Amanuel Yfter

Amanuel Yfter Peace for East Africa ✌️ ሰላም ለመላው አለም
Peace for the whole world
(5)

የአእላፋት ዝማሬ መርሐ ግብር በአዲስ አበባ 😇
01/06/2026

የአእላፋት ዝማሬ መርሐ ግብር በአዲስ አበባ 😇

ድንግል ማርያም በቤተ መቅደስ አሰምታ ትናገር ነበር🎤ሰላም ላንቺ ይሄን አለኝ ቅዱስ ገብርኤልሌላ ምንም አላውቅ ያውቃል እግዚአብሔር/2/🙏💖†                  †             ...
12/29/2025

ድንግል ማርያም በቤተ መቅደስ አሰምታ ትናገር ነበር🎤
ሰላም ላንቺ ይሄን አለኝ ቅዱስ ገብርኤል
ሌላ ምንም አላውቅ ያውቃል እግዚአብሔር/2/🙏💖
† † †
ከመቅደስ ቁጭ ብዬ ትንቢት እየሰማሁ
ሀሩን አስማምቼ ጥበብን እየፈተልኩ
ሳለሁ በመገረም ያንን ቃል አስቤ
አምላክ ሰው ሆነብኝ ተመሰጠ ልቤ
ማናት ብዬ ሳስብ ያቺ ብላቴና
ገብርኤል ደረሰ ብስራቱን ያዘና
ዙፋኑ አደረገኝ የባሪያቱን ውርደት ተመልክቷልና
‹‹ድንግል ማርያም በቤተ መቅደስ››
🥰

በስእሏ ፊት ስቆም. . .ሰማይና ምድርን የፈጠረ የሰማያዊ ንጉሥ የኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ እመቤቴ ሆይ! መተዳደፍ በበዛበት ዓለም ስኖር ንጽሕናዋን እንዳላሳጣት ነፍሴን በአንቺ ዘንድ አኖራታለ...
12/29/2025

በስእሏ ፊት ስቆም. . .

ሰማይና ምድርን የፈጠረ የሰማያዊ ንጉሥ የኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ እመቤቴ ሆይ! መተዳደፍ በበዛበት ዓለም ስኖር ንጽሕናዋን እንዳላሳጣት ነፍሴን በአንቺ ዘንድ አኖራታለሁ፤ እግዚአብሔር ልጁን ወደ ዓለም በላከው ጊዜ ማረፊያ ያደረገው አንቺን ነውና ካንቺ የከበረ ቦታ ለነፍሴ ስለማላገኝላት በአንቺ ዘንድ አኖራታለሁ።

የአብ ሙሽራ እመ አምላክ ሆይ! ወደ አንቺ እጆቼን ዘርግቼ ጸሎቴን አደርሳለሁ፤
ዓይኖቼን ቀና አድርጌ ልመናዬን አቀርባለሁ፤ “የልብሱን ጫፍ የዳሰስሁ እንደሆነ እድናለሁ”
ብላ የተመኘችው ሴት ልብሱን ዳሳ ተፈወሰች፤ እኔ ግን አማኑኤል የሥጋን ልብስነት ካንቺ የለበሰብሽ፣ ከለበሰው ልብስ ይልቅ የከበርሽ እና ክርስቶስ ባሕርይሽን የተካፈለሽ መሆኑን አውቄ እጆቼን ለጸሎት ወደ አንቺ እዘረጋለሁ።

የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ የሆንሽ መመኪያዬ ክብሬ ድንግል ሆይ! ስምሽን በጉባኤ ዐውጃለሁ፤ በምስጋና ጊዜም እጠራሻለሁ፤ የአንቺ ምሳሌ የሆነውን ማዕጠንት ይዞ አሮን በወገኖቹ መካከል በተመላለሰ ጊዜ የሆነውን አውቃለሁ፤ ሕዝቡን ከደዌአቸው የፈወሳቸው ያንቺ ምሳሌ ከሆነው የወርቅ ማዕጠንት የሚወጣው የዕጣኑ መዓዛ ነው፤ እኔ ግን ከአሮን ማዕጠንት ይልቅ የከበርሺ አንቺን ይዤ በሕዝቡ መካከል እገባለሁ።

የጻድቃን እናት ሆይ! የኃጢአት ማዕበል እንዳይገፋኝ ወደ አንቺ እጠጋለሁ፤ ከሰማይ የቊጣ ዝናም በዘነመ ጊዜ ወደ መርከብ ገብቶ የዳነውን ኖኅን አስታውሳለሁ፤ ከመርከቧ ይልቅ አንቺ እንደምትበልጪም አውቃለሁ።

ስለዚህም የልጅሽን ምሕረት እስከማገኝ ድረስ በአንቺ ውስጥ ሰውነቴን ከሰይጣን እሰውራታለሁ። ድንግልናሽን መቅዘፊያ አድርጌ ከርኩስቴ እሻገርበታለሁ።

