ቀለም Kelem

ቀለም Kelem ከቀለም እውነትንም ዕውቀትንም ይቅሰሙ፡፡ Kelem means Color, explore realty and knowledge Informing the realities around the world focusing Ethiopian Issues

የሥራ ማስታወቂያለወዳጆቻችሁ አጋሩት!
12/22/2025

የሥራ ማስታወቂያ
ለወዳጆቻችሁ አጋሩት!

12/21/2025

ዘመናዊ የኢትዮጵያ ሠራዊት

ውድ የባንካችን ደንበኞች የጥንቃቄ መልዕክት አለን! ማንኛውንም በስልክ የሚመጣ ጥያቄ ባለመቀበል እራሳችሁን ከአጭበርባሪዎች ጠብቁ!!!ባንካችን ብሔራዊ ባንክ ያወጣውን መመሪያ መሰረት በማድረግ...
12/20/2025

ውድ የባንካችን ደንበኞች የጥንቃቄ መልዕክት አለን!

ማንኛውንም በስልክ የሚመጣ ጥያቄ ባለመቀበል እራሳችሁን ከአጭበርባሪዎች ጠብቁ!!!

ባንካችን ብሔራዊ ባንክ ያወጣውን መመሪያ መሰረት በማድረግ ደንበኞቻችን በአቅራቢያቸው ወደሚገኝ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ በመሄድ የባንክ ሒሳብ ቁጥራቸውን ከፋይዳ መታወቂያቸው ጋር እንዲያጣምሩ ያስተላለፈውን መልእክት እንደ አጋጣሚ በመጠቀም አጭበርባሪዎች ደንበኞቻችን ጋር እየደወሉ አገልግሎቱ በስልክ እንደሚሰጥ እንዲሁም የባንክ ሂሳብ በዚህ ምክንያት እንደሚዘጋ በማስመሰል ለማጭበርበር እየተጠቀሙበት እንደሚገኙ ደርሰንበታል።

በመሆኑም ክቡራን ደንበኞቻችን ሒሳብን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር የማጣመሩ ሥራም ሆነ ሌሎች ከሞባይል ባንኪንግ ጋር የተያያዙ እና ማናቸውም አገልግሎቶች እርስዎ በአካል ወደ ቅርንጫፍ ካልሄዱ/ካልቀረቡ በስተቀር በስልክ ተደውሎ የማይሰጥ መሆኑን አውቃችሁ በስልክ ለሚመጡ ጥያቄዎች ምላሽ ባለመስጠት እራሳችሁን ከአጭበርባሪዎች እንድትጠብቁ በአክብሮት እናሳውቃለን!

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

 #ፖሊስ በአምስት ክፍለ ከተሞች ከ54 ሺህ በላይ የ  #ሺሻ ዕቃዎችን እና ከ650 ኪሎግራም በላይ አደንዛዥ ዕፅ ማስወገዱን አስታወቀ።የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ በከተማዋ በተለያዩ ...
12/18/2025

#ፖሊስ በአምስት ክፍለ ከተሞች ከ54 ሺህ በላይ የ #ሺሻ ዕቃዎችን እና ከ650 ኪሎግራም በላይ አደንዛዥ ዕፅ ማስወገዱን አስታወቀ።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ በከተማዋ በተለያዩ ክፍለ ከተሞች ባካሄደው ተከታታይ እና የተቀናጀ ኦፕሬሽን፣ ለወንጀል መንስኤ ናቸው ያላቸውን በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የሺሻ መጠቀሚያ ዕቃዎችን፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ግራም አደንዛዥ ዕፆችን እና ሀሰተኛ የገንዘብ ኖቶችን በህግ አግባብ ማስወገዱን አስታወቀ።

ፖሊስ እርምጃውን የወሰደው “የወንጀል መንስኤዎችን በጥናት በመለየት እና የወንጀል ዕቅድ የሚወጣባቸውን ስፍራዎች በማድረቅ ሰላምን ለማረጋገጥ” በሚል እንደሆነ ገልጿል።

