NEXT ADDIS

NEXT ADDIS

ምንሊክ ተወልዶ ባያነሳ ጦሩን፣  ........................................በሉ እስኪ ጨርሱት!እንኳን አደረሰን፣ አደረሳችሁ!!via : fasil shiferaw
03/02/2025

ምንሊክ ተወልዶ ባያነሳ ጦሩን፣
........................................

በሉ እስኪ ጨርሱት!
እንኳን አደረሰን፣ አደረሳችሁ!!

via : fasil shiferaw

እንኳን አደረሳችሁ ኢትዮጵያውያን🔥🫡   #አድዋ
03/02/2025

እንኳን አደረሳችሁ ኢትዮጵያውያን🔥🫡

#አድዋ

03/01/2025

😍 ባቡሩ እንዴት ይፈጥናል 2 ሰዓት ብቻ ነው የሚፈጀው

ሁሌ ሳስታውሰው ሰውነቴን የሚያንቀጠቅጠኝን፣ በመደነቅ የሚሞላኝን የጀግንነት ታሪክ ላጋራችሁ (repost)ደጃዝማች አያሌው ብሩ ፣ በሰሜን ጎንደር  በኩል የሚዋጉ ወታደሮቻቸውን አሰልፈው የጦር...
02/23/2025

ሁሌ ሳስታውሰው ሰውነቴን የሚያንቀጠቅጠኝን፣ በመደነቅ የሚሞላኝን የጀግንነት ታሪክ ላጋራችሁ (repost)

ደጃዝማች አያሌው ብሩ ፣ በሰሜን ጎንደር በኩል የሚዋጉ ወታደሮቻቸውን አሰልፈው የጦር መሳሪያ ለሌለው እያደሉ እያለ እንዲህ ሆነ፣

“ የአስራ ስምንት ዓመት ልጅ በኩራት መንፈስ ዱላውን በቀኝ ትክሻው ላይ አድርጎ ይንጎራደድ ነበር። ዱላው የእንጨት ሲሆን ቀይ ቀለም ያለው ሆኖ እላዩ ላይ ጌጥ ተቀርፆበታል። የዚህ ወጣት ልጅ የተለየ ኩራት እና አካሄድ የሰዎችን አይን የመሳብ ችሎታ ፈጥሯል።

ደጃዝማችም አስጠሩትና ...
"በዚህ የሚያምር ዱላህ ምን ልታደርግበት ነው? "
"በዚህ ዱላ ነጭ ልገልበት ነው።"
"እንደሱ እንኳን ማድረግ አትችልም፣ በምትኩ ጠመንጃ ልስጥህ"
"የለም አመሰግናለሁ ፤ ለአባቴ የማልኩት ቃለ መሀላ ጣልያን ገድዬ ፣ ጠመንጃውን ወስጄ አሳያለሁ ፤ አለዚያ በዚህ በጦር ሜዳ እቀራለሁ”

እናመሰግናለን ኮርታችሁ መላውን የጥቁር ህዝብ ያኮራችሁ ጀግኖች አባት አርበኞቻችን

02/07/2025

💚 እናትዋ ጎንደር = ጎንክ - ልደር 🔥 💛 ❤️

ሀኪሙን አትግደሉ!(Whoever you are!)( የዶ/ር ወዳጄነህ መሐረነ መልዕክት)አንድ የህክምና ዶክተር የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ ሆኖ ሳለ ባብዛኛው ሰቃይ የሚባል የደረጃ ተማሪ ስለሆነ እውቀ...
02/04/2025

ሀኪሙን አትግደሉ!
(Whoever you are!)
( የዶ/ር ወዳጄነህ መሐረነ መልዕክት)

አንድ የህክምና ዶክተር የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ ሆኖ ሳለ ባብዛኛው ሰቃይ የሚባል የደረጃ ተማሪ ስለሆነ እውቀትን ለመሰብሰብ፣ አንደኝነቱን ለማስጠበቅ በትጋት ይማራል፣ በር ዘግቶ ያጠናል።

ዩኒቨርሲቲ ገብቶ ኮመን ኮርሶችን ካለፈ በኋላ ለማጥናት እጅግ ጊዜ የሚፈጁ እንደ አናቶሚ (Anatomy)፣ ፊዚዬሎጂ (Physiology)፣ ባዬኬሚስትሪ (Biochemistry)፣ ፋርማኮሎጂ (Pharmacology)፣ ፓቶሎጂ (Pathology) ማይክሮባዬሎጂ (Microbiology) የመሳሰሉ ኮርሶችን አንገቱን ደፍቶ ይማራል፣ ሌት ተቀን ያጠናል።

