Maleda Media

Maleda  Media IGNITING CIVIC ENGAGEMENT!

የሐዋሳ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ለማጠናቀቅ በሚል በሎተሪ በተሰበሰበው ገንዘብ ዙሪያ  ማብራሪያ ተሰቷል። ህብረተሰቡ ጉዳዪ በገለልተኛ አካል ኦዲት ተደርጎ ለህዝብ ይፋ እንዲሆን እየጠየቀ ይገኛል...
12/15/2025

የሐዋሳ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ለማጠናቀቅ በሚል በሎተሪ በተሰበሰበው ገንዘብ ዙሪያ ማብራሪያ ተሰቷል። ህብረተሰቡ ጉዳዪ በገለልተኛ አካል ኦዲት ተደርጎ ለህዝብ ይፋ እንዲሆን እየጠየቀ ይገኛል
*****
የሀዋሳ ከተማ ልማት ፈንድ ምክር ቤት ኮሚቴዎች የብሔራዊ ሎቴሪ አስተዳዳር ተወካዮች፣ የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ እና የከተማ አመራሮች በተገኙበት መድረክ ማብራሪያ ሰጥተዋል ።

በመድረኩ ዘርዘር ያሉ መረጃዎች የቀረቡ ቢሆንም የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ሕዝብ ግንኙት መረጃዎች መድረክ ላይ በቀረቡት ልክ ለህዝብ ከመስጠት ተቆጥቧል።

የማለዳ ሚዲያ ከውስጥ የመረጃ ምንጮቹ ባገኘው መረጃ መሠረት አጠቃላይ የታተሙ ትኬቶች 500,000 (አምስት መቶ ሺህ) መሆናቸውን፣ የተሸጡ ትኬቶች 140,000+ (መቶ አርባ ሺህ) ገደማ እንደሆነና ከዚህም 30,000,000 (ሰላሳ ሚሊየን ብር) የተሰበሰበ መሆኑን ተረድቷል።

ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳዳር "የተወሰኑ ቀሪ ትኬቶች እኛ ጋ አሉ" ያለ ሲሆን ከሎተሪ ገንዘብ መጭበርበር ጋር ስሙ ጎልቶ ሲነሳ የቆየው የምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ዘሪሁን ቃሚሶ ቀሪ የሎተሪ ትኬቶች መበላሸታቸውን ነው የገለፁት።

ተሸጠ ከተባለዉ 30,000,000 ብር ውስጥ 4,000,000 (አራት ሚሊዮን ብር) የብሔራዊ ሎተሪ ድርሻ መከፈሉን፣ 5,000,000 በሲዳማ ቡና እግር ኳስ ከለብ በኩል የተሸጠ ገንዘብ እነሱ ጋ እንደሚኖር ምክር ቤቱ ተስፋ እንደሚያደርግ፣ 19,000,000 (አሥራ ዘጠኝ ሚሊዮን ብር) በምክር ቤቱ ዝግ አካውንት ውስጥ እንደሚገኝ እና ቀሪ ገንዘብ 2,000,000 (ሁለት ሚሊዮን ብር) ለተለያዩ አስተዳዳሪያዊ ወጪዎች እንደወጣ በማብራሪያው ተመልክቷል።

ምክር ቤቱ ምንም እንኳን በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ ቢሰጥም ጠቅላላ ሂደቱ በገለልተኛ ኦዲት ተረጋግጦ በገንዘቡ ልማት ለመደገፍ የቶምቦላ ሎተሪ ለገዛው ለሰፊው ማህበረብ የተሰጠ ሕጋዊ መግለጫ የለም።

አስተይስየታቸውን ለማለዳ ሚዲያ የላኩ የህብረተሰቡ ክፍሎች ጉዳዩ በገለልተኛ አካል ኦዲት ተደርጎ ለህዝብ ይፋ እንዲሆን ጠይቀዋል።

ማለዳ ሚዲያ

ሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ (ሲፌፓ) የዘንድሮው 7ኛ ሀገራዊ ምርጫ እንደሚወዳደር  በይፋ አሳወቀ።*****የሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ (ሲፌፓ) በይፋዊ ማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገጹ እንዳሰፈረው የፓር...
12/15/2025

ሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ (ሲፌፓ) የዘንድሮው 7ኛ ሀገራዊ ምርጫ እንደሚወዳደር በይፋ አሳወቀ።
*****
የሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ (ሲፌፓ) በይፋዊ ማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገጹ እንዳሰፈረው የፓርቲዉ ስራ አስፈፃሚ 7ኛ ሀገራዊ ምርጫ ተሳትፎን በተመለከተ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ከፓርቲው ቁጥጥር ኮሚሽን ጋር በጋራ ገምግሞ ውሳኔ እንዳስተላለፈው ገልጿል።

ፓርቲው ከፍተኛ አካል ያላቸዉ የፓርቲዉ አመራር ጋር በጋራ በመሆን ፓርቲው በ7ኛ ሀገራዊ ምርጫ በሚሳተፍበት ሁኔታ እና በፓርቲው አሁናዊ ቁመና ላይ ጥልቅ ግምገማ ያካሄደ መሆኑን በመግለጽ፤ በምርጫው ለመወዳደር ዝግጁ እንደሆነና በክልሉ ባሉት አስራ ዘጠኙም የምርጫ ክልሎች የሚወዳደሩ እጩዎችን መልምሎ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እንደሚያቀርብ አቅጣጫ ተቀምጧል ብሏል።

በግምገማ ወቅት ፓርቲው ከምርጫ ቦርድና ከመንግስት አካላት እየደረሰበት ስላለው ተግዳሮትና እና ወደፊት ሊደርስበት ስለሚችሉ መሰናክሎች በጥልቀት ከተወያየ በኋላ ችግሩን በውይይትና በንግግር ለመፍታት እንደሚሞክር አቅጣጫ አስቀምጧል ተብሏል።

አክሎም በዋናነት የምርጫ ቦርድ ከዚህ በፊት የተሰጠው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውሳኔ ባለመፈፀምና በተለያዩ ጊዜ ፓርቲው በደብዳቤ የጠየቀውን ጥያቄዎችን በጊዜ ምላሽ ባለመስጠት ለዝግጅት መሰናክል እየሆነበት መሆኑን አንስቶ በሰፊው መወያየታቸውን በመግለጽ፤ ጉዳዩን ተከታትሎ የደረሰበት ደረጃ ለህዝብና ለአባላቱ ይፋ እንደሚደረግ አፅኖት ሰጥቷል።

በመጨረሻም ፓርቲው በሀገራዊ ምርጫ ተሳትፎ ዙሪያ የደረሰበት ደረጃና ሁኔታ ለመላው ሲዳማ ህዝብና ለአባላቶቹ ይፋ እንደሚያደርግ አቅጣጫ በማስቀመጥ ስብሰባውን አጠናቋል ስል በማህበራዊ ሚዲያ ይፋዊ ገጽ አስነብቧል።

ማለዳ ሚዲያ

የአሜሪካ  መንግስት ለኢትዮጵያውያን የሰጠውን ጊዚያዊ ከለላ ( Temporary Protected Status)  ማንሳቱን ዛሬ አስታወቀ ******የአሜሪካ የሃገር ውስጥ ደህንንት መስሪያ ቤት ዛ...
12/12/2025

የአሜሪካ መንግስት ለኢትዮጵያውያን የሰጠውን ጊዚያዊ ከለላ ( Temporary Protected Status) ማንሳቱን ዛሬ አስታወቀ
******
የአሜሪካ የሃገር ውስጥ ደህንንት መስሪያ ቤት ዛሬ ባወጣው መግለጫ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ሁኔታዎች ስለተሻሻሉ እና አሜሪካ የሚኖሩ የሃገሪቱ ዜጎች ቢመለሱ የከፋ የደህንነት ስጋት እንደማይገጥማቸው በመገምገም ጊዚያዊ ከለላቸውን ማንሳቱን ገልጿል።

