Ethio Beteseb Media

Ethio Beteseb Media ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ መንፈሳዊ እና ማኅበራዊ እንዲሁም ወቅታዊ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መረጃን የሚያደርስ ሚዲያ ነው ።
501(c)(3) Registered

📝እውነታው ይህ ነው ፦ ዛሬ ቅዱስነታቸው ከተናገሩት"ከውጪው ይልቅ የውስጡ ከባድ ነው።" ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ 📍ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ
10/15/2025

📝እውነታው ይህ ነው ፦ ዛሬ ቅዱስነታቸው ከተናገሩት

"ከውጪው ይልቅ የውስጡ ከባድ ነው።"

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ

📍ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ

" የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች።"                      ያዕቆብ መልእክት ፭፥፲፮
10/14/2025

" የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች።"
ያዕቆብ መልእክት ፭፥፲፮

📝ጥቅምት ፭

“የእግዚአብሔር ዓይኖች ወደ ጻድቃን ጆሮቹም ወደ ጩኸታቸው ናቸውና። መታሰቢያቸውን ከምድር ያጠፋ ዘንድ የእግዚአብሔር ፊት ክፉን በሚያደርጉ ላይ ነው። ጻድቃን ጮኹ፥ እግዚአብሔርም ሰማቸው ከመከራቸውም ሁሉ አዳናቸው።” መዝ ፴፬;፲፭

📍የጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በረከታቸው ፣ ረድኤታቸው ፣ በሁላችን ላይ ይደርብን 🙏

📝ተጀመረ  ፦ 👉አጠቃላይ መደበኛ  ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ  በየዓመቱ በጥቅምት ወር ፣ በሀገርም ፣በውጭም የሚገኙ የየአህጉረ ስብኩቱ ተዋካዮች የሚሳተፉበት ልዩ ጉባኤ ነው ። 👉ይህ ጉባኤ የጥቅ...
10/14/2025

📝ተጀመረ ፦

👉አጠቃላይ መደበኛ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በየዓመቱ በጥቅምት ወር ፣ በሀገርም ፣በውጭም የሚገኙ የየአህጉረ ስብኩቱ ተዋካዮች የሚሳተፉበት ልዩ ጉባኤ ነው ።

👉ይህ ጉባኤ የጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ከመደረጉ በፊት ቀድሞ መደረጉ ፣ አጠቃላይ ቤተክርስቲያን ሁለንተናዊ ተልዕኮ እና ተግዳሮት ላይ በግልጽ ተወያይቶ ፣ ሕግ አውጭው እና ሕግ አጽዳቂው የቤተክርስቲያን የመጨረሻው ብይን ሰጪ የሆነው ቅዱስ ሲኖዶስ ሊቀርቡ የሚችሉ አጀንዳዎች የሚለዩበት ፣

👉በበጀት ዓመቱ የተሰሩ የሥራ አፈጻጸም የሚገመገሙባቸው ፣ ይህንን ጉባኤ ያዘጋጁ የቀደሙ ብሩህ አይምሮ ያላቸው አባቶች ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴውፍሎስ ፣ ከዛም ይህንን መምሪያ ዛሬ ላለበት ደረጃ እንዲደርስ ፈር ከቀደዱ ብርቅዬ የቤተክርስቲያን አባት ሊቀ ጉባኤ አበራ ታሪክ የማይረሳቸው ፣ ስማቸው በደማቅ ቀለም ዛሬም ድረስ የተከተበ ነው ።

👉ከጉባኤው ምን እንጠብቅ ፦ ዛሬም እንደትላንቱ የመምበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ መደበኛ ሰበካ መምፈሳዊ ጉባኤ በደመቀ ሁኔታ ተከናወነ ፣ ተደረገ ፣ ተጀመረ እና አበቃ ብለን እንለፈው ።

