RN05 ከኢትዮጵያ እና ዲያስፖራ የሚተላለፍ ሚድያ!
አዲሱን ዩቱብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ:
https://www.youtube.com/c/RN05channel

https://t.me/RNZeroFive

https://rnzerofive.com/

ጋዜጠኛ ፀዳለ ጌችን ለምን አስተያየት ሰጠችበት ብለው "ህወሃትን ናፋቂ ናት" የሚሉ ተደማሪዎች በቀዳሚው ኢህአዴግ ዘመን ያልተወለዱና የሰራችዉን ያላዩ የዳግማዊ ኢህአዴግ ትውልዶች ወይንም የ ...
11/29/2025

ጋዜጠኛ ፀዳለ ጌችን ለምን አስተያየት ሰጠችበት ብለው "ህወሃትን ናፋቂ ናት" የሚሉ ተደማሪዎች በቀዳሚው ኢህአዴግ ዘመን ያልተወለዱና የሰራችዉን ያላዩ የዳግማዊ ኢህአዴግ ትውልዶች ወይንም የ 8 ዓመት ሕፃናት አልያም...ለመደመር ሲሉ አይምሮዋቸዉን በሾርት ሚሞርያዊነት የመደቡ መሆን አለባቸው!
በዛ ላይ ጌች እንኳን የተቸዉን ሲከላከል የዋለ ተወካይ ከፀዳለ ጎን ነበራቸው! በነገራችን ላይ በብልፅግና ደጋፊዎች የመናገር ነፃነት ህሳቤ ጌችን መጠየቅ, በሀሳብ መሞገት የሚያስጠይቅ ከሆነ ተቃውሞ ማንሳት የነበረባቸው ፀዳለ ላይ ሳይሆን የፕሮግራሙ አዘጋጅ ጋዜጠኛ መህዲ ሃሰን ላይ ነበር:: ምክንያቱም ጌችን ሲያንገላታ የዋለው አሱ ስለነበር:: እነሱ ግን ጌችንም መህዲን ሲያደንቁ ነው የሚስተዋሉት! እናም የፕሮፖጋንዳው መርህ ምንድን ነው? የሚለዉ የሚያውቁት ያው ከመርህ ምሕዋር ዉጭ የሆኑት አካላት እንጂ ማን ሊሆን ይችላል?


🗣️ የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው?
አስተያየትዎን ያጋሩ! 👇
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

🚩"አብልጠህ የምትወደዉን ትከተላለህ! የተከተልከዉን ትሆናለህ!"👉ቲክቶከሮቻችን ራሳችንን እንድናይባቸው የመረጥናቸው ባህሪዎቻችንና መስታዎቶቻችን ናቸው !~~~~~~~~ ዋው! ይህ የመኪና ሽልማ...
11/29/2025

🚩"አብልጠህ የምትወደዉን ትከተላለህ! የተከተልከዉን ትሆናለህ!"
👉ቲክቶከሮቻችን ራሳችንን እንድናይባቸው የመረጥናቸው ባህሪዎቻችንና መስታዎቶቻችን ናቸው !
~~~~~~~~

ዋው! ይህ የመኪና ሽልማት እንዲሁም ያንን አስከትሎ የገንዘብ፣ የድርጅቶች አምባሳደርነት ወዘተ የተዘጋጀው ለአመቱ ምርጥ ሃኪም ፣ ለአመቱ ልዩ መምህር፣ ለአመቱ ምርጥ ሳይንቲስት፣ ለምርጥ የአመቱ አሰላሳይ፣ለምርጥ የአመቱ ጸሃፊ፣ ለምርጥ የህዝብ አገልጋይ አልያም ለምርጥ ስብእና አይደለም! ለአመቱ "ምርጥ" ቲክቶከር እንጂ!
በኢትዮጵያ ስታንዳርድ "ምርጥ" ቲክቶከር ለመሆን ደግሞ መመዘኛው ምንድነው? ያልን እንደሁ፡ መመዘኛው በአብላጫው "ሰግጥና ፈምስ!" የሚል ነው፡፡ ይህ ማለት ደግሞ ምንም አይነት የሞራል፣ የባህልና መሰል ማእቀፎችን ጥሰህና የስነምግባር ድንበሮችን አልፈህ መንጋ እስካበዛልህ ድረስ ያሻህን ፈጽም! ፣ቢሻህ ተሳደብ፣ ቢሻህ እርቃንህን ደንስ፣ ቢሻህ ትሪ ሙሉ ምግብ ዘርግተህ አላምጥ፣ ቢሻህ አንዱን በአንዱ ላይ አስነሳ፣ ቢሻህ በየሳምንቱ ሃይማኖትህን ቀያይር፣ ቢሻህ ሁሉንም ተራ በተራ ዘርጥጥ፣ ቢሻህ ቢሻህ፣ ቢሻህ " የሚል ነው!
አሁን ከጥቂቶች በቀር አብዛኞቹን የሃገራችን ቲክቶከሮች ልጆቻችን እንዳያይዋቸውና አርዓያ እንዳያረጓቸው የምንደብቅባቸው ከመሆናቸው ባሻገር በእርግጥ ለማህበረሰቡ መታነጽ፣ ለህዝቡ አንድነት፣ለጥሩ ስነምግባር፣ እንደ እነሱ ሁኑ ተብሎ ልጆች እንዲመከሩ ወዘተ የሚያበረታታ ጠብ የሚል ነገር አላቸው ወይ ቢባል መሬቱ የሚጠብ ይመስለኛል፡፡
በእርግጥ እኔ በግሌ እንኳንስ የቲክቶክ፣ የዩትዩብም፣ የፌስቡክም ፣ የትዊተርም በአጠቃላይ የሁሉም ሶሻል ሚድያዎች "ተጽእኖ" ፈጣሪዎች በየአመቱ ቢሸለሙ ድጋፍ እንጂ ተቃዉሞ የለኝም። ተቃዉሞዬ ግን ምሳሌ እያደረግናቸዉና ታዳጊዎች ላይ ተጽእኖ እንዲፈጥሩ የምንፈቅድላቸው እነማንን ነው? የሚለዉና ከመንጋ መሰብሰብ ባሻገር ለተመራጭነት የምንመርጥባቸው የበጎ ተጽእኖ መስፈርቶችን የሚለካዉና የሚያስቀምጠው አካል ማን ነው? ገንዘብ ስላለው ብቻ ያሻዉን የሚመርጥ ወይንስ ምን አይነት ሃላፊነት መዉሰድ የሚችል አካል ነው? የሚለው ላይ ነው፡፡ አምባሳደር እያደረገ የሚሾማቸው ተቋም ንግዱን ከማሳለጥ ባሻገር ለማህበረሰቡ ምን አይነት መልዕክቶችን እያስተላለፈ ነው? የሚለው ነው፡፡ ፈመሱ እያለ እየጋበዘ ወደ አደባባይ የሚያወጣቸውና ከግል እውቅናቸው ባሻገር በማህበረሰቡ የእለት ተእለት ህይወት ዙርያ ምን አይነት በጎ ወይንም አሉታዊ ተጽእኖ እየፈጠሩ እንደሆነ በአግባቡ የማይሞግታቸው የሚድያ አካል ምን እያደረገ ነው? የሚለው ነው? ወዘተ
ምክንያቱም ሚልዮን ተከታዮችን ያስከተለ አንድ ሰው በስነምግባር መለክያ የማያልፍ ከሆነ ተመራጭነቱ የማስታወቅያ ገበያ ለሚሆንለት ለሶሻል ሚድያዉና ለራሱ ገቢ እንጂ ለማህበረሰብ ሊሆን አይችልምና፣ ይልቁንም ብዙ ተከታዮችን ማሰባሰብ ባይችል እንኳ በላቀ ስነምግባር ተጽእኖ ለመፍጠር የሚሞክረዉን ግን ደግሞ መንጋ ስላላሰለፈና ሶሻል ሚድያዎቹ ስላልሸለሙት ብቻ በማህበረሰባችን ዘንድ ከተሸላሚነት ሊታገድ አይገባምና ነው፡፡
እናም- "አብልጠህ የምትወደዉን ትከተላለህ! የተከተልከዉን ትሆናለህ!" እንዲሉ
ቲክቶከሮቻችን ራሳችንን የምናይባቸው ባህሪዎቻችንና መስታዎቶቻችን እንዲሆኑ ፈቅደናል፡፡ የተጽእኖ መለክያዎቻችን መንጋ ብቻ እስከሆነ ድረስ በማንኛዉም መንገድ መንጋ የሰበሰበ ሁሉ ተጽእኖ ፈጥሮብናል ወይንም እንዲፈጥርብን ይጠበቃል የሚል የገበያ ሜንታሊቲ ያዳበርን መሆኑን እዉቅና እስከሰጠን ድረስ በባህሪ እኛ እነሱ ነን! እነሱም እኛ ናቸው! እናም የምንሰጣቸው እውቅናና ሽልማት ለራሳችንም መሆን ለምንፈልገው ባህሪ እና ምኞት የምንሰጠው ነው!
እናም ጎበዝ "እየሰገጥን!!" ለማለት ነው ፡፡ ይሄው ነው!
🗣️ የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው?
አስተያየትዎን ያጋሩ! 👇
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

🛑በቆዳዋ "በእግዛብሄር የምትጠበቀዋ፣ ዲሞክራሲያዊቷ፣ የሰባዊ መብት ጠባቂዋ፣ ስልጡኗ" የምትሰኘው እስራኤል አጥንትና ስጋዋ (ዉስጧ) ይህና ከዚህም የባሰ ነው!~~~~~~~~ "እስራኤል "በተጨ...
11/29/2025

🛑በቆዳዋ "በእግዛብሄር የምትጠበቀዋ፣ ዲሞክራሲያዊቷ፣ የሰባዊ መብት ጠባቂዋ፣ ስልጡኗ" የምትሰኘው እስራኤል አጥንትና ስጋዋ (ዉስጧ) ይህና ከዚህም የባሰ ነው!
~~~~~~~~

