ቀለም Kelem

ቀለም Kelem ከቀለም እውነትንም ዕውቀትንም ይቅሰሙ፡፡ Kelem means Color, explore realty and knowledge Informing the realities around the world focusing Ethiopian Issues

ይህ ክስተት እንዳያልፋችሁ!
09/05/2025

ይህ ክስተት እንዳያልፋችሁ!

ኔፓል 26 የማኅበራዊ ሚዲያዎች በሀገሯ አገልግሎት እንዳይሰጡ አገደች።ኔፓል ውሳኔውን የወሰነችው የማኅበራዊ ሚዲያዎቹ የኔፓልን የምዝገባ መመዘኛ ባለማሟላታቸው ነው ብላለች።በኔፓል አገልግሎት ...
09/05/2025

ኔፓል 26 የማኅበራዊ ሚዲያዎች በሀገሯ አገልግሎት እንዳይሰጡ አገደች።

ኔፓል ውሳኔውን የወሰነችው የማኅበራዊ ሚዲያዎቹ የኔፓልን የምዝገባ መመዘኛ ባለማሟላታቸው ነው ብላለች።

በኔፓል አገልግሎት እንዳይሰጡ ከታገዱ ማኅበራዊ ሚዲያዎች መካከል ፌስቡክ፣ ኤክስ ፣ ኢንስታግራም፣ ቴሌግራም፣ ዋትስአፕ እና ዩቲዩብ ይገኙበታል።

የኔፓል መንግሥት ማኅበራዊ ሚዲያዎቹ እንዲመዘገቡ በተደጋጋሚ ጥያቄ ማቅረቡን አንሥቶ አለመመዝገባቸውን በማንሣት እስኪመዘገቡ ድረስ አገልግሎት እንዳይሰጡ ማገዱን ገልጿል።

ከኹለት ሳምንት በፊት የኔፓል ፍርድ ቤት በሀገሩ አገልግሎት የሚሰጡ ማኅበራዊ ሚዲያዎችን ለመቆጣጠር እንዲመች እንዲመዘገቡ ወስኖ ነበር።

በ2023 (እ.አ.አ) ኔፓል ቲክቶክንም በተመሳሳይ ጉዳይ አግዳ ነበር። በኋላ ግን በነሐሴ 2024 መመዝገቡን ተከትሎ እገዳውን አንሥታለች።

በርካቶች የመንግሥትን ውሳኔ ከቁጥጥር በላይ ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ መብትን የመጋፋት ተግባር አድርገው ወስደውታል።

አንዲት ፍየል ሦስት እግር ያለው ፍየል ወለደች።ግልገሉ የኋላ የግራ እግር ሳይኖረው መወለዱ መነጋገሪያ አድርጎታል። ፍየሉ የተወለደዉ በጉባ ወረዳ ነው።ምን፦ Zerihun Kefelegn
09/05/2025

አንዲት ፍየል ሦስት እግር ያለው ፍየል ወለደች።

ግልገሉ የኋላ የግራ እግር ሳይኖረው መወለዱ መነጋገሪያ አድርጎታል። ፍየሉ የተወለደዉ በጉባ ወረዳ ነው።

ምን፦ Zerihun Kefelegn

"ታላቁ የሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ አንጡራ ሀብት" ዶ.ር ዓለማየሁ ዋሴ የኢትዮጵያ አንጡራ ሀብት፣ ከፈጣሪ የተቸራት ገጸ በረከት፣ የጉስቁልና ዘመን ማክተሚያ ትዕምርት!ታላቁ የዓባይ ግድብ በስኬ...
09/04/2025

"ታላቁ የሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ አንጡራ ሀብት" ዶ.ር ዓለማየሁ ዋሴ

የኢትዮጵያ አንጡራ ሀብት፣ ከፈጣሪ የተቸራት ገጸ በረከት፣ የጉስቁልና ዘመን ማክተሚያ ትዕምርት!

