DONGA MEDIA NETWORK HADERO

DONGA MEDIA NETWORK HADERO Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from DONGA MEDIA NETWORK HADERO, Media/News Company, New York, NY.

11/26/2025

10/22/2025

ከጡንጦ ከተማ ማዘጋጃ ከዓመታት በፊት በፎርጂድ COC ምክንያት የተባረረው ግለሰብ ለአቶ ጌታሁን ለሬ እና ለወ/ሮ መስተወት ሙላቱ ለእያንዳንዳቸው 20,000 ብር በመክፈል ቀድሞ በምሰራበት ጡንጦ ከተማ ማዘጋጃ ሰሞኑን ወደ ስራ መመለሱ ታውቋል፡፡

10/20/2025

በጡንጦ ከተማ በተለምዶ የአርብ ገበያ በሚባል ቦታ ሊሰራ ተሞክሮ በሕዝብ ትግል የቆመውን እና ሌሎችንም የጌታሁን ለሬን እና የጀሌዎቹን የሌብነት ስራ በቀጣይ ይዘን እንመጠለን እስከዘው share እያደረገችሁ ጠብቁን፡፡

ጌታሁን ለሬ አቋምህን የማታስተካክል ከሆነ እያንዳንዱ ጉድህ አደባባይ ይወጠል !! ደመወዝ እና ሀደሮ ጡንጦ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ከመቼውም ጊዜ በላይ የመንግስት ሠራተኛው የኑሮ ውድነትን መቋ...
10/20/2025

ጌታሁን ለሬ አቋምህን የማታስተካክል ከሆነ እያንዳንዱ ጉድህ አደባባይ ይወጠል !!

ደመወዝ እና ሀደሮ ጡንጦ ዙሪያ ወረዳ

መንግስት ከመቼውም ጊዜ በላይ የመንግስት ሠራተኛው የኑሮ ውድነትን መቋቋም አለመቻሉን እና በወር የሚያገኘው ገቢ ዝቅተኛ መሆኑን ተሳቢ በማድረግ ይህን አስቸጋሪ ጊዜ እንድቋቋም የተለያዩ ድጎማ እያደረገ መሆኑ ግልጽ ነው። ነገር ግን በከምባታ ዞን በሀደሮ ጡንጦ ዙሪያ ወረዳ ላይ የተደራጀው ወንበዴ አመራር የመስከረምን ወር የመንግስት ሠራተኛ ደሞወዝ ላይ የተለመደውን ውንብድና ፈጽሟል። እንኳን ሙሉ የወር ደሞወዝ ተካፍሎም ቢሆን ኑሮ መቋቋም ባልተቻለበት 62 % ከፍሏል።
ቀሪ 38 % ደመወዙ የት ሄዳ? ይህም የሆነው በ2017 በጀት አመት ከሁለቱም ማዘጋጃ ቤቶች ማለትም ከጡንጦ ማዘጋጃ እና ከሌሾ ማዘጋጃ ቤቶች ለወሎ አበል የተወሰደ ብድር ተከፍሎ መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ።
ብድር የተወሰደው ዋና ዓለመ ከአመራርነት ሊትነሱ ስለሚትችሉ የሚለውን ሚስጥር በዞን አስተባባሪ ውስጥ የሚገኝ በፍቅር ታምረት ሀደሮ መጥቶ ለጌታሁን ለሬ ሹክ ብሎ ስሄድ በተለያየ መንገድ ማዘጋጃ ቤቶቹ ተበዝብዟል ። ይሁን እንጂ አቶ ጌታሁን ለሬ አሁን አስተዳዳሪ ሆኖ ስቀጥል በመንግሥት ሠራተኛ ደሞወዝ ላይ ፈርዶ ከመንግሥት ሠራተኛ ደሞወዝ ላይ አንስቶ ለማዘጋጃ ቤቶች ተከፍሏል።

