ƐŋU Love the Money and God!

  "በኢታንግ ልዩ ወረዳ ዛሬ ንጋት 11 ሰዓት በጀመረው ተኩስ ከ30 በላይ ሰዎች ተገድለዋል። የሞቱት ህፃናትም በርካታ ናቸው። የአጎቴ ልጆች የት እንዳሉ አይታቅም። ቤታቸው ተቃጥሏል" - ነ...
12/24/2025




"በኢታንግ ልዩ ወረዳ ዛሬ ንጋት 11 ሰዓት በጀመረው ተኩስ ከ30 በላይ ሰዎች ተገድለዋል። የሞቱት ህፃናትም በርካታ ናቸው። የአጎቴ ልጆች የት እንዳሉ አይታቅም። ቤታቸው ተቃጥሏል" - ነዋሪዎችና ቤተሰብ

➡️ "ሥራ እየሰራን ነው፤ ስንጨርስ እንነግራችኋለን"- የጋምቤላ ክልል ፕሬዝዳንት ወ/ሮ አለሚቱ ኡሞድ

በጋምቤላ ክልል ኢታንግ ልዩ ወረዳ ተርፋም ቀበሌ ዛሬ ረቡዕ ታህሳስ 15 ቀን 2018 ዓ/ም ከንጋቱ 11 ሰዓት ጀምሮ በተከፈተ ተኩስ "ከ30 በላይ ሰዎች መገደላቸውን" ነዋሪዎችና የዓይን እማኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።

በክልሉ የተለያዩ ወረዳዎች ባለፉት ሳምንታት በጸጥታ ችግር የንጹሐን ህይወት መቀጠፉን፣ ተጎጅዎች የህክምና አገልግሎት እንዳላገኙ ነዋሪዎች፣ የተጎጂ ቤተሰቦች፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን መግለጻቸው የሚታወስ ሲሆን፣ ዛሬ ደግሞ በኢታንግ ልዩ ወረዳ "በርካቶች ተገድለዋል" ተብሏል።

የአካባቢው ነዋሪዎችና አንድ የዓይን እማኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ "በኢታንግ ልዩ ወረዳ ዛሬ ንጋት 11 ሰዓት በጀመረው ተኩስ ከ30 በላይ ሰዎች ተገድለዋል። የሞቱት ህፃናትም በርካታ ናቸው" ብለዋል።

በወረዳው ተርፋም ቀበሌ የተኩል ልውውጥ ሲደረግ መዋሉን በመግለጽ፣ "ሁኔታው ከበድ እያለብን ነው" የሚሉት ነዋሪዎቹ፣ በርካታ ሰዎች በጥይት ተመትነው እንደቆሰሉ፣ ንጋት ላይ ሰዎች በተኙበት ቤት የማቃጠል ድርጊት እንደተፈጸመ አስረድተዋል።

ከቦታው ሆነው የተኩሱን ሁኔታ በቅርብ ርቀት ሲከታተሉ የነበሩ አንድ የዓይን እማኝ የክልሉ ነዋሪ፣ "የአንድ፣ የሁለት ዓመት ህፃናት" ጨምር ህይወታቸው ማለፉን ገልጸዋል። "የኔም የአጎቴ ልጆች የት እንዳሉ አይታቅም። ቤታቸው ተቃጥሏል። ልጆች፣ አረጋውያን፣ ወጣቶችም ተገድለዋል" ሲሉ ገልጸው፣ መንግስት ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጥ በአንክሮ አሳስበዋል።

"ቤቶች ተቃጥለዋል፤ በቃጠሎና በጥይት ህይወታቸው ያረፈው በርካታ ናቸው። በቦንብ የተመቱ ነዋሪዎችም አሉ" የሚሉት የዓይን እማኝ፣ "ከደቡብ ሱዳን የገቡ ሰዎች በተኩሱ ሲሳተፉ ተስተውለዋል" ሲሉ አክለዋል።

የጸጥታ ችግሩ በተመለከተ ምን ምላሽ እንዳላቸው ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጠየቃቸው የክልሉ ፕሬዚዳንት ወ/ሮ አለሚቱ ኡሞድ፣ " የጸጥታ አካላት ጋር ደውሉ ስብሰባ ላይ ነኝ" ያሉ ሲሆን፣ የጸጥታ ኃላፊው ስልክ እንዳላነሱ ስንነግራቸውም፣ "ሥራ እየሰራን ነው፤ ስንጨርስ እንነግራችኋለን " የሚል አጭር ምላሽ ሰጥተዋል።

የክልሉ ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ ለጊዜው ስልክ ያላነሱ ሲሆን፣ የክልሉ መንግስት በበኩሉ፣ የጋምቤላ ከተማን ጨምሮ "የጸጥታ ችግር በሚስተዋልባቸው የክልሉ አካባቢዎች" "ከጸጥታ አካላት ውጭ የሰውና የተሽከርካሪ" የሰዓት እላፊ ገደብ መጣሉን አስታውቋል።

በክልሉ የተለያዩ ወረዳዎች "በአኘዋክና ኑዌር ብሔረሰቦች መካከል" በተለያዩ ጊዚያቶች "ግጭት" ሲነሳ እንደነበር የሚታወቅ ሲሆን፣ ከአመት በፊት ቆሞ እንደነበር አሁን ደግሞ ማገርሸቱን፣ ችግሩን ለማስቆምም እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አሽኔ አስቲን ከሳምንት በፊት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው ይታወሳል።

የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ በበኩሉ፣ ችግሩን ለማስቆም እየተሰራ መሆኑን፣ 18 ተጠርጣሪዎች እንደተያዙ ከሳምንት በፊት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጹ የሚታወስ ሲሆን፣ ነዋሪዎቹ ደግሞ ዛሬ በኢታንግ ልዩ ወረዳ የተኩስ ልውውጥ እንደተደረገ ገልጸው፣ "በደቡብ ሱዳን የሚኖሩ የአኙዋክና ኑዌር ብሔረሰቦች" እንዳሉ፣ በዛሬ ተኩስም "ከደቡብ ሱዳን የመጡ ታጣቂዎች" እንተሳተፉ እየተናገሩ ናቸው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ


  |  "Over 30 people were killed in a shooting that began at 5:00 AM today in Itang Special Wereda. Many of the deceased...
12/24/2025

|
"Over 30 people were killed in a shooting that began at 5:00 AM today in Itang Special Wereda. Many of the deceased are children. The whereabouts of my cousins are unknown; their home has been burned down." — Residents and family members.
➡️ "We are working on it; we will inform you when we finish." — Mrs. Alemitu Umod, President of the Gambella Region.
Residents and eyewitnesses informed Tikvah Ethiopia that over 30 people were killed in a shooting that broke out at 5:00 AM today, Wednesday, December 24, 2025 (Tahsas 15, 2018 E.C.), in Terpham Kebele, Itang Special Wereda, Gambella Region.
It is recalled that residents, victims' families, and the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC) have reported the loss of innocent lives and a lack of medical services due to security issues in various weredas of the region over the past weeks. Today, reports indicate "many have been killed" in Itang Special Wereda.
Local residents and an eyewitness told Tikvah Ethiopia: "Over 30 people were killed in the shooting that started at 5:00 AM today in Itang Special Wereda. A large number of those killed are children."
Stating that an exchange of fire continued throughout the day in Terpham Kebele, residents described the situation as "becoming increasingly heavy." They explained that many people were wounded by gunfire and that homes were set on fire while people were still sleeping at dawn.
A regional resident who was an eyewitness and monitored the situation closely from the scene stated that children as young as one and two years old lost their lives. "I don’t know where my own cousins are. Their house was burned. Children, the elderly, and youth have been killed," the witness said, urgently appealing for the government to give the matter serious attention.
"Houses were burned; many died from both the fire and gunfire. There are also residents hit by grenades," the witness added, noting that "people who entered from South Sudan were observed participating in the shooting."
When Tikvah Ethiopia contacted the Regional President, Mrs. Alemitu Umod, for a response regarding the security crisis, she stated, "Call the security officials; I am in a meeting." When informed that the security head did not answer his phone, she gave a brief reply: "We are working on it; we will inform you when we finish."
While the head of the Regional Security Bureau did not answer his phone at the time, the regional government has announced a curfew on people and vehicles (excluding security forces) in "areas of the region where security problems are observed," including Gambella city.
It is well known that conflicts have frequently arisen between the Anyuak and Nuer ethnic groups in various weredas of the region. Mr. Ashne Astin, Head of the Regional Prosperity Party Office, told Tikvah Ethiopia a week ago that while the conflict had stopped a year ago, it has now resurfaced, and efforts are being made to stop it.
Similarly, the Regional Peace and Security Bureau stated a week ago that 18 suspects had been arrested. However, residents reporting on today's exchange of fire in Itang Special Wereda claim that "Anyuak and Nuer ethnic groups living in South Sudan" exist, and that "armed militants from South Sudan" participated in today's shooting.
Tikvah Ethiopia Addis Ababa
Would you like me to clarify any specific regional terms or provide more context on the locations mentioned in this report?

12/24/2025

🚨

በጋምቤላ ክልል ፤ ኢታንግ ልዩ ወረዳ፣ ፑልኮት / ተርፋም አካባቢ (ወደ ደቡብ ሱዳን ድንበር) ዛሬ ኃይለኛ ግጭት ሲካሄድ እንደዋለ፤ በዚህም የሰዎች ህይወት መጥፋቱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከጋምቤላ ቤተሰቦቹ ሰምቷል ድረግጽ የፈፀመው የአኝዋክ አሸባሪ GPLM የሚባለው ቡድን ነው ነዋሪዎች ገልጸዋል

ዛሬ በአካባቢው ያለው ሁኔታ እንደሚያስፈራ የገለጹልን ነዋሪዎች የፌዴራል መንግሥት አስቸኳይ መፍትሄ እንዲፈልግ አሳስበዋል።

በአንድ ቀበሌ ብቻ የበርካታ ሰዎች ህይወት መጥፋቱን አመልክተዋል።

ቤቶችም ሲቃጠሉ እንደዋሉ ጠቁመዋል።

ለስራ ጉዳይ ከጋምቤላ ከተማ 120 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ኚኛንግ እንዳለ የገለጸልን አንድ የቤተሰባችን አባልም የግጭቱን አሳሳቢነት ገልጾልናል።

መሄጃም ይሁን መምጫ መንገድ መዘጋቱን በመጠቆም ስጋት ላይ መውደቃቸውን አስረድቷል።

ግጭቱ እንዲበርድ አስቸኳይ መፍትሄ እንዲፈለግ እንዲሁም ወደ ጋምቤላ ከተማ የሚወጡበት መንገድ እንዲመቻችላቸው ጠይቋል።

በጋምቤላ ከተማ እና ዙሪያው በሌሎችም ቦታዎች ሰሞነኛው ግጭት በአገር መከላከያ እና ፌዴራል ፖሊስ እንዲረጋጋ ቢደረግም በኢታንግ ልዩ ወረዳ ያለው ሁኔታ አሳሳቢ መሆኑ ተገልጿል።



Address

Raleigh, NC

Telephone

+19109960736

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ƐŋU posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ƐŋU:

Shortcuts

Share