Ethio Daily ኢትዮ ዴይሊ

Ethio Daily ኢትዮ ዴይሊ Ethio daily is a way to get your Ethiopia-related videos to the people that matter to you. Follow us if you need hot news update

ወጣቷ በሰዉ እጅ ተገ""ድላ ተገኘች 😭እናንዬ ትባላለች ወጣትና የአንድ ልጅ እናት ስትሆን በጎንደር ከተማ ማራኪ ክፍለከተማ ነዋሪና ህይወትን ለማሸነፍ ምግብና መጠጥ በመሸጥ ራሷን ታስተዳድር ...
10/12/2025

ወጣቷ በሰዉ እጅ ተገ""ድላ ተገኘች 😭

እናንዬ ትባላለች ወጣትና የአንድ ልጅ እናት ስትሆን በጎንደር ከተማ ማራኪ ክፍለከተማ ነዋሪና ህይወትን ለማሸነፍ ምግብና መጠጥ በመሸጥ ራሷን ታስተዳድር ነበር ።

ከወራት በፊት ግን ለወትሮው እለት ከእለት ተዘግቶ የማያዉቀዉ የእናንንዬ ቤት ድንገት ለቀናት ሳይከፈት ይሰነባብታል ። ይህን የታዘቡ አከራዮች ለቤተሰቦቿ ይደዉላሉ ። ቤተሰቦቿም ያለችበትን ለማወቅ እንዳልቻሉና ለእነሱም ደብዛዋ እንደጠፋባቸዉ ይነግሯቸዋል ቤቷ እንደተዘጋ ይሰነብታል ።

ቀናት ቀናትን እየተኩ ሲሄዱ ቤተሰብ መጨነቅ ና ማፈላለግ ይጀምራሉ ። ከዚህ መካከልም ለቀናት ዝግ በነበረው የእጅ ስልኳ ተከፍቶ ለቤተሰቡ ደህና ነኝ አዲስአበባ በድንገት ስለሄድኩ ገንዘብ ስለቸገረኝ ላኩልኝ የሚል አጭር መልዕክት ለሟቿ ወንድም ይደርሳል ።

ወንድምዬዉም መጀመሪያ ክፉ ነገር ይፈጠራል ብሎ አልተጠራጠረም ነበርና ገንዘቡን ይልካል ። ብሩ እንደደረሳት ለማረጋገጥ ሲደዉል ግን ስልኩ መልሶ ተዘግቷል ለቀናት ለማግኘት ሙከራ ሲያደርግም በፅሁፍ መልዕክት ደህና እንደሆነችና በቅርቡ ወደ ጎንደር እንደምችመለስ በመፃፍ እንጂ በድምፅ ማግኘት አልቻለም ። ይሄኔ በመጠራጠር ማፈላለግ ይጀምራል ሆስፒታል እና ሌሎች ቦታዎች በሚያፈላልግበት ወቅት ይህቺው እናንዬ የተባለችው ወጣት አየሁኝ ሰማሁኝ የሚል በመጥፋቱ ጉዳዩን ወደ የህግ አስፈፃሚዎች በመዉሰድ በስልኳ አማካኝነት በተደረገ ክትትል የሟቿ የእጅ ስልክ እንደተባለው አዲስአበባ ሳይሆን ጎንደር እንደሆነ በጅፒኤስ አማካኝነት ይታወቃል ።

ፖሊስ ክትትሉን በመቀጠል የስልኩን አድራሻ ፈልጎ ሲያገኘዉ ግን እንደተባለው ግለሰቧ ሳይሆን ስልኩን የያዘው ሌላ ግለሰብ መሆኑን ያረጋግጣል ። ይህን ግለሰብም በቁጥጥር ስር በማዋል ምርምራ ይጀመራል ።

በምርመራ ወቅትም ይህ የድሮ ደንበኛዋ የነበረዉ ግለሰቡ እናንዬን መግደሉንና አስከሬኑንም ከከተማ ወጣ ባለ አቡነሐራ አካባቢ በተባለ ሰዋራ ስፍራ መጣሉን ያምናል ። ፖሊስም ወደስፍራው በመሄድ ማጣራቱን ሲቀጥል ከወር በፊት አንዲት ግለሰብ አስከሬን መገኘቱንና ምንም አይነት ማንነቷን የሚገልጽ መረጃ ባለመገኘቱ በመዘጋጃ ቤት አማካኝነት መቃብሯን ያረጋግጣል ።

በዚህ መልክ ተገድላ የተገኘችው የእናንዬ አስከሬን በማዘጋጃ ቤት ቤተሰብ ከሌላቸው መቀበርያ ቦታ ወጥቶ ወደ ትዉልድ ከተማዋ ደባርቅ መወሰዱንና በአስከሬን ምርመራ ወቅትም በሰዉ እጅ በአሰ""ቃቂ ሁኔታ መገደሏን ያረጋገጠው ፖሊስ ተጠርጣሪውን በህግ ጥላ ስር በማዋል የክስ ሂደት ላይ እንደሆነ ከጎንደር ካሉ የመረጃ ምንጮቻችን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል ።

ደፋሮቹ የጦርነት ዘጋቢዎች ተሸለሙ ! በድፍረት በሙያዊ መታመን በእሳት ውስጥ ደፍረው በመግባት ጋዛ፣ ሶሪያ፣ ዩክሬን ኢትዮጵያ የተከሰቱ ግጭቶችና ጦርነቶች ለአለም ያሳወቁ የጦርነት ዘጋቢዎች ...
10/12/2025

ደፋሮቹ የጦርነት ዘጋቢዎች ተሸለሙ !

በድፍረት በሙያዊ መታመን በእሳት ውስጥ ደፍረው በመግባት ጋዛ፣ ሶሪያ፣ ዩክሬን ኢትዮጵያ የተከሰቱ ግጭቶችና ጦርነቶች ለአለም ያሳወቁ የጦርነት ዘጋቢዎች ዓመታዊው የBayeux ሽልማት ማግኘታቸው ተነገረ ።

በትላንትናው እለት የፈረንሳዩዋ የባዩ ከተማ በተካሄደው የጋዜጠኞች የጦርነት ዘጋቢ የሽልማት ስነ ስርዓት ለ32ኛ ጊዜ የተከናወነ ሲሆን፤ ፍልስጤማዊው የፎቶ ጋዜጠኛ ሳሄር አልግሆራ፣አሊ ጀዳላህ (አናዶሉ ኤጀንሲ)፣ ጄሃድ አልሽራፊ፣ ቮልፍጋንግ ባወር (ዘይት ማጋዚን) የስዊዘርላንድ-ካናዳዊ ጋዜጠኛ ሞሪን ሜርሲየር እንዲሁም ስለኢትዮጵያ ዶክመንተሪ ፊልም የሰራችው ማሪያኔ ጌቲ (ክራከን ፊልምስ/አርቴ) ጨምሮ በርካታ ዘጋቢዎች ተሸልመዋል ።

