NEXT ADDIS

NEXT ADDIS

  አይኔፍ በ2025 ግሪጎርያን ካላንደር በአፍሪካ ከፍተኛ እድገት ያስመዘግባሉ ላቸውን የአፍሪካ ሀገራት እንደሚከተለው አውጦል።በዚህም ሀገራችን ኢትዮጵያን በቁጥር አንደኛ አድርጎ አስቀምጧታል...
09/23/2025

አይኔፍ በ2025 ግሪጎርያን ካላንደር በአፍሪካ ከፍተኛ እድገት ያስመዘግባሉ ላቸውን የአፍሪካ ሀገራት እንደሚከተለው አውጦል።
በዚህም ሀገራችን ኢትዮጵያን በቁጥር አንደኛ አድርጎ አስቀምጧታል ።

1. 🇪🇹 ኢትዮጵያ: 6.6%
2. 🇰🇪 ኬንያ: 4.8%
3. 🇲🇦 ሞሮኮ: 3.9%
4. 🇪🇬 ግብፅ: 3.8%
5. 🇩🇿 አልጄሪያ: 3.5%
6. 🇳🇬 ናይጄሪያ: 3%
7. 🇿🇦 ሳውዝ አፍሪካ: 1%

..................................

ኤምባሲው አሜሪካውያን  የኢትዮጵያን የኢሚግሬሽን  ህጎች እንዲያከብሩ አሳሰበ"ኢትዮጵያ ውስጥ በምትቆዩበት ጊዜ በህጋዊ ሁኔታ መቆየት በጣም አስፈላጊ ነው"''ጤና ይስጥልኝ ኢትዮጵያን የምትጎበ...
09/23/2025

ኤምባሲው አሜሪካውያን የኢትዮጵያን
የኢሚግሬሽን ህጎች እንዲያከብሩ አሳሰበ

"ኢትዮጵያ ውስጥ በምትቆዩበት ጊዜ በህጋዊ
ሁኔታ መቆየት በጣም አስፈላጊ ነው"

''ጤና ይስጥልኝ ኢትዮጵያን የምትጎበኙ የአሜሪካ ዜጎች!

የእናንተ አምባሳደር እንደመሆኔ መጠን፣ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ወይም ኢትዮጵያን የሚጎበኙ ሁሉም አሜሪካውያን፣ በዚህ አስደናቂ ሀገር ባላቸው ቆይታ ተገዢ የሚሆኑባቸውን የሀገሪቱን ህጎች እንዲያውቁ እና እንዲዘጋጁ በማድረጌ ክብር ይሰማኛል። ዛሬ እዚህ የሚገኙ ሁሉንም የአሜሪካ ዜጎች የሚመለከት አንድ ወሳኝ ጉዳይ ላይ ማተኮር እፈልጋለሁ፤ ይኸውም የኢትዮጵያን የኢሚግሬሽን ህጎች ማክበር ነው።

በህዳር 2017 (እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር) የኢትዮጵያ መንግስት የቪዛ ጊዜ አሳልፎ መቆየትንና ህገወጥ ስደትን ለመቀነስ ሲል፣ የቪዛ ጊዜ አሳልፎ የሚቆይ ግለሰብ የሚጣልበትን የገንዘብ ቅጣት፣ በአንድ ቀን ወደ 30 የአሜሪካ ዶላር አሳድጓል፤ ይህም በፍጥነት ሊጠራቀም የሚችል ነው። የኢትዮጵያ ኢሚግሬሽን ባለስልጣናት ቪዛ አሳልፎ በመቆየት የገንዘብ ቅጣት ያለባቸው የአሜሪካ ዜጎች ዕዳቸውን ሙሉ በሙሉ በዶላር እስኪከፍሉ ድረስ ከአገር እንዳይወጡ ለመከልከል እንደሚችሉ እባክዎ ልብ ይበሉ። የአሜሪካ ኤምባሲ ቪዛ አሳልፎ በመቆየት ምክንያት የሚጣለውን የገንዘብ ቅጣት ለመክፈል ብድር የመስጠት ፍቃድ ከአሁን በኋላ የለውም።

ስለዚህ በኢትዮጵያ ለቱሪስት ቪዛ ከሚፈቀደው 30 ወይም 90 ቀናት በላይ መቆየት ከፈለጉ ቪዛዎ ከማብቃቱ በፊት ከኢትዮጵያ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና መስሪያ ቤት የቪዛ ማራዘሚያ ወይም የመኖሪያ ፈቃድ (በተለምዶ “ቢጫ ካርድ” የሚባለውን) ይጠይቁ።