ንጽሕናሽን ልብስ አድርጌ ከኃጢአት ብርድ እድንበታለሁ።

የሔዋን የሚጎዳ ማሰሪያዋ በአንቺ የተቆረጠላት ንጽሕት ቅድስት ሆይ! ቤተ ክርስቲያን አንቺን ታመሰግንሻለች፤ በልጅሽ ጸዳለ ብርሃን ከድቅድቅ ጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃን ወጥታለችና።

በአንቺ ደስ ትሰኛለች፤ ዓለሙን ሁሉ የሚያጣፍጠውን የሕይወት ግንድ ይዘሽ ተገኝተሻልና።

ቤተ ክርስቲያን በአንቺ ትደነቃለች፤ አንበሳን የታቀፈች ጊደር፣ እሳትን የታቀፈች የሰው ዘር፣ ከሰማይ የምትበልጥ ምድራዊት፣ መለኮትን በሥጋ የወሰነች፣ ጥበትን ከስፋት ጋር አስተባብራ የያዘች ካንቺ በቀር ሌላ ሴት የለችምና።

ከገነት በተሰደደ ጊዜ የአዳም ተስፋው የሆንሽ እመብርሃን ሆይ! ሰይጣን ኃጢአቴን እያሳሰበ ተስፋ ሊያስቆርጠኝ ሲሞክር የማሸንፈው ስምሽን ለጠራ መታሰቢያሽን ላደረገ ምሕረትን እንደሚያደርግ ልጅሽ የገባልሽን ኪዳንሽን አስቤ ነው።

ኃጢአቴ በዝቶ ከልጅሽ መንግሥት እንዳያሳድደኝ በቃል ኪዳንሽ ተማጽኛለሁ።

ልጅሽ ከጌርጌሴኖን ተመልሶ ከመርከብ ሲወርድ ያገኘውን ሽባ ሰው የፈወሰው የተሸከሙትን ሰዎች እምነት አይቶ ነው ማቴ. 9፥2።

እኔንም ያንቺን እምነት አይቶ ይማረኝ! ንጽሕናሽን አይቶ ከርኩሰቴ ያንጻኝ!

ዓለሙን ሁሉ የሚያጣፍጠውን ጨው ይዘሽ የተገኘሸ አዲሷ የኤልሳዕ ማሰሮ አንቺ እያለሽልኝ ነፍሴ በኃጢአት ምሬት ተሞልታ መኖሯ ለምንድነው? ንጽሕት ጽዋዕ የወርቅ መቅጃ የተባልሽ ድንግል ሆይ! በአንቺ የተቀዳውን የሕይወት ውኃ ጠጥታ ነፍሴ ትዘምራለች።

የኤልሳዕ በረከት ለኢያሪኮ ነው ያንቺ በረከት ደግሞ በእኔ ላይ ይሁን።
የኤልያስ መሶብ የተባልሽ አማናዊት የመና ሙዳይ እመ አምላክ ሆይ! ዓለሙ ሁሉ በልቶት የዳነበት የሕይወት እንጀራ የተገኘው ካንቺ ነው።

የምንበላውን ያፈራሽልን የምንጠጣውን ያስገኘሽልን አንቺን የማያመሰግን ቢኖር የልጅሽ የመለኮቱ ብርሃን ያላገኘው ነው።
መኖሪያው ጨለማ ነው።
መንገዱ ዳጥና ጨለማ የሞላበት ነው።
ሰውነቱ የመለኮትን እስትንፋስ ያላገኘች ሸክላ ናት።

የፀሐየ ጽድቅ መውጫ ምሥራቅ፣ የብርሃን ደጃፍ ጸዳለ መብረቅ፣ ሐረገ ወይን እንተ በምድር፣ አዕጹቂሃ በሰማይ ዘይነብር፣ የአብ ጥበቡ ያረፈብሽ፣ የወልድ አካሉ ያደረብሽ፣ የመንፈስ ቅዱስ ግብር የተገለጠብሽ ቢጸ ሱራፌል፣ መንበረ ልዑል፣ እመ አዶናይ እመቤቴ! እንደ ጴጥሮስ ጥላሽን ጣይብኝ! እንደ ጳውሎስ ሰበንሽን አስነኪኝ! ያኔ ድኜ ወደ ልጅሽ መንግሥት ከሚገቡት ጋር እጨመራለሁ።

ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነ!
እግዝእትነ ማርያም ትምክሕተ ዘመድነ!
ዕፀ መስቀሉ ምርጉዝነ!
አሜን!

የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል የስሙ ትርጓሜ “እግዚእ ወገብር፤ አምላክ ሰው ሆነ፣ ሰው አምላክ ሆነ” ማለት ነው፡፡ቅዱስ ገብርኤል የጌታችን መድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መምጣትና ...
12/27/2025

የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል የስሙ ትርጓሜ “እግዚእ ወገብር፤ አምላክ ሰው ሆነ፣ ሰው አምላክ ሆነ” ማለት ነው፡፡

ቅዱስ ገብርኤል የጌታችን መድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መምጣትና ሰው መሆን ለመናገር ተልኮ የምሥራች ዜናን ያበሠረ፤ በዲያቢሎስ የተንኮል ወጥመድ ገብተው ለተሰናከሉት ፈጥኖ ለመርዳት የሚደርስ፣ በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩት ሁሉ የብርሃን ፋና ያበራ፣ ሰብአ ሰገልን የመራ መልአክ ነው፡፡

ከቀድሞ ጀምሮ ቅዱሳን ነቢያት ከእግዚአብሔር ተልከው መንፈስ ቅዱስ እንዳናገራቸው ዓለምን ስለማዳን ከጽዮን የሚወጣ ከያዕቆብ በደልን የሚያርቅ ጌታ “ይወርዳል ይወለዳል” በማለት በየወገናቸውና በየዘመናቸው የተናገሩትን የነቢያትን ትንቢት መፈጸሙን የሚያበስረውን የምሥራችን ቃል የተናገረ ነው፡፡ የጨለማ አበጋዝ በሆነ በሰይጣን ተንኮል በሰው ልቦና ውስጥ አድሮ የነበረውን ከእፉኝት መርዝ የከፋ የኀዘን ስሜት ያጠፋ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡

ቅዱስ ገብርኤል ከሌሎች መላእክት ተለይቶ ዘወትር በምንጸልያቸው ጸሎቶች ስሙ የሚጠራ መልአክ ነው፡፡ ይኸውም በዘወትር ጸሎቶች በአቡነ ዘበሰማያት፣ በሰላመ ቅዱስ ገብርኤል፣ በውዳሴ ማርያም፣ በይዌድስዋ መላእክትና በመሳሰሉት ጸሎቶች ዘወትር ስሙ የሚጠራ ነው፡፡ ካህናት አባቶች ቅዱስ ገብርኤል ስእለት ሰሚና ፈጥኖ ደራሽ መልአክ እንደሆነ ይነግሩናል፡፡ ይኽም በክርስቲያኖችም ዘንድ እጅግ ተወዳጅ እንዲሆን አድርጎታል፡፡ ፈጥኖ ደራሹ መልአክ፣ ስእለት ሰሚው መልአክ ይሉታል፡፡ የአምላክ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ከሌሎች መላእክት ሁሉ በይበልጥ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልን እንደምትወደው በድርሳነ ገብርኤል “ወንድሞቻችን ሆይ፣ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከመላእክት ሁሉ ይልቅ ቅዱስ ገብርኤልን በይበልጥ እንደምትወደው ተመልከቱ፤ የልጅዋን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ከእርሷ መወለድ ያበሠራት እርሱ ነውና” የሚል ተጽፎ ይገኛል፡፡

ከሰባቱ ሊቃነ መላእክትም አንዱ በእግዚአብሔር ፊት የሚቆመው ታማኝ መልአክ ይህ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ በተረዳኢነቱና በአማላጅነቱ፣ ያዘኑትን ለማጽናናት የምሥራች ለመንገር ከእግዚአብሔር ወደ ምእመናን ይላካል፡፡ ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን አባቶቻችን እንዳስተማሩን በዘመኑ ጣኦት የሚያመልከው ንጉስ ናቡከደነፆር በባቢሎን ምርኮ የወሰዳቸውን የእግዚአብሔር ሰዎች አናንያ፤ አዛርያ፤ ሚሣኤል እጅግ ይወዳቸው ነበር፡፡ ከባቢሎናውያን ይልቅ ጠቢባን የነበሩት ሶስቱ ሕጻናት በትንቢተ ዳንኤል ምዕራፍ ሦስት ሰፍሮ የምናገኘው ታሪካቸው እንደሚነግረን ንጉሱ የጣኦት ምስል አሰራ በገሊላ አውራጃ ያለውን ሕዝብ ጠርቶም ለጣኦቴ ያልሰገደ ወደ እሳት ውስጥ ይጣላል ብሎ አወጀ። የንጉስ ትህዛዝ ነውና ሕዝቡ ሁሉ ለጣኦቱ ሲንበረከክ እነርሱ ግን ቆመው ያዩ ነበር።

