Ethio Beteseb Media

Ethio Beteseb Media ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ መንፈሳዊ እና ማኅበራዊ እንዲሁም ወቅታዊ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መረጃን የሚያደርስ ሚዲያ ነው ።
501(c)(3) Registered
(3)

✏ጽንሰታ ለማርያም♣" ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተፀነስኪ አላ በሩካቤ ዘበሕግ እምሐና ወኢያቄም ተወለድኪ፤ ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነሽ አይደለም፤ በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐና ...
08/13/2025

✏ጽንሰታ ለማርያም

♣" ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተፀነስኪ አላ በሩካቤ ዘበሕግ እምሐና ወኢያቄም ተወለድኪ፤

ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነሽ አይደለም፤ በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ።"
ቅዳሴ ማርያም

👉በፈቃደ እግዚአብሔር፣ በብስራተ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል እመቤታችን እግዝእትነ ማርያም ነሐሴ ፯ ቀን ተፀነሰች

የእመቤታችን በረከትና ምልጃ ከሁላችን ጋር ይሁን🙏

https://youtu.be/0DbWT6YDeME?feature=shared
08/11/2025

https://youtu.be/0DbWT6YDeME?feature=shared

Tizitaw : ተልኮውን ጨረሶ ተመልሷል// በመንግሥት ድጋፍ የተሰራው ሤራ//የሃይማኖት ተቋማት? የቤተክህነቱ መሪዎች ?

ለዲያቆናት የተዘጋጀ ልዩ ስልጠና በኢንግልዘኛ  የሚሰጥ ፦ ይመዝገቡ   there is no age restriction for this class.
08/08/2025

ለዲያቆናት የተዘጋጀ ልዩ ስልጠና በኢንግልዘኛ የሚሰጥ ፦ ይመዝገቡ there is no age restriction for this class.

A six-week online training course for Ethiopian Orthodox deacons (ages 13–18). Learn the faith, liturgy, discipline, and leadership needed to serve in the Church with reverence, purity, and spiritual strength.

ጾመ ፍልሰታየጾም ትርጕም‹‹ጾም›› ማለት ‹‹ጾመ –  ተወ፤ ታቀበ፤ ታረመ፤›› ካለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ቃል ሲኾን የቃሉ ትርጕም ደግሞ ምግብ መተው፣ መከልከልና መጠበቅ ማለት ነው ፡ ጾም ...
08/07/2025

ጾመ ፍልሰታ

የጾም ትርጕም

‹‹ጾም›› ማለት ‹‹ጾመ – ተወ፤ ታቀበ፤ ታረመ፤›› ካለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ቃል ሲኾን የቃሉ ትርጕም ደግሞ ምግብ መተው፣ መከልከልና መጠበቅ ማለት ነው ፡ ጾም ጥሉላትን፣ መባልዕትን ፈጽሞ መተው፣ ሰውነትን ከመብልና ከመጠጥ እንደዚሁም ከሌላውም ክፉ ነገር ዅሉ መጠበቅ፣ መግዛት፣ መቈጣጠር፣ በንስሐ ታጥቦ በጸሎት ወደ እግዚአብሔር መቅረብና እርሱንም ደጅ መጥናት ማለት ነው፡፡

የጾም ሥርዓቱና ጥቅሙ

‹‹መላው ሕዋሳታችን ካልጾሙ የምግብና መጠጥ ጾም ብቻ ዋጋ የለውም፡፡ መጽሐፉም የሚለው ‹ወደ አፍ የሚገባ ሰውን አያረክስም፤ ከአፍ የሚወጣ እንጂ› ነው፡፡ ስለዚህ ዐይን፣ ጆሮ፣ እግርና እጅ የመሳሰሉት የስሜት ሕዋሳታችን መጾም አለባቸው፡፡ ከምግብና መጠጥ ይልቅ የሚበልጡት እነዚህ ናቸው፡፡ ከምግብና መጠጥ የምንቆጠበው በራሱ ኃጢአት ስለ ኾነ ሳይኾን ምግብና መጠጥ ሥጋን አጥግቦ በገደል ስለሚጥል ወዳልተፈለገ አቅጣጫ ስለሚጎትት ከእግዚአብሔር ጋር ያለን ግንኙነት እንዲቋረጥ ይደረጋል፡፡ ስንጾምም ከሐሜት፣ ከአሉባልታ፣ ከዝሙትና በሐሰት ከመመስከር፣ ወዘተ. መቆጠብ አለብን››

