ቀለም Kelem

ቀለም Kelem ከቀለም እውነትንም ዕውቀትንም ይቅሰሙ፡፡ Kelem means Color, explore realty and knowledge Informing the realities around the world focusing Ethiopian Issues

18/07/2025

ማስታወቂያ
ቱርክ መሄድና መሥራት ለምትፈልጉ

ከጎጎ ቱር ኤንድ ትራቭል
0982123312

የባሕርዳር ከተማ አስተዳድር የጸጥታ ምክር ቤት ልዩ  ልዩ ውሳኔዎችን አስተላለፈ። የባሕርዳር ከተማ አስተዳድር ከዚህ በፊት የከተማችንን የጸጥታ ኹኔታ መነሻ በማድረግ የኅብረተሰቡን ደህንንነት...
17/07/2025

የባሕርዳር ከተማ አስተዳድር የጸጥታ ምክር ቤት ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን አስተላለፈ።

የባሕርዳር ከተማ አስተዳድር ከዚህ በፊት የከተማችንን የጸጥታ ኹኔታ መነሻ በማድረግ የኅብረተሰቡን ደህንንነት ከማስጠበቅ አኳያ ልዩ ልዩ ክልከላዎችን የጸጥታ ምክር ቤቱ ማውጣቱ ይታወቃል።

አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ በባሕርዳር ከተማ አስተዳድር በተከታታይ በተሠራው ጠንካራ የሕግ ማስከበር ሥራ እና በኅብረተሰቡ የላቀ ተሳትፎ የከተማዋ የሰላምና የጸጥታ ኹኔታ በከፍተኛ ኹኔታ እየተሻሻለ መምጣቱን ምክር ቤቱ ገምግሟል።

የከተማው ፀጥታ ምክር ቤት ሌላው አፅዕኖት ሰጦ የተመለከተው የከተማው ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ኹኔታ በጥሩ እንቅስቃሴ ላይ የሚገኝ መሆኑንና ይህንኑ በላቀ ኹኔታ ለማሳለጥና የከተማችን የቱሪዝም እና የልማት ተግባራት የበለጠ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ለማድረግ የሚከተሉትን ከዚህ በፊት ተጥለው የነበሩ ክልከላዎችን በከፊል አንስቷል ። ከእነዚህም መካከል፦

1. ማንኛውም የንግድ እንቅስቃሴ ያለገደብ 24 ሰዓት ክፍት በማድረግ እንዲሠሩ ተወስኗል፣

2. ከባጃጅ እና ከሞተር ሳይክል ውጭ ሁሉም ተሽከርካሪዎች ያለገደብ እንዲንቀሳቀሱ ተወስኗል፣

3. ማንኛውም ሰው ያለምንም የሰዓት ገደብ እንዲንቀሳቀስ ተፈቅዷል፣

👉ማሻሻያ ያልተደረገባቸውና አሁንም የተጣሉ ግዴታዎችን በተመለከተ፦

1.ማንኛውም ተሽከርካሪ በሚንቀሳቀስበት ጊዜ የፊት ለፊትና የኋላ ሰሌዳ አሟልቶ መንቀሳቀስ አለበት ይህንን ሳያደርግ ተገኝቶ በጸጥታ ሀይሉ ለሚወሰደው ማንኛውም ሕጋዊ እርምጃ ኅላፊነቱን ራሱ ይወስዳል፣

2.ማንኛውም እግረኛ ሲንቀሳቀስ ማንነቱን የሚገልጽ የቀበሌ የነዋሪነት መታወቂያ ይዞ መገኘት አለበት፣

3.የጸጥታ ሀይሉ እና በሚኖሩበት ቀበሌ ወይም ቀጠና ወይም ብሎክ ብቻ መሳሪያ ይዘው እንዲንቀሳቀሱ ከፈቀደላቸው መሳሪያ ፈቃድ ኩፖን ከተሰጣቸው ውጭ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ በፍጹም የተከለከለ ነው፣

4.የባጃጅ ተሽከርካሪ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት በኋላ ይዞ መንቀሳቀስ ክልክል ነው፣

5.ባለ ሁለት እግር ሞተር በማንኛውም ሁኔታ ይዞ መንቀሳቀስ በፍጹም የተከለከለ መኾኑን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ገጽ የተገኘ መረጃ ያሳያል።

ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅን ለማሻሻል የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ መርምሮ አፀደቀ:: አዲስ አበባ፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ2ኛ ...
17/07/2025

ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅን ለማሻሻል የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ መርምሮ አፀደቀ::


