Maleda Media

Maleda  Media IGNITING CIVIC ENGAGEMENT!

ግብፅ ለኤርትራ ሉዓላዊነት መከበር ድጋፏን እንደምትሰጥ አረጋገጠች*******የግብጹ ፕረዝዳንት አብደል ፈታህ አል ሲሲ ሀገራቸው ኤርትራ ሉዓላዊነት እና ግዛታዊ አንድነት  መከበር ድጋፏን እን...
10/30/2025

ግብፅ ለኤርትራ ሉዓላዊነት መከበር ድጋፏን እንደምትሰጥ አረጋገጠች
*******
የግብጹ ፕረዝዳንት አብደል ፈታህ አል ሲሲ ሀገራቸው ኤርትራ ሉዓላዊነት እና ግዛታዊ አንድነት መከበር ድጋፏን እንደምትሰጥ ከፕረዝዳንት ኢሳያስ ጋር ዛሬ በካይሮ ተገናኝተው በተወያዩበት ጊዜ አረጋግጠውላቸዋል።

“ግብፅ ከኤርትራ ጋር ባላት ስር የሰደደ ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ትኮራለች” ሲሉ ሲሲ በስብሰባው ወቅት ለኢሳያስ ነግሮዋቸዋል።

ፕረዝዳንት ኢሳያስ በበኩላቸው “ግብፅ በአፍሪካ ቀንድና በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና መረጋጋትን በማጠናከር እና የልማት ጥረቶችን ወደ ፊት ለማራመድ ለሚትጫወተው ሚና ጥልቅ አድናቆት እንዳለቸው ገልጸዋል።

የኤርትራው ፕሬዝዳንት የግብፅ ጉብኝት ሀገሪቱ ከኢትዮጵያ ጋር ከባህር በር ጥያቄ በተያያዘ ውጥረት ውስጥ በገባችበት ወቅት ነው።

ማለዳ ሚዲያ

ብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮቹን ለስልጠና ጠራ***የብልፅግና ፓርቲ በሀገሪቱ በሁሉም መዋቅር ላይ የሚሰሩ ከፍተኛ አመራሮችን ለስልጠና መጥራቱን ታውቀዋል።የፓርቲው ስልጠና ዛሬ በአዳማ ከተማ...
10/30/2025

ብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮቹን ለስልጠና ጠራ
***
የብልፅግና ፓርቲ በሀገሪቱ በሁሉም መዋቅር ላይ የሚሰሩ ከፍተኛ አመራሮችን ለስልጠና መጥራቱን ታውቀዋል።

የፓርቲው ስልጠና ዛሬ በአዳማ ከተማ የተጀመረ ሲሆን ስልጠናው ለሚቀጥሉት አስራ አምስት ቀናት እንደሚቆይ ተገልጿል።

ማለዳ ሚዲያ

ሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ በሀገራዊ ምርጫ ለመወዳደር  ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝ የፓርቲው ምክትል ፕረዝዳንት አቶ ደሳለኝ ደምሴ ተናገሩ****ሲዳማ ክልል ውስጥ ከሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች...
10/30/2025

ሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ በሀገራዊ ምርጫ ለመወዳደር ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝ የፓርቲው ምክትል ፕረዝዳንት አቶ ደሳለኝ ደምሴ ተናገሩ
****
ሲዳማ ክልል ውስጥ ከሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የክልሉ መንግሥት ዋነኛው ተቃዋሚ የሆነው ሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ በመጪው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚወዳደር አስታወቀ።

የፓርቲው ምክትል ፕረዝዳንትና የፖለቲካ ጉዳዮች ኋላፊ አቶ ደሳለኝ ደምሴ አስተያየታቸውን ለማለዳ ሚዲያ ሲሰጡ የክልሉ መንግሥት በፓርቲያቸው ውስጥ ሰርጎ ገብ አንጃ አደራጅቶ ከምርጫ ውድድር ሊያስቀራቸው ከፍተኛ ጥረት እንዳደረገ ተናግረል።

የክልሉ መንግሥት በህዝቡ ላይ የሚያደርሰውን በደል የሚያጋልጡ ሀቀኛ ፓርቲዎችን ለማፍረስ ቀንና ማታ ሰርቷል ያሉት ምክትል ፕረዝዳንቱ፤ የፓርቲያቸው ቢሮ ተሰብሮ ሙሉ ሰነዶችና ንብረት እንዲሰረቅ መደረጉን አንስተዋል።

“ሀሳብ ይፈራል” ባሉት የክልሉ መንግሥት ጫና ቢደርስባቸውም ጫናውን ተቋቁመው በመጪው ሀገራዊ ምርጫ ለመወዳደር “በእኛ በኩል ፍላጎት አለን” ብለዋል አቶ ደሳለኝ።

