New Dawuro Media

  • Home
  • New Dawuro Media

New Dawuro Media አዳስ ነገር | ጠቃሚ መረጃወች | ማህበራዊ አገልግሎቶች

New Dawuro Media is ideal page to knew the history , culture and entire society of Dawro Zone.

የዳውሮ ዞን እጅግ ሰፊ የሆነ የቆዳ ስፋት ያለዉ ፤ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ ቅርሶች ባለቤት ፤ አኩሪ ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቋንቋ ያለዉ ዞን መሆኑን ለዓለም ህዝብ ማሳወቅ ፤ በተጨማሪም በየማህበራዊ መሰረቶች እና በመንግስታዊ መዋቅሮች የሚዲያ ሥራዎችን ተከታትሎ መረጃዎችን ለህዝብ ማድረስ እና በዳዉሮ ዞን ሆነ በዓለም ዙሪያ የሚታዩ ክስተቶችን ለቻናላችን ቤተሰቦቸ ማድረስ ቀዳሚ ስራችን ነዉ፡፡

ዳዉሮ ዞን ከኢትዮጵያ ዉብ ገፅታ ማሳያዎች አንዱ ነዉ፡፡ ዞኑ በደቡብ ክልል የሚገኝ

ሲሆን የዞኑ ዋና ከተማ ታርጫ ትባላለች፡፡ ታርጫ ገስጋሽ ነገር ግን በሚሌኒየሙ ከተወለዱ ከተሞች አንዷ ናት፡፡ ከሐዋሳ በ282 ኪ.ሜ ከአዲስ አበባ ደግሞ በሻሸመኔ አድርገዉ በወላይታ ሶዶ የሚጓዙ ከሆነ 455 ኪ.ሜ ከአዲስ አበባ በሌላኛዉ መንገድ በጅማ አርገዉ የሚጓዙ ከሆነ ደግሞ በ479 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚያገኟት ከተማ ስትሆን ከተማዋ በየግዜዉ እያስመዘገበች ባለዉ እድገት ሳቢያም የብዙዎችን ትኩረት ስባለች፡፡

በደቡብ ከጋሞ ጎፋ በምዕራብ ከኮንታ ልዩ ወረዳ በሰሜን ምዕራብ ከኦሮምያ ክልል በሰሜን እስከ ሰሜን ምስራቅ ከከንባታ ጠንባሮ ዞን በምስራቅ ከወላይታ ዞን ይዋሰናል፡፡ ከሰሜን ምዕራብ እስከ ደቡብ ጫፍ ድረስ በጎጀብና በኦሞ ወንዞች ተፋሰስ የተከበበዉ ..

  💪💪 🌴🍀🌱🌴☘️🍀🌿🍃🎋🍀🌱🌴🎄🌲🌿በታርጫ ከተማ የአንድ ጀንብር የችግኝ ተከላ መርሀ-ግብር ‘‘በመትከል ማንሰራራት’’ በሚል መርህ ቃል እየተከናወነ ይገኛል።የ2017 ዓ.ም የሁለተኛ ዙር አረን...
31/07/2025

💪💪 🌴🍀
🌱🌴☘️🍀🌿🍃🎋🍀🌱🌴🎄🌲🌿
በታርጫ ከተማ የአንድ ጀንብር የችግኝ ተከላ መርሀ-ግብር ‘‘በመትከል ማንሰራራት’’ በሚል መርህ ቃል እየተከናወነ ይገኛል።

የ2017 ዓ.ም የሁለተኛ ዙር አረንጓዴ አሻራ የአንድ ጀንብር ተከላ መርሀ-ግብር ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም በታርጫ ከተማ አስተዳደር የደን ፣ ጥምር ደንና ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸዉ ችግኞች ተከላ እየተከናወነ ይገኛል።

በከተማ አስተዳደር የታርጫ ከተማ ወጣቶች በነቂስ በመውጣት በሳዳም ተራራ አሻራቸውን በማሳረፍ ላይ ይገኛሉ።

እቅዳችን ይሳካል፣ ሀገራችንም ይለማል!
🌿🌴🌱🍀☘️🍃🎋🌲🌳☘️🍀🌿

የ2018 የትምህርት ዘመን ውጤታማ እንዲሆን የትምህርት አመራርና ባለድርሻ አካላት በልዩ ትኩረት መስራት አለባቸው፦ አቶ ማስረሻ በላቸው‎‎"የጋራ ርብርብ ለላቀ የትምህርት ጥራት" በሚል መሪ ...
30/07/2025