አዲስ አበባ፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ2ኛ አስቸኳይ ስብሰባው፤ የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011ን ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ በአብላጫ ድምጽ አፅድቋል፡፡

የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ እውነቱ አለነ ሪፖርት እና የውሳኔ ሀሳብ ለምክር ቤቱ ያቀረቡ ሲሆን፤ የማሻሻያ ረቂቅ አዋጁ በነባሩ አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ላይ የተስተዋሉ ክፍተቶችን በማረም በፖለቲካ ፓርቲዎች አስተዳደር፣ በምርጫ እና በምርጫ ስነ-ምግባር የባለድርሻ አካላት መብትና ግዴታ ሚዛናዊነትን ለመጠበቅ የሚያስችል ድንጋጌዎችን ያካተተ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ረቂቅ አዋጁ ዓለም አቀፍ ምርጥ ተሞክሮዎችን በመውሰድ እና ቴክኖሎጂን በመጠቀም ጥርጣሬና ሥጋትን በማስወገድ ጊዜና ወጪን ሊቆጠብ በሚችል እንዲሁም ዘመናዊ አሰራርና ለመተግበር የሚያግዝ መሆኑን ሰብሳቢው አያይዘው አብራርተዋል፡፡

የማሻሻያ ረቂቅ አዋጁ ከዚህ በፊት የታዩ እና ወደፊትም ሊከሰቱ ይችላሉ ተብሎ የሚገመቱ ተግዳሮቶችን በመቅረፍ የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት፣ ፍትሃዊና ተዓማኒነት ያለው የምርጫ ሂደት እንዲኖር የሚያስችል መሆኑን የተከበሩ አቶ እውነቱ አለነ አመላክተዋል፡፡

ረቂቅ አዋጁ ሴቶችን፣ አካል ጉዳተኞችን እና ወጣቶችን በምርጫ ለመሳተፍ እድል የሚፈጥር እና በምርጫ ሂደት የሚነሱ ቅሬታዎችን በተገቢው መንገድ ለመፍታት የሚያስችል መሆኑን የተከበሩ አቶ እውነቱ አለነ አያይዘው አብራርተዋል፡፡
ከምክር ቤት አባላት በርካታ ጥያቄዎች የቀረቡ ሲሆን፤ በምርጫ ጣቢያ የነበረው የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ ለምን ቀረ? በሚል ለቀረበ ጥያቄ መልስ ሲሰጡ፤ በየምርጫ ጣቢያዎች ኮሚቴ ከመዋቀሩ ይልቅ በክልል ደረጃ የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ ተዋቅሮ ለችግሩ በማዕከል ደረጃ ምላሽ እንዲሰጥበት ማድረግ እንደሚቻል የተከበሩ አቶ እውነቱ አለነ አስረድተዋል፡፡

የፓርቲ አባላት መዋጮ ክፍያን በተመለከተም ከ30 ወደ 20 በመቶ መቀነስ መቻሉን ምርጫ ቦርድ ፓርቲዎችን በገንዘብ ለመደገፍ ይህ እንደግዴታ የማይታይ እንደሆነና ተፎካካሪ ፓርቲዎች በራሳቸው ውስጠ ደንብና መመሪያ መሰረት መተግበር የሚችሉ መሆኑን የተከበሩ አቶ እውነቱ ጠቁመዋል፡፡

በሀገር ደረጃ አዳዲስ ክልሎች መመስረታቸው፤ ሀገራዊ ፓርቲ ለመመስረት ከአሁን በፊት በአራት ክልሎች የድርጅት አባል ማፍራት አለባቸው የሚለው አሁን ላይ ወደ ስድስት ክልሎች እንዲያድግ መደረጉን የተከበሩ አቶ እውነቱ አለነ ገልጸዋል፡፡
የምክር ቤት አባላት በበኩላቸው፤ ረቂቅ አዋጁ መሻሻሉ ለቀጣይ ለሚደረገው ሀገራዊ ምርጫ የዲሞክራሲአዊ ስርዓትን ለመገንባት አቅም የሚፈጥር መሆኑን ጠቁመው፤ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ሰብሰብ ብለው አንድ ጠንካራ ድርጅት መፍጠር እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡

በኢትዮጵያ መድበለ ፓርቲ ስርዓት እንዲጎለብትና የዲሞክራሲ ባህል እንዲዳብር በግልፅ የተገኙ ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች በረቂቅ አዋጁ መመላከት እንዳለባቸው የተፎካካሪ ፓርቲ የምክር ቤት አባላት አስገንዝበዋል፡፡

