Sebez media - ሰበዝ ሚዲያ

Sebez media - ሰበዝ ሚዲያ What Sebez Media does is touches all forms of events like politics, social life, social media, Ethio
(1)

ብርቱዋ እናት አረፉየብዙዎች እናት የብርታትና ጥንካሬ ምልክት ናቸው።ከተወጠረ የላስቲክ ቤት ንግድ ተነስተው ከትልቅ ደረጃ ደርሰዋል።ወ/ሮ አማረች ፈለቀ የሃዋሳ ሴንትራል ሆቴል ባለቤት አርፈዋ...
01/06/2023

ብርቱዋ እናት አረፉ

የብዙዎች እናት የብርታትና ጥንካሬ ምልክት ናቸው።

ከተወጠረ የላስቲክ ቤት ንግድ ተነስተው ከትልቅ ደረጃ ደርሰዋል።

ወ/ሮ አማረች ፈለቀ የሃዋሳ ሴንትራል ሆቴል ባለቤት አርፈዋል።

ወ/ሮ አማረች ባደረባቸው ህመም በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር በህክምና ሲረዱ ቆይተው ህይወታቸው ማለፉን ሠምተናል።

የብራዚሉ ኮኮብ  ፔሌ በ82 አመቱ ከዚህ አለም በሞት ተለየ።
12/29/2022

የብራዚሉ ኮኮብ ፔሌ በ82 አመቱ ከዚህ አለም በሞት ተለየ።

በሕገ-ወጥ መንገድ ከ5 ቢሊየን ብር በላይ ሲያንቀሳቅስ የነበረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር መለ— — — — — — — —የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኅብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማና ባደረገው ብርቱ ክትትል...
10/26/2022

በሕገ-ወጥ መንገድ ከ5 ቢሊየን ብር በላይ ሲያንቀሳቅስ የነበረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር መለ
— — — — — — — —

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኅብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማና ባደረገው ብርቱ ክትትል በህገ-ወጥ መንገድ መንገድ ከ5 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር (ከአምስት ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር) በላይ ሲያንቀሳቅስ የነበረ ግለሰብ ከ25 ግብረ-አበሮቹ ጋር በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራባቸው መሆኑን ገለፀ፡፡

በወንጀሉ የተጠረጠረው ሳሙኤል እጓለ አለሙ በቅፅል ስሙ ሳሚ ዶላር የሚባል ሲሆን ነዋሪነቱን በአዲስ አበባ ከተማ በማድረግ ወደ አሜሪካን ሀገር በተደጋጋሚ የሚመላለስ የኤሌክትሪክ መሳሪያዎች፣ የቤት እና የቢሮ እቃዎች እንዲሁም ተዛማጅ መገልገያዎች የችርቻሮ ንግድ ፍቃድን ሽፋን በማድረግ ሕገ-ወጥ የውጭ ምንዛሬና በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር ወንጀል ተጠርጥሮ በራሱና ዮዲት እጓለ አለሙ ከተባለች እህቱ ጋር በመሆን በስማቸው በተለያዩ ባንኮች በከፈቷቸው ሃያ አምስት የባንክ አካውንቶች በአንድ ዓመት ውስጥ ከ247 ሚሊየን ብር (ሁለት መቶ አርባ ሰባት ሚሊየን ብር) በላይ ማንቀሳቀሳቸውን ፖሊስ ደርሶባቸው ምርመራ እየተጣራባቸው መሆኑ ታውቋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ግለሰቡ ከሃያ አምስቱ የወንጀል ግብረ-አበሮቹ ጋር በመሆን በህገ-ወጥ መንገድ ከ5 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር (ከአምስት ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር) በላይ ሲያንቀሳቅሱ እንደነበር በቅድመ ምርመራ ተደርሶባቸዋል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ በሕገ-ወጥ የውጭ ሀገር የገንዘብ ዝውውር፣ በግብር ስወራ ወንጀል እና ከህወሃት የሽብር ቡድን ጋር የግንኙነት መረብ በመፍጠር ከፍተኛ ገንዘብ ሲያዘዋውሩ እንደነበር ተጠርጥረው ምርመራ እየተካሄደባቸው ይገኛል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ በአጠቃላይ በአንድ ዓመት ውስጥ 5,248,000,000 (አምስት ቢሊዮን ሁለት መቶ አርባ ስምንት ሚሊየን ብር) በላይ በሕገ-ወጥ መንገድ ሲያንቀሳቅሱ እንደነበር ፖሊስ ባደረገው ምርመራ ደርሶባቸዋል።

በመጨረሻም ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ ኅብረተሰቡ ላደረገው ቀና ትብብር ተቋሙ ላቅ ያለ ምስጋና እያቀረበ ተመሳሳይ የወንጀል ድርጊት ሲያጋጥም በአፋጣኝ በስልክ ቁጥሮች 0115 30 91 39፣ 0111 11 94 75፣ 0111 71 10 12 እንዲሁም 816 ነፃ የስልክ መስመር በመጠቀም ጥቆማ በመስጠት የተለመደ ድጋፍና ትብብር እንዲያደርግ ጥሪውን ያስተላልፋል።

Federal Police

የሶማሌ ክልል ምክር ቤት አባል እና የብልፅግና ፓርቲ ማእከላዊ ኮሚቴ አባል ወ/ሮ ጁዋሪያ መሀመድ ኢብራሂም  በጅግጅጋ ኤርፖርት  ውስጥ ከአንድ የፀጥታ ሀይል አባል በተተኮሰ ጥይት ህይወታቸው...
10/25/2022

የሶማሌ ክልል ምክር ቤት አባል እና የብልፅግና ፓርቲ ማእከላዊ ኮሚቴ አባል ወ/ሮ ጁዋሪያ መሀመድ ኢብራሂም በጅግጅጋ ኤርፖርት ውስጥ ከአንድ የፀጥታ ሀይል አባል በተተኮሰ ጥይት ህይወታቸው አልፏል።

ጉዳዩ በህግ አግባብ ተይዞ እየተጣራ ሲሆን በቀጣይ ሁኔታው የደረሰበት ደረጃ በሚመለከተው አካል የሚገለፅ ይሆናል።

በማእከላዊ ኮሚቴ አባላችን ላይ በደረሰው ህልፈት ፓርቲያችን ብልፅግና የተሰማውን መሪር ሀዘን እየገለፀ ለወዳጅ ዘመዶቿ እና ለትግል አጋሮቿ መፅናናትን ይመኛል።

Source: Prosperity party

የአፍሪካ ህብረት ድርድሩ በደ/አፍሪካ ተጀምሯል ብሏል
10/25/2022

የአፍሪካ ህብረት ድርድሩ በደ/አፍሪካ ተጀምሯል ብሏል

በፈተና የተሞላ ህይወትአራት ልጆቼን ቀብሬያለውየቀረኝ ብቸኛ ልጅም የአእምሮ ህመምተኛ ሆነብኝhttps://youtu.be/4HJKcs6QqU0
08/24/2022
Ethiopia: Heart touching story in Addis Media | አራት ልጆቼን ቀብሬ አንድ የአእምሮ ታማሚ ብቻ ቀርቶኛል |

በፈተና የተሞላ ህይወት

አራት ልጆቼን ቀብሬያለው

የቀረኝ ብቸኛ ልጅም የአእምሮ ህመምተኛ ሆነብኝ

https://youtu.be/4HJKcs6QqU0

Heart touching story in Addis Ababa@Sebez Media story in AddisEthiopian News Today Aug 24, 2022What Sebez Media does is touches all forms of events like poli...

08/14/2022

አቡበከር ናስር ከመሪያ ጎሉ በውሃላ

ትናንት ምሽት በቱሉ ዲምቱ መንገድ ላይ የደረሰ ዘግናኝ አደጋ ነውሀሳቡ ፈጥኖ ከቤቱ መድረስ ከልጆቹ ጋር መተያየት ነበር።ከአደጋው ከደቂቃዎች በፊት ደውሎም ልጆቹን ደርሻለው ጠብቁኝ እንዳተኙ ...
08/14/2022

ትናንት ምሽት በቱሉ ዲምቱ መንገድ ላይ የደረሰ ዘግናኝ አደጋ ነው

ሀሳቡ ፈጥኖ ከቤቱ መድረስ ከልጆቹ ጋር መተያየት ነበር።
ከአደጋው ከደቂቃዎች በፊት ደውሎም ልጆቹን ደርሻለው ጠብቁኝ እንዳተኙ ብሏቸዋል።

በመኪናው ላይ ለቤቱ የጫነው ሽንኩርትና ከሰል ይታያል።
እንዳሰበው በሰላም መድረስ ከቤተሰቡ መገናኘትን አልታደለም። ከቤቱ ሳይደርስ ክፉ ቀደመው

ከከባድ የጭነት ተሽከርካሪ ጋር ተጋጨ መኪናው ከቁጥጥሩ ውጪ ሆነ ዘግናኙ አደጋም ደረሰ።

በመኪናው ውስጥ አብሮ የነበረው ሰው ሲተርፍ አሽከርካሪው ሆስፒታል እንደደረሰ ህይወቱ አልፏል።

እባካችሁን በጥንቃቄ እናሽከርክር!