በደረሰባቸው “የደህንነት ስጋት” ከሀገር ውጭ የሚገኙት የፖርቲው ዋና ፕረዝዳንት ረዳት ፕ/ር ተሰማ ኤሊያስ የአቶ ደሳለኝን አስተያየት በሚያጠናክር መልኩ በማህበራዊ ሚዲያ ገጻቸው አማካኝነት ባጋሩት መልዕክት “ሲፌፓ ለምርጫ ይወዳደራል፤ ዝርዝር ጉዳዩ በፓርቲው ይቀርባል” ማለታቸው ይታወሳል።

ማለዳ ሚዲያ

ይህ  ከታች በፎቶ የምትመለከቱት የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት አባል የነበረ ዳዊት ፍሳ አሰፋ ይባላል። ወደ ትውልድ አካባቢዉ ሲዳማ ክልል አርቤጎና ወረዳ ያዬ ከተማ ከተመለሠ በኋላ አጎቱን ...
10/30/2025

ይህ ከታች በፎቶ የምትመለከቱት የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት አባል የነበረ ዳዊት ፍሳ አሰፋ ይባላል።

ወደ ትውልድ አካባቢዉ ሲዳማ ክልል አርቤጎና ወረዳ ያዬ ከተማ ከተመለሠ በኋላ አጎቱን አቶ አዳነ አሰፋ በዘግናኝ ሁኔታ ጨፍጭፎ ከገደለ በኋላ አምልጧል።

ስለዚህ ሰው መረጃ ያላቹ በአከባቢያችሁ ለሚገኙ የህግ አካለት እንድታሳውቁ ቤተሰብ ለወገን ጥሪውን ያስተላልፋል።

ማለዳ ሚዲያ

በአሜሪካዋ ፍሎሪዳ ሴት በመድፈር  ህይወቷ እንዲያልፍ ያደረገ  ግለሰብ የሞት ቅጣት ተፈፀመበት********ኖርማን ሚርል ግሪም ጁንየር  የተባለ የፍሎሪዳ ነዋሪ በእ.ኤ.አ ሐምሌ ወር 1998 ...
10/30/2025

በአሜሪካዋ ፍሎሪዳ ሴት በመድፈር ህይወቷ እንዲያልፍ ያደረገ ግለሰብ የሞት ቅጣት ተፈፀመበት
********
ኖርማን ሚርል ግሪም ጁንየር የተባለ የፍሎሪዳ ነዋሪ በእ.ኤ.አ ሐምሌ ወር 1998 ሲንቲያ ካምፕቤል የተባለችን ጎረቤቱን ከደፈረ በኃላ የግድያ ወንጀል በመፈፀሙ ከ20 ዓመታት በላይ የእስር ጊዜ በኃላ በትላንትናው እለት የሞት ፍርዱ ተፈፃሚ ተደርጎበታል::

በትላንትናው ዕለት ፍርዱ የተፈፀመው በተወጋው ሁለት መርዝ የያዘ መርፌ ታስሮ በቆየበት የፍሎሪዳው ማረሚያ ነበር::

በአሜሪካዋ ፍሎሪዳ ግዛት በዚህ ዓመት በተመሳሳይ ፍርድ የተፈፀመው 15ኛው የሞት ፍርድ እንደሆነም ተዘግቧል::

ማለዳ ሚዲያ

የመንገድ መሠረተ ልማት እጦት ለከፋ ችግር መዳረጋቸውን የጭሬ ወረዳ ነዋሪዎች ገለፁ******በወረዳው በመንገድ መሠረተ ልማች ችግር ቅሬታቸውን ለማለዳ ሚዲያ የተናገሩ የቦኮላና ላሌሳ አከባቢ ...
10/29/2025

የመንገድ መሠረተ ልማት እጦት ለከፋ ችግር መዳረጋቸውን የጭሬ ወረዳ ነዋሪዎች ገለፁ
******
በወረዳው በመንገድ መሠረተ ልማች ችግር ቅሬታቸውን ለማለዳ ሚዲያ የተናገሩ የቦኮላና ላሌሳ አከባቢ ነዋሪዎች ናቸው።

ነዋሪዎቹ በመንገድ እጦት ነፍሰጡር ወደ ሆስፒታል ማድረስ አለመቻሉን፣ ታማሚና ወላድ በቃሬዛ ከቦኮላ እስከ ጭሬ ከተማ ለመሸከም እንደሚገደዱ ተናግረዋል።

በመንገድ መሠረተ ልማት ችግር ጋር የቴሌ ኮሙኒኬሽን ኔትወርክ ማስፋፊያ አለመኖር ታክሎበት ማህበረሰቡን ለተደራራቢ እንግልትና ስቃይ መዳረጉን ነው ነዋሪዎቹ የሚናገሩት።