እዚህ ኢትዮጵያ የተወለዱና የአሜሪካን ፓስፖርት እንደ ብቸኛ መታወቂያቸው የሚጠቀሙ ልጆችን ጨምሮ የውጭ ፓስፖርት ያላቸው ሁሉም ልጆች ለቪዛ አሳልፎ የመቆየት ቅጣት ተገዢ ናቸው። ስለዚህ እባክዎ በኢትዮጵያ የሚገኙ የአሜሪካ ዜግነት ያላቸው ልጆች የአሜሪካ ፓስፖርታቸው ውስጥ የፀና የኢትዮጵያ ቪዛ ወይም “ቢጫ ካርድ” እንዳላቸው ያረጋግጡ።

በኢትዮጵያ የምትገኙ አሜሪካውያን ሁሉ የኢትዮጵያን የኢሚግሬሽን ደንቦች እንድታከብሩ እና ቪዛዎቻችሁን እና/ወይም የመኖሪያ ፈቃዶቻችሁን ጊዜ ከማለፉ በፊት እንድታሳድሱ አሳስባለሁ። የውጭ ዜጎች በአሜሪካ ውስጥ ሲሆኑ ለአሜሪካ ህጎች ተገዢ እንደሚሆኑ ሁሉ፣ በውጭ ሀገር በምትሆኑበት ጊዜ ለምትገኙበት ሀገር ህጎች ተገዢ መሆናችሁን አስታወሱ። ኢትዮጵያ ውስጥ በምትቆዩበት ጊዜ በህጋዊ ሁኔታ መቆየት በጣም አስፈላጊ ነው። ይህ እንደ ዓለም አቀፍ ዜጋ ያለባችሁ ግዴታና ኃላፊነት ሲሆን፤ ከዚህም በላይ ገንዘባችሁን ለመቆጠብ ብልህ ውሳኔ ነው።

ለዚህ ወሳኝ ጉዳይ ትኩረት ስለሰጣችሁ አመሰግናለሁ። መልካም ቀን!'' –

አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ

አፍጋኒስታናዊው ታዳጊ በአውሮፕላን ጎማ ሥር ተደብቆ ሕንድ ገባየ13 ዓመቱ አፍጋኒስታናዊ ታዳጊ በመንገደኞች አውሮፕላን ጎማ ሥር ተደብቆ ከአፍጋኒስታን መዲና ካቡል ተነስቶ ኒው ደልሂ ገባ።በሰ...
09/23/2025

አፍጋኒስታናዊው ታዳጊ በአውሮፕላን ጎማ ሥር ተደብቆ ሕንድ ገባ

የ13 ዓመቱ አፍጋኒስታናዊ ታዳጊ በመንገደኞች አውሮፕላን ጎማ ሥር ተደብቆ ከአፍጋኒስታን መዲና ካቡል ተነስቶ ኒው ደልሂ ገባ።
በሰሜናዊ አፍጋኒስታን በምትገኘው ኩንዱዝ ከተማ ነዋሪ የሆነው ታዳጊው ሰኞ ዕለት አውሮፕላኑ በሕንድ በደልሂ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ካረፈ በኋላ በማኮብኮቢያው ሥፍራ ሲዘዋወር መገኘቱን ባለሥልጣናት ተናግረዋል።
ታዳጊው በሕንድ የፀጥታ አካላት በቁጥጥር ሥር ውሎ ለበርካታ ሰዓታት በፖሊስ ከተጠየቀ በኋላ በተመሳሳይ በረራ ወደ ካቡል እንዲመለስ ተደርጓል።
ታዳጊው አደገኛ ጉዞውን ያደረገው በመጓጓት የተነሳ እንደሆነ በተደጋጋሚ ለባለሥልጣናቱ መናገሩ ተገልጿል።
የሕንድ ማዕከላዊ ኢንደስትሪ የጸጥታ ኃይል ቃል አቀባይ እንዳሉት ታዳጊው የበረራ ቁጥሩ አርኪው- 4401 በሆነው የካም አየር መንገድ አውሮፕላን ምንም በማይታወቅ ሁኔታ ተደብቆ ደልሂ ገብቷል።

