Maleda Media

Maleda  Media IGNITING CIVIC ENGAGEMENT!

የደቡባዊ ሲዳማ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ እራሱን ማጥፋቱ ተነገረ ****የደቡባዊ ሲዳማ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉነህ ተክሉ እራሱን ማጥፋቱ ተነገሯል።የማለዳ ምንጮች ከስፍራው...
24/07/2025

የደቡባዊ ሲዳማ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ እራሱን ማጥፋቱ ተነገረ
****
የደቡባዊ ሲዳማ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉነህ ተክሉ እራሱን ማጥፋቱ ተነገሯል።

የማለዳ ምንጮች ከስፍራው እንደነገሩን የጽ/ቤቱ ኃላፊ በዞን ደረጃ ከተካሄደው ግምገማ መድረክ በኃላ ራሱን አጥፍቶ መገኘቱ ታውቋል።

አቶ ሙሉነህ ተክሉ የደቡባዊ ሲዳማ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ ከመሆናቸው በፊት የአለታ ጩኮ ከተማ ከንቲባ እንደነበር የማለዳ ምንጮች ገልጸዋል።

ማለዳ ሚዲያ

ከሲያትል አንዲት ሴት ገድሎ ኬንያ ገብቶ የነበረ ወጣት በ ኤፍ ቢ አይ  (FBI) ተያዘ **********************በአሜሪካ ሲያትል አቅራቢያ በሚገኝ ከተማ ( Tukwila) ከአጋሩ ...
24/07/2025

ከሲያትል አንዲት ሴት ገድሎ ኬንያ ገብቶ የነበረ ወጣት በ ኤፍ ቢ አይ (FBI) ተያዘ
**********************
በአሜሪካ ሲያትል አቅራቢያ በሚገኝ ከተማ ( Tukwila) ከአጋሩ ጋር በመሆን አንዲት የ67 አመት ሴት በጥይት ገድሎ በመሸሽ ኬንያ ተደብቆ የነበረ የ 20 አመት ወጣት በ ኤፍ ቢ አይ ክትትል ተያዘ።

ይህ ሳልማን ሃጂ የተባለ ወጣት ኤልይስ አብዲ ከተባለ አጋሩ ጋር በመሆን የሟችን እህት ቦርሳ ለመቀማት ሲሞክር ትግል ስለገጠመው ገድሏት ቀደም ብለው ከሌላ ሴት በቀሙት መኪና መሸሻቸውን የፖሊስ ሪፖርት ያመለክታል።

ከግድያው አራት ቀናት በኻላ ወደ ኬንያ ሽሽቶ መደበቅ ቢችልም ከወራት ከትትል በኻላ ተይዞ ወደ ሲያትል ተመልሶ ክስ ተመስርቶበታል።

ከዚህ ቀደምም ኬቨን የተባለ የኬንያ ዜጋ የሴት ጓደኛውን ገድሎ ኬንያ ናይሮቢ ቢገባም በተመሳሳይ የኤፍ ቢ አይ ኤጀንቶች ተይዞ ለአሜሪካ ተላልፎ መሰጠቱ ይታወሳል።

ማለዳ ሚዲያ

የማሌዢያው ጠቅላይ ሚኒስትር አንዋር ኢብራሂም የሀገሪቱን የኑሮ ውድነቱን ለማቃለል ለዜጎች ገንዘብ ለማከፋፈል ወሰኑ****የማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንዋር ኢብራሂም የኑሮ ውድነቱን ለማቃለል ...
23/07/2025

የማሌዢያው ጠቅላይ ሚኒስትር አንዋር ኢብራሂም የሀገሪቱን የኑሮ ውድነቱን ለማቃለል ለዜጎች ገንዘብ ለማከፋፈል ወሰኑ
****
የማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንዋር ኢብራሂም የኑሮ ውድነቱን ለማቃለል ለሁሉም አዋቂ ዜጎች 100 ርንጊት (24 ዶላር) ወይም 3232 ብር ከኦገስት 1 ጀምሮ ለመስጠት መወሰናቸውን አሳውቁ።

መንግስት በድጎማ የሚያስገባውን የፔትሮል ዋጋ እንዲሁ ከ2.05 ሪንጊት በሊትር ወደ 1.99 ሪንጊት እንደሚቀንስ እና በ10 የክፍያ አውራ ጎዳናዎች ላይ የታቀዱ የዋጋ ጭማሪዎችን እንደሚያቆም ጠቅላይ ሚኒስትር አንዋር ተናግረዋል።

