RN05 ከኢትዮጵያ እና ዲያስፖራ የሚተላለፍ ሚድያ!
አዲሱን ዩቱብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ:
https://www.youtube.com/c/RN05channel

https://t.me/RNZeroFive

https://rnzerofive.com/

07/26/2025

🔻ህዝበኝነት ወይንስ መርህ?!
~~~~~~~~~

"populist" ወይንም "ህዝበኛ" የሆኑ ፖለቲከኞች በሁሉም አለም አሉ፡፡ ከብዙ መገለጫዎቻቸው በጥቂቱና በአጭሩ ወገንተኝነታቸው ለመርህና ለተመሳሳይ ሚዛን ሳይሆን ሕዝብን የሚያስቀድሙና ሁሉንም ለህዝብ የሚያደርጉ መስለው መታየትን ይወዳሉ፡፡ ከህዝብ ግብረመልስ የማያሰጣቸው ከሆነ ግዴታቸዉም ቢሆን አያደርጉትም>>ይልቅ የህዝብን ሥስ ልብ በመፈለግ ትኩረት የሚያሰጣቸው ሆኖ ከተገኘ ከመርህ ጋር ቢጋጭም ከማድረግ አይመለሱም፡፡ ምንም መርህን የሚቃረን ቢሆን እንኳ ህዝቡ ትኩረት ይሰጣቸዋል ወይንም ክብር ይሰጣቸዋል በሚሉት ጉዳዮች ላይ መገኘትን ያዘወትራሉ፡፡ ይህ ማለት አሁን አሁን ተዉት እንጂ ጠ/ሚ አብይ አህመድ populist ወይንም ህዝበኛ በነበሩበት የመጀመርያዎቹ አመታት ስልጣናቸው ወቅት የእያንዳንዱን ዜጋ ለቅሶ ካልደረስኩ፣ የህዝቡን ሰርግ ተገኝቴ ካልባረኩ ወይንም ካልበላሁ, አልያም በየመንገዱ ላይ ከሰዉ ጋር ፎቶ ካልተነሳሁ ወዘተ እያሉ በህዝቡ መሃል ለመታየት ሲጥሩ እንደነበረው ማለት ነው፡፡ ያንን ያደርጉ የነበረው ህዝብን የመውደድ መርህ ኖሯቸው ሳይሆን መስለው በመታየት ህዝበኝነታቸዉን ማጉላት ስለነበረባቸው ነው፡፡ ያ አካሄድ መርሃዊ ስላልነበረ አሁን ሲያደርጉት አይስተዋሉም፡፡
ለቁልቢ ገብሬል ክብረ በአል ወደ ድሬዳዋ ያቀኑትን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሊቃነ ፓፓሳትን የድሬዳዋው ከንቲባ ራሳቸው ተቀብለው፣ በራሳቸው መኪና ጭነው ከመዉሰዳቸዉም በላይ ቪድዮዎ ቆረጥ እያደረጉ እያዩ ቆመው እየመረቁና እያበረታቱ ቴምርና ዉሃ ሲያከፋፍሉ የተቀረጹትን ቪድዮዎ በማህበራዊ ሚድያ ላይ እየተዘዋወረ ብዙ ጭብጨባና ሙገሳ አስገኝቶላቸዋል፡፡
ብዙዎች ታድያ "ይህ ምን ችግር አለው? እንዴትስ ህዝበኛ ያሰኛቸዋል?" እያላችሁ ይሆናል፡፡ በመሰረቱ ይህ ብዙ አይገርምም! በተለይ ሙስሊም በዝ በሆኑ የሃገራችን ክፍሎች እንዲህ አይነቱን ነገር ማየት የተለመደ ፣ ወይንም የሚጠበቅ ፣አልያም ግድ የሆነ የሚመስልባቸው ብዙ አጋጣሚዎችን አይተናል፡፡ በርግጥም ለመከባበርና ለመቀራረብ ሁሌም ምሳሌ የምናደርገው ክርስትያን በዝ የሆነዉን የሰሜኑን የሃገራችንን ክፍል ሳይሆን ሙስሊም በዝ የሆኑትን የደቡብ, የደቡብ ምእራብና፣ የምስራቅ የሃገራችንን ክፍሎች ነው፡፡ ይህ ድርጊት የሚገርመው የሙስሊሙ መሪዎችን የትግራይ አልያም የአማራ ክልል መሪዎች ተቀብለው በዚህ መልክ ቢያስተናግዱ ነበር እንጂ ያኛው የሚጠበቅ ነው፡፡
