12/22/2023
መልካሙን ሳናስበው አጣነው ።
ለተቸገረ ደራሽ ; ለተራበ አብይ ;ሰው ሲከፋው መካሪ እና እንዲሁም ከጓደኞቹ ጋር በመሆን ብዙ ህፃናትን ኢትዮጵያ ውስጥ የሚያሳድግ እንደ ስሙ እጅግ መልካም ሰው ነበረ።
መልካሙ ደምሴ እጅግ ተወዳጅ በነበረው የመጀመሪያው የETV 120 የመዝናኛ ፕሮግራም አዘጋጅ የነበረ ሲሆን ነዋሪነቱን በአትላንታ ካደረገ ጊዜ ጀምሮ በተለያዩ የበጎ አድራጎት ስራዎች በመሳተፍ ይታወቃል፡
ከነዚህም ውስጥ በተስፋ ለኢትዮጵያ ምግባረ ሰናይ ድርጅት ውስጥ መስራች እና የቦርድ አባል ፤ በምሳሌ ምግባረ ሰናይ ድርጅት ውስጥ መስራች እና የቦርድ አባል ፤ በሰሜን አሜሪካ የጥበብ ባለሙያዎች ማህበር [EASNA) መስራች እንዲሁም በአድማስ ሬዲዮ ተወዳጅ ጋዜጠኛ በመሆን እያገለገለ የነበረ ወዳጃችን ነበረ።
ስለ መልካሙ ብዙ ማውራት ይቻል ነበረ ግን አቅም አጣሁ። መልኬ ያንተን ሞት እያመንኩ ባይሆንም ነፍስህን ልዑል እግዚአብሔር እንዲምራት እፀልያለሁ። ለቤተቦችህ እና ለእኛ ለወዳጆችህም መፅናናትን ተመኘሁ።
😭