በተጨማሪም በዚህ አመት የሚደረጉ ህዝባዊ በዓላትን በማጠፍ ወጪ ለመቀነስ ከውሳኔ እንደደረሱም አክለዋል።

ፕረዝዳንቱ ከዚህ ውሳኔ የደረሱት በኑሮ ውድነቱ እና በምርጫ ጊዜ የገቧቸውን ቃል ባለመፈጸማቸው የተቆጡ ተቃዋሚዎች ከስልጣናቸው እንዲወርዱ የሚጠይቅ ሰልፍ መጥራታቸውን ተከትሎ መሆኑን ከአልጀዚራ ያገኘነው ዘገባ ያመለክታል።

ማለዳ ሚዲያ

የሐዋሳ ዩኒቨርስቲ ስር የሚገኙ ሁለት ካምፖሶች የህልውና ስጋት ጥላ ተጋርጦባቸዋል ተባለ።****የሐዋሳ ዩኒቨርስቲ የዳዬ ካምፖስ እና አዋዳ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅን ለማጠፍ ዩንቨርስቲው ተ...
23/07/2025

የሐዋሳ ዩኒቨርስቲ ስር የሚገኙ ሁለት ካምፖሶች የህልውና ስጋት ጥላ ተጋርጦባቸዋል ተባለ።
****
የሐዋሳ ዩኒቨርስቲ የዳዬ ካምፖስ እና አዋዳ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅን ለማጠፍ ዩንቨርስቲው ተጠባባቂ ፕረዚዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ በከፍተኛ ቁርጠኝነት እየሰራ እንደሚገኝ የኮሌጆቹ ታማኝ ምንጮች ለማለዳ ሚዲያ አረጋግጠዋል።

የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ዳዬ ካምፓስ የተማሪ ቁጥር ያነሰባቸው የትምህርት ክፍሎችን በአንድ ላይ በማዋሃድ አሊያም በማጠፍ ቅነሳ ለማድረግ የሚያስችል ዕቅድ ነድፎ ቀትግበራ ላይ መሆኑን ተነግሯል።

ከዚህ በተጨማሪ በተለይም የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ዳዬ ካምፓስ ወደ ሀዋሳ ከተማ የማዛወር ፍላጎት የፕሬዝዳንቱ ሌላኛው እቅድና ተልዕኮ እንደሆነም ተጠቅሷል።

የዩንቨርስቲው ፕረዝዳንት የዳዬ ካምፓስ እራሱን የቻለ ዩንቨርሲቲ እንዲሆን ጥረት የሚደረግበት ወቅት ይህንን ሃሳብ ይዞ መነሳታቸው በአከባቢው ነዋሪ በኩል ከፍተኛ ስጋት እና ጥርጣሬ እየፈጠረ ይገኛል ተብሏል።

በሌላ በኩል ዩንቨርስቲው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዩኒቨርስቲው በሥራ ኃላፊዎች ምደባ ዙሪያ ስልታዊ የብሔር መድሎ እየተበራከተ መምጣቱን የምናገሩት ሌላ ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁ አስተያየት ሰጪ በተቋሙ የትምህርት ሚኒስቴሩ የሚያራምዱት አክራር ብሔር ጠል ፖሊሲ ትግበራ የአከባቢውን ተወላጆች የማስወገድ ተግባር ላይ መጠመዳቸውንም ተናግሯል።

የዳዬ ካምፓስ ተመሳሳይ እጣ ፈንታ ለይርጋዓለም አዋዳ ቢዝነስ ካምፓስም እንደተጋረጠበት የነገሩን አስተያየት ሰጪያችን እየተፈጠረ ያለው ችግር ዩኒቨርስቲው ለአካባቢው ማህበረሰብ የሚሰጠውን ችግር ፈቺ የምርምር ሥራዎች እና የማህበረሰብ አገልግሎት ግዴታ እንዳይወጣ እንቅፋት ይሆናል ሲሉ ስጋታቸውን አጋርተውናል።

ከኮሎጆቹ ጋር የተቆራኘ ኑሮ ለመሠረቱ በሺዎቹ የሚቆጠሩ የየአካባቢው ሠራተኞችም የስራ አጥነትን ጨምሮ የተለያዩ ማህበረሰብ ተኮር ቀውስ ስለሚያስከትል ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ትኩረት አካላት የተቋሙ መሪዎች አደገኛ አካሄድ በቅርበት እንዲከታተሉ ጥር ቀርቧል።