ነገሩ ግን ወዲህ ነው፡፡ የድሬዳዋ ከንቲባም ሆነ የሙስሊም በዝ ክልሎች ፕሬዝዳንቶችና ባለስልጣኖቻቸው ተመሳሳይ ድርጊቶችን የሚፈጽሙት በመከባበር መርህ ስለሚያምኑ ሳይሆን የራሳቸዉን ቆዳ ለማዋደድ ህዝበኛ ወይንም populist ሆነው ነው፡፡ ለዚህም ሌላው ማሳያ ያኔ ህዝበኛ ሳሉ ቀጣዩ ንጉሳችን ሲባሉ የነበሩት የሶማሌ ክልሉ ሙስጠፌን ማንሳት ይቻላል፡፡ እነዚህ ሰዎች እዉነት በመከባበር መርህ የሚያምኑ ቢሆኑ ኖሮ በሰሜኑ የሃገራችን ክፍሎችም ሆነ በሌሎች የሀገራችን ከተሞችና ገጠሮች በተቃራኒው የሚጣሱ የሃይማኖት ጭቆናዎች እንቅልፍ የሚነሷቸዉና የሚረብሻቸው ስለሚሆኑ እንዲሁም ከመርሃቸው ጋር ስለሚጋጭ በፍጹም ሊቀበሉት የማይችሉት ጉዳይ በመሆኑ ያላቸዉን ስልጣንና ግንኙነት ተጠቅመው የክልል መሪዎችንና አስተዳደሮችን በመወትወት እንዲስተካከል ሲሰሩ እናያቸው ነበር፡፡
ከዚህም አልፎ በተለይ በአክሱምና በላሊበላ ሙስሊሙ የሃይማኖትም ሆነ የዜግነት መብቱን በመቀማት ዋነኛ ሚና ያላትን ቤተክህነት ፓፓሳት እግር ስመው ከተቀበሉ በኋላ ዉሃና ቴምር ሰጥተው ወይንም ቤተክርስትያን አድሰዉና አሸብርቀው ከማስረከብና ከመሸኘት ባሻገር ሙስሊሙን "መስጂድ አትሰራም ፣ የቀብር ቦታ አይገባህም ወዘተ" እያሉ ለዘመናት የመጨቆንና የማንገላታት መሰረቱ ቤተክህነታዊ ስለሆነ ይህንን ስህተት በማረቅ የተሻለ መከባበር እንዲኖር የአቋም ለዉጥ እንዲያመጡ በማግባባት ሚናቸዉን ይወጡ ነበር፡፡ የህዝበኝነት ሳይሆን የመርህ ቢሆን ኖሮ ታዳጊ ሴት ተማሪዎች በሂጃባቸው ሰበብ ትምህርት ሲከለከሉ ድምጻቸዉን በሰማን ነበር፡፡ ነገር ግን ያንን ለማድረግ ፕሮቶኮላቸው የማይፈቅደዉና ሌላኛዉን ለማድረግ የሚችሉት ጉዳዩ የመርህ ሳይሆን የህዝበኝነት ስለሆነ ነው፡፡
ጉዳዩ ሃይማኖትን የማክበር, የመቻቻል ምሳሌ የመሆን ቢሆን ኖሮ አክሱምን፣ ላሊበላንና እንዲሁም ሌሎች የጭቆናና የአፓርታይድ መናኸርያ የሆኑ ከተሞችን በመጎብኘት ሙስሊሙ ያለበትን ሁኔታ በተጨባጭ ባዩ ነበር፡፡ እናም ይህ የሙስሊም በዝ ከተሞች ባለስልጣናት የሚያሳዩት የተለየ አካሄድ ጥሩ ቢሆንም መሰረቱ ግን በእኔ ግምት ትኩረት ፈላጊነት populism (ህዝበኝነት) አልያም የበታችነት ስሜት ነው ፡፡ በነገራችን ላይ ይህ የህዝበኝነት አባዜ ከሌሎች ይልቅ በሙስሊሙ ባለስልጣናት፣ ምሁራንና ኤሊቶች ላይ በስፋት ይታያል ለማለት ነው:: ይሄው ነው!
*** የእርሶስ ምልከታ ምን ያለ ነው? ይጻፉና እስኪ እንየው!
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

07/25/2025

🚩መንገዶች ሁሉ ወደ ካይሮ ያመራሉ
👉ኢትዮጵያዊያኖች ግን ቀድመው ጋዛ ደርሰዋል!
~~~~~~~~~~~