ናቡከደነፆር እርሱ ላስቆመው ጣኦት አለመስገዳቸውን ሲሰማ ተናደደ፣ ተበሳጨም እሳቱን 7 እጥፍ እንዲነድ አስደረገ ሦስቱንም አስሮ እሣቱን እያሳየ "ከመቃጠል ወይስ ለእኔ ጣኦት መስገድ የቱ ይሻላል?" ቢላቸውም የእግዚአብሔር የሆነ ሰው ምንም ነገር አያስፈራውምና "የምናመልከው አምላካችን ከሚነደው ከእሳቱ እቶኑ ሊያድነን ይችላል፣ ባያድነንም ግን አንተ ላቆምከው ጣኦት አንሰግድም" አሉት፡፡ በዚህ ጊዜ ጉልበት ያላቸው ሠዎች ተፈልገው ሦስቱን ወጣቶች አስረው ወደ እሳት ቶን ውስጥ ጣሏቸው አስረው የጣሏቸውን ወታደሮች የእሳቱ ወላፈን አቃጠላቸው ሠለስቱ ደቂቅን ግን መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ እሳቱን አበረደላቸው፣ አጠፋላቸው። ከእሳቱ ላይ ሆነውም እግዚአብሔርን አመሰገኑ፡፡

ታቦት አቁሞ ልመና ልናዋግዘው ይገባል ። -አቡነ አብርሃም ታቦት አቁሞ ልመና ነውር ነው። እስከመቼ ድረስ ነው እጅህን ኪስህ ውስጥ አስገባ አስወጣ እየተባለ ምዕመናን የሚቀማው። ይሄ ቅሚያ ማ...
12/27/2025

ታቦት አቁሞ ልመና ልናዋግዘው ይገባል ። -አቡነ አብርሃም

ታቦት አቁሞ ልመና ነውር ነው። እስከመቼ ድረስ ነው እጅህን ኪስህ ውስጥ አስገባ አስወጣ እየተባለ ምዕመናን የሚቀማው። ይሄ ቅሚያ ማታለል ነው።

ታቦት ቁሞ አይመከርም አይምክርም።ታቦተ ህጉ ከቆመ ዝማሬ ፤አምልኮ ፤ውዳሴና ቃለ እግዚአብሔር ብቻ ይቀርባል ። እግዚአብሔርን የምንለምነው ሰላሙን ስጠን ....

ፍቅሩን ስጠን ፤ አንድነቱን ስጠን ፤በልዩ ልዩ ችግር የሚገኙ ወገኖቻችን እርዳ፤ ህፃናትን አሳድግ ፤ ህሙማን ፈወስ የቸርነትህን ስራ አድርግ ብለን እንፀልያለን ።

እንዲሁ አይነት ነገር አየኝ አላዩኝ ተብሎ መደረግ የለበትም መስተካከል መቻል አለበት ። ሀረር በነበሩኩበት ሰአት ታቦት አስቁሞን ልመና ማስቆም ችየ ነበር። እኛ ያላከበረውን ታቦተ ህጉን በጭራሽ ማንም ሊያከብርልን አይችልም ማለታቸውን ግዮን ማለዳ ተመልዕክቷል።
❗ Bazen Media - ባዜን ሚዲያ ❗

 #ምልጃሽ እየደገፈኝ በጌታ ፊት ስትቆሚ🎤ጸሎቴን እያሳረግሽ ልመናዬን ስትሰሚከጎኔ ሳትለዪ ተቆጠሩ ዘመናትይሄው ለዚህ ደረስኩኝ ከእናትም በላይ ሆነሽ እናት🙏💖†                  † ...
12/26/2025

#ምልጃሽ እየደገፈኝ በጌታ ፊት ስትቆሚ🎤
ጸሎቴን እያሳረግሽ ልመናዬን ስትሰሚ
ከጎኔ ሳትለዪ ተቆጠሩ ዘመናት
ይሄው ለዚህ ደረስኩኝ ከእናትም በላይ ሆነሽ እናት🙏💖
† † †
አንድ እርምጃ ሳልራመድ አንቺን ይዤ ተነሳሁ
እመቤቴ ዛሬም ባርኪኝ ውዳሴሽን አበዛለሁ
የአምላኬ እናት ዛሬም ባርኪኝ ውዳሴሽን አበዛለሁ
‹‹እመቤቴ ዛሬም ባርኪኝ››🥰

የሁሉ እናት ምልጃዋ ዘወትር አይለየን አሜን🙏❤🌹

12/25/2025

ኣንድነት ሓይል ኣለው ችግራችን የሚፈታው በኣንድነት ነው::

በምልጃዋ ያመኑትን ሁሉ ሊምርላት ቃል ኪዳን ሰጣትነቢዩ ቅዱስ ሕዝቅኤልም የዘለዓለም ድንግልናዋን በትንቢት መጽሐፉ ምዕራፍ 44÷1 ሲናገር “ወደ ምሥራቅ ወደሚመለከተው በስተውጭ ወዳለው ወደ መ...
12/25/2025

