ዱባ ፔጅ

ዱባ ፔጅ

🚨 አስደንጋጭ ዜና! ከ60 ሚሊየን ብር በላይ ለመዝረፍ የሞከሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ! በጎፋ ዞን፣ ገዜ ጎፋ ወረዳ፣ በሐምሌ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በተከሰተው አስከፊ የመሬት መንሸ...
10/07/2025

🚨 አስደንጋጭ ዜና!
ከ60 ሚሊየን ብር በላይ ለመዝረፍ የሞከሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ!

በጎፋ ዞን፣ ገዜ ጎፋ ወረዳ፣ በሐምሌ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በተከሰተው አስከፊ የመሬት መንሸራተት አደጋ ሰለባ ለሆኑ ዜጎች ከተሰበሰበው የድጋፍ ገንዘብ ላይ ከ60 ሚሊየን ብር በላይ ለመዝረፍ የሞከሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የዞኑ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አስታወቀ።

* አደጋው በደረሰባቸው ወገኖች ህይወትና ችግር ለመበልጸግ ያሰቡት ተጠርጣሪዎች፣ ለተጎጂዎች የተሰበሰበውን 60,276,383 ብር ከጎፋ ዞን አደጋ ስጋት አካውንት ለመውሰድ ሞክረዋል።

* ገንዘቡን ለመዝረፍም ቀደም ሲል ቮይድ በተደረገ የቼክ ቁጥር (42221123) አስመስለው በማሳተም ሙከራ አድርገዋል።

* የወንጀል ሙከራው የተጋለጠው ከአዲስ አበባ ንግድ ባንክ ሸገር ቅርንጫፍ ለጎፋ ዞን አስተዳደር በተደረገ ፈጣን ጥቆማ ምክንያት ነው።

* በጥቆማው መሠረትም ከአዲስ አበባና ከክልል ፖሊስ ጋር በመተባበር፣ ገንዘቡ ሳይወጣ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ሊውሉ ችለዋል።

የዞኑ መንግሥት ኮሙኒኬሽን፣ ሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ የለገሰውን ድጋፍ 'ወደ ኪሴ ገብቶ ካልበለጸግኩ' በሚል አስተሳሰብ የተጠመዱ አካላት ያሰቡት "አስነዋሪና ስብዕና የጎደለው ተግባር" አለመሳካቱን ገልጿል።

⚠️ ማስጠንቀቂያ ለመገናኛ ብዙኃንና ለሕብረተሰቡ:
* ሐሰተኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡና ሕዝብን የሚያወዛግብ መረጃ ከማስተላለፍ እንዲቆጠቡ ተጠይቋል።

* ሕብረተሰቡም ትክክለኛና ተጨባጭ መረጃን ከመንግሥት ምንጮች ብቻ እንዲከታተል አሳስቧል።
የምርመራው ሂደት ሲጣራ ተጨማሪ መረጃ እንደሚሰጥም ተገልጿል።

09/28/2025

መልካም እድል ለስራ ፈላጊዎች
ስራ መስራት ለሚፈልጉ ታስቦ የተከፈተ ምርጥ ቻናል ነው አሁኑኑ ይቀላቀሉ
https://t.me/+TGc0J8ASCCRkYjU0

ወጣቶቹ የጠ/ሚ አብይ አህመድን 49ኛ ልደት ቲሸርት አሰርተው ኬክ ቆርሰው አክብረዋል።"ኑርልን ስንልህ ስለምንወድህ ብቻ ሳይሆን ስለምታስፈልገን ጭምር ነው" በማለት መልዕክት አስተላልፏል።
08/16/2025

ወጣቶቹ የጠ/ሚ አብይ አህመድን 49ኛ ልደት ቲሸርት አሰርተው ኬክ ቆርሰው አክብረዋል።
"ኑርልን ስንልህ ስለምንወድህ ብቻ ሳይሆን ስለምታስፈልገን ጭምር ነው" በማለት መልዕክት አስተላልፏል።

