NEXT ADDIS

NEXT ADDIS

ኤችአይቪ ኤድስ ቫይረስ በደማቸው ውስጥ ከሚገኝባቸው ሰዎች አብዛኛዎቹ ሴቶች መሆናቸው ተገለፀበኢትዮጵያ ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ ከሚገኝባቸው 573ሺ ሰዎች መካከል የሴቶች ቁጥር ከፍተኛ መሆኑን...
12/02/2025

ኤችአይቪ ኤድስ ቫይረስ በደማቸው ውስጥ ከሚገኝባቸው ሰዎች አብዛኛዎቹ ሴቶች መሆናቸው ተገለፀ

በኢትዮጵያ ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ ከሚገኝባቸው 573ሺ ሰዎች መካከል የሴቶች ቁጥር ከፍተኛ መሆኑን የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ አስታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት ባጠናው ጥናት መሰረት በአዲስ አበባ 3.1 በመቶ የኤችአይቪ ኤድስ ቫይረስ ስርጭት መኖሩን ገልጿል፡፡

የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ሀላፊ ዶክተር ዮሀንስ ጫላ የኤድስ ቀን በማስመልከት ባስተላለፉት መልእክት የቫይረሱን ስርጭት ለመከላከል በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ቢሆንም ብዙ የሚቀሩ ነገሮች መኖራቸው ነው፡፡

በከተማው በቫይረሱ የተያዙ ከመቶ ሺ በላይ ሰዎች መኖራቸውን የገለፁት ሀላፊው በበሽታው አዲስ ከሚያዙ እና የሞት መጠን ላይ የሴቶች ቁጥር ከፍተኛ መሆኑን አንስተዋል፡፡

ከእናት ወደ ልጅ ቫይረሱን ለመከላከል የሚሰራው ስራ የተሻለ ውጤት የታየበት መሆኑን በመግለፅ በተለይም በትምህርት ቤቶች እና ከትምህርት ቤት ውጪ በአፍላ ወጣቶች ላይ የሚስተዋልውን መዘናጋት ሁሉም በትብብር ሊሰራበት እንደሚገባም አስገንዝበዋል፡፡

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙ ተማሪዎች ስለ ቫይረሱ ያላቸውን ግንዛቤ እንዲያሳድጉ ካሁን ቀደም የነበሩ ስራዎች መጠናከር ይገባቸዋል ተብሏል፡፡

መናኸሪያ ሬዲዮ

የእስራኤል ጠ/ሚኒስትር ለቀረበባቸው የሙስና ክስ የይቅርታ ጥያቄ አቀረቡጥያቄውን የአገሪቱ ተቃዋሚዎች ነቅፈውታል  የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ለቀረበባቸው የሙስና ክስ የይ...
11/30/2025

የእስራኤል ጠ/ሚኒስትር ለቀረበባቸው
የሙስና ክስ የይቅርታ ጥያቄ አቀረቡ

ጥያቄውን የአገሪቱ ተቃዋሚዎች ነቅፈውታል

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ለቀረበባቸው የሙስና ክስ የይቅርታ ጥያቄያቸውን ለሐገሪቱ ፕሬዚዳንት አቀረቡ። ኔታንያሁ የተመሰረተባቸው የሙስና ወንጀል ክስ እንዲሰረዝላቸው ነው የይቅርታ ጥያቄ ያቀረቡት፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፅሕፈት ቤት ዛሬ ባወጣው መግለጫ፤ በቤንጃሚን ኔታንያሁ ላይ የተመሰረተው የሙስና ክስ ሐገሪቱን ክፉኛ መከፋፈሉን ጠቁሞ፤ ረዥም ጊዜ የወሰደው የክስ ሂደት ዶሴ መዘጋቱ ለሐገሪቱ ብሔራዊ አንድነት እንደሚጠቅም አስታውቋል፡፡

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቅርቡ እስራኤልን በጎበኙበት ወቅት፣ የእስራኤል ፕዚዳንት አይዛቅ ሔርዞግ፣ ለኔታንያሁ ምህረት እንዲያደርጉ መጠየቃቸው ይታወሳል፡፡

ይህ በዚህ እንዳለ፣ የኔታንያሁ የይቅርታ ጥያቄ ከሐገሪቱ ተቃዋሚዎች ብርቱ ነቀፌታን አስከትሏል። ጥያቄው የሐገሪቱን የዴሞክራሲ ተቋማት የሚያዳክምና እሳቸው ከህግ በላይ መሆናቸውን የሚያሳይ አደገኛ ምልክት ነው በሚል ተችተውታል፡፡