ምክር ቤቱ፤ የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅ፤ አዋጅ ቁጥር 1394/2017 አድርጎ በሁለት ተቃውሞ፤ በአራት ድምጸ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምጽ አፅድቋል፡፡

መስከረም 8 ቀን 2018 ዓ.ም ሁሉም ተማሪ ዩኒቨርስቲ የሚገባበት እለት መሆኑ ተነገረመስከረም 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የቀጣዩ አመት የዩኒቨርስቲ ት/ት ይጀመራል ሲል ትምህርት ሚኒስቴር ...
17/07/2025

መስከረም 8 ቀን 2018 ዓ.ም ሁሉም ተማሪ ዩኒቨርስቲ የሚገባበት እለት መሆኑ ተነገረ

መስከረም 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የቀጣዩ አመት የዩኒቨርስቲ ት/ት ይጀመራል ሲል ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።

የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የፈተና ውጤት ጳጉሜ ላይ ይፋ ይሆናል በማለት እስከዚያም ድረስ የሚቆየው ፈተና ያልወሰዱና በመጪው ነሐሴ ወር ለፈተና የሚቀመጡ ቀሪ ተፈታኝ ተማሪዎች በመኖራቸው መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ተናግረዋል።

በተለያየ ምክንያት ዘግይተው ትምህርት የጀመሩ በመኖራቸው ነው ፈተና እኩል ያልወሰዱ ተፈታኞች ያሉት በማለትም በመሆኑም ጳጉሜ ወር ላይ የ12ኛ ክፍል የፈተና ውጤት ከታወቀ በኋላ መስከረም 8 ቀን ሁሉም ተማሪ ዩኒቨርስቲ የሚጀምርበት እለት እንደሚሆን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

የትምህርት ካላንደርን በአግባቡ አክብሮ በመስራት የፈተና ጊዜያትንም ላለመሻማት ይሰራል ሲሉ ያከሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ከመስከረም ጀምሮ ጥብቅ አሰራር እንደሚኖር ገልጸዋል።

እንደ ሀገር እኩል ውጤት ተናግሮ በእኩል ትምህርት ለማስጀመር ሲባል ቀሪ ያልተፈተኑ ተፈታኝ ተማሪዎችን ጠብቆ ማስጨረስ እንደሚገባ የተናገሩት የትምህርት ሚኒስትሩ በራሳቸው ፈቃድና ምክንያት አስቀድመው ፈተና ላይ ካልተቀመጡት በቀር ሌሎቹ የመመዘኛ መስፈርቱ አካል መሆናቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አዲስ ህግ አውጥቷል‼️ በሁሉም የሊግ እርከን የሚገኙ ክለቦች በ2018 የውድድር ዓመት ምዝገባ ወቅት የክለብ ስያሜያቸው ከብሔር ስም ጋር የተገናኘ ከሆነ በመቀ...
17/07/2025

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አዲስ ህግ አውጥቷል‼️


በሁሉም የሊግ እርከን የሚገኙ ክለቦች በ2018 የውድድር ዓመት ምዝገባ ወቅት የክለብ ስያሜያቸው ከብሔር ስም ጋር የተገናኘ ከሆነ በመቀየር ማስመዝገብ ይኖርባቸዋል ተብሏል፡፡

ክለቦች በኦፊሴላዊ መለያ (አርማ) ላይ ፖለቲካዊ እና የብሔር ይዘት ያላቸው መልዕክቶች እና ምስሎችን መጠቀም የተከለከለ መሆኑም ተገልጿል።

የስፔኑ ኃያል ክለብ ባርሴሎና፣ በአንድ ወቅት በክለቡ አፈ ታሪክ ሊዮኔል ሜሲ ይለበስ የነበረውን ታሪካዊውን የቁጥር 10 ማሊያ፣ ለታዳጊው ኮከብ ላሚን የማል ማበርከቱን በይፋ አረጋግጧል።የ18...
16/07/2025

የስፔኑ ኃያል ክለብ ባርሴሎና፣ በአንድ ወቅት በክለቡ አፈ ታሪክ ሊዮኔል ሜሲ ይለበስ የነበረውን ታሪካዊውን የቁጥር 10 ማሊያ፣ ለታዳጊው ኮከብ ላሚን የማል ማበርከቱን በይፋ አረጋግጧል።

የ18 ዓመቱ ላሚን የማል፣ ይህንን ትልቅ ኃላፊነት የተረከበው ማሊያውን ለብሶት ከነበረውና በክረምቱ የዝውውር መስኮት በውሰት ወደ ሞናኮ ካመራው ሌላኛው የላ ማሲያ አካዳሚ ምሩቅ አንሱ ፋቲ ነው።

