ABREN MEDIA & Entertainment

ABREN MEDIA & Entertainment አብረን ሚዲያ፤ አብሮነት፤ ስነ ጽሁፍና ጥበብ፤ እድገትና ውበት፣ በነገር ሁሉ መልካምን እና ቀናን ነገሮች ፈልገን የምንገልጽበት መድረክ ነው።

https://youtu.be/y6cEBglaLL4?si=FULT_7Gg8nzlvOZV ከጋዜጠኛ ኤልያስ አወቀጋ ያደረኩት ክፍል አንድ ቃለ መጠይቅ።  አትሄጂም ስለተሰኘው መጽሃፌ ያደረግነው  ጠለቅ ያ...
12/15/2023

https://youtu.be/y6cEBglaLL4?si=FULT_7Gg8nzlvOZV ከጋዜጠኛ ኤልያስ አወቀጋ ያደረኩት ክፍል አንድ ቃለ መጠይቅ። አትሄጂም ስለተሰኘው መጽሃፌ ያደረግነው ጠለቅ ያለ ውይይት እንድታዳምጡ ጋበዝኳችሁ።

በደርግ ዘመን የነበረውን ክፉ ሕይወት... Nibab Television more :ቴሌግራም :- https://t.me/NahooT...

10/23/2023

እናውራ

ሰሞኑን አንዲት የምታምር ልጂ ምስል በፌስቡክ ላይ ሲመላለስና ባየሁት ቁጥር ልቤን ሲሰብረኝ ሰነበተ። ልጅቷ እራሷን እንዳጠፉችና የመጨረሻዋ ደብዳቤ ለፈጣራ እንደጻፈች የሚያሳይ አንጀት የሚበላ (dear God amen ) የሚል ምስል አብሮት አለ። በፈጣሪዬ እና በአሜን መካከል የሚታዩት የእንባዎችዋ ጠብታወች ያማሉ። ባገኘሗትና እቅፍ አርጌ አይዞሽ ይሄ ቀን ያልፉል ባልኳት! ከነችግርሽ የሚወድሽ አምላክ አለ ባልኳት! አለያም የጨነቀትን ነገር እንድትተነፍሰው ባደረኳት!! የሚሉ ስሜቶች ይፈጥራል!!!!

አሁን ለዚች ቆንጆ እረፍዷል። ምንም ማረግ አይቻልም። ምን ሆንሽ? ምን ልርዳሽ? ወደማንላት አለም ሄዳለች። ግን እሷ እየታገለች የነበረውን ትግል እየታገሉ፣ ሳይስቁ ስቀው ልባቸው እየደማ ትግል ላይ ያሉ ብዙ አሉ።

አንዳንዴ አይዞሽ/አይዞህ የሚባሉት አራት ፊደል ያላቸው ቃላት የሰውን ነፍስ ያተርፉሉ። አንዳንዴ ያች ደቂቃ እስክታልፍ አብሮ ለተቀመጠና ለታገሰ፣ ና ጆሮ ላበደረ ሰው ብዙውን ነገር ዘክዝከው አውርደው ተንፈስ ካሉ በሗላ፤ ለካ የኔ አለመኖር የሚቆጨው ሰው አለ ወደሚል ሐሳብ ይሻገራሉ። አንዳንዴ ደግሞ በየሶሻል ሚዲያው ቢለቀልቁት በየቀኑ ቢጽፉም ቢያነቡም የሚሰማ ጠፍቶ ወይኔ የሚያስብል ቦታ ያደርሰናል።

አምስተኛው መጽሐፌ "አብረን" ዋና ካራክተርዋ እሪስዋን ስለምታጠፉ። የእህቴን፣ የጋደኛዬን፣ ያክስቴን ልጂ ታሪክ ነው እንዴ የጻፍሽው የሚል አራት ወይም አምስት መልክት በየወሩ ይሰርሰኛል። እኔ የጻፍኳት የተፈጠረች ካራክተር ብትሆንም ብዙዎች ይሄ ህመም እንደሚሰማቸው ስለተረዳሁ የቀረጽኳት ገጸባህሪ ናት።

የእውነት ትግል ውስጥ ያሉትን እንዴት እንርዳቸው። ከቀን ወደቀን ቁጥራቸው እየጨመረ ነው። አላየሁም አሉ የምንልበትን ሰአት አልፈናል። እና እናውራ!

