RN05 ከኢትዮጵያ እና ዲያስፖራ የሚተላለፍ ሚድያ!
አዲሱን ዩቱብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ:
https://www.youtube.com/c/RN05channel

https://t.me/RNZeroFive

https://rnzerofive.com/

❗️ጭንብሏ የወለቀባት ኢምፔሪያሊስቷ አሜሪካ~~~~~~~~~~ ማናለብኝነት ነፋፍቶ ያሳበጣት የጽዮናውያኑ መከታ፣ የኢምፔሪያሊዝም ዋልታ አሜሪካ የቬንዝዌላን ሉዓላዊ ግዛት በመውረር የሃገሪቱን ፕ...
01/05/2026

❗️ጭንብሏ የወለቀባት ኢምፔሪያሊስቷ አሜሪካ
~~~~~~~~~~

ማናለብኝነት ነፋፍቶ ያሳበጣት የጽዮናውያኑ መከታ፣ የኢምፔሪያሊዝም ዋልታ አሜሪካ የቬንዝዌላን ሉዓላዊ ግዛት በመውረር የሃገሪቱን ፕሬዚደንትና ባለቤቱን አፍና ወሰደች። ለዚህ የአለም አቀፍ ህግጋትን በግልጽ የጣሰ የወረራ እርምጃዋ ምክንያት ያደረገችው ሀገሪቱ አደንዛዥ እፆችን ወደ አሜሪካ ትልካለች የሚል ነው። ይህንን አሜሪካ የወሰደችውን የምናለብኝ የወረራ እርምጃ ሩስያ፣ ቻይናና ኮሎምብያን ጨምሮ አንዳንድ ሃገራት ቢያወግዙም አውሮፓውያን ግን መንተባተብን መርጠዋል።ከወቀሳ ለማምለጥ ሲሉ ደግሞ ፕሬዚደንቱ ማዶሮ አምባገነን መሪ ስለሆነ ሥልጣኑ ህጋዊነት የለውም የሚልን ትርክት ለህዝባቸው ለመሸጥ ሲጋጋጡ ታይተዋል።
ትራምፕ ቬንዝዌላን በመውረርና ፕሬዚደንቷን በማፈን የመንግሥት ለውጥ ለማምጣት የተነሳበት ምክንያት መንግሥቱ አምባገነን ስለሆነ ወይንም አደንዛዥ እፅ ወደ አሜሪካ ስለሚልክ ሳይሆን ሃገሪቱ ያላትን ከፍተኛ የቤንዚን ሃብት ለመቀራመት እንደሆነ ከማንም የተደበቀ አይደልም። የአንድ ሃገር መንግሥት በምዕራባውያኑ አገላለጽ አምባገነን ስለሆነ ብቻ የወረራ ሰለባ እንዲሆን የሚፈቅድ ህግ ቢኖር ኖሮ በርካታ ሃገራት ድሮ ገና በተወረሩ ነበር። ነገር ግን ሁሉም ሰው በደንብ እንደሚያውቀው ጥቅሟን እስካስጠበቁላት ድረስ አሜሪካ ከአምባገነን መንግሥታት ጋር ወዳጅ እንጂ ፀበኛ አይደለችም። እንዲያውም በተቃራኒው ወደ ዲሞክራሲ የሚደረጉ እርምጃዎችን በማደናቀፍ ነው የምትታወቀው።
አሜሪካ በተለይ አሁን ዶናልድ ትራምፕ ወደ ስልጣን ከመጣ በኋላ የዲሞክራሲ ጭንብሏን ሙሉ በሙሉ አውልቃ አስፈሪ ገጽታዋን በግልጽ ማሳየት ጀምራለች።ፍልስጤም ህዝቦች ላይ እየተፈጸመ ያለውን የዘር ፍጅት ከማሳለጥ አልፋ በግልጽ ወረራ ፈጽማለች። ኩባንና ግሪን ላንድ ያካተተ ተጨማሪ ወረራዎችን ለመፈጸምም እየዛትች ትገኛለች።
አሜሪካ በዚህ የማንአለብኝነት እርምጃዋ እያስተላለፈች ያለው መልዕክት ሃያላን አገራት ደካሞችን ያለምንም ምክንያት መውረር ይችላሉ የሚል ነው። አሜሪካ ቬንዝዌላ ላይ ወረራ ስትፈጽም ለሩሲያ ወይንም ለቻይና ወይንም ለሌሎች ሃያላን መንግሥታት እያለቻቸው ያለው “እናንተም አቅም ካላችሁ ጎረቤቶቻችሁን በወረራ ማንበርክርክ ትችላላችሁ” ነው። ይሄ መቸም ዞሮ ዞሮ ወደየት ሊያደርሰን እንደሚችል መገመት የሚያስቸግር አይመስለኝም። በአንድ ወገን በጉልበተኞች የመዋጥ አደጋ የተደቀነባቸው ሃገራት ያለባቸውን የደህንነት ስጋት ለመቅረፍ ሲሉ ለሃያላኑ ግብር የመክፈል ግዴታ ላይ እንዲወድቁ ሊያስገድድ ይችላል። በሌላ በኩል ደግሞ በተወሰነ ደረጃ ራሳቸውን የመከላከል አቅም ያላቸው ደግሞ ጡንቻዎቻቸውን ለማፈርጠም የጦር መሳርያ እሽቅድድም ውስጥ ሊገቡ ይችላሉ። ይህም ሁኔታ አለማችንን እጅግ በጣም ያልተረጋጋች ያደርጋታል የሚል ስጋት አለ።
ይሄ አሜሪካ እያሳየችው ያለ መጥፎ ባህሪይ ዞሮ ዞሮ ራሷንም የሚያጠፋ ቢሆን በሂደት ግን ብዙ ጉዳት ሊያስከትል የሚችል ነው። ደግሞ የጉዳቱ ሰለባዎች የሚሆኑት ሁሉም ሃገራት ናቸው። ይዘገይ ይሆናል እንጂ ማንም ከጉዳት የሚድን ሃገርም ሆነ ህዝብ የለም። ስለዚህ ይህንን ከመንገድ የወጣ ዋልጌ ድርጊት ሁሉም ሃገራት በአንድ ድምፅ ሊያወግዙት ይገባል።
🗣️ የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው?
አስተያየትዎን ያጋሩ! 👇
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

❓አዲሱ የቅኝ ግዛት ዘመን በአሜሪካ መሪነት ተጀምሯልን?~~~~~~~~~~~ ለዘመናት በአውሮፓውያን ሲተገበር የቆየው የቀጥታ እና የእጅ አዙር የቅኝ ግዛት ታሪክ፣ ዛሬ በፕሬዝዳንት ትራምፕ መሪ...
01/05/2026

❓አዲሱ የቅኝ ግዛት ዘመን በአሜሪካ መሪነት ተጀምሯልን?
~~~~~~~~~~~