ታላቁ የዓባይ ግድብ በስኬት መጠናቀቅ ለኢትዮጵያ ከዓድዋ ድል በኋላ የተጎናጸፈችው ግዙፍ ታሪካዊና ስትራቴጅካዊ ድል ነው፡፡

ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን በየዘመናቱ በርካታ ገድላትን የፈጸሙ ባለታሪኮች ቢሆኑም የዓድዋ ድልና ታላቁ የዓባይ ግድብ ስኬት ግን በሰማይ ላይ እንዳለ ችቦ ከኢትዮጵያ አልፎ በዓለም አደባባይ የሚታዩ አኩሪ ገድሎች ናቸው፡፡

የሕዳሴ ግድብ በስኬት መጠናቀቅ ከዓድዋ ድል ጋር የሚያመሳስለው ብዙ ጉዳዮች ቢኖሩም ሦስት መሠረታዊ ነገሮችን ግን መጥቀስ ተገቢ ነው፡፡

፩. የዓድዋ ጦርነትን እና የሕዳሴ ግድብ ግንባታን ኢትዮጵያ ያለማንም ረዳት፣ አጋዥ፣ ለጋሽ፣ አባዳሪ እና አይዞሽ ባይነት ብቻዋን የተወጣችውና የተጎናጸፈችው ድል መሆኑ፤

፪. የዓድዋ ጦርነትና የግድቡ ግንባታ ኢትዮጵያውያን አመላቸውን በጉያቸው፣ ልዩነታቸውን በጓዳቸው ትተው ገንዘባቸውን፣ ዕውቀታቸውን፣ ጊዜያቸውን፣ ላባቸውን፣ ደማቸውን አዋጥተውና አስተባብረው ያከናዎኑትና በድል የተወጡት ዘመን ተሻጋሪ አኩሪ ተግባር መሆኑ፤

፫. የዓድዋ ድልና የሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ የሰው ልጆች ሁሉ በሀገራቸውና በሉዓላዊ ግዛታቸው በነጻነት የመወሰን፣ ሦስተኛ ወገን ያወጣውን ሕግ መሰል ቀንበር፣ ውል መሳይ እግረ ሙቅ ያለመቀበል ጀግንነትን ያስተዋወቀ፣ በጥቅሉ የኮሎኒያሊስቶችን ቀንበር የሰበረ፤ ፍትሕን በራስ ዐቅም ያስከበረ ለመላው ታዳጊ ሀገር ሕዝቦች ትምህርት የሆኑ ድንበር ተሻጋሪ ድሎች መሆናቸው ነው፡፡

ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ፋይዳዉ እንደሌሎች ኘሮጀክቶች ነጠላ ትርክት የሚተረክለት፣ ውስን ጠቀሜታ ያለው አይደለም፡፡ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ እጅግ የገዘፈ ፋይዳና ስትራቴጅካዊ ጠቀሜታን ለኢትዮጵያ የሚያበርክት መሆኑ ጎላ ብሎ ሊነገር ይገባል፡፡ ከመሠረታዊ ፋይዳዎቹና ጥቅሞቹ ጥቂቶቹን ለመግለጽ፤

፩. ፖለቲካዊ ጥቅም፡- ኢትዮጵያ በሉዓላዊ ግዛቷ ውስጥ ያለ ማንም ፈቃድና ድጋፍ የተፈጥሮ ሀብቷን በማልማት ከድህነት መላቀቅ የምትችል ሀገር መሆኗን መሠረት ጥሎ አልፏል፡፡ በተጨማሪም የፖሊሲ ነጻነት ያላት ሀገር፣ በየትኛውም ዘመን ቢሆን መብቶቿንና ጥቅሞቿን ለማስከበር ወደ ኋላ የማይሉ ዜጎችና መንግሥት ያሏት ሀገር መሆኗን የመግለፅ ትልቅ ፋይዳን አጎናጽፏል፤

