Zehabesha

Zehabesha The official page of Zehabesha Newspaper and Zehabeshanews.com Ze-habesha is a free bilingual newspaper with production based in the Minnesota.

Ze Habesha LLC is an Ethiopian American media company based in Minnesota, with presence in the print and broadcast media. Zehabesha strives to provide unbiased information to the ever-growing Ethiopian American community and works toward bridging cultures
Ze-Habesha is a diversified news and information newspaper that represents America’s local and national Ethiopian community. Zehabesha, publishe

d bi-monthly by the Ze-Habesha LLC, has been in publication for 7 years. As of early 2008, Ze-Habesha has non paid subscribers, with a total circulation of 10,000 copies in Major Twin cites areas, including South Dacota, Chicago, Dallas, Atlanta, Las Vegas, and etc...
Ze-Habesha Newspaper has a number of blogs that are updated regularly with community events and news. Please Visit us www.Zehabeshanews.com

(ዘ-ሐበሻ ዜና) የትራምፕ አስተዳደር አሜሪካ ውስጥ ሰክረው በሚያሽከረክሩ እና ህግ በሚጥሱ የውጭ ዜጎች ላይ ጥብቅ እርምጃ መውሰድ መጀመሩን አስታወቀ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ቶሚ...
08/07/2026

(ዘ-ሐበሻ ዜና) የትራምፕ አስተዳደር አሜሪካ ውስጥ ሰክረው በሚያሽከረክሩ እና ህግ በሚጥሱ የውጭ ዜጎች ላይ ጥብቅ እርምጃ መውሰድ መጀመሩን አስታወቀ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ቶሚ ፒጎት እንደገለጹት፣ ህግ መጣስ የቪዛ ስረዛን የሚያስከትል ሲሆን፣ ይህ ጥብቅ እርምጃ የውጭ ዜጎችን ህጋዊ ደረጃ ሊያሳጣ የሚችል ነው።

አስተዳደሩ የቪዛ ስረዛን እንደ ብሔራዊ ደህንነት ማስጠበቂያ እርምጃ አድርጎ እየተጠቀመበት ይገኛል። ቃል አቀባዩ "እያንዳንዱ የቪዛ ውሳኔ የብሔራዊ ደህንነት ውሳኔ ነው፤ ድንበር ማስከበር ደቡባዊውን ድንበር መጠበቅ ብቻ ሳይሆን፣ ማን በህጋዊ መንገድ ወደ ሀገር እንደሚገባ መቆጣጠርም ጭምር ነው" ብለዋል። በዚሁ መሰረት በ2025 ዓ.ም ብቻ ከ100,000 በላይ የውጭ ዜጎች ቪዛ የተሰረዘ ሲሆን፣ ይህ አሃዝ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በስልጣን በነበሩበት የመጨረሻ ዓመት ከተሰረዘው እጥፍ በላይ መሆኑ ተገልጿል።

አብዛኛዎቹ ቪዛዎች የተሰረዙት ግለሰቦቹ ከተፈቀደላቸው ጊዜ በላይ በመቆየታቸው ቢሆንም፣ በርካታ ዜጎች ደግሞ በወንጀል ድርጊቶች እና ሰክሮ በማሽከርከር (DUI) ምክንያት ቪዛቸውን ተነጥቀዋል። ቶሚ ፒጎት እንዳስረዱት፣ አሜሪካ ውስጥ ቪዛ ይዘው ህግ የሚጥሱ ሰዎች የሀገሪቱን ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥሉ በመሆናቸው ቪዛቸው ወዲያውኑ ይሰረዛል። ለዚህም ማሳያ ሰክረው በማሽከርከር አደጋ ያደረሱ እና በፍርድ ቤት የታዘዘ የህግ ማስከበር ፕሮግራም ላይ ሰክረው የተገኙ የውጭ ዜጎችን በምሳሌነት ጠቅሰዋል።

ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ባለፈው ግንቦት ወር በ'ዳካ' (DACA) ጥበቃ ስር አሜሪካ ይኖር የነበረው የ27 ዓመቱ ማይክል ሮዛሪዮ-ክሩዝ፣ በተቃራኒ አቅጣጫ ሰክሮ በማሽከርከር ባደረሰው አደጋ ዕድሜያቸው ከ18 እስከ 20 የሆኑ የአራት ወጣቶችን ህይወት በማጥፋቱ ክስ ተመስርቶበታል። የሀገር ውስጥ ደህንነት ኃላፊ ማርክዌይን ሙሊን ይህንን አሳዛኝ ክስተት በማንሳት ግለሰቡ ከነጭራሹኑ አሜሪካ ውስጥ መግባት አልነበረበትም ያሉ ሲሆን፣ የኢሚግሬሽን እና ጉምሩክ ማስከበር (ICE) በግለሰቡ ላይ የእስር ማቆያ ትዕዛዝ አውጥቷል።