ለዘመናት በአውሮፓውያን ሲተገበር የቆየው የቀጥታ እና የእጅ አዙር የቅኝ ግዛት ታሪክ፣ ዛሬ በፕሬዝዳንት ትራምፕ መሪነት አዲስ መልክ ይዞ ብቅ ያለ ይመስላል። አዲሱ የአሜሪካ አስተዳደር ከቃላት ባለፈ፣ የተፈጥሮ ሃብት ያላቸው ሀገራት ሃብታቸውን ለአሜሪካ ጥቅም እንዲያውሉ፣ ካልሆነ ግን በኃይል ተገደው እንደሚነጠቁ በተግባር እያሳየ ይገኛል።
ይህ አካሄድ ዓለም አቀፍ ሕጎችን የጣሰ እና የሀገራትን ሉዓላዊነት የሚደፍር መሆኑ ተስተውሏል። በተለይም በነዳጅ ሃብቷ ቀዳሚ የሆነችውን የቬንዙዌላን ፕሬዝዳንት ከነባለቤታቸው አፍኖ ወደ ኒውዮርክ በመውሰድ ማሰር፣ እንዲሁም "ቬንዙዌላን የማስተዳድራት እኔ ነኝ፣ ሃብቷም የኛ ነው" የሚለው አዋጅ የቀኝ ገዥነት መንፈስን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።
📍 የላቲን አሜሪካ ስጋት እና የቀጠናው ውጥረት
-------------------------------------------
አሜሪካ አሁን ደግሞ ፊቷን ወደ ሌሎች የላቲን አሜሪካ ሀገራት አዙራለች፦
👉ኮሎምቢያ፦ ፕሬዝዳንት ጉስታቮ ፔትሮን "በአደንዛዥ ዕፅ ንግድ" በመክሰስ ዛቻ ሰንዝረዋል። ፕሬዝዳንት ፔትሮ በበኩላቸው "አሜሪካ ካሰበች ትሞክረው፤ ጠንካራው መከላከያችን ለወረራ እጅ አይሰጥም" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
👉ኩባ እና ሜክሲኮ፦ ኩባ ቀጣይዋ ኢላማ መሆኗ ሲነገር፣ ሜክሲኮ ደግሞ "ለአሜሪካ ስጋት ነች" በሚል ቀጣይ እርምጃ እንደሚጠበቅባት ተገልጿል።
👉ግሪንላንድ፦ ትራምፕ ወደ አውሮፓም በመሻገር በዴንማርክ ስር ያለችውን ግሪንላንድን "ለአሜሪካ አስፈላጊ ስለሆነች ጠቅልለን እንወስዳለን" በማለት በይፋ አውጀዋል።
📍 የኢትዮጵያ ስጋት እና የአየር ኃይሉ "ጠንካራ" ምላሽ
----------------------------------------------
ይህ ከአለም አቀፍ ህግ ያፈነገጠ እርምጃ ኢትዮጵያንም ሆነ ማንኛውንም ሀገር የማይምር አዲስ ምዕራፍ መሆኑ ግልጽ ነው። የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ንግግር በሀገር ሉዓላዊነት ላይ የተቃጣ በመሆኑ፣ ይህንን ተከትሎ ለሚመጣ ነገር ሁሉ አጸፋዊ እርምጃ ለመውሰድ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዝግጁ መሆኑን አስታውቋል።
👉የኢፌዴሪ አየር ኃይል አዛዥ ሜጀር ጀነራል ይልማ መርዳሳ ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደተናገሩት፤ የፕሬዝዳንት ትራምፕ ንግግር "ኃያል ሀገርን እመራለሁ" ከሚል ፕሬዝዳንት የሚጠበቅ አይደለም። የአንድን ሀገር ሉዓላዊነት በንግግርም ቢሆን መጣስ ከባድ ጥፋት መሆኑን የገለጹት አዛዡ፣ ይህንን ተከትሎ ሊመጣ የሚችል ማንኛውንም ዓይነት ጥቃት ለመመከት አየር ኃይሉ ሙሉ ዝግጁነት እንዳለው አረጋግጠዋል።
ይህም የሚያሳየው ወረራውና ዛቻው ራሳቸውን መከላከል በማይችሉ ሀገራት ላይ ብቻ ሳይሆን፣ ለአሜሪካ አልታዘዝም ለሚሉ ቢያንስ የኒዩክሌር ቦምብ ያልታጠቁ ሀገራት ላይም የተደቀነ ስጋት መሆኑን ነው።
📌መደምደሚያ፡ የጋራ ተግዳሮት እና መውጫ መንገድ
------------------------------------------------
ይህ አዲሱ የቅኝ አገዛዝ ስርዓት ይፋ ከሆነ፣ ሀገራት በብሔር፣ በሃይማኖት ወይም በአህጉር ሳይለያዩ በጋራ እስካልተጋፈጡት ድረስ አደጋውን በተናጠል ማስቀረት እጅግ አዳጋች ይሆናል።
የአለም አቀፍ ስርዓት ሚዛኑን በሳተበት እና "ጉልበተኛው ሁሉን ይወስዳል" በሚለው መርህ መመራት በጀመረበት በዚህ ወቅት፣ የሀገራት ህልውና የሚወሰነው በውስጣዊ አንድነታቸው እና በጋራ የመከላከል አቅማቸው ላይ ነው። እንደ ኢትዮጵያ ያሉ ሀገራት ይህንን አዲስ የቅኝ ግዛት ማዕበል ለመቀልበስ፣ በዲፕሎማሲው መስክ መጠናከር ብቻ ሳይሆን፣ የማይበገር የህዝብ አንድነት ሊኖራቸው ይገባል። ከሁሉ በላይ ደግሞ፣ የአለም አቀፍ ህግጋት እንዲከበሩና የሀገራት ሉዓላዊነት እንዲጠበቅ ታዳጊ ሀገራት በጋራ መቆም ብቸኛው እና የመጨረሻው መውጫ መንገድ ነው።
❗️ እናም "የአለም ሃገራት ወዛደሮች / ጭቁን ህዝቦች ተባበሩ!!" ለማለት ነው!
🗣️ የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው?
አስተያየትዎን ያጋሩ! 👇
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