፪. ኢኮኖሚያዊ ጥቅም፦ የዓባይ ግድብ የሚያመነጨው ኃይል የኢንዱስትሪ መሠረት፣ የኑሮ ማሻሻያ ግብዓት፣ የቱሪዝም መዳረሻ፣ የውጭ ምንዛሬ ምንጭ ሆኖ ኢኮኖሚዋን ያነቃቃል፤ የጀርባ አጥንት ሆኖ ይደግፋል፤ ታላቅና አዲስ ሐይቅ ፈጥሮ ለአካባቢው የተረጋጋ ሥርዓተ ምህዳር በማበርከት በርሃማነትን ለመቋቋም ደጀንና ጸጋ ይሆናል።

፫. የደኅንነትና የፀጥታ ጥቅም፤

ኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች አሏት ከተባለ በዋነኝነት የጠላትነት ሰበብ ሆኖ የሚጠቀሰው የዓባይ ውኃ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ከበለፀገች ዓባይን ትገድባለች፤ ስለዚህ
‘ሠላምና መረጋጋት አግኝታ ለኢኮኖሚዋ ዕድገት ወሳኝ ሊሆን የሚችለውን ዓባይን እንዳትገድብ በውስጥም በውጭም ሰላሟን እንንሳት’ የሚል ኋላቀርና ክፉ አስተሳሰብ ነበር፡፡ አሁን የፈሩት ይደርሳል የጠሉት ይወርሣል ነውና በዓባይ ወንዝ ላይ ሊገነቡ ከሚችሉት ግድቦች መካከል ትልቁ የሆነው የሕዳሴው ግድብ ተጠናቅቆ ውኃ ተሞልቶ ታሪክ መታጠፊያው ላይ መድረስ ግዴታ ሆኗል፡፡ ይህ ስኬት የጠላቶቿን ሰበብ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ያመከነ ስለሆነ ጠላቶቿ የመጨረሻ ሞኝ ካልሆኑ በስተቀር ከዚህ ቀደም የሚከተሉትን ፖሊሲ መከተል ፋይዳ የሌለው፣ አዋጭ ያልሆነ መናኛ ሀሳብ መሆኑን ትምህርት የሠጠ ሆኗል፡፡

ስለሆነም ከእንግዲህ ግድቡን በማስቆም ሰበብ ኢትዮጵያን ማወክ ጊዜ ያለፈበት ተግባር ብቻ ሳይሆን ግድቡን መተናኮልም የኒውክሌር ማብላያን ጋንን ሸንቁሮ የራስን ትውልድና ሀገርን እንደማጥፋት ይቆጠራል፡፡ እናም የሕዳሴ ግድብ ለእናት ሀገሩ ኢትዮጵያ በልጆቿ የተበረከተ የሠላምና የደኅንነት ዘብ ሆኖ የቆመ ስትራቴጅካዊ የኒኩሌር ኃይል ነው፡፡

፬. የዲኘሎማሲ ጥቅም፦ ኢትዮጵያ ግድቡን ስትጀምር የማንንም ጥቅም ለመጉዳት ሳይሆን በመተባበር መንፈስ ራስን የማልማት ኘሮጀክት እንደሆነ አበክራ ስትገልጽ ቆይታለች፡፡ ‘ከዚህ ቀደም በተናጠል ተፈረሙ የተባሉት የቅኝ ገዥዎች ውሎች ትብብርን የማያስጠብቁ፤ በወንደማማች ሕዝቦች መካከል መጠራጠርንና መቃቃርን የሚፈጥሩ፣ በጥቅሉ ከሞራል የወረዱ ውሎች ናቸው’ በማለት ስትሟገት ቆይታለች፡፡ በዚህ አቋሟ አሁን በተግባር የውኃው ፍሰት ሳይቀንስ፣ በታችኛው የተፋሰሱ ሀገራት ላይ ጉዳት ሳያስከትል ግድቡ በውኃ ተሞልቶ መጠናቀቁ
‘ሀበሾቹ ፍትሕ ያውቃሉ’ የተባለውን ቀደምት ቃል ዳግም ያስመሰከረ ኢትዮጵያ ለእውነትና ፍትሕ የቆመች ሀገር መሆኗን የሚያሳይ በወርቅና በአልማዝ የተከፈፈ የዲኘሎማሲ ካባ የሚያጎናጽፋት ይሆናል።