ነዋሪዎቹ የገጠማቸውን አንገብጋቢ የመንገድ ችግር በእራሳቸው ለመፍታት የአከባቢውን ነዋሪዎች እያስተባበሩ
የሚገኙ ሲሆኝ መንግሥት ለጭሬ ህዝብ ችግር ለመፍታት የማይንቀሳቀስ አሆነ ተቃውሟቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አሳስበዋል።

ማለዳ ሚዲያ

10/29/2025

ጃማይካ በሜሊሳ አውሎ ንፋስ ተመታች
********
አውሎ ነፋሱ ከአትላንቲክ አውሎ ነፋሶች አንዱ ሲሆን በደቡብ ምዕራብ ጃማይካ ውስጥ ባሉ ቤቶች፣ ሆስፒታሎች እና ትምህርት ቤቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ተዘግቧል።

እስከአሁን በሜሊሳ አውሎ ንፋስ የሰባት ሰዎች ሕይወት ማለፉን ሲኤን ኤን የዘገበ ሲሆን ኩባና ሐይቲም የአውሎ ንፋሱ ተጠቂ ሀገራት እንደሚሆኑ ተነግሯል።

ማለዳ ሚዲያ

10/29/2025

ሐዋሳ

ጉዱማሌ ፓርክ (አሞራ ገደል)

“እንደ ከአሁን በፊቱ አስመራ የመሄድ  ፍላጎት አለኝ” - ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ.ር)************ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በዛሬው የፓርላማ ውሎ ለኤርትራ መ...
10/28/2025

“እንደ ከአሁን በፊቱ አስመራ የመሄድ ፍላጎት አለኝ” - ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ.ር)
************

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በዛሬው የፓርላማ ውሎ ለኤርትራ መንግስት ባስተላለፉት መልእክት ከዚህ ቀደም ተሰምተው የማያውቁ በርካታ ጉዳዮችን አንስተዋል።

“ለኤርትራ መንግስት ያለኝ መልእክት ቢኖር ወደ ጎረቤት ሃገር ጥይት ማስተላለፍ ተገቢ ስላልሆነ ጥይት አስተላላፊ አትሁኑ” በማለት የጀመሩት ዶ/ር አብይ ኤርትራን “ሀገር ሁኑ” ብሏል፡፡

“አባይ ጸባይ ገዝቷል፡፡ የእኛም ሽፍቶች ጸባይ ይገዛሉ፡፡ ስለማናዉቅ አይደለም፤ እናያችኋለን፡፡ ጥይት ማቀባበል ይቅርባችሁ” በማለት የኤርትራ መንግሥት ወደ ኢትዮጵያ ህገ ወጥ ጦር መሳሪያ እያስተላለፈ እንደሚገኝ ፍንጭ ሰተዋል።

“ህገ ወጥ የሰዎች ዝውዉር ይቅር፡፡ የሚመጣ ሰዉ ካለ በህጋዊ መንገድ ይምጣ፡፡ ህገ ወጥ ንግድ ቢቀር ፤ ፎርጅድ ብር ቢቀር ፤ አሜሪካ ቁጭ ብሎ ጥቁር ገበያ ማሳደግ ቢቀር ፤ እንደ ጎረቤት ሃገር እንተሳሰብ” ሲሉ

ከጦር መሳሪያ ዝውውር በተጨማሪ ሀገሪቱ በህገ ወጥ የሰው ንግድ፣ በህገ ወጥ ንግድ፣ ሀሰተኛ የብር ኖቶችን አሳትሞ በማሰራጨት፣ በጥቁር ገበያ ንግድ ነው ሀገሪቱን የከሰሱት።

“በንግድ፤ በተፈናቃይና በሌላዉም ህጋዊነትን እንከተል” ሲሉ ጥሪ ያቀረቡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ “እንደጎረቤት ሃገር በሰላም አብረን ለማደግና በፍቅር አብረን ለመቀጠል ኢትዮጵያ ፍላጎት አላት ብለዋል።”

እኔ እንደ ከአሁን በፊቱ አስመራ የመሄድ ፍላጎት አለኝ፡፡ ነገር ግን የምሄድበት ምክንያት ትርፍ ሊኖረዉ ይገባል፡፡ ትርፍ ከሌለዉ ግን ጊዜ ማባከን ነዉ፡፡ ባሌ የምመላለስበትን ጊዜ በከንቱ አስመራ በመመላለስ ማባከን አልፈልግም፡፡ ጊዜ የለኝም፡፡” - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

ማለዳ ሚዲያ

ኬንያ ውስጥ ቱሪስቶችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ አውሮፕላን ተከሰከሰ ***ኬንያ ውስጥ ቱሪስቶችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ አውሮፕላን የባሕር ዳርቻ ግዛት በሆነችው ክዋሌ ውስጥ ወድቆ መከስከሱን የ...
10/28/2025