ባርሴሎና ይህንን ዜና ይፋ ያደረገው እጅግ ልዩ እና ልብ በሚነካ መንገድ ነው። ክለቡ፣ ላሚን የማል ባደገበት ሰፈር ውስጥ በሚገኝና በልጅነቱ ይጫወትበት በነበረ የመጫወቻ ሜዳ ላይ፣ ለታዳጊው ኮከብ ክብር የተሰራን አንድ ትልቅ ግድግዳ ላይ የተሳለ ምስል (mural) በማሳየት ነው። ይህም ክለቡ ለታዳጊው ያለውን ክብርና ከስሩ መሰረቱ ጋር ያለውን ግንኙነት ያሳያል ተብሏል።

በባርሴሎና ክለብ ታሪክ የቁጥር 10 ማሊያ፣ ከተራ ቁጥር የዘለለ ትርጉም አለው። ይህ ማሊያ እንደ ሊዮኔል ሜሲ፣ ሮናልዲንሆ እና ሪቫልዶ ባሉ የዓለም እግር ኳስ ፈርጦች የተለበሰ ሲሆን፣ የብቃት፣ የተስፋና የክለቡ የፈጠራ አቅም ምልክት ተደርጎ ይቆጠራል።

ላሚን የማል በ18 ዓመቱ ይህንን ታላቅ ኃላፊነት መረከቡ፣ ክለቡ በእሱ ላይ የጣለውን ከፍተኛ እምነትና ለወደፊቱ የክለቡ መሪ እንዲሆን ያለውን ተስፋ በግልጽ ያሳያል።

አሜሪካ የግለሰቦችን የማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ልትመረምር ነው!ዐዲሱ መመሪያ መሠረት በጉብኝት ቪዛ መደብ ውስጥ የF ፣ M እና J ሁሉም የተማሪ እና የልውውጥ (Exchange) ቪዛ አመልካቾ...
16/07/2025

አሜሪካ የግለሰቦችን የማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ልትመረምር ነው!

ዐዲሱ መመሪያ መሠረት በጉብኝት ቪዛ መደብ ውስጥ የF ፣ M እና J ሁሉም የተማሪ እና የልውውጥ (Exchange) ቪዛ አመልካቾችን የበይነ መረብ (online) አጠቃቀም ጨምሮ ሁሉን አካታች እና ጥልቅ የሆነ ማጣራት እናካሄዳለን።

ይህን የማጣራት ሥራ ለማቀላጠፍ ሁሉም የ F ፣ M እና J ጉብኝት ቪዛ አመልካቾች ሁሉንም የማኅበራዊ ትስስር ገጽ መለያቸውን (Social media profile) ከግል ሴቲንግ (private setting) ወደ ክፍት/ይፋዊ ሴቲንግ (public setting) እንዲያስተካክሉ ይጠየቃሉ።

በዚህ ላይ ምን አስተያዬት አላችሁ?

የውጭ አገር የሥራ ዕድል!ይህንን መረጃ ለወዳጆቻችሁ በማጋራት ሕጋዊ የሥራ ስምሪት እንዲኖር አድርጉ!በሥራና ክህሎት ሚንስቴር የውጪ አገር ሥራ ስምሪት በሠለጠነ እና በከፊል የሠለጠነ የሰው ኀ...
16/07/2025

የውጭ አገር የሥራ ዕድል!

ይህንን መረጃ ለወዳጆቻችሁ በማጋራት ሕጋዊ የሥራ ስምሪት እንዲኖር አድርጉ!

በሥራና ክህሎት ሚንስቴር የውጪ አገር ሥራ ስምሪት በሠለጠነ እና በከፊል የሠለጠነ የሰው ኀይል የዜጎችን መብት፣ ደኅንነት እና ጥቅም አስጠብቆ በማሰማራት ትልቅ ስኬት መመዝገቡ ይታወቃል።

አሁንም ሕጋዊ የውጪ አገር ሥራ ስምሪት በሠለጠነ የሰው ኀይል በተለያዩ የሞያ ዘርፎች ከፍተኛ ቁጥር ያለው የሰው ኀይል ይፈለጋል።

በመኾኑም ከዚህ በታች በተዘረዘሩት የሞያ ዘርፎች መሰማራት የምትፈልጉ በሙሉ ከታች በተቀመጠው ሊንክ በመግባት ፎርሙን ሞልታችሁ የዕድሉ ተጠቃሚ እንድትኾኑ ስንል እናሳውቃለን።