፭. የመንፈስና የሥነ ልቦና ልዕልና ማጎናጸፍ፦

የዓባይ ወንዝ ወይም ጊዮን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከተጠቀሱት አራት ወንዞች አንዱ ሲሆን ይህም ወንዝ ‘ኢትዮጵያን ይከባል’ ተብሎ ተጽፏል፡፡ የዓባይ ወንዝ እስከ ዛሬ ድረስ ለሺህ ዓመታት ከኢትዮጵያ ተነስቶ ኢትዮጵያን ከፍሎ ሲጓዝ እንጅ ሲከባት አልታየም ነበር፡፡ የፈጣሪ ቃል አይታበልምና ከእንግዲህ የዓባይ ወንዝ በፍካሬያዊ ትርጉሙ ወደ ኃይል ተቀይሮ በኢትዮጵያ ምድር ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምዕራብ እስከ ምሥራቅ ይዘዋወራል፡፡ በየቤታችን ራትና መብራት ሆኖ ይገባል፣ የመኪኖቻችን፣ የባቡሮቻችን ጉልበት ሆኖ በየጋራውና በየሸንተረሩ፣ በየሜዳውና በየከተማው ይዘዋወራል፡፡

ዓባይ በበረከቱ ኢትዮጵያን ይከባል፡፡ የፈጣሪን ቃልኪዳን በዘመናችን እውን ሆኖ አየን፤ እንደተነገረልን የአማኞች ሀገር፣ ጉስቁልና የማይገባን፣ በተፈጥሮ የታደልን ሕዝቦች መሆናችንን እንድናምን
ወደላይ ተስፈንጥረን እንድንዘል አንችልም፣ አይሆንልም የሚልን አዚምን የሰበረ፣ከዚህ በላይ የሥነ ልቡና ከፍታን የሚፈጥር፣ የትንሣኤ ምልክትስ ምን ይኖራል?!

ይህ እውን እንዲሆን ላስቻሉ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ምስጋና ይድረሳቸው! እንድናከናውን ለፈቀደልን ፈጣሪም ክብር ሁሉ ለእርሱ ይሁን!

ጸሐፊና ተመራማሪ
ዓለማየሁ ዋሴ እሸቴ (ዶ.ር)

ሕገ ወጥ እርድ ማከናወን በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን ባለሥልጣኑ አስታወቀሕገወጥ እርድ ማከናወን በጥብቅ እንደተከለከለ የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን አስታውቋል።የአዲስ አበባ ከተማ ...
09/04/2025

ሕገ ወጥ እርድ ማከናወን በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን ባለሥልጣኑ አስታወቀ

ሕገወጥ እርድ ማከናወን በጥብቅ እንደተከለከለ የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን አስታውቋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቄራዎች ድርጅትና ከከተማ አስተዳደሩ ንግድ ቢሮ ጋር መጪዉን ዐዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ የሚፈጸም ሕገ ወጥ እረድን ለመከላከል ያለመ የውይይት እያካሄደ ነው።

በውይይቱ የተገኙት የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘርይሁን ተፈራ ጤንነቱ የተጠበቀ እርድ ማከናወን ቅድሚያ እንደሚሰጠው ተናግረዋል።

ቄራዎች ድርጅት ጤንነቱ የተጠበቀ ሥጋ ለኅብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግና ዘመናዊ የእርድ አገልግሎት ለመስጠት ከፍተኛ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝም አስታውቀዋል።

ከእርድ እስከ ስርጭት የሥጋ ደኅንነት እንዲጠበቅ ኅብረተሰቡ የእንስሳት እርድ አገልግሎትን ከቄራዎች ድርጅት እንዲያገኝም አሳስበዋል።
በድብቅ የሚከናወን ሕገወጥ እርድን ከፍተኛ ቁጥጥር በማድረግ ከመከላከል ባሸገር በተግባሩ የሚሳተፉ አካላትን ተጠያቂ ማድረግ እንደሚገባ አመላክተዋል።