በዚህም በቦሌ ክፍለ ከተማ ከሐምሌ 2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ህዳር 2018 ዓ.ም ድረስ በምሽት ጭፈራ ቤቶች፣ በፔንሲዮኖች እና በጫት ማስቃሚያ ቤቶች ላይ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ 17,095 የሺሻ ዕቃዎች፣ 605 ኪሎ ግራም ሀሺሽ እና 100 ኪሎ ግራም ጫት ተይዞ መወገዱን የቦሌ ክፍለከተማ ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ረ/ኮሚሽነር አድማሱ ኢፋ ገልጸዋል።

በተመሳሳይ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ባለፉት ወራት በተሰራ ኦፕሬሽን 22,750 የሺሻ ማስጠቀሚያ ዕቃዎች የተወገዱ ሲሆን፣ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ 209 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው በ105 የምርመራ መዝገቦች ክስ እንዲመሰረትባቸው መደረጉ ተገልጿል።

በተጨማሪም በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በመኖሪያ ቤቶችና ሆቴሎች ውስጥ በተደረገ ፍተሻ 13,420 የሺሻ ዕቃዎች፣ 50 ኪሎ ግራም አደንዛዥ ዕፅ፣ 300 ፍሬ ትራማዶል እና ሀሰተኛ የገንዘብ ኖቶች መወገዳቸው ተጠቁሟል።

በአራዳ ክፍለ ከተማ ደግሞ ከ1,500 በላይ የሺሻ ዕቃዎች እና 2 ኪሎ ግራም አደንዛዥ ዕፅ የተወገደ ሲሆን፣ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በተለይም “አሜሪካ ግቢ” ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ተመሳሳይ የማስወገድ እርምጃ መወሰዱን ኮሚሽኑ አስታውቋል።

የየክፍለ ከተማው የፖሊስ አመራሮች እንደገለጹት፣ ሺሻ እና አደንዛዥ ዕፅ መጠቀም ለከባድ ወንጀሎች መፈጸም ዋነኛ መንስኤ ከመሆናቸው ባለፈ፣ አምራች የሆነውን የወጣት ኃይል ከዓላማው የሚያሰናክሉ ተግባራት ናቸው።

በመሆኑም ኅብረተሰቡና የሃይማኖት አባቶች ወጣቱን ከመምከር ባለፈ፣ መሰል ህገ-ወጥ ተግባራት የሚፈጸሙባቸውን ስፍራዎች ለጸጥታ አካላት ጥቆማ በመስጠት ትብብራቸውን እንዲያጠናክሩ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።

ከቤተሰብ ንግድ ወደ ስኬታማ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ : ፀጋዬና እቴነሽ የሀገር ልብስ መሸመንና ልብስ ስፌት በኢትዮጵያ ባህላዊ ልብሶችን በዘመናዊ መንገድ የሚያመርቱ ኢንተርፕራይዞች መኖር የሀ...
12/18/2025

ከቤተሰብ ንግድ ወደ ስኬታማ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ : ፀጋዬና እቴነሽ የሀገር ልብስ መሸመንና ልብስ ስፌት

በኢትዮጵያ ባህላዊ ልብሶችን በዘመናዊ መንገድ የሚያመርቱ ኢንተርፕራይዞች መኖር የሀገራችንን ባህል ለማንገብና ኢኮኖሚያዊ እድገት ለማምጣት ትልቅ ሚና ይጫወታሉ። ከእነዚህ መካከል በኦሮሚያ ክልል ሸገር ሲቲ ሱልልታ የሚገኘው ፀጋዬና እቴነሽ የሀገር ልብስ መሸመንና ልብስ ስፌት መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ይገኝበታል። ይህ ኢንተርፕራይዝ የተለያዩ አቡጀዲ ጨርቆችን፣ ነጠላ፣ ጋቢ፣ ፎጣ፣ ሻርፕ፣ ስካርቭ እንዲሁም የልጆች ማቀፊያ በማምረት ለሀገር ውስጥ ገበያ በማቅረብ ላይ ይገኛል።