ማለዳ ሚዲያ

 | ፍትህ የተዛባበት ማንኛውም ሰው ፍትህ የሚያገኝበት የእውነተኛ የፍትህ አደባባይ ነው አቦ ዎንሾ። አቦ ዎንሾ በዎንሾ ወረዳ ከይርጋለም በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኝ የባህላዊ ዳኝነት ስፍራ ነ...
23/07/2025

| ፍትህ የተዛባበት ማንኛውም ሰው ፍትህ የሚያገኝበት የእውነተኛ የፍትህ አደባባይ ነው አቦ ዎንሾ። አቦ ዎንሾ በዎንሾ ወረዳ ከይርጋለም በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኝ የባህላዊ ዳኝነት ስፍራ ነው።

ሥፍራው ከአሥራ ስድስት ትውልድ በፊት ከሲዳማ ጎሳዎች አንዱ በሆነውና በሆሎና ጋርብቾ አባት በአቦ የተመሠረተ የባህላዊ የዳኝነት ቦታ ነው። በሲዳማ በሁሉም የሲዳማ ንዑስ ጎሳዎች ደረጃ ልክ እንደ አቦ የየራሳቸው የባህላዊ ዳኝነት የሶንጎ ስፍራዎች አሉአቸው።

የአቦ ባህላዊ የዳኝነት ሥፍራ ልዩ ስም ተብሎ ይታወቃል። በአቦ ጋጣ (ባህላዊ የዳኝነት ሥፍራ) የማይዳኝ ነገር የለም። ሰው ከሲዳማ ብቻ ሳይሆን ከመላው የሀገሪቷ ክፍል ፍትህ ተነፍጎ፣ ሃቁ እንዲወጣለት፣ እውነተኛ ፍትህ ፍለጋ ወደ አቦ ይመጣል። በአቦ ጋጣ ፍትህ ፍለጋ የመጣ ማንኛውም ሰው ያለዘር፣ ሃይማኖትና ቀለም ልዩነት ይዳኛል። ነጩም ፍትህ ፈልጎ ከመጣ ይዳኛል።

በመደበኛ ፍርድ ቤቶች የፍትህ አሰጣጥ ሥርዓት እውነተኛ ፍትህ በጠበቆች ጥንካሬ፣ በጉቦ፣ በዘመድ አዝማድ እገዛ፣ በባለስልጣናት ጫና ወዘተ ሊዛባ ይችላል። በመደበኛው ፍርድ ቤት ክደህ ልትረታ ትችል ይሆናል። በአቦ የባህላዊ ዳኝነት ሥፍራ ግን ፍትህ የምታገኘው በማመን ብቻ ነው። የፍትህ ሥርዓቱን በሚመሩ ሽማግሌዎች ፊት ሀላሌን (እውነትን) ብቻ መናገር ይጠበቅብሃል። እውነትን ከካድክ መዘዙ ክፉ ነው። ሕይወትህን ሁሉ የሚያሳጣ ነገር ሊገጥምህ ይችላል። በአቦ ባህላዊ የዳኝነት ሥፍራ ከሳሽና ተከሻሽ በእውነት (ሀላሌ) ብቻ አሸናፊ የሚሆንበ አደባባይ ነው። ፍትህ ከሰፈነልህ የፍንጥር ትንሽ ገንዘብ ወደህና ፈቅደህ እንደ አቅምህ ብትሰጥ እንጂ በዚህ ሥፍራ በጉቦ ፍትህ አይሸጥም። እሱም ከለሌህ አትገደድም። ፍትህ በነፃ ብቻ ነው የሚሰጠው።

በዚህ የባህላዊ ዳኝነት ሥፍራ አራት ሽማግሌዎች የፍትህ አሰጣጥ ሥርዓቱን ይመራሉ፦ ጋና፣ ጋዳላ፣ ቃሪቻና ዎማ ተብለው ይታወቃሉ። አነኝህ የአቦ ባህላዊ ዳኝነት ሥርዓት መሪዎች ወደ ገበያ በፍፁም የማይሄዱ ናቸው። በቄያቸው የግብርና ሥራቸውን ከመሥራትና ከማሠራት በስተቀር ሌላ ቦታ አይሄዱም። ውሎአቸው በአቦ ጋጣ በመገኘት የፍትህ ጉዳዮችን ማየት ነው። በትውልድ ቅብብሎሽ አሁን ያሉቱ መሪዎች አሥራ ስድስተኛው ትውልድ የአቦ ባህላዊ የዳኝነት ሥፍራ መሪዎች ናቸው።