በሌሎች ካምፓሶች ያሉ ጓደኞቹ ዘና ፈታ ሲሉ የህክምና ተማሪው ግን ጊዜ የለውም። ገርል ፍሬንድ፣ የዳንስ ምሽት፣ የሙዚቃ ኮንሰርት ብሎ ነገር አያውቅም።

እነዚህን ትምህርቶች በብዙ ትጋት ከጨረሰ በኋላ ክሊኒካል አመታት ይጠብቁታል ። የውስጥ ደዌ ህክምና፣ የቀዶ ጥገና፣ የማህፀንና ፅንስ፣ የህፃናት ህክምና፣ የአእምሮ ህክምና፣ የቆዳ የአይን ወ.ዘ.ተ የህክምና አይነቶችን ይማራል። ህሙማንንም ይጎበኛል። ከዚያም ኢንተርን ዶክተር ይሆናል።

ኢንተርን ሀኪም ሆኖ ሌት ተቀን ነው ስራው። ተረኛ ሆኖ አድሮ ጠዋት ወደ ቤቱ አይሄድም። ደክሞት፣ ርቦት ስራውን ይቀጥላል። ጊዜ መምጣቱ አይቀርምና የምርቃቱ ቀን ሲደርስ የህክምና ዶክተር ሆኖ ይመረቃል።

ሀኪሙ ገጠር ተመድቦ እጅግ ትንሽ በሚባል ደሞዝ በቀን ከ 30 እስከ 40 የሚደርሱ ታማሚዎችን ያክማል። አሁንም ለመዝናናት ጊዜ የለውም። የቀንም የሌሊትም ተረኛ ሀኪም እሱው ነው።

የገጠር አገልግሎቱን ከጨረሰ በኋላ ስፔሻሊስት ለመሆን ተመልሶ ወደ ዩኒቨርሲቲ ይመጣል። እረፍት የሌለባቸው አራት አመታትን ያሳልፋ። እንደዚህ ነው ስፔሻሊስት ሀኪም የሚሆነው። ሰብ ስፔሻሊስት ለመሆን ደግሞ ተጨማሪ አመታት በሀገር ውስጥ ወይም በውጪ ሀገር መስራት ይኖርበታል።

በዚህ ሁሉ ዶክተሩ ለመዝናናት ፋታ የለውም። ለወሬ፣ ለአሉባልታ፣ ለአላስፈላጊ ንትርክ ጊዜ የለውም። ትኩረቱ ህመምተኞቹ ናቸው። እርካታው የእነርሱ መዳን ነው።

ሀኪም እርስ በርሱ አይወዳደርም፣ ምቀኝነት አያውቅም። አንዱ ዶክተር ወደ ሌላው ዶክተር "ለተሻለ ህክምና " ብሎ ታማሚውን በሪፈራል ይልካል። በተለየ ትጋት ለታማሚዎ ይደክማል።

ዶክተር አንዷለም ዳኜ ስፔሻሊስት ብቻ አልነበረም። ሰብ ስፔሻሊስት ነበር። በእርሱ ደረጃ ያሉ ሀኪሞች ኢትዬጵያ ውስጥ ጥቂት ናቸው። በብዙ ወረፋ ነው የሚገኙት። ዶ/ር አንዷለም ኑሮውን በአሜሪካ አድርጎ ቢሆን ኖሮ በአመት ከ 200 እስከ 300 ሺ ዶላር ይከፈለው ነበር። በዚያ እንዳሉ ጓደኞቻችን ትልቅ ቤት ገዝቶ የአሜሪካንን ከፍ ከፍ ያሉ መኪኖች በሩ ላይ ይደረድር ነበር። እርሱ ግን ህዝቤን፣ ወገኔን ባገለግል ይሻላል ብሎ በሀገሩ መኖርን መረጠ፣ በባህር ዳር ከተመ። የድሆች ፈጥኖ ደራሽ፣ የሚስኪኖች መድሃኒታቸው ሆነ።

ምን አይነት የደነቆረ አእምሮ ነው የእርሱን ሞት የሚያቅደው?
ምን አይነት የአውሬ አይን ነው እርሱን በክፉ የሚመለከተው ? ምን አይነት የተረገመ ጣት ነው በእርሱ ላይ ቃታ የሚስበው? ምን አይነት ክፏ አጋንንት ነው በእርሱ ሞት ሀሴት የሚያደርገው? በተወደደ ሃኪም ሞት ምን ትርፍ ይገኛል? የልጆች አባትን መግደል እንዴት ድል ይሆናል?