በየጎዳናው የወደቁ ከ200 በላይ የአዕምሮ ህሙማንን ከጎዳና አንስቶ የሚያኖረው ሰሊሆም የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር በመድሃኒት እጦትና በሌሎች ችግሮች ምክንያት ስራዬ እየከበደብኝ ነው ሲል...
08/13/2022

በየጎዳናው የወደቁ ከ200 በላይ የአዕምሮ ህሙማንን ከጎዳና አንስቶ የሚያኖረው ሰሊሆም የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር በመድሃኒት እጦትና በሌሎች ችግሮች ምክንያት ስራዬ እየከበደብኝ ነው ሲል ተናገረ፡፡

የአዕምሮና ተጓዳኝ ህመም ያለባቸውን ሰዎች ከጎዳና አንስቶ የሚያኖረው ማዕከሉ ህፃናት፣ ወጣቶችና አረጋዊያን በየቀኑ መውሰድ ያለባቸውን መድኃኒት ወጪ መሸፈን ከአቅሜ በላይ እየሆነብኝ ነው ብሏል፡፡

የእንጦጦ ቅዱስ ራጉኤል ቤተ ክርስቲያን ግቢን ተከራይቶ ስራውን የሚከውነው ማዕከሉ ከ200 በላይ የአዕምሮ ህሙማንን ማኖር የሚችልበት ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡

ወጣት ሚኪያስ ለገሰ የሰሊሆም የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር መስራች ነው፡፡

የተቋሙ መስራች እንደነገረን በተለይ በዚህ ክረምት ወደ ግቢው የተቀላቀሉ የአዕምሮ ህሙማን ቁጥር ከፍተኛ በመሆኑ ማዕከሉ ከአቅሙ በላይ ተጨናንቋል ፡፡

አዲስ ህሙማንን ማንሳት ብናቆምም ሕፃናትን ጨምሮ ሌሎች የአዕምሮ ህሙማንን ከደጃፋችን ጥለው ስለሚሄዱ እነሱን ማንሳት የግድ እየሆነብን ግቢውም እየተጨናነቀ ነው ብሏል።

ሚኪያስ እንደነገረን በአሁኑ ሰዓት የማዕከሉ የዕለት ወጪ ወደ 20,000 ብር ደርሷል፡፡

ለግቢው ኪራይም በየወሩ 7000 ይከፍላሉ፤ ይሄ ሁሉ ያለምንም ቋሚ ገቢ የሚሸፈን ነው ይላል።

ተቋሙ የራሱን ማዕከል ለመገንባት ያቀረበው የቦታ ጥያቄ እስካሁን ምላሽ እንዳላገኘም ነግሮናል።

ይህ ሁሉ ሲደራረብ አንዳንዴ በስራችን ተስፋ ስለመቁረጥ እንድናስብ ያደርገናል ይላል ሚኪያስ፡፡

ስሊሆም የአእምሮ ህሙማ መረጃ ማህበር የተመሰረተው በ2008 እንደሆነ በዚሁ የበጎ አደራጎት ስራ ከ6 ዓመታት በላይ ማሳለፉንም ከመስራቹ ሰምተናል፡፡

ምንጭ፦ ሸገር ራዲዮ

  ETHIOPIAእንኳን ደስ ያለን!የማይረሳ ድንቅ ምሽት!ኢትዮጵያ በኮሎምቢያ ካሊ የዓለም ከ20 ዓመት በታች የአትሌቲክስ ሻምፒዮና የመዝጊያ ውድድር ደምቃ አመሸች።አራት የፍፃሜ ውድድር፦አራት...
08/06/2022

ETHIOPIA
እንኳን ደስ ያለን!

የማይረሳ ድንቅ ምሽት!

ኢትዮጵያ በኮሎምቢያ ካሊ የዓለም ከ20 ዓመት በታች የአትሌቲክስ ሻምፒዮና የመዝጊያ ውድድር ደምቃ አመሸች።

አራት የፍፃሜ ውድድር፦

አራት ወርቅ ሁለት ብር

በሴቶች 1500ሜ ወርቅ

በወንዶች 800ሜ ወርቅ

በሴቶች 5000ሜ ወርቅ እና ብር

በወንዶች 3000ሜ መሰናክል ወርቅ እና ብር

በአንድ ምሽት ተጨማሪ 4 ወርቅና 2ብር
በድምሩ 6 ሜዳሊያ

የምሽቱን የመዝጊያ ውድድር አለማየት ያስቆጫል።

በተለይ የሴቶች 5000ሜትር እና የወንዶች 3000ሜትር መሰናክል ልዩ ነበር፣ አትሌቶቻችን ኢትዮጵያ ሁሌም ተተኪ እንዳላት በሚገባ አሳይተውናል።

ውድድሩ ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያ 6 ወርቅ

5 ብር

1 ነሀስ

በማግኘት ከአፍሪካ ቀዳሚ ከዓለም አሜሪካና ጀማይካን ተከትላ ሶስተኛ ሆና አጠናቃለች።

ቤልግሬድ2022 -  የዓለም የቤት ውስጥ ውድድር፤ሜዳልያው 4 ወርቅ፣ 3 ብር፣ 2 ነሃስ፣ በድምሩ 9 ደርሷል፡፡ደረጃችንም እስከ አሁን 1ኛ ሲሆን አሜሪካን አስከትለን እንገኛለን፡፡ኢትዮጵያችን...
03/20/2022

ቤልግሬድ2022 - የዓለም የቤት ውስጥ ውድድር፤
ሜዳልያው
4 ወርቅ፣ 3 ብር፣ 2 ነሃስ፣ በድምሩ 9 ደርሷል፡፡
ደረጃችንም እስከ አሁን 1ኛ ሲሆን አሜሪካን አስከትለን እንገኛለን፡፡
ኢትዮጵያችን እንኳን ደስ አለሽ!

ምንጭ: ኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን

እንኳን ደስ አለን!በ18ኛው የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሴቶቾ 3000 ሜትር ውድድር ወርቅና ነሀስ አግኝተናል።በሴቶች ምድብ የ3,000ሜ የፍፃሜ ውድድር  ወርቅና ነሐስ በአትሌ...
03/18/2022

እንኳን ደስ አለን!

በ18ኛው የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሴቶቾ 3000 ሜትር ውድድር ወርቅና ነሀስ አግኝተናል።

በሴቶች ምድብ የ3,000ሜ የፍፃሜ ውድድር ወርቅና ነሐስ በአትሌት ለምለም ሐይሉና በአትሌት እጅጋየሁ ታዬ ስናገኝ ዳዊት ስዩም አምስተኛ በመሆን አጠናቀዋል።

እንኳን ደስ አለን!

ጉቦ ለመቀበል የተደራደሩት ጋዜጠኞች ገንዘቡን ሲቀበሉ ተይዘው ክስ ተመስርቶባቸዋል_____ ____ ___ ___ ___ ___ __ __ __ዐቃቤ ህግ ከባድ የሙስና ወንጀል በፈፀሙ በኢትዮጵያ ብ...
03/18/2022

ጉቦ ለመቀበል የተደራደሩት ጋዜጠኞች ገንዘቡን ሲቀበሉ ተይዘው ክስ ተመስርቶባቸዋል
_____ ____ ___ ___ ___ ___ __ __ __

ዐቃቤ ህግ ከባድ የሙስና ወንጀል በፈፀሙ በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የኦሮምኛ ክፍል ኃላፊና በግብረ አበሩ ላይ ክስ መሰረተ

ዐቃቤ ህግ ክስ የመሰረተው አንድ የግል ድርጅት በሚያመርተው የታሸገ ውሃ ውስጥ በሃሰት ባዕድ ነገር እንደተገኘ ጠቅሶ በሚዲያ እንደሚያጋልጥ በማስፈራራት በጥሬ ገንዘብና በቼክ ግምሽ ሚሊዮን ብር ጉቦ ሲቀበል በተያዘው የኢቢሲ ጋዜጠኛና ግብረ አበሩ ላይ ነው፡፡

በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የኦሮምኛ ክፍል ኃላፊው በላቸው ጀቤሳ ዋቆ እና በ2ኛ ተከሳሽ አለማየሁ ቂጢሳ ሚጄና ላይ ክሱን የመሰረተው በጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዘርፍ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጄነራል ዐቃቤ ህግ ነው ።

