ዲንካ ቲዩብ

ዲንካ ቲዩብ News and media

10/14/2025
  ✍️በኢሠራ ባሌ ከተማ አስተዳደር የሚትገኘው የባሌ ብሩህ ተስፋ 1ኛ/ደ/ት/ቤት  #በእንግልዝኛ ት/ት ክፍል በዲፕሎማ ወይም በዲግሪ የተማሩ እጩ መ/ር ውጤት ከ 2.6 እና በላይ የያዘዉን ...
10/12/2025


✍️በኢሠራ ባሌ ከተማ አስተዳደር የሚትገኘው የባሌ ብሩህ ተስፋ 1ኛ/ደ/ት/ቤት #በእንግልዝኛ ት/ት ክፍል በዲፕሎማ ወይም በዲግሪ የተማሩ እጩ መ/ር ውጤት ከ 2.6 እና በላይ የያዘዉን ለመቅጠር ይፈልጋል።
እነሆ ብቅ ይበሉ!!!!
ብሩህ ተስፋ በተስፋ ትጠብቃለች።

 #ሼርበጨንቻ ዙሪያ ወረዳ በዶኮ ዮይራ ቀበሌ ሱራ ሚፃ በሚባል ጎጥ፣ በሱራ ተራራ ሻዶ ካንቼ ተብሎ በሚጠራ ወንዝ ውስጥ ማንነታቸው ያልታወቁ አንዲት እናት ሞተው ተገኝተዋል ።ቢያንስ ዕድማቸው...
10/01/2025

#ሼር
በጨንቻ ዙሪያ ወረዳ በዶኮ ዮይራ ቀበሌ ሱራ ሚፃ በሚባል ጎጥ፣ በሱራ ተራራ ሻዶ ካንቼ ተብሎ በሚጠራ ወንዝ ውስጥ ማንነታቸው ያልታወቁ አንዲት እናት ሞተው ተገኝተዋል ።ቢያንስ ዕድማቸው እስከ 80 የሚገመቱ ናቸው። እባካችሁ ሼር በማድርግ ለወዳጅ ዘመድ አንድታደርሱ እንማፀናለን።

በቀን 21/01/2018 ዓ.ም
Daniel Makbel

የሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን የጀግንነት ታሪክ ዳግም በደማቅ ቀለም የተጻፈበት ነው - ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር)አዲስ አበባ፣ መስከረም 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ‌‎የደቡብ ምዕራብ ኢትዮ...
09/19/2025

የሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን የጀግንነት ታሪክ ዳግም በደማቅ ቀለም የተጻፈበት ነው - ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር)

አዲስ አበባ፣ መስከረም 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ‌‎የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር) ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን የድል እና የጀግንነት ታሪክ ዳግም በደማቅ ቀለም የተጻፈበት ነውአሉ።

የሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቅቆ መመረቁን አስመልክቶ ‘በኅብረት ችለናል’ በሚል መሪ ሀሳብ በቦንጋ ከተማ ክልል አቀፍ የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በሰልፉ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ግድቡ የጀግንነት ታሪክ የተጻፈበት የዘመናችን የብልጽግና አሻራ ነው ብለዋል።

‎በቅኝ ግዛት ህግ በሀብታችን እንዳንጠቀም ሲሰራብን የቆየ ቢሆንም ይህንን በመስበር የአንድነታችን ማህተም የሆነውን ሕዳሴ ግድብ በላብ እና በደም ጠብታ ዕውን አድርገናል ነው ያሉት።

በአንድነት ስንቆም ከመልማት የሚያግደን የለም ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ‎ኢትዮጵያ ግድቡን ዕውን ያደረገችው በኢትዮጵያ ጥቅም የማይደራደሩ መሪና ህዝቦችን በማፍራቷ እንደሆነ ተናግረዋል።

ህብረ ብሔራዊ አንድነትን አጠናክሮ በማስቀጠል ወደፊት ታላላቅ ፕሮጀክቶችን ዕውን ለማድረግ የሕዳሴ ግድብ መመረቅ ማሳያ መሆኑን አመልክተዋል።

‎የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ በበኩላቸው፤ የውጭ እና የውስጥ ፈተናዎችን በማለፍ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ለፍጻሜ ማብቃቷ ትልቅ ድል መሆኑን ገልጸዋል።

