New Dawuro Media

New Dawuro Media አዳስ ነገር | ጠቃሚ መረጃወች | ማህበራዊ አገልግሎቶች

New Dawuro Media is ideal page to knew the history , culture and entire society of Dawro Zone.

የዳውሮ ዞን እጅግ ሰፊ የሆነ የቆዳ ስፋት ያለዉ ፤ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ ቅርሶች ባለቤት ፤ አኩሪ ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቋንቋ ያለዉ ዞን መሆኑን ለዓለም ህዝብ ማሳወቅ ፤ በተጨማሪም በየማህበራዊ መሰረቶች እና በመንግስታዊ መዋቅሮች የሚዲያ ሥራዎችን ተከታትሎ መረጃዎችን ለህዝብ ማድረስ እና በዳዉሮ ዞን ሆነ በዓለም ዙሪያ የሚታዩ ክስተቶችን ለቻናላችን ቤተሰቦቸ ማድረስ ቀዳሚ ስራችን ነዉ፡፡

ዳዉሮ ዞን ከኢትዮጵያ ዉብ ገፅታ ማሳያዎች አንዱ ነዉ፡፡ ዞኑ በደቡብ ክልል የሚገኝ

ሲሆን የዞኑ ዋና ከተማ ታርጫ ትባላለች፡፡ ታርጫ ገስጋሽ ነገር ግን በሚሌኒየሙ ከተወለዱ ከተሞች አንዷ ናት፡፡ ከሐዋሳ በ282 ኪ.ሜ ከአዲስ አበባ ደግሞ በሻሸመኔ አድርገዉ በወላይታ ሶዶ የሚጓዙ ከሆነ 455 ኪ.ሜ ከአዲስ አበባ በሌላኛዉ መንገድ በጅማ አርገዉ የሚጓዙ ከሆነ ደግሞ በ479 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚያገኟት ከተማ ስትሆን ከተማዋ በየግዜዉ እያስመዘገበች ባለዉ እድገት ሳቢያም የብዙዎችን ትኩረት ስባለች፡፡

በደቡብ ከጋሞ ጎፋ በምዕራብ ከኮንታ ልዩ ወረዳ በሰሜን ምዕራብ ከኦሮምያ ክልል በሰሜን እስከ ሰሜን ምስራቅ ከከንባታ ጠንባሮ ዞን በምስራቅ ከወላይታ ዞን ይዋሰናል፡፡ ከሰሜን ምዕራብ እስከ ደቡብ ጫፍ ድረስ በጎጀብና በኦሞ ወንዞች ተፋሰስ የተከበበዉ ..

 #እንሰት--------------የእንስት ምርቶችን(ቡላ:ቆጮ:ቃጫ) የማዘጋጀት ሂደት በዘመናዊ ሳይንስና ተክኖሎጂ የታገዘ ባለመሆኑ ሥራዉ አስቸጋሪና ከባድ ነዉ። እንሰትን ከመፋቅ ጀምሮ፣ ጨምቆ...
12/27/2025

#እንሰት
--------------
የእንስት ምርቶችን(ቡላ:ቆጮ:ቃጫ) የማዘጋጀት ሂደት በዘመናዊ ሳይንስና ተክኖሎጂ የታገዘ ባለመሆኑ ሥራዉ አስቸጋሪና ከባድ ነዉ። እንሰትን ከመፋቅ ጀምሮ፣ ጨምቆ እንዲሁም ቆሮጦ ቂጣ እስከመጋገር ድረስ ያሉ ሂደቶች በባህላዊ መንገድ የሚከወን በመሆኑ እናቶች ላይ የሚያደርሰዉ ድካም እና የስራ ጫና ከባድ በመሆኑ ሁሌም ያሳስባል።

በተወሰነ መልኩ የእንሰት ተዋጽኦ ማምረቻ መሳሪያዎችን ከባህላዊዉ በማሻሻል አዘምኖ ለህብረተሰቡ ለማስተዋወቅ የተሞከረ ቢሆንም መሳሪያዎቹ እምብዛም ችግር ፈቺ ባለመሆናቸዉ ዛሬም ነባሩን ቁሶች ለመጠቀም ተገዷል። ይህ ደግሞ ሥራዉን ጉልበት ጨራሽ አድካሚ ከማድረግ አልፎ በቆጮ ምርት ጥራት፣ ዋጋ እና በቆይታ ጊዜ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር እሙን ነዉ።

