New Dawuro Media

New Dawuro Media አዳስ ነገር | ጠቃሚ መረጃወች | ማህበራዊ አገልግሎቶች

New Dawuro Media is ideal page to knew the history , culture and entire society of Dawro Zone.

የዳውሮ ዞን እጅግ ሰፊ የሆነ የቆዳ ስፋት ያለዉ ፤ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ ቅርሶች ባለቤት ፤ አኩሪ ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቋንቋ ያለዉ ዞን መሆኑን ለዓለም ህዝብ ማሳወቅ ፤ በተጨማሪም በየማህበራዊ መሰረቶች እና በመንግስታዊ መዋቅሮች የሚዲያ ሥራዎችን ተከታትሎ መረጃዎችን ለህዝብ ማድረስ እና በዳዉሮ ዞን ሆነ በዓለም ዙሪያ የሚታዩ ክስተቶችን ለቻናላችን ቤተሰቦቸ ማድረስ ቀዳሚ ስራችን ነዉ፡፡

ዳዉሮ ዞን ከኢትዮጵያ ዉብ ገፅታ ማሳያዎች አንዱ ነዉ፡፡ ዞኑ በደቡብ ክልል የሚገኝ

ሲሆን የዞኑ ዋና ከተማ ታርጫ ትባላለች፡፡ ታርጫ ገስጋሽ ነገር ግን በሚሌኒየሙ ከተወለዱ ከተሞች አንዷ ናት፡፡ ከሐዋሳ በ282 ኪ.ሜ ከአዲስ አበባ ደግሞ በሻሸመኔ አድርገዉ በወላይታ ሶዶ የሚጓዙ ከሆነ 455 ኪ.ሜ ከአዲስ አበባ በሌላኛዉ መንገድ በጅማ አርገዉ የሚጓዙ ከሆነ ደግሞ በ479 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚያገኟት ከተማ ስትሆን ከተማዋ በየግዜዉ እያስመዘገበች ባለዉ እድገት ሳቢያም የብዙዎችን ትኩረት ስባለች፡፡

በደቡብ ከጋሞ ጎፋ በምዕራብ ከኮንታ ልዩ ወረዳ በሰሜን ምዕራብ ከኦሮምያ ክልል በሰሜን እስከ ሰሜን ምስራቅ ከከንባታ ጠንባሮ ዞን በምስራቅ ከወላይታ ዞን ይዋሰናል፡፡ ከሰሜን ምዕራብ እስከ ደቡብ ጫፍ ድረስ በጎጀብና በኦሞ ወንዞች ተፋሰስ የተከበበዉ ..

 #ሀጁ ሙፍቲህ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ።ያለሃይማኖት ልዩነት በእዚህች ሀገር ላይ አንድ የሚወደድ ታላቅ ስብእና ያሳዩ ምርጥ አባት ነበሩ።በእዚህ ትውልድ መሃል የሚነበብ መጽሐፍ ሆነው በዚህ ...
10/19/2025

#ሀጁ ሙፍቲህ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ።

ያለሃይማኖት ልዩነት በእዚህች ሀገር ላይ አንድ የሚወደድ ታላቅ ስብእና ያሳዩ ምርጥ አባት ነበሩ።

በእዚህ ትውልድ መሃል የሚነበብ መጽሐፍ ሆነው በዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።

ነፍስ ይማርልን !!!

     #ተለቀቀ----------በNew Dawuro Media ተዘጋጅቶ የሚቀር በፍሬወይን መንጌ መሪነት የሚዘጋጀው ፍሬ ሾው በNew Dawuro Media YouTube Channel ተለቋል። ገብ...
10/19/2025

#ተለቀቀ
----------
በNew Dawuro Media ተዘጋጅቶ የሚቀር በፍሬወይን መንጌ መሪነት የሚዘጋጀው ፍሬ ሾው በNew Dawuro Media YouTube Channel ተለቋል። ገብታችሁ በማየት ሀሳብ አስተያየታችሁን አጋሩን አበረታቱን።

በየሳምንቱ በኒዉ ዳዉሮ ሚዲያ ተዘጋጅቶ የሚቀርበውን ፍሬ ሾው እና ልሎች ፕሮግራሞችን ለመከታተል የዩቱብ ቻናላችንን subscribe በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።

New Dawuro Media

Our YouTube channel link

👉 https://www.youtube.com/watch?v=9yOgo2_FHkI

በNew Dawuro Media ተዘጋጅቶ የሚቀር በፍሬወይን መንጌ መሪነት የሚዘጋጀው ፍሬ ሾው በቅርብ ቀን ለአድማጭ ተመልካች ይቀርባል። በNew Dawuro Media YouTube Channel ላይ በየሳምንቱ ተዘጋጅቶ የሚቀርበውን ፍ.....