እንደ ቃል አቀባዩ ማብራሪያ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቪዛን መሰረዝ አንድን ግለሰብ ከሀገር ለማስወጣት የመጀመሪያው እርምጃ ነው። ቪዛው ከተሰረዘ በኋላ ግለሰቡ የሚባረረው የፍትህ ሚኒስቴር የወንጀል ክስ ሂደቱን ካጠናቀቀ ወይም የእስር ጊዜውን ከጨረሰ በኋላ እንደሁኔታው ታይቶ ሊሆን ይችላል። በመጨረሻም የትራምፕ አስተዳደር ቪዛ ከተሰጠ በኋላም ቢሆን ተከታታይነት ያለው ማጣራት (continuous vetting) እንደሚያደርግ እና የአሜሪካን ህዝብ ደህንነት ለመጠበቅ 'አሜሪካ ቅድሚያ' (America first) የሚለውን የቪዛ ፖሊሲ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስጠንቅቋል።

(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ለፊፋ ፕሬዝደንት ድጋፍ እንደሚሰጥ አስታወቀ፡፡ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን(ካፍ) ለፊፋ ፕሬዝደንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ በሙሉ ድምፅ ድ...
08/07/2026

(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ለፊፋ ፕሬዝደንት ድጋፍ እንደሚሰጥ አስታወቀ፡፡ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን(ካፍ) ለፊፋ ፕሬዝደንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ በሙሉ ድምፅ ድጋፍ ለመስጠት መወሰኑን ገለፀ፡፡ በኢንፋንቲኖ አመራር ላይ በመላው አለም ተቃውሞ እየተነሳ ባለበት በዚህ ወቅት ካፍ ተቃራኒ አቋም በማንፀባረቅ ፕሬዝደንቱን ደግፏል፡፡ ካፍ ይህንን አቋሙን ዛሬ ይፋ ያደረገው የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ኢንፋንቲኖ በስልጣን ላይ የሚቆዩ ከሆነ በፊፋ ውድድሮች ራሱን እንደሚያገል ማስታወቁን ተከትሎ ነው፡፡ ለአህጉሪቱ እግር ኳስ እድገት ያበረከቱትን አስተዋፅኦ ያደነቀው ካፍ የፊፋ ፕሬዝደንትና ዋና ፀሀፊው ያቀረቡለትን ወቅታዊ ገለፃ እንደተቀበለው አስረድቷል፡፡

በዚህም በፊፋ ውስጥ ግልፅነት ያለው መልካም አስተዳደር ለማስፈን የሚደረገውን ጥረት እንደሚደግፍ አስታውቋል፡፡ የካፍ ፕሬዝደንት ፓትሪስ ሞትሴፕ ሲናገሩ ‹‹ለእኛ ለአፍሪካዊያን በአስተዳደርና በፍትህ ሂደት ውስጥ ግልፅነት ለድርድር የማይቀርብ ነው፡፡

ስለዚህም ከመንግስቶቻችን፣ ከንግድ ድርጅቶችና ከሌሎችም ተቋማት ይህንን እንጠብቃለን፡፡›› ያሉ ሲሆን ካፍ እነዚህን መርሆዎች በማክበር ከፊፋ፣ ከአባል ማህበራትና ሌሎችም አህጉራዊ ኮንፌዴሬሽኖችና የእግር ኳስ ባለድርሻ አካላት ጋር መስራቱን እንደሚቀጥል ገልፀዋል፡፡ በጉዳዩ ላይ የካፍ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ውይይት አድርጎ በሙሉ ድምፅ ለኢንፋንቲኖ ድጋፍ ለመስጠት ውሳኔ እንደደረሰም አስታውቀዋል፡፡

(ዘ-ሐበሻ ዜና) "የወረቀት ስምምነት የሳኡዲን ደህንነት አያረጋግጥም" ሲሉ የኢራን ባለስልጣን ተናገሩ፡፡ የኢራን የፓርላማ አባል ኢብራሂም ራዛኢ በኤክስ ገፃቸው ላይ ሳኡዲ አረቢያ ዛሬ ከቱር...
08/07/2026