08/03/2025
ሕንድ በሚገኝ አንድ የህክምና ት/ቤት ውስጥ ፕሮፌሰሩ አናቶሚ ለመጀመሪያ አመት ተማሪዎች እያስተማሩ ነው።ትምህርቱ የሚሰጠው  አስክሬን ላይ ነው።ፕሮፋ ለተማሪዎቻቸው የሕክምና ዶክተር ስትሆኑ ...
07/08/2025

ሕንድ በሚገኝ አንድ የህክምና ት/ቤት ውስጥ ፕሮፌሰሩ አናቶሚ ለመጀመሪያ አመት ተማሪዎች እያስተማሩ ነው።
ትምህርቱ የሚሰጠው አስክሬን ላይ ነው።

ፕሮፋ ለተማሪዎቻቸው የሕክምና ዶክተር ስትሆኑ ሁለት መሰረታዊ የሆነ ባህሪያት ሊኖራችሁ ይገባል አሉ።-The 1st is that never be DISGUSTED about anything in the body." አሉ። በ ምሳሌ አስረዱ ጣታቸውን በ ሟች ANU$ ውስጥ አስገቡ ከዚያም ጣታቸውን አፋቸው ውስጥ አስገብተው ቀመሱት።

ከዚያም ተማሪዎቹን ተመሳሳሳይ ድርጊት እንዲፈፅሙ አዘዟቸው። ተማሪዎቹ ለብዙ ደቂቃዎች ካመነቱ በኾላ ሁሉም ጣቶቻቸውን በአስክሬኑ ANU$ ውስጥ አስገቡ እና መምህሩ እንዳደረጉት አደረጉ። ሁሉም ጣታቸውን ቀምሰው ሲጨርሱ ምን እንደሚሰማቸው ገምቱ......

Then the professor looked at them and said: "The most important 2nd Quality is "Observation". (ማስተዋል) ነው አሏቸው።
I inserted my MIDDLE finger but tasted the 2nd finger...
Now, learn to pay attention
እያስተዋልን

ሰኔ 16
06/23/2025

ሰኔ 16

06/23/2025

‼️ሰበር ሰበር ‼️
ኢራን በኳታር በሚገኘው የአሜሪካው አል-ዑደይድ የጦር ካምፕ ላይ ጥቃት ፈፅማለች።

የቴሌግራም መስራች እና ኃላፊ ለወለዳቸው መቶ ልጆች ሃብቱን ሊያወርስ ነውበዓለማችን ታዋቂ ከሆኑ የመረጃ መለዋወጫ መተግበሪያዎች አንዱ የሆነው ቴሌግራም መስራች እና ኃላፊ ፓቬል ዱሮቭ ለወለዳ...
06/20/2025

የቴሌግራም መስራች እና ኃላፊ ለወለዳቸው መቶ ልጆች ሃብቱን ሊያወርስ ነው
በዓለማችን ታዋቂ ከሆኑ የመረጃ መለዋወጫ መተግበሪያዎች አንዱ የሆነው ቴሌግራም መስራች እና ኃላፊ ፓቬል ዱሮቭ ለወለዳቸው 100 ልጆች 13.9 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ሃብቱን ሊያወርስ እንደሆነ አስታወቀ።
እነዚህ መቶ ልጆች የተወለዱት ከ15 ዓመት በፊት በለገሰው ስፐርም አማካኝነት መሆኑን ተናግሯል።
"ሁሉም ልጆቼ ናቸው እናም እኩል መብት ይኖራቸዋል። እኔ ከሞትኩ በኋላ እርስ በርሳቸው እንዲበጣበጡ አልፈለግም" ሲል ዱሮቭ ለፈረንሳዩ የፖለቲካ መጽሔት ለ ፖይንት ተናግሯል።
ፓቬል በአባትነት እያሳደጋቸው ያሉ ስድስት ልጆችን ከሶስት አጋሮቹ አፍርቷል።
ሆኖም እሱ እንደሚለው "ጓደኛዬን ለመርዳት ከአስራ አምስት ዓመት በፊት ስፐርም የለገስኩበት ክሊኒክ በ12 አገራት ከ100 በላይ ህጻናት በኔ ስፐርም እንደተጸነሱ ነግሮኛል" ብሏል።
ሩሲያዊው የቴክኖሎጂ ባለጸጋ ጨምሮ እንደተናገረው ልጆቹ ውርሳቸውን 30 ዓመት እስከሚሞላቸው ድረስ እንደማያገኙት ለመጽሄቱ ተናግሯል።
"አንደ ተራ ሰው እንዲኖሩ እፈልጋለሁ፤ በራሳቸው ህይወታቸውን እንዲገነቡ፣ በራሳቸው መተማመን እንዲማሩ እንዲሁም መፍጠር እንዲችሉ እንጂ በባንክ አካውንታቸው ላይ ጥገኛ እንዲሆኑ አልፈልግም" ሲል ተናግሯል።