10/19/2025


----------
በNew Dawuro Media ተዘጋጅቶ የሚቀር በፍሬወይን መንጌ መሪነት የሚዘጋጀው ፍሬ ሾው በቅርብ ቀን ለአድማጭ ተመልካች ይቀርባል።

በNew Dawuro Media YouTube Channel ላይ በየሳምንቱ ተዘጋጅቶ የሚቀርበውን ፍሬ ሾው እና ልሎች ፕሮግራሞችን ለመከታተል የዩቱብ ቻናላችንን subscribe በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።

New Dawuro Media

Our YouTube channel link

👉 https://youtube.com/?si=kbycKs0Z189a0TPK

10/19/2025

አባቱ ተዋጊ ዉጊያ እያስተማረ
ልጅየው ተዋጊ ውጊያ እየተማረ
የአባት የልጅ እውቀት ውጊያ ሆኖ ቀረ .....

መልካም ሰንበት

የደመወዝ ጭማሪ ምክንያት በማድረግ ህገ-ወጥ ዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ የንግድ ድርጀቶች ላይ እርምጃ እየተወሰደ እንደሆነ ተገለፀ። በታርጫ ከተማ አስ/ር ሀገራዊ የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ጭማ...
10/18/2025

የደመወዝ ጭማሪ ምክንያት በማድረግ ህገ-ወጥ ዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ የንግድ ድርጀቶች ላይ እርምጃ እየተወሰደ እንደሆነ ተገለፀ።

በታርጫ ከተማ አስ/ር ሀገራዊ የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪን ምክንያት በማድረግ የዋጋ ጭማሪ ባደርጉ የንግድ ድርጅቶች ላይ አስተዳደራዊና ህጋዊ እርምጃ እየተወሰደ እንደሆነ የታርጫ ከተማ ንግድ ጽ/ቤት ገልጿል።

የታርጫ ኢንድስትሪና ንግድ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ብዙአለም ጎበዜ በከተማ አስተዳደር ደረጃ የህገ-ወጥ ንግድና ዋጋ ጭማሪ ለመቆጣጠር ጽ/ቤቱ የቁጥጥር ግብረ-ሃይል በማሰማራት ገበያውን ለመቆጣጠር ጥረት እያደረገ እንደሆነ ተናግረዋል። በዚህም መሠረት ከለጠፉት የዋጋ ዝርዝር ውጪ ሲሸጡ የተገኙ 29 ህገ-ወጥ የንግድ ድርጀቶች እና 30 የዋጋ ዝርዝር ያልለጠፉ አጠቃላይ 59 የንግድ ድርጀቶች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዷል ብለዋል።

በመሆኑም አለአግባብ ለመበልጸግ በሚሰሩ ነጋዴዎች ላይ እርምጃው የመውሰድና ህግ የማስከበር ሥራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ኃላፊዋ አንስተው በቀጣይነት ህገ-ወጥነትን ለመከላከል የሸማቹ ማህበረሰብ ሚና የጎላ በመሆኑ በየንግድ ድርጅቶች የተለጠፈውን የዋጋ ዝርዝር በማየት እንዲሸምትና ከተለጠፈው ዋጋ ውጪ የሚያስከፍሉ ግለሰቦች ሲያጋጥሙ ለተቋሙ ጥቆማ በመስጠት ህገ- ወጥነትን በጋራ እንከላከል በማለት ጥሪ አቅርበዋል።

የጥቆማ ስልኮች
0917004353
0913968552
0928253705
0938512724
0917008808

  አቶ ያዕቆብ ሌንጫ የዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል። ከዚህ ቀደም የታርጫ ጠቅላላ ሆስፒታል ስራ አስኪያዥ በመሆን ሆስፒታሉን እስከማሸለም ድረስ ጠንካራ የመሪነት ስራ የሰሩ ...
10/18/2025