እንዴት ነው ህዝብን አያገለገሉ ያሉ የህክምና ዶክተሮች ለግድያ የሚታጩት ? ለምንድን ነው የህክምና ባለሙያዎች በፍርሃት የሚኖሩት? እነርሱኮ የቆሰለ ሰው ሲመጣ የመንግስት ወታደር ይሁን፣ የፋኖ ታጣቂ ይሁን፣ የሸኔ ታጣቂ ይሁን ያለ ልዩነት ያክማሉ፣ ለመዳኑ ሌት ተቀን ይለፉለታል።

እባካችሁ ሀኪሙን አትግደሉት ! የጤና ባለሙያውን አታስጨንቁ ! መምህሩ ላይ አትተኩሱ ! ይልቁን መንግስትም ሆነ በተያየ ቦታ ያሉ ታጣቂዎች ለባለሙያው ጥበቃ ማድረግ ነው ያለባችሁ። ያልታጠቁ ሰዎችን መግደል የትም ሀገር ጀግንነት ሆኖ አያውቅም! ይህ ፅሁፍ የሚያስቆጣው ካለ ገዳይነቱን መሰከረ!

እግዚአብሔር ኢትዬጵያን ያስባት። የዶክተሩንም ልጆች ፈጣሪ ያሳድግለት።

ማንም ሁኑ ማን (whoever you are) ሀኪሙን አትግደሉ! 🙏

በሀገራችን ከጥቂት የሰብ ስፔሻሊስት ሐኪሞቻችን ውስጥ አንዱ የሆኑት ዶክተር አንዷለም ዳኘ ተገደሉበባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጠቅላላ ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስት እና የጉ...
02/02/2025

በሀገራችን ከጥቂት የሰብ ስፔሻሊስት ሐኪሞቻችን ውስጥ አንዱ የሆኑት ዶክተር አንዷለም ዳኘ ተገደሉ

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጠቅላላ ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስት እና የጉበት፣ የቆሽት እና የሃሞት መስመር ሰብ ስፔሻሊት ሃኪም፣ ተመራማሪ እና መምህር እንዲሁም በጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የቀዶ ሕክምና አገልግሎት ክፍል ዳይሬክተር የነበሩት ዶ/ር አንዷለም ዳኘ ጠብቀው በተወለዱ በ37 አመታቸው በደረሰባቸው ድንገተኛ ሞት የተሰማንን መሪር ሃዘን እየገለፅን ለሟች ቤተሰቦች፣ ጓደኞች፣ የሥራ ባልደረቦች እና ለመላው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ መፅናናትን እንመኛለን።

ዶ/ር አንዷለም በዩኒቨርሲቲያችን፣ ብሎም በአገራችን አሉን ከምንላቸው በቁጥር ትንሽ የዘርፉ ሰብ ስፔሻሊስት ሐኪሞቻችን ውስጥ አንዱ የነበሩ ሲሆን ከስራ ውለው ወደቤታቸው ሲመለሱ በአጋጠማቸው ግድያ ህይወታቸውን አጥተዋል። በሐኪማችን ላይ ያጋጠመውን ግድያ እና በተደጋጋሚ በዩኒቨርሲቲው ሰራተኞች ላይ እየደረሰ ያለውን ተደጋጋሚ ያልተገባ መሰል ድርጊት ባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ በጥብቅ ያወግዛል። በየትኛውም አካል ሊሰነዘር የሚችል ይሄን አይነት መሰል ድርጊትም ለአገርም ሆነ ለወገን ጉዳይ እንጅ አንዳች የሚጨምር ነገር እንደሌለ ሁሉም ሊገነዘበው የሚገባ ጉዳይ ነው።