"እስራኤል "በተጨባጭ የሚታይ የተደራጀ እና ሰፊ መንግሥታዊ የስቅይት ፖሊሲ" እየተገበረች ስለመሆኑ ማስረጃ ማግኘቱን የተባበሩት መንግሥታት የባለሙያዎች ኮሚቴ አስታወቀ። ኮሚቴው፤ እስራኤል በእስር ላይ ያሉ ፍልስጤማውያን ላይ የምትፈጽማቸው 'የስቅይት ተግባራት'፤ "ጦር ወንጀል እና በሰብአዊነት ላይ የሚፈጸም ወንጀል" ተብለው የሚፈረጁ እንደሆኑ ድምዳሜ ላይ ደርሷል።"
BBC News Amharic
🗣️ የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው?
አስተያየትዎን ያጋሩ! 👇
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

11/26/2025

🌋አለም ስለ ሃይሊ ጉቢው ድንገተኛ የእሳተ ጎመራ ፍንዳታ ማዉራቱን ቀጥሏል!
~~~~~~~~~+


"ታሪካዊው ፍንዳታ፡ ሃይሊ ጉቢ ከ10,000 ዓመታት በኋላ ነቃ" የሚለው ዜና በአለም ሚድያዎች የጋራ ዜና ሆኖ ቀጥሏል፡፡

ሃይሊ ጉቢ እሳተ ገሞራ በኢትዮጵያ ሰሜን ምስራቅ አፋር ክልል፣ ኤርታሌ የተባለው የእሳተ ገሞራ ሰንሰለት አካል ሲሆን፣ ከ10,000 ዓመታት በላይ ዝም ብሎ ከቆየ በኋላ በቅርቡ (በኖቬምበር 23, 2025 አካባቢ) በድንገት ተነስቶ ፍንዳታ አሳይቷል።

ፍንዳታው በአፋር ክልል፣ የኤርታሌ እሳተ ገሞራ ሰንሰለት ደቡባዊ ጫፍ የተካሄደ እና በታሪክ ተመዝግቦ ከሚታወቀው ጊዜ አንስቶ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ የተከሰተ ፍንዳታ ነው:: ፍንዳታው ከ10,000 እስከ 12,000 ዓመታት የቆየ ከእንቅልፍ መንቃትና ምልክት ሳያሳይ ድንገት የመፈንዳት ሂደት እንደነበረው ሳይንቲስቶች ይናገራሉ። በሌላ በኩል የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የጂዮ ፊዚክስና ስፔስ ሳይንስ ተመራማሪው ዶ/ር ኤልያስ ለዌ በበኩላቸው በአካባቢው ከወራቶች በፊት በተከታታይ መለስተኛ ፍንዳታዎችን ሲመዘግቡ መቆየታቸዉንና ሰሞኑን ደግሞ የመሬት መወጣጠር እንደነበር ተናግረዋል፡፡
ፍንዳታውን በተመለከተ በጣም ኃይለኛ የነበረ ሲሆን፣ የአመድ ደመና ከ10 እስከ 15 ኪሎ ሜትር (45,000 ጫማ) ከፍታ ላይ ተንሳፍፏል ነው የተባለው ። ከፍተኛ ከፍታ ላይ የደረሰው የእሳተ ገሞራው አመድ በቀይ ባህር በኩል ተሻግሮ ወደ የመን፣ ኦማን እና አልፎ ተርፎም ወደ ሕንድ አቅጣጫ መጓዙ ተዘግቧል።
በአካባቢው ላይ ምንም ዓይነት የሰው ሕይወት ወይም የከብት መጥፋት ሪፖርት ባይደረግም፣ በአካባቢው በሚገኙ መንደሮች ላይ አመድ በመርጨቱ የአካባቢው ማኅበረሰብ የሚተዳደርበት የከብት መኖ ላይ ኢኮኖሚያዊ ተጽዕኖ ሊኖረው እንደሚችል ተገልጿል። በተጨማሪም፣ አመዱ በአየር መንገዶች ላይ ችግር በመፍጠሩ ለበረራ መቋረጥ እና የአውሮፕላን መስመሮች መለወጥ ምክንያት ሆኗል። ዶ/ር ኤልያስ ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በሰጡት ማብራርያ እንዲህ አይነት ፍንዳታ ሲከሰት አመዱ ለሳንባ ካንሰር ሊያጋልጥ ስለሚችል ገሞራው በሚፈነዳበት ሰሞን የአካባቢው ነዋሪዎች ጭምብል እንዲለብሱ መክረዋል፡፡
ሳይንሳዊ ጠቀሜታዉን በሚመለከት ለረጅም ጊዜ የተኛ እሳተ ገሞራ በድንገት መንቃት እንዴት ሊከሰት ይችላል? የሚለውን ለመረዳት ለሳይንቲስቶች ትልቅ ትምህርት ሰጥቷል ነው የተባለው ። ይህ ክስተት በዘመናዊው ምልከታ ከተከሰቱት ትልልቅና ብርቅዬ የእሳተ ገሞራ እንቅስቃሴዎች አንዱ ተደርጎ እንደሚወሰድ አለም አቀፍ ሚያዎችና የሙያው ባለቤቶች በስፋት እያብራሩ ይገኛሉ።
🗣️ የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው?
አስተያየትዎን ያጋሩ! 👇
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

⛔️ጭካኔ ተፈሪ እንጂ ተከባሪ አያደርግም!🚩ስለ ዜጎቻችን ስንቆረቆር -በጉዳታቸው ክፋት ልክ እንጂ በጎጂው ማንነት ላይ ተመስርተን ሊሆን አይገባም!~~~~~~~~ ይህ የክፋት ጥግን በሚያሳይ መ...
11/26/2025

⛔️ጭካኔ ተፈሪ እንጂ ተከባሪ አያደርግም!
🚩ስለ ዜጎቻችን ስንቆረቆር -በጉዳታቸው ክፋት ልክ እንጂ በጎጂው ማንነት ላይ ተመስርተን ሊሆን አይገባም!
~~~~~~~~