አቶ ያዕቆብ ሌንጫ የዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል። ከዚህ ቀደም የታርጫ ጠቅላላ ሆስፒታል ስራ አስኪያዥ በመሆን ሆስፒታሉን እስከማሸለም ድረስ ጠንካራ የመሪነት ስራ የሰሩ ብርቱ ሰወሰ ናቸው። በድጋሚ እንኳን ደስ አሎት እያልን የተጣለቦትን የህዝብ አደራ በአግባቡ እንደወጡ አደራ እያልን ። መልካም የሥራ ዘመን እንዲሆንሎት እንመኛለሁ። 🙏🙏🙏

የታርጫ ጠቅላላ ሆስፒታል አመራሮች፣ የሕክምና ባለሙያዎችና የአስተዳደር ሠራተኞች እንኳን ደስ አላችሁ። ይህ የትጋታችሁ ውጤት ነው። ይህ ውጤት እንዲመጣ ቀን ከሌት ስትለፋ ፡ ስታሳካ የቆነኸው...
10/18/2025

የታርጫ ጠቅላላ ሆስፒታል አመራሮች፣ የሕክምና ባለሙያዎችና የአስተዳደር ሠራተኞች እንኳን ደስ አላችሁ። ይህ የትጋታችሁ ውጤት ነው። ይህ ውጤት እንዲመጣ ቀን ከሌት ስትለፋ ፡ ስታሳካ የቆነኸው የሆስፒታሉ ስራ አስኪያዥ አቶ ያዕቆብ ሌንጫ እንኳን ደስ አለህ በድጋሚ 🙏🙏🙏

 ?-------------የቀድሞ ታርጫ አየር ማረፊያ  አመሰራረት ታሪክ በትንሹ :-ህዝባችንና እንደራሴዎቻችን በተለያየ ጊዜ መንገድ የሌለው/መኪና የማይገባበት/አካባቢ ግን የተለያየ አኩሪ ባህ...
10/18/2025

?
-------------
የቀድሞ ታርጫ አየር ማረፊያ አመሰራረት ታሪክ በትንሹ :-

ህዝባችንና እንደራሴዎቻችን በተለያየ ጊዜ መንገድ የሌለው/መኪና የማይገባበት/አካባቢ ግን የተለያየ አኩሪ ባህልና ታሪክ ያለው በኦሞና ጎጀብ ወንዞች የተከበበ ጠንካራ ህዝብ ፣ግብር ለማዕከላዊ መንግስት የሚገብር ህዝብ፣ ብዙና ልዩ ልዩ ምርቶችን የሚያመርት ህዝብ ስለመኖሩ በሸንጎ ይነሳ ነበርና በኃይለ ስላሴ ዘመነ መንግስት (1945 ዓ/ም) ከከፋ ጠቅላይ ግዛት ለኩሎኮንታ አውራጃ አስተዳዳሪ አቶ አበበ ገብሬ ትዕዛዝ ይተላለፋል፡፡ የኩሎ ኮንታ አውራጃ አስተዳዳሪ አቶ አበበ ገብሬ በወቅቱ ሲያስተዳድሩዋቸው ከነበሩት ባልደረቦቻቸው ጋር በመሆን የቀድሞን የታርጫ አየር ማረፊያ ቦታ ይመርጣሉ፡፡

ከመረጡም በኋላም አቶ አበበ ገብሬ ቀጥታ ከአከባቢው/ #ከዋካና ታርጫ/ ህዝብ ጋር በተለይም አካባቢ ከሚያስተዳድሩት ባላባቶች (ከ6 ቀበሌ በላይ ህዝብን በማሰባሰብ የሚያስተዳድሩ እና እንዳሁኑ የተጠናከረ የመንግስት ስርዓት በሌለበት ህዝቡ ሲያጠፉ የሚቀጡ ሲጣሉ የሚያስታርቁ ባላባት ነበሩና) ጋር ውይይት አድርገዋል።

አቶ አበበ ገብሬ ይህንን ሀሳብ ለህዝቡ ባቀረቡበት ወቅት ህዝቡ በእልልታና ሆታ የተቀበለው ሲሆን ለተቀደሰ ሀሳባቸውም ለአየር ማረፊያ የተመረጠውን ይዞታ ባለይዞታዎች ለልማት ካላቸው ፅኑ ፍላጎት የተነሳ ያለ ምንም ካሳ ክፍያ በነጻ ሰጥተዋል።ለመገንባትም ተስማምተዋል፡፡ አስተዳዳሪውም ይህን የተቀደሰ ሀሳብ ለሚያስተዳድሩዋቸው አጎራባች ላሉት ባላባቶችና ሹማምንቶች ያቀርባሉ ። በዚህ የተቀደሰ ሀሳብ ህዝቡም ባላባቶችም ሹማምንቱም ይስማማሉ።