ከዚያም በአካባቢው ብቻውን ሲዘዋወር በፖሊስ መገኘቱንና ለጥያቄ መወሰዱን ቃል አቀባዩ አክለዋል።
ታዳጊው በተደጋጋሚ የአውሮፕላኑን የኋላ ጎማ በሚይዘው ክፍል ውስጥ ተደብቆ መጓዙን ለባለሥልጣናት ተናግሯል።
በአውሮፕላኑ ላይ ተጨማሪ ፍተሻ የተደረገ ሲሆን የአየር መንገዱ ሰራተኞች ቀይ ቀለም ያለው ትንሽ የድምጽ ማጉያ [ ስፒከር] አግኝተዋል።
የ13 ዓመቱ ታዳጊ ወደ ኢራን መጓዝ ፈልጎ እንደነበርና የገባበት አውሮፕላን ወደ ቴህራን ሳይሆን ወደ ሕንድ መዲና ደልሂ የሚበር መሆኑን እንደማያውቅ ዘ ኢንዲያን ኤክስፕረስ ጋዜጣ ዘግቧል።
እንደ ጋዜጣው ዘገባ ከሆነ ታዳጊው ካቡል አየር ማረፊያ የተወሰኑ ተሳፋሪዎችን ተከትሎ ሾልኮ በመግባት የአውሮፕላኑን የማረፊያ ጎማ በያዘው ክፍል ውስጥ ነበር ገብቶ የተቀመጠው።
በወቅቱ ይዞት የነበረውም ቀይ ቀለም ያለው የድምጽ ማጉያ ብቻ ነበር።
በቅርብ ጊዜያት ብዙውን ጊዜ አገራቸውን ጥለው ለመውጣት እና ወደ አሜሪካ አሊያም አውሮፓ ለመግባት የተደረጉ ተመሳሳይ ክስተቶች አጋጥመዋል። ሆኖም ከዚህ መሰል አደገኛ ጉዞ በሕይወት የሚተርፉት ጥቂቶች ናቸው።
ባለሙያዎች እንደሚሉት በእንደዚህ ዓይነት መልኩ ተደብቀው የሚጓዙ ሰዎች አውሮፕላኑ በሚያርፍበት ወቅት ራሳቸውን የሚስቱ ሲሆን የአውሮፕላኑ ጎማ በሚወርድበት ወቅትም ለሞት ሊዳርግ የሚችል የመውደቅ አደጋ ያጋጥማቸዋል።
እንደ አውሮፓውያኑ 2022 የ22 ዓመቱ ኬንያዊ በኔዘርላንድስ አምስተርዳም ከእቃ ጫኝ አውሮፕላን ጎማ ውስጥ በሕይወት መገኘቱ ይታወሳል።

ዝናቡ ይቀጥላል!..በሚቀጥሉት አስር ቀናት አብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ  በሚቀጥሉት አስር ቀናት አብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ከቀላል እስከ መካ...
09/23/2025

ዝናቡ ይቀጥላል!..

በሚቀጥሉት አስር ቀናት አብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ

በሚቀጥሉት አስር ቀናት አብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።

በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ እንዲሁም መካከለኛ የሀገሪቱ ክፍሎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች እንደሚጠቁሙ ኢንስቲትዩቱ አስታውቋል።

የምዕራብ፣ መካከለኛው እና ደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ ክፍሎች አልፎ አልፎ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ጠቁሟል።
በሌላ በኩል በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት የደቡብና ደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ ክፍሎች ከቀላል እስከ መካከለኛ ደረጃ ያለው የዝናብ መጠን እንደሚያገኙ ይጠበቃል ብሏል።

በሚቀጥሉት አስር ቀናት በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብ፣ በሰሜን፣ በሰሜን ምዕራብ እንዲሁም በመካከለኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ርጥበት ይኖራቸዋል ብሏል።
ይህም በአመዛኙ ለግብርና ስራ እንቅስቃሴ አዎንታዊ ሚና እንዳለው ጠቁሟል።
በአብዛኞቹ ተፋሰሶች ላይ ከመጠነኛ እስከ ከፍተኛ መጠን ያለው የገጸ ምድር የውሃ ፍሰት እንደሚጠበቅ ትንበያዎች እንደሚያሳዩ ተመላክቷል።
የአባይ፣ የባሮ አኮቦና የኦሞ ጊቤ ተፋሰሶች ላይ ከመካከለኛ እስከ ከፍተኛ ርጥበት የገጸ ምድር ውሃ እንደሚያገኙም አመላክቷል፡፡

በተመሳሳይ ገናሌ ዳዋ፣ ዋቤ ሸበሌ፣ የታችኛው ኦሞ ጊቤና የአዋሽ ተፋሰስ ከቀላል እስከ መካከለኛ ርጥበት እንዲሁም የዋቤ ሸበሌ ተፋሰስ ቀላል መጠን ያለው የገጸ ምድር ውሃ እንደሚኖራቸው ጠቅሷል።