ይህ የክፋት ጥግን በሚያሳይ መልኩ እጁን በመጥረብያ፣ ጆሮዉን በቢላ በፋኖ አማካኝነት በጭካኔ የተቆረጠ የተባለዉን ወገናችን አሳዛኝና አስደንጋጭ ቪደዮ በሶሻል ሚድያው እየተሰራጨ ሲዘዋወር በተደጋጋሚ አየሁት፡፡ ይህን ወንጀል ሊፈጽም የቻለ ጨካኝ አካል የሃይማኖት ቤቶችንና የሃይማኖት አባቶችን ብሎም ያልታጠቁ ንጹሃንን እየገደለ ዜና መሆኑ እንዲታረምና እንዲስተካከል ካላደረገዉና እለት ከእለት ጭራሽ የባሱ ዘግናኝ ድርጊቶችን የሚፈጽም ከሆነ በህዝቡ ዘንድ መፈራትን እንጂ መከበርን እንደማያመጣለት ሊገነዘበው ይገባል፡፡ ለፖለለቲካም ተብሎ የተቀመረ ከሆነ ጉዳዩ የታወቀ እለት ቀማሪው ከህዝብ ልብ እንደሚወጣና ፈጠነም ዘገየ ተጠያቂም እንደሚሆን ሊያውቀው ግድ ይላል
በሌላ በኩል የብልጽግና ተደማሪ አክቲቪስቶችም ሆኑ አንዳንድ የመንግስት ሹማምንት ጭምር ይህንን አሰቃቂ ወንጀል ለማጋለጥ መረባረባቸው አበጃችሁ የሚያሰኛቸው ሲሆን ይህ ተፈጸመ የተባለው አውሬያዊ ወንጀል እነሱ በሚደግፉት አካል ቢፈጸም ወንጀሉን እንደወንጀል ያወግዙት ነበር ወይ? የሚለዉን ጥያቄ ለሚያስብ ሰው ያለንበት ሁኔታ፣ ጩኸታችንና ተቆርቋሪነታችን ለዜጎችና ለሰላማዊው ህዝብ በመጨነቅ ሳይሆን በፖለቲካና በጥቅም ወገንተኝነት መሆኑን ይረዳል>> ለምን ቢሉ እነዚህ አካላት በሚደግፉት መንግስት ወታደሮችና በኤርትራም መንግስት ወታደሮች አማካኝነት ኢትዮጵያዊያን ላይ የተፈጸሙትን ወንጀሎችና አሁንም በደቡብና በሰሜን የሃገራችን ክፍሎች በሰላማዊ ዜጎቻችን ላይ የሚፈጸሙትን ወንጀሎችን ሁሉ "ለጽድቅ ነው!" ሲሉና ተቺዎችን እየተከታተሉ ለማሸማቀቅ ሲሞክሩ የነበሩና ያሉ ተደማሪዎች በመሆናቸው ነው!
ጎበዝ የምደግፈውና የምንነቅፈው፣ የተደመርንለትና የተቀነስንበት አካል እንዳለ ሆኖ በየትኛዉም አጽናፍ ያሉ ሰላማዊ ዜጎቻችን ላይ የሚደርሰዉን ወንጀል በጋራ ልናስተጋባና ልንከላከል ይገባል!
አለመታደል ሆኖ ዛሬ ወገኖቻችን በኦሮምያም፣ በአማራ ክልልም፣ በቤሻንጉልም ሆነ ሌሎች ቦታዎች ሁሉ ሰላማዊ ዜጎች ከታጣቂዎችም ከመንግስትም ከሁሉም አቅጣጫ ይገደላሉ፣ ይታፈናሉ፣ ይደፈራሉ ወዘተ። ይህም በመሆኑ ስለ ዜጎቻችን ስንቆረቆር -በጉዳታቸው ክፋት ልክ እንጂ በጎጂው ማንነት ላይ ተመስርተን ሊሆን አይገባም! ለማለት ነው! ሄው ነው!
🗣️ የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው?
አስተያየትዎን ያጋሩ! 👇
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

? ከአቶ ጌታቸው ረዳ ምን ተጠብቆ ነበር?~በነገራችን ላይ አቶ ጌታቸው ጠቅላይ ሚ/ር አብይ አሕመድ ጀኖሳይድ ስለመፈፀማቸው በጋዜጠኛው ሲጠየቁ "አዎ ምን ጥያቄ አለው ፈፅሟል እንጂ!"ብለው አ...
11/25/2025