የዐቃቤ ሕግ ክስ እንደሚያስረዳው 1ኛ ተከሳሽ በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (EBC) የኦሮምኛ ዝግጅት ክፍል ኃላፊ ሆኖ ሲሰራ ከ2ኛ ተከሳሽ ጋር በመመሳጠር የሸገር ውሃ አምራችና አከፋፋይ ከሆነው “ ኩኒስ በሪ ጠቅላላ ንግድ ኃ/የተ/የግ/ማህበር” የተባለውን ድርጅት በሀሰት የሚያመርተው ውሃ ባዕድ ነገር እንዳለበትና በሚዲያ እንደሚያጋልጡት አስፈራርተውታል።
ተከሳሾቹ ከጥር ወር 2014 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ድርጅቱ ባለቤት በተደጋጋሚ ስልክ በመደወል “ኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ ከሚገኝ አንድ ሱቅ ውስጥ የሸገር ውሀ ለመጠቀም ገዝተን ከውሀው ውስጥ ሶፍት መሳይ ቆሻሻ ነገር ያገኘንበት በመሆኑ ይህንንም ለኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጥቆማ ስላቀረብን አግኝተህ አናግረን ” በማለት ካግባቡት በኋላ 1ኛ ተከሳሽ “በታሸገው ውሀ ውስጥ ከተገኘው ባዕድ ነገር ጋር ተያይዞ መረጃን በሚዲያ ከተላለፈ ስለምትጎዱ እኛም ደግሞ ጉዳዩን በሚዲያ ከማስተላለፍ እንድንታቀብ፤ የተበላሸውን ውሃና ለኢቢሲ (EBC) ያስገባነውን በምስል የተደገፈ ጥቆማ እንድንመልስላችሁ ገንዘብ ክፈሉን” በማለት ብር 500,000 (አምስት መቶ ሺህ ብር) ለመቀበል በተስማሙት መሰረት ከድርጅቱ ባለቤት ሲቀበሉ በህግ አስከባሪ አካላት የተያዙ በመሆኑ ሁለቱም ተከሳሾች በዋና ወንጀል አድራጊነትና ተካፋይ በመሆን በፈፀሙት ጉቦ መቀበል ካበድ የሙስና ወንጀል በጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዘርፍ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጄኔራል ዐቃቤ ህግ ኮፖሊስ ጋር በመሆን ሲያካሂድ የነበረውን ምርመራ በማጠናቀቅ ክስ መስርቶባቸዋል ፡፡

ክሱም ዛሬ መጋቢት 09/2014 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ሰዓት በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ሙስና ወንጀል ችሎት ተከሳሾች በፅ/ቤት ቀርበው ክሱ እንዲደርሳቸው ተደርጎ ለመጋቢት 12/2014 ዓ.ም ክሱን በንባብ ለማሰማት ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል።

ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ

አዲስ አበባ ሰላም ነች ስጋት ሊሆኑ የሚችሉ ነገሮች በቁጥጥር ስር ውለዋልዶ/ር ቀንአ ያደታ የአ/አ የሰላምና ፀጥታ ሀላፊው ዛሬ በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ መግለጫን ሰጥተዋልበአ/አ ለሽብር ተግባር...
11/25/2021

አዲስ አበባ ሰላም ነች ስጋት ሊሆኑ የሚችሉ ነገሮች በቁጥጥር ስር ውለዋል

ዶ/ር ቀንአ ያደታ የአ/አ የሰላምና ፀጥታ

ሀላፊው ዛሬ በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ መግለጫን ሰጥተዋል

በአ/አ ለሽብር ተግባር ሊውል ታስቦ የነበረ ከፍተኛ መጠን ያለው የጦር መሳሪያ፤ገንዘብ፤ አልባሳትና ገንዘብ በቁጥጥር ስር ውሏል።
የውጭ ጫናው አሁንም እንደቀጠለ ቢሆንም ምንም የሚያሰጋ ነገር ግን የለም ህዝቡም ሊረጋጋ ይገባዋል ብለዋል።

መስከረም 20 ቀን ድምፅ በተሰጠባቸው በሁሉም ምርጫ ክልሎች ብልፅግና ፓርቲ ማሸነፉ ይፋ ተደርጓል። በሶማሌ አንድ የምርጫ ክልል አንድ የግል ተወዳዳሪ ለክልል ም/ቤት ከማሸነፋቸው ውጪ ያሉትን...
10/12/2021

መስከረም 20 ቀን ድምፅ በተሰጠባቸው በሁሉም ምርጫ ክልሎች ብልፅግና ፓርቲ ማሸነፉ ይፋ ተደርጓል።

በሶማሌ አንድ የምርጫ ክልል አንድ የግል ተወዳዳሪ ለክልል ም/ቤት ከማሸነፋቸው ውጪ ያሉትን ሁሉንም የህዝብ ተወካዮችና የክልል ም/ቤት ወንበሮች ብልፅግና ፓርቲ ማሸነፉን ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ አድርጓል።

ምንጭ: ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ከመስቀል አደባባዩ የመድረክ ስራ ጀርባ ያሉት አርክቴክት እኚህ ናቸው ተብሏል። አርክቴክት አለበል ደስታ
10/07/2021

ከመስቀል አደባባዩ የመድረክ ስራ ጀርባ ያሉት አርክቴክት እኚህ ናቸው ተብሏል።

አርክቴክት አለበል ደስታ

10/05/2021

አዲስ ምዕራፍ

መስቀል አደባባይ

ከኮንዶሚኒየም ተመዝጋቢ ከ60 በመቶ በላዩ የአ/አ ነዋሪ አይደለም!— — — — — — — —በአዲስ አበባ የጋራ መኖሪያ ቤት ለማግኘት ተመዝግቦ ከሚጠባበቅ አንድ ሚሊየን ገደማ ህዝብ ከ600 ሺ...
09/15/2021

ከኮንዶሚኒየም ተመዝጋቢ ከ60 በመቶ በላዩ የአ/አ ነዋሪ አይደለም!
— — — — — — — —

በአዲስ አበባ የጋራ መኖሪያ ቤት ለማግኘት ተመዝግቦ ከሚጠባበቅ አንድ ሚሊየን ገደማ ህዝብ ከ600 ሺህ በላዩ የአዲስ አበባ ነዋሪ አይደለም ተባለ።

የሚበዙት የቤት ተመዝጋቢዎች አዲስ አበባ የት እንደሆነች እንኳን የማያውቁ እጣ ሲደርሳቸው ሽጠው የሚሄዱ እንጂ የሚኖሩበት አይደሉም ተብሏል።

ይህንን የተናገሩት የአ/አ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ናቸው።

ምክትል ከንቲባዋ በተደረገ ጥናት ውጤት መሰረት ይህው ተረጋግጧል ብለዋል።

ለእጣ ማውጣቱን ስራ እንዲያግዝ ተብሎ የተሰራው ሶፍትዌርም ብዙ ችግር ያለበት የሚፈለገውን ሰው ብቻ ለይቶ እንዲያወጣ ተደርጎ የተሰራ ችግር ያለበት ነው ብለዋል።

እነዚህን ችግሮች ስናርም ቆይተናል ያሉት ምክትል ከንቲባዋ አሁን በተለያየ ማጣራት ያገኘነውንና ግንባታቸው ያለቁ 30ሺህ ገደማ ቤቶችን ለእድለኞች እናስተላልፋለን ብለዋል።

የ1997 ተመዝጋቢዎችም ቅድሚያ ይሰጣቸዋል ብለዋል።

Via: Sheger Fm Radio

ነገሩ እንዴት ነው?ፕሬዳንት ባይደንና ባለቤታቸው እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ ብለዋልበአማርኛ ሁሉ መልካም እንቁጣጣሽ ብለዋል.
09/10/2021

ነገሩ እንዴት ነው?

ፕሬዳንት ባይደንና ባለቤታቸው እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ ብለዋል

በአማርኛ ሁሉ መልካም እንቁጣጣሽ ብለዋል.

የመድረክ አቀራረቡና ሙዚቃን የሚጫወትበት መንገድ ይለያል። • አዲስ አበባ ቤቴ• ችግርሽ በኔ አልፏል• ተማር ልጄ• ማን ይሆን ትልቅ ሰውእጅግ ብዙ ድንቅ ስራዎችን ሠርቷል። ብላኮ-ሶል: ሸበሌ...
09/03/2021

የመድረክ አቀራረቡና ሙዚቃን የሚጫወትበት መንገድ ይለያል።

• አዲስ አበባ ቤቴ

• ችግርሽ በኔ አልፏል

• ተማር ልጄ

• ማን ይሆን ትልቅ ሰው

እጅግ ብዙ ድንቅ ስራዎችን ሠርቷል።

ብላኮ-ሶል: ሸበሌስ: ሶል-ኤኮስ እና ሌሎችም ደማቅ ስራዎችን አብሮአቸው የሰራ የግል የሙዚቃ ቡድኖች ናቸው።

ቀድሞ የሚታወቅበት የሙዚቃ ክፍሉ የፖሊስ ሰራዊት የሙዚቃ ክፍል ነበር።

አለማየሁን በቅርብ የሚያውቁት ጥንቅቅ ያለ በቀጠሮ ቀልድ የማያውቅ በስራው የማይደራደር ነው ይሉታል።

ከምንም በላይ ኢትዮጵያን የእውነት ይወዳል ስለልጆቿ ችግር አብዝቶ ይጨነቃል ንግግሩም ቀጥተኛ ነው።

ይህ ታላቅ ሙዚቀኛ ቀኑ ደርሶ ተለየን። ነፍስህ በሰላም ትረፍ

ታላቁ ኢትዮጵያዊ የሙዚቃ ሰው አረፈ!ቤተሰቦቹ እንዳሉት ቀን በሰላም ውሎ አመሻሽ ላይ ድንገት አመመኝ ብሎ ወደ ሆስፒታል ሄደ በህክምና ላይ እንዳለ ህይወቱ አለፈ በቃ የሆነው ይህው ነው። ይህ...
09/03/2021

ታላቁ ኢትዮጵያዊ የሙዚቃ ሰው አረፈ!