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ት/ቤት የ12ኛ ክፍል ፈተና ካስፈተናቸው ተማሪዎች መካከል  89.7በመቶ ለከፍተኛ ትምህርት ማሳለፉ ተገለፀየጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማህብረሰብ ት/ቤት በ2017 ዓ....
09/23/2025

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ት/ቤት የ12ኛ ክፍል ፈተና ካስፈተናቸው ተማሪዎች መካከል 89.7በመቶ ለከፍተኛ ትምህርት ማሳለፉ ተገለፀ

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማህብረሰብ ት/ቤት በ2017 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ 68 ተማሪዎች መካከል 61 ተማሪዎች ከ50% በላይ ያስመዘገቡ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ በሪሚዲያል ፕሮግራም የሚሳተፉ መሆኑን የት/ቤቱ ዳይሬክተር አቶ ፀጋዬ የኃላሸት ገልፀዋል:: 6ተማሪዎች ደግሞ ከ500 በላይ በማስመዝገብ አኩሪ ውጤት አስመዝግበዋል። አጠቃላይ የማሳለፍ ምጣኔ ሲታይ 89.7 በመቶ መሆኑን ዳይሬክተሩ አክለው ገልፀዋል።

‎© ጎንደር ዩኒቨርስቲ

 #ማሳሰቢያ : ዛሬ ለሊት 8:00 ሰዐት ከድሬ ደዋ ሂርና መንገድ ከቁሊቢ ላንጌ መዳረሻ ብዛት ያላቸው ሹፌሮችና ረዳቶች ታግተዋል  መንግድ ዝግ ንው ባላችሁብት ጠብቁ የሚል መልዕክት ደርሶናል...
09/23/2025

#ማሳሰቢያ : ዛሬ ለሊት 8:00 ሰዐት ከድሬ ደዋ ሂርና መንገድ ከቁሊቢ ላንጌ መዳረሻ ብዛት ያላቸው ሹፌሮችና ረዳቶች ታግተዋል መንግድ ዝግ ንው ባላችሁብት ጠብቁ የሚል መልዕክት ደርሶናል።
13/01/2018

© የሾፌሮች አንደበት

“በኤርትራክተሮች 55 ሺህ ሔክታር ሰብል ላይ የኬሚካል ርጭት ተደርጓል”         - የብሔራዊ ኤር ዌይስ ድርጅት   | 55 ሺህ ሔክታር ሰብል በኤርትራክተሮች ኬሚካል መረጨቱን የብሔራዊ ...
09/23/2025

“በኤርትራክተሮች 55 ሺህ ሔክታር ሰብል ላይ የኬሚካል ርጭት ተደርጓል”

- የብሔራዊ ኤር ዌይስ ድርጅት

| 55 ሺህ ሔክታር ሰብል በኤርትራክተሮች ኬሚካል መረጨቱን የብሔራዊ ኤር ዌይስ ድርጅት አስታወቀ።

የብሔራዊ ኤር ዌይስ ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ገዛኸኝ ብሩ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜ የተጀመረው በአውሮፕላን የሰብል ላይ የኬሚካል ርጭት በኤርትራክተሮች 55 ሺህ ሔክታር ሰብል ኬሚካል ተርጭቷል።

ይህም በምርትና ምርታማነት ላይ ውጤት የሚያስገኝ መሆኑንተናግረዋል።

እንደ አቶ ገዛሃኝ ገለጻ፤ አውሮፕላኖቹ በትርፍ ጊዜ ለአርሶ አደሮች ኬሚካሎችን በመርጨት ገቢ እያስገኙ ነው፡፡ እስካሁን ባለው ሂደትም 55 ሺህ ሔክታር ኬሚካል ተረጭቷል፡፡ ይህም በምርታማነት ላይ ከፍተኛ አወንታዊ አስተዋዕጾ ያበረክታል፡፡

የአውሮፕላኑ ርቀት የተመጠነና ከመሬት ከሶስት ሜትር እስከ አምስት ሜትር ብቻ ከፍታ የሚረጭ በመሆኑ ኬሚካሉ በንፋስ የመወሰድ እድሉ አንደሌለው አብራርተዋል፡፡

በተጨማሪም በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተቃኘ በመኆኑ ኬሚካሉ በእያንዳንዱ ሰብል ላይ እንዲያርፍ የሚደረግ በመሆኑ አመርቂ ውጤት እያስገኘ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

መንግሥት በሰብል ላይ በተለያዩ ሁኔታዎች የሚደርሱ ጉዳቶች ለመከላከል 800 ሚሊየን ብር በጀት በመመደብ አምስት አውሮፕላኖች መግዛቱን ተናግረዋል፡፡

