ምድረ ቀደምት ግጥም በመሠንቆ/Meder Kadamt Poetry on Masinqo

ምድረ ቀደምት ግጥም በመሠንቆ/Meder Kadamt Poetry on Masinqo Welcome to Medere Kademt( the cradle of humanity, where we first walked on two legs. The origin of o

   #በጣናነሽክፍል 1ጊዜዉ 2004/5 ይመስለኛል የግንቦት ወር ሐሙስ ማለዳ ከተንጣለለዉ የጣና ሃይቅ ፊት ለፊት ከግዙፏ ጣናነሽ መርከብ ስር ተገኝቻለሁ አልፎ አልፎ በጣና ሃይቅ ና በሃዋሳ ...
06/22/2025

#በጣናነሽ
ክፍል 1
ጊዜዉ 2004/5 ይመስለኛል የግንቦት ወር ሐሙስ ማለዳ ከተንጣለለዉ የጣና ሃይቅ ፊት ለፊት ከግዙፏ ጣናነሽ መርከብ ስር ተገኝቻለሁ አልፎ አልፎ በጣና ሃይቅ ና በሃዋሳ ፍቅር ሃይቅ በባቡጋያ መሰል ሃይቆች ከማደርገዉ የጀልባ ሽርሽር ባለፈ ረጅም ርቀት የባህር ጉዞ አድርጌ ስለማላዉቅ የአዲስ ነገር የመሞከር ጉጉትና በባህር ዉስጥ ምን ሊፈጠር ይችላል የሚል ስጋት እንደ ሸበበኝ ከጧት እንቅልፍ ጋር እየታገልኩ የጣናንና የጨረቃን ጉርብትና እያደነኩ እያለ የመርከቧ የመጨረሻ የመንገደኞች ጥሪ ጡሩንባ ነፍታ ጣናነሽ ለጉዞ መንገደኞች ደግሞ ወደ መርከቧ ሆድ ለመግባት እንቅስቃሴ ተጀምሮ በተደበላለቀ ስሜት ወደ 3ኛ ደረጃ የመንገደኞ መቀመጫ(ቴራስ)ከጓደኞቸ ጋር ተሳፈርኩ::
ስለ የባህር ጉዞ ካነሳሁ አይቀር የባህርን ዉበትና የመርከበኛን ሕይዎትን በተመለከተ የማወቅ ጉጉት የፈጠረብኝ የተሰኘ መፅሐፍ ነዉ:: አንብባችሁት ይሆን?
በመርከብ ስለመጓዝ crazy ሃሳብ ያመጣዉ ማን እንደሆነ ባላስታዉስም ከጣና ዳር ከቀድሞዉ ጊዮን ሆቴል ጎን መርከቦች ድርጅት ቢሮ ከጉዞዉ ሁለት ቀን በፊት ተገኝተን ለጉዞ በ3ኛ ማዕረግ ደረጃ 137 ብር ከፍለን ትኬት እንደቆረጥን አስታዉሳለሁ:: ዕለተ ሐሙስ እስኪደርስ በጉጉት መጠበቃችን ከጉዞ እንዳንዘገይ በየሩማችን በየ ደቂቃዉ እንቅልፍ እንዳይጥለን እየተደዋወልን ቸክ ስንደራረግ ከቆየን በኋላ ልክ ከለሊቱ 11:00 ከሆቴላችን ዉጥተን በነፋሻማዉ ዓየር ታጅበን ወደ ተንጣለለዉ የጣና ሃይቅ ወደ የሐይቁ ሞገስ ጣናነሽ የደረስን።
👉🏼ሐሙስ ማለዳ በሰዓቱ የደረሰዉተሳፋሪዉ ሁሉ ወደ መረከቧ ሆድ ገብቶ ካበቃና ጣናነሽ የመጨረሻ ጡሩንባዋን ካሰማች በኋላ መልህቋን ሰብስባ ጉዞ ጎርጎራ
Tip ጎርጎራ ለመድረስ በርከት ያሉ ደሴቶችና የባህር ላይ የተለያዩ ትዕይንቶችን ያለፍን በመሆኑ የባህር ላይ የጉዞ ትወስታየን በሚቀጥለዉ ክፍል እተርካለሁ::