ምልክቱ ምንድነው? ከጠረጠርንስ ምን እናርግ? ሌሎችም ሌሎችም ሃሳቦችን አክሉበት እና እንወያይበት።

#እመቤትመንግስቴ #ዝምከምልብዬ #አብረን #በቃ

09/26/2023

ዳንደላይን

በጨዋታ መሐል እትዬ ጥሩወርቅ "ይሄ ደፉር ዛሬ ጠዋት ያለኝን ጉድ ልንገራችሁ" ብለው ጀመሩ።

"ምነ አለሽ"ብለው ቡና ሊጠጡ የተሰበሰቡት ሴቶች ጠየቁ።
እትዬ ጥሩ (የሰፈሩ ሰው እንደሚጠራቸው) ቤታቸውን ተከራይቶ ስለተቀመጠው የኪውባ ወታደር ሲያወሩ ሁልግዜም "የኔው ቤት ጉደኛ "ይጨምሩበታል። ስለሱ ሲያወሩ የሰፈር ሰው በመገረም ሲለሚያዳምጣቸው ሳይጨማምሩበት አይቀሩም።

እትዬ ጥሩ ባላቸው ከሞቱና ንብረታቸውን ከተወርሱ በሗላ መንግስት ከሚሰጣቸው ሁለት መቶ ሐምሳ ብር ውጭ ምንም ገቢ ያልነበራቸው፤ የተወሰነውን የሰርቪስ ክፍል አከራይተው ለተከራዩት ሰወች ምግብ እየሰሩ ነበር የሚተዳደሩት።
ከነዚህ ሰወች መሐል ሄሱዝ የተሰኘ የኪውባ ወታደር አለበት። የኔው ጉደኛ የሚል ቅጽል ስም ቢሰጡትም ለትዬ ጥሩ ሁሉ ነገሩ ያስገርማቸዋል። እማማ ጥሩ ስለ አበላሉ፣ ስለ አለባበሱ፣ ስለደግነቱ፣ ስለ ቋንቋውእና ስለ ሁሉም ነገር ማውራት ይወዳሊ።

"ምን ቢልሽ ነው ዛሬ በጠዋቱ እንዲህ የተንተከተክሽው" አሉ እትዬ የሺ።

"ሆ " ብለው ጀመሩ እማማ ጥሩ።
ቁርስ አቀረብንለት፣ የጨዋ ቁርስ ለዛውም። ሳይበላው ተነሳ። ምነ ሆነሃል ብለን ጠየቅነው። ሰለቸኝ አላለንም!! ሁሌ የምታቀርቡት አንድ አይነት ነው። አንዳንድ ቀን ሌላ ነገር ለምነ አትሰረሩም አለን! ጉድ እኮ አያልቅም ብለው ሳይጨሬሱ።
የሰፈሩ ሴቴቹ በሙሉ አንድ ላይ ተንጫጩ። "ተናቅን፤ ምግባችን ተናቀ በሚል አነጋገር ተያዬ።" እድል ቢያገኙ እና አቅም ቢኖራቸው የሚደበድቡት ይመስል ነበር።

"መች እሱ ብቻ" አሉ እትዬ ጥሩ። አገራችን ድሐ ናት አንተ የለመድከው ምግብ የለንም ስንለው ምን ቢመልስ ጥሩ ነው። "ድሐ አይደላችሁም ጥጋበኛና፣ በጣም መራጮች ናችሁ፣ ከዚያ በላይ ደግሞ ብዙም ለአዲስ ነገር ቦታ አትሰጡም አለን።" የይንቨርስቲ ተማሪ ልጃቸው ያስተረጎመችውን እየደገሙ። እውጭ ወጥቶ ከዛፍ ላይ ኮክ አራግፎ እሱን እየገመጠ ሄደ አሉ እማማ ጥሩ።

የስድብ ናዳ ከሰፈሩ ሴት ወረደበት። "ይበለው ከኛ ቅንጬ እና ፍትፍት ደረቅ ኮክ ከመረጠ ምን አገባን።" ያድርቀውና፣ "የአህያ ስጋ ከአልጋ ሲሉት ከአመድ" አሉ ተባባሉበት።