Driving & Transportation
1. Light Vehicle Driver
2. Heavy Vehicle Driver (e.g., Grader Operator)
3. House Driver
4. Trolley Operator

Security & Safety
5. Security Guard
6. CCTV Surveillance Operator
7. Office Security Personnel
8. Plumber
9. Electrician
10. HVAC Technician
11. AC Technician
12. Pumper

Domestic & Facility Services
13. Housekeeper
14. House Maid
15. House Cleaner
16. Housekeeping Supervisor
17. Houseman
18. Caretaker
19. Steward
20. Laundry Attendant
21. Bellman

Hospitality & Food Services
22. Receptionist
23. Waiter/Waitress
24. Barista
25. Sous Chef
26. Pastry Chef / Dessert Chef
27. Garde Manger Chef
28. Arabica Cuisine Chef
29. Kitchen Assistant
30. Private Cook
31. Room Attendant
32. Hotel Assistant Manager

Healthcare & Caregiving
33. Nurse
34. Junior Nurse
35. Home Care Nurse
36. Private Nurse
37. Junior Midwife / Clinical Nurse
38. Elderly Care Assistant
39. Live-in Support Assistant
40. Neonatal Intensive Care Unit (NICU) Nurse
41. Junior Physiotherapist

Childcare Services
42. Babysitter
43. Childcare Worker

Beauty & Salon Services
44. Hairdresser
45. Hairstylist
46. Beauty Therapist
47. Salon Manager
48. Nail Technician
49. Nail Art Instructor
50. Massage Therapist
51. Makeup Artist

Agriculture & Farming
52. Indoor Farmer
53. General Farm Worker

Administrative & Marketing
54. Junior Administrative Assistant
55. Junior Marketing Assistant
56. Junior Account Manager
57. Sales Representative
58. Purchaser

Skilled Labor
59. Construction Worker
60. Laborer
61. Tailor
62. Storekeeper
63. Supervisor

Retail & Customer Services
64. Cashier
65. Promoter

https://forms.gle/TF5BcYBtrhwkyjR59

መልካም ዕድል!

የሥራ ባለቤት እርስዎ ነዎት!

አፍሪካ ቀስ በቀስ እየተሰነጠቀች አዲስ ውቅያኖስ የመፍጠር ኹኔታዋ እየሰፋ ነው ተባለ።ለዓመታት የሳይንስ ሊቃውንትን ትኩረት ሲስብ የቆየው የአፍሪካ ቀጣናዊ ለውጥ ዐዲስ ምዕራፍ ላይ ደርሷል። ...
15/07/2025

አፍሪካ ቀስ በቀስ እየተሰነጠቀች አዲስ ውቅያኖስ የመፍጠር ኹኔታዋ እየሰፋ ነው ተባለ።

ለዓመታት የሳይንስ ሊቃውንትን ትኩረት ሲስብ የቆየው የአፍሪካ ቀጣናዊ ለውጥ ዐዲስ ምዕራፍ ላይ ደርሷል።

አፍሪካ ቀስ በቀስ እየተሰነጠቀችና በመካከሉ ዐዲስ ውቅያኖስ የመፍጠር ሂደት ላይ እንደሚገኝ የሚያሳዩ መረጃዎች እየወጡ ነው።

ጥልቅ ስምጥ ሸለቆዎች በምሥራቅ አፍሪካ በኩል ተፈጥረው እየሰፉ ይገኛሉ።

ይህ ስምጥ ሸለቆ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋ በመሄድ በምሥራቅ አፍሪካ በኩል የሚገኘውን ክፍል ከቀሪው አህጉር የመለየት አዝማሚያ እያሳየ ነው።

ጂኦሎጂስቶች እንደሚሉት፣ ይህ ሂደት የሚሊዮኖች ዓመታት የሚወስድ ነው፤ በመጨረሻም ኹለቱን የአፍሪካ ክፍሎች የሚለይ ዐዲስ ውቅያኖስ ይፈጥራል ነው የተባለው።

ይህ ተፈጥሯዊ ሂደት በምድር ንጣፍ (tectonic plates) እንቅስቃሴ ምክንያት የሚከሰት ነው። የአፍሪካ ታርጋ (African Plate) ከሌሎች ታርጋዎች ጋር በሚያደርገው እንቅስቃሴ የሚፈጠር መሆኑ ተመላክቷል።