በአሁኑ ሰአት ጋዛ በርሃብ እየወደቀች ነው፡፡ በጽዮናዊያኑ ፍጹም ጭካኔና የዘር ማጥፋት ብሎም ጀኖሳይድ ስራ የተበሳጨው የአለም ህዝብ የሚያደርገው ግራ በገባው በዚህ ወቅት ወደ 30 ሺ የሚጠጉ የአለም ዜጎች ከተለያዩ ሃገሮች ተቀናጅተው ወደ ካይሮ እየገቡ ይገኛል ፡፡ አላማቸዉም የራፋህን ድንበር አልፈው ወደ ጋዛ በመግባት ህይወትን መታደግ ነው፡፡ እዚያም ትንቅንቁ የሚጀምረው ከግብጽ መንግስት ጋር በመሆኑ ጉዟቸዉን ከግብጽ መንግስት ጋር በመግባባት ህጋዊ ለማድረግ እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ ይህም "የጋዛ የእግር ጉዞ አብዮት መጀመርያ" እየተባለ ይገኛል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ በደቡብ አፍሪካ በሚገኘው ነጃሺ ኢትዮ ኢስላሚክ ትረስት አማካይነት ለፍልስጤማውያን የጋዛ ነዋሪዎች ይደርስ ዘንድ የተሰባሰበ ገንዘብ በትክክል ለተረጂዎች ደርሶ አስፈላጊው የምግብና ሌሎች መሰረታዊ አቅርቦቶች ለህዝቡ መድረሱን ትረስቱ ለ አረጋግጧል።
ከቦታው በተላከ የቪዲዮና የምስል ማስረጃ መሰረት ለተራቡት የጋዛ ነዋሪዎች ምግብ ሲከፋፈል ከመታየቱም በላይ የምስጋና መልዕክቶችም ተላልፈዋል።
ከነጃሺ ኢስላሚክ ትረስት በተጨማሪ እዛው በደቡብ አፍሪካ ጆሀንስበርግ የሚንቀሳቀሰው የጆሀንስበርግ የሙስሊም ሴቶች የሰደቃ ጀምዓም ከአባላቶቹ በኩል ያሰባሰበው ዕርዳታ በመጀመርያው ዙር ተልኮ ለተረጂዎች ደርሷል።
ትረስቱ ማህበረሰቡን በማነሳሳት ትልቅና አመርቂ ስራ የሰራ ሲሆን ይበልጥ የዕርዳታው መድረስ የህዝቡን ተነሳሽነት ጨምሮታል። በአንድ ዙር የተጀመረው የዕርዳታ ማሰባሰብ ወደ 4 ዕርከን ከመሸጋገሩም ሌላ የህዝቡ መነሳሳት በመጨመሩ ለሌላ ዙር ተነሳሽነት እየታየ ያለበት ሁኔታም እየተስተዋለ ነው።
"በዚህ ስራ ላይ ነጃሺ ትረስት ህዝቡን በማነሳሳት ለዚህ ትልቅና በጎ ዓላማ በማስተባበሩ አላህ ምንዳቸውን ይክፈላቸው፣የደቡብ አፍሪካ ኢትዮ ሙስሊም ላደረገውም ትብብር ትልቅ ክብር ይገበዋል።" ሲል የትረስቱ አመራር ለ ክፍል ባስተላለፈው መልእክት ምስጋናዉን አቅርቧል፡፡

እንደ ትረስቱ ገለጻ ይህንን ለማሳካት ሂደቱ ቀላል እንዳልነበረና የተለያዩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን ማግኘትና ባለው ቀጭን መስመር ለማለፍ ጊዜና ከፍተኛ ትዕግስት አስፈልጎ ነበር፡፡

እኛም ይህ የሚመሰገን ተግባር የፈጸሙ በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ለሌሎችም አርአያ እንደሚሆኑ በማመን፣ ዛሬ ንጹሃን ጋዛዊያን ሆን ተብሎ በጦር መሳርያና በርሃብ በጅምላ እንዲያልቁ ሲደረግ ተቀምጬ አላይም በሚል ዘር፣ ሃይማኖትና አህጉር ሳይለየው በተለያዩ የአለማችን ክፍል ያለው ህዝብ በነቂስ ወጥቶ የሚችለዉን ለማድረግ በሚጥርበትና እንቅልፍ ባጣበት በዚህን ሰአት ኢትዮጵያዊያኖችም ድርጊቱን ከመጥላትና ከማዉገዝ ጀምረን የምንችለዉን በማድረግ ከንጹሃን ጋዛዊያን ጎን በመቆም ሰብዓዊነትን ከፍ በማድረግ ታሪክ ልንጽፍ ይገባል እንላለን!