የካፋ ዞን ማህበረሰብ ለግድቡ ግንባታ ላደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበው፤ በሌሎች ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ላይ አንድነታችንን በማጠናከር ድጋፋችንን እናስቀጥላለን ብለዋል።

‎በፍሬው አለማየሁ

Natnael የሚያስመሰግን ድንቅ ተግባር ፈጽመሃል!🙏መሰከረም  07/2018 ዓ.ምበደቡብ አሪ ወረዳ በመንድር ቀበሌ በእፎይታ ልማት ቡድን ላይ በአንዲት አርሶአደር ላይ የመብረቅ አደጋ ተከስቶ...
09/18/2025

Natnael የሚያስመሰግን ድንቅ ተግባር ፈጽመሃል!🙏

መሰከረም 07/2018 ዓ.ም
በደቡብ አሪ ወረዳ በመንድር ቀበሌ በእፎይታ ልማት ቡድን ላይ በአንዲት አርሶአደር ላይ የመብረቅ አደጋ ተከስቶ የህክምና እርዳታ እየሰጠሁዋት እገኛለሁ🙏

ለማህበረሰባችን ጥንቃቄ ይረዳ ዘንድ ከዝህ በታች ሳነብ ያገኘሁትን ተጋሩልኝ🙏🙏

ከመብረቅ አደጋ ራሳችንን እንዴት መጠበቅ እንችላለን?

በአብዛኛውን ጊዜ የዝናብ ወቅትን ተከትሎ በተለይም በክረምት ወራት የመብረቅ አደጋ ሲከሰት ይስተዋላል፡፡

ለመሆኑ መብረቅ ምንድነው? እንዴትስ ይፈጠራል? አደጋና ከአደጋው ማምለጫ መንገዱስ?

ለነዚህ ጥያቄዎች ተባባሪ ፕሮፌሰር ታደሰ ተረፈ ቀደም ሲል በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአትሞስፌሪክና ኦሺየኒክ ሳይይንስ መምህር የነበሩና የዘርፉ ተመራማሪ ምላሽ አላቸው፡፡

መብረቅ የሚፈጠረው ኤሌክትሮኖች ወደ ላይ እና ወደ መሬት በሚንቀሳቀሱበት ጊዜ ነው፡፡እንቅስቃሴያቸው ኃይል ስለሚፈጥር አየሩን በከፍተኛ ደረጃ ያሞቀዋል፡፡ የመብረቅ ሙቀት እስከ 30 ሺህ ዲግሪ ሴልሺየስ ሊደርስ ይችላል፡፡

በዚህ ጊዜ ከፍተኛ ድምጽና ብልጭታ ይፈጠራል፡፡ ብልጭታውን ቀድመን አይተን ዘግየት ብሎ ድምጹ ይሰማል፡፡

ታዲያ ኤሌክትሮኖች ወደ ደመናው እና ወደ ምድር ሲጓዙ ከአካባቢው ከፍ ያለ ኤሌክትሪክ አስተላላፊ መሆን የሚችልን እንደ ተራራ፣ዛፍ፣ ከአካባቢው ከፍ ያለ ህንጻ፣ ባዶ ሜዳ ላይ ከፍ ብሎ የተገኘ ሰውም ቢሆን ሲያገኙ እሱን እንደአስተላላፊ ይጠቀሙበታል፡፡

አደጋው የሚከሰተው በዚህ ጊዜ ነው፡፡ አንድ ሰው ወይም ሌላ ነገር በመብረቅ ተመታ የሚባለው ከፍተኛ ሙቀት ያለው የኤሌክትሪክ ሞገድ በሰውነቱ ሲገባ ነው፡፡

በመብረቅ መመታት ለሞት የሚያበቃ ትልቅ አደጋ ነው፡፡እንደ ዘርፉ ባለሙያዎች ገለጻ መብረቅ ዝናቡ ከሚጥልበት እስከ አስር ማይል ርቀት ጉዳት ሊያደርስ ይችላል፡፡

ለመሆኑ ከመብረቅ አደጋ ራሳችንን እንዴት መጠበቅ እንችላለን?
በዝናብ ወቅት የቤት በርና መስኮትን መዝጋት፣ ከከፍታ ቦታ መራቅ፣ በመኪና ውስጥ ከሆኑ ዘጋግቶ መቀመጥ፣ ሜዳ ላይ ለብቻ አለመገኘት ከመብረቅ አደጋ ራስን ለመጠበቅ ያስችላል፡፡