ለዙማ ፕሬስ የሚዘግበው ፍልስጥኤማዊ የፎቶ ጋዜጠኛ ሳሄር አልግሆራ ለሁለት ዓመት ገደማ በጋዛ ሰርጥ በሃማስና እስራኤል መካከል ሲካሄድ የቆየውን አውዳሚ ጦርነትና የደረሰውን አስከፊ ሰብአዊ ቀውስ «በእሳት እና ረሃም መካከል » በተሰኘውና በተከታታይ በሰራቸው የፎቶ ዘገባዎች በመስራቱ ለሽልማት መብቃቱ እንዲሁም ከሳሄር በተጨማሪ የጀርመኑ የሳይት ጋዜጣ ዘጋቢ ዎልፍ ጋንግ ባየር፣ በህትመት ጋዜጠኝነት ዘርፍ አሸናፊ መሆኑ ተነግሯል።

በሕትመት ጋዜጠኝነት ዘርፍ ቮልፍጋንግ ባወር (ዘይት ማጋዚን) በሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም አሁንም ቀዶ ጥገና በማድረግ ተግድሎ እየፈፀመ የሚገኝ ሆስፒታል “የተረሳው” በሚል በሰራው ስራ አንደኛ በመሆን አሸንፏል።

ጋዜጠኛው በእንባ ታጅቦ ባስተላለፈው የቪዲዮ መልእክት በሆስፒታሉ የሚገኙትን "ዶክተሮች፣ ነርሶች እና በጎ ፈቃደኞች በየቀኑ የሚቻለውን ሁሉ ለሚያደርጉ በሙሉ" ምስጋና አቅርቧል።

በቴሌቭዥን ዘርፍ ጁሊ ደንገልሆፍ፣ ጀምስ አንድሬ እና ሶፊያ አማራ ከፈረንሳይ 24 አንደኛ በመሆን አሸንፈዋል፣ “ውስጥ የአሳድ የሽብር ማሽን” በሚል ዘገባ በሶሪያ መንግስት ነፃ ባወጣቸው እስር ቤቶች ላይ ያተኮረ ስራቸዉ ለዚህ ክብር አብቅቷቸዋል ።

በኢትዮጵያ ስላለው ግጭት “ትግራይ፡ መደፈር፣ ዝምተኛው መሳሪያ” የተሰኘው ዘጋቢ ፊልም የሰራች ማሪያኔ ጌቲ (ክራከን ፊልምስ/አርቴ) በኬን መታሰቢያ ሙዚየም በተካሄደው ሽልማቴ ግራንድ ፎርማት የቴሌቭዥን ዋንጫ አሸንፋለች ።

ከሲኤንኤን ዘጋቢዎች ጆማና ካራድሼህ፣ ታረቅ አል ሂሉ፣ መሀመድ አል ሳዋሊ፣ ሚክ ክሬቨር እና ማርክ ባሮን ስለ ጋዛ ህፃናት ህይወት በሰሩት ዘጋቢ ፊልም በተማሪዎች እና በሰልጣኞች የተሰየመውን ልዩ የኖርማንዲ ሪጅን ሽልማት አግኝቷል።

በአሜሪካዊው ጋዜጠኛ ጆን ሊ አንደርሰን የሚመራው የBayeux Calvados-Normandy Award ለ32ኛ ጊዜ ባዘጋጀው ሽልማት በመቶዎች የሚቆጠሩ ዓለም አቀፍ ዳኞች ድምፅ መሰረት በማድረግ በአስሩ ምድቦች አሸናፊዎችን እንደመረጡ ተናግረዋል ።

አሸናፊዎች በጣም ጠንካራ የጋዜጠኝነት ሙያ የገባቸው መሆኑን በመግለፅ አክብሮታቸዉን ገልፀዋል ።

በስነ ስርዓቱ ላይም በቅርቡ በስራ ላይ እያሉ ለተገደሉ ጋዜጠኞች ክብር ተሰጥቷል ሲል ያስነበበው France 24 ነዉ ።

የኔታ ቲዩብ ዘጋቢ ፦ ታዴ የማመይ ልጅ

የኦክቶፐስ ኃይል፡ የጥልቁ ጥበበኛ ታሪክ 🐙💧ከብዙ ጊዜ በፊት፣ በሰፊው የውቅያኖስ ዓለም ውስጥ፣ አንድ ልዩ ፍጡር ይኖር ነበር—ኦክቶፐስ ይባላል። ከሌሎች የባሕር ፍጥረታት በተቃራኒ፣ ኦክቶፐስ...
10/12/2025

የኦክቶፐስ ኃይል፡ የጥልቁ ጥበበኛ ታሪክ 🐙💧

ከብዙ ጊዜ በፊት፣ በሰፊው የውቅያኖስ ዓለም ውስጥ፣ አንድ ልዩ ፍጡር ይኖር ነበር—ኦክቶፐስ ይባላል። ከሌሎች የባሕር ፍጥረታት በተቃራኒ፣ ኦክቶፐስ ራሱን ለመከላከል የሚያገለግል ጠንካራ ቅርፊት ወይም ጠንካራ ጥርስ አልነበረውም። ነገር ግን የነበረው ነገር ከዚህ ሁሉ በላይ ኃይለኛ ነበር—ስምንት እጆች፣ ዘጠኝ አእምሮዎች እና ከአደጋ በፊት የመሸሻ መንገዶችን የመገመት ብልሀት። 🧠

አዳኞች ሲመጡ፣ ኦክቶፐስ በቀላሉ በቀለም ጭጋግ ውስጥ ይጠፋል 💨። የውሃ ፍሰቶች ሲቀየሩ፣ እራሱን ከፍሰቱ ጋር በማላመድ ቅርፁን ይቀይራል 🔄። በሰው እጅ በጠርሙስ ውስጥ ሲታሰር፣ ክዳኑን መክፈት ተምሯል 🗝️። ውቅያኖሱ ሲቀየር፣ የኮራል ሪፎች ሲፈራረሱ፣ እና የውሃው ሙቀት ሲጨምር፣ ኦክቶፐስ የሚጸናበት ጥበብ ነበረው።

የጥልቁን የመጀመሪያ ህግ ተምሮ ነበርና፡ “ለመኖር፣ ባህሩን አትቃወም—ባህር ሁን እንጂ።”

እናም፣ ትላልቅና ጠንካራ የሆኑ ሌሎች ፍጥረታት ሲጠፉ፣ ኦክቶፐስ በሕይወት ቆየ፣ ተሻሻለ፣ እናም በሁሉም ጥልቅ የውቅያኖስ እና የባህር ክፍሎች ውስጥ ተስፋፋ። ይህም ያደረገው በቁጥጥር ሳይሆን፣ በፍፁም መላመድ ነው። ✨

የኦክቶፐስ ጥበብ፡ የአመራር ትምህርቶች 🐙🧠

እውቀት ሁልጊዜ በምትጠብቀው ቦታ አይገኝም
ኦክቶፐስ አንድ ማዕከላዊ አእምሮ ያለው ሲሆን፣ በእያንዳንዱ እጅ ደግሞ ስምንት ትናንሽ “ንዑስ-አእምሮዎች” አሉት። እያንዳንዱ እጅ በተናጥል ውሳኔ መስጠት ይችላል።