የ2018 የትምህርት ዘመን ውጤታማ እንዲሆን የትምህርት አመራርና ባለድርሻ አካላት በልዩ ትኩረት መስራት አለባቸው፦ አቶ ማስረሻ በላቸው

‎"የጋራ ርብርብ ለላቀ የትምህርት ጥራት" በሚል መሪ ቃል የክልሉ ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የትምህርት ሴክተር ንቅናቄ መድረክ በታርጫ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

‎በመድረኩ የተገኙት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው ሀገር የሚገነባው ጥራት ባለው የትምህርት ስርዓት መሆኑን ተናግረዋል።

‎ባለፉት በርካታ ዓመታት ለትምህርት ተደራሽነት የተሰራውን ያህል ለትምህርት ጥራትና ፍትሐዊነት ባለመሰራቱ ተጠባቂ ውጤት ባለመገኘቱ የለውጡ መንግስት የትምህርት ዘርፉን የማሻሻል ስራ እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

‎በክልሉ የትምህርት ጥራት ለማረጋገጥና የትምህርት መሠረተ ልማት ለማሻሻል በተከናወነ ስራ ተጨባጭ ውጤቶች መገኘታቸውንም ተናግረዋል።

‎በ2017 የትምህርት ዘመን የታዩ ክፍተቶችን በማረም የ2018 የትምህርት ዘመን ውጤታማ ለማድረግ የትምህርት አመራርና ባለድርሻ አካላት በልዩ ትኩረት መስራት እንዳለባቸውም ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል።

‎በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አልማው ዘውዴ በበኩላቸው በ2017 የትምህርት ዘመን የተሻሉ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።

‎መንግስት የትምህርት ጥራቱን ለማሻሻል በርካታ የትምህርት ፖሊሲዎችን በማሻሻሉ ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆናቸውን አቶ አልማው ተናግረዋል።

‎በክልሉ መንግስት የትምህርት መሠረተ ልማት ማሻሻል፤ የመጽሐፍ ህትመት፤ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታን ጨምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ ፋይዳ ያላቸው ተግባራት መከናወናቸውንም አቶ አልማው ተናግረዋል።

‎የ2018 የትምህርት ዘመን ውጤታማ እንዲሆን በበጀት ዓመቱ የታዩ ክፍተቶች በማረም በቁርጠኝነት መስራት እንደሚያስፈልግ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

‎በንቅናቄው የክልሉ ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የትምህርት ሴከተር ንቅናቄ ሰነድ በክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ በዶ/ር ደስታ ገነሜ እየቀረበ ይገኛል።

‎በመድረኩ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸውን ጨምሮ የክልል፤ የዞን፤ የወረዳና የከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፤ የትምህርት አመራሮችና ባለድርሻ አካላት እየተሳታፉ ይገኛሉ።

30/07/2025

ሳይኮሎጂ ምን ይላል?

29/07/2025
 ካልታሰበ አደጋ ፈጣር ይጠብቀን/ቃችሁ!"ድንገት ከዕለታት አንድ ቀን ምን እንደምንሆን አስባችሁ ታውቁ ይሆን"?በእርግጥ ሙሉ ጤንነት ሃብት ዕውቀት ጉልበት እያለን አስበን ላናወቅ እንችል ይሆ...
29/07/2025


ካልታሰበ አደጋ ፈጣር ይጠብቀን/ቃችሁ!

"ድንገት ከዕለታት አንድ ቀን ምን እንደምንሆን አስባችሁ ታውቁ ይሆን"?

በእርግጥ ሙሉ ጤንነት ሃብት ዕውቀት ጉልበት እያለን አስበን ላናወቅ እንችል ይሆናል። በህይወታችን የእሳት ቃጠሎ አይነት አደጋ አይድረሰን። እሳት ምንም አያስተርፍም።

በዕለት እሁድ በቀን 20/11/2017 ዓ.ም ከቀኑ 6:00 ገደማ ተርጫ ከተማ በተለምዶ ብሩህ ካፌ ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካቢብ የተነሳ ድንገተኛ የእሳት አደጋ በግምት ከአራት ሚልዮን ብር በላይ የሚጠጋ ሃብትና ንብረት በደቂቃዎች ውስጥ ወደ አመድ ተቀይሮ አይተናል።

በዚሁም የእሳት አደጋ አንድ የኤሌክትሮኒክስ ቤት ከነሙሉ እቃዎች፣ አንድ የኮስሞቲክስ ቤት ሙሉ በሙሉ እና ሁለት ክፍል ቤት በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ወደ አመድነት ተቀይሯል።