ቤተሰቦቹ እንዳሉት ቀን በሰላም ውሎ አመሻሽ ላይ ድንገት አመመኝ ብሎ ወደ ሆስፒታል ሄደ በህክምና ላይ እንዳለ ህይወቱ አለፈ በቃ የሆነው ይህው ነው።

ይህቺን የተፃፈች ቀን ማን ያልፋታል..

አሌክስ ነፍስህ ከደጋጎቹ ጎን ትረፍ።

ይልማ ገብረአብአበበ ብርሃኔአበጋዝ ክብረ ወርቅ ሺዎታአቤል ጳውሎስአቤል ሙልጌታሃብታሙ ቦጋለናትናኤል ጌታቸውሚኪ ሃይሉ ታምሩ አማረወንድወሰን ይሁብምህረተአብ ደስታእዩኤል መሀሪእና ሌልችም በርካ...
09/02/2021

ይልማ ገብረአብ
አበበ ብርሃኔ
አበጋዝ ክብረ ወርቅ ሺዎታ
አቤል ጳውሎስ
አቤል ሙልጌታ
ሃብታሙ ቦጋለ
ናትናኤል ጌታቸው
ሚኪ ሃይሉ
ታምሩ አማረ
ወንድወሰን ይሁብ
ምህረተአብ ደስታ
እዩኤል መሀሪ
እና ሌልችም በርካቾች የተሳተፉበት ነው።

የራሄል ጌቱ አልበም “እቴሜቴ” ቅዳሜ ይወጣል።

ቀድመው ስራውን የገመገሙት የእውነት ሰምታችሁ ፍረዱ ድንቅ ስራ ነው እያሉ ነው።

እሷም የልቤ የደረሰበት ድንቅ ስራን ሰርቻለው ብላ በድፍረት ተናግራለች።

በስራው ውስጥ የተሳተፉ ሶስት ትውልድ የተሳተፈበት የተዋጣለት አልበም ብለውታል።

ድምፃዊቷ ራሄል በዚህ ከባድ በሆነ የእርጋታና የአርምሞ ወቅት ዝምታችሁን አዚሜያለሁ ብላለች።

ለማንኛውም ሙሉ አልበሙ እንዲሁም “ኢትዮጵያዬ” የተሰኘው የሙዚቃ ቪዲዮ ቅዳሜ ይወጣል።

“ስድስተኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መስከረም 24 ቀን 2014 ተሰይሞ መንግስት ይመሰርታል”  አቶ ታገሰ ጫፎ
08/31/2021

“ስድስተኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መስከረም 24 ቀን 2014 ተሰይሞ መንግስት ይመሰርታል”

አቶ ታገሰ ጫፎ

ኢትዮጵያዊቷ ያለምዘርፍ የዓለምን የግማሽ ማራቶን  የዓለምን ሪከርድ በመስበር አሸነፈች— — — — — — — —• “በህይወቴ ሙሉ ስደክምለት የነበረው ነገር ዛሬ እውን ሆነ” አትሌት ያለምዘርፍ...
08/29/2021

ኢትዮጵያዊቷ ያለምዘርፍ የዓለምን የግማሽ ማራቶን የዓለምን ሪከርድ በመስበር አሸነፈች
— — — — — — — —

• “በህይወቴ ሙሉ ስደክምለት የነበረው ነገር ዛሬ እውን ሆነ” አትሌት ያለምዘርፍ ከድሏ በውሃላ የተናገረችው ነው።

• ኢትዮጽያዊቷ ያለምዘርፍ የውሃላ በአንትሪም ኮስት የግማሽ ማራቶን ውድድር የዓለምን ሪከርድ በመስበር አሸንፋለች።

• የገባችበት ሰዓት 63 ደቂታ ከ 43 ሰከንድ ነው።

• ያለምዘርፍ በኬንያዊቷ የዓለም ሪከርድ ባለቤት ሩት ኬፕጌቲች ተይዞ የነበረውን ፈጣን ሰዓት በ19 ሰከንድ በማሻሻል ያሸነፈች ሲሆን ግማሽ ማራቶንን ከ64 ደቂቃ በታች የሮጠች የመጀመሪያዋ አትሌት ሆናለች።

የቶኪዮው ውጤት አደብዝዞት እንጂ አትሌቶቻችን ናይሮቢ ላይ ታሪክ ሰርተዋል!— — — — — — — —• የዓለም ከ20 ዓመት በታች የአትሌቲክስ ሻምፒዮና በናይሮቢ ለ5 ቀናት ሲካሄድ ቆይቶ ዛሬ ...
08/22/2021

የቶኪዮው ውጤት አደብዝዞት እንጂ አትሌቶቻችን ናይሮቢ ላይ ታሪክ ሰርተዋል!
— — — — — — — —

• የዓለም ከ20 ዓመት በታች የአትሌቲክስ ሻምፒዮና በናይሮቢ ለ5 ቀናት ሲካሄድ ቆይቶ ዛሬ ተጠናቋል።

• ኢትዮጵያ ኬንያ ፊንላንድና ናይጄሪያን ተከትላ ከዓለም አራተኛ ሆና ውድድሩን አጠናቃላች።

• ኢትዮጵያ በውድድሩ ሶስት ወርቅ ሰባት ብርና ሁለት ነሀስ በድምሩ 12 ሜዳሊያዎችን ማግኘት ችላለች።

• በተለይ በ3 ሺህ ሜትር የወርቅ እንደገና በ5 ሺህ ሜትር የብር ሜዳሊያን ማምጣት የቻለው ታደሰ ወርቁ የውድድሩ መነጋገሪያም ድምቀትም ነበር።

• በአጠቃላይ የውድድሩ ሂደት አሁንም በአትሌቲክሱ ገና ብዙ ድል እናያለን ብለን ተስፋ እንድናደርግ አድርጎን ተጠናቋል።

• የቶኪዮው ኦሎምፒክ ደካማ ውጤት ነገሩን ሁሉ አደበዘዘው እንጂ በናይሮቢ የተገኘው ውጤት ብዙ የሚያስብል ነበር።

ምስጋና በውድድሩ የኢትዮጵያን ስም ከፍ ላደረጋችሁ ሁሉ ይሁን!!!

ይህንን ሰው የምታውቁት ካላችሁ ከቤተሰቡ አገናኙት— — — — — — — እኔ ያገኘሁት ከአዲስ አበባ በአምቦ መስመር ሆለታ ከተማ ወልመራ በመባል የሚጠራ መንደር ውስጥ ነው። ለሚያየው ሰው የአ...
08/06/2021

ይህንን ሰው የምታውቁት ካላችሁ ከቤተሰቡ አገናኙት
— — — — — — —

እኔ ያገኘሁት ከአዲስ አበባ በአምቦ መስመር ሆለታ ከተማ ወልመራ በመባል የሚጠራ መንደር ውስጥ ነው።

ለሚያየው ሰው የአእምሮ እክል እንደገጠመው በቀላሉ መረዳት ይቻላል።

ግን ወደዚህ መንደር ማን አመጣው? እንዴትስ እዚህ መንደር ደረሰ?... ማንም አያውቅም።

ከአካባቢው ነዋሪዎች እንደሰማሁት ይህ ሰው በዛ መንደር በአንዱ አጥር ጥግ ድንገት ከተገኘ ሁለት ሳምንት አልፎታል።

ሰው ምግብ ካልሰጠው እሱ ምግብ ፍለጋ ወዴትም አይሄድም ከተቀመጠበት ቦታ ሳይነሳ ሁለት ሳምንት አልፎታል።

የአካባቢው ነዋሪዎች በወጠሩለት ላስቲክ ዳስ ውስጥ ኑሮን ይገፋል።

ያናገርኳቸው የአካባቢው ነዋሪዎች አንዳንዶቹ ሰላይ ነው ብለው ይጠረጥራሉ አንዳንዶች ወንጀለኛ ነው ተደብቆ ነው እንጂ ካላጣው ቦታ እዚህ የገጠር መንደር ምን አመጣው ይላሉ አንዳንዶች ደግሞ እንዴት እንደመጣ አናውቅም ግን የአእምሮ ህመምተኛ ነው ይሉታል።

ሌላው የሚገርመው ይህ ሰው ወደዚህ ሰፈር ከመጣ በውሃላና የላስቲክ ዳስ በነዋሪው ከተሰራለት በውሃላ ቤቱ በሌሎችም የአእምሮ ህመምተኛ በሚመስሉ ሰዎች የሚጎበኝ መሆኑ ነው። ይህ ሰው በዛች ዳስ ውስጥ መኖር ከጀመረ ወዲህ እዛ አካባቢ ታይተው የማይታወቁ እሱን መሰል ሰዎች እየመጡ አብረውት አድረው ሲነጋጋ ከአካባቢው ይሄዳሉ ተብያለው።

ወደ ተቀመጠበት ቀርቤ አናገርኩት ከአለም-ገና ነው የመጣሁት ሰቃይ የዩኒቨርስቲ ተማሪ ነበርኩኝ አለኝ እዚህ ምን አመጣህ ብለው ምርምር ላይ ነኝ አለ። ሌላም ያልገቡኝን ብዙ ነገሮችን አከታትሎ አወራ።

ይህ ሰው ማነው? ነዋሪው እንደሚለው ሰላይ አሊያም የተደበቀ ወንጀለኛ ወይንስ ሁኔታው እንደሚናገረው የአእምሮ ህመምተኛ?