ከዚህ በፊትም 50% ደመወዝ ያልተከፈለ እያለ አሁንም 40 % አስቀርቶ ከፍሏል።

የክልሉ መንግስት የዚህ ወረዳ የሀብት አመራር ስርዐቱን በግልጽ ገብቶ ማየት አለበት።

በ2017 በጀት አመት በዚያ ወረዳ ለውሎአበል (6231) ብቻ ወደ 13,000,000 ሚሊዮን አከባቢ ተመርቷል። እንግዲህ ይህ ሁሉ ሀብት የተመራበት መንገድ እጅግ አስካፊ መሆኑን መገመት አያቅትም።

የከምባታ ዞን አስተባባሪ አካለት በተላይም በፍቅር የሚባለው ሴሰኛ የሀደሮ ጡንጦ ዙሪያ ወረዳ ህዝብ የማይፈልገውን አመራር ሀይል በመጠቀምና በአፋ-ሙዝ በማስፋራረት አያደረጃ የቆያ ሲሆን አሁን በሪፎርም ወቅትም ጭምር የወረዳ ነዋሪ ህዝብ የማይፈልገውንና ያልወካለውን አመራር በሀይልና የብልጽግናን መሪ በልተከተላ መልኩ የወረዳ ህዝብ ከጫፍ እስካ ጫፍ በብልጽግና ፓርቲ ላይ እምነት እንዲያጣና በሌሎች ተፎካካሪ ፖርቲዎች ላይ አባል እንዲሆኑ ለማድረግ የዞኑ አስተባባሪ በአቋሚ እየሳራ የሚገኝ በመሆኑ የሚመለካተወ አካልና ህዝብ ቀጥሎ ልመጣ ያላውን ችግር ከግምት ወስጥ በማስገባት ትግል ልያደርግ ይገባል ።

ለዚህም ማሳያ የወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት ባለሙያዎች ከአባልነት ለመውጣት መመልከቻ ለፓርቲ ጽ/ቤት አቅርበዋል።

ይህ ባንዳ ጌታሁን ላሬ የሚበለው ወሮበላ የወረዳን ህዝብ አይወክልም ስንል በምክንያት ነው።
ዝርዝር ሀሳቡን እንመልካት

1ኛ/ ከዚህ በፊትም የወረዳ አስተዳዳሪ ለመሆን ቀድሞ አስተዳዳሪ በነበረው የተከበሩ አቶ ደስታ ሆጎሮ ላይ አጀንዳ ፈጥሮ በጡንጦ ከተማ ህገወጥ ታፔላ በወጠቶች አስተክሎ ይህን ታፔላ እኔ አስነቅላለሁ የህዝቡንም አጀንዳ እኔ አጠፋለሁ ለእኔ አስተዳዳሪነቱን ስጡኝ የሚል ሀሳብ አቅርቦ በዞኑ ተቀባይነት አግኝቶ አስተዳዳሪ ከሆነ ቦኃላ ታፔለውን አስነቅሎ ወዲያው የሌብነት መረብ ዘርግቶ መስረቅ ጀመረ።

ከገጠር ቀበሌ እስካ ከተማ ድረስ የመሬት ሽያጭ ፣ የሳር ሺያጭ ፣ የደን ሽያጭ ፣የወል መሬት እና የከተማ መሬት እየቸበቸበ የራሱን ሀብት ሰብስቧል። ይሀ ብቻ አይደለም በጊዜው የፐብልክ ሰርቭስ ጽ/ቤት ኃላፊ የነበረችው ከወ/ሮ መስተዋት ሙላቱ ጋር አንድ ላይ በመሆን የወረዳን የጽ/ቤት አመራሮችን በስልጣን በማስፋራረትና ጫና ያለበትን ተልዕኮ በመስጣት ከፍተኛ ሌብነት ውስጥ ገባ።

የወንድሙን የሟች ተክሉ ላሬ ልጅ ጨምሮ 370 ስራ አጥ ወጣቶችን ከ25,000 ብር እስካ 60,000 ብር የሚሰበስብ ዳለለን በየመስኩ አዳረጅቶ አቅም የሌለቸውን አርሶ አደሮችን ያስጨነቃ ቦዘኔ ነው። አቅም ያለው አርሶ አዳር እና ቤተሰብ ውጭ ሀገር የምኖሩ በዘመድ አዝማድ ገንዘብ በማስላክ በቁጥር ብዙ ሠረተኞችን ቀጥሯል። አቅም የሌላው የከተማ ይዞታ ጭምር በክራይ በመስያዝ በእጅ መንሻ ልጁን እንደያስቀጥር ያስደረገና ለረሱ በግፍ ሀብት የሰባሰበ ሌባ ነው።