🔹 እውነተኛ አመራር እውቀትን ማዕከላዊ ብቻ ማድረግ ማለት አይደለም። ታላላቅ መሪዎች እውቀትን ያሰራጫሉ፣ ነገር ግን ዓላማን ያማክራሉ። ስልጣን የተሰጣቸው ቡድኖችን ይፈጥራሉ። 🤝
መላመድ መርጡ የመቆያ መንገድ ነው

ኦክቶፐስ ቀለሙን፣ ቅርፁን፣ ሸካራነቱን እና ባህሪውን በቀላሉ ይቀይራል። ይህን የሚያደርገው ለመኖር እና ለመዋሃድ እንጂ ለማሳየት አይደለም። ሲፈልግ ድንጋይ፣ ኮራል ወይም መርዛማ ዓሣ ሊሆን ይችላል። 🦎

🔹 በለውጥ ጊዜ ግትርነት ገዳይ ነው። መላመድ፣ ቅርፅ መቀየር እና እውቀት ያድናሉ። መሪነት ቋሚ ማንነት ሳይሆን ተለዋዋጭ ችሎታ ነው። 🌊

ለስላሳ ኃይል (Soft power) ከጠንካራ ኃይል በላይ ያሸንፋል
ኦክቶፐስ አጥንት፣ ትጥቅ፣ ወይም ጥፍሮች ሳይኖረው፣ ሙሉ በሙሉ በእውቀት እና በፈጠራ ላይ ይተማመናል። ለስላሳነቱ (ደካማ የሚያስመስለው) እንዲያሸንፍ ያደርገዋል።

🔹 በአመራር ውስጥ፣ ለስላሳ ኃይል—ርኅራኄ፣ የማወቅ ጉጉት፣ ፈጠራ—ብዙውን ጊዜ ከጠንካራ ኃይል ይበልጣል። ለስላሳነት ደካማነት አይደለም። በለውጥ ዓለም ውስጥ የህልውና ቅርፅ ነው። 💡
መደበቅ እና ስትራቴጂያዊ ታይነት 🕵️♂️

ኦክቶፐስ መቼ መደበቅ (በአደን ጊዜ) እና መቼ መታየት (በስሪያ ጊዜ) እንዳለበት ያውቃል።

🔹 ታላላቅ መሪዎች መቼ ከፊት መምራት እና መቼ ከኋላ መምራት እንዳለባቸው ያውቃሉ። ታይነት መሣሪያ እንጂ ሱስ መሆን የለበትም።

የማወቅ ጉጉት የእውቀት ሥር ነው

ኦክቶፐሶች በመጫወት እና በመመርመር ይማራሉ። እውቀታቸው ወደበለጠ የማወቅ ጉጉት ይመራል።

🔹 የማወቅ ጉጉት የፈጠራ እናት ናት። መሪ “ለምን?” ብሎ መጠየቅ ሲያቆም፣ መውደቅ ይጀምራል።
ራስን መስዋዕት ማድረግ🕯️

ሴቷ ኦክቶፐስ እንቁላል ስትጥል፡በጭራሽ ሳትበላ እስከምትሞት ድረስ ህይወቷን በሙሉ እንቁላሎቿን በመጠበቅ ሞቷ ሕይወት ይሰጣል።

🔹 የትውልድ አመራር መስዋዕትነት ነው። ታላላቅ መሪዎች የድካማቸውን ፍሬ ላያዩ ይችላሉ፣ ነገር ግን ቁርጠኝነታቸው ቀጣይነትን ያረጋግጣል።

መደበቅ እና ትክክለኛነት🎭
ኦክቶፐስ ለመኖር ይደበቃል ነገር ግን በነፃነት ሲሆን እውነተኛ ባህሪውን ያሳያል። ይህ ትክክለኛነት እና ህልውናን ማመጣጠን እንደሚያስፈልግ ያስተምራል።

🔹 መሪዎች መቼ እውነትን መግለፅ፣ መቼ መጠበቅ፣ እና ግልፅነትን ከጥንቃቄ ጋር እንዴት ማመጣጠን እንደሚችሉ ስትራቴጂያዊ ትክክለኛነትን መማር አለባቸው።

እድሳት እና ፈውስ፡ የመሪነት ቁርጠኝነት 💫
ኦክቶፐስ አንድ እጅ ቢቆረጥበት፣ በቀላሉ ሌላ ያበቅላል። ይህ ህመም ጊዜያዊ ነው፤ እድሳት ተፈጥሮአዊ ነው የሚለውን መርህ ያስተምራል።

🔹ውድቀት እና መጥፋት የአመራር ውቅያኖስ አካል ናቸው። የሚገልጽህ ነገር መድማትህ ሳይሆን—እንደገና መወለድህ ነው። እውነተኛ መሪዎች ከስብራታቸው በፍጥነት ያገግማሉ። 💪
የኦክቶፐስ ባህሪ ከስትራቴጂያዊ አመራር አንጻር 🌐

የኦክቶፐስ ባህሪ ለዘመናዊ የአመራር ሥርዓቶች ጥልቅ ትምህርቶችን ይሰጣል።

ብዙ አእምሮዎች 🧠: በሁሉም ጥግ ላይ ውሳኔ መስጠትን መፍቀድ።

መደበቅ🦎: መሪዎች አካባቢን ማንበብ እና መላመድ አለባቸው።

እድሳት 💪: መሪዎች ሃገራት እና ድርጅቶችን ከውድቀት መዳን መቻል አለባቸው።

የማወቅ ጉጉት 💡: የመማር ባህሎች ከግትር ተዋረዶች ይበልጣሉ።

መስዋዕትነት 🕯️: መሪዎች ለቀጣዩ ትውልድ እንጂ ለራሳቸው ህልውና አይኖሩም።

በትራፊክ አደጋ የ10 ሰዎች ሕይወት ተቀጠፈበአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን፣ ጨፋ ሮቢት ከተማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ10 ሰዎች ሕይወት ተቀጠፈ፡፡ አደጋው 60 ሰዎችን አሳፍሮ...
10/12/2025

በትራፊክ አደጋ የ10 ሰዎች ሕይወት ተቀጠፈ

በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን፣ ጨፋ ሮቢት ከተማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ10 ሰዎች ሕይወት ተቀጠፈ፡፡

አደጋው 60 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ፣ ልዩ ስሙ ጃራ ድልድይ በተባለ ቦታ ላይ ከከባድ ጭነት ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ የተከሰተ ነው ተብሏል፡፡

በአደጋውም እስካሁን የ10 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የከተማው ከንቲባ አቶ ሰይድ መሃመድ ለፋና ዲጀታል ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪም በርካታ ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱን ጠቁመው ÷ የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል አመልክተዋል፡፡

''የሌላ ሀገር ዜግነት መቀበል ወራዳነት ነው'' ኮሎኔል አብዲሳ አጋህይወታቸው ካለፈ ነገ ጥቅምት 3 ድፍን 41 ዓመት የሚሞላቸውን ኮሎኔል አብዲሳ አጋን መዘከር ቀጥለናል፡ በወለጋ የተወለደው...
10/12/2025