ኬንያ ውስጥ ቱሪስቶችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ አውሮፕላን ተከሰከሰ
***

ኬንያ ውስጥ ቱሪስቶችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ አውሮፕላን የባሕር ዳርቻ ግዛት በሆነችው ክዋሌ ውስጥ ወድቆ መከስከሱን የአገሪቱ አቭዬሽን ባለሥልጣን አስታወቀ

በአደጋው በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩ 11 አውሮፓውያን እና ኬንያዊ አብራሪ ሕይወታቸው ማለፉን የአውሮፕላኑ ባለቤት የሆነው ኩባንያ አስታውቋል።

ሞምባሳ ኤር ሳፋሪ የተባለው ድርጅት እንዳለው በአውሮፕላኑ ውስጥ ስምንት ሃንጋሪያውያን፣ሁለት ጀርመናውያን እና አንድ ኬንያዊ የነበሩ ሲሆን በአደጋው የሁሉም ሕይወት ማለፉን ቢቢሲ ዘግቧል።

የኬንያ ሲቪል አቪየሽን ባለሥልጣን እንዳለው ቱሪስቶቹን ያሳፈረው አውሮፕላን አደጋው የደረሰበት በጎብኚዎች ከምትዘወተረው የባሕር ዳርቻ መዝናኛዋ ዲያኒ በማለዳ ተነስተው ወደ ፓርኩ ሲያመሩ ንጋት 11 ሰዓት ተኩል አካባቢ ነው።

የአገሪቱ ሲቪል አቪየሽን ባለሥልጣን የአደጋ ጊዜ አገልግሎት ሠራተኞች በአደጋው ስፍራ ደርሰው ያጋጠመውን ጉዳት እና የአደጋውን ምክንያት እየመረመሩ እንደሆነ ተጠቅሷል።

ማለዳ ሚዲያ

በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የኦክስጅን ማምረቻ ፋብሪካ ግንባታ እየተፋጠነ እንደሆነ  ተዘገበ። የኦክስጅን ማምረቻ ፋብርካው ከዚህ በፊት በኦክስጅን እጦት ለአላስፈላጊ ወጪና...
10/28/2025

በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የኦክስጅን ማምረቻ ፋብሪካ ግንባታ እየተፋጠነ እንደሆነ ተዘገበ።

የኦክስጅን ማምረቻ ፋብርካው ከዚህ በፊት በኦክስጅን እጦት ለአላስፈላጊ ወጪና እንግልት ሲዳረጉ የነበሩ ህሙማንን ችግር እንደሚያቃልል ተስፋ ተጥሎበታል

ማለዳ ሚዲያ

ኢትዮጵያ በቀጥታ ወደ ቀይ ባሕር የሚያመራ አዲስ የባቡር መስመር ለመገንባት ማቀዷ ተዘገበ  ****የኢትዮጵያ የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን (ኢምባኮ) ሰሜን ኢትዮጵያን ከታጁራ፣ ከአሰብ እና ከምፅ...
10/28/2025

ኢትዮጵያ በቀጥታ ወደ ቀይ ባሕር የሚያመራ አዲስ የባቡር መስመር ለመገንባት ማቀዷ ተዘገበ
****
የኢትዮጵያ የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን (ኢምባኮ) ሰሜን ኢትዮጵያን ከታጁራ፣ ከአሰብ እና ከምፅዋ የቀይ ባሕር ወደቦች ጋር ለማገናኘት የሚያስችል ደረጃውን የጠበቀ የባቡር መስመር የመገንባት እቅድ ይፋ አድርጓል ሲል ስፑትኒክ ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል።

ዕቅዱ 1.58 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ወጪ ይጠይቃል ተብሏል፡፡

የዜና ምንጩ እንዳስነበበው 216 ኪሎ ሜትር ርዝመት ይኖረዋል ተቢሎ የሚጠበቀው የወልድያ-ሐራ ገበያ-መቐለ ነጠላ የባቡር መስመር፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የባሕር በር ለማግኘት እያደረገ ያለውን ጥረት የሚያስፈጸም ነው ብሎታል።

"የባቡሩ መስመሩ ኢትዮጵያን ከታጁራ፣ አሰብ እና ምፅዋ ወደቦች ጋር ያገናኛል" ሲል ያጠቃልል ሲል ሚዲያው አገኘው ያለውን ምንጭ ጠቅሶ አስነብቧል።

እቅዱ ማክሰኞ ጥቅምት 11 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል በተካሄደው፣ ብሔራዊ የባቡር ንግድና ኢንቨስትመንት ጉባኤ ላይ በቀረበው የ21 ገጽ የኩባንያው ሪፖርት ላይ መዘርዘሩንም አክሏል።

ማለዳ ሚዲያ

Address

Seattle, WA
98134

Telephone

(206) 460-2119

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Maleda Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share