❤️❤️ምስጋና❤️❤️ /አዝማሪ/ 👉🏼በከባድ የጤና እና የኢኮኖሚ ችግር ዉሰጥ የምትገኘዉ የሙዚቃ ባለዉለታ አስረሱ ጎነበ ማናት??በ1968  በጎንደር ክፍለ ሀገር ታግሎ አታጋይ የሚል የመጀመሪያ...
02/02/2025

❤️❤️ምስጋና❤️❤️
/አዝማሪ/

👉🏼በከባድ የጤና እና የኢኮኖሚ ችግር ዉሰጥ የምትገኘዉ የሙዚቃ ባለዉለታ አስረሱ ጎነበ ማናት??

በ1968 በጎንደር ክፍለ ሀገር ታግሎ አታጋይ የሚል የመጀመሪያዉ የኪነ ጥበብ ቡድን በአብየ ይርጋ አማካኝነት ሲመሰረት የመጀመርያዋ መስራች አባልና ተመራጭ ድምፃዊ ነበረች::
ሀገራችን ኢትዮጵያ በሶማሊያ ስትወረር ካራማረ ድረስ ከሌሎች ባልደረቦቿ በመዝለቅ የወገንን ጦር በፉከራ እና በኪነ ጥበብ ስራዎቿ አነቃቅታለች አታግላለች በዚህም ከፕሬዘዳንት መንግስቱ ሃይለ ማርያም እጅ የክብር ሽልማት ወስዳለች
ታግሎ አታጋይ ከፈረሰ በኋላ የፋሲለደስ የባህል ቡድን ሲመሰረት ከመስራቾች ማሃል ግንባር ቀደም ናት በወቅቱ በኪነ ጥበብ ስራ ከፍተኛ ደሞዝ ተከፋዮች ማሃል ስሟ የሚጠቀስ አንጋፋ ድምፃዊ ናት
በ1982 ከአብየ ይርጋ ዱባለ አርቲስት ሃምሳል ምትኬ እና ከድምፃዊ ጌታቸዉ ዘዉዱ ጋር በጋራ በመሆን ካሴት አሳትማለች
በ1991 ሁለተኛ ስራዋን ተደራሽ ያረገች ሲሆን
በ1999 ድሬ ደዋ በጎርፍ በተጠቃበት ጊዜ 3ኛ ካሴት አሳትማ ገቢዉ ለድሬ ደዋ በግርፍ ለተጠቁ ወገኖቻችን ይዉል ዘንድ ሰጥታለች
ይህች ድምፀ መረዋ አርቲስት እንደሻማ ቀልጣ የባህል ሙዚቃ አብዮትን ያስተዋወቀች የተጠላ የተናቀዉን ዘርፍ እሷና ባልደረቦቿ በከፈሉት ዋጋ በዚህ ዘመን ከፍ ብሎ እንዲታይ ያስቻለ በመሆኑ ግጥም በመሰንቆ ዝግጅት በሕይዎት ዘመንሽ ላደረግሽልን አስተዋፅዖ በመረዋ ድምፅሽ ትላንትን ከነገ ጋር ያገናኘሽ ዛሬ መሆንሽ ከፍ ያለ ምስጋና እያቀረበ ሽልማት አበርክቷል

እሷን ማገዝ ለምትፈልጉ ደሞ Mitiku Muche ማነጋገር ትችላላቸሁ

ጉርሻና ቅምሻ የመፅሐፍት ምረቃ በወመዘክርበደራሲ ገጣሚ ማትያስ ከተማ የተፃፈዉ ጉርሻና ቅምሻ መፅሃፍ የሀገራችን ታላላቅ ደራሲዎችና የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች በተገኙበት ዕሁድ መስከረም 12 ከጠ...
09/20/2024

ጉርሻና ቅምሻ የመፅሐፍት ምረቃ በወመዘክር
በደራሲ ገጣሚ ማትያስ ከተማ የተፃፈዉ ጉርሻና ቅምሻ መፅሃፍ የሀገራችን ታላላቅ ደራሲዎችና የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች በተገኙበት ዕሁድ መስከረም 12 ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ ይመረቃል በመሆኑም በዕለቱና በሰአቱ በክብር ተገኝተዉ እንዲመርቁልን በአክብሮት ጋብዘነዎታል::