ይህ በቁጥር 370 እና ከዚያ በላይ ከተቀጠሩ ተቀጣሪዎች ውስጥ 174ቱ ያለ መደብ እና መደብ መታወቂያ ቁጥር በሌላበት ቦታ የተጣሉ ናቸው።

እዚያ ወረዳ ላይ መንግስት performance ኦዲት ማስገባት አለበት ባይ ነኝ።

እውነት ለመናገር ወረዳው እስካሁን ላለው በደመወዝ ቀወስና ወዝፍ ዕዳ ላይ እንድወድቅ የአንባሰውን ሚና የተጨዋታ የወንድሙን ልጅ ጭምር በገንዘብ የቀጠራ አውሬ ህልና ብስ ሌባ ነው።

ለዚህም የተቀጠሩ ስራ አጥ ወጣቶችና ያስቀጠረው ቤተሳብ እንድሁም ደግሞ የወረዳ ህዝብ ህያው ምስክር ነው ።

2ኛ/ ከበድ ቅሌት ደግሞ መንግስት ለህዝብ ጥያቄ ምላሽ ከመስጣት አንጻር ለወረዳው የሙያና ቴክንክ ኮሌጅን የፋቀዳ ሲሆን ኮሌጁ ከተከፋታ በኃላ ቢሮውን በጊዜያዊነት ጡንጦ ላይ የአስቴር መንግስቴ የመንገድ ፕሮጃክት ለወረዳ አስረክቦ በወጣው ቤት ቋሚና ጊዜያዊ ሙሉ የቢሮ ቁሳቁስ ባለበት ላይ ኮሌጁ ስራውን እንድጀምር ለወረዳው ልክ አስረክቦ ስወጣ በማግስቱ ለኮሌጁ ቢሮውን ለማስረከብ ቀድሞ በማታ ላይ በአጎቱ ልጅ በአቶ ካሰ ከበዳ አይሱዝ መክና ሙሉ የቢሮ ዕቃ በወቅቱ የፐብል ሰርቭስ ምክትል ኃላፊ ከነበረው ከካሰ ወንድም በአቶ ምህረቱ ከበዳ አመካይነት ወደ ቤቱ ያስገባ ሲሆን ለዝህ በአቶ ጌታሁን ላሬ ቤት ያላው ፍርጅ፣ሶፋ የአቶ ጌታሁን ላሬ ልብ ፣የወረዳ ህዝብ አቶ ካሰ ከበዳና ሌሎችም ምስክር ነቸው ።

3ኛ/ በከምባታ ዞን ንግድና ገባያ ልማት ኃላፍ ሆኖ እያለ ከሁሉም ከዞኑ ወረዳዎች መንግስት የሱኳርና ዘይት አቅርባዎችን በማህባር እንድዳረጁ ያደረገውን እንደምክንያት በመጠቀም በሁሉም አካባቢ ላይ ህጋ ወጥ ቡድን በገንዘብ እንድዳረጀ በማድረግና ገንዘብ በመወስድ ከዞኑ ኃላፍነት በከፍተኛ ክራይ ሰብሳብነት የተባራራና ወንድሙን ሞች ኤፌሬምን ጭምር በግፍና በእርግማን ገብቶ እንድሞት ያዳረገ ጨካኝ አውሬ ነው ።

4ኛ/ በጡንጦ ከተማ ላይ የከተማ የፕላን መስፋፋትን እንደ ምቹ አጋጠሚ በመጠቀም ጡንጦ ላይ የምስግን አርሶ አዳሮችን መሬት ቀምቶ በሀይል በመወሳድ አርሶ አዳሮችን መሬት አልባ ያደረገ ነው።

5ኛ/ ከ2014 ጀምሮ ወረዳውን እኔ ነኝ መምራት ያለብኝ በሚል ብዙ ሴራ ስያሴር እና መንገድ እንደሚያስዘጋ ይታወቃል። ይህ ብቻ አይደለም በአቶ ጨኬቦ ጨፌቦ ቤት በተወረወረው ቦምብ ላይ ከጨኬቦ ጨፌቦ ጋር በመመካከር ያስጠለ እና በግላጭ እጁ ያለበት ሰው ነው።