በምሥራቅ አፍሪካ ያለው ስምጥ ሸለቆ ከቀይ ባሕር ወደ ደቡብ እየተጓዘ የሚገኝ ነው። ይህ የመሰንጠቅ ሂደት በአካባቢው የመሬት መንቀጥቀጥና የእሳተ ገሞራ እንቅስቃሴ እንዲበዛም አስተዋጽኦ ያደርጋል ነው የተባለው።

ይህ ዐዲስ ውቅያኖስ ሲፈጠር፣ የአፍሪካ ካርታ በዐዲስ መልክ እንደሚቀየርና በርካታ ተፈጥሯዊና ጂኦግራፊያዊ ለውጦች እንደሚከሰቱም የሳይንስ ሊቃውንት ይገልጻሉ።

ይህ ክስተት ለአካባቢው ሥነ-ምኅዳር፣ የአየር ንብረት እና ለሰው ልጅ ሰፈራ ዐዲስ ተጽእኖዎች ሊኖሩት እንደሚችሉም ይጠበቃል ተብሏል።

ይህን ሂደት ለመከታተል እና ሳይንሳዊ ምርምሮችን ለማካሄድ ዓለም አቀፍ ተቋማትና ሳይንቲስቶች በትኩረት እየሠሩ እንደሚገኙም ተመላክቷል።

የሰዎችን በተለይ ደግሞ የሴቶችን እርቃን እየቀረፁ ማስፈራሪያ ፣ ገንዘብ ማግኛ የሚዳርጉ ሰዎች መኖራቸው ይነገራል፡፡ ይህ ከሞራልና ከሕግ አኳያ እንዴት ይታያል?አሁን አሁን የሰዎችን እርቃን ...
14/07/2025

የሰዎችን በተለይ ደግሞ የሴቶችን እርቃን እየቀረፁ ማስፈራሪያ ፣ ገንዘብ ማግኛ የሚዳርጉ ሰዎች መኖራቸው ይነገራል፡፡

ይህ ከሞራልና ከሕግ አኳያ እንዴት ይታያል?

አሁን አሁን የሰዎችን እርቃን በተንቀሳቃሽ ምስል እየቀረጹ ይህ ያክል ገንዘብ የማሰጠኝ ከሆነ በኢንተርኔት ላይ አሰራጫለሁ እያሉ ገንዘብ የሚሰበስቡ እንዳሉ በተደጋጋሚ ተሰምቷል፡፡

ሰዎች ደግሞ የተጠየቁትን ገንዘብ መክፈል ሲያቅታቸው ራሳቸውን እስከ ማጥፋት ሙከራ እንደሚያደርጉም ሰምተናል፡፡

እንዲ ዓይነቱ ተግባር የሚፈጸመው የእሴት መሸርሸር እና የሥነ ምግባር ዝቅጠት ሲኖር ነው ሲሉ በጉዳዩ ላይ የጠየቅናቸዉ ባለሞያዎች ነግረውናል፡፡

አቶ ቴዎድሮስ አዱኛ የማኅበረሰብ ሳይንስ ባለሞያ ናቸው፡፡ የዚህ ችግር መነሻው ወላጆች ልጆቻቸውን የሚያሳድጉበት መንገድ አንዱ ቢሆንም ገንዘብና ጥቅምን ስሕተት ባለው መንገድ ለማግኘት መሞከር ያመጣው እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

እንዲህ ዓይነቱ ድርጊት የሚያመጣው ቀውስ የአንድ ግለሰብ ብቻ ሳይሆን የማኅበረሰብን ቀውስ ያስከትላል ሲሉ የነገሩን ባለሞያው ጥቃት የደረሰባቸው ሰዎችም የወደፊት ሕይወታቸው አደጋ ላይ እንደሚወድቅ ያስረዳሉ፡፡

በአደባባይ ነውርን ከሚያለማምዱት በተጨማሪ ይህንን በመከታተል የሚያበረታቱትም ማኅበረሰብአዊ ቅጣት ያስፈልጋቸዋል ይላሉ፡፡

አቶ ጥጋብ ደሳለኝ የሕግ ባለሙያ ናቸው፡፡ ከዚህ ቀደም በዚህ ማኅበራዊ ሚዲያ የሚደረጉትን አጸያፊ ተግባር ለመቆጣጠር ከሕጉ በተጨማሪ ሌሎች ተቋማት መሥራት እንዳለባቸው ነግረውናል፡፡

በማኅበራዊ ሚዲያ እንዲህ ዓይነቱን የሰዎችን ክብር የሚነካ የጥፋ ድርጊት የሚፈጽሙ ሰዎች በሕጉ ከአንድ ዓመት እስከ አምስት ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት እንደሚቀጡ ተቀምጧል፡፡