ኢንተርፕራይዙ በ2005 ዓ.ም. በአቶ ፀጋዬ እና ቤተሰባቸው አማካኝነት ተመሠረተ። በመጀመሪያ በ5,200 ብር ጠቅላላ ሀብት የጀመሩት ኢንተርፕራይዝ ፤ በትጋትና በቁርጠኝነት በመስራታቸው አሁን ላይ ወደ 30 ሚሊዮን ብር የሚገመት ሀብት ማንቀሳቀስ ችሏል። በተጨማሪም ለ14 ዜጎች ቀጥተኛ የሥራ ዕድል በመፍጠር ለሀገር ውስጥ የሥራ ፈጠራ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል።

ፀጋዬና እቴነሽ የሚያመርቷቸው ምርቶች በጥራትና በባህላዊ ውበት ይታወቃሉ። ከተለምዷዊ አቡጀዲ ጨርቆች ጀምሮ እስከ ዘመናዊ ዲዛይን ያላቸው ፎጣዎች ድረስ ምርቶቹን በተለያየ ምርጫ ለሀገር ውስጥ ገበያን እያቀረበ ይገኛል።

ለቀጣይ ተጨማሪ ዘመናዊ ማሽነሪዎችን በማሟላት ምርታቸውን ከሀገር ውስጥ በተጨማሪ ወደ ውጭ ሀገር ለማቅረብ አቅደው በመስራት ላይ ይገኛሉ። እንዲህ ያለው እቅድ የሀገሪቱን የወጪ ንግድ ለማጠናከርና ተጨማሪ የሥራ ዕድል ለመፍጠር ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።

ከጋምቤላ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የተላለፈ መልእክት።ኅብረተሰቡ ለፀጥታ አካላት እያደረገ ያለውን ትብብር እንዲያጠናክር የክልሉ መንግሥት ጥሪ አቅርቧል።ውድ የክልላችን ሕዝቦች ጋምቤላ ከተማን...
12/18/2025

ከጋምቤላ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የተላለፈ መልእክት።

ኅብረተሰቡ ለፀጥታ አካላት እያደረገ ያለውን ትብብር እንዲያጠናክር የክልሉ መንግሥት ጥሪ አቅርቧል።

ውድ የክልላችን ሕዝቦች ጋምቤላ ከተማን ጨምሮ በተወሰኑ ወረዳዎች በተከሰተው የፀጥታ መደፍረስ መንግሥት ከኅብረተሰቡ ጋር በመሆን ሰላም ለማስፈን ሥራዎችን እየሠራ ይገኛል።

በዚህም በግጭቱ እጃቸው አለበት ተብለው የተጠረጠሩ ወንጀለኞችን የፀጥታ አካላት በቁጥጥር ስር እያዋሉ ይገኛሉ።

ሰላሙ በይበልጥ የተረጋጋ እንዲሆን መላው ሕዝብ ለሰላም መከበር ተባባሪ መሆን ይኖርበታል።

በመሆኑም የፀጥታ አካላት የቀሩ ወንጀለኞችን ለመያዝ ጥረት እያደረጉ ሲሆን በከተማው ውስጥ የምትንቀሳቀሱ ሁሉም ተሽከርካሪዎች በፀጥታ አካላት በኩል ለፍተሻ ትብብር በማድረግ ለዘላቂ ሰላም መስፈን የበኩላችሁን ኃላፊነት እንድትወጡ እና ተባባሪ እንድትሆኑ እናሳስባለን።

በተለይም ታርጋ የሌላቸው ተሽከርካሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር እንደሚውሉ ዐውቀው ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ተመላክቷል።

መላው የክልሉ ሕዝብ የየአካባቢውን ሰላም በንቃት በመጠበቅ መንግሥት ችግሩ በተፈጠረበት ቦታ ላይ እየሰራው ያለውን የሕግ ማስከበር ሥራ እንዲደግፍም ጥሪ ቀርቧል።

✈️ውጪ ሀገር/UAE የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ዕድል 👉በሥራና ክህሎት ሚንስቴር በቀረበው የውጪ ሃገር ሥራ ስምሪት የሰለጠነ እና በከፊል የሰለጠነ የሰው ሃይል የዜጎችን መብት፣ ደህንነት እና ...
12/18/2025