"ነገሮች እስኪስተካከሉ ድረስ ቬንዝዌላን አስተዳድራለሁ " ማለታቸዉን ተከትሎ ከአነጋጋሪዎቹ የፕሬዝደንት ትራምፕ ወቅታዊ መገለጫ ፎቶዎች መካከል አንዱ !
01/05/2026

"ነገሮች እስኪስተካከሉ ድረስ ቬንዝዌላን አስተዳድራለሁ " ማለታቸዉን ተከትሎ ከአነጋጋሪዎቹ የፕሬዝደንት ትራምፕ ወቅታዊ መገለጫ ፎቶዎች መካከል አንዱ !

ይሳተፉ!!!ከ 1959 ጀምሮ 11 ተከታታይ የዩኤስ አሜሪካ ፕሬዝደንቶች  በተለያዩ ዘዴዎች  ሊያስወግዱት ሞክረው  ሁሉንም ያከሸባቸዉና በ 2016 በ 90 አመቱ በተፈጥሮ ሞትየሞተ የሀገር መሪ...
01/04/2026

ይሳተፉ!!!
ከ 1959 ጀምሮ 11 ተከታታይ የዩኤስ አሜሪካ ፕሬዝደንቶች በተለያዩ ዘዴዎች ሊያስወግዱት ሞክረው ሁሉንም ያከሸባቸዉና በ 2016 በ 90 አመቱ በተፈጥሮ ሞትየሞተ የሀገር መሪ ማን ይባላል? በሲአይኤ ለምን ያህል ጊዜ የመግደል ሙከራ ተደርጎበት ነበር????

የሁለቱ መሪዎች ቀጣይ ወግ! (ማነው የሚዋሸው?)~~~~~~~~~~ ፕሬዝደንት ትራምፕ:-   "ቬንስዌላ የተረጋጋ አስተማማኝ ሽግግር እስከሚደረግ ድረስ አሜሪካን አሜሪካ (እኔ) አስተዳድራለሁ !...
01/04/2026

የሁለቱ መሪዎች ቀጣይ ወግ! (ማነው የሚዋሸው?)
~~~~~~~~~~

ፕሬዝደንት ትራምፕ:- "ቬንስዌላ የተረጋጋ አስተማማኝ ሽግግር እስከሚደረግ ድረስ አሜሪካን አሜሪካ (እኔ) አስተዳድራለሁ !" ደግሞም " ከምክትል ፕሬዝደንቷ ጋር ተነጋግሬ አሜሪካ የምትፈልገዉን ሁሉ እናደርጋለን ብላኛለች!"
የቬንዝዌላ ምክትል ያሁኗ ጊዝያዊ ዋና ፕሬዝደንት :- "በቬንዝዌላ ያለው አንድ ፕሬዝደንት ብቻ ነው እሱም ማዱሮ ይባላል! አሜሪካ በአስቸኳይ ልትለቀው ይገባል፣ አሜሪካ የሰራችው ስራ ለሌሎችም ሃገራት ዋስትና የማይሰጥ ነው!" "ሃገራችንን ከጣልቃ ገብነት ለመጠበቅ መላ ማግኘታችን የማይቀር ነው!"
🗣️ የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው?
አስተያየትዎን ያጋሩ! 👇
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

01/04/2026

No comment!

🌍ሉዓላዊነት በጉልበት ሲተካ፡ የቬንዙዌላው ክስተት እና  !⚠️ከህግ ወደ ኃይል የበላይነት የሚደረግ ሽግግር~~~~~~~~~~~~~  የቬንዙዌላው ፕሬዝደንት ኒኮላስ ማዱሮ በአሜሪካን ቁጥጥር ስር...
01/03/2026

🌍ሉዓላዊነት በጉልበት ሲተካ፡ የቬንዙዌላው ክስተት እና !
⚠️ከህግ ወደ ኃይል የበላይነት የሚደረግ ሽግግር
~~~~~~~~~~~~~