በዚህ ፕሮግራም ተጠቃሚ የነበሩ ኢትዮጵያውያን በሁለት ወር ውስጥ እራሳቸውን ዲፖርት እንዲያደርጉ ተጠይቀዋል። ይህን ካደረጉ የአሜሪካ መንግስት የ አውሮፕላን ትኬት እና አንድ ሺ ዶላር ቦነስ እንደሚሰጥ አስታውቋል።

ይህ መግለጫ የሚመለከታቹ ኢትዮጵያውያን ምንም አይነት ውሳኔ ከመወሰናቹ በፊት የህግ ባለሙያዎችን ታማክሩ ዘንድ እናበረታታለን።

ማለዳ ሚዲያ

Today, Secretary of Homeland Security Kristi Noem announced her decision to terminate the Temporary Protected Status designation of Ethiopia.

በዩኒክ ስታር ኮሌጅ እህት ኩባንያ  በሲዳማ ክልል  ዳዬ ባንሳ እየተገነባ ያለ  ሎጅ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት  ባለመጀመሩ  ቅር  መሰኘታቸውን የአከባቢው ነዋሪዎች ገለፁ ።******በቦኖራ...
12/12/2025

በዩኒክ ስታር ኮሌጅ እህት ኩባንያ በሲዳማ ክልል ዳዬ ባንሳ እየተገነባ ያለ ሎጅ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ባለመጀመሩ ቅር መሰኘታቸውን የአከባቢው ነዋሪዎች ገለፁ ።
******
በቦኖራ ወንዝ የአቦሬ ፏፏቴ አጠገብ እየተገነባ የነበረ ሎጅ ተጠናቆ ለጎብኚዎች አገልግሎት መስጠት ሳይጀምር ከአሥርት ዓመታት በላይ በማስቆጠሩ በአከባቢው ማህበረሰብ ቅሬታ አስነስቷል።

ቅሬታቸውን ለማለዳ ሚዲያ ያሰሙ አንዳንድ የዳዬ ከተማ ነዋሪዎች የአከባቢው ማህበረሰብ የወል ሃብት የሆኑትን ፏፏቴና የዉሃ ሃብት አጥሮ ሳያለሙ ለዓመታት ማቆየት ተገቢ እንዳልሆነ ይናገራሉ።

ጉዳዩ የሚመለከተው የመንግሥት አካላም ፕሮጀክተቶቹ ለምን በተያዘላቸው ጊዜ እንዳልተጠናቀቁ ለህዝቡ መረጃ የመስጠት ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ቦኖራን የመሰለ ፏፏተቴ ለጎብኚዎች አገልግሎት እንዳይሰጥ በግለሰቦች ይዞታ ስም ታጥሮና ተቆልፎ መቀመጡ ለማህበረሰቡ ኪሣራ መሆኑን ያነሱት አስተተያየት ሰጪዎቹ ፕሮጀክቱ ቶሎ ተጠናቀው ለጎብኚዎች ክፍት እንዲሆንና የአከባቢው ማህበረሰብም ተጠቃሚ እንዲሆን ከመንግሥት ድጋፍና ብርቱ ክትትል እንደሚያስፈልግ ተጠቁሟል።

ማለዳ ሚዲያ

‎”ዲሽታ ጊና “- የኣሪ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ ባህል እየተከበረ ነው። ****የኣሪ ብሔረሰብ የሀገር ሽማግለዎች ከዞኑ አስተዳደር ጋር በመመካከር የዘንድሮ በዓል በማርበርግ ቫይረስ ምክንያ...
12/12/2025

‎”ዲሽታ ጊና “- የኣሪ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ ባህል እየተከበረ ነው።
****
የኣሪ ብሔረሰብ የሀገር ሽማግለዎች ከዞኑ አስተዳደር ጋር በመመካከር የዘንድሮ በዓል በማርበርግ ቫይረስ ምክንያት በአደባባይ እንደማይከበር ውሳኔ አስተላልፈዋል።

በኣሪ ብሔረሰቡ ዘንድ የአብሮነት ፣ የዕርቅና የሠላም፣ የመረዳዳትና የአዲስ ዘመን ብስራት ወቅት ተደርጎ የሚወሰደው የዲሽታ ጊና በዓል በየዓመቱ በታህሳስ ወር መግቢያ በታላቅ ድምቀት ይከበራል።