ከአድካሚዉ እንሰትን ፍቆ ከማጠናቀቅ ወዲያ ያለዉ ጭንቀት ደግሞ የተፋቀዉን በባክቴሪያ አማካይነት ለማብላላት (fermentation) የሚወስደዉ ረጅም ጊዜ ነዉ። በባህላዊ መንገድ ለማብላላት የሚጠቀሙት እርሾ( 'ጋማ') ፍቅፋቂዉን አብላልቶ ዝግጁ ለማድረግ ጊዜ ከመፍጀቱ ባሻገር በጥቃቅን ተህዋሲያን (microbes) መካከል ለአልሚ ምግቦች(nutrients) ና ለኦክሲጅን ሽሚያ መኖሩ፤ በዋናነት ደግሞ መጥፎ የቆጮ ጠረን መፍጠር፣ በተመጋቢዉ ዝቅተኛ ቅቡልነት እንዲኖረዉ ማድረግና አስፈላጊ የምግብ ንጥረ ነገሮች እንዲቀንሱ ያደርጋል።

እንግዲህ ወንድማችን Melesse Tadesse የምርምር ስራዉን እንዲሰራ ምክንያት የሆነዉ እላይ እንደጠቀስኩት በማላላት ሂደት የሚፈጀዉን ጊዜ በማሳጠር፣ የምርት ጥራቱ የተጠበቀ የተሻለ የምግብ ንጥረነገር ያለዉ ቆጮ እንዴት ማምረት እንደሚቻል የሚያትት ነዉ።

ለዚህም የተፋቀዉን እንሰት ለማብላላት የሚጠቅሙ ተሕዋሲያንን ለይቶ በማዉጣት በማብላላት ላይ የሚኖራቸዉን ሚና በመገምገም ዉጤቱን ከባህላዊ የማብላላት ሂደት ጋር በንጽጽሮሽ ለማስቀመጥ ሞክሯል።

በመጨረሻም የምርምር ግኝቱ(ዉጤቱ) እንደሚያሳየን በሳይንሳዊ መንገድ የተደረገዉ የማብላላት ሂደት፦
1ኛ በጣም አጭርና በ15 ቀን ተብላልቶ ለምግብነት ሊዉል የሚችል ቆጮ ማግኘት መቻሉን፣
2 የተሻለ ጠረን ያለዉ፡ በተመጋቢዉ የተሻለ ቅቡልነት ያለዉ ቆጮ ማግኘት መቻሉ፣
3 የምግብ ንጥረ ነገር ይዘታቸዉ ከባህላዊዉ መንገድ ጋር ሲነጻጸር ከፍ ያለ ፕሮቲን ይዘት ያለዉ መሆኑን መረዳት ተችሏል።

ዝርዝር የምርምር ሂደቱን፣ ዉጤትና ሪኮሜንዴሽኑን መመልከት ለሚፈልግ የሥራዉ ባለቤት( Meles Tadesse )ማግኘት ይችላል። ተመራማሪ የሆናችሁ ተጨማሪ ተዛማች ሥራዎችን ለመስራት የምትፈልጉ Contact ብታደርጉ።
Badege. w Feb 26/2022


ለመላው የዳውሮ ህዝብና ለታርጫ ከተማ ነዋሪዎች የቀረበ የልማት ጥሪ!የታርጫ ከተማ ከ90ሺህ በላይ ህዝብና መላው የኢትዮጵያ ብሔሮችና ብሔረሰቦችን አቅፋ የያዘች ከተማ ናት። ከተማችን ታርጫ የ...
12/27/2025

ለመላው የዳውሮ ህዝብና ለታርጫ ከተማ ነዋሪዎች የቀረበ የልማት ጥሪ!