*** የእርሶስ ምልከታ ምን ያለ ነው? ይጻፉና እስኪ እንየው!
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

🚩ፈረንሳይ ለፍልስጤም እውቅና ለመስጠት መወሰኗን ይፋ አደረገች!👉እስራኤል የማክሮንን ዉሳኔ ተቃዉማለች!!! ~~~~~~~~~~~  የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በጋዛ ያለውን ጦርነት ...
07/24/2025

🚩ፈረንሳይ ለፍልስጤም እውቅና ለመስጠት መወሰኗን ይፋ አደረገች!
👉እስራኤል የማክሮንን ዉሳኔ ተቃዉማለች!!!
~~~~~~~~~~~

የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በጋዛ ያለውን ጦርነት በአስቸኳይ ማቆም እና ሰብአዊ ቀውሱን ማቃለል እንደሚያስፈልግ በመጥቀስ ፈረንሳይ ለፍልስጤም እንደ ሀገር እውቅና እንደምትሰጥ በዛሬው እለት ሀሙስ እንደ ፈረንጆቹ ሃምሌ 24/ 2025 አስታወቁ። ይህንንም ዉሳኔያቸዉን ለፍልስጤሙ ፕሬዝደንት ማህሙድ አባስ ያሳወቁ ሲሆን ዉሳኔያቸዉን በመጪው መስከረም ወር በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ስብሰባ ላይ ይፋ እንደሚያደርጉ ነው ያረጋገጡት፡፡
ማክሮን ሀገራቸው ፈረንሳይ ለፍልስጤም የሃገርነት እውቅና ልትሰጥ እንደምትችል ጭምጭምታዉን ካሳወቁባቸው ያለፉት ወራትና ሳምንታት ጀምሮ የጦር ወንጀለኛ በሚል የተከሰሱት ናትያንያሁና የተለያዩ የእስራኤል ባለስልጣናት ማክሮን ላይ ከፍተኛ ነቀፌታ በማቅረብ ዉሳኔያቸዉን ለማስጣል ግፊት ሲያደርጉ መቆየታቸው ይታወሳል፡፡ ያም ሆኖ ማክሮን የእስራኤልን ቁጣ ወደ ጎን በመተው ዉሳኔያቸዉን አስተላልፈዋል፡፡
ማክሮን ይህንን ዉሳኔያቸዉን ይፋ ያደረጉት የእስራኤል ካቢኔ ዌስት ባንክን የእስራኤል አካል አድርጎ ለመጠቅለል ዉሳኔ ባሰተላለፈ ማግስት ነው፡፡
*** የእርሶስ ምልከታ ምን ያለ ነው? ይጻፉና እስኪ እንየው!
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

🔺ይህ ሚልዮኖች በፊልም እያዩ የሚያለቅሱበት የነገ ታሪክ ፣ግን ደግሞ የዛሬያችን እዉነታ ነው!~~~~~~~~~~~~ የሰሜን አፍሪካ ሃገራት ዜጎች በባዶ የሃይላንድ ላስቲኮች ሩዝና የተለያዩ ምግ...
07/24/2025

🔺ይህ ሚልዮኖች በፊልም እያዩ የሚያለቅሱበት የነገ ታሪክ ፣ግን ደግሞ የዛሬያችን እዉነታ ነው!
~~~~~~~~~~~~

የሰሜን አፍሪካ ሃገራት ዜጎች በባዶ የሃይላንድ ላስቲኮች ሩዝና የተለያዩ ምግቦችን እያሸጉ ወደ ጋዛ አቅጣጫ እየወረወሩ የሚያሳዩ ቪድዮዎች ብዙ ተመልካቾችን እየሳቡ ይገኛሉ፡፡ በምግብ የታሸጉ የሃይላንድ ላስቲኮችን ወደ ባህር ሲወረዉሩ ምኞታቸው ፈጣሪ ኖህን በጀልባ አንሳፎ ወደ ሚፈለገው ቦታ እንዳደረሰው ሁሉ ይህንንም ያደርስላቸው ዘንድ በመመኘት ነው፡፡
ይህንን ድርጊት ሲፈጽሙ ምግቡ ባይደርሳቸዉም ወይንም ደርሶ ብዙ ባይጠቅማቸዉም እንኳ መሪዎቻቸው ሊያደርጉት ያልቻሉት ወይንም ያልፈቀዱትን እነሱም እንደ ህዝብ በከበባው ምክንያት ማድረግ ያልቻሉትን በዚህ መንገድ ግዴታቸዉን ለመወጣት መገደዳቸዉን በመግለጽ ነው፡፡
*** የእርሶስ ምልከታ ምን ያለ ነው? ይጻፉና እስኪ እንየው!
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