ሕገወጥ እርድ የጤና ችግር ከማስከተሉም በተጨማሪ የከተማዋን ንጽሕና በከፍተኛ ደረጃ ይበክላል፡፡

ለቤተሰብ ፍጆታ በግል የሚደረግ እርድ ግን የተከለከለ አይደለም ተብሏል፡፡ ይሁን እንጅ በንጽሕና እና በከፍተኛ ጥንቃቄ መከወን እንዳለበት ተነሥቷል።

ኢትዮጵያ የኑክሊየር ኃይል እንድትጠቀም ተፈቀደ።የዓለማቀፉ አቶሚክ ኃይል ተቆጣጣሪ ድርጅት ኃላፊ ራፋኤል ግሮሲ ዛሬ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጋር በስልክ ተወያይተዋል።በውይይታቸውም በ...
09/03/2025

ኢትዮጵያ የኑክሊየር ኃይል እንድትጠቀም ተፈቀደ።

የዓለማቀፉ አቶሚክ ኃይል ተቆጣጣሪ ድርጅት ኃላፊ ራፋኤል ግሮሲ ዛሬ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጋር በስልክ ተወያይተዋል።

በውይይታቸውም በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የካንሰር ሕክምና ለመስጠት ለሚያደርገው ጥረት ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል። የኑክሊዬር ተቆጣጣሪ አካሉ ኢትዮጵያ የኑክሊዬር ኃይልን ለመጠቀም ከፈለገች ድጋፍ እንደሚያደርግም ግሮሲ ተናግረዋል።

የዝውውር ማስታወቂያ ለወዳጆቻችሁ አጋሩት።የፌደራል የሥነ ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከዚህ በታች በተጠቀሱት ክፍት የሥራ መደቦች ብቁ ሠራተኞችን አዘዋውሮ ማሠራት ይፈልጋል።በመሆኑም መስ...
09/03/2025

የዝውውር ማስታወቂያ

ለወዳጆቻችሁ አጋሩት።

የፌደራል የሥነ ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከዚህ በታች በተጠቀሱት ክፍት የሥራ መደቦች ብቁ ሠራተኞችን አዘዋውሮ ማሠራት ይፈልጋል።

በመሆኑም መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች [email protected] ላይ ማመልከት ትችላላችሁ።

ለተጨማሪ መረጃ- ነሐሴ 28/2017 ዓ.ም የወጣውን ሪፖርተር ጋዜጣ ማየት እንዲሁም በ0930620738 ደውለው መጠይቅ ይችላሉ።

የሥራ ማስታወቂያ!
09/03/2025

የሥራ ማስታወቂያ!

የመረጃ ማግኛ ምርጫዎ ስላደረጉን እናመሰግናለን!  Yoseph Reliance, Bekele Girma, Gargarsaa Waaqàyyofaan Jira, Abu Ayman Ismael, Ämį Ķahn I...
09/03/2025

የመረጃ ማግኛ ምርጫዎ ስላደረጉን እናመሰግናለን! Yoseph Reliance, Bekele Girma, Gargarsaa Waaqàyyofaan Jira, Abu Ayman Ismael, Ämį Ķahn II, Amare Misganaw, Wodajo Wondimu, אני צךיך עזךה, Salahadin Kedir, እውነቱ አምላክ ለፍጥረቱ ያስባል, Marelgn Asfaw, Asfaw Abraham, Gere Weldu, Tagesse Berhanu Berhanu, Mehamed Jemal, Tadesse Min, Odduu Oromoo, Teshale Alemu Sda, Ebc Ethiopia, Danal Asfaw, Ethiopia Strong, Sabboonaa Gammachuu Tuufaa, Akililu Dejene, አህመድ እባቡ እሸቱ, Adimasu Arja, ዘወይን ወይዩ, Amsalu Kassahun, አዲስ ምዕራፍ, Tesfa Galcha, Yoseph Tegene, Yosef Bekele, Getu Tsega, Addisu Erku, Back Up, Ayana Molla Awoke, Eleis Bamude, ዮናስ ፍቅር, ያልተፈታው ህልሜ ታሪኩ ብዙነው, Boju Kasaye, Melaku Birhan, Temesgen Temrsgen Tigabu, Mesfin Yata, Abdissa Muche, Sara Ethiopia, Abraham Ayele, Birhanu Eshetu, Haysam Ahmed, Selemon Gedefaw, ቃለ-አብ አድማስ