የተገዙት አውሮፕላኖች ከሀገሪቷ መልክአ ምድር እና ከቆዳ ስፋት አንፃር ተለይተው የተገዙ ናቸው ያሉ ሲሆን፤ በተጨማሪም አውሮፕላኖቹ ሲገዙም የግብርና እና የአቬሽን ባለሞያዎችን በማካተት በዘርፉ ዓለም የደረሰበትን ቴክኖሎጂ እንዲያሟሉ መደረጉን ጠቁመዋል።

አውሮፕላኖቹ ትንኞችን እና የመሳሰሉትን በሰበል ላይ ጉዳት የሚያደርሱ በሽታዎችን ለመቆጣጠር ያስችላሉ።
የአውሮፕላኖቹ መገዛት ጥቅሙ በቀላሉ የሚታይ አይደለም፡፡ አንዱ አውሮፕላን በቀን በአማካኝ አንድ ሺህ 200 ሔክታር መሬት ላይ ኬሚካል መርጨት ይችላል።

በአጠቃላይ የተገዙት አውሮፕላኖች በወር በአማካኝ 180 ሺህ ሔክታር መሸፈን እንደሚችሉም ነው የተናገሩት።

በኢትዮጵያ በ2012 ዓ.ም ከፍተኛ የበርሃ አንበጣ ወረርሽኝ ተከስቶ እንደበር ጠቁመው፤ ወረርሽኙ ለመከላከል መንግሥት ከውጪ አውሮፕላን በውድ ዋጋ በመከራየት ኬሚካል ሲያስረጭ ቢቆይም ያን ያህል ውጤታማ ባለመሆኑ ጉዳት ሲያደርስ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡

የግብርና ሥራ እና ተዛማጅ ተባዮችን ለመከላከል የሚሠራውን በተመለከተም በተካሔደው ጥናት፤ ተመራጭ ሆነው የተገኙት አውሮፕላኖች ኤር ትራክተሮች ተገዝተዋል ብለዋል፡፡

አውሮፕላኖቹ ፈጣን፣ ዘመናዊ እና አቅም ያላቸው በመሆናቸው የማዕድን አሰሳ፤ የዱር እሳት የማጥፋት ሥራ እና የዓየር ላይ ካርታ የማንሳት ሥራ መሥራት እንደሚችሉም ተናጋረዋል፡፡


አውሮፕላኖቹ በሌሎች ክልሎችም ግሪሳ ወፍን ለማጥፋት ተሰርቷል ያሉት አቶ ገዛሃኝ ለአብነትም ትግራይ ክልል፣ ራያ አማራ ክልል፣ በኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ከሚሴ አካባቢ እና ጨርጨር ማሽላ ላይ ርጭት ተደርጓል፡፡

በተጨማሪም ከሠመራ በመነሳት ዱብቲ አካባቢ የመከላከል ሥራ ተሠርቷል። ጎዴ የሩዝ ምርት ላይ የተከሰተውን ግሪሳ ወፍ መከላከል የተቻለው በእነዚሁ አውሮፕላኖች ነው ብለዋል።

በምሕረት ሞገስ

 #ጤና : በነጭ ሽንኩርት ሊታከሙ የሚችሉ 30 ህመሞች❶ እንቅልፍ ማጣት ፣ ማይግሬንበየቀኑ ጥቂት ነጭ ሽንኩርት መመገብ ከእነዚህ በሽታዎች ሁሉ ይጠብቅዎታል። ደምን በማጥራት ከብዙ መርዞች ያ...
09/23/2025

#ጤና : በነጭ ሽንኩርት ሊታከሙ የሚችሉ 30 ህመሞች

❶ እንቅልፍ ማጣት ፣ ማይግሬን
በየቀኑ ጥቂት ነጭ ሽንኩርት መመገብ ከእነዚህ በሽታዎች ሁሉ ይጠብቅዎታል። ደምን በማጥራት ከብዙ መርዞች ያጸዳል። ይህንን ይሞክሩ እና ውጤቱ አያሳዝዎትም፤ ምክንያቱም ያለ መድሃኒት የዕለት ተዕለት ጤና ነው።

❷ አስካሪስ (የሆድ ትል)
ሁለት የሾርባ ማንኪያ የተከተፈ ነጭ ሽንኩርት በ6 የሾርባ ማንኪያ የሎሚ ጭማቂ ውስጥ ይጨምሩ። ለ12 ሰዓታት ያህል ይዘፍዝፉት። ከዚያም አጥልለው ይጠጡ።

❸ አስቴኒያ (ድካም)