መብረቅ ወደ የኤክትሪክ ገመድ ገብቶ ተጨማሪ የኤሌክተሪክ ፍሰት በመጨመር ኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን ሊያቃጥል ይችላል፡፡ ስለዚህ ሬጉሌተር መግጠም ወይም በመብረቅ ሰዓት ሶኬቶችን መንቀል እንደሚያስፈልግ ተገልጿል፡፡

ህንጻዎች እንዳይመቱ አናታቸው ላይ የብረት ገመድ ተዘርግቶ አንዱን ጫፍ ወደመሬት በመቅበር መከላከል እንደሚቻል ባለሙያው ማብራሪያ ሰጥተዋል ፡፡

በድንገት አንድ ሰው በመብረቅ ቢመታ በፍጥነት ራቁቱን መሬት ላይ ማስተኛት ወይም አንገቱ ሲቀር መሬት ውስጥ መቅበር ሳይንሳዊ መድህን መሆኑን ይነገራል፡፡ በተጨማሪም የጤና ባለሙያ ክትትል ያስፈልጋል፡፡

የአሜሪካ የበረራና የጠፈር አስተዳደር (ናሳ) መረጃዎ በመብረቅ አደጋ በዓለም ላይ በየዓመቱ በአማካኝ 24 ሺህ ሰዎች ሕይወታቸውን ያጣሉ፤ እስከ 240 ሺህ ሰዎች ደግሞ ጉዳት ይደርስባቸዋል፡፡

Via EBC

ባደረገንላት የህክምና እርዳታም ከፈጣሪ እገዛ ጋር እናታችን በጥሩ ጤንነት ላይ ትገኛለች 🙏🙏ክብር ለከበረው ጌታ ይሁን

ከናትናኤል ገጽ ላይ ያገኘሁት መረጃ ነው።

የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ምርቃት በምስል
09/17/2025

የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ምርቃት በምስል

🤔🤔🤔የስራችሁን ይስጣችሁ😂😂😂
08/08/2025

🤔🤔🤔የስራችሁን ይስጣችሁ😂😂😂

በታርጫ ከተማ በሁለት የንግድ ሱቆች የተከሰተውን የእሳት አደጋ በህብረተሰብ ተሳትፎ መቆጣጠር ተችሏል።በዛሬው ዕለት ልክ ከቀኑ 6:00 አከባበር በኮሬ መሰመር በሁለት የንግድ ሱቆች የተከሰተው...
07/27/2025

በታርጫ ከተማ በሁለት የንግድ ሱቆች የተከሰተውን የእሳት አደጋ በህብረተሰብ ተሳትፎ መቆጣጠር ተችሏል።

በዛሬው ዕለት ልክ ከቀኑ 6:00 አከባበር በኮሬ መሰመር በሁለት የንግድ ሱቆች የተከሰተው የእሳት አደጋ በወጣቶች፣ በከተማ ነዋሪዎች ተሳተፎ መቆጣጠር መቻሉ ተገልጿል።
የታርጫ ከተማ መንግሥት የከተማ ወጣቶችንና ለአከባቢ ማህበረሰብ ልባዊ ምስጋና ያቀርባልስለ የከተማ መ/ኮ/አሳውቋል

ብዝኃነትን ከእምቅ የተፈጥሮ ሀብት ጋር ያጣመረው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል************* ኅዳር 14 ቀን 2014 ዓ.ም የተመሰረተው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በድንቅ ተፈጥሮ...
07/24/2025

ብዝኃነትን ከእምቅ የተፈጥሮ ሀብት ጋር ያጣመረው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል
*************

ኅዳር 14 ቀን 2014 ዓ.ም የተመሰረተው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በድንቅ ተፈጥሮ የታደለ እና በርካታ ብሔሮች የሚገኙበት የትንሿ ኢትዮጵያ አምሳል ነው።

ከፋ፣ ሸካ፣ ኮንታ፣ ቤንች ሸኮ፣ ዳውሮ እና ምዕራብ ኦሞ በክልሉ የሚገኙ ዞኖች ሲሆኑ፣ በእነዚህ ዞኖች የሚገኙ ብሔሮች የኢትዮጵያ ጌጦች ናቸው።

በእምቅ ተፈጥሮ ሀብቱ የሚታወቀው ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የታላላቅ የኃይል ማመንጫ ግድቦች እና የቱሪስት መዳረሻ ነው።