👉የብዙዎች እምነት የተለመደ በውዳሴ ከንቱ ያሽቆጠቆጠ ፣ ብፁዕ ሊቀ ጳጳሱን የሚያወድስ ፣ ያልሰሩትን ሰሩ ፣ ያላጠመቁትን አጠመቁ ፣ ያልተፈጸ ሐዋርያዊ ጉዞ ከአራት ኪሎ በርቀት ተከናወነ ተብሎ ብቻ ይነገርበት።

👉 ለምን እንዲህ ሆነ ሲባል ግልጹን ስንነጋገር በዚህ መምሪያ ለአራት ዓመት በዋና ጸሐፊነት እኔ ቀሲስ ሳሙኤል አገልግያለው ፣ መምሪያው ልዑካን እንዲመጡ ደብዳቤ ይጽፋል ፣ የሪፖርት አቀራረብ መርህን ተከትሎ እንዲቀርብ መረጃ ይልካል ፣

👉ይሁን እንጂ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ የሚመደበው በዋናው መስራቤት በጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ቢሆንም ፣ ለሀገረስብከቱ ሊቀጳጳስ ግን እንደፈለጉ የሚያንቀሳቅሱት ሻንጣ ነው ፣ አድርግ የተባለው ያደርጋል ፣ በል የተባለውን ይላል ፣ ከዛም በላይ ዕድሜውን ለማርዘው ሙሉ ሪፖርቱ በጳጳሱ ውዳሴ ፣ ምስጋና አገልግሎት ይከናወናል ፣

👉ይህ የማይካዳው እውነታ ነው ፣ በዚህ መልእክ ለዕድምተኞቹ ሊቀ ጳጳሱን በደንብ ካልገለጠ ሊቀ ጳጳሱ በገዛ ፈቃዳቸው በምትኩ ሌላ ሰው መመደብ ይችላሉ ፣ እውነት ሀሰት ብልን ብንጠይቅ ዛሬ ጠቅላይ ቤተክህነቱን ያጨናነቁት ከሀገረስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው አንዳንዶች በግፍ ፣ አንዳንዶች ለመሸጋገሪያ ወደ አዲስ አበባ የተዛወሩ ሊመሰክሩ ይችላሉ ።

👉ከሪፓርቱ አቀራረብ መሰልቸት የተነሳ ከሚያዳምጠው የማያዳምጠው የጉባኤው ዕድምተኛ ይበልጣል ፣ አንዳንዱም ሳይጨርስ ወደ ገንዘቡ ሪፓርት ይባላል ፣ አንብቦ ሲጨርስ ፐርሰንት ያስገባበትን ደረሰኝ ለሀገረስብከቱ ጳጳስ ሰጥቶ ለዋናው ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ ጳጳሱ ያቀብላሉ ።

👉ዉዉይት የሌለው ፣ መሠረታዊ በቤተክርስቲያን ወቅታዊ ችግር ላይ ትኩረት ያልሰጠ፣ የበሰሉ ሀሳቦች የማይንሸራሸሩበት ፣ ግልጽ ድጋፍ እና ውዳሴ እጅ ከፍ አድርጎ በማጨብጨብ የሚገለጽበት ፣ ተቃውሞ እና ትችት መግለጫው በእግር መሬት የሚደበደብበት አስልቺ ስብሰባ ነው በየወቅቱ የሚደረግበት፦

👉 ሌላው ለብዙዎች ግርምታ የሚፈጥረው ከውጭ የሚላኩ ሪፓርቶች ፣ ተወካይ ከመጣ በተወካዮቻቸው ፣ ካልመጣም እዛው በሀገረስብከቱ ጳጳስ በተሰየመ አንድ ሰው ይቀርባል መቸስ የውጭውን አገልግሎት እና የቤተክርስቲያን ምስረታ ያላወቀ አፉን ከፍቶ ሊሰማ ይችል ይሆናል እኔም እዛ ሆኜ ምልከተዬ እንደሱ ነበር እና ፣