ነገር ግን አቶ አበበ ገብሬ በዝውውር ይነሱና በ1950 ዓ/ም አቶ ኃይሌ ለውጤ ይመጣሉ። አቶ ኃይሌ ለውጤም ጠንካራ የልማትና የሥራ ሰው በመሆናቸው ሥራውን ካለበት አስቀጥለዋል።

የእሳቸውም የትኩረት አቅጣጫ የቦታ ዝግጅትና የሰው ኃይል ቅጥር ስለነበር ለቦታ ዝግጅትም፦
1ኛ/ የሰው ሀይል
2ኛ/ ማሽን/መቆፈሪያ/
3ኛ/ የምግብ ዝግጅት
ለማድረግ ከህዝቡና አካባቢን ከሚያስተዳድሩት ባላባቶች ጋር ውይይት በማድረግ #ከዋካና ደጋማ አካባቢ ስንቅ፣ የሰው ኃይል መቆፈሪያ በማዘዝ ተጨማሪ የሰው ኃይል ከታርጫና አካባቢው በማቀናጀት ቁፋሮ አስጀምረዋል። ግን ለቁፋሮ ማሽን ማግኘት አልተቻለም።

በ2.5 ኪ.ሜ ርዝመት፣በ70 ሜትር ስፋት በ20 ሄክታር መሬት ላይ በሰው ኃይል ግንባታው እንደተሰራ ይነገራል፡፡
አቶ ኃይሌ ለውጤ #የዋካ ከተማ የቦታ አቀማመጧ ለከተማው ዕድገት ምቹ አይደለም ብለው በ1953 ዓ/ም ከተማው #ከዋካ ወደ ታርጫ እንዲከትም አድርገዋል።

ይሁን እንጂ ከተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች በደረሳቸው ተቃውሞ(በወቅቱ ታርጫ ለኑሮ አይመችም በሚል) 1 አመት ሳይቆይ በ1954 ዓ.ም ከተማው ከታርጫ ወደ #ዋካ ተመልሷል።
ለመጀመሪያ ጊዜ ቀድመው የራሳቸውን መኖሪያ ቤት ታርጫ ያሰሩ መሪም ነበሩ።የታርጫን ከተማ ቀድመው የከተሙና በከተማነት ደረጃ ያሰቡት አቶ ኃይሌ ለውጤ ናቸው። (በ1993 ዓ.ም አቶ ዳሮታ ዶጃሞ በይፋ ከተሙት።

የቀድሞ ታርጫ አየር ማረፊያ ለጥ ባለ ሜዳ ላይ የተገነባ ነበር። አልፎ አልፎ ድንጋዮችና ዛፎችም እንደነበሩበት ይነገራል፡፡አንበሳ፣ጎሽና ሌሎችም እንስሳት ነበሩበት። አባቶች እንደሚናገሩት ከሆነ በግንባታው ሂደት በወባ በሽታና በሌሎችም ጉዳቶች ብዙ መስዋዕትነት የተከፈለበት ብዙ የሰው ነፍስ የተገበረበት ጭምር እንደሆነ ይነገራል፡፡

በግንባታው ወቅት የመሬቱን ጨፌያማነት ለማስተካከል ሲባል ትላልቅ ድንጋይ/ቋጥኝ/ ሲያጋጥም በሰዓቱ ድንጋይ መስበሪያ እና ትላልቅ ድንጋዮችን ማውጫ ማሽኖች ባለመኖራቸው ያላቸው አማራጭ ድንጋዩን ወደ ውስጥ ከ4 ሜትር በላይ ቆፍሮና በእሳትና በመዶሻ የማፈረካከስ ሥራ መሰራቱን ይነገራል፡፡

ከብዙ ውጣ ውረድ መስዋዕትነትና ድካም በኋላ አባቶቻችንም ሳይሰለቹ ከ1945 - 1957 ለተከታታይ 12 አመት በስራ እንዳሳለፉ እና እንዳጠናቀቁ ይነገራል፡፡

ከ12 አመት ልፋትና ድካም ውጣ ውረድ በኋላ በአቶ አበበ ገብሬ የተጀመረው እሳቸው በሥራ ምክንያት ሲቀየሩ በአቶ ኃይሌ ለውጤ ተጠናቅቆ በ1957 ዓ/ም ህዝብ ተሰብስቦ ሲመረቅ ለመጀመሪያ ጊዜ ዳኮታ የሚትባል የፈረንሳይ ስሪት አእሮፕላን ታርጫ አየር ማረፊያ አርፋለች።