ሆንግ ኮንግ የሦስት ቀናት ሀዘን  አወጀችቻይና በረጃጅም ፎቆች ላይ የእሳት አደጋ ደህንነት ፍተሻ ጀመረችሆንግ ኮንግ በከተማዋ የደረሰውን  እጅግ አስከፊ የእሳት አደጋ ተከትሎ፣ ከዛሬ ጀምሮ ...
11/29/2025

ሆንግ ኮንግ የሦስት ቀናት ሀዘን አወጀች

ቻይና በረጃጅም ፎቆች ላይ የእሳት አደጋ ደህንነት ፍተሻ ጀመረች

ሆንግ ኮንግ በከተማዋ የደረሰውን እጅግ አስከፊ የእሳት አደጋ ተከትሎ፣ ከዛሬ ጀምሮ የሶስት ቀናት የሃዘን አውጃለች፡፡

ባለፈው ረቡዕ በሆንግ ኮንግ ዋንግ ፉክ ኮርት በተባለ የመኖሪያ ህንፃ በተከሰተውና ከ40 ሰአታት በላይ በቆየው የእሳት አደጋ፤ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 128 መድረሱን ባለሥልጣናቱ አርብ ከሰአት በኋላ የገለጹ ሲሆን፤ መርማሪዎቹ ግን ህንፃዎቹ ውስጥ ተጨማሪ በአደጋው የሞቱ ሰዎች ሊገኙ እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል።

ከአስርት ዓመታት ወዲህ አስከፊ ነው በተባለው የእሳት አደጋ፣ እስካሁን በትንሹ 150 ሰዎች የጠፉ በመሆናቸው የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ ይችላል ተብሎ ይጠበቃል።

በሆንግ ኮንግ ቅዳሜ ዕለት ይፋዊና የሶስት ቀናት የሐዘን ጊዜ መጀመሩን ተከትሎም፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በከተማይቱ በደረሰው ከባድ የእሳት ቃጠሎ ለሞቱ 128 ሰዎች አበቦችና በእጅ የተፃፉ የመታሰቢያ መልዕክቶችን ማስቀመጣቸውን ቀጥለዋል።

በአደጋው የሞቱ ሰዎችን ለማሰብ ዛሬ ቅዳሜ ጧት የሆንግ ኮንግ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጆን ሊን ጨምሮ ከፍተኛ ባለስልጣናት ከመንግስት ዋና መሥሪያ ቤት ፊትለፊት ለሶስት ደቂቃ ያህል የህሊና ፀሎት አድርገዋል። እስከ ሰኞ ድረስ በሁሉም የመንግስት ህንጻዎች ሰንደቅ አላማ በግማሽ ዝቅ ብለው ይውለበለባል።

ቃጠሎውን ተከትሎ ቻይና በመላ ሀገሪቱ ሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች ላይ የእሳት ደህንነት ቁጥጥር ዘመቻ እያካሄደች ነው።
የዘመቻው ትኩረትም በውጭ በኩል የግድግዳ እድሳትና የውስጥ ማሻሻያ በሚያደርጉ ህንጻዎች ላይ እንደሚሆንም የአደጋ ጊዜ አስተዳደር ሚኒስቴር ዛሬ ቅዳሜ በሰጠው መግለጫ ማስታወቁን ዶቸ ቬለ ዘግቧል።

“ገቢ ለመሰብሰብ” በሚል የተዘረጉ ኬላዎች “በፍጥነት እንዲነሱ” ትዕዛዝ ተላለፈበአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች “ገቢ ለመሰብሰብ” በሚል የተዘረጉ ኬላዎች “በፍጥነት እንዲነሱ” የክልሉ ገቢ...
11/28/2025

“ገቢ ለመሰብሰብ” በሚል የተዘረጉ ኬላዎች
“በፍጥነት እንዲነሱ” ትዕዛዝ ተላለፈ

በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች “ገቢ ለመሰብሰብ” በሚል የተዘረጉ ኬላዎች “በፍጥነት እንዲነሱ” የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ትዕዛዝ ሰጠ። ይህን ትዕዛዝ ተላልፎ በተገኘ ማንኛውም የመንግስት አካል ላይ የጸጥታ ኃይሎች ለሚወስዱት “እርምጃ”፤ ቢሮው ኃላፊነት የማይወስድ መሆኑንም አስታውቋል።

ቢሮው ይህንን ያሳወቀው፤ በክልሉ የዞንና የከተማ አስተዳደር ስር ላሉ የገቢዎች መምሪያዎች ከትላንት በስቲያ ረቡዕ ህዳር 17 ቀን 2018 በጻፈው ደብዳቤ ነው። መስሪያ ቤቱ ትዕዛዙን ለመምሪያዎቹ ያስተላለፈው፤ የአማራ ክልልን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች “ገትተዋል” የተባሉ ኬላዎች እንዲነሱ ከክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ደብዳቤ ከተጻፈለት ከአንድ ሳምንት ገደማ በኋላ ነው።

በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የተቋቋሙ ኬላዎች የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርት እንቅስቃሴን “ሲያስተጓጉሉ” እና “ሲያዘገዩ” እንደነበር በደብዳቤው የጠቀሰው የክልሉ ገቢዎች ቢሮ፤ “ያልተገባ ክፍያ በማስከፈል” የምርት ዋጋ እንዲጨምር ማድረጋቸውን አትቷል። እነዚህ ድርጊቶች “የኑሮ ውድነትን በማባባስ”፤ በሸማቾች ላይ ጫና ማሳደራቸውንም ደብዳቤው አክሏል።

በአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የከተማ አገልግሎት ገቢ ባለሙያ የሆኑት አቶ አሰፋ ወርቅዬ፤ ዞኖችና ከተሞች ኬላዎችን ሲያቋቋሙ የነበረው “ገቢን ለመሰብሰብ በሚደረግ ጥረት” እንደነበር ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አስረድተዋል። ሆኖም በተወሰኑ ኪሎሜትሮች ልዩነት የሚቋቋሙ ኬላዎች መበራከታቸው የአሽከርካሪዎች “መጉላላት” ማስከተሉን እንዲሁም በእነዚህ ቦታዎች የሚጠየቁ ክፍያዎች “የምርት ዋጋ ጭማሪ እንዲኖር ማድረጉን” አብራርተዋል።

የጠፈር ተመራማሪዎችን ቆይታ ለማቅለል ያለመው የጠፈር ላይ እርሻሳይንቲስቶች ወደ ጨረቃና ማርስ ለተልዕኮ የሚሄዱ የጠፈር ተመራማሪዎች ጤናማ ቆይታ እንዲኖራቸው የሚያስችል ዕቅድ አውጥተዋል። ዕ...
11/28/2025

የጠፈር ተመራማሪዎችን ቆይታ ለማቅለል
ያለመው የጠፈር ላይ እርሻ

ሳይንቲስቶች ወደ ጨረቃና ማርስ ለተልዕኮ የሚሄዱ የጠፈር ተመራማሪዎች ጤናማ ቆይታ እንዲኖራቸው የሚያስችል ዕቅድ አውጥተዋል። ዕቅዱ ጠፈር ላይ እፅዋት ማብቀል ሲሆን፣ ይህም የጠፈር ተመራማሪዎች ከምድር በሚመጡ የምግብ አቅርቦቶች ላይ ብቻ ጥገኛ እንዳይሆኑ ያደርጋል።

በዚህም ጠፈርተኞች ጠፈር ላይ የበቀሉ ትኩስ ምግቦችን እንዲያገኙ ከማስቻሉም ባለፈ፣ እፅዋቱን በመጠቀም ውኃንና አየርን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል የጠፈርተኞችን ጤና ለመጠበቅ ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል ተብሏል፡፡

እፅዋቶቹ የተፈለገውን አቅርቦት ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን በየጊዜው ለመፈተሽ ደግሞ "ባዮሬጀነሪ ላይፍ ሰፖርት ሲስተም" (BLSS) የተሰኘ ማዕቀፍ አቋቁመዋል።

ፕሮጀክቱ ከተለያዩ አገሮችና የጠፈር ኤጀንሲዎች የተውጣጡ ከ40 በላይ ሳይንቲስቶችን በማሰባሰብ ጥልቅ የጠፈር ምርምር እየተደረገበት ይገኛል። ከዚህ ባሻገር ፕሮጀክቱ "ናሳ" ከአፖሎ 17 ተልዕኮ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ሰዎችን ወደ ጨረቃ ለመውሰድ የነደፈው የ"አርቴሚስ" 3 ተልዕኮ አካል ነው።

እ.ኤ አ 2027 በሚደረገው በዚህ ተልዕኮ አራት የጠፈር ተመራማሪዎች ወደ ጨረቃ ምህዋር ይጓዛሉ ተብሎ ሲጠበቅ ፤ ዋናው ግብ ናሙናዎችን መሰብሰብ ፣ አዲስ የሳይንስ ምርምር ማካሄድና ይህን ፕሮጀክት ማስፋፋት መሆኑን ኢቢሲ አስነብቧል፡፡

የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ዕለታዊ ሁኔታህዳር 19/ 2018 Marburg Virus Disease Daily update Ethiopia November 28/ 2025 Ministry of Health,Et...
11/28/2025

የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ዕለታዊ ሁኔታ
ህዳር 19/ 2018
Marburg Virus Disease Daily update
Ethiopia
November 28/ 2025

Ministry of Health,Ethiopia
Ethiopian Public Health Institute

ከሆንግ ኮንግ የእሳት አደጋ ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ 11  ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉበአደጋው 128 ሰዎች ሲሞቱ፤ ከ200 በላይ ሰዎች  የገቡበት አልታወቀምበሆንግ ኮንግ የ128 ሰዎችን ሕ...
11/28/2025