እጅግ በጣም የሚያሳዝን ክስተት ነው። ልብ ይበሉ አደጋው የደረሰባቸው ወንድሞቻችን በዚህን ሰዓት ከስራ ውጪ ናቸው። መግቢያ ቤት እንኳን የላቸውም። የልጅነት ሃብትና ንብረት በደቂቃዎች ውስጥ ከነሙሉ ልብስና ጫማ ጭምር አጥተዋሉ።

ወድ ወገኖች በሃገር ውስጥም ከሃገር ዉጪም ያላችሁ ፈጣሪ ካልታሰበ አደጋ ይጠብቀን ይጠብቀን/ቃችሁ። ከድንገት ይሰውረን/ራችሁ! ከምንም ጊዜ በላይ የእኛን እጅ ይጠባበቃሉ። "ለወገን ደራሽ ወገን ነውና" በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን? የአቅማችሁን ያህል ተባበሩልን🤲 ያለዉን የሰጠ ንፉግ አይባልም! ''C'oraay C'uchchiide Wongiriya kuntsee''.

በጎነት ሐይማኖትን አይጠይቅም። ብሔርንና ጾታን አይለይም። በባህልና በእምነት አይወሰንም ብቻ "ሰውን ለመረዳት ሰው መሆንን ይጠይቃል"።

መልካም ተግባር ለመፈጸም ጊዜው አሁን ነው።
መስጠት ማለት ካለው ማካፈል እንጂ ስለተረፈው አይደለም። ለመስጠት ልቡ የፈቀደው👇

ለዚሁም በጎ ተግባር በተከፈተዉ ጣምራ/ በሦስት ሰው ስም የተከፈተው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደብተር ቁጥር ማገዝ ይችላል::



ሼር፣ ኮሜንት፣ በማድረግ ለልቤ ደጋጎች እናዳርስ🤲
በጎነት የህሊና ሥራ ነው። እውነተኛ ህሊና ያለው ሰው ያለገደብ ይሳተፋል።

ከላኩ በኃላ የባንክ screenshot በውስጥ መስመር ይላኩልን Mengistu Tofu Ficho Mengistu Tofu
Daniel Desta @ዝምተኛዉ ልጅ

29/07/2025


--------------
ልጅ አርሴማ ዜናው
ከዳውሮ ዞን ቶጫ ኪዳነምህረት ት/ት ቤት የተላከ። እርሶም የልጆትን ጣፋጭ አንደበት ለተወዳዱ የNDM ቤተሰቦች ያጋሩ በቴሌግራም 0917411711 ይላኩል። እኛም ለሚድያችን ቤቴሰብ እናጋራለን።

     !እንደ ሀሳብ ከሰሞኑን አንዳንድ አከባቢዎች ከተሞቻቸውን የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ ተግተው እየሰሩ ይገኛሉ። የእኛም የደቡብ ምዕራቧ ፈርጥ የሆነች ውብ ከተማችን ታርጫ ከሳዳም ተራራ ...
28/07/2025


!

እንደ ሀሳብ ከሰሞኑን አንዳንድ አከባቢዎች ከተሞቻቸውን የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ ተግተው እየሰሩ ይገኛሉ። የእኛም የደቡብ ምዕራቧ ፈርጥ የሆነች ውብ ከተማችን ታርጫ ከሳዳም ተራራ ስር መከተሟ ልዩ እድል ነው እና ታርጫችንን የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ የሳዳም ተራራ ደረጃ ፕሮጀክት እንዲጀመር እና በህብረተሰብ ድጋፍ እና በመንግስት ትብብር የሚገነባበት መንገድ እንዲመቻች ሀሳብ ለማንሳት እወዳለሁ።

ይህንን ሀሳብ የምትደግፉ ይህንን ፖስት በሼር ለብዙዎች እንዲዳረስ አግዙን።


!

28/07/2025

#ይብቃን !

 21 ሚሊዮን ችግኝ በአንድ ጀንበር በክልላችን ይተከላል።ሀሙስ ሐምሌ 24/ ዓ/ም  አይቀርም
28/07/2025



21 ሚሊዮን ችግኝ በአንድ ጀንበር በክልላችን ይተከላል።

ሀሙስ ሐምሌ 24/ ዓ/ም አይቀርም

28/07/2025

Address


47172

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when New Dawuro Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to New Dawuro Media:

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Contact The Business
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share