ምን እሱ ብቻ። ይሄ ቅጠል ልጆቹ የሚጫወቱበት ጢቢ ጢቢ የሚሉት አይቀረው፣ የውሻ ምላስ ብለን እንደ አረም ነቅለን የምንጥለው አይቀረው። ቀቅላችሁ ካላመጣችሁ እያለ መከራችንን ነው የሚያሳየን። እመ ብርሐን ሰተት አርጋ ወደመጣበት ተመልሰው እንጂ አሉ። ሌሎቹን ጎረቤቶች አይን አይን እያዬ።

እውነቱን ለመናገር እንዲሄድቤቸው አይፈልጉም። የሌሎቹ ሶስት ተከራዮች ሂሳብ በአንድነት ተደምሮ እሱ የሚከፍላቸውን አይተካከልም። በእጥፍ ነው የሚከፍላቸው። ደግ ነው ምናምን ከውጭ ገዝቶ ከገባ ሳያካፍላቸው ወይ ለሱ የገዛውን ለሳቸው ሲይገዛላቸው አይቀርም። ከዚያም በላይ በጎረቤቶች ዘንድ ተደማጭነትን ሰጥቷቸዋል። ባፋቸው የሚናገሩትን ልባቸው ባያምነውም ከመናገር ወደሗላ አይሉም።

ሰሞኑን የሰፈሩን ቡና ጨዋታ ማሰላሰል ጀምሬአለሁ። በተለይ ደግሞ የሱ (ኢሱዝ ለማለት የሚጠቀሙበት ስም) አደረገ የሚባለውን።

አንድ ጤናን በተፈጥሮ መንገድ የሚል ኮንፍረንስ ተካፍዬ ስለ ዳንደላይን (የውሻ ምላስ) ጥቅም በጣም በከባድ ሰማሁ። ስለ ሳማም እንደዛው። ጢቢ ጢቢ ቅጠል፣ ስለ ሚጥሚጣም ሌሎችም ሌሎች ቅመማ ቅመሞች ጠንከር ያለ ሙገሳ ስሰማ ዋልኩና ከዛሬ አርባ አመት በፊት የሰማሁትን ወሬ አስታወሰኝ።

እኔ የምኖርበት አካባቢው ካለ የጤና ምግብ አቅራቢ (whole food) የውሻ ምላስ በውድ ዋጋ ገዛሁ። እንዴት አርጌ እንደምሰራው ብዙ ባላውቅም ይሄን ያህል ጥቅም ካለው በሚል ነበር። እንደ ጎመን ሸርድጄ ቀቀልኩት። ጣእሙ ያው ጎመን ሆኖ አገኘሁት። ከዛሬ ጀምሬ ምግቤ ውስጥ እንደማጠቃልለው ለራሴ ነገርኩ።

ሁለት ነገር ተማርኩ። እናቶቻችን የትኛውም የሳይንስ ወረቀት ከመታተሙ በፊት ጠንቅቀው ያወቁት ቅመማ ቅመም ትልቅ ሐብት መሆኑን እና አዲስ ነገር ደፍሮ መሞከርን አስፈላጊ መሆኑን።

#እመቤትመንግስቴ #ዝምከምልብዬ #አብረን #በቃ

09/21/2023

ዝም አልልም

ነግረውኝ ነበር ደግመው ደግመው
ዝም በይ ዝምታ ወርቅ ነው

አይኔ እያየ ክፉን ነገር
ዝምታ ወርቅ ነው ብዬ ባልናገር

ማን ይሆን ወንጀለኛው?
ማን ይሆን ባለ በደል?

እኔ እያየሁ ያላየሁት ሰምቼ ያልሰማሁት
ወይስ እነሱ ዝም በይ ዝምታ ወርቅ ነው ያሉት

#ዝምከምልብዬ #በቃ #እመቤትመንግስቴ #አብረን

05/01/2023
ጎራ በሉ
11/14/2022

ጎራ በሉ

10/18/2022

ያቀ ዛሬ ሆነ

አንድ ወቅት ላይ የምኖርበት አካባቢ ያለ የደራሲያን ስብስብ የሚሰጠው የአምስት ቀን ስልጠና ላይ እንድገኝ ተጋበዝኩ። እውነት ለመናገር በዚህ ደረጃ ያለ ስልጠና ስካፈል የመጀመሪያ ጊዜዬ ሰስ ነበር፤ ምን እንደሚጠብቀኝ በፍጹም አላወኩም። ግን በመጋበዜ ከልክ ያለፈ ተደስቼ የሚመጣውን ሁሉ ለመቀበል እራሴን አሰናዳሁ።