የብሔረሰቡ ተወላጆች በያሉበት ቦታ ሆነው በዓሉን እንዲያከብሩ የሚገኙ ሲሆን በሐዋሳና አከባቢው የሚገኙ የኣሪ ብሔረሰብ ተወላጆች በሱሙዳ አደባባይ ሰብሰብ አክብረውታል።

ማለዳ ሚዲያ

በአዲስ አበባ ቦሌ የሚገኘው 'ኬና ሆቴል' ባለቤት አቶ ታደሰ ኢዴማ  በቁጥጥር ስር  ዉለው  ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን የማለዳ ምንጮች ጠቆሙ።በተመሳሳይ  የሀዋሳ ሴራሚክስ ፉብሪካ፥ ዱቄ...
12/11/2025

በአዲስ አበባ ቦሌ የሚገኘው 'ኬና ሆቴል' ባለቤት አቶ ታደሰ ኢዴማ በቁጥጥር ስር ዉለው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን የማለዳ ምንጮች ጠቆሙ።

በተመሳሳይ የሀዋሳ ሴራሚክስ ፉብሪካ፥ ዱቄት ፍብሪካ፥ እንዲሁም በአዲስ አበባ ግዙፍ የቡና ማበጠሪያ እና ሌሎች ፉብሪካዎች ከፍተኛ ባለ ድርሻ የሆኑት አቶ ተሽቴም መታሰራቸውን የደረሱን መረጃዎች ያመለክታሉ።

ሁለቱም ባለ ሃብቶች ከዶላር ጥቁር ገበያ እና ህገ- ወጥ የገንዘብ ዝውውር ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው የታሰሩ መሆኑን የገለፁልን ምንጮቻችን ባለ ሃብቶቹ ቁልፍ ከሆኑ የመንግስት ባለ ስልጣናት ጋር በቅርበት ይሰሩ እንደነበር ይታወቃል።

ማለዳ ሚዲያ

በሲዳማ ክልል አሮሬሳ ወረዳ የማጆ ሆስፒታል የጤና ባለሙያዎች ሥራ አቆሙየጤና ባለሙያዎቹ ሥራ ለማቆም የተገደዱት የትርፍ ጊዜ ክፍያ ባለመከፈሉና ደሞዛቸው በአዲሱ የዴሞዝ ስኬል መሠረት ባለመሠ...
12/11/2025

በሲዳማ ክልል አሮሬሳ ወረዳ የማጆ ሆስፒታል የጤና ባለሙያዎች ሥራ አቆሙ

የጤና ባለሙያዎቹ ሥራ ለማቆም የተገደዱት የትርፍ ጊዜ ክፍያ ባለመከፈሉና ደሞዛቸው በአዲሱ የዴሞዝ ስኬል መሠረት ባለመሠራቱ እንደሆነ ለማለዳ ሚዲያ ተናግረዋል።

ባለሙያዎቹ ቅሬታቸውን አስቀድመው ጉዳዩ ለሚለመከታቸው አካላት በጽሑፍ ያሳወቁ ቢሆንም አጥጋቢ ምላሽ ባለማግኘታቸው ሥራ ለማቆም መገደዳቸውን ነው የሚገልፁት።

በክልሉ ከአዲሱ ደሞዝ ክፍያ ጋር ተያይዞ ዛሬም ያልተፈቱ ችግሮች በተለያዩ ወረዳዎች የሚስተዋሉ ሲሆን የመብት ጥያቄ የሚያነሱ መምህራንን፣ የጤና ባለሙያዎችንና ሌሎች የመንግሥት ሠራተኞችን መንግሥት እያሠረ እንደሚገኝ የማለዳ ምንጮች ከሥፍራው አረጋግጠዋል።

Afaan Oromoo |  ዘንድሮ በአዲስ አበባ (ፊንፊኔ) በሚሰጡ የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል የሚኒስትሪ ፈተናዎች አፋን ኦሮሞ እንደሚካተት፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አስታወ...
12/10/2025