ይህ ብቻ አይደለም በቦምብ ውርወራ ፣በማዘጋጃ ቤት ዝርፊያ በር እንዲሰበር ደነቡ አቡዬ የሚባለውን የሚስቱ እህት በል በመጠቀም ብዙ ወንጀሎችን ሰርቷል።

ይህ ሁሉ የወረዳ አስተዳዳሪ ቢንያም አይናለምን እና የፓርቲ ኃላፊ ግዛቸው ጴጥሮስን አስነስቶ እሱ ለመሾም ያደረገ ሴራ ነበር ይታወቅም ነበር።

በዚህ አንጻር በወማዎች በሽማግሌዎች አማካይነት አነዚህን ከሀዲዎችን1) በፍቅር ታምረት ፤ 2) ጌታሁን ላሬ ፣ 3) አየለ ቡባሞ እና ግብረአበሮቹን ጠርተው አደብ ግዙ ተብለውም ነበር ተገስጻውም ነበር ተመልሰናል ይቅርታ በማለት አስመስለው ክህዳት የፈጸሙ ባንዳዎች ናቸው። ከዞን ጋር ቃለ መሃላ ፈጽመው ስለመጡ በህዝቡ ጨንቃ ላይ ተቀምጧል።

6ኛ) ጡንጦ ማዘጋጃ ቤትን አመራርን አስተዳደሪ በሆነው በ 1 አመት ውስጥ 5 አመራሮችን ቀይሯል በመጨረሻም ወ/ሮ መስታወት ሙላቱን የለመዱትን ስርቆት ለመፈጸም ውክልና ሰጥቷት የማዘጋጃ ቤት ብር ሙጢጥ እያደረጉ መሆናቸውን ታማኝ ምንጮች ያሳያሉ።
ጡንጦ ህዝብ ንቃ።

7ኛ) እጅግ አስነዋሪ ስራ ደግሞ አመራር የሚሾመው በገንዘብ ነው። የቀበሌም ሆነ የወረዳው አመራር የሚሾመው ከ30 አስካ 50 ሺህ ብር ከፍሎ ነው። አሁንም ይህ ቀጥሏል።

8ኛ) ኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡ የጌታሁን ላሬ ምድረዊ ግፍ የሰማይ እግዝአብሔር ከልቆጠራ በስተቀር ሰው ቆጥሮ አይጨርስም ።

ህዝቡ የሚጠይቀው ደኝነት የክልሉ መንግስት በአስቸኳይ ጠልቃ ገብቶ ይህን የብልጽግና አረም ከወረደችንም ሆነ ከህዝባችን ላይ የማይነቅል ከሆነ የወረዳው መንግስት ሰራተኞች እና አርሶአደር አባለት ፓርቲውን የማንፈልግ መሆኑን እየገለጽን ምርጫ የሚባል ነገር የማይሰራ መሆኑን ጭምር እንድታወቅልን እንፈልጋለን።

10/11/2025

ከጠምባሮ አብራክ የተገኘው አርቲስት Ashenafi sahle የጠምባሮ ዶንጋ እና ከምባታ ወንድማማች ሕዝቦችን ሙዚቃ በቅርብ ቀን ጠብቁ ብሏል፡፡

ህመምሽ ምን ነበር ?        አንች ውብ ከተማ አንች ደማቅ ሀገር ፣       ተምሳሌት የሆንሽው መገኛ የሰው ዘር ፣       ሳትከፋፍይን በኃይማኖት በዘር ፣        ሰብስበሽ ያኖር...
10/10/2025

ህመምሽ ምን ነበር ?