✈️ውጪ ሀገር/UAE የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ዕድል

👉በሥራና ክህሎት ሚንስቴር በቀረበው የውጪ ሃገር ሥራ ስምሪት የሰለጠነ እና በከፊል የሰለጠነ የሰው ሃይል የዜጎችን መብት፣ ደህንነት እና ጥቅም አስጠብቆ በማሰማራት በተከናወኑ ተግባራት ትልቅ ስኬት መመዝገቡ ይታወቃል።

👉አሁንም በዚሁ ህጋዊ የሥራ ስምሪት ወደተባበሩት አረብ ኤምሬትስ/UAE/ በተለያዩ የሞያ ዘርፎች የሰው ሃይል ይፈለጋል።

📌የኮንትራት ቆይታ:ሁለት አመት
📌ተፈላጊ ፃታ:ወንድ

🚧የሞያ ዘርፎች:-
1.Construction Laborers (የኮንስትራክሽን ሰራተኛ / ረዳት)
2.Mason(ግንበኛ)
3.እስቲል ፊክሰር (ፌራዩ)
4.Shuttering Carperter (አናፂ)
5. Delivery Boy (ሞተረኛ)
6. Walkers (እግረኛ ተላላኪ)
7. Plumber (የቧንቧ ሰራተኛ)
8. Electrician (የኤሌክትሪክ ሰራተኛ)
9. Scaffholders (የብረት መወጣጫ ባለሞያ)
10. Ductmen (የቬንትሌሽን ባለሞያ)
11. Supervisors and Foreman
12. Timekeepers (የሰራተኛ ሰአት ተቆጣጣሪ)
13. Camp Boss Assistant (የካምፑ አለቃ ተጠሪ)

☝️በተዘረዘሩት የሞያ ዘርፎች ለመወዳደር https://forms.lmis.gov.et/triple-one-uae/ በመግባት ፓስፓርት፣ የሰራተኛ መለያ ቁጥር/Labor id/፣ የነዋሪነት መታወቂያ እና አስፈላጊ መረጃዎችን በማስገባት ከታህሳስ 08 እስከ ታህሳስ 14 2018 መወዳደር ይቻላል።

💰የትኬት፣ የጤና ምርመራ እና ቪዛ በአመልካቾች የሚሸፍኑ ወጪዎች መሆኑን እንገልፃለን። ሌሎች በስራ ቆይታ ላይ የሚያስፈልጉ የመኖርያ ቤት፣የማብሰያ ክፍልእና ከነማብሰያ እቃዎች፣ኢንሹራንስ እና የህክምና ወጪ በአሰሪው የሚሸፈኑ ወጪዎች ይሆናል።

✅ ለማንኛውም አስተያየትና ጥያቄ 9138 ነፃ የሥልክ መስመር ይጠቀሙ

12/18/2025

በኢራን ከባድ ዝናብ ከዘነበ በኋላ የውኃ አካላት ወደ ቀይ ደም ቀለም መቀየራቸው ተነገረ።

ከ50 ዓመታት ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ድርቅ እየተፈተነች ባለችው ኢራን ዝናብ ከዘነበ በኋላ የሆርሙዝ ደሴት በቀይ ውኃ መሸፈኑ ተነግሯል።

በኢራን 100 ሚሊሜትር መጠን ያለው ዝናብ የጣለ ሲሆን ይህም ከኢራን አማካይ ወርኃዊ የዝናብ መጠን በ5 እጥፍ የበለጠ ነው።

ከባድ ዝናቡ የውኃ እና የአሸዋውን ቀለም የቀየረው ሲሆን አንዳንዶች ኹነቱን ከመንፈሳዊ ነገሮች ጋር አያይዘውታል።

ሳይንቲስቶች ግን ቀይ ደም የሚመስለው ቀለም የሆርሙዝ አካባቢ ከፍተኛ የሆነ የአይረን ኦክሳይድ ክምችት ስላለውና ኦክሳይዱ ከዝናብ ጋር ሲገናኝ የሚፈጠር እንደሆነ ተናግረዋል።