የታርጫ ከተማ ከ90ሺህ በላይ ህዝብና መላው የኢትዮጵያ ብሔሮችና ብሔረሰቦችን አቅፋ የያዘች ከተማ ናት። ከተማችን ታርጫ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከብዙሃ ማዕከል ከተሞች አንዷና የማህበራዊ ክላስተር መቀመጫ ከተማ ናት።

ለታርጫ ከተማ እዚህ ደረጃ ለመድረስ በርካታ አባቶች፣ ሙሁራንና ነዋሪዎች ከፍተኛ መሰዋእትነት ከፍለዋል።

የታርጫ ከተማ ሜዳማና ለኑሮ ምቹ እንዲትሆን በከተማ ማስተር ኘላን በጠበቀ መልኩ መመሰረቷ እጀግ ተመራጭ ያደርጋታል። የታርጫ ከተማ ከክልል ከተማነትም በተጨማሪ የዞኑ መቀመጫና የታርጫ ዙርያ ወረዳ መቀመጫ ናት። የታርጫ ከተማ አራት ዋና ዋና መግቢያ በር ያላት ስትሆን ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ በከተማ ውሰጥ የተፈጠረው መነቃቃት ትልቅ ተሰፋ የሚጣልባት አድርጎታል።

በከተማ ውሰጥ አዲሱ የፓርቲ ኢንሼቲቭ የሆነውን የከተማ ኮሪደር ልማትና የከተማ ገጽታ ግንባታ ለማሰቀጠል ፣ከተማችን ታርጫ ለኑሮ ምቹና ተወዳዳሪ ስሉጥ (Smart City ) እንዲትሆን የከተማ መንግሥት እልህ አስጨራሽ ትግል እያደረገ ይገኛል።

የታርጫ ከተማ ከተክሌሀይማት እስከ ባህል ማዕከል እንዲሁም ከትልቁ ንግድ ባንክ እሰከ ታርጫ አጠቃላይ ሆስፒታል ድረስ ያለውን መንገድ ዳር ግራና ቀኝ የአረንጓዴ ልማት፣ የእግረኛ መንገድና የሳይክል መንገድ በተሳካ ሁኔታ ለመገንባት ከተማ አስተዳደሩ ወደ ሥራ ገብቷል።
የኮሪደር ልማት እንደ ታርጫ ከተማ አስተዳደር እስከ ዛሬ ደረሰ በበቂ ሁኔታና ሁሉም አከባቢ ባማከለ መልኩ ያልተጀመረ በመሆኑ በርካታ የቤት ሥራ ከፊት ለፊት የሚጠብቀን ይሆናል።

ስለሆነም መላው የዳውሮ ህዝብ ከጎናችን እንድቆም እንጠይቃለን።
በዛሬው ዕለት ሁሉ አቀፍ የኮሪደር ልማት ሥራን ለማሳካት የሀይማኖት አባቶች፣ የሃገር ባለውለታ አባቶች፣ ከሙሁራንና ከአልሚ ባለሀብቶች የተሳተፉበት የሀብት አሰባሳቢ ኮሚቴ በማዋቀር ሀብት የማሰባሰብ ዘመቻ በይፋ አስጀምረናል።

ስለሆነም መላው የዳውሮ ህዝብ፣ የዳውሮ ባለውለታዎች፣ የታርጫ ከተማ ነዋሪዎችና ከሀገር ውጭ የሚኖሩ የዳውሮ ተወላጆች ፣የንግዱ ማህበረሰብና ኢንቨስተሮች በእውቀት፣ በገንዘብና በምክር እንዲትደግፉ የታርጫ ከተማ መንግሥት ስም ጥሪዬን አቀርባለሁ።
ኑ የታርጫ ከተማ ሀሉአቀፍ ኮሪደር ልማት በጋራ እናልማ!!
እግዝአብሔር ኢትዮጵያውያንና ህዝቦቿን ይባርክ!
ታህሳስ 16/2018ዓ.ም
ታርጫ

12/27/2025

#ሴቶች

12/27/2025

?፧🤔

 !🇨🇭-----------------የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኀበር የዳውሮ ታርጫ ቅርጫፍ መድኃኒት መደብር  ቀድሞ አገልግሎት ከሚሰጥበት አድራሻ ለውጥ በማድረግ ለተገልጋይ እንዲቀርብ በማሰብ እ...
12/27/2025