አንች ውብ ከተማ አንች ደማቅ ሀገር ፣
ተምሳሌት የሆንሽው መገኛ የሰው ዘር ፣
ሳትከፋፍይን በኃይማኖት በዘር ፣
ሰብስበሽ ያኖርሽን ሚስጥሩ ምን ነበር ?
ህንፃው ምን ቢረዝም ቢፀዳ ውበቱ ፣
ምንገዱ ቢፀዳ ቢንጣለል አስፋልቱ ፣
ተከብሮ ካልኖረ ሰው በማንነቱ ፣
ከተበለሻሸ ከታች መሰረቱ ፣
ስላገር አንድነት ደጋግሞ ማውራቱ ፣
ሰው ሰው ካልሸተተ ምንድን ነው ? ውበቱ ።
ድንጋይ ቤት አይሆንም ህንፃው ቢደረደር ፣
ምንገድ ተዘጋግቶ ቢበጅለት አጥር ፣
በፍቅር በጋራ ተሳስቦ የሚኖር ፣
የሰው ልጅ ልብ ነው የሌለው ዳር ደንበር ፣
ታዲያ እንድህ ከሆነ እውነት ለመናገር ፣
ካለ ሰው ቢወዱት ምን ያደርጋል ሀገር ።
ምስቅልቅልሽ ጠፍቶ ችግርሽ በርትቶ ፣
ስቅታ በዝቶብሽ ሀዘንሽ በርትቶ ፣
ቁጥሮችሽ ላልተው፧ ማሰሪያሽ ተፈቶ ፣
ህልምሽ እውን ሆኖ የጎደለሽ ሞልቶ ፣
ያኑርሽ ፈጣ የሰውን ልብ ገዝቶ ፣
አንች ውብ ከተማ አፍሪካዊት ምድር ፣
ማንም ያልደፈረሽ ልዕዋላዊት ሀገር ፣
ለብዙ ሺ አመታት ያኖርሽን በፍቅር ፣
ተጋብተን ተዋልደን ሳንቆጥር የሰው ዘር ፣
ዛሬ ተከፋፍለን በኃይማኖት በዘር ፣
ተቆጭና ገልማጭ የሌለባት ሀገር ፣
ተብሎ ስማችን በዓለም ላይ ሲነገር ፣
ለብዙ ዘመናት የተለየሽ ፋቅአር ፣
ሁሉም ያልተረዳው ህመምሽ ምን ነበር ።


መልካም አዳር !!

ምንም እንኳን ከተማ የነዋሪዎች ብትሆንም በተደጋጋሚ ሀደሮ ከተማ ላይ የሚሰራው አደረጃጀት ነዋሪዎቿን ሆነ ህዝብን መሰረት ያደረገ አይደለም።በተለይ የዶንጋ ብሄረሰብ በከተማዋ ከለው ታሪክ አን...
10/10/2025

ምንም እንኳን ከተማ የነዋሪዎች ብትሆንም በተደጋጋሚ ሀደሮ ከተማ ላይ የሚሰራው አደረጃጀት ነዋሪዎቿን ሆነ ህዝብን መሰረት ያደረገ አይደለም።
በተለይ የዶንጋ ብሄረሰብ በከተማዋ ከለው ታሪክ አንፃር የከተማው ወይም የቦታው አራሽ እና ነበር ህዝብ እንደሆነ ግልጽ ነው።

የአደረጃጀት ስብጥር ምልመለ ነዋሪ እና ህዝብ ከሆነ ሀደሮ ከተማ ላይ 80% ያህል የከተማዋ ነዋሪ የዶንጋ ብሄረሰብ መሆኑ እየታወቀ በከተማው አደረጃጃት ላይ አንድም ጊዜ ከንቲባ ወይም ብልፅግና ፖርቲ ሲሆን እና በሚገባው ልክ በከተማው ሀላፊነት ሲሰጥ አይታይም። ምክንያትስ ምንድነው?
አደረጃጃቱ ሀደሮ ከተማ ላይ ያለውን የዶንጋ ብሄረሰብ ተወላጆች የከተማውን ህዝብ ያለማከለ አደረጃጃት ስለሆነ አደረጃጀቱን በመቃወም ለመብተችን እንታገል። ለመብትህ ቆርጠህ ካልታገልክ ማንንም አምጥተው ይጭኑብሃል እየሆነ ያለውም ሀቅ ይህ ነው።
1,ታምሬ ታደሰ ሀድያ
2,አደነ ፍቅሬ ዶንጋ
3,አበረ ተፈሰ ከምባታ
4,ተፈራ ማቴዎስ ከምባታ
ሀደሮ ከተማ ላይ ያለችሁ ምሁራን፣ ነገዴዎች፣ ሽማግሌዎች፣ ወጣቶች ሆይ ለህዝባችሁ ተነሱ! ለመብታችሁ ታገሉ!