? ከአቶ ጌታቸው ረዳ ምን ተጠብቆ ነበር?
~
በነገራችን ላይ አቶ ጌታቸው ጠቅላይ ሚ/ር አብይ አሕመድ ጀኖሳይድ ስለመፈፀማቸው በጋዜጠኛው ሲጠየቁ "አዎ ምን ጥያቄ አለው ፈፅሟል እንጂ!"ብለው አላረጋገጡም, ግን ደግሞ ጠቅላዩ ' በፍፁም ጀኖሳይድ አልፈፀሙም!" ብለውም አልተከላከሉም!!
አቶ ጌታቸው በጦርነቱ ወቅት ጀኖሳይድ መፈፀሙን አምነዋል, ፈፃሚዎቹ ደግሞ በደፈናው የተለያዩ አካላት መሆናቸዉን ጠቅሰዋል:: በስተመጨረሻም ይህን የተለያዩ አካላት ጀኖሳይድ ፈፅመዉበታል ያሉትን ጦርነት የመሩት ደግሞ ዶ/ር አብይ መሆናቸዉን አምነዋል::
እና ቃለ ምልልሱን የተከታተለ ሁሉ በሂደቱ በተዘዋዋሪም ቢሆን የዓለም ህዝብ በአብዛኛው የሚረዳው የትኛዉን ሃሳብ ይመስላቹሃል?



🗣️ የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው?
አስተያየትዎን ያጋሩ! 👇
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

🔔ለብልጽግናና ተደማሪዎቹ ወቅቱ "የጽሞና ጊዜያቸው" ቢሆን!~~~~~~~~~~~~~~~~~ ሁሉም መንግስት፣ ተቋምም ሆነ አቋም ራሱን የሚፈትሽበት፣ ከፊት ለፊት ብቻ ሳይሆን ከተቃራኒው በኩል ራሱ...
11/24/2025

🔔ለብልጽግናና ተደማሪዎቹ ወቅቱ "የጽሞና ጊዜያቸው" ቢሆን!
~~~~~~~~~~~~~~~~~

ሁሉም መንግስት፣ ተቋምም ሆነ አቋም ራሱን የሚፈትሽበት፣ ከፊት ለፊት ብቻ ሳይሆን ከተቃራኒው በኩል ራሱን የሚያይበት የራሱ የሆነ የጥሞና ጊዜ አለው! ያንን ወሳኝ ወቅት መለየት እና በአግባቡ መጠቀም ደግሞ የባለቤቱ ዋና ኃላፊነት ነው።
አሁን በእኔ አስተሳሰብ፣ አገሪቱን በበላይነት የሚመሩት የብልጽግና ፓርቲና ተደማሪዎቹ የጽሞና ወቅት የሚያሻቸው ሰአት ላይ የሚገኙ ይመስላል። ይህ ማለት ከወትሮው የፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ እና ግላዊ እሳቤዎች ወጥቶ ለአፍታ ቆም ማለት እና በጥልቀት መመርመርን ይጠይቃል።

👉የጥሞና ትኩረት አቅጣጫዎች፡
1️⃣የኢኮኖሚው ምሰሶዎች: የሀገሪቱን ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ በጥልቀት መመርመር፣ "እያጠገብናችሁ ነው፣ ምን ጎድሎ!" ከሚለው ግትር አካሄድ ወጥቶ የህዝቡን የኑሮ ውድነት በህዝቡ ምላስ ለመቅመስ መሞከርና ዉድነቱን መቀነስ የሚችሉ ዘላቂ መፍትሄዎችን መፈለግ።
2️⃣የማኅበራዊ ትስስር: "ድሮም ትጠላሉ ነበር ወይንም አዲስ ችግር የለም አልያም ህዝቡ ፍቅር በፍቅር ነው ! " የሚሉ የተሳሳቱ ትርክቶችን ጋብ አድርጎ ማኅበራዊ መስተጋብሩን ማጠናከር እና በዜጎች መካከል ያለውን መተማመን የሚገነቡ ስራዎችን ለይቶ መተግበር።
3️⃣በዋናነት የፖለቲካዊ መስተጋብር: "የሚመጥነን አልያም የሚችለን ተቃዋሚ የለም! ከእና ዉጭ ለሃገርና ለዲሞክራሲ የሚታመን የለም!" የሚሉ የሚመስሉ ፖለቲካዊ የማግለያ መሳርያዎችን በመተዉና ከገፊነት በመውጣት ከሁሉም የፖለቲካ ኃይሎች ጋር ያለውን ግንኙነት እንደገና መፈተሽ፣ የሃገሪቱን ሚድያዎችን ተቋማት እኩል እንዲጠቀሙ ማድረግ፣ ሁሉን አቀፍ ውይይት የሚያደርጉበትን ሁኔታ መፍጠር እና አገራዊ መግባባትን (National Consensus) ማዕከል ያደረገ እርምጃ መውሰድ። በዚህም ሊመጣ የሚችለዉን ፖለቲካዊ አምባገነንነትንና መቀንጨርን መታደግ!
4️⃣የሰላም ተቀዳሚነትና ስጋቶችን መፍታት: ብልጽግና ፓርቲ በሀገር ውስጥ እየተሳተፈባቸው ያሉ ተጨባጭ ጦርነቶች እና እንዲሁም ከውጭ ባሉ የጦርነት ስጋቶች ላይ ያለውን አመለካከት በግልጽ መፈተሽ ይኖርበታል።
"እናሸንፋለን! ማንም አይችለንም!" ከሚለው የዘወትር ግትር አቋም እና "ሰላምን የሚሻ እኔ ያልኩትን ብቻ መመዘኛ ያድርግ!" ከሚል አታካችነት ባሻገር፣ ሃገሪቱ የሁሉም መሆኗንና ሁሉም ባለድርሻ መሆኑን በመገንዘብ በሰጥቶ መቀበል መርህ እነዚህን ግጭቶች እና ስጋቶች በዘላቂ ሰላም የሚቋጩበትን መንገድ በአስቸኳይ እና በጥልቀት መመርመር ያስፈልጋል።

⚠️ ወሳኝ መደምደሚያ: ጊዜን አለማባከን
ብልጽግና ወቅቱ የጥሞና ጊዜ የሚያስፈልግበት ሰአት ነው ብሎ ቢጠሙን በእርግጥም ለሀገር የሚያስፈልጉትን አስፈላጊ እና ወሳኝ እርምጃዎችን ለመውሰድ የሚያስችለዉን እዉነተኛ አቅጣጫ ለማግኘት እና ወደ ዉድቀት ሳይሆን ወደ ፖለቲካዊ ስኬት በመምጣት ሃገርንና ህዝብን ለማዳን ወሳኝ ይሆንለታል።
ነገር ግን፣ ብልጽግና ፓርቲና ተደማሪዎቹ የሚያደርጉት ነገር ሁሉ ትክክልና ብልጽግና ብቻ መሆኑን በማመን ወይንም አይንና ጆሯቸዉን በመድፈን የጥሞና ጊዜ እንደማያሻቸው በመቁጠር በዋዛ ፈዛዛ የሚያሳልፉት እንደሁ፣ አሁን ያሉት ውስብስብ ውጥረቶች ተባብሰው ለራሳቸውም ሆነ ለአጠቃላዩ የሀገር ሕልውና የሚተርፍ አደጋ መከተሉ የማይቀር ስለመሆኑ ሩቅ ሳንሄድ ከሀገራችን ታሪክ የምናውቀው እውነት ነው። በመሆኑም አሁን ለብልጽግና የቀረው ጊዜ - ጥሞና ዉስጥ በመግባት ከተሰቀለበት ማማ ወርዶ መሬት ላይ ባለዉ እዉነታ ተመስርቶ በጥልቅ አስተሳሰብ ለተሃድሷዊ ዉስኔ (Decision) የሚንቀሳቀስበት ብቻ ነው። ለማለት ነው! ይሄው ነው
🗣️ የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው?
አስተያየትዎን ያጋሩ! 👇
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

🚩ሙስሊሙ ማስታገሻ ሳይሆን ዘላቂ ፈውስ ይሻል!~~~~~~~~~~~~~ ሰሞኑን መጅሊስ የትምህርት ሚኒስቴር ሙስሊም ተማሪዎች ላይ የያዘዉን የተሳሳተ አቋም ለመቃወም ጠንከር ጠንከር ያሉ ቃላትን ...
11/22/2025

🚩ሙስሊሙ ማስታገሻ ሳይሆን ዘላቂ ፈውስ ይሻል!
~~~~~~~~~~~~~