የመጀመሪያው ቀን ገብተን እንደተቀመጥን የእለቱ መምህር በፈገግታ ተቀበለን። አጠር ያለ ንግግር ከአደረገ በሗላ፣ አምስት አምስት እሩብ ካርዶች (3×5) ለሁላችንም አደለን እና ህይወታችሁን በአምስት ምእራፍ ከፋፍላችሁ፤ ታራካችሁን በነዚህ አምስት ካርዶች ላይ አስፍሩ የሚል ቀጭን ትዛዝ አከለበት። እዚያ ላይ ቢያቆም መልካም ነበር ግን ከአምስት ቀን በሗላ የፕሮግራሙ የመጨረሻ ቀን ስመለስ ሁላችሁም የጻፋችሁትን መድረክ ላይ ለማንበብ ተዘጋጁ ብሎ ፈገግ አለ።

ብዙዎቻችን ግራ በመጋባት ተያየን። ምን ማለቱ ይሆን? በነዚህ የወረቀት እሩብ አምስት ካርዶች ላይ ሰው የህይወት ታሪኩን እንዴት አርጎ ማሳረፍ ይችላል? እርስ በርሳችን ተፉጠጥን።
እውነት ለመናገር ከየት ጀምሬ፣ የቱን አንስቼ፣ የቱን እንደምተወው ማሰብ ጀመርኩ። ለኔ አይደለም የህይወት ታሪክና ያለፈውን ሳምንት ለመግለጽ በቂ ቦታ የተሰጠኝ ስላልመሰለኝ መጨነቅ ጀመርኩ።

መምህሩ መደናገራች የገባው ይመስል፤ አንድ እናንተ የተቀመጣችሁበት ቦታ ላይ የነበረች ሴት የጻፈችውን ታሪክ እንደ ምሳሌ አነብላችሗለሁ አለና ለኛ የሰጠንን የሚመስሉ አምስት እሩብ ካርዶችን አውጥቶ ማንበብ ጀመረ።

የወረቀቱ ባለቤት "ፖርሻ ኔልሰን" ትባላለች። አንድ አንድ ወቅት ላይ ልክ ዛሬ እንደተሰበሰብነው ሰዎች ይሄው ጥያቄ የቀረባላት ጸሐፊ ስትሆን፤ መልስ ስትሰጥ የህይወትዋን በአምስት ምእራሮች እንደሚከተለውም ውብ አርጋ ስላስቀመጠቻቸው ለሌሎች ተማሪወች በምሳሌነት እንደሚጠቀሙባቸው ከነገረን በሗላ መምህራችን አነበበልን።

ምእራፍ አንድ

በአንድ ጎዳናላይ ስጓዝ የተቆፈረ ጉድጓድ ነበር። አላየሁትም! ወደኩ። ከዚያ ጉድጓድ ለመውጣት ብዙ ግዜ ፈጀብኝ። ብዙም ተሰቃየሁ። ግን የኔ ስህተት አይደለም። ጉድጓዱን የቆፈሩት ሰወች ስህተት ነው በሚል እራሴን አጽናናሁ። የልጅነት ጊዜዬን አብዝቶ አስታወሰኝ።

ምእራፍ ሁለት

በዚያው ጎዳና ላይ እራሴን አገኘሁት። የተቆፈረው ጉድጓድ አሁንም አለ። አላየሁም አሉ ብዬ መንገዴን ቀጠልኩ። እንደገና እዛው ጉድጓድ ውስጥ ወደኩ። የገዛ ጥፋቴ ነው ብዬ ተነጫነጭኩ። አሁንም እረጂም ግዜ ወሰደብኝ። ልጅነቴን ሳይሆን አሃያወቹን እድሜዬን አስታወሰኝ።

ምእራፍ ሶስት

እራሴን እንደገና እዛው መንገድ ላዬ አገኘሁት። የተቆፈረው ጉድጓድ አሁንም አለ። በደንብ አርጌ አይቼዋለሁ። ግን ልማድ አይደል እንደገና ወደኩ። መውጣቱን ስለተለማመድኩት ብዙ ግዜ አልፈጀብኝም። ጥፋቱ የኔ እንደሆነ እና መጠንቀቅ እንዳለብኝ ለራሴ መከርኩት። ወደ ስላሰዎቹ ቁጥሬ የዞረ መሰለኝ።