አድርሽኝ @ በመምህር  Weba    ጾመ ፍልሰታን በመላው ኢትዮጵያ ያለንና በውጭ ሀገር ያሉ በሚሊዮን የምንቆጠር ኦርቶዶክሳውያን በናፍቆት የምንጠብቃት የጾም ወቅት ናት፡፡ ከእመቤታችን ረድኤ...
07/31/2024

አድርሽኝ
@ በመምህር Weba
ጾመ ፍልሰታን በመላው ኢትዮጵያ ያለንና በውጭ ሀገር ያሉ በሚሊዮን የምንቆጠር ኦርቶዶክሳውያን በናፍቆት የምንጠብቃት የጾም ወቅት ናት፡፡ ከእመቤታችን ረድኤትን በረከትን የምንጎናጸፍባት ተናፋቂ እና ተወዳጅ የሱባኤ ወቅት፡፡ ለጎንደር ሕዝበ ክርስቲያን ደግሞ ጾመ ፍልሰታን ከሁሉም ኢትዮጵያውያውን በበለጠ በጉጉት እንዲጠብቋት የሚያደርግ አንድ ተጨማሪ ምክንያት አላቸው-የአድርሽኝ ጽዋ፡፡
በጎንደር ከገጠር እስከ ከተማ ያለው ሕዝበ ክርስቲያን በሥራ ምክንያት ማስቀደስ ያልቻለው ሁሉ ከእመቤታችን በረከት የሚሳተፍበት በየቀኑ የሚጠጣ ጽዋ-አድርሽኝ፡፡ መንፈሳዊና ማኅበራዊ ፋይዳው ግዙፍ የሆነ ትውፊት።
የትግራይ ተወላጅ የሆኑት ደጃዘረማች ደብለ ኢየሱስ የጻድቁ ዮሐንስ የልጅ ልጅ፣ የዐፄ ኢያሱ የእኅት ልጅ ከሆኑት አምላካዊት (ወለተ ሐዋርያት) ጋር ተጋብተው ዐፄ ዮስጦስን ወለዱ። ንጉሥ ዮስጦስ የዙፋን ዘመናቸው አጭር (፲፯፻፫–፲፯፻፰) ብትሆንም ያችውም ተቀናቃኝ አላጣትም፡፡ ታዲያ አንዴ በሐምሌ ክረምት ከተነሣባቸው ክፉ ጠላት (ሱዳኖች ናቸው የሚሉ አሉ፣ የሀገር ውስጥ ተቀናቃኝ ነው የሚሉም አሉ) ጋር ለሰልፍ ከመውጣታቸው በፊት ራሳቸው ወደተከሏትና በጣም ይወዷት ወደ ነበረችው ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን መጡ፡፡ በሚወዷት ሥዕለ ማርያም ፊት ቆመው፦ “የፍልሰታ ጾም መጣልኝ እያልኩ ቀን ስቆጥር ክፉ ጠላት ተነሥቶብኛል፡፡ ልጅሽ ወዳጅሽ በሰልፌ እንዲቆም፣ ኃይል እንዲሆነኝ በአንቺ ተማጽኛለሁ፡፡ ስዕለቴ ሠምሮ ተመልሼ ሱባኤሽን በደጅሽ እንዳሳልፍ ካደረስሽኝ በየዕለቱ ዝክርሽን እዘክራለሁ፡፡” ሲሉ ብፅዐት ገቡ፡፡ ሠምሮላቸው ጠላታቸውን ድል ነስተው ለጾመ ፍልሰታ በአጸዷ ተገኙ፡፡ በተሳሉት መሠረት እንደ ንጉሥ በግብረ አዳራሽ በመኳንንትና መሳፍንት ተከበው፣ በዙፋን ተሰይመው እያዘዙ «እገሌን አስተናግድ፣ ና እዚህ ቅዳለት፣ እዛ ጎድሏል ...» እያሉ ሳይሆን እንደ ማንኛውም ተረኛ ባለጽዋ ታጥቀውና አደግድገው አስተናገዱ፡፡ ለጾም እንደሚገባ ብቁልትና አሹቅ አዘጋጅተው፣ ጠላ እስጠምቀው፣ ከቅዳሴ መልስ ካህናቱንና ሕዝቡን “አድርሽኝ አልኳት አደረሰችኝ!” እያሉ እየመሰከሩ ዐሥራ አራቱንም ቀን በድንግል ማርያም ስም ዘከሩ፡፡ ይሕ የጾም ግብርም አድርሽኝ ተባለ፡፡ ሊቃውንቱም ሥርዐት ሆኖ እንዲጸና አደረጉት።