የአቦ ባህላዊ የዳኝነት ሥፍራ ሌላኛው ግርማ ሞገስ የተፈጥሮ ደን ነው። 96 ሄክታር መሬት የሚሸፍነው ደን በተፈጥሮ የበቀለ ነው። በአቦ ጋጣ እድሜ ጠገብ ረጃጅም ሀገር በቀል ዛፎችን ብቻ መመልከት የተለመደ ነው። በዚህ ሥፍራ አይደለም ዛፍ የዛፍ ቅርንጫፍ መቁረጥ በፍፁም የተከለከለ ነው። በአቦ ባህላዊ የዳኝነት ሥፍራ ፍትህ ከተፈጥሮ ጥበቃና እንክብካቤ ጋር ተዋህዳ ለአከባቢው ልዩ ክብር አሰጥታለች።

ማለዳ ሚዲያ

ፕሬዜዳንት ሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደ  በደቡባዊ ዞንእያደረገ ባለው ሹምሽር ተከትሎ በአከባቢው ውጥረት መንገሱን ተነገረ ****በትግራይ ክልል ደቡባዊ ዞን የጊዚያዊ አስተዳደሩ ትእዛዝ በሰጠው አ...
22/07/2025

ፕሬዜዳንት ሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደ በደቡባዊ ዞን
እያደረገ ባለው ሹምሽር ተከትሎ በአከባቢው ውጥረት መንገሱን ተነገረ
****
በትግራይ ክልል ደቡባዊ ዞን የጊዚያዊ አስተዳደሩ ትእዛዝ በሰጠው አድማ በታኝ ፓሊስ የተደገፈ የስልጣን ሹምሽር እየተካሄደ መሆኑ ተነግሯል።

ከትናንት ሀምሌ 14/2017 ዓ.ም ጀምሮ ከመቐለ ወደ ማይጨው ከተማ በተላከ የአድማ ብተና ፓሊስ ጥብቅ ቁጥጥር ስር የስልጣን ሹምሽር እየተካሄደ ያለው።

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ሌ/ጄ ታደሰ ወረደ የስልጠን ሹም ሽሩ “ሰላማዊ ነው” ቢሉም የቀድሞ ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ጨምሮ በርካቶች ድርጊቱ “በሀይል የሚደረግ ግጭት ቀሰቃሽ የስልጣን ንጥቂያ” ብለውታል።

የዞኑ አስተዳደር አቶ ጌታቸው ረዳ በወርሃ መጋቢት 2017 ዓ.ም ከትግራይ ከወጡበት ጀምሮ የአመራር ለውጥ ያልተደረገበት አከባቢ ሆኖ ቆይቷል።

የዞኑ አስተዳደር አመራሮች ባለፉት ወራት ህወሓት እንደማይወክላቸው የሚገልፅ ሰፋፊ ህዝባዊ ሰልፎች ማካሄዳቸውን ተነግሯል።

በሌላ በኩል የጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደ ከዞኑ የአመራር ቦታ የሚነሱ ሀላፊዎች በክልል የሃላፊነት ቦታ እንደተዘጋጀላችው በሰጡት መግለጫ አስታውቋል።

የስልጣን ሽምሹሩ እንዲተገበር የሚያሳልጥ ፓሊስ ወደ አከባቢው መላኩንም ጠቅሷል።

ፕሬዝዳንቱ አክለውም በዞኑ የለውጥ አመራር ለማድረግ ያስፈለገበት ምክንያት ቀጣይ አደጋዎች ለማስቀረትና የክልሉ የፀጥታ ችግር ለመፍታት ያለመ ነው ብለውታል።

መንግስት በዞኑ በግድ ማድረግ ያለበት ነው እያደረገ ያለው ስለሆነም ሂደቱ ማደናቀፍ የማይቻል እንደሆነ ተናግሯል።

በትግራይ ደብባዊ ዞን እየተከናወነ ያለውን ጉዳይ “በዞኑ ህዝብ ላይ የተጫነ አስገዳጅ የስልጣን ንጥቂያ ነው” በማለት ብርቱ ትችት አዘል ፅሁፍ ካጋሩት በርካቶች አንዱ አቶ ጌታቸው ረዳ በማህበራዊ ገፁ ላይ ባሰፈሩት ሀሳብ ገልጿል።