ሰሞኑን መጅሊስ የትምህርት ሚኒስቴር ሙስሊም ተማሪዎች ላይ የያዘዉን የተሳሳተ አቋም ለመቃወም ጠንከር ጠንከር ያሉ ቃላትን ተጠቅሟል። ሚኒስቴሩንም ሆነ ሌሎች የሃገሪቱን ህገ መንግሥት በጣሰ መልኩ የሙስሊሙን የመማር መብት ለመግፈፍ የሚሞክሩ አካላትን በሙሉ በህግ ተጠያቂ አደርጋለሁ ሲልም ዝቷል። በየክልሉ ያሉ መጅሊሶችንም በመቀስቀስ የተቃውሞ ድምፆቻቸውን እንዲያሰሙ አድርጓል። ይህንንም የሙስሊሙን ከፍተኛ ተቃውሞ ተከትሎ የትምህርት ሚኒስቴር መግለጫ ሰጥቷል። በመግለጫው ላይ ሙስሊሞችን በቀጥታ ላለመተንኮስ ሙከራ ሲያደርግ ተስተውሏል። እንደተለመደው እንደተፈለገ ሊተርጎሙ የሚችሉ ሃረጎችን በማስቀመጥ ከሃይማኖት ጋር በተገናኘ ሊያስቀምጡ የፈለጉትን ገደብ አድበስብሰው አልፈዋል።
ይሄ ሁሉ መልካም ነው። ይሄ ሁሉ ከዚህም ቀደም በተደጋጋሚ ያየነው ድራማ ነው። ልክ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ እንዳየነው የሙስሊሙ ህዝብ ተቃውሞው ሲበረታ ተቃውሞውን ለማርገብ መጅሊስ ተቃዉሞዉን ይገልጻል። ትምህርት ሚኒስቴርም የሙስሊሙን ቁጣ ለማርገብ ለዘብ ይላል። ነገሮች በዚያው ተድበስብሰው ይቀራሉ። መጅሊሱም፣ ህዝበ ሙስሊሙም ቀድሞ ወደ ነበሩበት ማንጎላጀት ይመለሳሉ። ያኔ ይህንን አጋጣሚ አድፍጠው ሲጠብቁ የቆዩት በኢስላም ጥላቻ የተመረዙ ባለሥልጣናት እነኝህ እንደተፈለገ ሊተረጎሙ የሚችሉ አንቀፆችን ከየመሳብያው እያወጡ ዋቢ በማድረግ ሙስሊሞች በሚንቀሳቀሱባቸው ጎዳናዎች ላይ ጋሬጣ መነስነሱን ይያያዙታል። ከሙስሊሙ በተለየ መልኩ ፣እነዚያ ደማቸው በኢስላም ጥላቻ የተመረዙ ባለሥልጣናት ሙስሊሙ ላይ ሲዶልቱ እንጂ ተኝተው አያድሩም። አሁንም ለጊዜው ለዘብ ማለታቸው ወይንም ነገሮችን አድበስብሰው ለማለፍ የፈለጉት የሙስሊሙን ቁጣ ለማስተንፈስ እንጂ አቅጣጫ ቀይረው አይደለም። እንደተለመደው አዘናግተውን ከኋላ መጥተው ማጅራታችን ላይ ጉብ ይላሉ።
እነኝህ በኢስላም ጥላቻ የተመረዙ አካላት ተስፋ ቆርጠው አቅጣጫ እንዲቀይሩ ካስፈለገ ሙስሊሙ በጊዚያዊ ድል መብቃቃቱን አቁሞ ጥያቄው ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እልባት እንዲያገኝ ያለማቋረጥ መሥራት ይኖርበታል። መጅሊሱ ይህንን ጉዳይ የሚከታተል ኮሚሽን ማቋቋሙን ሰምተናል። የዚህ ኮሚሽን ግብ የሙስሊሙን ሃይማኖቱ መደራደርያ ሳይደረግ የመማር መብት ጥያቄ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እልባት እንዲያገኝ ማስቻል ሊሆን ይገባል። ይህ ኮሚቴ ሲቋቋም በአደባባይ እንደተነገረን ሁሉ ሥራውን ጨርሶ ሲፈርስም በግልጽ ሊነገረን ይገባል። ምንም እንኳን ኮሚሽኑ ተጠያቂነቱ ለመጅሊሱ ቢሆንም መጅሊሱ ተጠያቂነቱ ለህዝበ ሙስሊሙ ስለሆነ ይህ ያቋቋመው ኮሚሽን ያሳካቸውና ያላሳካቸው ግቦች ለህዝቡ በዝርዝር ሊነገረው ይገባል። ይሄ ተመዟል የተባለው የመጅሊሱ የ "ይበቃል!" ጎራዴ የጠላቶቹን የጥላቻና የመብት ገፈፋ ልማድ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ሳይቀላ ወደ አፎቱ መመለስ የለበትም።
ነገር ግን፣ ወንድም እህቶች፣ ይሄ ሊሳካ የሚችለው ሙስሊሙ ማህበረሰብ የመጅሊሱን እንቅስቃሴዎች በንቃት እስከተከታተለና ሃላፊዎቹን ተጠያቂ ለማድረግ እስከተዘጋጀ ድረስ ብቻ ነው። አለበለዚያ ግን ስጋቴ ልክ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ እንዳየነው አሁን ለአንድ ተጨማሪ ጊዜ ከፈውስ ይልቅ በማስታገሻ አንዳንሸወድ ነው።
🗣️ የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው?
አስተያየትዎን ያጋሩ! 👇
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