የ40 ዓመቱ ወጣት አሁን ኑዛዜውን ማሰፈር ያስፈለገበት ምክንያት ከስራው ጋር በተያያዘ ያለውን አደጋ በመገንዘብ እንደሆነ ያስረዳል። "ነጻነትን መደገፍ ኃያላን መንግሥታትን ጨምሮ በርካታ ጠላቶችን ያተርፍልሃል" ይላል።
ሚስጥራዊ እና ግላዊነትን በጠበቀ መልኩ መረጃዎችን መለዋወጥ የሚያችለው ቴሌግራም ከአንድ ሚሊዮን በላይ ወርሃዊ ተጠቃሚዎች አሉት።

በፈረንሳይ ከቀረበበት ከባድ የወንጀል ክስ ጋር በተያያዘ ምንም አይነት ጥፋት እንዳልፈጸመም በድጋሚ ተናግሯል።
ኃላፊው መተግበሪያውን ወንጀል ለመከላከል ተገቢውን የመከላከል ስራ አልሰራም በሚል ባለፈው ዓመት በፈረንሳይ ክስ ተመስርቶበታል።
ከአደንዛዥ ዕጽ ዝውውር፣ የህጻናት ወሲባዊ ጥቃት ይዘት እና ማጭበርበር ጋር በተያያዘ ከህግ አስከባሪ አባላት ጋር እየተባባረ አይደለም የሚለውን ኃላፊው አጣጥሏል።
ቴሌግራም ከዚህ ቀደም በቂ የቁጥጥር እና የክትትል ስርዓት አልዘረጋም የሚለውን አልተቀበለውም።
ክሱን "ፍጹም እርባና የሌለው" ሲል የቴሌግራም ኃላፊው ለመጽሄቱ ተናግሯል።
"ወንጀለኞች የእኛን ጨምሮ ሌሎች መረጃ መለዋወጫ መተግበሪያዎችን ስለሚጠቀሙ እነዚህን መተግበሪያዎች የሚያስተዳድሩትን ወንጀለኛ አያደርጋቸውም" ሲል አክሏል።
በሩሲያ የተወለደው ፓቬል ቴሌግራም መቀመጫውን ባደረገበት ዱባይ ውስጥ ነው ነዋሪነቱ።
ፓቬል የፈረንሳይ እና የተባበሩት አረም ኤምሬትስ ጥምር ዜግነት አለው።
የሩሲያው ማህበራዊ ሚዲያ ቭኮንታኬ መስራች የሆነው ፓቬል ከዚህ ቀደም ክሬምሊን ጽሁፎችን ሳንሱር እንዲያደርግ የቀረበለትን ጥያቄ ውድቅ በማድረጉ ከዚህ ማህበራዊ ሚዲያ መባረሩን ተናግሯል።
ፓቬል ቴሌግራምን የመሰረተው በአውሮፓውያኑ 2013 ሲሆን መተግበሪያውም በሩሲያ ውስጥ ተወዳጅ ሆኖ ቆይቷል።
ቴሌግራም እስከ 200 ሺህ አባላት ያሉትን ቡድኖችን መመስረት ይፈቅዳል።