‹‹የጾም መሠረቱ ሃይማኖት ነው፡፡ በሃይማኖት የተነሣ ለተወሰኑ ጊዜያት ከምግብና ከመጠጥ የምንከለከልበት ኹኔታ ይኖራል፡፡ ነገር ግን ጾም ይህ ብቻ አይደለም፤ ሁለት ዓይነት መስመር አለው፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአጽዋማት ወቅት ከምግበ ሥጋና ከኃጢአት ትከለክላለች፡፡ ከኃጢአት ዅልጊዜም እንከላከላለን፡፡ ከምግብ የምንከለከለው ምግብ ኃጢአት ስለኾነ ሳይኾን ከሃይማኖት የተነሣ ነው፡፡ ምግብ በልተን ፈቃደ ሥጋችንን ከምናደልብ እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ሥጋችንን ጎስመን ያለ ምግብና ያለ መጠጥ እግዚአብሔርን እያመሰገንን የምንኖርበትን ሰማያዊና ዘለዓለማዊ ሕይወት የምናስብብት መንገድ ነው።

የጾም ዓይነቶች

ጾም የግል እና የዐዋጅ (የሕግ) ጾም በመባል በሁለት ይከፈላል፡፡ የግል ጾም ደግሞ የንስሐና የፈቃድ ጾም ተብሎ በሁለት ይከፈላል፡፡ የዐዋጅ (የሕግ) አጽዋማት ሰባት ናቸው፡፡ እነዚህም ዐቢይ ጾም፣ ጾመ ሐዋርያት (የሰኔ ጾም)፣ ጾመ ነቢያት (የገና ጾም)፣ ጾመ ገሃድ፣ ጾመ ነነዌ፣ ጾመ ድኅነት (ረቡዕ እና ዓርብ) እና ጾመ ፍልሰታ ናቸው፡፡ የዚህ ጽሑፍ መነሻም ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ የኾነው ጾመ ፍልሰታ ነው፡፡ ምክንያቱም አሁን ወቅቱ የፍልሰታ ጾም ስለኾነ፡፡

የፍልሰታ ጾም

ጾመ ፍልሰታን ከሌሎቹ አጽዋማት ልዩ የሚያደርገው ምን እንደ ኾነ እንመለከታለን፡፡ የፍልሰታን ጾም ሕፃን አዋቂው ሳይቀር በልዩ ሥነ ሥርዓትና በደመቀ ኹኔታ ይጾማል፡፡ አብዛኞቹ ምእመናን የዕረፍት ጊዜ በመውሰድ በገዳማትና በየአብያተ ክርስቲያናት ሱባዔ በመግባት ከነሐሴ አንድ ጀምሮ እስከ አሥራ አምስት ቀን ድረስ ጾም፣ ጸሎት በማድረግ ይቆያሉ፡፡ ጾም ጸሎት ሲያደርጉ ደግሞ በድሎት ሳይኾን በየዋሻው፣ በየመቃብር ቤቱና አብያተ ክርስቲያናት ዙሪያ እንጨት ረብርበውና ሳር ጎዝጉዘው ጥሬ እየበሉ ነው፡፡

ፍልሰታ ምን ማለት ነው?