ከፍ አድርገን ድምፃችንን ያሰማነው፤ ክብር የሆነውን የሰው ልጅ ያጣነው፤ አካለ ጎዶሎ የሆነው፤ ሰላማዊ ወጣቶች አካባቢውን ለቀው የተሰደዱበት፤ በመቶዎች የሚቆጠሩ ንፁሃን በማረሚያ የታጎሩበት፤...
10/09/2025

ከፍ አድርገን ድምፃችንን ያሰማነው፤ ክብር የሆነውን የሰው ልጅ ያጣነው፤ አካለ ጎዶሎ የሆነው፤ ሰላማዊ ወጣቶች አካባቢውን ለቀው የተሰደዱበት፤ በመቶዎች የሚቆጠሩ ንፁሃን በማረሚያ የታጎሩበት፤ ዝቅ ብለን ለሕዝባችን ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ለውጥ እንዲኖር ነው።
አንድ ክፍለ ዘመን የተሻገረውን የዶንጋን ህዝብ መዋቅራዊ በደል የተጠየፍነው፣ ከሸዋ ክፍለሀገር እስከ ደቡብ ብሄር ብሄረሰቦች እናም እስከዛሬው ማዕከላዊ እትዮጵያ ክልል ድረስ ከከምባታ እና ሀዲያ አውራጃ እስከ ከምባታ ዞን የምንታገለው እንደ ሀገር በኢትዮጵያ ውስጥ የዶንጋን ሕዝብ እኩል ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ለማስቻል እንጂ ከዚህ ቀደም በከሸፈው መዋቅር ያለፍላጎቱ ህዝቦችን ተደራጅቶ ባህሉ ቋንቋው እንድሞት፤ እንደጠፋ፤ እንዲንገላታ ፤ እንዲገፋ ፤ አልፎም ተርፎ እንዲሰቃይ አልነበረም፤ አይደለምም።

ስለሆነም የዶንጋ ሕዝብ በሰላማዊ መንገድ ሲያነሳቸው የነበሩ እና እስካሁን የሚያነሳቸው ፍፁም ሕጋዊ የሆኑ በልዩ ወረዳ የመደራጀት፤ የምርጫ ክልል ሌሎችም የልማት ጥያቄዎች ተገቢ ምላሽ ሊሰጣቸው ይገባል።

ፍትህ ለዶንጋ ብሔረሰብ ⚖️

ጥያቄዎች ሕጎችንና አሰራሮችን በመከተል ወንድማማችነትና አንድነትን በሚያጠናክር አግባብ ሕገ መንግሥታዊ ምላሽ እንዲያገኙ በትኩረት እንደሚሠራ ተገለጸ***************************...
10/06/2025

ጥያቄዎች ሕጎችንና አሰራሮችን በመከተል ወንድማማችነትና አንድነትን በሚያጠናክር አግባብ ሕገ መንግሥታዊ ምላሽ እንዲያገኙ በትኩረት እንደሚሠራ ተገለጸ
************************************************
(ዜና ፌዴሬሽን) መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም፣ አዲስ አበባ፣

የሚቀርቡ ጥያቄዎች ሕጎችንና አሰራሮችን በመከተል ወንድማማችነትና አንድነትን በሚያጠናክር አግባብ ሕገ መንግሥታዊ ምላሽ እየሰጡ መሄድ ተጠናክሮ አንደሚቀጥል የማንነት፣ የአስተዳደር ወሰንና የሰላም ግንባታ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ጥላሁን ከበደ ገለጹ፡፡

