10/30/2025
                                            ግብፅ ለኤርትራ ሉዓላዊነት መከበር ድጋፏን እንደምትሰጥ አረጋገጠች
*******
የግብጹ ፕረዝዳንት አብደል ፈታህ አል ሲሲ ሀገራቸው ኤርትራ ሉዓላዊነት እና ግዛታዊ አንድነት  መከበር ድጋፏን እንደምትሰጥ ከፕረዝዳንት ኢሳያስ ጋር ዛሬ በካይሮ ተገናኝተው በተወያዩበት ጊዜ አረጋግጠውላቸዋል።
“ግብፅ ከኤርትራ ጋር ባላት ስር የሰደደ ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ትኮራለች” ሲሉ ሲሲ በስብሰባው ወቅት ለኢሳያስ ነግሮዋቸዋል።
 
ፕረዝዳንት ኢሳያስ በበኩላቸው “ግብፅ በአፍሪካ ቀንድና በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና መረጋጋትን በማጠናከር እና የልማት ጥረቶችን ወደ ፊት ለማራመድ ለሚትጫወተው ሚና ጥልቅ አድናቆት እንዳለቸው ገልጸዋል።
የኤርትራው ፕሬዝዳንት የግብፅ ጉብኝት ሀገሪቱ ከኢትዮጵያ ጋር ከባህር በር ጥያቄ በተያያዘ ውጥረት ውስጥ በገባችበት ወቅት ነው።
ማለዳ ሚዲያ