የፖለቲካና የፀጥታ ሁኔታዉ ተባብሷል።በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱት ሁለቱ ዋነኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ ዓረና ትግራይ እና ሳልሳይ ወያነ ትግራይ፣ በክልሉ ያለው የፖለቲካ እና የጸጥታ ሁኔታ እጅግ ...
09/02/2025

የፖለቲካና የፀጥታ ሁኔታዉ ተባብሷል።

በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱት ሁለቱ ዋነኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ ዓረና ትግራይ እና ሳልሳይ ወያነ ትግራይ፣ በክልሉ ያለው የፖለቲካ እና የጸጥታ ሁኔታ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን አስታወቁ። በተለይ ዓረና ትግራይ፣ "የጊዜያዊ አስተዳደሩ ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት በማጣቱ በአዲስ መተካት አለበት" ሲል ጠንካራ ጥሪ አቅርቧል።

ዓረና ትግራይ ለሉዓላዊነት እና ዴሞክራሲ ፓርቲ ባወጣው መግለጫ፣ ከፕሪቶሪያው ስምምነት በኋላ በትግራይ የተቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር፣ ሌሎችን የፖለቲካ ኃይሎች ባገለለ መልኩ በህወሓት ብቻ የተመሰረተ በመሆኑ ህዝባዊ ቅቡልነቱን ሙሉ በሙሉ እንዳጣ ገልጿል።

ፓርቲው፣ ክልሉ አሁን ባለው የፖለቲካ እና የወታደራዊ ሁኔታ ከቀጠለ ወደ ከፋ "የእርስበርስ ጦርነት" ሊያመራ እንደሚችል ከባድ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል።

ከዚህም በላይ፣ ዓረና በህወሓት ላይ የሰላ ትችት የሰነዘረ ሲሆን፣ የህወሓት ቡድን "ከሻዕብያ እና ከአማራ ታጣቂዎች" ጋር ግንኙነት እያደረገ ነው ሲል ወንጅሏል። ይህ ግንኙነት "ጥፋት ሊያስከትል የሚችል ነው" ያለው ዓረና፣ ህወሓት ከዚህ ድርጊቱ እንዲታቀብ ጥሪ አቅርቧል።

ሌላኛው ተቃዋሚ ፓርቲ ሳልሳይ ወያነ ትግራይ በበኩሉ፣ በትግራይ ያሉትን በርካታ ችግሮች ለመፍታት ብቸኛው መንገድ "ብሔራዊ ጉባኤ" ማካሄድ ነው ሲል የመፍትሔ ሀሳቡን አቅርቧል።

የሁለቱ ተቃዋሚ ፓርቲዎች መግለጫ፣ በክልሉ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ ያለው ውጥረት እየጨመረ መምጣቱን እና በጊዜያዊ አስተዳደሩ ላይ ያለው ተቃውሞ እየጠነከረ መሄዱን በግልጽ ያሳያል።

የአንድ መንደር ሙሉ 1000 ሰዎች ሕይወት በመሬት መንሸራተት አደጋ ተቀጠፈ።በጎረቤት ሱዳን ከባድ ዝናብ ባስከተለው የመሬት መንሸራተት አደጋ 1000 ሰዎች ሕይወታቸዉን አጡ።በሱዳን ምዕራባዊ ...
09/02/2025