🚩አለም የተጸየፋቸው፣ እነሱም አለምን ማየት የተጸየፉት ህጻናት! ይህ አለም ለህጻናት መብትና ለሰባዊነት ያለው መርህ ያደጉ ሃገራትና ከጽዮናዊያን አዉሮፓዊያን ዉጭ ሲሆን ከድስት መቀመጫ በባሰ...
07/24/2025

🚩አለም የተጸየፋቸው፣ እነሱም አለምን ማየት የተጸየፉት ህጻናት!
ይህ አለም ለህጻናት መብትና ለሰባዊነት ያለው መርህ ያደጉ ሃገራትና ከጽዮናዊያን አዉሮፓዊያን ዉጭ ሲሆን ከድስት መቀመጫ በባሰ መልኩ የተለበለበ፣ የታመቀና የጠቆረ ነው! ኢኚህ መብቶቻቸው ሁሉ ተወስደው በርሃብ እንዲረግፉ የተፈረደባቸው ህጻናት ለቀሪው ጨካኝ አለም ይህንኑ እያሳዩና "የድስጡን ጀርባ ትመስላላችሁ" እያሉን ይመስላል! ከነዚህ መሃል ስንቶቹ እንደረገፉ ማወቅ ኢጅግ ይከብዳል!

👉 ሰበር የትዝብት ዜና!~~~~~~~~~~~  የእስራኤሉ የዉጭ ጉዳይ ሚንስትር በዩክሬን ጉብኝት ላይ ሲሆኑ፣ ሩሲያ በዩክሬን በተለይ በሰላማዊ ዜጎች ላይ የምትፈጽመዉን ግድያ እንድታቆምና ወደ ...
07/23/2025

👉 ሰበር የትዝብት ዜና!
~~~~~~~~~~~

የእስራኤሉ የዉጭ ጉዳይ ሚንስትር በዩክሬን ጉብኝት ላይ ሲሆኑ፣ ሩሲያ በዩክሬን በተለይ በሰላማዊ ዜጎች ላይ የምትፈጽመዉን ግድያ እንድታቆምና ወደ ሰላም እንድትመጣ ጠየቁ!
,
👉ይህ በአመቱ ዉስጥ ከታዘብኳቸው ትዝብቶች ሁሉ ገራሚው ሆኖ አግኝቸዋለሁ! ለምን ቢሉ - ዉሃዉን በእንስራው በዉጭ በኩል ቀዱትና ነው!
ይሄው ነው!
*** የእርሶስ ምልከታ ምን ያለ ነው? ይጻፉና እስኪ እንየው!
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

🚨በጋዛ እስካሁን ከ80 በላይ ህጻናት በረሃብ አለንጋ ተገርፈው ሞተዋል!🚩የዘር ማጥፋት ወንጀል በጋዛ! ~~~~~~~~~~~~~~~~~ እስካሁን ድረስ፣ በሐምሌ 23፣ 2025 (እንደ አውሮፓውያን...
07/23/2025

🚨በጋዛ እስካሁን ከ80 በላይ ህጻናት በረሃብ አለንጋ ተገርፈው ሞተዋል!
🚩የዘር ማጥፋት ወንጀል በጋዛ!
~~~~~~~~~~~~~~~~~

እስካሁን ድረስ፣ በሐምሌ 23፣ 2025 (እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር) የጋዛ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር (የሐማስ መንግስት አካል እና በህክምና ባለሙያዎች የሚተዳደር፣ አኃዞቹም በተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና ሌሎች ባለሙያዎች ዘንድ እምነት የሚጣልባቸው ናቸው) ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ ቢያንስ 80 ህጻናት በረሃብ አለንጋ ተገርፈው ቆዳቸው ከአጥንታቸው ጋር ተጣብቆ ሞተዋል።