‹‹ፍልሰታ ማለት ‹ፈለሰ – ተሰደደ› ከሚለው ግሥ የወጣ ነው፡፡ ‹ፍልሰት› ማለት ደግሞ የተለያየ ትርጕም ቢሰጠውም ‹ፍልሰታ ለማርያም› ተብሎ ሲገለጽ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከሚያልፈው ወደ ማያልፈው ዓለም ከመቃብር የወጣችበት (የተነሣችበት) ቀን ማለት ነው፡፡ ወይም ደግሞ ከሥጋዊው ዓለም ወደ መንፈሳዊው ዓለም የተሸጋገረችበት ማለት ነው፡፡››
፡ ‹‹‹ፍልሰታ ለማርያም› የሚለው የግእዝ ቃል ሲኾን ‹ፍልሰታ› ማለት ደግሞ ‹ፈለሰ› ከሚል ግሥ የተገኘ ነው፡፡ ‹ፍልሰት› ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ መሔድን (መፍለስን) ያመለክታል፡፡ እመቤታችን ካረፈች በኋላ የሥጋዋን መፍለስ አስመልክቶ ሐዋርያት የእመቤታችን ሥጋ የት እንደ ተቀበረ አላወቁም ነበርና እግዚአብሔር የእመቤታችንን ሥጋ እንዲገልጥላቸው የጾሙት ጾም ነው፡፡ ሐዋርያት ሁለት ሱባዔ ጾመው የእመቤታችንን ሥጋዋን ሰጥቷቸው ትንሣኤዋንና ዕርገቷን በማየት በረከት ያገኙበት ጾም ነው፡፡ ስለኾነም ምእመናን ፍልሰታ ለማርያምን ከልጅ እስከ አዋቂው በጾም በጸሎትና በመቍረብ በጋራ በፍቅር፣ በሰላም ያሳልፉታል፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ እመቤታችንን እንዲጠብቃት ከተደረገ በኋላ ሐዋርያት ‹‹የእመቤታችን ነገር እንዴት ነው?›› ብለው በጠየቁት ጊዜ ‹‹እመቤታችንማ በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር ናት›› ብሎ ነገራቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ሐዋርያት እመቤታችን ከመቃብር መነሣቷንና ማረጓን ማየት አለብን፤ እንዴት ዮሐንስ አይቶ እኛ ሳናይ እንቀራለን ብለው በመንፈሳዊ ቅናት በመነሣሣት ነሐሴ አንድ ቀን በዕለተ ሰኞ ሁለት ሰባት ሱባዔ ያዙ፡፡ በዐሥራ አራተኛው ቀን ጌታችን የእመቤታችንን ሥጋ አንሥቶ ሰጣቸውና በጌቴሴማኒ ቀበሯት፡፡ እመቤታችን በ፷፬ ዓመቷ ጥር ፳፩ ቀን ዐርፋ ነሐሴ ፲፬ ቀን ተቀብራለች፡፡

ይኹንና ሐዋርያት ቢቀብሯትም ትንሣኤዋንና ዕርገቷን አላዩም ነበር፡፡ ትንሣኤዋንና ዕርገቷን ያየው ሲቀብሯት ያላየው ሐዋርያው ቶማስ ነው፡፡ ቶማስ እንዲያስተምር ሕንድ አገር ዕጣ ደርሶት አስተምሮ በደመና ሲመለስ ነሐሴ ፲፮ ቀን እመቤታችን ስታርግ ሕዋ ላይ ተገናኙ በማለት ሊቀ ማእምራን ደጉ ያስረዳሉ፡፡ እንደ እርሳቸው አገላለጽ ምእመናን ጾመ ፍልሰታ የእመቤታችን ዕረፍት፣ ትንሣኤና ዕርገቷ የሚዘከርበት ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ የኾነ ጾም ነው፡፡ በየዓመቱ ሕፃን አዋቂው ሳይቀር የእመቤታችን ፍቅር አድሮባቸው ጾሙን ይጾማሉ፣ ያስቀድሳሉ፤ ይቈርባሉ፡፡

የፍልሰታን ጾም ከሌሎቹ አጽዋማት ልዩ የሚያደርገው ምንድን ነው?