በምልጃዋ ያመኑትን ሁሉ ሊምርላት ቃል ኪዳን ሰጣት

ነቢዩ ቅዱስ ሕዝቅኤልም የዘለዓለም ድንግልናዋን በትንቢት መጽሐፉ ምዕራፍ 44÷1 ሲናገር “ወደ ምሥራቅ ወደሚመለከተው በስተውጭ ወዳለው ወደ መቅደሱ በር አመጣኝ፤ ተዘግቶም ነበር። እግዚአብሔርም ይህ በር ተዘግቶ ይኖራል እንጂ አይከፈትም፣ ሰውም አይገባበትም፤ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ገብቶበታልና ተዘግቶ ይኖራል፤” ብሎአል። የተዘጋ የመቅደስ በር የተባለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት። “ይህ በር ተዘግቶ ይኖራል እንጂ አይከፈትም፤” የሚለው ኃይለ ቃል በድንግልና ጸንታ እስከ ዘለዓለሙ እንደምትኖር ይነግረናል። “ሰው አይገባበትም የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ገብቶበታልና ተዘግቶ ይኖራል” ሲልም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በድንግልና ፀንሳ፣ በድንግልና የወለደችው ኢየሱስ ክርስቶስ የባህርይ አምላክ በመሆኑ፣ ከርሷ በተዋህዶ ሰው የሆነ የባህርይ አምላክ እንጂ ዕሩቅ ብእሲ አይወለድምና በድንግልና እንደጸናች ትኖራለች ማለቱ ነው።

“እግዚአብሔር አንድ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወድዶአልና። ፍቅርም እንደዚህ ነው፤ እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታችንም ማስተስረያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው አይደለም፤” ይላል። ዮሐንስ 3÷17፣ 1ኛ ዮሐንስ 4÷10። ይህን መውደድ ይህን ፍቅር የገለጸው ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም በሕቱም ድንግልና በመወለድ ነው። የእመቤታችን ድንግልና በሦስት ወገን ነው፤ በሥጋዋ÷ በነፍሷና በልቡናዋ ነው። ይህ ድንግልና የዘለዓለም ድንግልና ነው። ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ኢሳይያስ “ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ ድንግል ትፀንሳለች፣ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፣ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች፤” ብሎአል። ኢሳይያስ 7÷14።

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከመጽነሷ በፊት፣ በጸነሰችም ጊዜ፣ ከጸነሰችም በኋላ ድንግልናዋ የጸና ነው፤ ከመውለዷ በፊት፣ በወለደችም ጊዜ፣ ከወለደችም በኋላ ኅትምት በድንግልና ናት። የውዳሴ ማርያም አንድምታ ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ገብርኤል አንቺ ከሴቶች ሁሉ ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ ያላትን አብራርቶ ይነግረናል፡፡ እመቤታችን መልአኩ ሲያበስራት “ወንድ ሳላውቅ ይህ ነገር እንደምን ይሆንልኛል?” የሚል ጥያቄ አንስታ ነበር፡፡ ይህን ያለችው ክብር ይግባትና የወንድ ሀሳብ በአእምሮዋ ፈጽሞ ተመላልሶ ስለማያውቅ ነው፡፡ ሌሎች ሴቶች ስለወንድ ከመናገርና በሕጋዊ ሩካቤ ከመገናኘት ቢታቀቡ ከማሰብ ግን አይነጹም፡፡ እምቤታችን ግን ከመናገር ከማድረግ ከማሰብ ንጽህት ናት፡፡ ከዚህች ቅድስት ድንግል ጋርም በመቃብሩ ስፍራ በጎልጎታ ተደፍታ ስትለምነው በምልጃዋ ያመኑትን ሁሉ ሊምርላት ቃል ኪዳን ሰጣት፡፡

በሥላሴ አኗኗር ወልድ ለአብ ተቀዳሚና ተከታይ የሌለው አንድ ልጅ እንደሆነ ሁሉ ለእናቱ ለቅድስት ድንግል ማርያምም ተቀዳሚና ተከታይ የሌለው አንድ ልጇ ነው። በጳጳስ ወንበር ቄስ፣ በንጉሥ ዙፋን ራስ ደፍሮ እንደማይቀመጥ ሁሉ በአምላክ ዙፋን በቅድስት ድንግል ማርያም ማኅፀን ማን ያድራል? ለዚህም ነው እግዚአብሔር ለነቢዩ ለሕዝቅኤል አስቀድሞ የነገረው። ጠቢቡ ሰሎሞንም በመኃ 4÷12 “እኅቴ ሙሽራ የተቈለፈ ገነት፣ የተዘጋ ምንጭ፣ የታተመ ፈሳሽ ናት፤” ብሎአል። እንደተቆለፈች አምላክ ብቻ አድሮባት የወጣባት ገነት፣ እንደተዘጋች የዘለዓለምን ሕይወት ክርስቶስን ያመነጨች፣ እንደታተመች የሕይወትን ውኃ ክርስቶስን በአራቱም ማዕዝን አፍስሳ የተጠሙ ነፍሳትን ያረካች፣ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ብቻ ናት።