ለምናልባቱ ብዬ ይህንን ምስል በስልኬ አስቀርቼ ተለየሁት።

ኢትዮጵያ!እንኳን ደስ ያለን ከቤጂንግ በውሃላ የኦሎምፒክ የ10ሺህ ሜትር ወንዶች ድል ወደ ሀገሩ ተመለሰ። ሰለሞን ባረጋ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ አስገኝቷል።
07/30/2021

ኢትዮጵያ!

እንኳን ደስ ያለን

ከቤጂንግ በውሃላ የኦሎምፒክ የ10ሺህ ሜትር ወንዶች ድል ወደ ሀገሩ ተመለሰ።

ሰለሞን ባረጋ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ አስገኝቷል።

ዐቃቤ ሕግ በእነ ዶ/ር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል መዝገብ በ62 ሰዎች ላይ ክስ መሰረተ— — — — — — —ክስ የተመሰረተባቸው ተከሳሾች የህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ...
07/23/2021

ዐቃቤ ሕግ በእነ ዶ/ር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል መዝገብ በ62 ሰዎች ላይ ክስ መሰረተ
— — — — — — —

ክስ የተመሰረተባቸው ተከሳሾች የህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ውሳኔ በመስጠት ከፍተኛ ተሳትፎ የነበራቸው የህውሀት መዓከላዊ ኮሚቴ አባላትና የክልልመንግስቱ ካቢኔ አባላት እንዲሁም በትጥቅ ጥቃት ላይ ከፍተኛ ሚና የነበራቸው የኢፈርት ድርጅቶች፣ የግልና የመንግስት ድርጅት አመራሮች፣ የትግራይ ምርጫ ኮሚሽን አመራር አባላት፣ በትግራይ በተካሄደው ኢ-ሕገ-መንግስታዊ ምርጫ ላይ ተሳትፎ ያደረጉት ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ሊቃነ-መናብርትና የቀድሞ የህውሀት ከፍተኛ አመራር የነበሩ ታዋቂ ግለሰቦች ላይ ነው የፌዴራሉ ዐቃቤ ሕግ ክስ የመሰረተው፡፡

ክሱ የተመሰረተው በሁለት የወንጀል አንቀጽ ስር ሲሆን የመጀመሪያው በሀይል በዛቻ በአድማና ህገ-ወጥ በሆነ መንገድ ኢ-ሕገመንግስታዊ ምርጫ በማካሄድ በሕገ-መንግስት የተቋቋመና እውቅና ያለው የክልል መንግስት መለወጥ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 238 ስር የተደነገገውን በመተላለፍ ሲሆን በሁለተኛ ክስ የፌዴራሉን መንግስት በሀይል ለመለወጥ በማሰብ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ የፌዴራል መንግስትን በመሳሪያ ጥቃት መለወጥ የሚችል የትግራይ ወታደራዊ ኮማንድ የተባለ የጦር ሀይል በማደራጀት የፌዴራል መንግስት የሀገር መከላከያ ሰራዊቱ ላይ ጥቃት በማድረስ የሽብር ወንጀልን ለመከላከል የወጣውን አዋጅ አዋጅ ቁጥር 1176/2011 አንቀጽ 3/1እና 3/2 በመተላለፍ ወንጀል ነው፡፡ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ለክሱ አስረጅነት 510 የሰው ምስክሮችን እና እና 5329 ገጽ የሰነድ ማስረጃዎችን በማያያዝ ለፍርድ ቤቱ ቅርቧል፡፡

የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሕገ-መንግስትና የሽብር ወንጀሎችን የሚያየው 1ኛ ችሎት ክሱን በመዝገብ ቁጥር 27128102 በመቀበል በማረሚያ ቤት የሚገኙ ተከሳሾችን ማረሚያ ቤቱ እንዲያቀርብ ቀሪ ተከሳሾችን የፌዴራል ፖሊስ መጥሪያ አድርሶ እንዲያቀርብ በማዘዘዝ ለሐምሌ 26 ቀን 2013ዓ.ም ቀጠሮ ሰቷል፡፡

ምንጭ: ጠቅላይ ዐቃቤ-ህግ

ህግ ተላልፈዋል የተባሉ የሞተር ብስክሌቶች በአ/አ በቁጥጥር ስር እየዋሉ ነው። የሞተር ብስክሌቶቹ ታርጋ ጭቃ በመቀባት ታርጋ በማጠፍና በሌላም መንገድ እንዳይያዙ እያደረጉ ጥፋት ሲፈፅሙ የነበ...
07/19/2021

ህግ ተላልፈዋል የተባሉ የሞተር ብስክሌቶች በአ/አ በቁጥጥር ስር እየዋሉ ነው።

የሞተር ብስክሌቶቹ ታርጋ ጭቃ በመቀባት ታርጋ በማጠፍና በሌላም መንገድ እንዳይያዙ እያደረጉ ጥፋት ሲፈፅሙ የነበሩ ናቸው ብሏል የአ/አ ፖሊስ።

ይህ ምስል ዛሬ በአራዳ ክ/ከተማ የተነሳ ነው

የኢትዮጵያ ጥንታዊ መፃህፍት ከመሸጥ ድነዋል!— — — — — — — —• ኢትዮጵያ ለጨረታ ሊቀርቡ የነበሩ ጥንታዊ መፃህፍቶቿን ከመሸጥ ማዳን ችላለች። • ጥንታዊ መፅሐፍቶቹ በኔዘርላንድ በተያዘ...
07/02/2021

የኢትዮጵያ ጥንታዊ መፃህፍት ከመሸጥ ድነዋል!
— — — — — — — —

• ኢትዮጵያ ለጨረታ ሊቀርቡ የነበሩ ጥንታዊ መፃህፍቶቿን ከመሸጥ ማዳን ችላለች።

• ጥንታዊ መፅሐፍቶቹ በኔዘርላንድ በተያዘው ወር ለጨረታ ሊቀርቡ እንደነበር ተወርቷል።

• ጥንታዊ መፃህፍቱ በቁጥር ሶስት ሲሆኑ በሆላንድ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የበረታ ክርክር በማድረግ የጨረታው ሂደት እንዲቋረጥ ተደርጓል።

• ከዛም ኤምባሲው ባደረገው ጥረት ቅርሶቹ በሆላንድ ላለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እንዲመለሱ ተደርጓል።

በሆላንድ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ላደረገው የተሳካ ጥረት ምስጋና ይገባዋል።

መረጃ: በኔዘርላንድ የኢትዮጵያ ኤምባሲ

ግን ለየስርዓቱ እንዲህ አቅላችሁን ስታችሁ ትችሉታላችሁ?— — — — — — — —ዛሬ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ሁሉ እረ ጉድ ስሙ እያሉ ዶ/ር ቴድሮስ ከዓለም የጤና ድርጅት እንዲለቁ ተጠየቀ ...
07/01/2021

ግን ለየስርዓቱ እንዲህ አቅላችሁን ስታችሁ ትችሉታላችሁ?
— — — — — — — —

ዛሬ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ሁሉ እረ ጉድ ስሙ እያሉ ዶ/ር ቴድሮስ ከዓለም የጤና ድርጅት እንዲለቁ ተጠየቀ ሲሉን ዋሉ።

ያጠፋ ይቀጣ ይጠየቅ ይነሳ ጥያቄው እሱ አይደለም ግን ገና አንድ የሚዲያ ተቋም በቂ መረጃ እንኳን ሳይኖረው ያወጣውን መረጃ እንዲህ መቀባበሉ ከምን የመጣ ይሆን?

ስለምንተዋወቅ ምክንያቱን አላስረዳም።

ግን አንድ ነገር ብቻ ልበል የዓለም ህዝብ ዶ/ር ቴድሮስን የሚያውቃቸው ኢትዮጵያዊ በመሆናቸው ነው።

ደግሞስ ምን አለ ለሌላው አይናችሁ ስር ላፈጠጠ እውነት እንዲህ ብትጣደፉ?

ለየ ስርዓቱስ እንዲህ አቅላችሁን ስታችሁ ትችሉት ይሆን?