''የሌላ ሀገር ዜግነት መቀበል ወራዳነት ነው'' ኮሎኔል አብዲሳ አጋ

ህይወታቸው ካለፈ ነገ ጥቅምት 3 ድፍን 41 ዓመት የሚሞላቸውን ኮሎኔል አብዲሳ አጋን መዘከር ቀጥለናል፡ በወለጋ የተወለደው አብዲሳ የኢትዮጲያን ጦር የተቀላቀለው በ14 አመቱ ሲሆን ጣልያን ኢትዮጲያን ስትወር አገሩን ለመከላከል በሚደረግ ውጊያ ላይ መሳተፍ ጀመረ። እጅግ ዘመናዊ መሳሪያዎች ከታጠቀው የጣልያን ጦር ጋር በሚደረገው ውጊያ ላይ ባጋጠመው የመቁሰል አደጋ ህክምና ላይ ከቆየ በኋላ አዲስ አበባ ውስጥ ፒያሳ አካባቢ በሚገኝ ቤት በቁም እስር ላይ ነበር። በኋላ ጣልያን ኢትዮጲያን እንዲያስተዳድር በሾመችው ግራዚያኒ ላይ የመግደል ሙከራ ከተደረገ በኋላ አብዲሳ አጋ እና ሌሎች 37 የሚሆኑ የቁም እስረኞች ተጠርጣሪ ተብለው በከባድ ስቃይ እስር ቤት ከቆዩ በኋላ በወቅቱ የጣልያን ግዛት በነበረችው በሱማሊያ በኩል ወደ ሲሲሊ ተወስዶ በጣልያን አገር የጦር እስረኛ ተደረገ። በእስር ቤት ጠባዎች ጥብቅ ቁጥጥር የሚደረግበት አብዲሳ እዛው ታስሮ የሚገኝ ሁሊዮ የተባለ የዩጎዝላቪያ ምርኮኛ በጋራ እቅድ በማውጣት ከእስር ቤት ማምለጥ ቻለ። ከእስር ካመለጡ በኋላ ከፋሺስት ጣልያን ወታደሮች በመደበቅ እና በመሸሽ ፋንታ በአብዲሳ መሪነት እና እቅድ አውጪነት በሌሊት ታስረው ወደነበረበት እስር ቤት ተመልሰው ጠባቂዎቹ ላይ ጥቃት በመፈጸም የታሰሩትን እስረኞች በሙሉ ነጻ በማውጣት የኢትዮጲያውያንን ጀግንነት በአድዋ ብቻ ሳይሆን በጣልያን ምድርም ያስመሰከረ ድንቅ ተዋጊ ነበር።

የአብዲሳ ጀግንነት በዚህ አላበቃም ከእስር ቤት ያስመለጧቸውን ሰዎች በማሰባሰብ የራሱን ጦር ካደራጀ በኋላ ጣልያኖችን በገዛ አገራቸው ያንቆራጥጣቸው ገባ። ከአድዋ ጀምሮ የኢትዮጲያውያንን ወኔ የተረዱት ጣልያኖች የአብዲሳን ጦር በፍርሃት ያዩ የነበረ ሲሆን በተለያዩ ቦታዎች ከጣልያን ጦር ጋር በመዋጋት ብዙ ድሎችን እያስመዘገበ ነበር። ቆራጥነቱን የተረዱት ጣልያኖች የሚያረጉት ግራ ቢገባቸው ከበርካታ ስጦታዎች ጋር ጦሩን ይዞ የጣልያንን ሰራዊት እንዲቀላቀል መማጸን ጀምረው ነበር። የሌላ ሀገር ዜግነት መቀበል ወራዳነት ነው በማለት ለፋሺስት ጦር መዋጋት አገር መክዳት እንደሆነ አስረግጦ የተናገረው አብዲሳ ትግሉን አፋፍሞ በቀጠለበት ወቅት የሁለተኛው የአለም ጦርነት ተቀሰቀሰ።
የተባበሩት የአሜሪካ እና እንግሊዝ መንግስታት ከጀርመን ጋር ያበረችውን ጣልያንን እየተዋጉ በነበረ ሰዓት ስለ አብዲሳ ዝና ከሰሙ በኋላ ለጦሩ የሚገባውን ድጋፍ በማድረግ የፋሺስት ስርዓቱን ለማዳከም ከሚያግዙ መንገዶች አንዱ ሆኗቸው ነበር። በድጋፉ በመጠናከር ፋሺስቱን ሰራዊት ማርበድበድ የቀጠለው አብዲሳ የጣልያን ጦር ተሸንፎ ዋና ከተማዋ ሮም በአሜሪካን እና እንግሊዝ የሚመራ ጦር እጅ ስር ከወደቀች በኋላ የሚመራቸውን ከተለያዩ አገር የወጡ ወታደሮች በሙሉ ክንዳቸው ላይ የኢትዮጲያን ባንዲራ እንዲያስሩ በማድረግ የሃገሩን ባንዲራ እያውለበለበ ሮም ከተማ ሲገባ በአለም አቀፉ ህብረት ጦር ትልቅ አቀባበል ተደርጎለት ነበር። ከዛም በኋላ ከተጨማሪ ወታደሮች ጋር በአለም አቀፉ ህብረት ስር የሚመራ ጦር መሪ በመሆን ጀርመንን ለማሸነፍ በሚደረገው የመጨረሻ ውጊያ ላይ ተሳትፎ ግዳጁን በሚገባ በመወጣት የኢትዮጲያን ባንዲራ ከእጁ ሳይለይ በርካታ የጀርመን ከተሞችን ነጻ ማውጣት ችሎ ነበር።

ምንጭ:- “አብዲሳ አጋ በኢጣሊያ በረሃዎች የተሰኝ መጽሀፍ

Via Muktarovich usmanova

ጌታችን ከሐዋርያት አስቀድሞ የመረጠው ደቀ መዝሙር እንደሆነ መጽሐፈ ስንክሳር ይናገራል፡፡እርሱም በየአገሩ እየተዘዋወረ ወንጌልን በመስበክ ከአይሁድና ከአረማውያን ወገን ብዙዎችን ወደ ክርስትና...
10/12/2025

ጌታችን ከሐዋርያት አስቀድሞ የመረጠው ደቀ መዝሙር እንደሆነ መጽሐፈ ስንክሳር ይናገራል፡፡

እርሱም በየአገሩ እየተዘዋወረ ወንጌልን በመስበክ ከአይሁድና ከአረማውያን ወገን ብዙዎችን ወደ ክርስትና መልሶ አጥምቋል፡፡ በማቴዎስ 10÷3 እንደተጻፈው አባቱ እልፍዮስ ይባላል፡፡ በሉቃስ 6÷16 ደግሞ ሐዋርያው “ታዴዎስ ልብድዮስ”፣ “የያዕቆብ ልጅ ይሁዳ” እየተባለም ተብሎ ሲጠራ እናያለን፡፡ አንድ ቀን ወደ ሀገረ ስብከቱ ወደ ሦርያ ለስብከተ ወንጌል ሲሔድ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በጐልማሳ አምሳል ተገልጦ “ወዳጄ ታዴዎስ ሆይ፣ እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ” ብሎ ሰላምታ ሰጥቶት ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ የሐዋርያት አለቃ ቅዱስ ጴጥሮስም እንደ አባትነቱ ወደ ሦርያ አብሮት ሔዶ ነበረ፡፡ ከከተማዋ አጠገብ ሲደርሱም አንድ ሽማግሌ በሮችን ጠምደው ሲያርሱ አገኙ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም ሽማግሌውን ምግብ ለመናቸው፡፡