ከሆንግ ኮንግ የእሳት አደጋ ጋር በተያያዘ
የተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ

በአደጋው 128 ሰዎች ሲሞቱ፤ ከ200 በላይ ሰዎች የገቡበት አልታወቀም

በሆንግ ኮንግ የ128 ሰዎችን ሕይወት ከቀጠፈው የእሳት አደጋ ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ ተጨማሪ ስምንት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ የሀገሪቱ ገለልተኛ የጸረ ሙስና ኮሚሽን (ICAC) እንዳስታወቀው÷ በቁጥጥር ስር የዋሉት ግለሰቦች ከአደጋው በፊት ሲከናወን ከነበረው የህንጻዎች መልሶ ጥገና ሂደት ጋር በተያያዘ በመጠርጠራቸው ነው።

ተጠርጣሪዎቹ ጥገናውን የሚያካሂደው የኢንጂነሪንግ ኩባንያ ዳይሬክተርን ጨምሮ የንዑስ ኮንትራክተሮች ሰራተኞች እንዳሉበት ተነግሯል። የአደጋውን መድረስ ተከትሎ ቀደም ሲል ሦስት ሰዎች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን፤ አሁን ላይ ተጨማሪ ስምንት ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተካሄደ ይገኛል።

የደረሰው ከባድ አደጋ መንስኤው ምን እንደሆነ እስካሁን በግልጽ ባይታወቅም፣ ለህንጻው መልሶ ጥገና ተብሎ ተወጥሮ የነበረ ተቀጣጣይነት ያለው የፕላስቲክ መረብ አደጋውን አስከፊ አድርጎታል። የአደጋውን ምክንያት ለማጣራት ፖሊሶች ወደ ህንፃው በመግባት ምርመራ እያደረጉ ሲሆን፤ በሚቀጥሉት ሳምንታት ውስጥ ውጤቱ ይፋ እንደሚደረግ ተመላክቷል፡፡

በሆንግ ኮንግ ባለፈው ረቡዕ በጋራ መኖሪያ ቤት ሕንጻዎች ላይ በተከሰተው የእሳት አደጋ 128 ሰዎች ሲሞቱ፤ ከ200 በላይ ሰዎች ደግሞ እስካሁን የገቡበት አልታወቀም ተብሏል፡፡

ከ4 ሺህ 600 በላይ ሰዎች በሚኖሩባቸው ሕንጻዎች የተከሰተውን የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ማዋል የተቻለ ሲሆን፤ በክስተቱ ላይ የሚደረገው ማጣራት እንደቀጠለ ነው፡፡ አደጋው ከመድረሱ በፊት ሁሉም ሕንጻዎች ላይ የተገጠሙ የእሳት አደጋ የጥንቃቄ መልዕክት መሳሪያዎች አገልግሎት እየሰጡ እንዳልነበር መገለጹን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ከ100 ቢ. ብር በላይ በመሰወር የተጠረጠሩ የስፖርትአወራራጅ ድርጅት ባለቤቶችና ተባባሪዎቻቸው ተያዙ ለመንግሥት ገቢ መሆን የነበረበትን ከ100 ቢሊየን ብር በላይ በመሰወር ወንጀል የተጠረጠሩ...
11/28/2025

ከ100 ቢ. ብር በላይ በመሰወር የተጠረጠሩ የስፖርት
አወራራጅ ድርጅት ባለቤቶችና ተባባሪዎቻቸው ተያዙ

ለመንግሥት ገቢ መሆን የነበረበትን ከ100 ቢሊየን ብር በላይ በመሰወር ወንጀል የተጠረጠሩ የስፖርት አወራራጅ ድርጅት ባለቤቶችና ተባባሪዎቻቸው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ፡፡

አገልግሎቱ እንደገለጸው፤ በቤቲንግ የስፖርት አወራራጅ ድርጅቶችና ፊንቴክ ወይም አግሪጌተር በሚባሉ የገንዘብ ክፍያ ስርዓት አቅራቢ ተባባሪ ተቋማት ዙሪያ ጥናትና ክትትል ሲከናወን ቆይቷል፡፡

ፈቃድ ያላቸውና ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር በገቡት ውል መሰረት የማይሠሩ፣ በሕገ-ወጥ ድርጊት ተሰማርተው በመገኘታቸው ፈቃዳቸው የተሰረዘባቸው እንዲሁም ምንም አይነት ፈቃድ ሳይኖራቸው በስፖርት አወራራጅነት ተሰማርተው የነበሩ አካላት በዓለም አቀፍ የኢንተርኔት ትስስር አማካይነት በሕገ-ወጥ ድርጊት ተሰማርተው መገኘታቸው ተገልጿል።

የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት፣ የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት፣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ፣ የአዲስ አበባና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች የፀጥታ አካላት እንዲሁም በኅብረተሰቡ ትብብር አማካኝነት 24 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን መግለጫው አስታውቋል፡፡

በተለይ በሕጋዊነት ሽፋን ፈቃድ ያወጡት ድርጅቶች ላይ ክትትል ለማድረግ ሙከራ በተደረገበት ወቅት ሁሉም ፈቃድ ሲያወጡ ይዘውት ከነበረው ቢሮ መልቀቃቸውና አድራሻቸውን መሰወራቸው ተረጋግጧል፡፡

የቤቲንግ የስፖርት አወራራጅ ድርጅቶቹ ፊንቴክ ወይም አግሪጌተር ተብለው ከሚጠሩ የፋይናንስ ስርዓቶችን ከሚያሳልጡላቸው የሀገር ውስጥ የክፍያ ስርዓት አቅራቢ ተቋማት ጋር በመመሳጠር በአጠቃላይ ሲያንቀሳቅሱት ከነበረው የገንዘብ መጠን መንግሥት በተለያዩ የገቢ አማራጮች ማግኘት የነበረበትን 100 ቢሊየን ብር በላይ መሰወራቸው እንደተደረሰበት አመላክቷል፡፡

የቤቲንግ የስፖርት አወራራጅ ድርጅቶቹ በተለያዩ የገንዘብ ክፍያ ስርዓቶች አማካይነት የሚሰበስቡትንና የሚያዘዋውሩትን የገንዘብ መጠን ያማከለ ግብር አለመክፈላቸው እንደተደረሰበት የጠቆመው መግለጫው÷ በክሪፕቶከረንሲና በተለያዩ ዓለም አቀፍ የሃዋላ ገንዘብ ማስተላላፊያ አማራጮች አማካኝነት የሚያገኙትን ገቢ በውጭ ምንዛሪ በመቀየር ሲሰውሩና ከሀገር እንዲወጣ ሲያደርጉ መቆየታቸውን አስታውቋል፡፡

ፊንቴክ ወይም አግሪጌተር የሚባሉት የሀገር ውስጥ የገንዘብ ክፍያ ስርዓት አቅራቢ ተቋማቱ ከብሔራዊ ባንክ ፈቃድ በመውሰድ የሚንቀሳቀሱ ቢሆንም፤ የደንበኛን ምስጢር መጠበቅ የሚል ሙያዊ አሠራርን እንደ ሽፋን ተጠቅመው የቤቲንግ የስፖርት አወራራጅ ድርጅቶች የሚያንቀሳቅሱትን የገንዘብ መጠን ከሚመለከታቸው የመንግሥት አስፈፃሚ ተቋማት በመደበቅ ወይም አሳንሶ በማቅረብ በግብር ስወራ እንዲሁም ከፍተኛ የሀገር ሀብትን ወደ ውጭ በማሸሽ ወንጀል ላይ ተሳትፎ እንዳላቸው የአገልግሎቱ መግለጫ አብራርቷል፡፡

የተለያዩ ሀገራት ዜግነት ያላቸው ግለሠቦች ጭምር ከኢትዮጵያ ውጪ ሆነው ሀገር ውስጥ ለሚገኙ ተባባሪዎቻችው ውክልና በመስጠት ሕገ-ወጥ ድርጊቱን ሲፈጸሙ መቆየታቸው እንዲሁም ውጭ ሀገር የበለጸጉ ሶፍትዌሮች ጥቅም ላይ መዋላቸውና ድርጅቶቹ ቋሚ አድራሻ የሌላቸው መሆኑ ወንጀሉን ውስብስብና ለቁጥጥር አስቸጋሪ አድርጎት ቢቆይም፣ የደኅንነት ተቋሙ ከሌሎች የመረጃና የጸጥታ አካላት ጋር በመተባበር ባደረጉት ስምሪት ተጠርጣሪዎቹ መያዛቸው ተመላክቷል፡፡

በሕገ ወጥ ድርጊቱ ከሀገር ሲሸሽ የነበረው ከፍተኛ ገንዘብ ሽብርተኝነትንና ጸረ ሰላም ቡድኖችን በገንዘብ ለመደገፍ፣ በሕገ-ወጥ መንገድ የተገኘን ገንዘብ ሕጋዊ ለማስመሰል እንዲሁም ለኮንትሮባንድ ንግድ ማካሄጃ እንደሚውል የጠቆመው መግለጫው፤ ሀገራዊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን በመጻረር የኢትዮጵያን ብሔራዊ ደኅንነትና ጥቅሞች ስጋት ላይ ለመጣል የሚደረግ እንቅስቃሴ አካል በመሆኑ ዜጎች ማንኛውም አይነት ተመሳሳይ እንቅስቃሴዎች ሲመለከቱ ለደኅንነትና ጸጥታ አካላት የሚሰጡትን ጥቆማ አጠናክረው እንዲቀጥሉ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በመግለጫው አመላክቷል ሲል ኤፍኤምሲ ዘግቧል፡፡