ከምንም የፖለቲካ ጉዳይ ጋር የማይገናኝ የግል እይታ ተደርጎ ይቆጠርልኝ።

በቅርቡ የሚመረቁት የጀነራል ሰዓረ መኮንንና የአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ መታሰቢያ ሀውልቶች— — — — — — — —
06/28/2021

በቅርቡ የሚመረቁት የጀነራል ሰዓረ መኮንንና የአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ መታሰቢያ ሀውልቶች
— — — — — — — —

የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት የሕወሃት የሽብር ቡድን አባላት ሕንጻዎች በገለልተኛ አስተዳዳሪ ተይዘዉ እንዲተዳደሩ ወሰነ— — — — — — — — —የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ ጊዜ ቀ...
06/25/2021

የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት የሕወሃት የሽብር ቡድን አባላት ሕንጻዎች በገለልተኛ አስተዳዳሪ ተይዘዉ እንዲተዳደሩ ወሰነ
— — — — — — — — —

የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት በተለያዩ የመዝገብ ቁጥሮች (በመ/ቁ 007198፣ 263719፣ 007109፣ 006060፣ 263591፣ 006914፣ 006059 እና 007029) ሰኔ 16፣ 17 እና 18 ቀን 2013 ዓ.ም በዋለዉ ችሎት ዋና ዋና የሕወሃት የሽብር ቡድን አባላት የንግድና የመኖሪያ ሕንጻዎች ላይ ገለልተኛ አስተዳዳሪ እንዲሾም ዉሳኔ ሰጠ፡፡

በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ በወንጀል የተገኘ ሀብት ማስመለስ ዳይሬክተር ጄነራል የሆኑት አቶ ዓምአንተ አግደዉ እንደገለጹት ፍ/ቤቱ ይህንን ዉሳኔ የሰጠዉ የሽብር ቡድኑ በሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት መፈጸሙን ተከትሎ የወንጀል ምርመራና የሀብት ጥናት እየተከናወነ መሆኑን መነሻ በማድረግ ፤ ቡድኑ ከሕንጻዎቹ የሚያገኘዉን ገቢ የሽብር ተግባሩን ፋይናንስ ለማድረግ እንዳያዉል ለመከላከል፣ በተጠረጠሩበት የሽብር እና ሌሎች ወንጀሎች በፍ/ቤት ጥፋተኛ ሆነዉ ከተገኙ ሀብታቸዉ የሚወረስ በመሆኑ ተጠብቆ እንዲቆይ፣ የሽብር ቡድኑ በመከላከያ የሰሜን ዕዝ ሀብት፤ በተለያዩ መሰረተ ልማቶችና ስቪል ተቋማት ላይ ላደረሰዉ ዉድመትና ጉዳት ለማካካሻነት የሚዉል በመሆኑ እንዲሁም የተጠርጣሪዎችን ንብረት የያዙ አካላት የሚፈጽሙትን ምዝበራ ለመከላከል ሲባል በተጠረጠሩበትና በተከሰሱበት ወንጀል ፍ/ቤት የመጨረሻ ዉሳኔ እስኪሰጥ ድረስ ገለልተኛ አካል እንዲያስተዳድራቸዉ ዐቃቤ ሕግ ለፍ/ቤት አቤቱታ ማቅረቡን ተከትሎ ነዉ ብለዋል፡፡

ፍ/ቤቱ የዐቃቤ ሕግን አቤቱታ ከመረመረ በኋላ ሕንጻዎችን የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን እና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሥር የሚገኘዉ ኮመርሽያል ኖሚኒስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እንዲያስተዳድር ዉሳኔ ሰጥቷል፡፡

በዚህ ዉሳኔ አስተዳዳሪ የተሾመላቸዉ የንግድና መኖሪያ ሕንጻዎች አጠቃላይ ብዛት ከ 30 በላይ ሲሆኑ ከእነዚህ መካከል፡-

በ ጄ/ል ፃድቃን ገ/ተንሳይ ስም አዲስ አበባ የሚገኙ 2 (ሁለት ህንጻዎች) ፣

በ ጄ/ል አበበ ተክለሃይኖት ስም አዲስ አበባ የሚገኝ አንድ G+5 ሕንጻ (ወለላ ሕንጻ)፣

በ ብ/ጄ ምግበ ሃያለ ስም አዲስ አበባ እና መቀሌ የሚገኙ 2 (ሁለት) ሕንጻዎች፣

በ ብ/ጄ ታደሰ ወረደ ስም መቀሌ የሚገኙ 2 (ሁለት) ሕንጻዎች፣

በ ብ/ጄ ተክላይ አሸብር ስም አዲስ አበባ የሚገኝ G+5 ሕንጻ (ብሌን ሕንጻ)

በ ብ/ጄ ዮሀንስ ወ/ጅወርጊስ ስም መቀሌ የሚገኙ 3 (ሦስት) ሕንጻዎች፣

በሜ/ጄ ሕንጻ ወ/ጊወርጊስ ስም መቀሌ የሚገኝ 1 (አንድ) ሕንጻ፣

በሜ/ጄነራል ኢብራሂም አብዱል ጄሊል ስም መቀሌ የሚገኝ 1 (አንድ) ሕንጻ እና

በሃይለ ተስፋኪሮስ ገ/ሕይወት ስም መቀሌ የሚገኙ 3 (ሦስት) የነዳጅ ማደያዎች ይገኙበታል፡፡

በወንጀል የተገኘ ሀብት ማስመለስ ዳይሬክተር ጄነራሉ አክለዉ እንደገለጹት የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ከዚህ በተጨማሪ በዶ/ር አዲስ አለም ባሌሜና የሜ/ጄ ጻድቃን ባለቤት በወ/ሮ ኤልሳ አሰፋ ተክለሚካኤል ስም የሚገኙ ሕንጻዎችን ጨምሮ በሌሎች የሽብር ቡድኑ አባላት ሃብት ላይ አስተዳዳሪ ለማሾም እየተሰራ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡

በሀብት ምርመራ እና መለዬት ሂደት የሽብር ቡድኑ አባላት ተሽከርካሪዎችን ከቆሙበት በማንሳት ጋራዥ ዉስጥ የመደበቅና አካላቸዉን ፈቶ የማስቀመጥ፣ ለዉጭ ዜጎች በማከራየት የኪራይ ገንዘብ ዉጭ አገር ለመቀበልና በማሸሽ ለሽብር አላማ ለማዋል፣ የኪራይ ዉሎችን በመንደር ዉል በማድረግ ግብር እንዲሰወርና የሽብር ቡድን አባላትን ንብረት በኪራይ መያዛቸዉ እንዳይታወቅ የማድረግ ተግባር መፈጸም፣ አንዳንድ ህንጻዎችን ለሌላ ሦስተኛ ወገን የባንክ ማስያዣ በማድረግ ገንዘብ የማሸሽ ሙከራዎች ስለማድረጋቸዉ ተረጋግጧል፡፡

እነዚህን የወንጀሎች ተግባራትን አዲስ አበባ በሚገኙ ወኪሎችና ተከራዮች አማካኝት እየፈጸሙ መሆኑ በመታወቁ ከዚህ አንጻር ተጨማሪ ምርመራዎች በመጣራት ላይ ናቸዉ፡፡

በመጨረሻም የሀብት ማስመለስ ዳይሬክተር ጄነራሉ አቶ ዓለምአንተ አግደዉ እንደገለጹት የሕወሃት የሽብር ቡድን አባላትን ንብረት በኪራይ፣ በዉክልና፣ በጠባቂነት፣ በአደራና በሌላ ማናቸዉም መንገድ ይዘዉ የሚገኙ አካላት ልደታ ከፍተኛ ፍ/ቤት ግቢ ዉስጥ በሚገኘዉ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ህንጻ 1ኛ ፎቅ በወንጀል የተገኘ ሀብት ማስመለስ ዳይሬክቶሬት ጄነራል ቢሮ በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 0112733154 ወይም በEmail፡- [email protected] በማሳወቅ ራሳቸዉን ከወንጀል ተጠያቂነት ነጻ እንዲያደርጉ፣
በሌላ በኩል ባንኮች ለሚሰጡት ብድር መያዣ የሚያደርጉት ንብረት የሕወሃት የሽር ቡድን አባላት አለመሆኑን ወይም ከእነርሱ ጋር ግንኙነት የሌለዉ መሆኑን አስቀድመዉ በቂ ማጣራት በማድረግ ማረጋገጥ ያለባቸዉ ሲሆን ይህንንም ከጠቅላይ ዐቃቤ ሕግና ከሌሎች የሚመለከታዉ የሕግ አስከባሪ ተቋማት ጋር በቅርበት መረጃ መለዋወጥ እንዳለባቸዉ አስገንዝበዋል፡፡

ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ

የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በገለልተኛ አስተዳዳሪ ቁጥጥር ሥር ሆነዉ እንዲተዳደሩ ዉሳኔ የሰጠባቸዉ የሕወሃት የሽብር ቡድን አባላት ሕንጻዎች መካከል በከፊልSource: ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ
06/25/2021

የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በገለልተኛ አስተዳዳሪ ቁጥጥር ሥር ሆነዉ እንዲተዳደሩ ዉሳኔ የሰጠባቸዉ የሕወሃት የሽብር ቡድን አባላት ሕንጻዎች መካከል በከፊል

Source: ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ

06/21/2021

“የህዝቡ የመምረጥ ፍላጎት ልባችንን አሙቆታል እናመሰግናለን”

ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ

ድምፅ መስጠት ምሽት 3 ሰዓት ተጠናቋል— — — — — — — —የድምፅ አሰጣጡ ስራ ምሽት 3 ሰዓት ተጠናቋል። የተለየ ችግር ካልተፈጠረ በቀር ሁሉም ጣቢያዎች ወደ ድምፅ ቆጠራ ይገባሉ። ጉልህ ...
06/21/2021