አስፈላጊ ነጥቦች ፦

ይህ ቁጥር በየጊዜው የሚለዋወጥ ነው፣ የቅርብ ጊዜ ዘገባዎች በምግብ እጥረት ምክንያት የሞቱት ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ያመለክታሉ። ለምሳሌ፣ በሐምሌ 22፣ 2025፣ የጋዛ ከተማ የአል-ሺፋ ሆስፒታል ኃላፊ፣ ባለፉት ሶስት ቀናት ውስጥ በመላው የፍልስጤም ግዛት ውስጥ 21 ህጻናት "በምግብ እጥረት እና በረሃብ" መሞታቸውን ገልጸዋል።

ሁኔታዉን እግር ከእግር ተከታትሎ ዳታ ለመሰብሰብ ያለው ሁኔታ ኢጅግ አስቸጋሪ በመሆኑ ተጨማሪ የሞቱ ብዙዎች እንዳልተመዘገቡ ይታመናል፡፡

የተባበሩት መንግስታት አለማቀፍ የህጻናት የአደጋ ጊዜ መርጅያ ተቋም ዩኒሴፍ (UNICEF) በግንቦት ወር ብቻ ከ6 ወር እስከ 5 ዓመት ዕድሜ ያላቸው 5,119 (አምስት ሺህ አንድ መቶ አስራ ዘጠኝ ) ህጻናት ከባድ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ህክምና አስፈልጓቸው እንደነበር ዘግቧል፣ ይህም ከኤፕሪል 2025 ጋር ሲነጻጸር ወደ 50% የሚጠጋ ጭማሪ ነው ያሳየው። በተጨማሪም ከ2025 መጀመሪያ አንስቶ እስከ ግንቦት ወር መጨረሻ ድረስ በአማካይ በቀን 112 ህጻናት ለተመጣጠነ ምግብ እጥረት ህክምና እንደሚጋለጡ ገልጸዋል። እንግድያው ይህ የዘር ማጥፋት ወንጀል ካልሆነ ሌላ ምንድን ነው?
*** የእርሶስ ምልከታ ምን ያለ ነው? ይጻፉና እስኪ እንየው!
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

07/22/2025

አደገኛው ጋዛ!
~~~~
የፍልስጤም ጤና ቢሮ እንደገለፀው በአሁኑ ሰዓት ቢያንስ 17 ሺ ሕጻናት በምግብ እጦት በከፍተኛ ስቃይና አደጋ ላይ ናቸው!

~ወደ 26 የሚጠጉ ሀገራት ጦርንርቱ ማብቃት አለበት ሲሉ ~ፈረንሳይ ደግሞ የውጭ ሚዲያዎች ወደጋዛ ሊገቡ ይገባል አለች~~~~~~~~~~~  ዩናይትድ ኪንግደም ከ 25 አለም አቀፍ አጋሮች ጋር ...
07/22/2025

~ወደ 26 የሚጠጉ ሀገራት ጦርንርቱ ማብቃት አለበት ሲሉ
~ፈረንሳይ ደግሞ የውጭ ሚዲያዎች ወደጋዛ ሊገቡ ይገባል አለች
~~~~~~~~~~~


ዩናይትድ ኪንግደም ከ 25 አለም አቀፍ አጋሮች ጋር እስራኤል በጋዛ ሰርጥ የምታደርገውን ጦርነት በአስቸኳይ እንድታቆም እና በሰብአዊ ርዳታ ፍሰት ላይ የጣለችውን እገዳ ያለ ምንም መዘግየት እንድታነሳ አሳሰቡ ።

የመግለጫው ፈራሚዎች :-
_________________

አውስትራሊያ፣ ኦስትሪያ፣ ቤልጂየም፣ ካናዳ፣ ዴንማርክ፣ ኢስቶኒያ፣ ፊንላንድ፣ ፈረንሳይ፣ አይስላንድ፣ አየርላንድ፣ ጣሊያን፣ ጃፓን፣ ላትቪያ፣ ሊትዌኒያ፣ ሉክሰምበርግ፣ ኔዘርላንድስ፣ ኒውዚላንድ፣ ኖርዌይ፣ ፖላንድ፣ ፖርቱጋል፣ ስሎቬኒያ፣ ስፔን፣ ስዊድን፣ ስዊዘርላንድ እና የአውሮፓ ህብረት የእኩልነት እና የቀውስ አስተዳደር ኮሚሽነር ናቸው ።
___________________