አቶ ጌታቸው “ኃላቀር ቡድን” ሲሉ የገለፁት የህወሓት አመራር በክልሉ ደቡብና ደብባዊ ዞኖች ወታደራዊ ዘመቻ በማካሄድ ሌላ ቀውስ እንዲፈጠር እየሰራ ነው " ሲሉ ከሰዋል።

ማለዳ ማዲያ

የኢትዮጵያ መንግሥት በታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤቱ በኩል ለሰሞንኛው የዶናልድ ትራምፕ ንግግሮች ምላሽ ሰጠ*****የአሜሪካው ፕረዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ታላቁ የኢትዮጵያ ህ...
22/07/2025

የኢትዮጵያ መንግሥት በታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤቱ በኩል ለሰሞንኛው የዶናልድ ትራምፕ ንግግሮች ምላሽ ሰጠ
*****
የአሜሪካው ፕረዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በአሜሪካ መንግሥት ገንዘብ ተገንብቷል በማለት በተደጋጋሚ ላሰማቸው ንግግሮች ቀጥታ ምላሽ መስጠት ያልፈለገው የኢትዮጵያ መንግሥት በግድቡ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በኩል ምላሽ ሰቷል።

በጠቅላይ ሚኒስትሩ አሊያም በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል ለፕረዝዳንቱ “ግድቡ በአሜሪካ ድጋፍ ተገነባ” የሚለውን ሀሰተኛ መረጃ ያልተከላከለው የኢትዮጵያ መንግሥት ግድቡ የተገነባበትን የገንዘብ ምንጭ በማስተባበሪያው በኩል ለፕረዝዳንቱ ንግግር ምላሽ ለመስጠት ተገዷል።

ጽህፈት ቤቱ በመግለጫው ግድቡ በሁሉም ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ትብብር መገንባቱን ገልጾ፣ እስካሁን በሀገር ውስጥ ከቦንድ ሽያጭና በስጦታ 20 ንጥብ 1 ቢሊዮን ብር፣ ከዲያስፖራው ማህበረሰብ 1 ነጥብ 6 ቢሊዮን፣ ከልዩ ልዩ ገቢዎች 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር፤ በአጠቃላይ ላላፉት 14 ዓመታት ከ23 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን አሳውቋል።

ማለዳ ሚዲያ

ሀዋሳ ለቅዱስ ገብርኤል ንግስ በዓል እየተዘጋጀች ነው‎የቅዱስ ገብርኤል ንግስ በዓል በሀዋሳ ከተማ ‎በዓመት ሁለት ጊዜ የሚከበር ሲሆን ዘንድሮም ለሁለተኛ ጊዜ ሐምሌ 19 ለማክበር ከተማዋ ዝግ...
22/07/2025

ሀዋሳ ለቅዱስ ገብርኤል ንግስ በዓል እየተዘጋጀች ነው

የቅዱስ ገብርኤል ንግስ በዓል በሀዋሳ ከተማ ‎በዓመት ሁለት ጊዜ የሚከበር ሲሆን ዘንድሮም ለሁለተኛ ጊዜ ሐምሌ 19 ለማክበር ከተማዋ ዝግጅት ላይ መሆኑዋን ተገልጿል።

የንግስ በዓልም በሰላም ተከብሮ እንድጠናቀቅ የከተማ አስተዳደሩ እንዲሁም የሲዳማ ክልል ፓሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝ አሳውቋል።

በኢትዮጵያ በቱሪዝም መዳረሻነት የምትታወቀው ሀዋሳ ከተማ የህዝብና ሀይማኖታዊ በዓላትን በደማቅ ሁኔታ የማስተናገድ የቆየ ባህል ያላት ከተማ መሆኗም ተመልክቷል።

ማለዳ ሚዲያ

ፍርድ ቤት አለልኝ አዘነ በባለቤቱና በባለቤቱ እህት ባል መገደሉን አረጋግጦ የፍርድ ውሳኔ አሳለፈ።****የኢትይጵያ ብሔራዊ ቡድን እና ባህርዳር ከተማ እግር ኳስ ክለብ ተጫዋች የነበረው አለል...
22/07/2025