“በሬዎቼን ጠብቁ” ብላዋቸውም ሊያመጡላቸው ወደ ቤታቸው ሔዱ፡፡ ሽማግሌው እስኪመለሱ ቅዱስ ጴጥሮስ ሠላሳ ትልም ካረሰ በኋላ ቅዱስ ታዴዎስ በዚያ የነበረውን የሥንዴ ዘር ዘራበት፡፡ የተዘራውም ወዲያዉኑ በቅሎ፣ አድጎ፣ እሸት ኾነ፡፡ ሽማግሌው ምግብ ይዘው ከቤታቸው ሲመለሱም ሐዋርያት ያደረጉትን ተአምር አይተው ደነገጡ፡፡ ከእግራቸው ሥር ወድቀውም “እናንተ ከሰማይ የወረዳችሁ አማልክት ናችሁን?” አሏቸው፡፡ እነርሱም “እኛ የእግዚአብሔር ባሮች እንጂ አማልክት አይደለንም” አሉ፡፡ ሽማግሌውም ስላደረጋችሁልኝ በጎ ሥራ በምትሔዱበት ቦታ ኹሉ ልከተላችሁን? አሏቸው፡፡ እነርሱም “በሬዎቹን ለጌታቸው መልስና በቤትህ የምንበላውን ታዘጋጅልን ዘንድ ለባለቤትህ ንገራት ወደ ከተማዋ ገብተን የላከን አምላካችን እግዚአብሔር እስከሚጠራን ጊዜ ድረስ እንቆያለንና” አሏቸው፡፡

ሽማግሌውም የሥንዴው እሸት ይዘው፣ በሬዎቻቸውን እየነዱ ወደ ከተማ ሲሔዱ ሰዎች ወቅቱ የእርሻ እንጂ የእሸት ጊዜ ስላልነበረ እየተገረሙ “እሸቱን ከወዴት አገኘኸው?” አሏቸው፡፡ ሽማግሌው ግን መልስ አልሰጧቸውም፡፡ ሐዋርያት እንደዘዟቸው በሬዎቹን ለጌታቸው መልሰው ሚስታቸው ራት እንድታዘጋጅላቸው ነገሯት፡፡ የከተማው መኳንንት ስለ እሸቱ ሲሰሙ “በክፉ አሟሟት እንዳትሞት ከወዴት እንዳገኘኸው ንገረን” አሏቸው፡፡ ሽማግሌውም ሐዋርያት ያደረጉትን ሁሉና ወደ እርሳቸው ቤት ቢመጡ ሊያገኟቸው እንደሚችሉ ነገሯቸው፡፡ መኳንንቱም ሰይጣን ልቡናቸዉን አነሳስቶታልና ሐዋርያቱን ለመግደል ወሰኑ፡፡ ሌሎች ግን “አምላካቸው ኢየሱስ የሚሹትን ሁሉ ያደርግላቸዋልና ልንገድላቸው አንችልም፡፡ ይልቅ በከተማው በር አመንዝራ ሴት ርቃኗን ብናስቀምጥ ወደ ከተማችን አይገቡም” አሉ፡፡ በከተማዋ መግቢያ በር እንደተባባሉት ሴቲቱን እርቃኗን አስረዋት ጠበቋቸው፡፡

ቅዱሳን ሐዋርያቱ ግን በሰዎቹ ልብና በሴቲቱ ላይ ያደሩትን ርኩሳን መንፈስ አስወጥተው በማስተማር በሥላሴ ስም አጥምቀው አገልጋዮችን ሾሙላቸው፡፡ ያቺንም ሴት ዲያቆናዪት አደርጎ ሾማት፡፡ ብዙ ድንቅና ተአምራትም አደረጉ፡፡ ሕዝቡም በእግዚአብሔር አመኑ፡፡ ከዚህ በኋላ አንድ ሰይጣን ያደረበትና ገንዘብ የሚወድ ጐልማሳ ባለጸጋ ቅዱስ ታዴዎስን በበዙ ተፈታተነው እርሱም ጌታችን እንደተናገረ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ስትሾልክ አሳየው፡፡ ያ ባለጸጋም ከቅዱስ ታዴዎስ እግር ስር ወድቆ ይቅርታ ጠየቀ ገንዘቡንም ሁሉ ለድሆች አከፋፈለ፡፡ ተምሮና አምኖም ተጠመቀ፡፡ ቅዱስ ታዴዎስ በየአገሩ እየተዘዋወረ ወንጌልን ሲሰብክ ቆይቶ ከአይሁድና ከአረማውያን ዘንድ ብዙ መከራ ከደረሰበት በኋላ አገልግሎቱን ፈጽሞ ሐምሌ 2 ቀን ዐርፏል፡፡ በብዙ ስጋዊ መከራ ውስጥ የሚያልፉ ቅዱሳን ገዳማውያንም የሐዋርያትን ፈለግ ተከትለው ዓለምን ንቀዋል፡፡ ገዳማቸውን እየደገፍን በዓታቸውን እያጸናን ከበረከታቸው እንካፈል፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

በጭቁኑ የማዳጋስካር ህዝብ ላይ ቃታ አናስብም ! /መከላከያ /እ.ኤ.አ. በ2009 በሀገሪቱ በተደረገ መፈንቅለ መንግስት ፕሬዚዳንት አንድሪ ራጆኤሊ ከብክበዉ ቤተመንግሥት ያስገቡት የስልጣናቸው...
10/12/2025

በጭቁኑ የማዳጋስካር ህዝብ ላይ ቃታ አናስብም ! /መከላከያ /

እ.ኤ.አ. በ2009 በሀገሪቱ በተደረገ መፈንቅለ መንግስት ፕሬዚዳንት አንድሪ ራጆኤሊ ከብክበዉ ቤተመንግሥት ያስገቡት የስልጣናቸው መሰረት የነበሩት
የማዳጋስካር ወታደሮች አመፁን በመደገፍ በዋና ከተማው ከተሰበሰቡ ፀረ-መንግስት ተቃዋሚዎች ጋር መቀላቀላቸው ተነገረ።

በማዳጋስካር በውሃ እና በመብራት መቆራረጥ በተማረሩ ዜጎች መስከረም 25 ቀን የተቀሰቀሰውና በወጣቶች እየተመራ ከእለት ወደ እለት በፍጥነት እየሰፉ በሄደው ተቃዉሞና አመፅ ቅዳሜ ከሰአት በኋላ በዋና ከተማው ጎዳናዎች ላይ በተካሄደው ተቃውሞ
የመንግስቱ ምርጥ የተባሉት ካፕሳት ክፍል ወታደሮች ተቃውሞን ተቀላቅለዋል። ተብሏል

የፕሬዚዳንት አንድሪ ራጆኤሊናን አገዛዝ በመቃወም የተቃውሞ ሰልፎች እየጨመሩ በመጡበት ወቅት የማዳጋስካን ወታደሮች ትእዛዝን በመጣስ በሺዎች የሚቆጠሩ የመንግስት ተቃዋሚዎችን በዋና ከተማይቱ አንታናናሪቮ ባዘጋጁት አመፅ መቀላቀላቸው የተገለፀ ሲሆን ሰልፈኞቹ ከሬጅመንቱ ጋር በመሆን ሰልፍ የወጡ ሲሆን በህዝቡ ላይ ጥይት አንተኩስም ሲሉ ቀደም ብለው ተናግረው እንደነበር ተዘግቧል ።