ልዩ እናትነቷን ያመኑ፣ ምልጃዋን ተስፋ ያደረጉ ገዳማውያን ዘወትር በጸሎታቸው ይጠሯታል፡፡ ገዳማቸውን እንደገፍ በአታቸውን እናጽና ከበረከታቸው እንካፈል፡፡

የስደት ስንቄ እመቤቴ ማርያም አማልጅኝ ከልጅሽ🤲🤲
12/24/2025

የስደት ስንቄ እመቤቴ ማርያም
አማልጅኝ ከልጅሽ🤲🤲

ፍቅርን ሳታውቁ ትዳርን እንዳታስቡ….✍🏽✅ላወቀበት ሰው ትዳር የመንግስተ ሰማያት መግቢ በር ነው።የትዳር መሰረቱ ፍቅር ሲሆን የፍቅር ባለቤቱ ደግሞ ፈጣሪ ነው። ፍቅርንና ትዳርን የሚሰጥ ፈጣሪ...
12/23/2025

ፍቅርን ሳታውቁ ትዳርን እንዳታስቡ….✍🏽
✅ላወቀበት ሰው ትዳር የመንግስተ ሰማያት መግቢ በር ነው።የትዳር መሰረቱ ፍቅር ሲሆን የፍቅር ባለቤቱ ደግሞ ፈጣሪ ነው። ፍቅርንና ትዳርን የሚሰጥ ፈጣሪ ሲሆን አክብሮ መያዝ ግን የእኛ ነው።ፈጣሪ ለሰው ልጆች ክቡር ፍጡር የሆነውን ሰውን ነፍስን ከነ ሙሉ አካሉ በስጦታነት ሲሰጠን በፍቅር ተንከባክበን፣አክብረንና ተጠንቅቀን መያዝ ግደታ አለብን።
✅ስለሆነም ፈጣሪ ሩህሩህ አምላክ ነውና ሁሉን በህግና ስርዓት እንደንመራ ፍቅርን እንደት ማክበር እንዳለብን በመፅሀፍ ቅዱስ 1 ቆሮንቶስ 13 ጠቅሶ ስለ ፍቅር እንደሚከተለው አስተምሮናል።አንብባችሁ ተጠቀሙበት..✍🏽
“1) በሰዎችና በመላእክት ልሳን ብናገር፣ ፍቅር ግን ከሌለኝ እንደሚጮኽ ናስ ወይም እንደሚንሿሿ ጸናጽል ነኝ።
2) የትንቢት ስጦታ ቢኖረኝ፣ ምስጢርን ሁሉና ዕውቀትን ሁሉ ባውቅ፣ ተራራንም ከቦታው የሚነቅል እምነት ቢኖረኝ፣ ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ።
3) ያለኝን ሁሉ ለድኾች ብሰጥ፣ ሰውነቴንም እንዲቃጠል ለእሳት ብዳርግ፣ ፍቅር ግን ከሌለኝ ምንም አይጠቅመኝም።
4) ፍቅር ታጋሽ ነው፤ ደግሞም ቸር ነው። ፍቅር አይመቀኝም፤ አይመካም፤ አይታበይም፤
5) ተገቢ ያልሆነ ነገር አያደርግም፤ራስ ወዳድ አይደለም፤ አይበሳጭም፤ በደልን አይቈጥርም።
6) ፍቅር ከእውነት ጋራ እንጂ በዐመፅ ደስ አይሰኝም።
7) ፍቅር ሁልጊዜ ይታገሣል፤ ሁልጊዜ ያምናል፤ ሁልጊዜ ተስፋ ያደርጋል፤ ሁልጊዜ ጸንቶ ይቆማል።
8)- ፍቅር ከቶ አይወድቅም፤ ነገር ግን ትንቢት ቢሆን ይሻራል፤ ልሳንም ቢሆን ይቀራል፤ ዕውቀትም ቢሆን ይሻራል።
9) ምክንያቱም የምናውቀው በከፊል ነው፤ ትንቢት የምንናገረውም በከፊል ነው።
10) ነገር ግን ፍጹም የሆነው ሲመጣ በከፊል የነበረው ይሻራል።
11) ልጅ ሳለሁ እንደ ልጅ እናገር ነበር፤ እንደ ልጅ ዐስብ ነበር፤ እንደ ልጅም አሰላ ነበር።ከጐለመስሁ በኋላ ግን የልጅነትን ነገር እርግፍ አድርጌ ትቻለሁ።
12) አሁን የምናየው በመስተዋት ውስጥ እንደሚታይ በድንግዝግዝ ነው፤በዚያ ጊዜ ግን ፊት ለፊት እናያለን። አሁን የማውቀው በከፊል ነው፤ በዚያ ጊዜ እኔ ራሴ ሙሉ በሙሉ የታወቅሁትን ያህል ዐውቃለሁ።
13) እንግዲህ እምነት፣ ተስፋ፣ ፍቅር እነዚህ ሦስቱ ጸንተው ይኖራሉ፤ ከእነዚህም የሚበልጠው ፍቅር ነው!!”
💯ፍቅርን ኑሩት እንጅ አታስመስሉበት!!
✅ሁሉም ሰው ያውቀው፣ይረዳውና ይማርበት ዘንድ ሸር አድርጉት