ፍርድ ቤት አለልኝ አዘነ በባለቤቱና በባለቤቱ እህት ባል መገደሉን አረጋግጦ የፍርድ ውሳኔ አሳለፈ።
****
የኢትይጵያ ብሔራዊ ቡድን እና ባህርዳር ከተማ እግር ኳስ ክለብ ተጫዋች የነበረው አለልኝ አዘነ ግድያ ሲመረምር የቆየው የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ገዳዮቹ የገዛ ባለቤቱና የባለቤቱ እህት ባል መሆናቸውን በማረጋገጥ የፍርድ ውሳኔ አሳልፏል።

በዚህ መሠረት ፍርድ ቤቱ የአለልኝ ባለቤት አደይ ጌታቸዉና በእህቷ ባል ሉንጎ ሉቃስ ላይ የ16 እና 15 ዓመት ፅኑ እስራት ፈርዶባቸዋል።

ጋብቻውን በፈጸመ በ15ኛ ቀኑ “ራሱን አጠፋ” ተብሎ የነበረው አለልኝ አዘነ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከፍተኛ ክፍያ ከሚያገኙ ወጣት እግር ኳስ ተጫዋቾች መካከል የሚጠቀስ ነበር።

ማለዳ ሚዲያ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኣሪ ዞን ደቡብ ኣሪ ወረዳ በኮመር ቀበሌ በናዳ የአምስት ሰዎች ህይወት አለፈ።በቀበሌው በቀን 13/11/2017 ዓ.ም በዕለተ እሁድ 10:00 አከባቢ በጣለው ከባድ ዝና...
21/07/2025

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኣሪ ዞን ደቡብ ኣሪ ወረዳ በኮመር ቀበሌ በናዳ የአምስት ሰዎች ህይወት አለፈ።

በቀበሌው በቀን 13/11/2017 ዓ.ም በዕለተ እሁድ 10:00 አከባቢ በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት በተነሳ ናዳ ምክንያት የአምስት ሰዎች ህይወት ሊያልፍ ችሏል።

በናዳው የአንድ ቤተሰብ አባላት ሙሉ ህይወት ያለፈ ሲሆን ሟች አቶ ተረቱ ካይቲ 2 ወንድ ልጆች ፣ 1 ሴት ልጅ እና ከልጆች እናት ጋር ወንድ 3፣ ሴት 2 በአጠቃላይ የ5 ሰዎች ህይወት አልፏል።

በተጨማሪም በናዳው ምክንያት ከ 200 ሰዎች በላይ ከአከባቢያቸው ተፈናቅለዋል።

እስከአሁን ድረስ የአንድ ሰው አስከሬን እንኳን ልገኝ አለመቻሉ አደጋው እጅግ የከፋ መሆኑን የወረዳው መንግሥት ኮሙኒኬሽን የዘገበው።

ማለዳ ሚዲያ

የምርመራ  ዘገባ (ጥቆማ) ማለዳ ሚዲያ ******በፕረዝደንቱ  ወንድም  እና ሌሎች ባለ ስልጣናት መሪነት የተነጠቀው የቀይ መስቀል ማህበር ቤትና ሰፊ መሬት **********ነገሩ እንዲህ ነው...
21/07/2025

የምርመራ ዘገባ (ጥቆማ)
ማለዳ ሚዲያ
******
በፕረዝደንቱ ወንድም እና ሌሎች ባለ ስልጣናት መሪነት የተነጠቀው የቀይ መስቀል ማህበር ቤትና ሰፊ መሬት
**********
ነገሩ እንዲህ ነው …
ለማለዳ ሚዲያ አቶ ቸሩ ሌዳሞ የተባሉ ግለሰብ (የሲዳማ ክልል ፕረዝደንት አቶ ደስታ ሌዳሞ ወንድም) በሃዋሳ ከተማ በተለምዶ 05 ሰፈር 7 ላውንጅ ገባ ብሎ የሚገኝ አምስት ሺ ካሬ ሜትር መሬት ላይ የሚገኝ ቤት በተጭበረበረ መንገድ በመውሰድ ለአቶ ይድነቃቸው አስፋው ( የእንጆሪ ላውንጅ ባለቤት) ከሃያ ሶስት ሚልየን ብር በላይ በሆነ ገንዘን መሸጣቸውን መረጃ ይደርሳል።