የቬንዙዌላው ፕሬዝደንት ኒኮላስ ማዱሮ በአሜሪካን ቁጥጥር ስር መዋላቸዉን ፕሬዝደንት ትራምፕ ይፋ ማድረጋቸው ታውቋል፡፡ ይህ ጽሁፍ የቬንዙዌላውን ክስተት መነሻ በማድረግ፣ የአለምን የፖለቲካ ስርዓት ለውጥ እና ለታዳጊ ሃገራት ያለውን ትርጉም በዝርዝር ይተነትናል።

🛑ከህግ የበላይነት ወደ ጉልበት የበላይነት፦ የቬንዙዌላው ክስተትና የዓለም ስርአት መሸርሸር:-
በአሁኑ ወቅት በአለም አቀፍ ፖለቲካ ውስጥ እያየን ያለነው ክስተት፣ ከሁለተኛው የአለም ጦርነት በኋላ የተገነባው "በህግ ላይ የተመሰረተ የአለም ስርአት" (Rules-based International Order) ለከፍተኛ አደጋ መጋለጡን ነው። የቬንዙዌላው ፕሬዝደንት ኒኮላስ ማዱሮ በዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በወታደራዊ ሃይል ተይዘው ቁጥጥር ስር መዋላቸው፣ ይህ ስርአት ፈርሶ የጉልበተኞች የበላይነት በይፋ መንገሱን የሚያሳይ ትልቅ ማሳያ ነው።

📍1. የቬንዙዌላው ክስተት ዳራ እና የታሪክ መታጠፊያ
ቬንዙዌላ በአለም ላይ ካሉ ግዙፍ የነዳጅ ክምችቶች አንዱ ያላት ሃገር ብትሆንም፣ ላለፉት አስርት ዓመታት የምዕራባውያን ኢኮኖሚያዊ ማዕቀብ እና የውስጥ ፖለቲካዊ ሽኩቻ ማዕከል ሆና ቆይታለች። ኒኮላስ ማዱሮ "የሃገሬን ጥቅም እና ሉዓላዊነት አሳልፌ አልሰጥም" በሚል መርህ ከምዕራባውያን ጋር ሲላተሙ ቆይተዋል።
ዶናልድ ትራምፕ ወደ ስልጣን ሲመለሱ፣ ይህንን ግጭት ከዲፕሎማሲያዊ እና ከኢኮኖሚያዊ ጫና ባለፈ ወደ ወታደራዊ እርምጃ አሸጋግረውታል። ማዱሮን በቁጥጥር ስር ለማዋል የተጠቀሙበት ምክንያት "የዕፅ ዝውውር" እና "የሰብአዊ መብት ረገጣ" ቢሆንም፣ ከጀርባው ያለው እውነታ ግን የሃገሪቱን የተፈጥሮ ሀብት እና የላቲን አሜሪካን ጂኦ-ፖለቲካ ለመቆጣጠር የሚደረግ የጉልበት እርምጃ ነው። ይህ እርምጃ የአንዲትን ሃገር መሪ በሃይል ማስወገድና መያዝ "የተለመደ አሰራር" እንዲሆን መንገድ ከፍቷል።
📍2. የአለም አቀፍ ህግጋት መፍረስ እና "የጫካ ህግ" መመለስ
ከ1945 በኋላ የተመሰረተው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ቻርተር፣ ማንኛውም ሃገር በሌላ ሃገር የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ እንዳይገባ እና የሃገራት ሉዓላዊነት እንዲከበር ይደነግጋል። ሆኖም ግን የማዱሮ በሃይል መያዝ የሚከተሉትን ክፍተቶች ቁልጭ አድርጎ አሳይቷል፦
- የሉዓላዊነት ትርጉም ማጣት፦ ሉዓላዊነት አሁን ላይ የሚከበረው ጉልበት ላላቸው ሃገራት ብቻ ሆኗል። ትናንሽ ሃገራት የራሳቸውን ፖሊሲ ለመቅረጽ ሲሞክሩ፣ ኃያላን ሃገራት "ብሄራዊ ጥቅሜን ይነካል" በሚል ሰበብ ወታደራዊ እርምጃ እንዲወስዱ አረንጓዴ መብራት ሰጥቷቸዋል።

- የተቋማት አቅም ማጣት፦ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና ሌሎች አለም አቀፍ ተቋማት እንዲህ ያሉ የጉልበት እርምጃዎችን መከላከልም ሆነ መኮነን የማይችሉበት ደረጃ ላይ ደርሰዋል። ይህ ደግሞ አለም ወደ ቀድሞው "አቅም ያለው ያዛል ወይንም ይገዛል" (Survival of the fittest) ወደሚለው ህግ መመለሷን ያረጋግጣል።
- የህግ መጥፋት፦ ህግ የሚሰራው ለደካማ ሃገራት ብቻ ሆኗል። ኃያላን ሃገራት ህግ ሲጥሱ "አለምን ለማዳን" በሚል ስም ተጠያቂነት የሌለበት ድርጊት ይፈጽማሉ።