!🇨🇭
-----------------
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኀበር የዳውሮ ታርጫ ቅርጫፍ መድኃኒት መደብር ቀድሞ አገልግሎት ከሚሰጥበት አድራሻ ለውጥ በማድረግ ለተገልጋይ እንዲቀርብ በማሰብ እና የህዝብ አስተያየት በመቀበል ወደ ታርጫ ጠቅላላ ሆስፒታል ቀረብ በማለት ከታርጫ ጠቅላላ ሆስፒታል ማህበረሰብ መድሀኒት መደብር ፊት ለፊት አገልግሎት መስጠት ጀምረናል።

ይምጡ ይገልገሉ!
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኀበር የዳውሮ ታርጫ ቅርጫፍ።

12/26/2025

#አትስገብገቡ አቶ ወርቁ አይተነው 👌
!

12/26/2025

!

12/26/2025


!

12/26/2025

አይደለም!

📘 200 ችግር | 200 መፍትሔየትዳርዎን ችግር በቀላሉ የሚፈታ መጽሐፍ!   | ከዚህ ቀደም “የትዳር ሐኪም” በማቅረብ በሺዎች የሚቆጠሩ ትዳሮችን ያዳነው👉 መልሕቅ የትዳር ማማከርና ማሰልጠኛ...
12/26/2025

📘 200 ችግር | 200 መፍትሔ
የትዳርዎን ችግር በቀላሉ የሚፈታ መጽሐፍ!

| ከዚህ ቀደም “የትዳር ሐኪም” በማቅረብ በሺዎች የሚቆጠሩ ትዳሮችን ያዳነው
👉 መልሕቅ የትዳር ማማከርና ማሰልጠኛ ተቋም
አሁን ደግሞ ከፍተኛ ዋጋ ያለው አዲስ ስጦታ ይዞላችሁ ቀርቧል!

🔑 በመጽሐፉ ውስጥ ምን ታገኛላችሁ?

✔️ በትዳር ውስጥ በተደጋጋሚ የሚከሰቱ 200 ችግሮች
✔️ ለእያንዳንዱ ችግር ተፈትኖ የተረጋገጠ መፍትሔ
✔️ በቀላል ቋንቋ፣ ተግባራዊ እና ቀጥተኛ መመሪያ

💰 ዋጋው?
🔥 200 ችግር – 200 መፍትሔ
🔥 በ200 ብር ብቻ!

➡️ ለእያንዳንዱ የትዳር ችግር መፍትሔ – በ1 ብር ብቻ!

📍 እንዴት ታገኙታላችሁ?
📞 0988 507070 ይደውሉ እና ይዘዙ

🏢 ስለሺ ሕንፃ – ቢሮ ቁጥር 504 በመሄድ በቀጥታ ያግኙ

ክፍት የሥራ ማስታወቂያ የጋሞ ልማት ማህበር ዋና ሥራ አስፈፃሚ  እና ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ቦታዎች ላይ ከታች የተቀመጡ መስፈርቶችን የሚያሟሉ ተወዳዳሪዎችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል:...
12/26/2025

ክፍት የሥራ ማስታወቂያ

የጋሞ ልማት ማህበር ዋና ሥራ አስፈፃሚ እና ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ቦታዎች ላይ ከታች የተቀመጡ መስፈርቶችን የሚያሟሉ ተወዳዳሪዎችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል::

ክፍት የሥራ ቦታዎች

1/የጋሞ ልማት ማህበር ዋና ሥራ አስፈፃሚ፣

2/የጋሞ ልማት ማህበር ምክትል ሥራ አስፈፃሚ የበጎ አድራጎት ዘርፍ ኃላፊ፣

3/የጋሞ ልማት ማህበር ምክትል ሥራ አስፈፃሚ የቢዝነስ ዘርፍ ኃላፊ፣

4/ በጋሞ ልማት ማህበር ምክትል ሥራ አስፈፃሚ ማዕረግ አስተዳደርና ፋይናንስ ኃላፊ

ቅድሚያ ለጋራ ልማት!
ታህሳስ 16/2018 ዓ/ም

https://www.facebook.com/100064550267419/posts/1336002995228030/

Address

Sellersburg, IN
47172

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when New Dawuro Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to New Dawuro Media:

Share