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

02/02/2025

😂 የብረት መዝጊያ አማች 😂 😀

ቡና → Ethiopian buna ceremony
02/01/2025

ቡና → Ethiopian buna ceremony

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ 70ኛ ዓመት እና የአጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 100ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል በድምቀት እየተከበረ ነው።በምሥረታ በዓሉ መርሐ ግብር የተገኙበት የትምህርት ሚኒስትሩ ብር...
01/23/2025

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ 70ኛ ዓመት እና የአጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 100ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል በድምቀት እየተከበረ ነው።

በምሥረታ በዓሉ መርሐ ግብር የተገኙበት የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) እንደገለጹት ዩንቨርሲቲዎች የምርምር ስራ የሚሰሩ ሰላማዊ ስፍራዎች ናቸው።

የትምህርት ሚኒስትር ዩንቨርስቲዎች ራስ አገዝ እንዲሆኑ ለሪፎርም ስራ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ገልፀው ዩንቨርስቲዎች ራስ አገዝ ሲሆኑ የፈጠራ እና የምርምር ስራቸው የተሻለ እንዲሆን እድል ይፈጥራል ብለዋል። የትምህርት ስርዓቱን በማዘመን ተደራሽ እና አካታች እንዲሆን እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ አንጋፋ ዩንቨርሲቲዎች መካከል የጎንደር ዩንቨርስቲ አንዱ ነው ያሉት ሚኒስትሩ በዓሉን ስናከብር ተቋሙ ለኢትዮጵያ ያበረከተውን በማሰብ የተሰሩ ስራዎችን በማድነቅ ያልተሰሩትን በቁጭት ለመፈጸም መሆኑን ገልጸዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በ70 ዓመት እድሜው በኢትዮጵያ እውቀትና ፈጠራ እንዲስፋፋ በማድረግ ፈር ቀዳጅ ተቋም ነው ብለዋል።

ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ እድገት የምንሰራበት በዓል መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ የአጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታሉ ለኢትዮጵያ ጤና አጠባበቅ ስርዓት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያን ዘላቂ ልማት በማሳለጥ የጎላ አበርክቶ እንዳለው ገልጸው፣ በቀጣይ ለሁለንተናዊ እደገት ያለው አበርክቶ ተጠናክሮ እንዲቀጥ አሳስበዋል።

የጎንደር ዩንቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አስራት አፀደወይን (ዶ/ር) በበኩላቸው የአጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታሉ ለመመስረት ምክንያት የሆነው በደንቢያ የወባ በሽታ መስፋፋትና ህዝቡ በበሽታው መጠቃቱን ተከትሎ መሆኑን ገልጸዋል።
ተቋሙ በህክምና አገልግሎትና በምርምር ስራው ባሻገር ለማህበረሰቡ ከፍተኛ አሰተዋጽኦ ማድረጉን ገልጸዋል።

የጎንደር ዩንቨርስቲ ለትምህርት ጥራት ለማሻሻል በርካታ ስራዎች በተሰራው በርካታ ለውጦች የተገኙ ቢሆንም በቀጣይም በርካታ ስራዎች እንደሚጠብቃቸው ገልጸዋል።

የምስረታ በዓሉ መርሐ ግብር ህብረተሰቡን መሰረት ያደረገ መሆኑን ፕሬዚዳንቱ ገልፀዋል።

የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባና የዩንቨርስቲው የቦርድ አባል አቶ ቻላቸው ዳኘው የከተማው ህዝብ የእኔ ብሎ ለሚያስበው ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ 70ኛ ዓመት እና የአጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 100ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች ከጎንደር ዩንቨርስቲ ጎን መሆናቸውን አቶ ቻላቸው ገልጸዋል።

በመርሀ ግብሩ ላይ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ፣የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው ዳኘው፣የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አስራት አፀጸወይን (ዶ/ር)፣የቀድሞ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

💥💥💥
04/29/2024

💥💥💥

የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ይሆናልአዲስ አበባ፣ መስከረም 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ እንደሚሆ...
10/08/2023

የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ይሆናል

አዲስ አበባ፣ መስከረም 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ እንደሚሆን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ሚኒስቴሩ ተማሪዎች ትክክለኛውን መረጃ ከትምህርት ሚኒስቴር ገጽ ላይ እንዲከታተሉም አሳውቋል፡፡

Address

New York, NY

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when NEXT ADDIS posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category

ETHIOBRANA

MEDIA AND ENTERATMENT