Afaan Oromoo | ዘንድሮ በአዲስ አበባ (ፊንፊኔ) በሚሰጡ የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል የሚኒስትሪ ፈተናዎች አፋን ኦሮሞ እንደሚካተት፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው በደብዳቤው መመሪያው በመንግሥት፣ በግልና በዓለም አቀፍ (International) አስፈታኝ ትምህርት ቤቶች ተፈጻሚ እንዲሆንና ትምህርት ቤቶቹም ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል፡፡

ለ8ኛ ክፍል አማርኛና አፋን ኦሮሞ እንደ አንደኛ ቋንቋ እንደሚሰጡ በደብዳቤው መመልከቱን ሪፖርተርስ ዘግቧል።

ማለዳ ሚዲያ

በአዲስ አበባ ከተማ ከመሬትና መሬት አስተዳደር ጋር ተያይዞ ሙስናና ሌብነት መንሰራፋቱ ተጠቆመ።******የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ በብልሹ አሰራር ውስጥ ተዘፍቀው በተገኙ አመራሮችና ባለ...
12/10/2025

በአዲስ አበባ ከተማ ከመሬትና መሬት አስተዳደር ጋር ተያይዞ ሙስናና ሌብነት መንሰራፋቱ ተጠቆመ።
******
የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ በብልሹ አሰራር ውስጥ ተዘፍቀው በተገኙ አመራሮችና ባለሙያዎች ላይ እርምጃ እየወሰድኩ ነው ብሏል። ህብረተሰቡም በ7079 ነፃ የስልክ መሥመር ተጨባጭ ጥቆማ ይስጠኝ ብሎአል።

ቢሮው የሰነዳቸው መረጃዎች እንደሚያመላክቱት በ2017/18 በጀት ዓመት በብልሹ አሰራር ውስጥ ተዘፍቀው የተገኙ 138 አመራርና ሠራተኞችን በመለየት 66ቱን ከስራ ማሰናበትን ጨምሮ በከባድ የዲሲፕሊን ቅጣት የተቀሩት ደግሞ በቀላል የዲስፕሊን ቅጣት እንዲቀጡ ማድሰጉን አስታውቋል።

ቢሮው ምንም እንኳን እርምጃ እየወሰድኩ ነው ቢልም ችግሩ ከቁጥጥር ውጭ እንደሆነ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ይናገራሉ። “ሙስና ካልሰጠህ፣ ካልተጠቃቀምክ ሕግና ሥርዓት ሰለተከተልክ የሚያልቅልህ ጉዳይ የለም። ኢንቨስትመንትና ትላልቅ ፕሮጀክት ላይ ለመሳተተፍ ከደላላ እስከ ቢሮ ኃላፊዎች ቀድመው በፐርሰንት ይቀባበሉሃል። በትንሹ መታወቂያ ለማውጣትና ያገባ/ያላገባ የድጋፍ ደብዳቤ ብትፈልግ ከ15 -20 ሺህ ብር ጉቦ መክፈል የተለመደ አሠራር እየሆነ መጥቷል “ ይላሉ።

ብዙዎች በአዲስ አበባ በዘመድ አዝማድ ትሥሥር ወይም በጉቦ ካልሆነ የመንግሥት አገልግሎት ማግኘት አዳጋች እየሆነ መምጣቱ ላይ ይስማማሉ።

ማለዳ ሚዲያ

የወላይታ  የዘመን መለወጫ በዓል "ጊፋታ" በዓለም ቅርስነት ተመዘገበ****የወላይታ የዘመን መለወጫ በዓል "ጊፋታ" በዓለም ቅርስነት መመዝገቡን ተገልጿል።ጊፋታ በአለም ቅርስነት የተመዘገበው ...
12/10/2025

የወላይታ የዘመን መለወጫ በዓል "ጊፋታ" በዓለም ቅርስነት ተመዘገበ
****
የወላይታ የዘመን መለወጫ በዓል "ጊፋታ" በዓለም ቅርስነት መመዝገቡን ተገልጿል።

ጊፋታ በአለም ቅርስነት የተመዘገበው ህንድ በተካሄደው 20ኛው የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባሕል ድርጅት (ዩኔስኮ) የማይዳሰሱ የባሕል ቅርሶች ጥበቃ ኮሚቴ ጉባኤ ላይ ነው።