ከዚህ ቀደም ብሎ በከተማዋ ወጣ ብሎ በሚገኝ የጦር ሰፈር ውስጥ በተደረገ ስብሰባ፣ በ2009 በራጆኤሊና መነሳት ውስጥ ትልቅ ሚና የተጫወተው የ CAPSAT ክፍል ውስጥ ያሉ ወታደሮች፣ የፕሬዚዳንቱን መልቀቅ ለሚጠይቁ ተቃዋሚዎች ያልተለመደ ህዝባዊ የአብሮነት ጥሪ አቅርበዋል።

በሶኒዬራና አውራጃ የሚገኘው የጦር ሰፈር ወታደሮች በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በተለጠፈው ቪዲዮ ላይ "ሀይልና ፣ ወታደር፣የህዝብ ጠባቂ እንጂ የወንበር ማስጠበቂያ አይደለም ።
ጄንዳርሮችን እና ፖሊሶችን ለለዉጥ እንተባበር እና ጓደኞቻችንን፣ ወንድሞቻችንን እና እህቶቻችንን ለመተኮስ ደሞዝ አንከፍልም" ብለዋል።

በተመሳሳይ በአውሮፕላን ማረፊያው የሚገኙ ወታደሮች "ሁሉም አውሮፕላኖች እንዳይነሱ ። የአለቆቻችሁን ትእዛዝ አትታዘዙ። እና በሌሎች ካምፖች ውስጥ ያሉ "ጓደኞቻችሁን እንዲተኩሱ ትእዛዝ እንዳይሰጡ"“በሮቹን ዝጋ እና መመሪያችንን ጠብቅ” ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል ።

ጥቅምት 11 ቀን 2025 ከሰአት በኋላ ከአንታናናሪቮ በስተደቡብ ከምትገኘው ሶኒየራና ከሚገኘው ካፕሳት ክፍል ወታደሮች ጋር በመሆን የታጠቁ ተሽከርካሪዎችን እየነዱ የማዳጋስካር ባንዲራ እያውለበለቡ መታየታቸውን የዘገቡት ሮይተርስ አልጀዚራ ሲኤንኤን የዜና ወኪሎች ናቸው ።

የኔታ ቲዩብ ዘጋቢ ፦ ታዴ የማመይ ልጅ

የአሜሪካ አዛዥ ናዛዥነት ከእንግዲህ አክትሟል ! /ኪም ጆንግ ኡን/የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን በሚቀጥሉት ሳምንታት ሊሞክረው ይችላል ብለው የሚያምኑትን አዲስ አህጉር አቀፍ ባሊስቲክ ...
10/12/2025

የአሜሪካ አዛዥ ናዛዥነት ከእንግዲህ አክትሟል ! /ኪም ጆንግ ኡን/

የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን በሚቀጥሉት ሳምንታት ሊሞክረው ይችላል ብለው የሚያምኑትን አዲስ አህጉር አቀፍ ባሊስቲክ ሚሳኤልን በዛሬው እለት በፒዮንግያንግ አደባባዮች ማሳየታቸው ተነገረ ።

የኮሪያ የሰራተኞች ፓርቲ የተመሰረተበትን 80ኛ አመት በዓል ተከትሎ በፒዮንግያንግ አደባባይ በተዘጋጀው ትርኢት ሰሜን ኮሪያ የላቀውን Hwasong-20 አቋራጭ ባሊስቲክ ሚሳኤልን አሳይታለች ሲል የመንግስት ሚዲያ KCNA ዘግቧል።

አሁን ባሉት የአሜሪካ ሚሳኤል መከላከያ ስርዓቶች ላይ ጭንቀትን ይጨምራሉ የተባለለትን አህጉር አቀፍ ባሊስቲክ ሚሳኤል ባሳዩበት ትልቅ ወታደራዊ ሰልፍ የቻይናው ጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ኪያንግ፣ የቀድሞ የሩሲያ ፕሬዚዳንት ዲሚትሪ ሜድቬዴቭ እና የቬትናም ኮሚኒስት ፓርቲ መሪ ቶ ላም ተገኝተዋል ተብሏል ።

በሰልፉ ላይ ባደረጉት ንግግር ኪም በውጭ አገር ለሚያገለግሉት የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች በተለይም በሩሲያ የዩክሬን ጦርነት ውስጥ “ሞቅ ያለ ማበረታቻ” አቅርበዋል፣ ጀግንነታቸው ከአገር መከላከያ አልፎ “ከሶሻሊስት ግንባታ” ታላቅ አስተዋጽኦ እንዳለዉ መግለፃቸውን ኬሲኤንኤን ዘግቧል።

ሀገራቸው “ከአሜሪካ ኢምፔሪያሊስቶች እየተባባሰ የመጣውን የኒውክሌር ጦርነት ስጋት” ለመከላከል የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ልማቷን እና ኢኮኖሚዋን በአንድ ጊዜ እያራመደች ነው ብለዋል።

“ፓርቲያችን እና መንግስታችን አሁንም ጠንከር ያሉ ፖሊሲዎችን በመቀበል፣ ጠንካራ መርሆችን በማክበር እና ደፋር የመከላከያ እርምጃዎችን በመውሰድ የጠላቶቻችንን ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ እርምጃዎችን እየታገለ ነው” ሲል ኪም ተናግሯል።

የላቀውን Hwasong-20 አቋራጭ ባሊስቲክ ሚሳኤልን KCNA የሀገሪቱ “ጠንካራው የኒውክሌር ስትራቴጂካዊ የጦር መሳሪያ ስርዓት” በማለት ገልጿል።

የHwasong ICBM ሰሜን ኮሪያ በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ የትኛውም ቦታ ላይ እንድትመታ ሊያስችላት ይችላል የተባለ ሲሆን
ለማረጋገጥ ግን ከዚህ አመት መጨረሻ በፊት ሲፈተሽ ለማየት መጠበቅ አለብን "በዩኤስ የተመሰረተው ካርኔጊ ኢንዶውመንት ለአለም አቀፍ ሰላም አንኪት ፓንዳ ተናግረዋል።

የኔታ ቲዩብ ዘጋቢ ፦ ታዴ የማመይ ልጅ

"ተማሪዎች በምደባ ሳይሆን በፍላጎታቸው ወደ ዩኒቨርስቲ እንዲገቡ ይደረጋል" ትምህርት ሚኒስቴር  👉 የዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች እና የሥራ ኃላፊዎች ስለ ተማሪዎቻቸው ትክክለኛ መረጃ ካላቀረቡ ከ...
10/11/2025

"ተማሪዎች በምደባ ሳይሆን በፍላጎታቸው ወደ ዩኒቨርስቲ እንዲገቡ ይደረጋል" ትምህርት ሚኒስቴር

👉 የዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች እና የሥራ ኃላፊዎች ስለ ተማሪዎቻቸው ትክክለኛ መረጃ ካላቀረቡ ከኃላፊነታቸው ይነሳሉ ተብሏል