ሃማs የተገደሉ የእስራኤል ታጋቾችን አስክሬን ከግብፅ በተላከ መቆፈርያ እያወጣ ያስረክባል (ይህ ስምምነታቸዉን ስለሚያሟላ መሆን ያለበት ነው ), ገራሚው ግን አሁንም እስራኤል በየቀኑ አዳዲስ...
11/20/2025

ሃማs የተገደሉ የእስራኤል ታጋቾችን አስክሬን ከግብፅ በተላከ መቆፈርያ እያወጣ ያስረክባል (ይህ ስምምነታቸዉን ስለሚያሟላ መሆን ያለበት ነው ), ገራሚው ግን አሁንም እስራኤል በየቀኑ አዳዲስ ፍልስጤማውያንን ትገድላለች! በነገራችን ላይ እስካሁን ድረስ የፍልስጤማውያንን አስክሬን ከፍርስራሾች ዉስጥ ማሽኖችን ተጠቅሞ ማውጣትን እስራኤል አልፈቀደችም!
ግብፅም ሆነች ሌሎች ማሽኖቻቸዉን የላኩት የታጋቾቹ አስከሬኖች ተቆፍሮ እንዱወጡ እንጂ በእስራኤል እና አጋሮቿ ቦምቦች ከህንፃዎች ጋር አብረው ተመተው በየፍርስራሾቹ ስር ለተቀበሩት ለፍልስጤማውያኞቹ አስከሬኖችም ይወጣበት ዘንድ አይደለም!

አለማችን ፍትህ አልባ ነች እንጂ መቼም "ድንቅ" ናት!

📌ተማሪዎችን ግብረገባዊ ለማድረግ ልክ ቫለንቲና ደይ እንደሚከለከለው ሃይማኖታዊ የግዴታ ሥርዓትንም መከልከል?! ትምህርት ሚኒስትርን ማን ያስተምርልን?! መጅሊሱ ሳይረፍድ ሊመክር ይገባል~~~~...
11/19/2025

📌ተማሪዎችን ግብረገባዊ ለማድረግ ልክ ቫለንቲና ደይ እንደሚከለከለው ሃይማኖታዊ የግዴታ ሥርዓትንም መከልከል?! ትምህርት ሚኒስትርን ማን ያስተምርልን?! መጅሊሱ ሳይረፍድ ሊመክር ይገባል
~~~~~~~~~~~

የተማሪዎች የሥነ ምግባር ረቂቅ መመሪያ በውስጡ ምን ምን አካቷል?

"Crazy day፣ olds day፣ Valentine day " እና ሌሎችም አላስፈላጊ የሆኑ ባህልን የማይገልፁ ድርጊቶችን ማክበር ይከለክላል።

መመሪያው በመንግስት፣ መንግስታዊ ባልሆኑ፣ የግል፣ በኃይማኖት ተቋማት የሚተዳደሩ ትምህርት ቤቶችና ከኢትዮጵያ ውጪ ባሉ ኮሚዩኒቲ ትምህርት ቤት በሚማሩ ተማሪዎች ላይ ተፈፃሚ ይሆናል።

በመመሪያው የተማሪዎች መብትና ግዴታዎች ሲቀመጡ በተማሪዎች ግዴታ ስር ፀጉርን በአግባቡ መሰራት/ማሳጠር፣ ከተፈጥሯዊ ጸጉራቸው ውጪ እንዳይጠቀሙ ተቀምጧል።

የሴቶቾ የትምህርት ቤት የደንብ ልብስ ቀሚስ ቁመት ከባት በታች መሆን ያለበት ሲሆን ከአካባቢው ባህል ጋር የማይቃረን ልብስ መልበስ የሚለውም ተካቷል።

በመመሪያው ከተከለከሉ ተግባራት መካከል ሲጋራ ማጨስ፣ አልኮል መጠጣት፣ ጫት መቃም፣ ዕፆችን መጠቀም/ማዘዋወር እንደዚሁም ሞባይልና የሙዚቃ ማዳመጫዎችን ወደ ትምህርት ቤት ይዞ መምጣት ይገኙበታል።

በትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ ኃይማኖታዊ አምልኮ ስርዓትና የፖለቲካ እንቅስቃሴዎችን ማከናወንም በመመሪያው ተከልክሏል።

በመመሪያው ሀገራዊ እሴት ያልሆኑ መጤ ነገሮችን በሰውነት ላይ መነቀስ ሲከለከል፤ ሴት ተማሪዎች የጥፍር፣ የፀጉርና የከንፈር ቀለም ከመቀባትና ከመኳኳል እንደዚሁም አላስፈላጊ ጌጥ ከማድረግ ይከለክላል።

በተጨማሪም በረቂቁ በትምህርት ቤት ውስጥ አላስፈላጊ የሆኑ የኢትዮጵያዊነት ባህልን የማይገልፁ ያላቸውን ድርጊቶች (Crazy Day, Gentle Day, Olds Day, Baby Day, Fruit Day, Tomato
Day, Valentine Day, April the full, Color Day, Pyjama Day…etc) መፈጸም፤ እና ሌሎችም አላስፈላጊ የሆኑ ባህልን የማይገልፁ ድርጊቶችን ማክበር እንደማይቻል ተገልጿል።

የተከለከሉ ተግባራትን በሚፈፅመት ላይ የተለያያ የእርምት እርምጃዎች ሲቀመጡ ቀላል እርምጃ ሊያስወስዱ በሚችሉ ጥፋቶች ስር ከፀጉር ጋር የተያያዙ እና ሌሎች ቀላል ጥፋቶች ተካተዋል።

የትምህርት ቤት ፕላዝማና ኮምፒውተር ለሌላ አላማ መጠቀም፣ በአጥር መዝልና መሽሎክ፣ ከላይ የተጠቀሱ አላስፈላጊ ባህሎችን ማክበር፣ አሉታዊ ምልክቶችን መነቀስ፣ ድብድብ እንደዚሁም ኃይማኖታዊ ስርዓት መፈፀምና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ማድረግ በከባድ ጥፋት ውስጥ ተካተዋል።

የቅጣት እርከኑ እንደ ተማሪዎች የትምህርት ደረጃና ጥፋቱ ሲለያይ ለከባድ የስነ ምግባር ግድፈት በመደበኛ ህግ መሰረት የህግ ተጠያቂነት ይኖራል።

መመሪያው የዲሲፕሊን ክስ አመሰራረት፣ የዲስፕሊን ኮሚቴ ስብጥር እንደዚሁም ተግባርና ኃላፊነትን በዝርዝር አስቀምጧል።

በተጨማሪ መመሪያው በየደረጃው ያሉ የባለድርሻ አካላትን ተግባርያ ኃላፊነትም ዘርዝሮ ሲያስቀምጥ ማንኛውም ትምህርት ቤት ያለ መሸኛ ተማሪዎችን ተቀብሎ መመዝገብንም ከልክሏል።

ትምህርት ሚኒስቴር በመመሪያው ላይ ምክረ ሃሳብ ያላቸው ሰዎች በ https://forms.gle/R72ai6EiMnzZtGsC6 እንዲያቀርቡ ጠይቋል።

ማስፈንጠሪያ (Link)

💥መጅሊስ ሆይ! - ኡማውን በመግለጫ ማጨናበር ይብቃ!!~~~~~~~~  መጅሊሰል አዕላ ለበርካታ ወራት አምጦ አምጦ ሲያበቃ በሂጃብ ጉዳይ አንድ መግለጫ ማውጣቱን ተመለከትን። ምናልባትም መግለጫ...
11/19/2025

💥መጅሊስ ሆይ! - ኡማውን በመግለጫ ማጨናበር ይብቃ!!
~~~~~~~~