በአከርካሪ አጥንት ላይ የሚደረግ ማሳጅ ውጤታማ ህክምና ነው። ግማሽ ጠርሙስ በነጭ ሽንኩርት እና በኮኮናት ጭማቂ ሞልተው ለሁለት ቀናት ያቆዩት። በቀን ሁለት ጊዜ ትንሽ ብርጭቆ ይጠጡ።

የነጭ ሽንኩርት ጭማቂ + የሎሚ ጭማቂ + የኮኮናት ጭማቂ ቅልቅል ይጠጡ።

❹ ቃጠሎ
አንድ የሾርባ ማንኪያ የነጭ ሽንኩርት ጭማቂ ከአንድ የሾርባ ማንኪያ የወይራ ዘይት ወይም የሺአ ቅቤ ጋር ይቀላቅሉ። ውህዱን በደንብ ይምቱት። የተጎዳውን ቦታ በቀስታ በመንካት ይተግብሩ።

❺ የሽንት ጠጠር
ሁለት የሾርባ ማንኪያ የተከተፈ ነጭ ሽንኩርት በሩብ ሊትር የፈላ ውሃ ውስጥ ለ20 ደቂቃዎች ያህል ይዘፍዝፉት። ጠዋት በባዶ ሆድ እና ማታ ከመተኛትዎ በፊት ይጠጡ።

❻ ካንሰር
ነጭ ሽንኩርት በአንጀት ውስጥ መበስበስን በመከላከል የካንሰር መንስኤዎች ላይ በጎ ተጽእኖ እንዳለው በመደበኛነት መጠቀም ያሳያል።

❼ የጥርስ መቦርቦር
የነጭ ሽንኩርት ፍሬዎችን ይፍጩ። የተገኘውን ልጥፍ የበሰበሰ ጥርስ ላይ ይተግብሩ።

❽ ኮሌስትሮል
በፆም ወቅት 120 ግራም ቅቤ የበሉ ሰዎችን ኮሌስትሮል ነጭ ሽንኩርት እንደሚቀንስ በጥናት ተረጋግጧል።

❾ የእግር ቁርን
የተፈጨ ነጭ ሽንኩርት ወይም አንድ ቁራጭ ነጭ ሽንኩርት ቁርኑ ላይ በማድረግ እንዳይፈስ በፋሻ ያስሩት። ቁርኑ እስኪወድቅ ድረስ በየቀኑ (ከ8 እስከ 10 ቀናት) ይህንን ያድርጉ።

❿ ሳይስታልጂ (የፊኛ ህመም)
ዲኮክሽን፡ 3 የሾርባ ማንኪያ የተከተፈ ነጭ ሽንኩርት በግማሽ ሊትር ውሃ ውስጥ ለአንድ ደቂቃ ያህል ያፍሉት። ይህንን ውህድ በመጠቀም በሚያምዎት ቦታ ላይ መጭመቂያዎችን ያድርጉ።

⓫ የስኳር በሽታ
ነጭ ሽንኩርት ደምን ከስኳር ያጸዳል። ከስኳር በሽታ ህክምናዎች አንዱ በየቀኑ የነጭ ሽንኩርት እና የፓርስሊ ቅልቅል መመገብ ነው። አንድ የብሪታንያ የህክምና ጆርናል ነጭ ሽንኩርት የደም ዝውውርን ከልክ ያለፈ ግሉኮስ በማጽዳት ረገድ ውጤታማ መሆኑን ገልጿል።

⓬ የምግብ አለመፈጨት
ከምግብ በኋላ ከ2 ሰዓት በኋላ የነጭ ሽንኩርት ሻይ (2 ፍሬዎችን በአንድ ሊትር የፈላ ውሃ ውስጥ) ይውሰዱ።

⓭ ተቅማጥ
አንድ የሾርባ ማንኪያ የተከተፈ ነጭ ሽንኩርት በሩብ ሊትር ውሃ ውስጥ ለ15 ደቂቃዎች ያህል ያፍሉት። በዚህ ዲኮክሽን ኤነማ ያድርጉ።

⓮ ማስነጠስ
ብዙ ነጭ ሽንኩርት ይመገቡ። አስገራሚ እፎይታ ያስገኛል።

⓯ የጉበት ችግር
አንድ የሻይ ማንኪያ የተከተፈ ነጭ ሽንኩርት ይውሰዱ። ማታ ከመተኛትዎ በፊት ከአንድ የሾርባ ማንኪያ የወይራ ዘይት ጋር በመቀላቀል መውሰድ ጉበትን ያነቃቃል።