ረድኤት በረከታቸው ይደርብንና ፃድቁ   ያደረጉት ተአምር ይህ ነው፡- ከዕለታት በአንደኛው ቀን የክቡር አባታችን የአረጋዊ በዓል በሚከበርበት ዕለት መነኮሳቱ ከተራራው ግርጌ ወይም ከገመዷ ሥር...
12/23/2025

ረድኤት በረከታቸው ይደርብንና ፃድቁ ያደረጉት ተአምር ይህ ነው፡- ከዕለታት በአንደኛው ቀን የክቡር አባታችን የአረጋዊ በዓል በሚከበርበት ዕለት መነኮሳቱ ከተራራው ግርጌ ወይም ከገመዷ ሥር ለተሰበሰቡት ሰዎች የዝክር ጠላ ሲያወርዱ የጠላው እንስራ ከላይ ወደታች ወደቀ፡፡ ነገር ግን የእንስራው ክዳኗ እንኳን ሳይከፈት ከወደቀችም በኋላ 50 ክንድ ያህል መሬት ለመሬት ከተንከባለለች በኋላ በስተመጨረሸ ልክ ሰው እንዳስቀመጣት ሆና ተቀመጠች፡፡ ያችም የጠላ ማድጋ ከዚያ ትልቅ ገደል ላይ ወድቃ ምንም መሰበር እንዳልደረሰባት ጠላውም ምንም ጠብ እንዳላለ ባዩ ጊዜ በዚያየተሰበሰቡ ሁሉ ይህን አይተው በእጅጉ አደነቁ፡፡ አባታችን የባረከው የዝክሩ በረከት ነው በማለት ሁሉም ክዳኑን ከፍተው ከመጠጣት ይልቅ እንደቀባ ቅዱስ ሰውነታቸውነ ተቀቡት፡፡ ብረት እንኳን ከከፍታ ቦታ ላይ ወደ መሬት ቢወድቅ ይጣመማል የዚህ ማድጋ ነገርስ ድንቅ ነው እያሉ አደነቁ፡፡ የዝክሩንም ጠላ የቀመሱት ድውያን ተፈወሱበት፡፡ ሕዝቡም የአቡነ አረጋዊንም ዝክር በይበልጥ ማዘከር ጀመሩ፡፡ እኅት ወንድሞች አስተውሉ! የቅዱሳን አባቶች ገድላቸው የተነበበት ውሃ፣ ለዝክራቸው የተዘጋጀው ጠላ ድኅነተ ሥጋን ድኅነተ ነፍስን ያስገኛል፡፡

ከመሰወራቸው በፊት በዚህች ምድር ላይ ሳሉ በደብረ ዳሞ ሰማያዊ የመሥዋዕት ኅብስትና ንዋያተ ቅድሳት ከሰማይ ወርደውላቸዋል፡፡ ብፁዕ አባታችን በደብረ ዳሞ መጠነኛ ቤትን ሠራና ይዞት የመጣውን ታቦት በውስጡ አስገባው፡፡ ስለ ቊርባኑም ነገር ወደ #እግዚአብሔር ጸለየ፡፡ መላእክትም ለመሥዋዕቱ ሥርዓተ ዝግጅት የሚያስፈልጉትን የወርቅ ጻሕል፣ የብር ጽዋ፣ ለልብሰ ተክህኖ የሚያገለግሉ የወርቅ ላንቃ፣ ካባ፣ በውስጧ ትኩስ ኅብስት ያለባት መሶበ ወርቅ ለመሠዊያው የሚያስፈልገውን ሁሉ ከሰማይ ይዘውለት ወርደዋልና ዛሬም አባታችን በረድኤት በገዳሙ ላይ ጠለ ምሕረቱን ያወርዳል፡፡
አባታችን በደብረ ዳሞ እጅግ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን ያደረጉ ነበር፡፡ አቡነ አረጋዊ ከወንድሞቻቸው ጋር ሆነው እነዚህ ዘጠኙ ቅዱሳን አገራችንን በኪደተ እግራቸው ባርከዋታል፡፡