👉ግርም የሚለው ግን እንዴት ፐርሰንት አያስገቡም እል ነበር ፣ ለካ ጥርስ የሌላቸው አንበሳ መሆናቸውን እዚህ የመጣ ነው የሚያውቀው ፣ የቤተክርስቲያኑ ባለቤት ወይም ባለ መብት የቤተክርስቲያን መስራቾች ናቸው በተለይ በአሜሪካ ፦ ብቻ ጉድ ይታያል ፣ ብሎም ይሰማል ።

በመጨረሻም በመምሪያ የተዘጋጀ የሽልማት አሰጣጥ የሚካሄድበት ፣ ያልተሸለመ ሀገረስብከት በሰልፍ ቀርቦ መምሪያውን በጥያቄ ኩርፊያውን የሚገልጽበት ፣ ከዛም የጋራ አቋም መግለጫ ተነቦ፣ የራት ግብዣ በመመሪያው እና በማኅበረ ቅዱሳን ጽ/ቤት ተዘጋጅቶ ፣ የስብሰባው ፍፃሜ ይሆናል ።

📌ዘንድሮስ ከዚህ የተለይ ምን እንጠብቅ ፦

👉ስለቤተክርስቲያን ውስብስም የውስጥም የውጭም ችግር ይወሳ ይሆን ፦ ለችግሮቹ መፍትሔ በጋራ ይፈለግ ይሆን ?

👉 ሀገር ሰላም አጥታ በእርስ በእርስ ጦርነት የወገን ደም እንጅረት ወንዝ በየቀኑ እየፈሰሰ መቀጠል አለበት ወይ? ወይስ በየዓመቱ እንደሚደረገው የሰላም ኮሚቴ ተሰየመ እየተባለ ይታለፍ ይሆን ?

👉 ለቤተክርስቲያን ከባድ ፈተና የሆኑት የሐሰት አጥማቂያን በየጊዜው መፈብረክ ፣ ብሎም ሰንሰለታቸውን እስከ ውጭ ድረስ አድርገው በጳጳሳት ድጋፍ እየተሰጣቸው በግለቻው ቤተክርስቲያን እስከመክፈት በደረሱት ምንደኞች ዉይይት ተደርጎ ብይን ይሰጥ ይሆን ?

👉 የቤተክርስቲያኒቱ የመልካም አስተዳደር እጦት ፣ ሙስናው ፣ ምዝበራው ፣ ቅጥፈቱ እረ ስንቱ ተነስቶ በአጥፊዎች ላይ ከታች እስከ ላይ ብይን ይሰጥ ይሆን ?

👉 ብዙ ልጽፍ አልኩኝ እና ልቤ ተወው ሲለኝ እኔ ተውኩት እስኪ ጨምሩበት***************** ,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,?

📍ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ የሁሉም ለሁሉም ድምፅ

10/12/2025

I got over 5,000 reactions on one of my posts last week! Thanks everyone for your support! 🎉

10/12/2025

ሰላም ቤተሰቦች በደብሩ የሚተላለፉት መንፈሳዊ አገልግሎቶች እንዲደርሶዎ ፦ like and ,followe the the page https://www.facebook.com/share/19pvSnMwWt/

10/11/2025

በዓለ ንግስ

10/11/2025

የቅድስት አርሴማ አመታዊ ክብረ በዓል ክገነተ ደናግል ቅድስት አርሴማ እና ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ገዳም!