መጅሊሰል አዕላ ለበርካታ ወራት አምጦ አምጦ ሲያበቃ በሂጃብ ጉዳይ አንድ መግለጫ ማውጣቱን ተመለከትን። ምናልባትም መግለጫውን አሁን ያወጣው ዶክተር ብርሃኑ አዳማ ላይ በተደረገ አንድ ስብሰባ ላይ በሂጃብ ጉዳይ ከመጅሊሱ ባልሥልጣናት ጋር ስምምነት ላይ ተደርሷል ሲል መናገሩ ይፋ ከሆነ በኋላ በሙስሊሙ ማህበረሰብ ዘንድ የተፈጠረውን መደናገጥ ለማርገብ በሚል ሊሆን ይችላል። አለበለዝያ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ላይ በአጠቃላይ በሃገሪቱ በተለይ ደግሞ አክሱም ላይ በሂጃብ ሰበብ ጭቆና መፈጸም የጀመረው ትላንትና አይደለም። አሁን በዚህ መግለጫቸው እንዳደረጉት መንግሥት የሴቶቹን ህገመንግሥታዊ መብት እንዲያስከብር መለመን ቀደም ብለውም ይችሉ ነበር።
ደግሞ ይህች መግለጫ እንደ ትልቅ ቁም ነገር ተቆጥራ ስትራገብ ማየት የሚገርም ነው። በአንዳዶች ዘንድ መጅሊሱ ልክ የአንበሳ ግዳይ የጣለ ያህል ነው እየተፎከረ ያለው። እንኳን መጅሊሱ ጥርስ አወጣ! ሲል የመጅሊሱን መግለጫ አወድሶታል።
እመኑኝ መግለጫ መውጣቱን እያጣጣልኩ አይደለም፤ ነገር ግን እያሳሰበኝ ያለው ልክ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ እንደተመለከትነው መጅሊሱም ሆነ ኡማው በመግለጫ ብቻ ተብቃቅቶ ጎራዴውን ወደ አፎቱ እንዳይመልስ ነው። የአሁኑም ሆነ የቀድሞው መጅሊስ መግለጫ ከማውጣት አልፎ በተጨባጭ ውጤት ማምጣት ላይ ያስመዘገበው ሪኮርድ ካለ ከቁጥር የሚገባ አይደለም። አብዛኞቹ ተመለሱ የሚባሉት የሙስሊሙ ጥያቄዎች ለውጤት የበቁት በመጅሊሱ ብርታት ሳይሆን ከመጅሊሱ ውጪ በተደረጉ ጥረቶችና መስዋዕትነቶች ነው። መጅሊሱ አንድ ሰው ከሶ አሳስሮ አያውቅም። መጅሊስን የሚያክል ግዙፍ ተቋም በትንንሽ ትምህርትቤቶችና ዩኒቨሪሲቲዎች ሲደፈርና ሲዋረድ የኖረ ተቋም ነው። ትምህርት ሚኒስቴር እኮ ከመጅሊሱ ጋር ሲነጻጸር ጭብጥ የሚሞላ ተቋም አይደለም።
መጅሊሱ የሚደፈረው አቅሙን ያልተገነዘበና በአቅሙ ልክ ለመንቀሳቀስ የሚያስችል ቁርጠኝነት የሌለው ተቋም በመሆኑ ብቻ ነው። ለምሣሌ ኦርቶዶክስን አዋርዶ፣ እምነታቸው አራክሶ ዘብጥያ ሳይወርድ የቀረ አለ? የለም። ሙስሊሙን አዋርዶ፣ እምነቱን አንኳሶ ያመለጠስ አለ? መልሱ አለ ብቻ ሳይሆን አንድም ለፍትህ የቀረበ የእስላም ጥላቻ አቀንቃኝ የለም!
ሰዎች፣ ይሄ የመጅሊስ መግለጫ በማንም ዘንድ ብዙም ክብደት የሚሰጠው አይደልም፤ ምክንያቱም መጅሊሱ ከመግለጫ አልፎ የመሄድ ልምድ እንደሌለው በተደጋጋሚ አሳይቷልና። መጅሊሱ ከመግለጫ አልፎ እንዲሄድ ከተፈለገ የሙስሊሙ ኡማም በመግለጫ ተጨናብሮ ሰይፉን ወደ አፎቱ የመመለስ ባህሉን መቀየር ይኖርበታል።
🗣️ የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው?
አስተያየትዎን ያጋሩ! 👇
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

🚩ዶናልድ ትራምፕ የጋዛ ጊዝያዊ አስተዳዳሪ እንደሚሆኑ ተነገረ!~~~~~~~~~~~~~~~ 👉የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት ዛሬ ማክሰኛ (እ.ኤ.አ. ህዳር 17, 2025) በጋዛ ዙርያ...
11/18/2025