ይኸው ከዚያ ዘመን ጀምሮ በጎንደር ከገጠር እስከ ከተማ የፍልሰታ ሱባኤ ተጀምሮ እስኪጨረስ ምእመናን ሰርክ ላይ በአንድ ሰው ቤት ተሰብስበው ጸበል ጸዲቅ ይካፈላሉ፡፡ ጽዋው አድርሽኝ ይባላል፡፡ ጾም ነውና በተመጠነ ሁኔታ በቆሎና በጠላ ብቻ ይዘከራል፡፡ በየቤቱ እየተዞረ ሳይሆን በአንድ ሰው ቤት ነው አድርሽኙ የሚጠጣው። ባለቤቱ በሃይማኖት የበረታ፣ በምግባሩ ነቀፋ የሌለበት፣ በአስታራቂነት የተመሰገነ ሰው መሆን አለበት። ተረኛው ሰው ዝክሩን (ቆሎውን በወራንታ፣ ጠላውን በገንቦ) አዘጋጅቶ፣ ጮፌውን (ቄጤማውን) አጭዶ ይመጣል። ቄጤማው በላይ በላይ እየተነሰነሰ(እየተጎዘጎዘ) ሱባኤው እስኪያልቅ ይቆያል እንጂ በየቀኑ አይጠረግም።
ባለተራው ጋቢውን አደግድጎ፣ “የጌታየ እናቱ፣ እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ አድርሽኝ ብየሽ አድርሰሽኛልና አወድስሻለሁ፡፡ ስምሽን እየጠራሁ እዘክራለሁ፤” ብሎ እንግዶቹን ማስተናገድ ይጀምራል፡፡
የአድርሽኝ ማኅበር የሚጠጡ በተለይ መነኮሳትና በዕድሜ የገፉ እናቶች “ኦ! ማርያም!” በተሰኘ ጥዑም መንፈሳዊ ዜማ፣ በፍጹም ተመስጦና መንበርከክ ይዘምራሉ፡፡
ነፍሷን ይማረውና አያቴ እማሆይ ጥሩ ካሣን አልፎ አልፎ ለፍልሰታ ካገኘኋት በለስላሳ ዜማ ማታ ማታ እየጸለየች «ኦ ማርያም...» ስትል መቼም አይረሳኝም። ለሰስ ያለው ድምፅዋን እየሰማሁ፣ ቅኝቱን ጠብቃ ጣል የምታደርገውን የመቁጠሪያዋን ቅጭልጭልታ እያዳመጥሁ ሸለብ ያደረግሁበት ትዝታዬ የልጅነት ትውስታዬ አንድ ምዕራፍ ነው። መቁጠሪያው መላእክት የቃኙት የበገና ድምፅ ይመስለኝ ነበር።
ተንከባክባ ያሳደገችን የጎንደር መካነ ስብሐት ልደታ ለማርያም ውሉደ ኤስድሮስ ሰንበት ትምህርት ቤት ይህ ትውፊት እንዳይጠፋ በማሰብ አባላቱ ሁሌ ሰርክ ሰዓት ላይ አድርሽኝን በሰንበት ትምህርት ቤት ተገኝተው ይጠጣሉ፡፡ ውዳሴ ማርያም ተደግሞ፣ ከመዝሙረ ዳዊት የተውጣጡ ምዕራፋት ይነበባሉ፡፡ ኦ ማርያም የተሰኘው የእናቶች የቆየ ዝማሬም ከፍ ባለ መንፈሳዊ መመሰጥ ይዘመራል፡፡
እመኑኝ እዚህ ዝማሬ ውስጥ አንዴ ከተሳተፋችሁ በየዓመቱ ፍልሰታ ስትመጣ ነፍሳችሁ ማረፊያ ፍለጋ ወደ ዮስጦስ ደብር፣ ወደ ታላቁና አራት ዐይናው ሊቅ ወደ ኤስድሮስ ወንበር፣ ልደታ ለማርያም ትናፍቃለች።
☞ ርኅርኅተ ኅሊና ድንግል ሆይ የቀረን ተስፋ የልጅሽ ቸርነት ያንቺ ቃል ኪዳን ነውና ምልጃሽ ለዐሥራት ሀገርሽ ሰላምን ያድርግልን። ጸሎትሽ ጥላቻን አጥፍቶ ለሕዝቧ ፍቅርን ይስጥልን።