በዚህ ዐዋጅ አምስት ሺህ እና ከዚያ በላይ ተከታዮች ባሉት የማኅበራዊ ሚዲያ ያሰራጨ ወይንም የሚያጋራ ከሆነ ደግሞ ከ50 ሺህ በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮና የአምስት ዓመት እስር የሚያስቀጣ እንደሆነ የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃ ስርጭት ዐዋጅ ላይ ተደግጓል፡፡

ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ 19 ነጥብ 1 ሚሊየን በላይ ነዋሪዎች ተመዝግበዋል። ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ እስካሁን 19 ነጥብ 1 ሚሊየን በላይ ነዋሪዎች መመዝገባቸውን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራ...
13/07/2025

ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ 19 ነጥብ 1 ሚሊየን በላይ ነዋሪዎች ተመዝግበዋል።

ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ እስካሁን 19 ነጥብ 1 ሚሊየን በላይ ነዋሪዎች መመዝገባቸውን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የህግና ፖሊሲ ዘርፍ ኃላፊ ጋብሬላ አብርሃም ገለጹ።

በኢትዮጵያ የነዋሪዎችን የመታወቅ መብት ለማረጋገጥ፣ በአገልግሎት ሰጭና ተቀባዮች መካከል መተማመን እንዲዳብር፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ግልጽነት፣ተጠያቂነትና የተሳለጠ አሰራር ለመዘርጋት የዲጂታል መታወቂያ ገቢራዊ ተደርጓል፡፡

የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የህግና ፖሊሲ ዘርፍ ኃላፊ ጋብሬላ አብርሃም ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፥ በአዲስ አበባ እና በክልል የዲጂታል የመታወቂያ ምዝገባ ማከናወንና ከተቋማት ጋር ትስስር መፍጠር በትኩረት እየተሰራ ይገኛል፡፡

ይህንን ተከትሎ እስካሁን 19 ነጥብ 1 ሚሊዮን ነዋሪዎች ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መመዝገባቸውንና ከ55 ተቋማት ጋር ትስስር መፍጠር መቻሉን ተናግረዋል።

በ2018 በጀት ዓመት የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባን የበለጠ ለማሳደግ እቅድ መያዙንና ከተቋማት ጋር ያለውን ትስስር ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰራም ጠቁመዋል፡፡

በተለይ በክልሎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባን ይበልጥ ለማስፋት ከተቋማት ጋር ያለውን ትስስር ለማጠናከር ትኩረት መደረጉን ተናግረዋል፡፡
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በክልሎች የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባን በተመለከተ ሰፊ የግንዛቤ ስራ መሰራቱን እና በዚህም ውጤት መገኘቱንም አስታውቀዋል።
ለዚህ ከከፍተኛ አመራሩ ጀምሮ ለስራው ትኩረት ሰጥቶ ህብረተሰቡ የዲጂታል መታወቂያ እንዲመዘገብ በማድረግ በኩል ትልቅ ተግባር ተከናውኗል ብለዋል፡፡
በአዲስ አበባ ማህበረሰቡ የፋይዳ ዲጂታል ትግበራ በትምህርት ቤቶች ውጤታማ እንዲሆን ያከናወነውን ተግባር በተሞክሮነት ወደ ክልሎች የማስፋት ስራ እየተሰራ መሆኑን ዳይሬክተሯ አስታውቀዋል፡፡

እንደ ዳይሬክተሯ ገለጻ የዲጂታል መታወቂያ ስርዓት የዲጂታል አገልግሎቱን ለማሳለጥና ጠንካራ የሆነ የማንነት አስተዳደር ስርዓት ለመፍጠር እያገዘ ይገኛል፡፡

የቤት ሰራተኛዋን ገድለው ሁለት ህፃናትን አግተው  10 ሚሊዮን ብር የጠየቁ አጋቾችን በቁጥጥር ስር አውሎ ህፃናቱን ለቤተሰቦቻቸው ማስረከቡን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡*...
12/07/2025

የቤት ሰራተኛዋን ገድለው ሁለት ህፃናትን አግተው 10 ሚሊዮን ብር የጠየቁ አጋቾችን በቁጥጥር ስር አውሎ ህፃናቱን ለቤተሰቦቻቸው ማስረከቡን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡
***
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 05 ቀን 2017 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ የወሩ ማብቂያ ሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ/ም፣ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 አለም ባንክ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ-ክርስቲያን አካባቢ ከቀኑ 11፡45 ሠዓት ላይ የቤት ሰራተኛ የሆነችውን ሀብታሟ ወርቁ በመኖሪያ ቤት ውስጥ በስለት ተወግታ መሞቷን እና እህትማማች የሆኑ የአስርና የሰባት ዓመት ዕድሜ ያላቸው ህፃን እምነት አሽናፊ እና ጄሪ አሽናፊ መጥፋታቸው ለአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ሪፖርት ይደሰርሰዋል፡፡