(ዘ-ሐበሻ ዜና) "የወረቀት ስምምነት የሳኡዲን ደህንነት አያረጋግጥም" ሲሉ የኢራን ባለስልጣን ተናገሩ፡፡ የኢራን የፓርላማ አባል ኢብራሂም ራዛኢ በኤክስ ገፃቸው ላይ ሳኡዲ አረቢያ ዛሬ ከቱርክና ከፓኪስታን ጋር የፈፀመችውን ወታደራዊ ትብብር ስምምነት ‹‹የወረቀት ስምምነት›› በማለት የገለፁት ሲሆን ይህ ደህንነቷን እንደማያስከብር አስታውቀዋል፡፡

የኢራኑ ባለስልጣን ከዚህ ቀደም ሳኡዲ አረቢያ ከአሜሪካ ጋር የነበራትን ስምምነትና በአሜሪካ መመካቷን አውስተው ‹‹የሪያድ መንግስት ከውጭ አገራት ደህንነት ጥበቃ ከመፈለግ ይልቅ ፖሊሲውን ቢያሻሽል ያዋጣዋል›› ብለዋል፡፡ ይሁን እንጂ ቱርክ ከሳኡዲ አረቢያና ከፓኪስታን ጋር ያደረገችው ስምምነት የመከላከል ባህርይ ያለው እንደሆነ ገልፃ ‹‹የትኛውንም አገር ኢላማ ያደረገ አይደለም›› ብላለች፡፡

የቱርክ ፕሬዝደንት ፅህፈት ቤት የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተሩ በርሀንቲን ዱራን በኤክስ ገፃቸው ላይ ‹‹የመካ ስምምነት በማንኛውም የተወሰነ አገር ላይ ያነጣጠረ ሳይሆን የ3ቱን አገራት የጋራ ደህንነትና መከላከያ የሚያጠናክር ነው፡፡ በዚህም በቀጠናችን ሰላምና መረጋጋትን ለማስጠበቅ ከፍተኛ አስተፅኦ ያደርጋል›› ብለዋል፡፡

(ዘ-ሐበሻ ዜና) አውሮፓ በከባድ የሙቀት ማእበል ውስጥ ወደቀች፡፡ በበርካታ የአውሮፓ አገራት ውስጥ የሙቀት መጠኑ ከ40 ዲግሪ ሰልሺየስ ወይንም ከ104 ዲግሪ ፋራናይት በላይ እየሆነ መምጣቱን...
08/07/2026

(ዘ-ሐበሻ ዜና) አውሮፓ በከባድ የሙቀት ማእበል ውስጥ ወደቀች፡፡ በበርካታ የአውሮፓ አገራት ውስጥ የሙቀት መጠኑ ከ40 ዲግሪ ሰልሺየስ ወይንም ከ104 ዲግሪ ፋራናይት በላይ እየሆነ መምጣቱን ኤኤፍፒ ዛሬ ባቀረበው ዘገባ ገልጿል፡፡ ይህም በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ሰዎች የጤና ማስጠንቀቂያ እስከ መስጠት እንዳደረሳቸው አስታውቋል፡፡ ሳይንቲስቶችና ባለስልጣናት እንዲህ አይነት ከባድ የሙቀት ማእበሎች እየተደጋገሙና እየተለመዱ መምጣታቸውን በመግለፅ ላይ መሆናቸውን የጠቀሰው ዘገባው ይህ ማእበል በማህበረሰብ ጤና ስርአቶች፣ በሀይል ማመንጫዎች፣ በትራንስፖርት ኔትወርኮችና በቱሪዝም መሰረተ ልማቶች ላይ ተፅእኖ መፍጠሩን አስረድቷል፡፡