ቡድኑ የሲቪሎችን ደህንነት መጠበቅ እንዳለበት አፅንዖት ሰጥቶ ሁሉም አካላት በአለም አቀፍ የሰብአዊ ህግ መሰረት ግዴታቸውን እንዲወጡ ይገባል ሲል ጥሪ አቅርቧል:: በተጨማሪም ፍልስጤማውያንን በግዳጅ ማፈናቀል የአለም አቀፍ የሰብአዊ ህግን መጣስ እንደሆነ በማሳሰብ ፍልስጤማውያንን so called “humanitarian city,” (ሰብዓዊ ከተማ ) ወደተሰኘ ቦታ ለማዛወር የቀረበውን ማንኛውንም ሀሳብ በጽኑ ውድቅ አድርገዋል።

ሃገራቱ "እኛ ፈራሚ ሃገራት በጋዛ ያለው ጦርነት አሁን ማብቃት አለበት! የሚል ቀላል እና አስቸኳይ መልእክት እናስተላልፋለን!፡" ሲል በ መግለጫው አሳስበዋል ።

ይህ በእንድሁ እንዳለ ፈረንሳይ በበኩሏ ዓለም አቀፍጋሼትኞች ወፈጋዛ መግባትና ረሃቡን ማሳየት አለባቸው ሲሉ ተናግረዋል:: የፈረንሳዩ ማክሮን እና ናታንያሁ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ጋዛን በተመለከተ በምያራምዱት አቅዋም መካረራቸዉና አንድ አንድ እየተባባሉ መሆኑ ይታወቃል::

እስራኤል ካለፈው ህዳር ወር ጀምሮ ምንም አይነት ዓለም አቀፍ የምግብና የመድሃኒት እርዳታ እንዳይገባ ማገዷና አሁን ደግሞ በራስዋና በአሜሪካ የተቀናበር በእርዳታ ስም የተራቡና የተጠሙ ፍልስጤማውያንን የመግደል እርምሃ እየወሰደች መሆኑ ብዙ ትችቶችን እያስነሳባት ይገኛል!

*** የእርሶስ ምልከታ ምን ያለ ነው? ይጻፉና እስኪ እንየው!
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

🚨"ዲሞክራሲያዊ" እና አለማቀፋዊ ጀኖሳይድ!~~~~~~~  ከጥቂት አመታት በኃላና ከዛም አልፎ መጪው ትዉልድ እነዚህን ሰቆቃዎች በሆሊዉድ ፊልሞች በኩል ይመለከታል::  በዶክመንተሪዎች ተደግፎ ...
07/21/2025