ድምፅ መስጠት ምሽት 3 ሰዓት ተጠናቋል
— — — — — — — —
የድምፅ አሰጣጡ ስራ ምሽት 3 ሰዓት ተጠናቋል።

የተለየ ችግር ካልተፈጠረ በቀር ሁሉም ጣቢያዎች ወደ ድምፅ ቆጠራ ይገባሉ።

ጉልህ ተብሎ ሊጠቀስ የሚችል ችግር አልተፈጠረም

ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ የምርጫ ቦርድ ሠብሳቢ አሁን እየሰጡ ካሉት መግለጫ

የድምፅ አሰጣጡ እስከ ምሽት 3 ሰዓት ይቆያልምርጫ ቦርድ
06/21/2021

የድምፅ አሰጣጡ እስከ ምሽት 3 ሰዓት ይቆያል

ምርጫ ቦርድ

በምርጫው አጠቃላይ ውሎ ዙሪያ የምርጫ ቦርድ መግለጫ እየተጠበቀ ነው— — — — — — — —በአዲስ አበባ ብዙዎቹ ቦታዎች መራጩ ህዝብ ለመምረጥ አሁንም ሰልፍ ይዞ እየጠበቀ ነው። በተለያዩ የም...
06/21/2021

በምርጫው አጠቃላይ ውሎ ዙሪያ የምርጫ ቦርድ መግለጫ እየተጠበቀ ነው
— — — — — — — —

በአዲስ አበባ ብዙዎቹ ቦታዎች መራጩ ህዝብ ለመምረጥ አሁንም ሰልፍ ይዞ እየጠበቀ ነው።

በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች በቁሳቁስ አቅርቦትና በሌሎችም ችግሮች የምርጫው ሂደት እንደታሰበው መፍጠን አልቻለም።

ምርጫ ቦርድ በነዚህና በሌሎችም አጠቃላይ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫን ከቆይታ በውሃላ ይሰጣል ተብሎ እየተጠበቀ ነው።

Address

Sterling, VA

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sebez media - ሰበዝ ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Sebez media - ሰበዝ ሚዲያ:

Videos

Share

እኛ !

ሀገራችንን ኢትዮጵያን የሚመለከቱ ወሬዎችን በፍጥነት እና በትጋት ለእናንተ ለማቀበል ይንን ገጽ ከፍተናል፡፡ወዳጆቻችን ይሁኑ!


Comments

በፈተና የተሞላ ህይወት

አራት ልጆቼን ቀብሬያለው

የቀረኝ ብቸኛ ልጅም የአእምሮ ህመምተኛ ሆነብኝ

https://youtu.be/4HJKcs6QqU0
አቡበከር ናስር ከመሪያ ጎሉ በውሃላ
ትናንት ምሽት በቱሉ ዲምቱ መንገድ ላይ የደረሰ ዘግናኝ አደጋ ነው

ሀሳቡ ፈጥኖ ከቤቱ መድረስ ከልጆቹ ጋር መተያየት ነበር።
ከአደጋው ከደቂቃዎች በፊት ደውሎም ልጆቹን ደርሻለው ጠብቁኝ እንዳተኙ ብሏቸዋል።

በመኪናው ላይ ለቤቱ የጫነው ሽንኩርትና ከሰል ይታያል።
እንዳሰበው በሰላም መድረስ ከቤተሰቡ መገናኘትን አልታደለም። ከቤቱ ሳይደርስ ክፉ ቀደመው

ከከባድ የጭነት ተሽከርካሪ ጋር ተጋጨ መኪናው ከቁጥጥሩ ውጪ ሆነ ዘግናኙ አደጋም ደረሰ።

በመኪናው ውስጥ አብሮ የነበረው ሰው ሲተርፍ አሽከርካሪው ሆስፒታል እንደደረሰ ህይወቱ አልፏል።

እባካችሁን በጥንቃቄ እናሽከርክር!
በየጎዳናው የወደቁ ከ200 በላይ የአዕምሮ ህሙማንን ከጎዳና አንስቶ የሚያኖረው ሰሊሆም የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር በመድሃኒት እጦትና በሌሎች ችግሮች ምክንያት ስራዬ እየከበደብኝ ነው ሲል ተናገረ፡፡

የአዕምሮና ተጓዳኝ ህመም ያለባቸውን ሰዎች ከጎዳና አንስቶ የሚያኖረው ማዕከሉ ህፃናት፣ ወጣቶችና አረጋዊያን በየቀኑ መውሰድ ያለባቸውን መድኃኒት ወጪ መሸፈን ከአቅሜ በላይ እየሆነብኝ ነው ብሏል፡፡

የእንጦጦ ቅዱስ ራጉኤል ቤተ ክርስቲያን ግቢን ተከራይቶ ስራውን የሚከውነው ማዕከሉ ከ200 በላይ የአዕምሮ ህሙማንን ማኖር የሚችልበት ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡

ወጣት ሚኪያስ ለገሰ የሰሊሆም የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር መስራች ነው፡፡

የተቋሙ መስራች እንደነገረን በተለይ በዚህ ክረምት ወደ ግቢው የተቀላቀሉ የአዕምሮ ህሙማን ቁጥር ከፍተኛ በመሆኑ ማዕከሉ ከአቅሙ በላይ ተጨናንቋል ፡፡

አዲስ ህሙማንን ማንሳት ብናቆምም ሕፃናትን ጨምሮ ሌሎች የአዕምሮ ህሙማንን ከደጃፋችን ጥለው ስለሚሄዱ እነሱን ማንሳት የግድ እየሆነብን ግቢውም እየተጨናነቀ ነው ብሏል።

ሚኪያስ እንደነገረን በአሁኑ ሰዓት የማዕከሉ የዕለት ወጪ ወደ 20,000 ብር ደርሷል፡፡

ለግቢው ኪራይም በየወሩ 7000 ይከፍላሉ፤ ይሄ ሁሉ ያለምንም ቋሚ ገቢ የሚሸፈን ነው ይላል።

ተቋሙ የራሱን ማዕከል ለመገንባት ያቀረበው የቦታ ጥያቄ እስካሁን ምላሽ እንዳላገኘም ነግሮናል።

ይህ ሁሉ ሲደራረብ አንዳንዴ በስራችን ተስፋ ስለመቁረጥ እንድናስብ ያደርገናል ይላል ሚኪያስ፡፡

ስሊሆም የአእምሮ ህሙማ መረጃ ማህበር የተመሰረተው በ2008 እንደሆነ በዚሁ የበጎ አደራጎት ስራ ከ6 ዓመታት በላይ ማሳለፉንም ከመስራቹ ሰምተናል፡፡

ምንጭ፦ ሸገር ራዲዮ
ETHIOPIA
እንኳን ደስ ያለን!

የማይረሳ ድንቅ ምሽት!

ኢትዮጵያ በኮሎምቢያ ካሊ የዓለም ከ20 ዓመት በታች የአትሌቲክስ ሻምፒዮና የመዝጊያ ውድድር ደምቃ አመሸች።

አራት የፍፃሜ ውድድር፦

አራት ወርቅ ሁለት ብር

በሴቶች 1500ሜ ወርቅ

በወንዶች 800ሜ ወርቅ

በሴቶች 5000ሜ ወርቅ እና ብር

በወንዶች 3000ሜ መሰናክል ወርቅ እና ብር

በአንድ ምሽት ተጨማሪ 4 ወርቅና 2ብር
በድምሩ 6 ሜዳሊያ

የምሽቱን የመዝጊያ ውድድር አለማየት ያስቆጫል።

በተለይ የሴቶች 5000ሜትር እና የወንዶች 3000ሜትር መሰናክል ልዩ ነበር፣ አትሌቶቻችን ኢትዮጵያ ሁሌም ተተኪ እንዳላት በሚገባ አሳይተውናል።

ውድድሩ ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያ 6 ወርቅ

5 ብር

1 ነሀስ

በማግኘት ከአፍሪካ ቀዳሚ ከዓለም አሜሪካና ጀማይካን ተከትላ ሶስተኛ ሆና አጠናቃለች።
ቤልግሬድ2022 - የዓለም የቤት ውስጥ ውድድር፤
ሜዳልያው
4 ወርቅ፣ 3 ብር፣ 2 ነሃስ፣ በድምሩ 9 ደርሷል፡፡
ደረጃችንም እስከ አሁን 1ኛ ሲሆን አሜሪካን አስከትለን እንገኛለን፡፡
ኢትዮጵያችን እንኳን ደስ አለሽ!

ምንጭ: ኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
እንኳን ደስ አለን!

