተጠይቀው ሲመልሱ "ሴት አስራ አምስት፣ ሕጻናት 16፣ አዛውን...
11/25/2025

📝ተገድሎ የማያልቅ ሕዝብ ፣ ገድሎ የማይጠግብ አገዛዝ

👉በቀበሌው ሚሊሻ መሆናቸውን የገለፁ ግለሰብ ደግሞ በጥቃቱ ስለተገደሉ ሰዎች ተጠይቀው ሲመልሱ "ሴት አስራ አምስት፣ ሕጻናት 16፣ አዛውንቶች 4፣ ሚሊሻ 5" በማለት በታጣቂዎቹ የተገደሉትን ሰዎች በፆታ እና በዕድሜ ዘርዝረዋል።

👉ቅዳሜ ዕለት 40 ሰዎች መቅበራቸውን የተናገሩት እኚህ ነዋሪ፣ እሁድ ዕለት ደግሞ ለተሻለ ሕክምና ወደ ሌላ ስፍራ ከተላኩት መካከል ሁለት ሰዎች ሞተው መምጣታቸውን ገልጸዋል።

👉በጥቃቱ የሚጠቡት ስድስት ሕጻናት መገደላቸውን ገልጸው፣ በአጠቃላይ ሕጻናት በሚል የመደቧቸው ዕድሜያቸው ከ15 ዓመት በታች መሆኑን ተናግረዋል።

©bbc

📍ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ

ሼር ቤተሰቦች ለሌሎች በማጋራት ፣ ላይክ በማድረግ ይመልከቱ
11/24/2025

ሼር ቤተሰቦች ለሌሎች በማጋራት ፣ ላይክ በማድረግ ይመልከቱ

በየቀኑ የግፍ ግድያ // ጂኖሳይድ በኢትዮጵያ // ምን እናድርግ ? // ቆይታ ከመምህር ፋንታሁን ዋቄ ጋር

📝ጂኖሳይድ በኢትዮጵያ ,,,! ምን እናድርግ ? 👉በዚህ ርዕሰ ጉዳይ  ከመምህር ፋንታሁን ዋቄ ጋር ልዩ ቆይታ ይኖረናል ፣ በተለይ እውን ኢትዮጵያ ውስጥ ጂኖሳይድ እየተፈጸመ ለመሆኑ ማሳያው ም...
11/24/2025

📝ጂኖሳይድ በኢትዮጵያ ,,,! ምን እናድርግ ?

👉በዚህ ርዕሰ ጉዳይ ከመምህር ፋንታሁን ዋቄ ጋር ልዩ ቆይታ ይኖረናል ፣ በተለይ እውን ኢትዮጵያ ውስጥ ጂኖሳይድ እየተፈጸመ ለመሆኑ ማሳያው ምንድን ነው ?

👉 ሰሞኑንን አንዳንዶች በሚዲያ ወጥተው የአርሲው ጭፍጨፋውን የጅምላ ግድያ እንጂ እኔ ጂኖሳይድ ተፈጽሟል በማለት ፣ የመጀመሪያ መሆን አልፈልግም ? ቤተክርስቲያንን አባቶች አላሉም ፣ በማለት የማደናገሪያ ሀሳብ ላይ ፣ ግሩም ዉይይት አድርገናል ፦

👉 ዘወትር አሰቃቂ ግድያ እየሰማን እና ተፈጸመ ብሎ ከማውራት ባለፈ ምን እናድርግ በሚለው ላይም መምህር ፈንታሁን ዋቄ ዕይታቸውን ያጋሩናል ፣ በአጠቃላይ ግልጽ ዉይይት እናደርጋለን ፣ ዛሬ በመደበኛ ኘሮግራማችን በቀጥታ ይጠብቁን ፦ https://www.youtube.com/

📍 ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ

📝ዛሬም መጽናናትን የሚሹ አሉ 👉በአዲስ አበባ ወይራ ሠፈር ኆኅተ ገነት ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ቀጠሎ ወደመ።👉ጳጳሳቱም እቦታው ተገኝተው ሕዝቡን አጽናኑ  እኛም አየ...
11/23/2025

📝ዛሬም መጽናናትን የሚሹ አሉ

👉በአዲስ አበባ ወይራ ሠፈር ኆኅተ ገነት ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ቀጠሎ ወደመ።

👉ጳጳሳቱም እቦታው ተገኝተው ሕዝቡን አጽናኑ እኛም አየን ፣ ግሩም ነው ፣ ይህ አይነቱ አገልግሎት ግን አዲስ አባባ ብቻ ባይሆን ፣

👉በአርሲ ዛሬም አማኙ ኦርቶዶክሳዊያኑ ክርስቲያን በእምነቱ ብቻ ይገደላል፣ ይታገታል ፣ ንብረቱ ይዘረፋል ፣ ቤተክርስቲያኑ ይቃጠላል ፣ ዛሬ መጽናናትን ይፈልጋሉ እና ለእነሱም ድረሱላቸው ፣

🙏“ እኛ ጋ የምስራች የለም። ሽርካ ወረዳ ላይ ትናንት ሌሊት ለዛሬ አጥቢያ ሦስት ሰዎች ተገድለዋል፤ አራት ሰዎች ታግተዋል ” - የአርሲ ዞን ሀገረ ስብከት

ግልባጭ
√ ለሀገረስብከቱ ጳጳስ አቡነ ያሬድ

📍ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ

11/23/2025

ዛሬም ግድያው ፣ እገታው እንደቀጠለ ነው
“ እኛ ጋ የምስራች የለም። ሽርካ ወረዳ ላይ ትናንት ሌሊት ለዛሬ አጥቢያ ሦስት ሰዎች ተገድለዋል፤ አራት ሰዎች ታግተዋል ” - የአርሲ ዞን ሀገረ ስብከት

Address

Maryland City, MD
20876

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Beteseb Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethio Beteseb Media:

Share