በቀጣይ የትምህርት ዘመን ሚኒስቴሩ ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እንደማይመድብ፤ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስታውቀዋል።

የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተልዕኮን እንዲተገበር እና የተቋማቱን አዳዲስ መለኪያን የያዘ ሁለተኛው የፊርማ ሥነ-ስርዓት በከፍኛ የጥምህርት ተቋማት እና በትምህርት ሚኒስቴር መካከል ተካሂዷል፡፡

በዚህ የፊርማ ሥነ-ስርዓት ላይ የሚኒስቴሩ ከፍተኛ አመራሮች፣ ጥሪ የተደረገላቸው ከፍተኛ የመንግሥት ሃላፊዎችና የሁሉም ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች ተገኝተዋል።

በዚህም የትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በርካታ የሪፎርም ሥራዎችን ቀርጾ በማከናወን ላይ እንደሚገኝ የተገለጸ ሲሆን፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በትምህርት ዘመኑ በእቅድ የሚያከናውኗቸውን ቁልፍ ተግባራት አፈጻጸም በመከታተል ለሚከሰቱ ክፍተቶች አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግና ተጠያቂነትን ማስፈን ተጠቃሽ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዚሁ መድረክ ላይ፤ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚገቡ ተማሪዎች በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ምደባ ሳይሆን በተማሪዎች ምርጫ እንዲሆን ይሰራል ሲሉ ተናግረዋል።

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጥራት ያለው ተማሪ ከማፍራት እና የጥናትና ምርምር ውጤት ከማቅረብ ረገድ ያሉት ዩኒቨርሲቲዎች በጣት የሚቆጠሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በዚህም አዲስ አሰራር 'የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ምን ያህል በተማሪዎች ተመራጭ ናቸው' የሚለው በትኩረት የሚታይ ነው ብለዋል።

የሥራ ዕድልን ከመፍጠር፣ ጥሩ ክፍያን ከማስገኘት፣ የትምህርት ዘርፍ፣ የትምህርት ጥራት ከማስጠበቅ ረገድ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተማሪዎች ተቀዳሚ ምርጫ ለመሆን ጥረት ሊያደርጉ ይገባል ሲሉም አሳስበዋል።

ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በፍላጎታቸው ማስገባት ዩኒቨርስቲዎችን ስጋት ውስጥ የሚጥል መሆኑንም፤ ፕሮፌሰሩ በፊርማ ሥነ-ስርዓቱ ወቅት ተናግረዋል።

በተያያዘ የዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች እና የሥራ ኃላፊዎች የተማሪዎቻቸውን ትክክለኛ መረጃ ካላቀረቡ ከኃላፊነታቸው የሚነሱ መሆኑ ተነግሯል።

በዚህም በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ስለ ተማሪያቸውና አጠቃላይ የትምህርት ስርዓት አፈጻጸም ትክክለኛ መረጃን ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ካላቀረቡ፤ የዩኒቨርስቲን ፕሬዚዳንቶች ጨምሮ አመራሮች ከኃላፊነታቸው እንደሚነሱ ተገልጿል።

በ2018 የትምህርት ዘመን ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተማሪያቸውን ትክክለኛ መረጃ የማቅረብ ግዴታ ተፈፃሚ እንደሚሆን የገለጹት ፕሮፌሰሩ፤ ይህም በቀጣይ 6 ወራት ይተገበራል ብለዋል፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መለኪያና የትምህርት ጥራትን ማስጠበቅ የሚያስችለው ስምምነት ከፍተኛ የትምህር ተቋማትን አቅጣጫ ለማስያዝ በማለም በባለፈው ዓመት የተጀመረ ስለመሆኑ አስታውሰዋል፡፡

ለሁለተኛ ጊዜ የተከናወነው ይህ የከፍተኛ ተቋማት እና የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ስምምነት ቀጣይነት እንደሚኖረውም አስታውቀዋል፡፡

የባለፈው በጀት ዓመት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሥራ አፈጻጸም ላይ ግምገማ መከናወኑን የገለጹም ሲሆን፤ ኃላፊነታቸውን በጥሩ የተወጡትን የማጠናከር እና በሥራቸው የደከሙትን በትኩረት እንዲሰሩ አቅጣጫ የሚሰጥበት እንደሆነም ተናግረዋል፡፡

ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ በሚያስችሉ የጋራ ሥራዎች ላይ መክረው የፊርማ ሥነ ስርዓት ካከናወኑት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መካካል የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተጠቃሽ ነው፡፡

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶክተር አስራት አጸደወይን መድረኩን አስመልክቶ ለአሐዱ እንደተናገሩት፤ ስምምነቱ ዩኒቨርሲቲዎች በተልኳቸው አተኩረው እንዲሰሩ አስቻይ በመሆኑ የተሻለ ውጤት ማምጣት ያስችላል፡፡

እንደ ፕሬዝዳንቱ ገለጻ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በስምምነቱ ላይ የተቀመጡት የመለኪ ነጥቦች በከፍተኛ ተቋማት አቅም መነሻነት በመሆኑ፤ ለቀጣይ በትምህርት ጥራት እና መሰል ጉዳዮች ላይ የተሻለ አፈጻጸም የሚያስገኝ ነው፡፡

የሀረማያ ዩኒቨርሲቱ ፕሬዝዳትን ዶክተር ጀማል የሱፍ በበኩላቸው፤ በትናንትናው ዕለት የተከናወነው ስምምነት በትምህርት ስርዓቱ ላይ በትምህርት ጥራት እና በምርምር ዘርፍ ላይ ከፍተኛ አውንታዊ ለውጥ የሚያስገኝ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡

በ2018 በጀት ዓመት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በኃላፊነት እና በሙሉ አቅም በመስራት በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተቀመጡ የመመዘኛ መስፈርቶችን ለመሟላት በጥረት ላይ እንደሚገኙ የገለጹት ደግሞ የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋና ሃጎስ ናቸው፡፡

በባለፈው በጀት ዓመት ጅማሮውን ያደረገው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥራቱን የጠበቀ የትምህርት ስርዓትን ለማስተግበር የሚረዱ 5 ቁልፍ ሥራዎች አፈጻጸምን አስመልክቶ፤ በዓመቱ መጨረሻ ላይ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማቱ የተሰሩ ሥራዎች ላይ ግምገማ የሚከናወንበት አሰራር ስለመኖሩ በመድረኩ ተጠቁመዋል፡፡

#አሐዱ

ኢራን የአለም የሰላም ስጋት በመሆኗ ኒኩሊየር አያስፈልጋትም ! /ትራምፕ /የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ የኢራንን የኒኩሊየር ማብላያ ጣቢያዎችን ላይ ድብደባ ባትፈፅም ...
10/11/2025

ኢራን የአለም የሰላም ስጋት በመሆኗ ኒኩሊየር አያስፈልጋትም ! /ትራምፕ /

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ የኢራንን የኒኩሊየር ማብላያ ጣቢያዎችን ላይ ድብደባ ባትፈፅም ኑሮ የመካከለኛው ምስራቅ የተጀመረው የእስራኤልና ሃማሰ ድርድር በፍፁም ሊሳካ የሚችል እንዳልነበር መናገራቸው ተሰማ ።