በ1957 ከተመረቀ በኋላ ከታርጫ አየር ማረፊያ አውሮፕላኑ በ8 ብር ከጂማ ታርጫና ከታርጫ ጂማ አገልግሎት ይሰጥ ነበር፡፡ ዳኮታ አእሮፕላን 36 ወንበሮች ያሉት ስለነበር ተሳፋሪ ሲታጣ ከታርጫ እህል፣ቆዳ፣ማር፣ዶሮ፣እንቁላል፣ቅቤ የመሳሰሉትን ይጭን ነበር። ካልሞላ ድንጋይም ይጭን ነበር ይባላል።ከአዲስ አበባና ጂማ የእርሻ መሳሪያ፣ አቡጀዲ(ልብስ)፣ ጨው የመሳሰሉትን ያመጣ እንደነበር ይነገራል፡፡

አገልግሎቱ እየተስፋፋ ሲመጣ በሳምንት ማክሰኞ እና ሐሙስ በተጠቀሰው በቀን 2 ዙር ከአ/አ ተነስቶ ጂማ፣ ታርጫ፣ሶዶ አገልግሎት ይሰጥ እንደነበር ይነገራል፡፡ተጓዦችም ከአእሮፕላን ወርደው ወደ #ዋካ/የአውራጃ ከተማ/ በበቅሎና ፈረስ ይሄዱ ነበር።ከመጀመሪያዎቹ የአየር መንገድ ተቀጣሪዎች መካከል ለአብነት ያህል አቶ ወራቦ ወጁ/ነፍስ ይማር/፣አቶ ከፍትመር መንገሻ/ነፍስ ይማር/፣አቶ አክርሶ ...ወዘተ ይገኙበታል።

Terefe Dodicho እንደጻፈው።

‎ !‎‎መ/ር ዘሪሁን ለማ በትምህርት ዘርፍ ጠንካራ መሠረት ያላቸው መምህር እና የስነ_ልቦና ምሁር ናቸው።የትምህርታቸው ጉዞ እንደሚከተለው ነው፡ ‎‎1. ዲፕሎማ በእንግሊዝኛ ትምህርት (ከአዋ...
10/17/2025

‎ !

‎መ/ር ዘሪሁን ለማ በትምህርት ዘርፍ ጠንካራ መሠረት ያላቸው መምህር እና የስነ_ልቦና ምሁር ናቸው።የትምህርታቸው ጉዞ እንደሚከተለው ነው፡



‎1. ዲፕሎማ በእንግሊዝኛ ትምህርት (ከአዋሳ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ) - ሐምሌ 1፣ 1993 ዓ/ም
‎2. የመጀመሪያ ዲግሪ በTEFL (ከጅማ ዩኒቨርሲቲ) - 2001 ዓ/ም
‎3. ማስተርስ ዲግሪ በማማከር ሳይኮሎጂ (Counseling Psychology) (ከጅማ ዩኒቨርሲቲ) - 2008 ዓ/ም



‎ከ24 ዓመታት በላይ በትምህርት ዘርፍ ያካበዱት ልምድ አላቸው፣አገልግሎታቸው በሶስት ዋና ዋና የመምህርነት ደረጃዎች ተሰማርተው አገልግሏል።

‎1.በቀድሞ ማረቃ ባሁኑ ማሪ_ማንሳ ወረዳ ማሪ መለስተኛ ትምህርት ቤት (1994-1996 ዓ/ም)
‎2. በማረቃ ወረዳ ዋካ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (1997 ዓ/ም)
‎3. በታርጫ ከተማ አስተዳደር ታርጫ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (1998-2018 ዓ/ም) - ለ20 ዓመታት በእንግሊዝኛ መምህርነት እና የስነ ልቦና አማካሪ ሆነው አገልግለዋል።

‎ ፡

‎ከመደበኛ አገልግሎታቸው በተጨማሪ የትምህርት ራዕይን ለማስፋት በሚከተሉት መስኮች አስተዋፅዖ አድርገዋል፡

‎· በአርባ ምንጭ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ (ታርጫ ቅርንጫፍ) ለ6 ዓመታት የሳይኮሎጂ ትምህርት ኮንትራት መምህር ሆነው አግልግሏል።
‎· በዳውሮ ታርጫ ካምፓስ ለ8 ዓመታት በሳይኮሎጂ ትምህርት ሌክቸረር ሆነው አስተምሯል።