ምእራፍ አራት

እዛው መንገድ ላይ እራሴን አገኘሁት። የተቆፈረው ጉድጓድ አሁንም አለ። ተመልሼ እዛው ጉድጓድ ውስጥ እነዳልወድቅ እጂግ በጣም ተጠንቅቆ አለፍኩ። እራሴንም ሆነ ሌሎችን መውቀስ አቆምኩ። ህይወት ላይ ያለኝ አመለካከትም ሆነ እድሜዬ ከፍ ብሎ አገኘሁት።

ምእራፍ አምስት

መንገድ ጀመርኩ። ቆም ብዬ ሳስብ በሌላ መንገድ መሄድ እንደምችል ስለተረዳሁ ያንን የተቆፈረ ጉድጓድ ያለበትን ትቼ በሌላ መንገድ ጉዞዬን ጀመርኩ። አሁን ሲገባኝ ይሄ እጂግ በጣም የተሻለ መንገድ ነው። ህይወት ትልቅ ትምህርት ቤት ነው። ከመንገዶችም ሁሉ የተሻለው ነው። የተቆፈረ ጉድጓድ የሌለበትን መንገድ መፈለግ የኔ ስራ ሆኖ አገኘሁ።

በመገረም እና በጥሞና አዳመጥኩት። መጽሃፍ ብትጽፍ እና ብዙ ሐተታት ብታስቀምጥ ከዚህ የላቀ ልታስተምረኝ እንደማትችል ተረዳሁ። ያላሰብኩት እንባ በፊቴ ላይ ሲወርድ ሙቀቱ ተሰማኝ።

ተራዬን ለመጻፍ ጀመርኩ

ምእራፍ አንድ

የተወለድኩት ኢትዮጵያ የምትባል ውብ ምድላይ ቢሆንም፤ ለግዜው ደርግ የሚባል የተሸቀበ እድል ገጥሟታል። የትኛው ደግ፣ የትኛው ክፉ ሰው መሆኑንን ለይተን ማወቅ ያቃተን ወቅት ላይ ያለነው። ቤተሰቦቻችን በየቀኑ ለቅሶቤቴ፣ በየቀኑ ጥቁር ልብስ፤ በየቀኑ ቀብር የሚውሉበት ምድር መሆኑን ተረዳሁ። የኔና የብጤዎቼ እድል እንደ ህጻን በመቦረቅ ፈንታ፤ ከረሜላ እንደተቀማ ልጂ በማናውቀው እና ባልገባን ችግር ቀን በቀን በሐዘን የተወረረ ሆነ። ከኔ የተሰረቀውን ወይም የተቀማነውን የልጅነት ዘመኔ ብዬ አሰብኩት።

ምእራፍ ሁለት

ችግሩ እየባሰ ነው። ብዙ ወላጆች ልጆቻቸውን አብዮት ለተሰኘ ሰደድ እሳት ገበሩ። የኛ ወላጆች ደግሞ ነገ እጣው የኛ እንዳይሆን ሰግተው የቀን ተቀን ህይወታቸው በፍርሐትና በማሸማቀቅ የተሞላ ሆነ። ለመኖር እና የመኖርን ነጻነት ለማወቅ ይህቺን ኢትዮጵያ የምትባል ምድር በቦሌም በባሌም መላቀቅ እንዳለብን ተረዳን። ዛሬን ያላየ ለነገ አይኖርም የሚለው እውነት በየመንገድ ላይ ወድቀው በምናያቸው ታላላቆቻችን አስከሬን ይገለጽ ጀመር። ስደት እውነት ሆነ። ከእናት አባቴ፤ ከእህት ወንድሞቼ፤ ከማውቀው ሁሉ ነገር ተለይቼ ወደ ማላውቀው አለም አመራሁ። ልጅነት አበቃ!!