በፌዴሬሽን ምክር ቤት የማንነት፣ የአስተዳደር ወሰን የሰላም ግንባታ ቋሚ ጸሐፊ የተከበሩ አቶ ፍቅሬ አማን በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግራቸው ቋሚ ኮሚቴው በበጀት ዓመቱ በርካታ አንኳር ጉዳዮችን ማከናወኑን በዋናነትም ከግጭት መከላከልና ከሰላም ግንባታ አንጻር በህዝቦች መፈቃቀድ ላይ የተመሰረተ አንድነት ስር እንዲሰድ ከሰላም ሚኒስቴር ጋር የመግባቢያ ሰነድ በመፈራርም ትኩረት ሰጥቶ መሥራትን ጨምሮ በህዝበ ውሳኔ የምርጫ ስርዓት መሰረት ራሳቸውን መልሰው ያደራጁ አዳዲስ ክልሎች በውስጣቸው በሚገኙ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች መካከል ህብረ-ብሔራዊ አንድነታቸውን እንዲያጠናክሩ መድረክ በማዘጋጀት የተሳካ ሥራ መሠራቱን ጠቁመዋል፡፡

በተጨማሪም ከሚመለከታቸው የቀርቡ አቤቱታዎች በኢፌዴሪ ሕገ መንግስት፣ በአዋጅ ቁጥር 1261/2013 እንዲሁም በደንብ ቁጥር 3 አማካኝነት ጥናቶችን በማድረግ ሕገመንግሥታዊ ምላሽ እንዲያገኙ የማድረግ ስራ ትኩረቱ እንደነበር የጠቀሱት የተከበሩ አቶ ፍቅሬ እስከ ክልል ጭምር በመሄድ የድጋፍና ክትትል ሥራ በማጠናከር ወደ ምክር ቤቱ የሚመጡ አቤቱታዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሱ መምጣታቸውን ገልጸዋል፡፡

የማንነት፣ የአስተዳደር ወሰንና የሰላም ግንባታ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ጥላሁን ከበደ ቋሚ ኮሚቴው ለሚቀርቡ ጥያቄዎች ሕገ መንግሥቱንና ሌሎችን አሠራሮች በመከተል ሕገ መንግሥታዊ ምላሽ እንዲያገኙ ጥልቅ ምርመራ በማድረግ የውሳኔ ሃሳቦችን ለም/ቤቱ በማቅረብ እያስወሰነ ሲሠራ መቆየቱን በማስታወስ በቀጣይም የሚቀርቡ አቤቱታዎችን ሕጎችንና አሠራሮች በመከተል ወንድማማችነትንና አንድነትን በሚያጠናክር አግባብ ሕገ መንግሥታዊ ምላሽ እየሰጡ መሄድ እንዲሁም ከግጭት መከላከልና ከሰላም ዕሴት ግንባታ አንጻር ከሚመለከተው ጋር ተቀናጅቶ መሥራት የቋሚ ኮሚቴው ትኩረት እንደሚሆን ገልፀው የቋሚ ኮሚቴውን ያለፈውን መደበኛ ቃለ ጉባዔ እና የዕለቱን የመወያያ አጀንዳዎች በማጸደቅ ውይይቱን በይፋ አስጀምረዋል፡፡

የ2017 በጀት ዓመት አፈጻፀም ሪፖርት እና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ በዝርዝር ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተካሄዷል፡፡ ሪፖርቱና ዕቅዱ ለተከበረው ምክር ቤት ቀርቦ ውይይት ከተደረገበት በኋላ እንደሚጸደቅ ይጠበቃል፡፡

የማንነት፣ የአስተዳደር ወሰንና የሰላም ግንባታ ቋሚ ኮሚቴ በሕገ-መንግስቱ አንቀፅ 62፣48 እና 39 እንዲሁም የፌዴሬሽን ምክር ቤት ስልጣንና ተግባር ለመዘርዘር በድጋሚ ተሻሽሎ በወጣው አዋጅ ቁጥር 1261/2013 መሰረት የሕዝቦች ጥያቄ ሕገ መንግሥታዊ ምላሽ እንዲያገኝ ጥልቅ ምርመራ በማድረግ የውሳኔ ሃሳቦችን ለም/ቤቱ እንደሚያቀርብ ይታወቃል::