የሆርሙዝ ደሴት የዓለማችን ዋነኛ የነዳጅ መሥመር በሆነው የሆርሙዝ ሰርጥ የሚገኝ ሲሆን በተለያዩ ቀለማት ያሸበረቀ በመሆኑ ቀስተዳመናማው ደሴት የሚል ስያሜም አለው።

ይኸው ደሴት በሚገኝበት የኢራን የአስተዳደር ክፍል በከባድ ዝናቡ የተነሣ መንገዶችም ተዘግተዋል።

በአማካይ በዚህ ዓመት የዝናብ መጠኗ በ89% የቀነሰባት ኢራን ዳግም መዝነብ መጀመሩን ተከትሎ ሰዎች አደባባይ ወጥተው ደስታቸውን ገልጸዋል።

ከወር በፊት ባለው የዝናብ እጥረት የተነሣ የዋና ከተማዋ ቴህራን 10 ሚሊዮን ነዋሪዎች ከተማዋን ለቅቀው እንዲወጡ ሊደረጉ ይችላሉ መባሉ ይታወሳል።

ከቬንዝዌላ ጋር ያለው ውጥረት እየተባባሰ በመጣበት ወቅት አሜሪካ በፓሲፊክ ውቅያኖስ በፈጸመችው የቅርብ ጊዜ ጥቃት 4 ሰዎችን ገደለች።አዲሱ ጥቃት በምሥራቅ ፓሲፊክ እና በካሪቢያን አካባቢ በሚ...
12/18/2025

ከቬንዝዌላ ጋር ያለው ውጥረት እየተባባሰ በመጣበት ወቅት አሜሪካ በፓሲፊክ ውቅያኖስ በፈጸመችው የቅርብ ጊዜ ጥቃት 4 ሰዎችን ገደለች።

አዲሱ ጥቃት በምሥራቅ ፓሲፊክ እና በካሪቢያን አካባቢ በሚንቀሳቀሱ ጀልባዎች ላይ አሜሪካ በወሰደችው እርምጃ የሞቱ ሰዎችን ቁጥር ወደ 100 አድርሶታል፡፡

በምሥራቅ ፓሲፊክ ውቅያኖስ የተፈጸሙት እነዚህ ሦስት የቅርብ ጊዜ ጥቃቶች፤ አሜሪካ ለቬንዝዌላ ቅርብ በሆኑት በትሪኒዳድ እና ቶባጎ ወታደራዊ ኃይሏን እያጠናከረች ባለችበት ወቅት የተከሰቱ ናቸው።

አሜሪካ በላቲን አሜሪካ ወታደራዊ ኃይሏን ማጠናከሯን በቀጠለችበት እና የቬንዝዌላን የነዳጅ መርከብ በቁጥጥር ስር ካዋለች ከቀናት በኋላ፤ በምሥራቅ ፓሲፊክ ውቅያኖስ በጀልባዎች ላይ በፈጸመችው ዐዲስ ጥቃት ስምንት ሰዎችን መግደሏን አስታውቃለች።

የአሜሪካ ጦር ደቡባዊ ዕዝ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጹ ላይ እንዳሰፈረው፤ በመከላከያ ጸሐፊው ፒት ሄግሴዝ ትዕዛዝ ሰኞ ዕለት በዓለም አቀፍ ውኃ ላይ በሚገኙ ሦስት ጀልባዎች ላይ ጥቃቶች ተፈጽመዋል።

በድምሩ ስምንት ሰዎች መገደላቸውን ደቡባዊ ዕዝ በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።

መግለጫው በመጀመሪያው ጀልባ ሦስት፣ በሁለተኛው ሁለት እንዲሁም በሦስተኛው ሦስት ሰዎች ተገድለዋል ያለ ሲሆን፤ ሟቾቹ ከዕፅ ዝውውር ጋር ግንኙነት እንዳላቸው ገልጾ ለዚህ ግን ምንም ዓይነት ማስረጃ አላቀረበም።