ኢትዮጵያ በዓለም ቅርስነት እንዲመዘገብ ያቀረበችው የወላይታ የዘመን መለወጫ በዓል "ጊፋታ" በሰው ልጅ የማይዳሰሱ የባሕል ቅርሶች ዝርዝር ስር ተመዝግቧል።

ማለዳ ሚዲያ

ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ሳውድ አረቢያ አቀኑ***የኤረትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ እና ሉዑካቸው ሳውድ አረቢያ ማቅናታቸውን ታውቋል።ፕሬዝዳንቱ እና ልዑካቸው ዛሬ ጠዋት ረፋድ ላይ በ...
12/09/2025

ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ሳውድ አረቢያ አቀኑ
***
የኤረትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ እና ሉዑካቸው ሳውድ አረቢያ ማቅናታቸውን ታውቋል።

ፕሬዝዳንቱ እና ልዑካቸው ዛሬ ጠዋት ረፋድ ላይ በሪያድ አየር ማረፊያ ስደረሱ ደመቅ ያለ አቀባበል እንደተደረገላቸው ተነግሯል።

ፕሬዝዳንቱ በሳውዲ ቆይታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር መሐመድ ቢን ሳልማን ጨምሮ
ከሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ተገናኝተው እንደሚሞክሩ ተዘግቧል።

ማለዳ ሚዲያ

ሱዳን ከኢትዮጵያ በሚያዋስናት የምስራቁ ድንበር በኩል አዲስ ወታደራዊ ግንባር ለመክፈት እንደተዘጋጀች ተነገረ*****ሱዳን ከኢትዮጵያ በምስራቅ በኩል በሚያዋስናት ድንበር አቅራቢያ አዲስ ወታደ...
12/09/2025

ሱዳን ከኢትዮጵያ በሚያዋስናት የምስራቁ ድንበር በኩል አዲስ ወታደራዊ ግንባር ለመክፈት እንደተዘጋጀች ተነገረ
*****
ሱዳን ከኢትዮጵያ በምስራቅ በኩል በሚያዋስናት ድንበር አቅራቢያ አዲስ ወታደራዊ ግንባር ለመክፈት በዝግጅት ላይ እንደሆነች የሱዳን ኦፊሴላዊ ምንጮች ገለጹ።

አዲሱ ውሳኔ የመጣው ኢትዮጵያ ታጣቂ ኃይሉን (RSF) እና የነሱ ደጋፊ የሆኑ ቅጥረኞች በሁለቱ ድንበር አቅራቢያ ስልጠና ወስደው ብሉ ናይል ክልልን እንዲያጠቁ ፈቅዳለች በሚል እንደሆነ አልጀዚራ ያናገራቸው የሱዳን መንግሥታዊ ምንጮች አረጋግጠዋል።

የሱዳን መንግስት ምንጮች እንደገለጹት የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ከሌሎች ቀጠናዊ ኃይሎች ጋር በመተባበር ከፈጥኖ ደራሽ ሠራዊቱ ጋር ወታደራዊ ቅንጅት መፍጠራቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት ሁለቱን አገራት በሰሜን ምስራቅ በሚያዋስነው በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዋና ከተማ በሆነችው አሶሳ ከተማ በኩል ለፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች የጦር ተሽከርካሪዎች፣ መድፍ እና የጠለፋ መሳሪያ ስርዓቶች እንዲቀርብ ማድረጓን ሱዳኖች እንደሚያውቁ የዜና ምንጩ አክሏል።

እንደ ተንታኞች ገለጻ ኢትዮጵያ በሱዳን ጦርነት ጣልቃ መግባቷ እና አሁን ሱዳን እከፍቷለው ያለችው የጦር ግንባር የህዳሴ ግድብ መገኛ ቀጠና በመሆኑ ከግብጾች ቀጠናዊ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ጋር ተዳምሮ ለኢትዮጵያ ስጋት ሊሆን ይችላል ተብሏል።

ማለዳ ሚዲያ

Address

Seattle, WA
98134

Telephone

(206) 460-2119

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Maleda Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share