ምእራፍ ሶስት

ስደትንና ከስደት ጋር አብረው የሚመጡትን መልካምና መጥፍ ገጾች መለማመድ ጀመርኩ። ናፍቆትን፣ ከሚወዱት ቤተሰብ መለየትን እና አዲስ ባህልን፣ አዲስ ቋንቋን እኩል መለማመድ ጀመርኩ። ቢሆንም እኔ የትኛው ቦታ ላይ እንዳለሁ፣ ወይም ለየትኛው አለም እንደተጻፍኩ በፍጹም ማወቅ አልቻልኩም። ማንነቴን ፈልጌ ለማግኘት እየታገልኩ ነው።

ምእራፍ አራት

አዲሱ አለም የሰጠኝን ጸጋ መቀበል ብችልም አገሬን ግን መርሳት አልቻልኩ። ግን የተሰጠኝን እድል መጠቀም እንዳለብኝ ተረዳሁ። ሁሉንም መልካም ነገር ባየሁ ቁጥር እንዴት አርጌ ወደ አገሬ እና እኔ ወደ ምወደው ምድር ለመውሰድ እንደምችል ማሰብ ጀመርኩ። ግንድ ውሐ ላይ ቢንሳፈፍም አዞ ግን መሆን አይችልም የሚለው የአገሬ ብሂል፤ አገሬ ብዬ የተቀመጥኩበት አገር የሰው አገር መሆኑን ሌት ተቀን እያስታወሰ ያስጨንቀኝ ጀመር።

ምእራፍ አምስት

የነጻው አለም ብዙም ነጻ ያልሆነ፣ ሰወችን በብቸኝነት እና በፍቅር እጦት፤ በእኔ እበልጥ እኔበልጥ ፉክክር አስሮ፤ አንድ እርምጃ ወደፊት ሳያራምድ ባሉበት የሚያስረግጥ፣ እደርሳለሁ በሚል ተስፋ የሚያመላልስ፣ የሚያዩት በርግጥ ግን የማይጨብጡት፣ የህልም ህልም መሆኑን ተረዳሁ። ይህን ማወቄም ለአገሬ እና ለተወለድኩባት ምድር የተለየ ፍቅር ሰጠኝ። እኔን ፈልጌ አገኘሗት። ነፍሴ ምድር ላይ ለተፈጠሩ የሰው ልጆች በሙሉ በፍቅር ሰገደች፤ ከፍቅር የላቀ ምንም ሐይል የማትሻ ሆና አገኘሗት።

አምስቱን ምእራፎቼን ሲደመድም ከዚህ የተሻለ ነገር ይኖረኝ ይሆን? ግን ለግዜው የለኝም። አንብቢ ቢለኝ ይሄን ላንበው ነው? አላነበውም!! ሌላ የተሻለ ነገር መጻፍ እችል ነበር? ወይስ ያለኝ ይሄ ነው? አምስት ምእራፍ በጣም ትንሽ ነው ለዛውም እያንዳንድ ምእራፍ ከሩብ ገጽ ያልበለጠ። ከራሴ ጋር ትግል ጀመርኩ።

መምህሩ የመጀመሪያ ቀን የሰጠንን የቤት ስራ ሊሰበስብ ተመለሰ። የልቤ ምት መጠኑ በጣም እንደጨመረ ተረዳሁ። አሁን አንብቢ ቢለኝ ምን ልል ነዉ።

መጨነቄ የገባው ይመስል ትኩር ብሎ እያየኝ። ዛሬ መድረክ ላይ ወጣችሁ አንብቡ አልላችሁም። ግን ስትወጡ በሩ ላይ ሶስት ምርጫ አላችሁ አንዱን ተጠቀሙ አለ።

የመጀመሪያው የያዛችሁትን ወረቀት በስተቀኝ በኩል ያለው እሳት ውስጥ ማቃጠል ነው። ይሄንን ለሰውም አላሳይም አልናገረውም እዚሁ ትቼው ነው የምሄድ የሚመጥነኝ ካላችሁ፤ ይሄን ተጠቀሙ።

ሁለተኛው ደግሞ በስተግራው ያለው ሳጥን ውስጥ በፖስታ ከታችሁ ማስቀመጥ ነው። አንብቤ አስተያየት እሰጣችሗለሁ። እይታችሁን አብረን እንቃኛለን።
ሶስተኛው ደግሞ ሳታቃጥሉ ወይም ለኔ ሳትሰጡ የጻፋችሁትን ይዛችሁት መሄድ ነው። ምናልባት አንድ ቀን መጽሐፍ ታርጉት ይሆናል። እሱም ካልሆነ ለሌላ ሰው የራሱን አምስት ምእራፍ እንዲጽፍ እድል ትሰጡበት ይሆናል አለን።