ጠቅላይ መምሪያው የፎረንሲክ፣ የምርመራ እና የክትትል ቡድን አባላትን በማደራጀት ወንጀል ወደተፈፀመበት ስፍራ ከሄዱ በኃላ ማስረጃዎችን በማሰባሰብ ሥራው መጀመሩን የጠቅላይ መምሪያው የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ገልፀዋል፡፡

የሟች ማንነት እንጂ የገዳይ ማንነት አለመታወቁ፣ ሀብታምን ማን ገደላት ? ህፃናቱስ የት ተሰውሩ? ለሚለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት እና ወንጀል ፈፃሚውን በቁጥጥር ስር ለማዋል እንዲሁም የጠፉትን ህፃናት ለማግኘት ክትትሉ በቀጠለበት ሒደት መንግስቱ ደላሳ የተባለ ግለሰብ ለህፃናቱን ወላጅ እናት ለወ/ሮ ሃዊ ዮሴፍ ስልክ በመደወል ህፃናቱን ማገቱን 10 ሚሊዮን ብር ካልተሰጠው ልጆቹን እንደሚገድላቸው እንዲሁም ጉዳዩን ለፖሊስ ካሳወቀች በህፃናቱ ላይ የከፋ እርምጃ እንደሚወስድ የሚገልፅ መልእክት ያስተላልፋል፡፡

ህፃናቱ ከዚህ ቀደም አጋቹን ስለሚያውቁትና የደገሰላቸውን የሞት ድግስ ባለማወቃቸው ያለ ጭንቀት ሲጫወቱ እና ልጆቹ እርሱ ጋር መሆናቸውን የሚያሳይ ቪዲዮ ለወ/ሮ ሃዊ ይልካል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር ባደረጉት የክትትል ሥራ የፖሊስ አባላት ቀንና ሌሊት ባደረጉት ያላሰለሰ ክትትል አጋቹን እና ሌሎች ተባባሪዎቹን ሐምሌ 5 ቀን 2017 ዓ/ም በቁጥጥር ስር በማዋል ሁለቱንም ህፃናት በአዳማ ከተማ ልዩ ቦታው ቦሌ ሰፈር እየተባለ ከሚጠራ አካባቢ ታግተው ከተቀመጡበት ቤት በሠላም ማስለቀቁን ኮማንደር ማርቆስ ጨምረው ገልፀዋል፡፡ ከወንጀሉ ጋር በተያያዘ አራት ተጠርጣዎችን ይዞ ምርመራው መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፡፡

የህፃናቱ ወላጅ እናት ወ/ሮ ሃዊ ዮሴፍ እና አባታቸው አቶ አሸናፊ ጫኔ እንዲሁም የአካባቢው ማህበረሰብ በተፈፀመው የወንጀል ድርጊት በእጅጉ ተጨንቀው እንደነበር ተናግረው የአዲስ አበባ ፖሊስ እና ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ባደረጉት ጥረት ልጆቻቸውን በሰላም በማግኘታቸው በፀጥታ አካላት ተግባር ኩራት እንደተሰማቸው ገልፀዋል፡፡

ወንጀል ፈፃሚዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል በተደረገው እንቅስቃሴ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት እንዲሁም የኦሮሚያ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ከፍተኛ ድርሻ ማበርከታቸውን ለዚህም በአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ስም ኮማንደር ማርቆስ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

መሰል ችግር ሲያጋጥም ለፖሊስ ሪፖርት ማድረግ ተገቢ እንደሆነ ፖሊስ አስታውቆ ነገር ግን ልዩ ልዩ ማህበራዊ ሚዲያ በመጠቀም ስለ ወንጀሉ መረጃ ማሰራጨት ለወንጀል ፈፃሚዎቹ ምቹ ሆኔታን እንደሚፈጥር ህብረተሰቡ ተገንዝቦ ተገቢው ጥንቃቄ ሊያደርግ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡

Address

Sydney Olympic Park, NSW

Telephone

+13609419683

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ቀለም Kelem posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ቀለም Kelem:

Share

ከየትም ቦታ የሥራ ማስታወቂያ ወሬ አያልፈንም፤ እናደርሳችኋለን፡፡

Informing the realities around the world focusing Ethiopian Issues