አዎ ነቢይ በሀገሩ ይከበራል።ልዩ የክብር ማስታወሻ ዝግጅት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር!!!!በቅርቡ በአጸደ ስጋ የተለየንን ሁለገብ ከያኒ ነቢይ መኮንን ለማክበር ልዩ ዝግጅት ተሰናድቷል። ሰኞ ...
07/29/2024

አዎ ነቢይ በሀገሩ ይከበራል።

ልዩ የክብር ማስታወሻ ዝግጅት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር!!!!

በቅርቡ በአጸደ ስጋ የተለየንን ሁለገብ ከያኒ ነቢይ መኮንን ለማክበር ልዩ ዝግጅት ተሰናድቷል።

ሰኞ ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓ.ም
ከ11:00 ሰአት ጀምሮ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል።

አዎን ነቢይ በሀገሩ ይከበራል!!!!

የነቢይ ወዳጆች ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ጋር በመተባበር

እንኳን ደስ አለን የተከፈለበት ማስታወቂያ ❗️አዲስ ነገር በአዲስ ዓመት ኤክስፖ ሱቆችን በዱቤ አቀረበታሜሶል ኮሙኒኬሽን ከአሴንቲክ ሶሉሽንስ ጋር በመተባበር የሚያዘጋጀው "አዲስ ነገር በአዲስ...
07/29/2024

እንኳን ደስ አለን የተከፈለበት ማስታወቂያ ❗️

አዲስ ነገር በአዲስ ዓመት ኤክስፖ ሱቆችን በዱቤ አቀረበ
ታሜሶል ኮሙኒኬሽን ከአሴንቲክ ሶሉሽንስ ጋር በመተባበር የሚያዘጋጀው "አዲስ ነገር በአዲስ ዓመት" ኤክስፖ 2017 በልዩ ሁኔታ ይከፈታል። በዚህ ኤክስፖ ላይ የለሚሳተፉ ተቋማት በኤግዚቢሽን ማዕከል ሱቆች በዱቤ የተዘጋጁላቸው ሲሆን ከዛሬ ጀምሮ የሱቆቹን ዋጋ 50 በመቶ በመክፈል ተመራጭ ቦታዎችን ይዘው 101 ፐርሰንት እንዲያተርፉ ታሜሶል ኮሙኒኬሽን ግብዣ አቅርቧል።

ለ20 ቀናተ በድምቀት በሚካሄደውና በልዩ ልዩ መንደሮች በተከፋፈለው በዚህ ኤክስፖ፣ፌስቲቫል፣ ባዛርና መዝናኛ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ሰው ይጎበዋል የተባለ ሲሆን በዚህ ትርፍ በሚገኝበትና ዓለምአቀፍ ደረጃውን በጠበቀ ኤክስፖ ምርትና አገልግሎታቸውን ማቅረብ ፈልገው ቅድሚያ ሙሉ ክፍያ መክፈል ላልቻሉ ተቋማት የቀረበ ልዩ እድል ነው ሱቅ በዱቤ ፕሮጀክት። ቀድመው የሚመጡ አስር ተቋማት የዚህ ልዩ ዕድል ተጠቃሚ ይሆናሉም ተብሏል።

Address

San Francisco, CA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ምድረ ቀደምት ግጥም በመሠንቆ/Meder Kadamt Poetry on Masinqo posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ምድረ ቀደምት ግጥም በመሠንቆ/Meder Kadamt Poetry on Masinqo:

Share