ይህም ተቺዎች የተሳሳተ መረጃ በቀላሉ እንዲሰራጭ እንዲሁም ለሴረኞች፣ የናዚ ደጋፊዎች፣ ህጻናት ደፋሪዎች እንዲሁም ከሽብር ጋር የተያያዙ ይዘቶች እንዲሰራጩ በር ከፍቷል ይላሉ።

ካሙዙ ካሳ
06/19/2025

ካሙዙ ካሳ

ኒውዮርክ ከድመቶች ጋር በጎዳና የሚኖረው ኢትዮጵያዊ በአካባቢው ዘ ካት ማን ተብሎ የሚጠራው ኢትዮጵያዊው እሸቴ ወልደ ይልማ ታሪክ ብዙዎችን እያነጋገረ ይገኛል።ለአንድ ዓመት በእግሩ ተጉዞ  ሱ...
06/19/2025

ኒውዮርክ ከድመቶች ጋር በጎዳና የሚኖረው ኢትዮጵያዊ

በአካባቢው ዘ ካት ማን ተብሎ የሚጠራው ኢትዮጵያዊው እሸቴ ወልደ ይልማ ታሪክ ብዙዎችን እያነጋገረ ይገኛል።

ለአንድ ዓመት በእግሩ ተጉዞ ሱዳን የስደተኞች መጠለያ የደረሰው እሸቴ በስደተኞች መጠለያም አምስት ዓመት ቆይቶ ከዛም ከዛሬ 40 ዓመት በፊት የአሜሪካን ምድር ሊረግጥ ችሏል።

አሁን ላይ በኒው ዮርክ ጎዳ ላይ ከድመቶች ጋር እየኖረ ያለው እሸቴ ጎዳና ከመውጣቱ በፊት በአንድ የግንባታ ድርጅት ውስጥ እየሰራ በደረሰበት አደጋ ለዓመታት ሆስፒታል ሕክምና ለመከታተል ይገደዳል።

ከዛም በኃላ ኑሮ ጎዳና ሆኗል።

ስለ እሸቴ ሕይወት፣ ለድመቶች ስላለው ልዩ ፍቅር እና የፍቅር ታሪኩ እንዲሁም አኗኗሩ የሚተርከው “The Cat Man Eshete” የተሰኘ ዘጋቢ ፊልም በአልጄዚራ ዊትነስ ተሠርቶለት ለዕይታ በቅቷል።

እሸቴ አብረውት የሚኖሩትን ድመቶች ቤተሰቦቼ ናቸው የሚል ሲሆን ሁሉንም በስማቸው ይጠራቸዋል።

ከድመቶቹ ቀድሞ በፍፁም ምግብ እንደማይበላም ዘጋቢ ፊልሙ ላይ ተናግሯል።

በእስራኤል በርካታ ተከታይ ያለው ኃይማኖት ምንድነው ብለን ስንጠይቅ የሚከተለውን መረጃ አግኝተናል።  1ኛ አይሁዶች 7.1 ሚሊዮን (73.6%)2ኛ ሙስሊም 1.7 ሚሊዮን (18.1%)3ኛ ክርስቲ...
06/18/2025

በእስራኤል በርካታ ተከታይ ያለው ኃይማኖት ምንድነው ብለን ስንጠይቅ የሚከተለውን መረጃ አግኝተናል።


1ኛ አይሁዶች 7.1 ሚሊዮን (73.6%)
2ኛ ሙስሊም 1.7 ሚሊዮን (18.1%)
3ኛ ክርስቲያን 180 ሺህ (1.9%) ከጎንደር
4ኛ ድሩዝ 151 ሺህ (1.6%)
ቀሪው 4.8% ኃይማኖት የለውም።

Address

New York, NY

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ዱባ ፔጅ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share