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለፎክስ ኒውስ በሰጡት ቃለ ምልልስ በዚህ አመት መጀመሪያ ላይ በኢራን የኒውክሌር መሥሪያ ቤቶች ላይ ስለደረሰው ጥቃት ሲናገሩ ኢራን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ለማምረት መቃረቧን እና ይህ ቢሆን ኖሮ የጋዛ የሰላም ስምምነት ሊሳካ አይችልም ነበር ብለዋል።

ፕሬዘዳንቱ በፎርድ፣ ናታንዝ እና ኢስፋሃን በሚገኙ የኢራን የኒውክሌር ፋሲሊቲዎች ላይ የአሜሪካ የቦምብ ጥቃት የቴህራንን የኒውክሌር መርሃ ግብር በእጅጉ ያዳከመ ትልቅ ስኬት ነው ከዚህ በኋላም ቴህራን በመካከለኛው ምስራቅ ፖለቲካ እጇን እንድትሰበስብ አድርጓል ብለዋል ።

ትራምፕ “ኢራን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ሊኖራት አንድ ወር ብቻ ቀርቷት ነበር፣ እና ያ እንዲሆን ብፈቅደው ኖሮ ይህ ስምምነት ሊሳካ አይችልም ነበር ወይም ከሆነ በላዩ ላይ ታላቅ ደመና ይኖረው ነበር ምክንያቱም ሃማስ የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ያላት ሀገር ከጎኑ በመሆኗ በጭራሽ ለሰላም ሸብረክ አይልም ነበር ብለዋል ።

አክለውም ለሰላም ስምምነቱ የተደረገው ጥረት ዓለምን አንድ ያደረገ እና ኢራን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ብታገኝ በሰላሙ እድገት ላይ ጥቁር ደመና ይፈጠር ነበር ኢራንን አቅም ማሳጣታችን ትክክለኛ ዉሳኔ ነበር ብለዋል። ሲል ያስነበቡት ታይምስ ኦፍ እስራኤል እና ዘ ሚዲሊስት ናቸው ።

የኔታ ቲዩብ ዘጋቢ ፦ ታዴ የማመይ ልጅ

ከ15th to 25th October 2025 G.C በኬኒያ በሚደረገው የዞን 3 የምስራቅ አፍሪካ የቦክስ ሻምፒዮና  ለመሳተፍ  የኢትዮጵያ ቦክስ ስፖርት ብሔራዊ ቡድን በዛሬው ዕለት ወደ ኬኒያ ...
10/11/2025

ከ15th to 25th October 2025 G.C በኬኒያ በሚደረገው የዞን 3 የምስራቅ አፍሪካ የቦክስ ሻምፒዮና ለመሳተፍ የኢትዮጵያ ቦክስ ስፖርት ብሔራዊ ቡድን በዛሬው ዕለት ወደ ኬኒያ አምርቷል።

ንብረትነቱ የአፍሪካ ቦክስ ኮንፌዴሬሽና የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝደንት የሆኑት በክቡር አቶ እያሱ ወሰን ድርጅቶች ኦሞቲክ ቢዝነስ ግሩፕና ፓራዳይዝ ሎጅ ከትጥቅ ጀምሮ ሙሉ የጉዞ የሽኝት ወጭ የተሸፈነ ሲሆን ወደ ኬኒያ ኢትዮጵያን በመወከል የተጓዘው የልኡካን ቡድኑ 2 ሴት 4 ወንድ በድምሩ 6 ቡጢኞች 2 አሰልጣኞች ሀገራችን ኢትዮጵያን ወክለዋል በኬኒያ ለሚካሄደው የዞን ሶስት የምስራቅ አፍሪካ የቦክስ ውድድር ቡድኑን በአሰልጣኝነት የሚመሩት የፌደራል ማረሚያ ቤቶች አሰልጣኝ ዘሪሁን ዳሞታ እና የአዲስ አበባ ፖሊሷ ዋና ሳጅን ፈለቀች ሰይፉ የተመረጡ ሲሆን በተጫዋችነት በወንዶች አቤል አባትዬ ከ አ.አ. ፖሊስ. ፍትዊ ጥዑማይ ከ ዩናይቴድ ስዊት ቦክስ አብርሀም አለም ከፌደራል ማረሚያ ኤርሚያስ መስፍን ከኦሜድላ እንዲሁም ከሴቶች ፈጣን ቢጆ ከድሬዳዋ ከተማ ሮማን አሰፋ ከ አዲስ አበባ ፖሊስ ተመርጠዋል::

በዛሬወ ዕለት ቅዳሜ ጠዋት በ1/02/2018ዓም ወደ አርባ ምንጭ ተጉዘው ልምምዳቸውን በውቢቷ በአርባ ምንጭ ከተማ በሚገኘው ፓራዳይዝ ሎጅ ማረፊያቸውን አድርገው በዛው ልምምዳቸውን ካደረጉ በኋላ ወደ ኬኒያ የሚያቀኑ ይሆናል::እናመሰግናለን ኦሞቲክ ቢዝነስ ግሩፕ ምንግዜም የቦክስ ስፖርት አጋር።!!

የኢትዮጵያ ቦክስ ፌድሬሽን

6ተኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር በይፋ ተከፈተ። “የሳይበር ደህንነት - የዲጂታል ኢትዮጵያ መሰረት” በሚል መሪ ቃል በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር   የተዘጋጀው 6ተኛው...
10/11/2025

6ተኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር በይፋ ተከፈተ።

“የሳይበር ደህንነት - የዲጂታል ኢትዮጵያ መሰረት” በሚል መሪ ቃል በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የተዘጋጀው 6ተኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር የሀገሪቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት እና የፌዴሬሽን ም/ቤት አባላት፣ የግል ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና መ/ቤት ተጀምሯል፡፡

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግራቸው የሳይበር ደህንነት ወር በአለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ6ተኛ ጊዜ በመከበር ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ የሳይበር ወር መከበር ዋና አላማ ሀገራት ለዜጎቻቸው እንዲሁም ለተቋማቶቻቸው የሳይበር ደህንነት ግንዛቤን ከፍ ለማድረግ የሚያስችሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ የንቅናቄ መርሃ ግብሮችን ለማከናወን እንደሆነም ዋና ዳይሬክተሯ ተናግረዋል፡፡

የዕለቱ የክብር እንግዳ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ክብርት አለምጸሃይ ጳውሎስ 6ተኛውን ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር በይፋ አስጀምረዋል፡፡ በመክፈቻ ንግግራቸውም አለም ወደ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በገባችበት በዚህ ጊዜ “ከሳይበር ደህንነት” ርእሰ ጉዳይ ውጪ ወቅታዊ እና ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ሌላ አብይ ጉዳይ ሊኖር አይችልም ብለዋል።

“የሳይበር ደህንነት - የዲጂታል ኢትዮጵያ መሰረት”

Address

4320 Cascade Falls Court
Royse City, TX
75189

Telephone

+12404687690

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Daily ኢትዮ ዴይሊ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share