📍3. አዲሱ የቀዝቃዛ ጦርነት እና የታዳጊ ሃገራት ስጋት
አሁን እየኖርን ያለነው በአዲሱ የቀዝቃዛ ጦርነት (New Cold War) ውስጥ ነው። ይህ ጦርነት በምዕራባውያን (በአሜሪካ መሪነት) እና በምስራቃውያን (በቻይና እና ሩሲያ መሪነት) መካከል የሚደረግ የጥቅም ፉክክር ነው።
- የውክልና ጦርነት (Proxy Wars)፦ ኃያላን ሃገራት በቀጥታ ከመጋጠም ይልቅ፣ እንደ ቬንዙዌላ ባሉ ታዳጊ ሃገራት ውስጥ ያሉ የፖለቲካ ልዩነቶችን እንደ ሽፋን በመጠቀም የራሳቸውን ጥቅም ያስከብራሉ።
- የሀብት ቅርምት፦ አፍሪካ እና ላቲን አሜሪካ ሰፊ የተፈጥሮ ሀብት ያላቸው በመሆኑ፣ የዚህ ፉክክር ዋነኛ ሰለባዎች ናቸው። የቬንዙዌላው እርምጃ ማንኛውም የተፈጥሮ ሀብት ያለው እና "አልገዛም!" የሚል መንግስት ላይ ሊደገም የሚችል ስጋት ነው።
- ገለልተኛ መሆን አለመቻል፦ በዚህ ምስቅልቅል ውስጥ "እኔ ገለልተኛ ነኝ" ብሎ መቆም የማይቻልበት ደረጃ ላይ ደርሰናል። ሃገራት ወይ ወደ አንዱ ጎራ መለጠፍ አለያም ለጥቃት መጋለጥ የሚል ምርጫ ውስጥ ገብተዋል።
📍4. ለህዝቦች እና ለመንግስታት የሚተርፈው ትምህርት:-

ከዚህ ክስተት የምንረዳው ትልቁ ቁምነገር፣ በአሁኑ አለም የህዝብን እና የሃገርን ጥቅም ለማስጠበቅ የሚከተሉት ነጥቦች ወሳኝ መሆናቸውን ነው፦

- የውስጥ አንድነት፦ አንድ መንግስት በውስጡ የህዝብ ድጋፍ እና አንድነት ከሌለው፣ ለውጭ ጉልበተኞች ጥቃት በቀላሉ ይጋለጣል።

- በኢኮኖሚ ራስን መቻል፦ በምዕራባውያን እርዳታ እና ብድር ላይ ብቻ ጥገኛ መሆን፣ የሃገርን ሉዓላዊነት አሳልፎ ለመስጠት እንደ መጀመሪያ እርምጃ ይቆጠራል።

- የራስ አቅምን መገንባት፦ "አለም አቀፍ ህግ ይጠብቀኛል" ከሚል የተሳሳተ ተስፋ ወጥቶ፣ የሃገርን መከላከያ እና ዲፕሎማሲያዊ አቅም ማጠናከር ብቸኛው የህልውና ዋስትና ሆኗል።
♦️ማጠቃለያ:-
~~~~~
የማዱሮ በቁጥጥር ስር መዋል አሁን ያለው የአለም ፖለቲካ ምን ያህል አደገኛ እና ህግ አልባ እየሆነ መምጣቱን ያሳያል። ማንኛውም መንግስትና ህዝብ ከጉልበተኛ ሃገራት ፍላጎት ውጭ የራሱን ርዕዮተ-ዓለም፣ ሀብትና ጥቅም ለማስጠበቅ ያለው እድል እየጠበበ ነው። ይህ ሁኔታ ለኢትዮጵያም ሆነ ለሌሎች አፍሪካ ሃገራት ትልቅ ማስጠንቀቂያ ሲሆን፣ ብቸኛው መፍትሄ የውስጥ አቅምን ማጠናከር እና በብልሃት መጓዝ ብቻ መሆኑን ያስገነዝባል።
🗣️ የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው?
አስተያየትዎን ያጋሩ! 👇
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

"ሊበሏት የፈለጓትን አሞራ ስሟን ይሏታል ጅግራ"~~~~~~~ ትራምፕ - "ኢራን ሰልፈኞችን መግደሏን ከቀጠለች ጣልቃ እገባለሁ ዋ!"ኢራን - "ትራምፕ ሆይ! በዉስጥ ጉዳዬ ዉስጥ ጣልቃ እገባለሁ...
01/02/2026

"ሊበሏት የፈለጓትን አሞራ ስሟን ይሏታል ጅግራ"
~~~~~~~

ትራምፕ - "ኢራን ሰልፈኞችን መግደሏን ከቀጠለች ጣልቃ እገባለሁ ዋ!"
ኢራን - "ትራምፕ ሆይ! በዉስጥ ጉዳዬ ዉስጥ ጣልቃ እገባለሁ ብትል ዉርድ ከራሴ ዋ!"
~ ትራምፕ ከጋዛዊያን 70 ሺዎች ነፍስ ይልቅ ለኢራናዊያን ሰልፈኞች ነፍስ አዝነው እንቅልፍ ማጣታቸው እኛንም እንቅልፍ ሊያሳጣን ምን ቀረው? !
❗️የዚህ አለም ግብዝነት አንዳንዴ አይታክታችሁምን ?!!
👉ይህን ትእይንት እኔ "ሊበሏት የፈለጓትን አሞራ ስሟን ይሏታል ጅግራ" ብየዋለሁ>> እናንተ ደግሞ የተሻለ ወይንም የሚመጥነው የተለየ አባባል ካላችሁ ጻፉ እባካችሁ !
🗣️ የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው?
አስተያየትዎን ያጋሩ! 👇
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ካውንስል ተማሪዎችን ማስመረቁ ተዘገበ ~~~~~~~~~  የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል በዲጂታል ክህሎት ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ EMYC || ታህሳስ 23/ ...
01/01/2026