ከእነዚህ አገራት መካከል በቀዳሚነት የጠቀሰው ጣሊያንን ሲሆን በዚህ አገር ለመጀመሪያ ጊዜ በዋና ዋና ከተሞች የጤና ማስጠንቀቂያ አዋጅ መተላለፉን አስረድቷል፡፡ የጣሊያን ጤና ሚኒስትር ትላንት ባወጣው መግለጫ በ27 ከተሞች ውስጥ ከፍተኛ ሙቀት መከሰቱ መመዝገቡን ገልፆ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል፡፡ ይህ ማስጠንቀቂያ እንደወትሮው አረጋዊያንንና ስር የሰደደ ህመም ያለባቸውን ብቻ የሚመለከት አይደለም፡፡ በማስጠንቀቂያው ሁሉም ነዋሪዎችና ቱሪስቶች ከፍተኛ ሙቀት በሚከሰትበት ወቅት ከፀሀይ ቀጥተኛ ብርሀን እንዲቆጠቡና በተቻለ መጠን ቤት ውስጥ በመቆየት ብዙ ውሀ እንዲጠጡ አሳስቧል፡፡ የተከሰተው ሙቀት በቱሪስት መስህቦች ጉብኝት ላይ ማስተካከያዎች እንዲረጉም ያስገደደ ነው፡፡

የጣሊያን ቱሪዝምና ባህል ቢሮ የሮም ኮሎሲምና ፓንቴዎንን ጨምሮ የትልልቅ መስህቦች በሮች በምሽት እንዲከፈቱ ትእዛዝ ማስተላለፉን ዘገባው ጠቅሷል፡፡ እንደዘገባው ኦስትሪያና ስሎቫኪያ ብሄራዊ የሙቀት ሪከርዳቸውን ሰብረዋል፡፡ ትላንት ሀሙስ በስሎቫኪያ ደቡባዊ ክፍል 42.2 ዲግሪ ሰልሺየስ ሙቀት መከሰቱን የአገሪቱ ሜትሮሎጂ ያረጋገጠ ሲሆን ይህም በአገሪቱ ውስጥ ከተፈጠረው ሙቀት ትልቁ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በዚህች አገር በጋብቺኮቮ የሚገኘው ትልቁ የሀይድሮ ኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጫ ግድብ በውሀ እጥረት የተነሳ ከስምንቱ ተርባይኖች ሰባቱን መዝጋቱም ተዘግቧል፡፡

በኦስትሪያም ሮብ እለት 41.2 ዲግሪ ሰልሺየስ የሆነ በአገሪቱ ታሪክ ትልቁ የሚባል ሙቀት እንደነበረ ተገልጿል፡፡ በሌላ በኩል በሀንጋሪ ለረጅም ጊዜ የዘለቀው ድርቅ የዳኑቢ ወንዝን የውሀ መጠን በመቀነሱ በአገሪቱ ብቸኛ የሆነው የኒውክሌይር ሀይል ማመንጫ ላይ ተፅእኖ አሳድሯል፡፡ እንደዘገባው ይህ ሀይል ማመንጫ ማብላያዎቹን ለማቀዝቀዝ የሚጠቀመው የዚህን ወንዝ ውሀ ነበር፡፡ በዚህ የተነሳ መንግስት የሀይል ቁጠባን በግዳጅ ማስተዋቅ የጀመረ ሲሆን ከቀኑ 5 ሰአት እስከ ምሽቱ 10 ባለው ጊዜ ኢንዱስትሪዎችና ቤተሰቦች የኤሌክትሪክ ፍጆታቸውን እንዲቀንሱ ማሳሰቢያ ሰጥቷል፡፡ የጭነት ባቡሮች በእነዚህ ሰአታት አገልግሎት እንዳይሰጡም ታግደዋል፡፡

ቡዳፔስት የምታትወቅበት የምሽት ላይ የሚያብለጨልጩ መብራቶችም እንዲጠፉ ተደርገዋል፡፡ በጀርመንም ቢሆን በራይንና በሌሎችም ወንዞች እየተከሰተ ያለው የውሀ መጠን መቀነስ በትራንስፖርትና ኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ ተፅእኖ እያሳደረ ነው፡፡ በፈረንሳይ የተከሰተው ሰደድ እሳትም የዚሁ የሙቀት መጨመሩ ተፅእኖ እንደሚገኝበት ዘገባው ገልጿል፡፡ ጁላይ 20 የጀመረው ሰደድ እሳት ከ60 ኪሎ ሜትር በላይ ስፋት ላይ ቃጠሎ መፍጠሩን ጠቅሶ ይህም ከቅርብ አስርታት ወዲህ በአገሪቱ ከተከሰቱ ትልልቅ ሰደድ እሳቶች አንዱ ሆኖ እንዳስመዘገበው አስረድቷል፡፡ ከአውሮፓ ውስጥ ቀዝቀዝ ያለ ሙቀት ያለው በእንግሊዝ ብቻ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ባለፈው ወር በነበረው ከፍተኛ ሙቀት የደረቁት ሳሮች ላይ ትላንት በተነሳው ቃጠሎ የተነሳ የሂዝሮው አየር ማረፊያ ደቡባዊ አውሮፕላን ማኮብኮቢያ ለጊዜውም ቢሆን እንዲዘጋ አስገድዶ እንደነበር ዘገባው ጠቅሷል፡፡