መረጃው የደረሰው ሚዲያችንም ጉዳዩን ለማጣራት ባደረገው ጥረት የጥቆማውን ትክክለኛነት የሚያመላክቱ የሰነድና የሰው ማስረጃ አግኝቷል።
*****
ከታች በታይፕራይተር ከተፃፈዉ ደብዳቤ መረዳት እንደሚቻለው ባለይዞታዋ ወይዘሮ ኒሻን ቤቱንና ግቢውን አስይዘው ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተበደሩትን 27,314.32 ብር ዕዳ መመለስ ባለመቻላቸው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሐዋሳ ቅርንጫፍ ሀራጅ አውጥቶ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ሲዳማ ዞን ቅ/ጽ/ቤት 27,314.32 ብር በመክፈል ቤቱንና ቦታውን የግሉ አድርጓል።

ግዢዉን ተከትሎ ቀይ መስቀል ማህበር ቦታው ርክክብ እንዲደረግለት ለባንኩ እና ለሐዋሳ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ደብዳቤ ፅፎ ጠይቋል። [በታይፕራይተር የተፃፈ ደብዳቤ በመመልከት መረዳት ይቻላል]

ይሁን እንጂ ቅ/ጽ/ቤቱ የስም ዝውውርና ሳይት ፕላን እንዲሠራለት ተደጋጋሚ ጥያቄ ለሐዋሳ ከተማ ቢያቀርብም በየወቅቱ የቅ/ጽ/ቤቱ ሥራ አስኪያጆች እየተቀያየሩ እና ጉዳዩ የሚመለከታቸው የሐዋሳ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ጉዳዩን እያጎተቱ ይዞታው ከወ/ሮ ኒሻን ወደ ሲዳማ ዞን ቀይ መስቀል ማህበር ስም ሳይዛወርና የሳይት ፕላንም ሳይሠራ ለዘመናት መቆየቱን ያገኘናቸው መረጃዎች ያሳያሉ።

በ2015 ዓ.ም የመሬት ምዝገባ በካደስትራል ሲጀመር ቦታው ምንም እንኳ ለረጅም ዓመታት በቀይ መስቀል ማህበር እጅ የቆየ ቢሆንም ( መጀመሪያ በክራይ መልክ ከዚያ በግዢ ) ሕጋዊ ፕላንና ሰነድ እንደሌለው በሐዋሳ ከተማ ሐይቅ ዳር ክፍለ ከተማ አስተዳደር ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት ይደርስበታል።

ውስብስቡ የመሬት ንጥቂያ ሥራ እዚህ ጋ ይጀምራል።

የሐይቅ ዳር ክፍለ ከተማ ከዋና ከተማ ማዘጋጀ ቤት ጋር በመተባበር የሲዳማ ቀይ መስቀል ማህበር ቅ/ጽ/ቤት ይዞታዬ ነው ሰለሚለው ቦታ ሕጋዊ ፕላን እንዲያቀርብ በደብዳቤ ይጠየቃል። የቀይ መስቀል ማህበር ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤትም በእጁ ያሉትን መረጃዎችና ማስረጃዎች ይዞ ይቀርባል። ሆኖም በሐይቅ ዳር ክፍለ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት ይዞታው የቀይ መስቀል ማህበር ቅ/ጽ/ቤቱ አለመሆኑ ይነገረዋል። በዚህ ምክንያት ብዙ ጭቅጭቅ ተነስቶ በቀድሞ የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ረ/ፕ ፀጋዬ ቱኬ አማካኝነት ንብረቱ በቀይ መስቀል ማህብር እጅ እንዲቆይ ይደረጋል።

የአሁን የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ መኩሪያ መርሻዬ ወደ ኃላፊነት ከመጣ ቦኋላ ቦታው በወ/ሮ ፀዳል ውድነህ ስም የሳይት ፕላን ፎርጅድ ካርታም ተዘጋጅቶለት፣ የ15 ዓመት ውዝፍ ግብር በማትታወቅ ነገር ግን ሕጋዊ ውክልና ሰጥታለች በተባለችው በወ/ሮ ፀዳል ውድነህ ስም እንዲከፈል ይደረጋል።

በወቅቱ የሲዳማ ክልል ቀይ መስቀል ማህበር ቅርንጫፍ ጽ/ቤትና የቦርድ አባላት ፦

1. አቶ ተሰማ ዲማ (ሰብሳቢ)፣
2. ዶ.ር አራርሶ ገረመው (አቃቤ ንዋይ)፣
3. አቶ ዮሐንስ ላታሞ (ፀሐፊ)፣
4. አቶ አክሊሉ አዱላ (አባል)፣
5. ፓስተር ጌቱ አያለው (አባል) ጉዳዩን ከርዕሰ መስተዳደር ጽሕፈት ቤት ጀምሮ በተዋረድ ለሚለመለከተው አካል ሁሉ ቢያሳውቁም ሰሚ ሳያገኙ ቀሩ።