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ካውንስል ተማሪዎችን ማስመረቁ ተዘገበ
~~~~~~~~~


የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል በዲጂታል ክህሎት ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ

EMYC || ታህሳስ 23/ 2018

የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል መስጂድ ኔት በተሰኘው ፕሮጀክቱ መስጂዶቻችን የአምልኮ ስፍራ ብቻ ሳይሆኑ፣ ሁለነ‍ንተናዊ የዕውቀት ማዕከላት፣ የቴክኖሎጂ እና የፈጠራ ምንጮች፣ የወጣቶች የሙያ ማዳበሪያዎች እና የማህበረሰብ ግልጋሎት ማዕከላት እንዲሆኑ የመትጋት ነብያዊ ሱናን (ሰዐወ) በመከተል ላይ ይገኛል።

በዚህም መሰረት ማዕከሉን ሸይኽ ሆጀሌ መስጂድ አድርጎ ያሰለጠናቸውን የመስጂድ ኔት የመጀመሪያ 16 ተማሪዎች በዛሬው ዕለት አስመርቋል።

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ዋና ስራ አስኪያጅ ኡስታዝ ነብዩ አያሌው ባደረጉት ንግግር:-

በሀገራችን ኢትዮጵያ በርካታ ሙስሊም ወጣቶች ሥራ አጥነት፣ ከዲጂታል እውቀት መገለል እና ዘመናዊ ክህሎትን የማግኘት ውስንነት እንደሚያጋጥማቸው አውስተው መስጂዶቻችንም ሆነ ተቀሞቻችን እነዚህን ችግሮች የሚቀርፉበት እና ከወጣቱጋ ውጤታማ በሆነ መልኩ የሚሰሩበት መድረክ ሳያመቻቹ መኖራቸውን ነገር ግን የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ይህንን ክፍተት ለመሙላት እየሰራ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል።

የምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ በተማሪዎች የተሰሩ ፕሮጀክቶችን ለታዳሚ በማሳየት እና በተለያዩ ሌሎች ዝግጅቶች እየቀጠለ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ባሳለፍነው ሳምንት የመስጂድ ኔት ፕሮጀክቱን ከአዲስ አበባ በመቀጠል በጅማ ከተማ ማስጀመሩ ይታወቃል፣ በቀጣይም በሌሎች ክልል ከተሞች ማእከላትን መገንባቱን እና ለወጣቶች ስልጠናዎችን መስጠቱን አጠናክሮ ይቀጥላል።

የሶማሌው ዲፕሎማት አስደማሚ ምላሽና ብቃት!~~~~~~~~~ እኚህ ዲፕሎማት በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሶማሌ ተወካይ ናቸው፡፡ እስራኤል ለሶማሌላንድ እውቅና መስጠትዋን ተከትሎ ድርጅቱ ባደ...
12/30/2025

የሶማሌው ዲፕሎማት አስደማሚ ምላሽና ብቃት!
~~~~~~~~~

እኚህ ዲፕሎማት በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሶማሌ ተወካይ ናቸው፡፡ እስራኤል ለሶማሌላንድ እውቅና መስጠትዋን ተከትሎ ድርጅቱ ባደረገዉ ጉባዬ ላይ ከእስራኤሉ ተወካይ ቀጥለው ንግግር አድርገዋል፡፡ ታድያ ንግግራቸው መነጋገርያ ሆኗል፡፡
የእስራኤሉን ተወካይ አይን አይኑን እያዩ " ደግሞ አታፍሩም፣ ከሰባ ሺህ በላይ የጋዛን ህዝብ ያዉም ህጻናትንና ሰላማዊ ዜጎችን፣ የአደጋ ጌዜ ሰራተኞችን፣ ጋዜጠኞችን ፣ሃኪሞችንና ሆስፒታል የተኙ ታካሚዎችን ወዘተ ሳትምሩ አይናችን እያየ ጨፍጭፋችሁ ስታበቁ እዚህ መጥታችሁ ስለ ዲሞክራሲ ልታወሩና እኛን በጀኖሳይድ ልትከሱ ትፈልጋላችሁ! ...የእስራኤሉን ተወካይ እያመላከቱ "የተሳሳተና አንድ ወገን የሆነ ግንዛቤህን ልናርመው ይገባል..... ሶማሌያን ማን እንደሆንን ልናስረዳህ ግድ ይለናል!" ....ወዘተ " በሚል ያደረጉት ንግግርና የነበራቸው በራስ የመተማመን ስሜት እስራኤልንና አጋሮችዋን ጨምሮ የአለሙ መንግስታት ጉባዬን ድባብ የተቆጣጠረ ነበር፡፡
🗣️ የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው?
አስተያየትዎን ያጋሩ! 👇
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