⓰ ስካቢስ (የቆዳ በሽታ)
8 የነጭ ሽንኩርት ፍሬዎችን በአንድ ሊትር ውሃ ውስጥ ለ20 ደቂቃዎች ያህል ያፍሉት። የተጎዱትን ክፍሎች በዚህ ዲኮክሽን ያጠቡ። ሳያጸዱ በአየር እንዲደርቅ ይተዉት። ከዚያም ከነጭ ሽንኩርት ጭማቂ እና ከሸክላ የተሰራውን ልጥፍ በክፍሎቹ ላይ ይተግብሩ።

⓱ ኪንታሮት
10 የተከተፈ ነጭ ሽንኩርት በድስት ውስጥ ያስቀምጡ፤ ያሞቁ እና ከዚያም የእንፋሎት ገላ መታጠቢያ ያድርጉ። ለአንድ ሳምንት ያህል አዲስ የነጭ ሽንኩርት ጭማቂ ህክምና ያድር

የአዳማ-አዋሽ ፈጣን መንገድ ግንባታን ለማስጀመር ከ181 ሚሊዮን ዶላር በላይ የፋይናንስ ድርድር ተጠናቀቀየአዳማ-አዋሽ የፈጣን መንገድ ሁለተኛ ክፍል ግንባታን አስመልክቶ በአፍሪካ ልማት ባንክ...
09/23/2025

የአዳማ-አዋሽ ፈጣን መንገድ ግንባታን ለማስጀመር ከ181 ሚሊዮን ዶላር በላይ የፋይናንስ ድርድር ተጠናቀቀ

የአዳማ-አዋሽ የፈጣን መንገድ ሁለተኛ ክፍል ግንባታን አስመልክቶ በአፍሪካ ልማት ባንክ፣ በገንዘብ ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር መካከል ሲካሄድ የነበረው የመጨረሻው የገንዘብ ድጋፍ ድርድር መጠናቀቁ ተገለፀ።

ይህ ድርድር ባንኩ ፕሮጀክቱን በቅርቡ ለቦርዱ አቅርቦ እንዲያፀድቅ የሚያስችል ሲሆን፣ ለፕሮጀክቱ ከታሰበው አጠቃላይ ወጪ ውስጥ 181.5 ሚሊዮን ዶላር በአፍሪካ ልማት ባንክ እንደሚሸፈን ይጠበቃል። የኢትዮጵያ መንግስት ደግሞ 34.2 ሚሊዮን ዶላር ለመሸፈን አቅዷል።

የፈጣን መንገዱ ግንባታ በሁለት ምዕራፎች የተከፈለ ነው። የመጀመሪያው 48 ኪሎ ሜትር በአፍሪካ ልማት ባንክ በሚሰጠው ብድር ሲገነባ፣ ቀሪው 19 ኪሎ ሜትር ደግሞ በኮሪያ ኤግዚም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚደረግለት ታውቋል።

ይህ መንገድ ኢትዮጵያን፣ ጅቡቲን እና ደቡብ ሱዳንን የሚያገናኝ ትልቅ ፕሮጀክት ሲሆን፣ በአፍሪካ ቀንድ ያለውን የትራንስፖርት ትስስር በማሻሻል ለንግድና ኢኮኖሚያዊ ልማት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።

የፋይናንስ ስምምነቱ በ2026 መጀመሪያ ላይ ተፈርሞ ግንባታው ወደ ትግበራ ይገባል ተብሎ ታቅዷል።

© CapitalNews

የዓለማችን 10ሩ  ከፍተኛ  ሰሊጥ አምራች አገራትኢትዮጵያ በ6ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለችበዓለም አቀፍ ደረጃ የሰሊጥ ዘር ኢንደስትሪ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የመጣ ሲሆን፤ ህንድ፣ ቻይና፣ሱዳን፣ ...
09/23/2025

የዓለማችን 10ሩ ከፍተኛ ሰሊጥ አምራች አገራት

ኢትዮጵያ በ6ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች

በዓለም አቀፍ ደረጃ የሰሊጥ ዘር ኢንደስትሪ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የመጣ ሲሆን፤ ህንድ፣ ቻይና፣ሱዳን፣ ማይናማር፣ታንዛኒያና እንዲሁም ኢትዮጵያ ከፍተኛ የገበያ ድርሻ ያላቸው ሀገራት ናቸው።

ስድስት በመቶ የሚሆነውን የዓለም የሰሊጥ ዘር ገበያ ድርሻ የያዘችው ኢትዮጵያ፤ ምርቷን ወደ አፍሪካ፣ እስያና መካከለኛው ምስራቅ ሀገራት በስፋት የምትልክ ሲሆን፤ ሰሊጥ ሀገሪቷ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ከምታገኝባቸው የግብርና ምርቶች የሚመደብ ነው፡፡