08/07/2026

የሞዴል ሩት ይርጋለም አባት፣ ልጃቸው ለሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ የቁንጅና ውድድር ተሳትፎ ወደ ፊሊፒንስ ዛሬ ምሽት ስታቀና በቦሌ አየር ማረፊያ

ሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ ሩት ይርጋለም፣ ዛሬ ምሽት ውድድሩ ወደሚካሄድበት ሃገር በቦሌ አየር ማረፊያ አሸኛኘት ሲደረግላት
08/07/2026

ሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ ሩት ይርጋለም፣ ዛሬ ምሽት ውድድሩ ወደሚካሄድበት ሃገር በቦሌ አየር ማረፊያ አሸኛኘት ሲደረግላት

08/07/2026

(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ ሰነድ መዋዕለ ንዋይ ገበያ (ESX) ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ለመግባት በመዘጋጀት ላይ ባለበት በዚህ ወሳኝ ወቅት፣ መስራች ዋና ሥራ አስፈጻሚው ዶ/ር ጥላሁን ኢ. ካሳሁን ከኃላፊነታቸው መልቀቃቸው ተነገረ። የተቋሙን የቦርድ ውሳኔ ተከትሎ፣ ወ/ሮ ዮዲት ካሳ የገበያው አዲስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመሆን መሾማቸውን ዘ-ሐበሻ ሰምቷል።

ዶ/ር ጥላሁን ተቋሙ ከጽንሰ-ሀሳብ ጀምሮ ሙሉ የሰነድ መዋዕለ ንዋይ ገበያ እስከመሆን በደረሰበት ጉዞ በዋና መሪነት አገልግለዋል። በቆይታቸውም መንግስታዊ አካላትን፣ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ባለሀብቶችን በማስተባበር ታሪካዊ የተባለለትን የካፒታል ማሰባሰብ ሂደት በስኬት ማጠናቀቃቸው፣ እንዲሁም የአሰራር፣ የቴክኖሎጂ እና የስትራቴጂ መሰረቶችን መገንባታቸው ይነገርላቸዋል።

የገበያው መግለጫ እንዳመለከተው "የእሳቸው አመራር የኢትዮጵያን የሰነድ መዋዕለ ንዋይ ገበያ መሰረት በመጣል እና ተቋሙን አቅራቢዎችን፣ ባለሀብቶችን እና ሰፊውን የፋይናንስ ዘርፍ የሚያገለግል ታማኝ ተቋም በማድረግ ረገድ ትልቅ ሚና ተጫውቷል።"

የዶ/ር ጥላሁንን ቦታ የተረከቡት ወ/ሮ ዮዲት ካሳ፣ ተቋሙ በፕሮጀክት ደረጃ ከነበረበት ጊዜ ጀምሮ አብረው የሰሩ ናቸው። አዲሷ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከዚህ ቀደም የተቋሙ የቢዝነስ ኃላፊ እና የኦፕሬሽን ኃላፊ በመሆን ገበያውን በማዋቀር እና ስትራቴጂያዊ እድገቱን በመምራት ሰፊ ልምድ አካብተዋል።

ይህ የኃላፊነት ሽግግር ሀገሪቱ ያላትን ብቸኛ እና የተደራጀ የሰነድ መዋዕለ ንዋይ ገበያ ቀጣይነት ለማረጋገጥ እና የወደፊት ተስፋውን ለማሳካት የተደረገ እንደሆነ ESX ገልጿል። ወ/ሮ ዮዲት ከፊታቸው የሚጠብቃቸው ቀጣይ የሥራ ምዕራፍ እጅግ ትልቅ ሀላፊነትን የሚጠይቅ ሲሆን፣ የሚከተሉትን ዋና ዋና ጉዳዮች ለማሳካት ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩ ይጠበቃል፡