በ18ኛው የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሴቶቾ 3000 ሜትር ውድድር ወርቅና ነሀስ አግኝተናል።

በሴቶች ምድብ የ3,000ሜ የፍፃሜ ውድድር ወርቅና ነሐስ በአትሌት ለምለም ሐይሉና በአትሌት እጅጋየሁ ታዬ ስናገኝ ዳዊት ስዩም አምስተኛ በመሆን አጠናቀዋል።

እንኳን ደስ አለን!
ጉቦ ለመቀበል የተደራደሩት ጋዜጠኞች ገንዘቡን ሲቀበሉ ተይዘው ክስ ተመስርቶባቸዋል
_____ ____ ___ ___ ___ ___ __ __ __

ዐቃቤ ህግ ከባድ የሙስና ወንጀል በፈፀሙ በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የኦሮምኛ ክፍል ኃላፊና በግብረ አበሩ ላይ ክስ መሰረተ

ዐቃቤ ህግ ክስ የመሰረተው አንድ የግል ድርጅት በሚያመርተው የታሸገ ውሃ ውስጥ በሃሰት ባዕድ ነገር እንደተገኘ ጠቅሶ በሚዲያ እንደሚያጋልጥ በማስፈራራት በጥሬ ገንዘብና በቼክ ግምሽ ሚሊዮን ብር ጉቦ ሲቀበል በተያዘው የኢቢሲ ጋዜጠኛና ግብረ አበሩ ላይ ነው፡፡

በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የኦሮምኛ ክፍል ኃላፊው በላቸው ጀቤሳ ዋቆ እና በ2ኛ ተከሳሽ አለማየሁ ቂጢሳ ሚጄና ላይ ክሱን የመሰረተው በጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዘርፍ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጄነራል ዐቃቤ ህግ ነው ።

የዐቃቤ ሕግ ክስ እንደሚያስረዳው 1ኛ ተከሳሽ በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (EBC) የኦሮምኛ ዝግጅት ክፍል ኃላፊ ሆኖ ሲሰራ ከ2ኛ ተከሳሽ ጋር በመመሳጠር የሸገር ውሃ አምራችና አከፋፋይ ከሆነው “ ኩኒስ በሪ ጠቅላላ ንግድ ኃ/የተ/የግ/ማህበር” የተባለውን ድርጅት በሀሰት የሚያመርተው ውሃ ባዕድ ነገር እንዳለበትና በሚዲያ እንደሚያጋልጡት አስፈራርተውታል።
ተከሳሾቹ ከጥር ወር 2014 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ድርጅቱ ባለቤት በተደጋጋሚ ስልክ በመደወል “ኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ ከሚገኝ አንድ ሱቅ ውስጥ የሸገር ውሀ ለመጠቀም ገዝተን ከውሀው ውስጥ ሶፍት መሳይ ቆሻሻ ነገር ያገኘንበት በመሆኑ ይህንንም ለኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጥቆማ ስላቀረብን አግኝተህ አናግረን ” በማለት ካግባቡት በኋላ 1ኛ ተከሳሽ “በታሸገው ውሀ ውስጥ ከተገኘው ባዕድ ነገር ጋር ተያይዞ መረጃን በሚዲያ ከተላለፈ ስለምትጎዱ እኛም ደግሞ ጉዳዩን በሚዲያ ከማስተላለፍ እንድንታቀብ፤ የተበላሸውን ውሃና ለኢቢሲ (EBC) ያስገባነውን በምስል የተደገፈ ጥቆማ እንድንመልስላችሁ ገንዘብ ክፈሉን” በማለት ብር 500,000 (አምስት መቶ ሺህ ብር) ለመቀበል በተስማሙት መሰረት ከድርጅቱ ባለቤት ሲቀበሉ በህግ አስከባሪ አካላት የተያዙ በመሆኑ ሁለቱም ተከሳሾች በዋና ወንጀል አድራጊነትና ተካፋይ በመሆን በፈፀሙት ጉቦ መቀበል ካበድ የሙስና ወንጀል በጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዘርፍ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጄኔራል ዐቃቤ ህግ ኮፖሊስ ጋር በመሆን ሲያካሂድ የነበረውን ምርመራ በማጠናቀቅ ክስ መስርቶባቸዋል ፡፡

ክሱም ዛሬ መጋቢት 09/2014 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ሰዓት በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ሙስና ወንጀል ችሎት ተከሳሾች በፅ/ቤት ቀርበው ክሱ እንዲደርሳቸው ተደርጎ ለመጋቢት 12/2014 ዓ.ም ክሱን በንባብ ለማሰማት ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል።

ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ
አዲስ አበባ ሰላም ነች ስጋት ሊሆኑ የሚችሉ ነገሮች በቁጥጥር ስር ውለዋል

ዶ/ር ቀንአ ያደታ የአ/አ የሰላምና ፀጥታ

ሀላፊው ዛሬ በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ መግለጫን ሰጥተዋል

በአ/አ ለሽብር ተግባር ሊውል ታስቦ የነበረ ከፍተኛ መጠን ያለው የጦር መሳሪያ፤ገንዘብ፤ አልባሳትና ገንዘብ በቁጥጥር ስር ውሏል።
የውጭ ጫናው አሁንም እንደቀጠለ ቢሆንም ምንም የሚያሰጋ ነገር ግን የለም ህዝቡም ሊረጋጋ ይገባዋል ብለዋል።
መስከረም 20 ቀን ድምፅ በተሰጠባቸው በሁሉም ምርጫ ክልሎች ብልፅግና ፓርቲ ማሸነፉ ይፋ ተደርጓል።

በሶማሌ አንድ የምርጫ ክልል አንድ የግል ተወዳዳሪ ለክልል ም/ቤት ከማሸነፋቸው ውጪ ያሉትን ሁሉንም የህዝብ ተወካዮችና የክልል ም/ቤት ወንበሮች ብልፅግና ፓርቲ ማሸነፉን ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ አድርጓል።

ምንጭ: ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
ከመስቀል አደባባዩ የመድረክ ስራ ጀርባ ያሉት አርክቴክት እኚህ ናቸው ተብሏል።

አርክቴክት አለበል ደስታ
አዲስ ምዕራፍ

መስቀል አደባባይ
ከኮንዶሚኒየም ተመዝጋቢ ከ60 በመቶ በላዩ የአ/አ ነዋሪ አይደለም!
— — — — — — — —

በአዲስ አበባ የጋራ መኖሪያ ቤት ለማግኘት ተመዝግቦ ከሚጠባበቅ አንድ ሚሊየን ገደማ ህዝብ ከ600 ሺህ በላዩ የአዲስ አበባ ነዋሪ አይደለም ተባለ።

የሚበዙት የቤት ተመዝጋቢዎች አዲስ አበባ የት እንደሆነች እንኳን የማያውቁ እጣ ሲደርሳቸው ሽጠው የሚሄዱ እንጂ የሚኖሩበት አይደሉም ተብሏል።

ይህንን የተናገሩት የአ/አ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ናቸው።

ምክትል ከንቲባዋ በተደረገ ጥናት ውጤት መሰረት ይህው ተረጋግጧል ብለዋል።

ለእጣ ማውጣቱን ስራ እንዲያግዝ ተብሎ የተሰራው ሶፍትዌርም ብዙ ችግር ያለበት የሚፈለገውን ሰው ብቻ ለይቶ እንዲያወጣ ተደርጎ የተሰራ ችግር ያለበት ነው ብለዋል።

እነዚህን ችግሮች ስናርም ቆይተናል ያሉት ምክትል ከንቲባዋ አሁን በተለያየ ማጣራት ያገኘነውንና ግንባታቸው ያለቁ 30ሺህ ገደማ ቤቶችን ለእድለኞች እናስተላልፋለን ብለዋል።

የ1997 ተመዝጋቢዎችም ቅድሚያ ይሰጣቸዋል ብለዋል።

Via: Sheger Fm Radio
ነገሩ እንዴት ነው?

ፕሬዳንት ባይደንና ባለቤታቸው እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ ብለዋል

በአማርኛ ሁሉ መልካም እንቁጣጣሽ ብለዋል.
የመድረክ አቀራረቡና ሙዚቃን የሚጫወትበት መንገድ ይለያል።

• አዲስ አበባ ቤቴ

• ችግርሽ በኔ አልፏል

• ተማር ልጄ

• ማን ይሆን ትልቅ ሰው

እጅግ ብዙ ድንቅ ስራዎችን ሠርቷል።

ብላኮ-ሶል: ሸበሌስ: ሶል-ኤኮስ እና ሌሎችም ደማቅ ስራዎችን አብሮአቸው የሰራ የግል የሙዚቃ ቡድኖች ናቸው።

ቀድሞ የሚታወቅበት የሙዚቃ ክፍሉ የፖሊስ ሰራዊት የሙዚቃ ክፍል ነበር።

አለማየሁን በቅርብ የሚያውቁት ጥንቅቅ ያለ በቀጠሮ ቀልድ የማያውቅ በስራው የማይደራደር ነው ይሉታል።

ከምንም በላይ ኢትዮጵያን የእውነት ይወዳል ስለልጆቿ ችግር አብዝቶ ይጨነቃል ንግግሩም ቀጥተኛ ነው።

ይህ ታላቅ ሙዚቀኛ ቀኑ ደርሶ ተለየን። ነፍስህ በሰላም ትረፍ
ታላቁ ኢትዮጵያዊ የሙዚቃ ሰው አረፈ!

ቤተሰቦቹ እንዳሉት ቀን በሰላም ውሎ አመሻሽ ላይ ድንገት አመመኝ ብሎ ወደ ሆስፒታል ሄደ በህክምና ላይ እንዳለ ህይወቱ አለፈ በቃ የሆነው ይህው ነው።

ይህቺን የተፃፈች ቀን ማን ያልፋታል..

አሌክስ ነፍስህ ከደጋጎቹ ጎን ትረፍ።
#}