የሩሲያ ኃይሎች የዩክሬኑን ኩፒያንስክን መቆጣጠራቸውን ከፍተኛ ወታደራዊ ባለሥልጣን ተናገሩእስካሁን ሩሲያ የዩክሬንን ግዛት 19% ያህል ተቆጣጥረዋል : የሩሲያ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ሐሙ...
11/28/2025

የሩሲያ ኃይሎች የዩክሬኑን ኩፒያንስክን መቆጣጠራቸውን ከፍተኛ ወታደራዊ ባለሥልጣን ተናገሩ

እስካሁን ሩሲያ የዩክሬንን ግዛት 19% ያህል ተቆጣጥረዋል : የሩሲያ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ሐሙስ ዕለት ለፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን እንደተናገሩት የሩሲያ ኃይሎች በሰሜን ምስራቅ ዩክሬን የምትገኘውን የኩፒያንስክ ከተማን ተቆጣጥረዋል

ዩክሬን በበኩሏ ሩሲያ ኃይል ለወራት ለመያዝ ስትጥርበት የነበረችውን የሎጂስቲክስ ማዕከል የሆነችውን ፖክሮቭስክን እና ከሩሲያ ድንበር አቅራቢያ የምትገኘውን ቮቭቻንስክን ጨምሮ በሁለት ሌሎች ከተሞች ሰፊ ክፍሎችን መያዟን የሚገልጹ የሩሲያ መግለጫዎችን ውድቅ አድርጋለች።

ክሬምሊን ቀደም ሲል እንደገለጸው ፑቲን የሩሲያ ኃይሎች "ምዕራብ" የተሰኘውን የቡድን አዛዥ ጽሕፈት ቤት ጎብኝተው የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ቫለሪ ገራሲሞቭን እና ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖችን አግኝተዋል።

ፑቲን በዩክሬን ምስራቅ በሚገኙ ሁለት ቁልፍ ከተሞች ኮስትያንቲኒቭካ እና ክራማቶርስክ እንዲሁም በካርኪቭ ክልል ዙሪያ በምትገኘው ኩፒያንስክ ዙሪያ ስላለው ሁኔታ መግለጫ እንደተሰጣቸው ክሬምሊን ተናግሯል።

"የ'ምዕራብ' ቡድን ክፍሎች የኩፒያንስክን ከተማ ነፃ አውጥተዋል በኦስኮል ወንዝ ግራ ዳርቻ የተከበቡትን የዩክሬን የታጠቁ ኃይሎችን መደምሰሳቸውን ቀጥለዋል" ሲሉ ገራሲሞቭ በክሬምሊን ድረ-ገጽ ላይ በተለጠፈ ቪዲዮ ላይ ለፑቲን ተናግረዋል።

ገራሲሞቭ በወታደራዊ ልብስ ከለበሱት ፑቲን ፊት ለፊት በከፍተኛ መኮንኖች መካከል ተቀምጠው የሩሲያ ኃይሎች የፖክሮቭስክን 70% መቆጣጠራቸውን ለፕሬዚዳንቱ ነግረዋቸዋል ።

የቮቭቻንስክ ከ 80% በላይ የሚሆነው ክፍልም በሩሲያ ቁጥጥር ስር መሆኑን ገልጸዋል።
በ1,200 ኪሎ ሜትር የፊት መስመር ላይ ከባድ ውጊያ እየተካሄደ ያለው በፖክሮቭስክ አቅራቢያ መሆኑን የገለጹት ገራሲሞቭ የዩክሬን ኃይሎች "ጠንካራ ተቃውሞ" እያሳዩ እንደሆነ ተናግረዋል።

ቪዲዮው ከፑቲን ጋር የተደረገው ስብሰባ በትክክል የት እንደተካሄደ ግልጽ አላደረገም።

የዩክሬን ጦር ሠራዊት በሰጠው የዘገየ የምሽት መግለጫ ላይ የዩክሬን ታጣቂ ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጽሕፈት ቤት ኩፒያንስክ በዩክሬን መከላከያ ኃይሎች ቁጥጥር ስር መሆኗን አስታውቋል

በካርኪቭ ክልል የሚገኘው የቮቭቻንስክ 80% እና የፖክሮቭስክ ከተማ 70% መያዛቸውን የሚጠቁሙ መግለጫዎችም እውነት አይደሉም ሲል አክሏል።

ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጽሕፈት ቤት በፖክሮቭስክ አካባቢ ከባድ ውጊያ መኖሩን የዘገበ ሲሆን የሩሲያ ኃይሎች 56 ጥቃቶችን እንደፈጸሙም ተገልጿል።

የሩሲያ ኃይሎች ሙሉውን ዶንባስ የዶኔትስክ እና የሉሃንስክ ክልሎችን ለመያዝ የሚያደርጉትን ዘመቻ አካል በመሆን በዶኔትስክ ክልል በኩል ወደ ምዕራብ መግፋት ቀጥለዋል።

የሩሲያ ኃይሎች በቅርቡ በዛፖሪዝሂያ ክልል ወደ ደቡብም ተጨማሪ ድሎችን አስመዝግበዋል

በአሁኑ ጊዜም ሩሲያ የዩክሬንን ግዛት 19% ያህል ይዘዋል።

በኢትዮጵያ ሉሲ በኖረችበት ዘመን እንደኖረ የተገመተ አዲስ ቅሪተ አካል ተገኘ👉 "የሉሲ የቅርብ ዘመድ'' የሚል ስያሜ የተሰጠው ቅሪተ አካል የ3 ነጠብ 4 ሚሊዮን ዓመት ዕድሜ እንዳለው ተነግሯ...
11/28/2025

በኢትዮጵያ ሉሲ በኖረችበት ዘመን እንደኖረ የተገመተ አዲስ ቅሪተ አካል ተገኘ

👉 "የሉሲ የቅርብ ዘመድ'' የሚል ስያሜ የተሰጠው ቅሪተ አካል የ3 ነጠብ 4 ሚሊዮን ዓመት ዕድሜ እንዳለው ተነግሯል

3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዓመት ገደማ ዕድሜ ያለው ቅሪተ አካል በአፋር ክልል መገኘቱን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን አስታውቋል።

ባለስልጣኑ ከተመራማሪዎች ጋር በመሆን ግኝቱን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጠው መግለጫ፤ ቅሪተ አካሉ የተገኘው በአፋር ክልል "ወረንሰ ሚሌ" ተብሎ በሚጠራው አካባቢ መሆኑ ተገልጿል።

ግኝቱን ይፋ ያደረጉት በአሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪ የሆኑት ዮሐንስ ኃይለሥላሴ (ፕ/ር)፤ አዲሱ ግኝት የ3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዓመት ዕድሜ እንዳለውና ይህም “ሉሲ” (ድንቅነሽ) በኖረችበት ዘመን ይኖር እንደነበር አመላካች ነው ብለዋል፡፡

በዚህም ምክንያት ለቅሪተ አካሉ ''የሉሲ የቅርብ ዘመድ'' የሚል ስያሜ እንደተሰጠው ተናግረዋል፡፡

በአፋር ክልል በተለያዩ የጥናት ጣቢያዎች መሰል ምርምሮች እየተካሄዱ መሆኑን የጠቆሙት ተመራማሪው፤ የተገኘው ቅሪተ አካል በሰው ዘር የለውጥ ሒደት (Evolution) ኢትዮጵያ የሰው ዘር መገኛ መሆኗን ዳግም ያረጋገጠ መሆኑን አብራርተዋል ሲል ኢብኮ ዘግቧል፡፡

የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አበባው አያሌው በበኩላቸው፤ መሰል የምርምር ግኝቶች ኢትዮጵያ ምድረ ቀደምትና የሰው ዘር መገኛ መሆኗን የሚያጠናክሩ ናቸው ብለዋል፡፡

የሉሲ ወይም የድንቅነሽ ቅሪተ አካል በሕዳር ወር 1967 ዓ.ም. በአፋር ክልል “ሃዳር” በተባለ ቦታ መገኘቱ ይታወሳል፡፡

በሐምሌ ወር 2017 የአሪዞና ስቴት ዩኒቨርስቲ የሳይንቲስቶች እና የተመራማሪዎች ቡድን 2 ነጥብ 8 ሚሊየን ዓመት የሚጠጋ ዕድሜ ያለውና የሰው ልጅን አመጣጥ አስረጂ የሆነ አዲስ የአውስትራሎፒቴከስ ዝርያ እና የሆሞ ቅሪተ አካላት፤ በአፋር ክልል ልዩ ሥሙ "ሌዲ ገራሩ" በተባለ የፓሊዮአንትሮፖሎጂ የጥናት ስፍራ ባደረጉት ምርምር ማግኘታቸው መገለጹም አይዘነጋም፡፡

© አሐዱ ሬዲዮ

ከቻይና ባንክ ለቢሾፍቱ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ግንባታ  500 ሚሊዮን ዶላር ተገኘ የቻይና ባንክ በቢሾፍቱ የሚገነባውን አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ግንባታ ለመደገፍ 500 ሚሊዮን ዶላር እ...
11/27/2025