1 ህንድ

2 ቻይና

3 ሱዳን

4 ምይናማር

5 ታንዛንያ

6 ኢትዮጵያ

7 ናይጄሪያ

8 ኡጋንዳ

9 ማሊ

10 ቡርኪናፋሶ

ምንጭ:- ESS- Feed

💫 አዲሱ ተግባራዊ ይሆናል የተባለው ደሞዝ ጭማሪ ጭምጭምታ
09/23/2025

💫 አዲሱ ተግባራዊ ይሆናል የተባለው ደሞዝ ጭማሪ ጭምጭምታ

 #ግእዝ is not OLD it’s GOLD. በተሳሳተ ስሌት ልጆችን ከትምህርት ገበታ አናርቃቸው‼️ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት መላክ ህጋዊ ኃላፊነት ብቻ ሳይሆን ለወደፊት ህይወታቸው...
09/22/2025

#ግእዝ is not OLD it’s GOLD. በተሳሳተ ስሌት ልጆችን ከትምህርት ገበታ አናርቃቸው‼️

ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት መላክ ህጋዊ ኃላፊነት ብቻ ሳይሆን ለወደፊት ህይወታቸው ሊሰጧቸው የሚችሉት ምርጥ ስጦታም ነው።📚

ከግእዝ አንፃር ግን:-

❶ ግእዝ ለኢትዮጵያዊያን የማንነታችን ስርና መሰረት ነው። A people who forget their heritage lose their future. Let’s value Ge’ez not as the past, but as power for Tomorrow.

❷ ግእዝ ሙዚየም ላይ የሚቀመጥ ጌጥ አይደለም፤ የሕያው ኃብታችን አካል እንጂ። ስለሆነም Whoever honors their roots grows stronger for the future.

❸ ያለ ግእዝ ነባር ታሪካችን ሁሉ ድምጽ አልቦ ነው። እናም Keeping it alive means keeping ourselves alive.

ስለሆነም ግእዝን ከ3ተኛ-8ተኛ ክፍል ማስተማር የተፈለገው ልክ እንደ ማንኛውም ቋንቋ ተማሪዎች የግእዝን ቋንቋ የመስማት፣ የማንበብና የመናገር ክህሎቶችን እና እውቀቶችን ለማስጨበጥ ታሳቢ ያደረገ መሆኑን በቢሮው በኩል የተዘጋጀውን የመማሪያና የማስተማሪያ መፀሀፎችን አግኝቶ ዝርዝር ይዘቱን በማየት መረዳት ይቻላል።

ምክኒያቱም Ge’ez is not a BURDEN, it’s a BRIDGE between generations.

ከዚያም በአመዛኙ በሙከራ ትግበራ ላይ ያለና በመምህራንና መሰል የግብዓት እጥረቶች ሳቢያ በሁሉም የክልሉ የመንግስት ትም/ት ቤቶች 100% እየተሰጠ የሚገኝ ባለመሆኑ በቀጣይ ስርዓተ ትምህርቱ እየዳበረ እንዲሄድ ለማሻሻያነት ግብዓት የሚሆኑ ጉዳዩችን በተደራጀ ሁኔታ ለሚመለከተው ተቋም ማድረስ ጠቃሚ ይመስለኛል።

ምክኒያቱም Ge’ez is the KEY, without it the door to our history stays CLOSED.

ነገር ግን ከዚህ ቀደም በቤተ ክርስቲያን በኩል ለሰንበትና ለአብነት ትም/ት ቤቶች፣ ለመንፈሳዊ ኮሌጆችና ተቋማት ላይ በማስተማሪያነት ከተዘጋጁት የመማሪያ መፀሃፎች ውስጥ ከፊል ገፆችን እያቀረቡ እንዲሁም አበው ለመንፈሳዊ ተማሪዎች ስለ ግእዝ ያስተማሩበትን ተንቀሳቃሽ ምስል በአስረጂነት በማቅረብ ነገርየውን የእምነት አጀንዳ እንዲይዝ ማድረግ ተገቢነት የለውም።

ምክኒያቱም ግእዝ ለቀድሞው እኛነታችን የጀርባ አጥንት ነው። ስለሆነም Cut the root and the tree cannot stand በሚል መነሻ እየተዘመተበት ያለው።

በመጨረሻም አዕምሮ የሚያውቀውን እውነት ልብ እስኪቀበል ጊዜ ይፈልጋል። This is my word on Ge’ez. ሰላም በሰላም።
Via Mohammed Yassin Abesha

Address

New York, NY

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when NEXT ADDIS posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

ETHIOBRANA

MEDIA AND ENTERATMENT