🚨"ዲሞክራሲያዊ" እና አለማቀፋዊ ጀኖሳይድ!
~~~~~~~

ከጥቂት አመታት በኃላና ከዛም አልፎ መጪው ትዉልድ እነዚህን ሰቆቃዎች በሆሊዉድ ፊልሞች በኩል ይመለከታል:: በዶክመንተሪዎች ተደግፎ ያጠናል, እንዴት እንዲህ ሆነ? እያለ ይጠይቃል? ይህ ሁሉ ሲሆን ያ ትዉልድ ምን እያደረገ ነበር? እያለ ይገረማል:: በየዓመቱ የጋዛ ጀኖሳይድን ለማሰብ እያለ የሚያከብርበትንም ቀንና ሰዓት ያበጃል :: አንተና እኔ ብሎም የዓለም ህዝብ ግን ዛሬ ይህንንና የባሰዉን "ዲሞክራሲያዊ" እና አለማቀፋዊ የጋዛ ጀኖሳይድ! በሰአቱና በቦታው ተገኝተን live ቁጭ ብለን እያየን ከዝያም እየበላንና እየጠጣን, ሥራችንንም እየሰራን, እንቅልፍም እየወሰደን እንገኛለን!
ታሪክ በዋናነት የሚያስጨንቀው አልፎ ሲተረክ ሳይሆን በሰዓቱ ተገኝተው ሲያልፉበት ነው ማለቴ ለዚሁ ነው :: ለማለት ነው ይሄው ነው!

*** የእርሶስ ምልከታ ምን ያለ ነው? ይጻፉና እስኪ እንየው!
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

Update!!ኡስታዝ አህመዲን ጀበል ከመጅሊስ መታገዱን በተመለከተ የዉስጥ ምንጩን ጠቅሶ ሆራይዘን ሚድያ የዘገበዉን ማስነበባችንን ተከትሎ አንዳንዶች ዘገባዉን ለማስነሳት, ሌሎች ደግሞ የበለጠ...
07/21/2025

Update!!
ኡስታዝ አህመዲን ጀበል ከመጅሊስ መታገዱን በተመለከተ የዉስጥ ምንጩን ጠቅሶ ሆራይዘን ሚድያ የዘገበዉን ማስነበባችንን ተከትሎ አንዳንዶች ዘገባዉን ለማስነሳት, ሌሎች ደግሞ የበለጠ መረጃ ለማግኘት ብዙዎች በዉስጥ መስመር ልታገኙን ሞክራቹሃል:: እኛም በበኩላችን ተጨማሪ መረጃዎችን ለማሰባሰብ ሞክረናል በዚህም መሰረት ኡስታዝ አህመዲን ጀበልን ስለ ጉዳዩ የሚያውቀዉን እንዲነግረን ጠይቀነው -
_____________

"እኔ ወደ መጅሊስ ከሄድኩ 1 ወር አልፎኛል። የሃሳብ ልዩነት ነበረን ።ግን ከጊቢ መግበት የመታገድ ነገር መረጃው የለኝም። ወደዚያ አልሄድኩምና የማውቀው ነገር የለም። " የሚል ምላሽ ሰጥቶናል:: በዝርዝር ሌላ ጊዜ የምናናግረው ይሆናል::
_______________

በጉዳዩ ዙርያ ያነጋገርነው ለመጅሊሱ ቅርብ የሆነ ሰው ደግሞ " እነ ሼህ ሃጂ ይህንን ያደርጋሉ ብዬ አላምንም ግን አጣራለሁ " የሚል ምላሽ ሰጥቶናል!

🚨 ኡስታዝ አሕመዲን ጀበል መጅሊስ እንዳይገባ ታገደ‼️   ~~~~~~~~~~~  ኡስታዝ Ahmedin Jebel-አሕመዲን ጀበል የፌዴራል መጅሊስ ቅጥር ግቢ  እንዳይገባ መታገዱን ምንጮች ለሆራይ...
07/21/2025

🚨 ኡስታዝ አሕመዲን ጀበል መጅሊስ እንዳይገባ ታገደ‼️
~~~~~~~~~~~

ኡስታዝ Ahmedin Jebel-አሕመዲን ጀበል የፌዴራል መጅሊስ ቅጥር ግቢ እንዳይገባ መታገዱን ምንጮች ለሆራይዘን ሚዲያ ገለፁ::

በሁለቱ መሃከል የቆዬ መልካም ግንኙነት የነበረ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየሻከር መምጣቱን ጨምረው የገለፁት ምንጮች ፤ በተለይ ኡስታዝ አሕመዲን ጀበል “መጅሊስን ማን ይምራው? ሳንተፋፈር በግልጽ እንነጋገርበት‼️ በሚል ርዕስ በማኅበራዊ ትስስር ገፁ በፅሁፍ ያጋራው እና ከ ነጃሺ ቲቪ የጀማል አሕመድ ሾው ጋር የመጅሊስ ምርጫን አስመልክቶ በሁለት ክፍል የቀረበ ቃለ ምልልስ ግንኙነታቸውን የበለጠ የማይታረቅ አድሮታል ብለዋል::

ኡስታዝ አሕመዲን ጀበለ እስከ ቅርብ ግዜ የጠቅላይ ም/ቤቱ ፕሬዝደንት አማካሪ ሆኖ ሲሰራ እንደቆየ የሚታወቅ ሲሆን ፤ 'ፕሬዝዳንቱ ምክር አይቀበሉም❗ ብለው በገዛ ፍቃዳቸው ከአማካርነት ራሳቸውን ካገለሉ ጥቂት አማካሪዎችም አንዱ እንደነበረ ምንጮች ጨምረው ለሆራይዘን ገልፀዋል::

ፕሬዝዳንቱም የኡስታዝ አሕመዲንን የሚዲያ ዘመቻ ይገታልኛል ወይም ይመክትልኛል በሚል እራሱን "የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የጋራ ፎረም" የተሰኘ የሎቢ ቡድን ማደራጀታቸውንም ምንጮች ለሆራይዘን ሚዲያ ጨምረው ገልፀዋል::
ዘገባው @የሆራይዘን ሚድያ ነው

ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

Address

St. Louis, MO

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when RN05 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to RN05:

Share