08/13/2023
የኢትዮጵያ መንግስት በፍኖተ ሰላም የሰው አልባ አውሮፕላን ጥቃት አደረሰ።
=====================================================
የኢትዮጵያ መንግስት በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን #ፍኖተ ሰላም መሀል ከተማ ላይ የድሮን ድብደባ ፈፀመ፡፡ በዚህ በኢትዮጵያ አየር ሃይል በተፈፀመው የሰው አልባ አውሮፕላን ጥቃት የበርካታ ንፁሃን ዜጎች ህይወት በአሳዛኝ ሁኔታ አልፏል። የፍኖተ ሰላም ከተማ አስተዳደር ከአዲስ አበባ 376 ኪ.ሜ ርቀት እንዲሁም ከክልሉ ርእሰ ከተማ ባህር ዳር 180 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የምትገኝ የምዕራብ ጎጃም ዞን መቀመጫ ናት፡፡
የአንድ ሐገር ሰራዊት ቀዳሚ ሚና ሀገርንና ህዝብን መከላከል ሲሆን መሰል ድርጊቶች በመንግስት እና በዜጎች መካከል አለመተማመንን መፍጠር ብቻ ሳይሆን የዜጎችን መብት ለማስጠበቅ የተነደፉትን አለም አቀፍ ህጎችንም ይጥሳል። በአማራ ክልል በተለያዩ ከተሞች በመንግስት እየተፈጸሙ ስላሉት የድሮን ጥቃቶች እና በንጹኃን ላይ ስለደረሰው ጉዳት ከክልሉም ሆነ ከፌደራል መንግስት አካላት የተሰጠ ማብራርያ እስካሁን የለም።
The Ethiopian government launched a attack in Selam.
================================================
The government carried out a drone strike on the city center of Fnote Salam in the West Gojam zone of the Amhara region. The attack, executed by the Ethiopian Air Force, has resulted in the tragic loss of many innocent lives. The primary role of a country's military is to protect the nation and its citizens. These recent drone attacks raise serious questions about the relationship between the Ethiopian government and its people and potential violations of international laws designed to safeguard civilian rights.
As of now, there has been no official explanation from either the state or the federal government regarding the drone attacks being carried out in various cities in the Amhara region. The lack of transparency and accountability adds to the growing concern over the harm done to innocent people.
OOHCHR AAmnesty International