* የሰነድ አቅራቢዎችን (issuer base) ቁጥር ማስፋፋት
* በገበያው ላይ የሚኖረውን የባለሀብቶች ተሳትፎ መጠን ማሳደግ
* የኢንቨስትመንት አማራጮችን፣ አዳዲስ ምርቶችን እና የገበያ ክፍሎችን ማስተዋወቅ
* የገበያውን መሰረተ ልማት ይበልጥ ማጠናከር

በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ሰነድ መዋዕለ ንዋይ ገበያ (ESX) የሰነድ መዋዕለ ንዋይ ገበያ ሥራዎችን የሚያከናውን ሲሆን፣ እንደ ራስ-ተቆጣጣሪ ድርጅት (SRO) እና የተጠናከረ አገልግሎት የሚሰጥ ማዕከላዊ የገበያ አደራጅ ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል።

(ዘ-ሐበሻ ዜና) ሱዳን ዘንድሮ ኢኮኖሚዋ በ9 ፐርሰንት እንደሚያድግ ገለፀች፡፡ በሌተና ጄኔራል አብዱል ፈታህ አልብሩሀን የሚመራው የሱዳን ወታደራዊ መንግስት የአገሪቱ ኢኮኖሚ በ9 ፐርሰንት ያ...
08/07/2026

(ዘ-ሐበሻ ዜና) ሱዳን ዘንድሮ ኢኮኖሚዋ በ9 ፐርሰንት እንደሚያድግ ገለፀች፡፡ በሌተና ጄኔራል አብዱል ፈታህ አልብሩሀን የሚመራው የሱዳን ወታደራዊ መንግስት የአገሪቱ ኢኮኖሚ በ9 ፐርሰንት ያድጋል የሚል እምነት እንዳለው አስታወቀ፡፡ ይህንን ያስታወቀው ትላንት በካርቱም በተካሄደው የሚኒስትሮች ካቢኔ ስብሰባ ላይ በቀረበው ሪፖርት ነው፡፡ የፋይናንስ ሚኒስትሩ ጅብሪል ኢብራሂም ባቀረቡት በዚህ ሪፖርት በአሁኑ ወቅት የአገሪቱ ኢኮኖሚ በማገገም ላይ መሆኑን ገልፀው በዚህም የአገሪቱ አጠቃላይ ምርት በ2026 በ9 ፐርሰንት ያድጋል የሚል ግምት እንዳላቸው አስረድተዋል፡፡

ባለፈው አመት ይህ እድገት 1.7 ፐርሰንት ብቻ እንደነበርም አውስተዋል፡፡ ጨምረውም በአገሪቱ ውስጥ የነበረው የዋጋ ግሽበት እየቀነሰ መምጣቱንና ከግብር የሚገኘው ገቢ ደግሞ በመጨመር ላይ መሆኑን ገልፀዋል ሲል ሱዳን ትሪቢዩን ዘግቧል፡፡ እንደዘገባው ከወራት በፊት የወጣው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሪፖርት በ2023 የሱዳን አጠቃላይ አገራዊ ምርት በ6.6 ቢሊዮን ዶላር ቀንሶ 32.4 ቢሊዮን ዶላር እንደደረሰ ይገልፃል፡፡ ይህም የ12 ፐርሰንት ቅናሽ መከሰቱን የሚያሳይ መሆኑን የጠቀሰው የተመድ ሪፖርት ከዚያ በኋላ ባሉት አመታትም እየቀነሰ መምጣቱን ማስረዳቱን አስታውቋል፡፡

እንዲሁም ከ2024 እስከ 2043 ባሉት አመታት ውስጥ የሱዳን ኢኮኖሚ በየአመቱ ከ1.2 ፐርሰንት በላይ እንደማያድግ ግምት ማስቀመጡን ዘገባው አውስቷል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ አይኤምኤፍ ባወጣው የ2026 የአለም ኢኮኖሚ ሪፖርት የሱዳን ኢኮኖሚ እንደሚያድግ የተነበየው በ0.7 ፐርሰንት ነው፡፡

የዕለቱ ዜናዎችን ይመልከቱ - VOEA Tv ዩቱብ ቻናል ላይ ይገኛል
08/07/2026

የዕለቱ ዜናዎችን ይመልከቱ - VOEA Tv ዩቱብ ቻናል ላይ ይገኛል

08/07/2026

ቀጣዩን ሰበር ዜና በእርግጠኝነት የሚያዩት ዘ-ሐበሻ ላይ ነው!

Address

Minneapolis, MN

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zehabesha posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Zehabesha:

Shortcuts

Share