ከቻይና ባንክ ለቢሾፍቱ አለም አቀፍ አየር
ማረፊያ ግንባታ 500 ሚሊዮን ዶላር ተገኘ

የቻይና ባንክ በቢሾፍቱ የሚገነባውን አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ግንባታ ለመደገፍ 500 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያቀርብ መግለጹን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አስታወቁ። ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ይህን የገለጹት በሞሮኮ ራባት እየተካሄደ ባለው የአፍሪካ ኢንቨስትመንት ፎረም ላይ ነው።

አቶ መስፍን ገንዘቡን የሚያቀርበው ባንክ የትኛው እንደሆነ ባይገልጹም፣ ይህ ድጋፉ ግን ለአየር ማረፊያው ግንባታ ስራ በጣም ወሳኝ ነው ብለዋል።

በአቡ ሴራ አካባቢ የሚገነባው የቢሾፍቱ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ፣ 12.5 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ወጪ የሚጠይቅ ሲሆን፤ ይህም የመሬት ግዢና የአካባቢው ነዋሪዎች ካሳን ያካትታል ተብሏል። ለግንባታ ስራው የሚውለው 8 ቢሊዮን ዶላር በግል ባለሀብቶች የሚቀርብ መሆኑም ተገልጿል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ለፕሮጀክቱ ግንባታ የሚሆን በቂ ገንዘብ ለመሰብሰብ ከብዙ የፋይናንስ ተቋማት ጋር ድርድር እያደረጉ መሆናቸውን አስታውቀዋል። "ከመካከለኛው ምስራቅ፣ ቻይና፣ ህንድ፣ አውሮፓና ከሰሜን_አሜሪካ ጋር እየተነጋገርን ነው፣ እያገኘን ያለነው ምላሽም ጥሩ ነው" ማለታቸውን አለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

🇺🇸 ነጩ ቤተ-መንግስት አቅራቢያ የተፈፀመው የተኩስ እሩምታ ሁለት የብሔራዊ ጥበቃ ወታደሮች በጽኑ ቆስለዋል ተጠርጣሪውም ቆስሏልሁለት የአሜሪካ የብሔራዊ ጥበቃ ወታደሮች ረቡዕ እለት ዋሽንግተን...
11/27/2025

🇺🇸 ነጩ ቤተ-መንግስት አቅራቢያ የተፈፀመው የተኩስ እሩምታ

ሁለት የብሔራዊ ጥበቃ ወታደሮች በጽኑ ቆስለዋል ተጠርጣሪውም ቆስሏል

ሁለት የአሜሪካ የብሔራዊ ጥበቃ ወታደሮች ረቡዕ እለት ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው ነጩቤተ-መንግስት አቅራቢያ በጥይት ተመተዋል።

ፕሬዝዳንት ትራምፕ እርምጃ እንደሚወስዱ ማረጋገጫ ሲሰጡ ተኳሹም መጎዳቱን አረጋግጠዋል።

ፖሊስ እንዳለው ክስተቱ የተፈጸመው ከህንጻው ጥቂት ብሎኮች ርቆ ብዙ የነጩ ቤተ-መንግስት ሰራተኞች በሚሰሩበት የአይዘንሃወር ስራ አስፈፃሚ ቢሮ ህንጻን ጨምሮ በ17ኛ ስትሪት ሰሜን ምዕራብ እና አይ ስትሪት ሰሜን ምዕራብ መገናኛ አቅራቢያ ነው።

እንደ ዩኤስ ቱዴይ እና ሌሎች በርካታ የአሜሪካ መገናኛ ብዙሃን ዘገባ ከሆነ ክስተቱ ከተፈጸመ በኋላ ነጩ ቤተ-መንግስት ዝግ እንዲሆን ተደርጏል

የመንግስት ባለስልጣናት ዋናውን የገንዘብ ግምጃ ቤት (Main Treasury) እና የፍሪድማን ባንክ ሕንፃን (Freedman’s Bank Building) ጭምር እንዲዘጉ (lockdown) ትዕዛዝ እንደሰጡ ተዘግቧል።

ትራምፕ በመግለጫቸው ሁለቱን የብሔራዊ ጥበቃ ወታደሮች በጥይት የመታው እንዲሁም ሁለቱም በጽኑ ቆስለው አሁን በተለያዩ ሆስፒታሎች ውስጥ የሚገኙ ሲሆን እሱም በከፍተኛ ሁኔታ ቆስሏል ነገር ግን ያለምንም ማመንታት እጅግ በጣም ከባድ ዋጋ ይከፍላል ብለዋል።

Address

New York, NY

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when NEXT ADDIS posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

ETHIOBRANA

MEDIA AND ENTERATMENT