የአንድ መንደር ሙሉ 1000 ሰዎች ሕይወት በመሬት መንሸራተት አደጋ ተቀጠፈ።

በጎረቤት ሱዳን ከባድ ዝናብ ባስከተለው የመሬት መንሸራተት አደጋ 1000 ሰዎች ሕይወታቸዉን አጡ።

በሱዳን ምዕራባዊ ክፍል ማራ በሚባለዉ ተራራማ አካባቢ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ ቢያንስ 1,000 ሰዎች መሞታቸውን የሱዳን ነፃነት ንቅናቄ ሠራዊት አስታውቋል።

በአካባቢው ለበርካታ ተከታታይ ቀናት የጣለው ከባድ ዝናብ የመሬት መንሸራተት አስከትሎ በአከባቢዉ የሚገኝ መንደርን ሙሉ በሙሉ አውድሟል።

የሱዳን ነፃነት ንቅናቄ ሠራዊት እንዳስታወቀዉ ከአንድ ሰው በስተቀር በትራሲን መንደር ውስጥ የነበሩ ሰዎች ኹሉ አልቀዋል።

የመሬት መንሸራተት አደጋዉ የትራሲን መንደር ሙሉ ለሙሉ በሚያስብል ደረጃ አውድሟል።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና ሌሎች ክልላዊ እና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች በማራ ተራራ አደጋ ለደረሰባቸው ተጎጂዎች አስቸኳይ ሰብአዊ ዕርዳታ እንዲያደርጉ አማጺ ቡድን ጥሪውን አቅርቧል። ሰዎቹ ካለቁ ድጋፉ ለማን እንደተጠየቀ ግን ግልጽ አይደለም።

በሱዳን ጦር እና በፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች (RSF) መካከል በተፈጠረው ግጭት በርካታ የሰሜን ዳርፉር ግዛት ነዋሪዎች ተፈናቅለው በማራ ተራሮች ውስጥ ተጠልለው እንደነበር ተገልጿል።

የዓለማችን ረዥሙ ድልድይ የደኅንነት ፍተሻ አለፈ።ቻይና የዓለማችን ረዥሙን ድልድይ ለትራፊክ ክፍት ልታደርግ ነው። በደቡብ ምዕራብ የቻይና ግዛት ጉዦው የተገነባው የታላቁ ሀውዢያንግ ኮረብታ ድ...
09/01/2025

የዓለማችን ረዥሙ ድልድይ የደኅንነት ፍተሻ አለፈ።

ቻይና የዓለማችን ረዥሙን ድልድይ ለትራፊክ ክፍት ልታደርግ ነው። በደቡብ ምዕራብ የቻይና ግዛት ጉዦው የተገነባው የታላቁ ሀውዢያንግ ኮረብታ ድልድይ 3 ሺህ 360 ቶን ክብደት የሚመዝኑ የከባድ ጭነት ተሽከርካሪዎችን በአንድ ጊዜ በመሸከም የደኅንነት ፍተሻዉን አልፏል።

ድልድዩ አጠቃላይ ርዝመቱ 2 ሺህ 890 ሜትር ነው፤ ከዚህ ውስጥ 1 ሺህ 420 ሜትሩ ወጥ ተንጠልጣይ ነው። ከሸለቆዉ ስር ጀምሮ ያለው የደልድዩ ከፍታም 625 ሜትር ነው። ይህም በዓለም ረዥሙ ድልድይ ያደርገዋል።

እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ጥር 2022 ግንባታው የተጀመረዉ ድልድዩ ዐራት ዓመታት ባልሞላ ጊዜ ግንባታዉ ተጠናቅቆ በተያዘዉ የአውሮፓውያኑ መስከረም መጨረሻ ለትራፊክ ክፍት ይደረጋል። ለዚህ የሚያበቃዉን የደኅንነት ፍተሻም ባለፈዉ ሳምንት አጠናቅቋል።

Address

Seattle, WA
1000

Telephone

+13609419683

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ቀለም Kelem posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ቀለም Kelem:

Share

ከየትም ቦታ የሥራ ማስታወቂያ ወሬ አያልፈንም፤ እናደርሳችኋለን፡፡

Informing the realities around the world focusing Ethiopian Issues