የፍልሰታን ጾም ከሌሎቹ አጽዋማት ልዩ የሚያደርገው ምንድን ነው?‹‹ኢትዮጵያ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የዐሥራት አገር በመኾኗ እና ሕዝበ ክርስቲያኑ ለእመቤታችን ልዩ ፍቅር ስላላቸው መሬት ላይ እየተኙ፣ ጥሬ እየበሉ በሰላም በፍቅር ይጾሙታል፡፡ ምእመናን ፍልሰታን ከሌሎች አጽዋማት በተለየ መልኩ መሬት ላይ እየተኙ ይጾሙታል፡፡ ይህ ደግሞ የእመቤታችን ፍቅር ስለሳባቸው ነው፤›› በማለት ያብራራሉ፡፡

የእመቤታችን በከረከት በሁላችን ላይ ይደር 🙏

08/07/2025

ይደመጥ👇

08/05/2025

እግዚአብሔር ድንቅ ነገር አደረገልን ፣ እኛም በዚህ ደስ አለን ፦ ታላቅ መንፈሳዊ ጥሪ

07/30/2025

✏በቅርቡ ይጠብቁን ፦

👉ሕዝቡ ሲነቃ ፣ እውነቱ ሲገለጥ ፣ ተከታይ ሲመነምን ፣ በውጭም በሀገርውስጥም ጋባዡ ሲቀዘቅዝ ፦ እንዲህ በአዲስ ድራማ ትከሰታለህ ፣ በተከታይ ሚዲያዎች ይቀናበር እና ዐይንህ አይቶ ጆሮስ ሰምቶ የፈረደበት ደብተራ እየተባለ ሲያጓራ ሲጮህ ትሰማለህ ......?

👉አስተውሉ,,,,! መንፈስ አውጪው ጥይቄ ይጠይቃል ? በደብተራ ተይዣለው የሚለውን አጥማቂው ለሕዝቡ መልእክት አስተላልፍ ይሉታል ? ታማሚው ይህ ሕዝብ ምን ያውቃል ብሎ እርፍ ! ገና ድራማው ይቀጥላል በቅርቡ ይጠብቁን ፦

👉ሚዲያውን መርዳት ለምትፈልጉ
https://donorbox.org/support-ethio-beteseb-media-2

👉ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ የሁሉም ለሁሉም ድምፅ
ቤተሰብ ይሁኑ ፦ https://t.me/ethiobeteseb

Dear Parents,This Saturday, we will be celebrating the students who successfully completed our Summer Course, Walking th...
07/28/2025

Dear Parents,

This Saturday, we will be celebrating the students who successfully completed our Summer Course, Walking the Narrow Path. We’re so proud of their hard work and spiritual growth over the past weeks.

We’re also excited to announce our next course: Training Young Deacons, specially designed to equip young deacons with the knowledge, discipline, and faith to serve. More details will be shared soon!

Thank you for your continued support.

Ethio beteseb and Yibel Accadamy

በቀጥታ ይከታተሉ
07/27/2025

በቀጥታ ይከታተሉ

ታላቅ የበረከት ስራ ከብስራተ ገብርኤል:- Day 03

እንኳን ለታላቁ መልአክ ለቅዱስ ገብርኤል ሐምሌ 19 ቀን ዓመታዊ ክብረ በዐል አደረሳችሁ አደረሰን!!!የዛሬ በዐል ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት እየሉጣንና ልጇን ሕጻኑ ቅዱስ ቂርቆስን...
07/26/2025

እንኳን ለታላቁ መልአክ ለቅዱስ ገብርኤል ሐምሌ 19 ቀን ዓመታዊ ክብረ በዐል አደረሳችሁ አደረሰን!!!

የዛሬ በዐል ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት እየሉጣንና ልጇን ሕጻኑ ቅዱስ ቂርቆስን ከሚነደው እቶነ እሳት የታደገበት ታላቅ በዐል ነው ።

በፍርድ ቦታ የህጻኑ ልብ ቆራጥ ነው። እምዬ (እናቴ ) ሆይ ምሥክርነታችንን ገድላችንን እንፈጽም ዘንድ ቁረጭ የአምላካችንን ፊቱን እናይ ዘንድ ( ቅዱስ ያሬድ ኢትዮጵያዊ)

ሁለተኛው ቀን የቅዱስ ገብርኤል ወዳጆች ሼር ቤተሰቦች
07/25/2025

ሁለተኛው ቀን የቅዱስ ገብርኤል ወዳጆች ሼር ቤተሰቦች

ታላቅ የበረከት ስራ ከብስራተ ገብርኤል:- Day 02

Address

Maryland City, MD
20876

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Beteseb Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethio Beteseb Media:

Share