እነርሱም ብዙ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን ያደረጉ ነበር፣ #መላእክትም ዘወትር ባለመለየት ይጎበኙዋቸው ነበር፡፡ ጌታችን አምላካችን #ኢየሱስ ክርስቶስም ዘወትር እየተገለጠላቸው ይባርካቸውና ቃልኪዳን ይሰጣቸው ነበር፡፡ በጸሎታቸውም አጋንንትን ያስወጣሉ፣ ድውያንን ይፈውሳሉ፣ ዕውራንን ያበራሉ፣ ሙታንን ያስነሣሉ፡፡ ለእያንዳንዳቸውም የሃይማኖታቸውን ኃይል አሳዩ፡፡ ከእነርሱ መካከል ተራራ ያፈለሱ አሉ፣ ባሕሩን ከፍለው ደረቅ መንገድ ያደረጉ አሉ፣ ጠዋት ዘርተው ማታ ሰብስበው የሚያጭዱ አሉ፣ ይኸውም የስንዴውን ነዶ በግራር ዛፍ ላይ አበራይተው የዛፉ ቅጠል ሳይረግፍ በሬዎቹም ከዛፉ ላይ ሳይወድቁ ምርቱ ብቻ እየወረደ በአውድማው ላይ እንዲከማች ያደረጉ አሉ፣ ወዲያውም ስንዴውን ለመገበሪያ ሠይመው ለዘጠኝ ሰዓት መሥዋዕተ ቊርባን ያደረሱ አሉ፡፡ በዓለት ድንጋይ ላይ የወይራ ተክል ተክለው በዚያኑ ጊዜ ጸድቆ ለምልሞ ታላቅ ዛፍ ከሆነ በኋላ በ #እግዚአብሔር ፈቃድ ግንዱ ደርቆ ቆርጠውና ፈልጠው እንጨቱን አንድደው እሳቱ ፍም ከወጣው በኋላ ፍሙን በቀጭን ሻሽ ወስደው ለዘጠኝ ሰዓት የቅዳሴ ማዕጠንት ያደረሱ አሉ፡፡ ለቤተክርስቲያን አገልግሎት የሚውልና ለሥርዓተ ቊርባን ማከናወኛ የሚሆን ውኃው ሳይፈስ በወንፊት ውኃ የሚቀዱ አሉ፡፡
ከእነሱም አንዱ በዐረፈ ጊዜ የሥጋው ሥርዓተ ግንዘት በመላእክት እጅ የተከናወነ አለ፡፡ ይልቁንም ቁመቱና ርዝመቱ ከታላላቅ ገደል እጅግ በጣም የሚበልጥ የድንጋይ ዓምድ ከወንዝ ማዶ ዘንበል ብሎ መጥቶ ሥጋቸውን በክብር ተቀብሎ በተራራው ጫፍ ላይ እስከዛሬም ድረስ ፈጽሞ ሳይነቃነቅና ሳይናወፅ ቀጥ ብሎ ቆሞ ይገኛል፡፡ የሰዎቹም የመግነዝ ምልክት ጥበበኛ እንደሣለው ሥዕል በድንጋዩ ዓምድ ላይ ተስሎ ወይም ተቀርፆ ይታያል፡፡ ቆመው ጸሎት በሚጸልዩበት ጊዜ ዓሥሩ የእጆቻቸው ጣቶችና ዓሥሩ የእግሮቻቸው ጣቶች እንደፋና የሚያበሩበትና እንደመብረቅ የሚብለጨልጩበት ጊዜ አለ፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለአንዳች ሐዋርያ ስብከት አስቀድማ በክርስቶስ እንዳመነችና በዚህም ምክንያት የልዕልናዋን ታሪክ ለዓለም ለማሳወቅ ፈጥነው የሄዱ አሉ፡፡ የኢትዮጵያ ምድር በእነዚህ የቅዱሳን ኪደተ እግር ተቀደሰች፣ በውስጧም በመመላለሳቸው አውራጃዎቿና አደባባዮቿ ሁሉ ታደሱ፡፡ መዓዛ ትምህርታቸውና ተአምራቶቻቸው በሁሉም አውራጃዎች ተሠራጨ፣ የእምነቷንም መሠረት አጸኑ፡፡
እናንተ ቅዱሳን ሆይ! የነገሥታት ልጆች ስትሆኑ ላባችሁን እያንጠፈጠፋችሁ በዱር በገደል መንከራተታችሁ፣ በቀበሮም ጉድጓድ መቀመጣችሁ፣ የምትለብሱት ሳታጡ በበርድ በቁር መራቆታችሁ ምንኛ ድንቅ ነው!? የምትበሉት የምትጠጡት ሳታጡ የነገሥታት ልጆች ስትሆኑ ማራብ መጠማታችሁስ እንደምን ያለ ነው!?
የአባታችን የአቡነ አረጋዊ የወንድሞቻቸው የተሰዓቱ ቅዱሳን ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን!🙏

12/22/2025

Address

Oakland, CA
694601

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amanuel Yfter posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Amanuel Yfter:

Share