በእስራኤል በኩል የባህር በር የማግኘት ሕልምና ኢ -አመክንዮ~~~~~~~~  ይህ ወዳጄ   የፃፈዉን ተከትሎ በቀረቡ አስተያየቶች ዙርያ ትዝብቴ ነው:: ( https://shorturl.at/KqR...
12/28/2025

በእስራኤል በኩል የባህር በር የማግኘት ሕልምና ኢ -አመክንዮ
~~~~~~~~

ይህ ወዳጄ የፃፈዉን ተከትሎ በቀረቡ አስተያየቶች ዙርያ ትዝብቴ ነው:: ( https://shorturl.at/KqR21):: ፅሁፉን ተከትሎ በቀረቡ አስተያየቶችና ሌሎችም ቦታዎች ባየሁዋቸው ፅሁፎችና ህሳቤዎች ተገርምያለሁ::
"የኢትዮጵያ መንግስት ራሱ ከሶማሌላንድ ጋር ተፈራርሞ ሊያስገኘው ያልቻለዉን የባህር በር ጉዳይ፤ "እስራኤል ለሱማሌላንድ በምትሰጠው እውቅና እናገኛለን" የሚል ኢ- አመክንዮ ሃገርን የመዉደድ መገለጫ ሃሳብ ተደረጎ መታየቱ ገራሚ ብቻ አይገልፀዉም! ይህ የጅዮ ፖሊቲክስ ክሽፈት ነዉ!
የሶማሌላንድ መንግስት ፈቅዶ የፈረመዉን ለኢትዮጵያ የባህር በር የመስጠትን ጉዳይ አይሆንም ብሎ ያስቀረው በዋናነት ራሱ የሶማሌላንድ ህዝብ ነዉ:: እኛ አሁን ይህንኑ የባህር በር እስራኤል የመንን አልማ በምትሰጠው አውቅና ሰበብ እናገኛለን ብሎ መፈንደቅ ከስሜታዊነት ዉጭ ተጨባጭ አይደለም::
ጎበዝ ሶማሌላንድ አላማዋ ከማንም ይሁን ከማን እውቅና ማግኘትና በሂደት ከዓለም ሀገሮች አንዷ ሆና ከዋናዋ ሶማሌ መላቀቅና ነፃ መሆን ነዉ:: በሌላ በኩል ደግሞ የእስራኤል ሕልምና ምኞት ሶማሌላንድንም ሆነ ማንኛዉንም እዛ አካባቢ ያለን ሀገር ፍላጎት አሟልታ የመንን መቅረብ ብሎም ሌሎች አጀንዳዎቿን ለማሳለጥ መጣር ነዉ::

ኢትዮጵያ የባህር በር ያስፈልጋታል! ይህ ጥያቄ የለዉም :: ነገር ግን የኢትዮጵያን የባህር በር ማግኘት ደግሞ የሚወሰነው የኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ በሚከተለው ትክክለኛና አዋጭ ዲፕሎማሲያዊ ጥረትና ታክቲክ ብቻ ነዉ::

አሁን በተያዘው የተሳሳተ ህሳቤ የሀገርን ፍቅር መግለፅ ቢያንስ በ 3 ምክንያቶች ገራሚና ስህተት ነዉ ::

1. የዲፕሎማሲ ግራ መጋባት፡ በራስ ስምምነት ያልተሳካን ጉዳይ በሌላ አካል እውቅና ይጠገናል ብሎ ማመን።

2. የአመክንዮ መዛባት፡ ስትራቴጂካዊ ጥቅምን ከስሜታዊ የፖለቲካ ድጋፍ ጋር ማደባለቅ።

3. የሀገር ፍቅር ትርጉም፡ እውነታን መካድ ወይም የራቀ ተስፋን መሰነቅና በዚህም ምክንያት ስሌት አለመስራት እንደ ሀገር ወዳድነት መቆጠሩ ነው። ይሄው ነው!

🗣️ የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው?
አስተያየትዎን ያጋሩ! 👇
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

🚩የእስራኤል የሶማሌላንድ እውቅና- ፊትና ኋላ! ~~~~~~~~ ለራሷ ሙሉ እውቅና የሌላት እስራኤል "ለሶማሌላንድ እውቅና ሰጠሁ!" ስትል አውጃለች። ሶማሌላንድም ለተሰጣት እውቅና ምስጋና አቅር...
12/27/2025

🚩የእስራኤል የሶማሌላንድ እውቅና- ፊትና ኋላ!
~~~~~~~~