በዳውሮ እና በኮንታ መካከል የሚገኘው እና በርካታ አጥቢ የዱር እንስሳትን በውስጡ የያዘው የጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ ያለው በዚሁ ክልል ሲሆን፣ ፓርኩ በውስጡ ከያዛቸው እንስሳት መካከልም የአፍሪካ የዝሆን፣ ጎሽ፣ ከርከሮ፣ ሳላ እና እንደ አጋዘን ያሉ የዱር እንስሳት እንዲሁም ብርቅዬ የወፍ ዝርያዎች ይገኛሉ።

በክልሉ ያለውን የቱሪዝም ሀብት በጥቅም ላይ ለማዋል በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በገበታ ለሀገር ፕሮጀክት ታላቁ የሃላላ ግንብን ተተንተርሶ የተገነባው የሃላላ ኬላ እና የጨበራ ጩርጩራ የዝሆን ዳና ሎጅ የሚገኙት በዚሁ አስደናቂ ክልል ነው።

የኦሞ ብሔራዊ ፓርክ በክልሉ የሚገኝ ሌላው የኢትዮጵያ በረከት ሲሆን፣ 75 አጥቢ እንስሳትን እና 325 የአዕዋፍ ዓይነቶችን እንደያዘ መረጃዎች ያመላክታሉ።

ኦሞ ብሔራዊ ፓርክ፣ ውድንቢዎች፣ የመጋላ ቆርኪ፣ ሳላዎች፣ የሜዳ ፍየሎች እና ሌሎም አጥቢዎች የሚገኙበት የክልሉ በረከት ነው።

ጊቤ አና ኦሞ ወንዞችን ወደ ቱርካና ሀይቅ የሚሸኘው ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ከግልገል ጊቤ በሚያመነጨው ኃይል ኢትዮጵያን እያበራ የሚገኝ ሲሆን፣ ቀጣይ የኢትዮጵያ የልማት አቅም የሆኑት የኦሞ እና ጎጀብ ወንዞችን በጉያው ይዟል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቅርብ ክትትል የሚያደርጉበት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ቀጥሎ ግዙፍ የሆነው ኮይሻ የኃይል ማመንጫ ግድብ መገኛ የሆነው ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የመጪው ጊዜ የኢትዮጵያ ብርሃን መፈንጠቂያ ነው።

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን "ኢቢሲ ወደ ይዘት" በሚለው እንቅስቃሴው ተጨማሪ የይዘት ምንጭ የሆነውን የታርጫ ስቱዲዮ በዚህ አስደናቂ ክልል ሥራ አስጀምሯል።

ስቱዲዮው የክልሉን ብዝኃ እና እምቅ የተፈጥሮ ሀብት ለመላው ኢትዮጵያ ለማስተዋወቅ የሚሠራውን ሥራ በእጅጉ የሚያግዝ ይሆናል።

#ታርጫ #ኢትዮጵያ #ዳውሮ

🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 እንኳን ደስ አላችሁ/እንኳን ደስ አለን!!!*********************************በነገው ዕለት በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ አዲስ ታሪክ ይሰራል! የኢትዮጵያ ብሮድ...
07/23/2025

🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
እንኳን ደስ አላችሁ/እንኳን ደስ አለን!!!
*********************************
በነገው ዕለት በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ አዲስ ታሪክ ይሰራል! የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (EBC) ዘመናዊ ስቱዲዮ በከፍተኛ የፈደራልና የክልል የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የብሮድካስት ባለስልጣናት ፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና መላው የዞናችን ህዝቦች በተገኘበት በይፋ ይመረቃል።

ይህ ስቱዲዮ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያን ድምፅ ከፍ አድርጎ የሚያሰማ፣ የክልላችንን ባህልን፣ታሪክና እሴትን እንድሁም የክልላችንን እምቅ አቅሞችን ለዓለም የሚያስተዋውቅ ታላቅ የድል ምዕራፍ ነው።

የታርጫ ከተማ አስ/ር የዚህን የስኬት ደስታ እያበሰረ ሁሉም የከተማችን ነዋሪዎች ነገ ከጠዋቱ 1:30 ላይ በዳውሮ ባህል ማዕከል ፊት ለፊት ባለው አደባባይ በመገኘት የደስታው ተካፋይ እንድሆኑ ጥሪ ያስተላልፋል።

Address

South Padre Island, TX
1221

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ዲንካ ቲዩብ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ዲንካ ቲዩብ:

Share