ከመስከረም ጀምሮ በፓሲፊክ ውቅያኖስ እና በቬንዝዌላ አቅራቢያ በሚገኘው የካሪቢያን ባሕር ውስጥ በደርዘን በሚቈጠሩ ጀልባዎች ላይ በተፈጸሙ ተመሳሳይ የአሜሪካ ጥቃቶች ቢያንስ 90 ሰዎች ተገድለዋል፤ ይህንንም የዓለም አቀፍ ሕግ ባለሙያዎች በአሜሪካ ጦር የተፈጸመ ‹‹ከሕግ አግባብ ውጪ የሆነ ግድያ›› ሲሉ ይተቹታል።

ቬንዝዌላ ጥቃቶቹ እና የአሜሪካ ወታደራዊ ከበባ ዓላማው የውጭ ኃይሎች የቬንዝዌላን እጅግ ብዙ የነዳጅ እና የጋዝ ሀብት እንዲዘርፉ ለማስቻል እንደሆነ ገልጻለች።

ለዚህም ማስረጃ ስታቀርብ፤ የአሜሪካ ኃይሎች ባለፈው ሳምንት በቬንዝዌላ የባሕር ዳርቻ የነዳጅ መርከብን በቁጥጥር ስር ከማዋላቸው በፊት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለጋዜጠኞች ‹‹ነዳጁን እኛ የምንወስደው ይመስለኛል›› ማለታቸዉን በማስታወስ ነው፡፡

የሐረር ከተማ የኮሪደር ልማት የመደመር መንግሥት ዕሳቤን በተግባር ያሳየ ነው። ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ"የሐረር ከተማ የኮሪደር ልማት የመደመር መንግሥት ዕሳቤ የኾኑት መፍጠርና መፍጠንን ...
12/17/2025

የሐረር ከተማ የኮሪደር ልማት የመደመር መንግሥት ዕሳቤን በተግባር ያሳየ ነው። ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ

"የሐረር ከተማ የኮሪደር ልማት የመደመር መንግሥት ዕሳቤ የኾኑት መፍጠርና መፍጠንን በተግባር ያሳየ ነው" ሲሉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ከበደ ዴሲሳ ገለጹ።

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አመራሮች በሐረር ከተማ የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎችንና የቱሪዝም መዳረሻዎችን ተመልክተዋል።

በመስክ ምልከታው ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ከበደ ዴሲሳ እንደገለጹት በከተማው የተከናወነው የኮሪደር ልማት ሥራዎች ዐዲስ ከተማን የመፍጠር ያህል አስደማሚ ኾኖ እንዳገኙት ገልጸዋል።

ሐረር ጥንታዊ የሥልጣኔ እና ቅርስ ከተማ ብትኾንም ቀድሞ የነበረው የከተማው ኺኔታ ጥንታዊነቷን የማይመጥን ነበር።

አሁን ላይ በአጭር ግዜ የተከናወነው የኮሪደር ልማት ሥራ የሐረርን መልክ የገለጠና በከተማ ልማት ዘርፍ ተጨባጭ ለውጥ የተመዘገበበት መኾኑን ገልጸዋል።

በተለይ በቅርስ ጥበቃ ዘርፍ ቅርሱን ማእከል በማድረግ የተሠራው ሥራ አበረታችና የቱሪዝም ፍሰቱን ለማሳደግ በሚያስችል መልኩ በልዩ ኹኔታ መከናወኑን አመልክተዋል።

ክልሉ ካለው አነስተኛ ገቢ አንጼር በአጭር ግዜ የተሠሩ አበረታች ሥራዎች ሐረር ከተማን በዐዲስ የወለዱ ናቸው።

የአካባቢውን ጸጋ ተጠቅሞ በአነስተኛ ወጪ የተከናወኑ ተግባራት ለሎች አካባቢዎች በተሞክሮነት የሚወሰዷቸው እንደኾኑም ተናግረዋል።

በተለይ የኮሪደር ልማቱ የመደመር መንግሥት ዕሳቤ የኾነው ፈጠራና ፍጥነትን በተግባር ማሳየቱንም ገልጸዋል።

Address

Seattle, WA
1000

Telephone

+13609419683

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ቀለም Kelem posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ቀለም Kelem:

Share

ከየትም ቦታ የሥራ ማስታወቂያ ወሬ አያልፈንም፤ እናደርሳችኋለን፡፡

Informing the realities around the world focusing Ethiopian Issues