‎ ፡

‎መ/ር ዘሪሁን የትምህርት ጥራትን ለመጠገን በዳውሮ ዞን ውስጥ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች በመጓዝ ለተማሪዎች እና ለማህበረሰቡ ጠቃሚና አስፈላጊ ስልጠናዎችን ሰጥተዋል።ከነዚህም መካከል፡

‎· በጊዜ አጠቃቀም፣ በንባብ ስነ ዜዴ፣ በቴክኖሎጂ አጠቃቀም እና በፈተና አሰራር ላይ ያተኮሩ ስልጠናዎች ሰጥተዋል። በዚህ ስራቸው ምክንያት ከየወረዳው ብዙ ሽልማቶችን እና የምስጋና ደብዳቤዎችንም ወስደዋል።
‎· ለወጣቶች ስለ ሱስ አጥቂ አስከፊነት እና ነጻ መውጣት የሚመለከቱ በመልካም ስነ ምግባር ላይ የተመሠረቱ ስልጠናዎችን በመስጠት በማህበረሰቡ ውስጥ ከፍተኛ አስተዋፅዖ አድርገዋል።

‎በአጠቃላይ መ/ር ዘሪሁን ለማ በትምህርት እና በማማከር ስራ ላይ ብቻ ሳይሆን በፖለቲካ፣በማህበራዊ እና በኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ያላቸውን አቅም ሁሉ ለህዝብ፣ ለመንግሥት እና ለማህበረሰቡ በመቅረፅ እጅግ አመርቂ አስተዋፅዖ አድርገዋል።

‎በዚህ ታላቅ አገልግሎት እና በተሰማራባቸው ልምድ እና ክህሎት ምክንያት፣ በትናንትናው ዕለት ለታርጫ ከተማ አስተዳደር የከንቲባ ልዩ አማካሪ ሆነው በእጩነት ቀርበው በጉባኤው ሙሉ ድምጽ ሹመታቸው ጽድቀዋል።

ከዝምተኛው ልጅ ገፅ የተወሰደ

‎ለመ/ር ዘሪሁን ለማ በአዲሱ በተሰማሩበት ስራ ቦታ ፍሬያማ እና ውጤታማ የስራ ዘመን እንዲሆን እንመኛለን!
Zerihun Lemma
እናመሰግናለን

10/17/2025

አርፍዶ የሚነቃ ሰው በጣም ሲበዛ መጥሮ ነው።

በአዲስ አበባ አንድም የቢንጎ ማጫወቻም ሆነ የአረቄ መሸጫ ቤት መኖር የለበትም ተባለ፡፡ከዚህ በፊትም እነዚህ ቤቶች ከከተማው አንዲጠፋ መመሪያ ተሰጥቶ ነበር፤ ግን አሁንም ድረስ ቤቶቹ መኖራቸ...
10/17/2025

በአዲስ አበባ አንድም የቢንጎ ማጫወቻም ሆነ የአረቄ መሸጫ ቤት መኖር የለበትም ተባለ፡፡

ከዚህ በፊትም እነዚህ ቤቶች ከከተማው አንዲጠፋ መመሪያ ተሰጥቶ ነበር፤ ግን አሁንም ድረስ ቤቶቹ መኖራቸውና በስራ ላይ መሆናቸው ታውቋል ተብሏል፡፡

በአጭር ጊዜ ውስጥም የአዲስ አበባ ከተማ ከቢንጎ ማጫወቻ እና የአረቄ መሸጫ ቤት ነፃ እንዲሆን ይደረጋል መባሉን ሰምተናል፡፡

ይህንን ያለው የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ነው፡፡

ቤቶቹ እንዳይኖሩ ይደረጋል ያለው ተቋሙ ምክንያቴም ቤቶቹ የወንጀል ምክንያት በመሆናቸው ነው ብሏል፡፡

የቢሮው ሀላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ የቢንጎ ማጫወቻ እና በየመንደሩ ያሉ አረቄ ቤቶች የከተማው ወንጀል መፈልፈያ ቦታዎች ናቸው ብለዋል፡፡

ይህንን ማስፈፀም ያልቻሉ ሀላፊዎችም በቦታቸው አይቀጥሉም ብለዋል፡፡

ዘገባው የሸገር ሬዲዮ ነው

Address

Sellersburg, IN
47172

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when New Dawuro Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to New Dawuro Media:

Share