ለራሷ ሙሉ እውቅና የሌላት እስራኤል "ለሶማሌላንድ እውቅና ሰጠሁ!" ስትል አውጃለች። ሶማሌላንድም ለተሰጣት እውቅና ምስጋና አቅርባለች። አንዳንድ የሶማሌላንድ ነዋሪዎችም አደባባይ ወጥተው ደስታቸውን ሲገልጹ የሚያሳይ ምስል በሰፊው ተሰራጭቷል። የእስራኤልን እውቅና የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን ጨምሮ፣ ቱርክ፣ ግብፅ፣ ጅቡቲና ሶማሊያ ተቃውመዋል። የሶማልያን የግዛት አንድነት የሚሸረሽር ማንኛውም አይነት ነገር ተቀባይነት አይኖረውም ብለዋል።
ይህንን እውቅና ተከትሎ ብዙ ትንታኔዎችን እየሰማን ነው። እስራኤል ለሶማሌላንድ እውቅና የሰጠችው በቀይባህር ዳርቻ የጦር ሠፈር መመስረት የሚያስችላትን ቦታ ለማግኘት ነው፣ ሶማሌላንድ የጋዛ ፍልስጤሞችን ማስፈሪያ ቦታ ለመስጠት ተስማምታለች ወዘተ የሚሉ አስተያየቶች እየተሰጡ ነው። አንዳንዶች ኢትዮጵያም እውቅና እንድትሰጥና ቀደም ተብሎ የመግባቢያ ሠነድ የተፈረመበትን ስምምነት ከሞተበት እንድትቀሰቅስ ሲመክሩ ተደምጠዋል።
እንደ እኔ እይታ እስራኤል ለሶማሌላንድ እውቅና በመስጠት አካባቢው ላይ ቦንብ አጥምዳለች። ያ ቦንብ ሊፈንዳም ላይፈነዳም ይችላል። የፈነዳ እንደሆን በተለይ የሚጎዳው የሶማሌን ህዝብ፣ በተለይ ደግሞ የሶማሌላንድን ህዝብ እንደሚሆን እገምታለሁ። እስራኤል ለሶማሌላንድ እውቅና በመስጠት ሃሳቧ ከሠመረ ታተርፍበታለች ካልሠመረ ግን የሚደርስባት ጉዳት የለም። ስለዚህ ለእስራኤል እርምጃው ጥሩ ሊሆን ይችላል፣ ለሶማሌላንድ ግን እውቅናው አደጋን አዝሎ እንደመጣ ነው የምረዳው። የሶማሌላንድ ከእስራኤል እውቅና ማግኘት የተወሰነውን የሶማሌላንድ የፖለቲካ ኤሊት ሊያስደስተው ቢችልም በህዝብ ዘንድ ግን የሚኖረው ተቀባይነት በጣም አናሳ እንደሚሆን መገመት ይቻላል። ከኢትዮጵያ ጋር ተፈርሞ የነበረው የመግባቢያ ሰነድ ሃገሪቱ ላይ የፈጠረውን ትርምስ የምናውቀው ነው። ህዝብ አልተቀበለውም ስለዚህ መንግሥቱም ከሥልጣን ተወገደ፣ ስምምነቱም በዝምታ ተቀበረ። ይሄ የእሥራኤል እውቅናም የሚቀሰቅሰው ማዕበል እንደሚኖር ይታመናል።
በመጀመርያ ደረጃ ሶማሌላንድ ውስጥ እስራኤል የጦር ሠፈር የማግኘት እድሏ የመነመነ ነው። ሶማልያን ጨምሮ እነ ሳውዲም ሆኑ ግብፅና ቱርኪያ ይህንን አይነቱን ነገር በዝምታ አይመለከቱም። የእስራኤል እዚያ መኖር ለሃገራቱ የደህንነት አደጋ የሚደቅን ስለሆነ አቅማቸው በፈቀደ ልክ ይታገሉታል ደግሞ አቅማቸው በቀላሉ የሚገመት ስላይደለ ሶማሌላንድን ብዙ ዋጋ ያስከፍላታል። ሶማሌላንድ በውስጧ በርካታ መጓተቶች ያሉባት ክልል እንደሆነች ይታወቃል። የጋዛ ፍልስጤሞችን ማስፈር የሚለውም ነገር የሚሰራ አይደለም። የአካባቢው ሃገራት በሙሉ የሚቃወሙትን ነገር ለማድረግ የሚያስችል ተጨባጭ ሁኔታ ሶማሌላንድ ውስጥ የለም።
ሌላው ትልቁ ችግር የእስራኤል እውቅና በሶማልያና በአካባቢው ሃገራት ላይ የሚፈጥረው ውጥረት ነው። ሶማልያ፣ እስራኤልን ተከትለው ሌሎች ሃገራትም እውቅና ሊሰጡ ይችላሉ የሚል ስጋት ካደረባት፣ ከዲፕሎማሲው ይልቅ የሃይል እርምጃ ወደ መውሰድ ልትሸጋገር ትችላለች። ይህም በሁለቱ ወገኖች መካከል ደም አፋሳሽ ጦርነትን ሊቀሰቅስ ይችላል። ጦርነት የተቀሰቀሰ እንደሆነ ደግሞ ጉዳቱ በቀላሉ የሚገመት ላይሆን ይችላል። ሌሎች እንደ አል-ሸባብ ያሉ ድርጅቶች ደግሞ የእስራኤልን መምጣት ደጋፊዎቻቸውን በማብዛት ሃይላቸውን ለማጠናከርያነት ሊጠቀሙበት ይችላሉ። ስለዚህ የእስራኤል እውቅና ለሶማሌላንድ ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ሊበዛ የሚችልበት አጋጣሚ የገዘፈ ሆኖ ነው የሚታየኝ።
ይህንን አጋጣሚ ተጠቅማ ኢትዮጵያም እውቅና ትስጥ ለሚሉ አጉል መካሪዎች የምላቸው አደብ ያዙ ነው። ኢትዮጵያ ለሶማሌላንድ እውቅና ብትሰጥና በእሳቱ ላይ ቤንዚል ብታርከፈክፍ ወላፈኑ እንደሚገርፋት ልናውቅ ይገባል። ደግሞም የአፍሪካ ህብረት መስራች የሆነች ሃገር የአፍሪካ ህብረት ያወገዘውን ተግባር መፈጸም ክብሯን አይመጥንም። ስለዚህ ተረጋጉ! ማለት እወዳለሁ፡፡
🗣️ የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው?
አስተያየትዎን ያጋሩ! 👇
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

Address

St. Louis, MO

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when RN05 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to RN05:

Share