09/22/2025
#ግእዝ is not OLD it’s GOLD. በተሳሳተ ስሌት ልጆችን ከትምህርት ገበታ አናርቃቸው‼️
ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት መላክ ህጋዊ ኃላፊነት ብቻ ሳይሆን ለወደፊት ህይወታቸው ሊሰጧቸው የሚችሉት ምርጥ ስጦታም ነው።📚
ከግእዝ አንፃር ግን:-
❶ ግእዝ ለኢትዮጵያዊያን የማንነታችን ስርና መሰረት ነው። A people who forget their heritage lose their future. Let’s value Ge’ez not as the past, but as power for Tomorrow.
❷ ግእዝ ሙዚየም ላይ የሚቀመጥ ጌጥ አይደለም፤ የሕያው ኃብታችን አካል እንጂ። ስለሆነም Whoever honors their roots grows stronger for the future.
❸ ያለ ግእዝ ነባር ታሪካችን ሁሉ ድምጽ አልቦ ነው። እናም Keeping it alive means keeping ourselves alive.
ስለሆነም ግእዝን ከ3ተኛ-8ተኛ ክፍል ማስተማር የተፈለገው ልክ እንደ ማንኛውም ቋንቋ ተማሪዎች የግእዝን ቋንቋ የመስማት፣ የማንበብና የመናገር ክህሎቶችን እና እውቀቶችን ለማስጨበጥ ታሳቢ ያደረገ መሆኑን በቢሮው በኩል የተዘጋጀውን የመማሪያና የማስተማሪያ መፀሀፎችን አግኝቶ ዝርዝር ይዘቱን በማየት መረዳት ይቻላል።
ምክኒያቱም Ge’ez is not a BURDEN, it’s a BRIDGE between generations.
ከዚያም በአመዛኙ በሙከራ ትግበራ ላይ ያለና በመምህራንና መሰል የግብዓት እጥረቶች ሳቢያ በሁሉም የክልሉ የመንግስት ትም/ት ቤቶች 100% እየተሰጠ የሚገኝ ባለመሆኑ በቀጣይ ስርዓተ ትምህርቱ እየዳበረ እንዲሄድ ለማሻሻያነት ግብዓት የሚሆኑ ጉዳዩችን በተደራጀ ሁኔታ ለሚመለከተው ተቋም ማድረስ ጠቃሚ ይመስለኛል።
ምክኒያቱም Ge’ez is the KEY, without it the door to our history stays CLOSED.
ነገር ግን ከዚህ ቀደም በቤተ ክርስቲያን በኩል ለሰንበትና ለአብነት ትም/ት ቤቶች፣ ለመንፈሳዊ ኮሌጆችና ተቋማት ላይ በማስተማሪያነት ከተዘጋጁት የመማሪያ መፀሃፎች ውስጥ ከፊል ገፆችን እያቀረቡ እንዲሁም አበው ለመንፈሳዊ ተማሪዎች ስለ ግእዝ ያስተማሩበትን ተንቀሳቃሽ ምስል በአስረጂነት በማቅረብ ነገርየውን የእምነት አጀንዳ እንዲይዝ ማድረግ ተገቢነት የለውም።
ምክኒያቱም ግእዝ ለቀድሞው እኛነታችን የጀርባ አጥንት ነው። ስለሆነም Cut the root and the tree cannot stand በሚል መነሻ እየተዘመተበት ያለው።
በመጨረሻም አዕምሮ የሚያውቀውን እውነት ልብ እስኪቀበል ጊዜ ይፈልጋል። This is my word on Ge’ez. ሰላም በሰላም።
Via Mohammed Yassin Abesha