ከዚያ በኋላ የመሬት ንጥቂያ ሴራ ዋና አቀነባባሪ ናቸው የተባሉት አቶ ቸሩ ሌዳሞ (የአቶ ደስታ ሌዳሞ ወንድም) በወቅቱ በአቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ ተባባሪነት ልዩ ኃይል ይዘው ወደ ማህበሩ ፅህፈት ቤት በማምራት በግቢው የሚገኘውን የቡና ተክልና ሙዝ አውድመው፣ የቅ/ጽ/ቤቱ ሠራተኞች ላይ ዝተው፣ የቦርድ አባላቱን አስፈራርተው ግቢውን እንዲለቁ ካደረጉ በኋላ በወ/ሮ ፀዳለ ስም በተዘጋጀው ውክልና ስም ከ 23 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ገንዘብ ለአቶ ይድነቃቸው አስፋው (የእንጆሪ ላውንጅ ባለቤት) እንደተሸጠ በማለዳ ምርመራ ተረጋግጧል።

ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ቢወስደውም የፍትህ ሥርዓቱ በርዕሰ መስተዳድሩ ፍላጎት የተተበተበ በመሆኑ ከሲዳማ ክልል ፍትህ ፈፅሞ ልያገኝ ባለመቻሉ አቤቱታውን ወደ ቀይ መስቀል ማህበር የበላይ ጠባቂ አቅርቦ ምላሽ እየተጠባበቀ ይገኛል።

መንግሥት የህዝብ ተቋማት የበላይ ጠባቂ እንደ መሆኑ ለእነኚህ ተቋማት መወገን ሲገባው በግለሰቦች ስም የማጭበርበሪያ ሰነድ በማዘጋጀት የተቋም መሬት ነጥቆ እስከመሸጥ ድረስ የደረሰ መሆኑን ከታች የተያያዙ ማስረጃዎችን ብቻ በማየት መረዳት ይቻላል።

በዚህ ዙሪያ የበለጠ መረጃ የሚሹ የሚዲያም ሆኑ ሌሎች ተቋማት ካሉ ማለዳ ሚዲያ የበለጠ መረጃ በመስጠት የሚተባበር መሆኑን ለመግለፅ እንወዳለን።

ማለዳ ሚዲያ

ሲዳማ ክልል የፏፏቴዎች ምድር ****የሲዳማ ክልል በተለይም ምስራቃዊ ዞን በፏፏቴዎች ገፀ በረከት የታደለ አከባቢ ነው። ከሐዋሳ በ109 ኪሜ ርቀት ላይ ቦና ዙሪያ ወረዳ፣ ዎራንቻ ላይ የሎጊታ...
20/07/2025

ሲዳማ ክልል የፏፏቴዎች ምድር
****
የሲዳማ ክልል በተለይም ምስራቃዊ ዞን በፏፏቴዎች ገፀ በረከት የታደለ አከባቢ ነው።

ከሐዋሳ በ109 ኪሜ ርቀት ላይ ቦና ዙሪያ ወረዳ፣ ዎራንቻ ላይ የሎጊታና ጋላና ፏፏቴዎች የጎብኝዎችን ቀልብ የሚስቡ ናቸው።

የሎጊታን ወንዝ ተሻግረው፣ የካራማራ ተራራ ለሁለት ከፍለው አቋርጠው ወደ ዳዬ ባንሳ ምድር ሲደርሱ ታላቁን የቦኖራ ፏፏቴ ያገኛሉ።

በዚህ አከባቢ ብዙም የማይታወቅ ነገር ግን መንፈስን የሚያድስ አንድ ፏፏቴ አለ። እሱም የአሳሮ ፏፏቴ ይባላል።

ወደ አሮሬሳ ሲወርዱ የጭጮን ፏፏቴ ያገኛሉ። በዳኤላ ወረዳም ልዩ መልክዓ ምድርና ፏፏቴ ይገኛል።

የምስራቃዊ ሲዳማ ዞን በፏፏቴዎች ብዛት የሚታወቅ የቱሪዝም መዳረሻ ነው።

ማለዳ ሚዲያ

Address

WA

Telephone

(206) 460-2119

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Maleda Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Telephone
  • Alerts
  • Contact The Business
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share