10/11/2025
10/10/2025

👉መልእክት ፩ 📌

•••• እውነትን ብቻ እንናገራለን 📌ጥብቅ መልእክት ለብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ​👉እጅግ ከታማኝ ምንጮች በተገኘ መረጃ መሠረት፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የቅዱስ...
10/09/2025

•••• እውነትን ብቻ እንናገራለን

📌ጥብቅ መልእክት ለብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት

​👉እጅግ ከታማኝ ምንጮች በተገኘ መረጃ መሠረት፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የቅዱስ ሲኖዶስ ጸሐፊውን የሚመለከቱ በርካታ አነጋጋሪ ጉዳዮች እየተከናወኑ እና መረጃዎች እየወጡ ነው ፦

​👉ስማቸው ለጊዜው ይቆየንና 10 በጠቅላይ ቤተክህነት፣ በክፍለ ከተማና በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አስተዳዳሪነት ሥራ ላይ ያሉ መነኮሳት ለጥቅምቱ ሲኖዶስ ጵጵስና ለመሾም በቅዱስ ሲኖዶስ ጸሐፊው ተመልምለው ረብጣ ገንዘብ ይዘው መሰለፋቸው እየተሰማ ነው፦

👉የቅዱስ ሲኖዶስ ጸሐፊው ወደ ቅዱስ ላሊበላ ገዳም ድረስ ደውለው "እኔ አሾምላችኋለሁ፣ ሰው አዘጋጅቻለሁ" በማለት ቃል መግባታቸው የመረጃ ምንጮቻችን ይናገራሉ ።

👉 በአዲስ አበባ ቁጭ ብለው ለሚያስተዳድሩት የራያ ሀገረ ስብከት ተጨማሪ ወረዳዎችን ለመጨመር በማሰብ፣ የህዝቡን ችግር እየተካፈሉ በአገልግሎት ላይ ካሉት ብፁዓን ሊቀ ጳጳሳት ሀገረ ስብከት ወረዳዎች ተቆርሰው እንዲደረቡ ሀሳብ እያቀረቡ ነው። ይህን ለማሳካት በቅርቡ የብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትን ስም በየሚዲያው እንዲጠፋ እየተደረገ መሆኑ የሚያሳዝን ነው።

👉"ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ላይ ያለሁት እኔው ነኝ፣ አቡነ ሳዊሮስ ከሚያበላሹት ላድነው ብዬ ነው" በሚል አባቶችን በማሰባሰብ ላይ መሆናቸው ተገልጿል።

👉ያለ ስልጣናቸው የአዲስ አበባ አስተዳዳሪዎችን በመሰብሰብ እና ገንዘብ በመቀበል ዝውውር በመስራት ላይ ሲሆኑ፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ይህን ዝውውር ካልተቀበለ "በጥቅምቱ ሲኖዶስ አመጽ ይነሳበታል" በማለት ማስፈራሪያ እያሰሙ ነው።

👉ፍኖተ ጽድቅ ሚዲያ ተመልሶ ወደ ስራ እንዲገባ በጥቂት አባቶች አስወስነው ደብዳቤውን ለማውጣት በዝግጅት ላይ መሆናቸው ተጠቁሟል።


📌ይህ ሁሉ ሲሆን ቤተ ክርስቲያን ሰው የላትም ወይ?

📌ብፁአን አባቶችስ ይህን እየሰሙ ለምን ዝም አሉ?

📌የወቅቱ የቤተክርስቲያን አንገብጋቢ ጥያቄ የጳጳሳት ሹመት ነውን? እንደራሴ ይሾም ? አይሾም ? ጠያቂው እና መላሹ ማን ነው ?

👉የቅዱስ ሲኖዶሱ ምልአተ ጉባኤ ይህንን ጉዳይ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ፣ ነገሩ ከወዲሁ ካልተቋጨ ለሀገርም ለቤተክርስቲያን እጅግ አደጋ የሆነ ሥራ በቅዱስ ሲኖዶሱ ዋና ጸሐፊ እየተሰራ እንዳላ ለመጠቆም እንወዳለን ፦

📍ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ የሁሉም ለሁሉም ድምፅ

የበረከት ጥሪ 🙏
10/07/2025

የበረከት ጥሪ 🙏

Address

Maryland City, MD
20876

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Beteseb Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethio Beteseb Media:

Share