09/25/2025

እንኳን ለ2018ዓ.ም የዶንጋ ብሔረሰብ የዓመት መለወጫ ለሆነው ዶንጊ መሳላ አደረሳችሁ አደረሰን ፡፡

አዲሱን ዓመት የሰላም የጤና የፍቅር እንድሁም የብልጽግና ያድርግልን፡፡

በዓሉን ሲናከብር የተቸገሩትን በመርዳት እና ካለን ላይ አከፍሎ በማጉረስ ይሁን፡፡

መላው የሀደሮ ጡንጦ ዙሪያ ወረዳ እና አጎራባች ወረዳዎች እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን!!የጡንጦ ከተማ ማዘጋጃ የጡንጦ ከተማ ገበያ ከዛሬ መስከረም 15 2018ዓ.ም ጀምሮ በየሳምንቱ...
09/25/2025

መላው የሀደሮ ጡንጦ ዙሪያ ወረዳ እና አጎራባች ወረዳዎች እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን!!

የጡንጦ ከተማ ማዘጋጃ የጡንጦ ከተማ ገበያ ከዛሬ መስከረም 15 2018ዓ.ም ጀምሮ በየሳምንቱ ሐሙስ ሐሙስ የሚቀጥል መሆኑን ገልፀዋል ፡፡

የጡንጦ ከተማ ማዘጋጃ ከዛሬ ጀምሮ በየሳምንቱ ሐሙስ ሐሙስ የሚውለውን የከብት÷የፍየል ÷ የበግ እና የአህያ ተራን አስመርቆ ለገበያተኛው ክፍት አድርጓል ፡፡

በመሆኑም የአከባቢው ነዋሪዎች እና ነገዴዎች በዛሬው ዕለት የተመረቀውን የከብት÷የፍየል ÷ የበግ እና የአህያ ተራን በየሳምንቱ ሐሙስ በነፃ መጠቀም እንደምችሉ አብስሯል ፡፡

የዶንጋ ብሄረሰብ የልዩ ወረዳ መዋቅር ህገ መንግስታዊ መብት ተጠቃሚ ባለመሆኑ ምክንያት አሉታዊ ጫና እየደረሰበት ነው ሲል የዶንጋ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስ...
09/24/2025

የዶንጋ ብሄረሰብ የልዩ ወረዳ መዋቅር ህገ መንግስታዊ መብት ተጠቃሚ ባለመሆኑ ምክንያት አሉታዊ ጫና እየደረሰበት ነው ሲል የዶንጋ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል።

የዶንጋ ብሔረስብ በሰፈረበት ጂዮግራፊ ወይም አካባቢ በሚገኘዉ ወረዳና ከተማ አስተዳደር መዋቅር ፍትሃዊ አገልግሎት የማግኘት መብት ተነፍጓል ያለው ዶንጋ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ድርጅት የብሔረሰቡን ባህል ልብስ ለብሶ የመንቀሳቀስ ነጻነት ተነፍጓል፣ የዶንጋን ባህል ልብስ በመስቀል በዓል የለበሱ ወጣቶች የመታሰር በደል ደርሰባቸዋል ብሏል።

የመስቀል በዓል (ዶንግ መሳለ) በራስ መዋቅር የማክበር መብት ተነፍጓል የተባለ ሲሆን የራስን እድል በራስ የመወሰን መብት ተጠቃሚ እንዳይሆን ተደርጓል ሲሉ የፓርቲው ኃላፊዎች በመግለጫው ገልጿል።

ብሔረሰቡ በኢ.ፌ.ድ.ሪ ህገ-መንግሥት አንቀጽ 39 (3) የተደነገገዉንና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህገ-መንግሥት አንቀጽ 48 (3) የተደነገገዉን ህገ-መንግሥታዊ መብት እንዳላገኘ ነው የተናገሩት።

ስለሆነም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ህገ-መንግስቱን የመተርጎም ኃላፊነት ተጠቅሞ የዶንጋ ብሔረሰብ በልዩ ወረዳ የመደራጀት ህገ-መንግሥታዊ መብት ተጠቃሚ እንድያደርግ በአጽኖት እናሳስባለን ሲል የዶንጋ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ድርጅት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል።

Address

New York, NY

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when DONGA MEDIA NETWORK HADERO posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share