🚩ዶናልድ ትራምፕ የጋዛ ጊዝያዊ አስተዳዳሪ እንደሚሆኑ ተነገረ!
~~~~~~~~~~~~~~~

👉የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት ዛሬ ማክሰኛ (እ.ኤ.አ. ህዳር 17, 2025) በጋዛ ዙርያ የሰጠው ውሳኔ 2803 አስመልክቶ ዋና ዋናዎቹን ነጥቦች በአጭሩ እነሆ፡-
❗️ይህ ሃሳብ በአሜሪካ, በቀጥታ በፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ የተነደፈ ነው -ይህ ማለት ደግሞ የእስራኤል መንግስት በተለይም የናትያንያሁን ቅድመ ይሁንታና ፍላጎት ያካተተ መሆኑ ይገመታል፡፡ ሃሳቡም ለጸጥታው ምክር ቤት ቀርቦ 13 አገሮች በድጋፍ፣ አንድም ተቃዋሚ ሳይኖር፣ እና ሁለት አገሮች ተአቅቦ በማድረግ (ቻይና እና ራሺያ) ፀድቋል።

👉 የጸደቀው ዉሳኔ ምን ያስከትላል?!
1. ዉሳኔው ዓለም አቀፍ የሰላም ግብረ ኃይል (ISF) ማቋቋም
ተልዕኮ: ውሳኔው በጋዛ ውስጥ በጊዜያዊነት የሚቆይ ዓለም አቀፍ የሰላም ግብረ ኃይል (ISF) እንዲቋቋም ያዛል።
ኃላፊነት: ይህ ኃይል ስራው የጋዛን ጎዳናዎች ደህንነት ማስጠበቅ፣ (እንደ ሐማስ ካሉ መንግስታዊ ያልሆኑ ታጣቂ ቡድኖች መሳሪያዎችን መውረስን ጨምሮ) ግዛቱ ዉስጥ ያሉ ታጣቂዎችን ትጥቅ ማስፈታት፣ ሲቪሎችን መጠበቅ እና ሰብአዊ እርዳታን ማጀብ እንደሚሆን ተገልጿል።
የሰላም አስከባሪው ምንጭ : ኃይሉ አለም አቀፍ ይባል እንጂ አሜሪካ እና እስራኤል ከሚፈልጓቸው ሃገራት ብቻ እንደሚዉጣጣ ይታመናል (ለምሳሌ ቱርክ በሰላም አስከባሪው ሃይል ዉስጥ መሳተፍ እንደማትችል ናታንያሁ ከወዲሁ ግልጽ አድርገዋል)፡፡ ይህም ሃይል ከእስራኤል፣ ከግብፅ እና አዲስ ይመሰረታል ከሚባለው ብቃቱ ከተረጋገጠ የፍልስጤም ፖሊስ ኃይል ጋር በቅንጅት ይሰራል ነው የተባለው።

2. የሽግግር አስተዳደር መመስረት
የሰላም ቦርድ (BoP): እስከ 2027 መጨረሻ ድረስ የጋዛ የሽግግር አስተዳደር ሆኖ የሚያገለግል የሰላም ቦርድ እንደሚቋቋም ይገልጻል።
ሊቀመንበር: ቦርዱ በራሳቸው በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እንደሚመራ ይጠበቃል። ይህም ራሳቸው ለራሳቸው የሰጡት ሹመት ዶናልድ ትራምፕን የጋዛ የበላይ ጠባቂና ፈላጭ ቆራጭ ያደርጋቸዋል>>(ይህም በመሆኑ ይህ ዉሳኔ ጋዛን በቅኝ የመያዝና የመግዛት እርምጃ ማሳያ ነው ሲሉ ብዙዎች ነቅፈዉታል )
መልሶ ግንባታ: በዉሳኔው መሰረት አዲሱ ቦርድ መልሶ ግንባታውን ያስተባብራል፣ የጋዛን ልማት ያመቻቻል፣ እንዲሁም የጋዛን የዕለት ተዕለት ሲቪል አስተዳደር ኃላፊነት ያለበትን የፍልስጤም የባለሙያዎች (ቴክኖክራሲያዊ) ኮሚቴን ይቆጣጠራል።
3. ወደ ፍልስጤም መንግስትነት የሚወስድ መንገድ?
የፍልስጤም አስተዳደር አስፈላጊ ማሻሻያዎችን ካደረገ እና የጋዛ መልሶ ግንባታ ከተጀመረ በኋላ፣ "ለፍልስጤማውያን ራስን በራስ የማስተዳደር እና ወደ መንግስትነት የሚወስዱ አስተማማኝ መንገዶች ሊፈጠሩ ይችላሉ" ይላል። (ይህንን በተመለከተ ሃማስ ሩስያና ቻይና ግልጽ ያልሆነ እና ወደፊት ፍልስጤማዊያን የሚያስተዳድሩት የፍልስጤም ሀገርነት የሚረጋገጥበት የጊዜ ሰሌዳ ያልተቀመጠ በመሆኑ ሃሳቡን ተችተዋል )

4. የድምፅ አሰጣጥ
ውሳኔው 13 አገሮች በድጋፍ፣ አንድም ተቃዋሚ ሳይኖር፣ እና ሁለት አገሮች ድምጸ ተአቅቦ በማድረግ (ቻይና እና ራሺያ) ፀድቋል።
5. ግብረ መልሶች !
ዩናይትድ ስቴትስ: ውሳኔውን እንደ "የሕይወት አድን" እና ለመካከለኛው ምሥራቅ "አዲስ አካሄድ" በማለት በደስታ ተቀብላዋለች።
እስራኤል: ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በተለይም የጋዛን ትጥቅ የማስፈታት ጥያቄን ስለሚመልስ ውሳኔውን እንደተቀበሉ ገልጸዋል። ነገር ግን፣ በቅንጅት መንግስታቸው ውስጥ ያሉ ብዙዎች ወደፊቱን የፍልስጤም መንግስት መፍጠር የሚለዉን ሀሳብን ይቃወማሉ። ፍልስጤም የሚባል ሃገርና ህዝብን እውቅና መስጠትን እንደ ስህተት ያያሉ በመሆኑም ዉሳኔዉን ሲቃወሙ ተደምጠዋል፡፡
ሐማስ: እንደተጠበቀውና ሰሞኑን ሲያስጠነቅቅ እንደነበረው ውሳኔውን ውድቅ አድርጓል። ዓለም አቀፉ ኃይል ትጥቅ የማስፈታት ሚና ይወጣል መባሉ ገለልተኝነቱን ያሳጣል ብሏል።
የፍልስጤም አስተዳደር: እማህሙድ አባስ የሚመራው የፍልስጤም አስተዳደር ውሳኔውን "ወደ ሰላም የሚወስድ አስፈላጊ የመጀመሪያ እርምጃ" ሲል በመቀበል፣ በጋዛ ውስጥ ኃላፊነቱን ለመውሰድ ዝግጁ መሆኑን ገልጿል። (ነገር ግን ይህ ስተዳደር እጅግ ለዘብተኛ ቢሆንም የእስራኤል ድጋፍ የሌለው ከመሆኑም በላይ ሰሞኑን ማህሙድ አባስ መታሰር አለበት የሚል የእስራኤል ባለስልጣናት ዘመቻ መከፈቱ ይታወቃል)
በእርግጥ ይህ ውሳኔ ያለዉን ግጭት አስቀርቶ ለጋዛና ለመላ ፍልስጤማዊያን ሰላምና ደህንነትን በመስጠት በሂደትም የራሳቸውን ሃገር እንዲመሰርቱ ያደርጋቸው ይሆን ወይንስ በእነ ትራምፕ በኩል ተዘዋዋሪ ቅኝ አገዛዝ ዉስት ይገቡ፣ እስራኤልም ያሰበችዉን በተዘዋዋሪ ታገኝ ዘንድ ያመቻች ይሆን?

🗣️ የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው?
አስተያየትዎን ያጋሩ! 👇
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive

Address

St. Louis, MO

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when RN05 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to RN05:

Share