በፍጥነት ይመታ የነበረው የልቤ ጋብ አለ። ለመወሰን የነበረኝ ግዜ እረጂም ባይሆንም የተሰጠኝ ምርጫው አስደሰተኝ። ምእራፎቼን ሰብስቤ በቦርሳዬ ከትቼ ወደቤቴ አመራሁ። አንድ ቀን እናንተም ለሌላው አምስት ካርድ ትሰጡ ይሆናል ያለው የመምህሩ አነጋገር አብሮኝ ቆየ።

የጻፍኩትን ደጋግሜ አየሁት። ከዚህ ቀደም በውስጤ ተቀብረው የነበሩ ብዙ ነገሮች ወደላይ ያኮበኩቡ ጀመር። ሌላም ሃሳብ ደጋግሞ ወደ አእምሮዬ መምጣት ጀመረ። ታሪካችን ሳንፈራ ሳንደብቅ በራሳችን አንደበትና ብእር ብንጽፈው፤ ብንናገረው ምን ይመስል ይሆን?

የተሰጠኝ የቤትስራ ዋናው አላማው አሁን ገና ቁልጭ ብሎ ታየኝ። አንድቀን አምስት ካርድ ለሌላ ትሰጡ ይሆናል ያለው የመምህ ድምጽ አስተጋባ። ያንን ንድ ቀን ዛሬ ሆኖ አገኘሁት። እነሆ አምስት አምስት ካርድ አደልኳችሁ። እራሳችሁን በርብሩ።

#እመቤትመንግስቴ #አብረን #ዝምከምልብዬ

My beautiful Sara, you are God's gift to me. I am blessed to be given a chance to call you my child, my sister, my frien...
10/09/2022

My beautiful Sara, you are God's gift to me. I am blessed to be given a chance to call you my child, my sister, my friend and my mirror. I love the strong woman you become. Your, love care and kindness for other human beings amazes me everyday. You are a joy to be around and I love you. Happy Birthday. Enjoy your day.

10/07/2022

ጭስ መውጫ

ከማልረሳቸው የልጅነት ትውስታዎች አንዱ፣ ከሞት ያመለጥኩበት ሌሊት ነው። አንድ ከባድ ዝናብ ጥሎ አጥንት የሚሰብር ብርድ የተከተለበት ምሽት እናቴ እስቲ እባካችሁ ከሰል አቀጣጥሉ እና አምጡ ትንሽ ይሙቀን አለች።
ከሰሉ ዝም ብሎ ከሚቃጠል ተብሎ ቡና ተፈላ። ሰብሰብ ብለን አንድ ክፍል ውስጥ ስንስቅ፤ የሰው አንድ ክፍል መሰብሰብ የከሰሉ ሙቀት፤ ሳቅና ጨዋታው ተጨምሮ ብርዱን እረስተነው አመሸን።
ቡናው አልቆ ሁሉም ወደ ክፍሉ ሲያመራ ግን አጂሬ ብርድ ተመልሶ ከተፍ አለ። እኔ ብልጥዋ አንድ መአት ከሰል ማንደጃው ላይ ጨምሬ ጎትቼ መኝታቤቴ አስገባሁት። ማንደጃውን ከጎኔ አስቀምጬ ትንሽ እሳት ከሞኩ በሗላ እንቅልፍ ድብን አርጎ ወሰደኝ።

ስነቃ ቤተሰብ ከቦኝ፣ ግማሹ ሲያለቅስ ግማሹ ደግሞ ውሃ ሲረጨኝ፣ ሌላው ወተት አግቷት ጢሱ ከውስጧ ካልወጣ ሰው አትሆንም ሲል፤ እኔ ደግሞ እውነት የተከሰተ ነገር ይሁን በህልም የተከሰተ መለየት አቅቶኝ ተፋጠጥን።
ቁም ነገሩ ያን ለት ሞትን አመለጥኩት። ወይም ደግሞ የተጠራሁበት ቀን አልነበረም ተመልሼ ከነዋሪዎች ተቀላቀልኩ። ያን ቀን ትልቅ ትምህርት ተማርኩ። የጭስ መውጫን ጥቅም እና መውጫ ያጣ ጥስ ሊገል እንደሚችል።
ሰሞኑን የተማርኩት ታላቅ ነገርም ከዚህ ቀን ትምህርቴ በምንም አይለኝም። በህይወታችን ውስጥ ያሉ አላስፈላጊ ነገሮች ሁሉ እንደ ጢሱ መውጫ እንደሚያስፈልጋቸው ተረዳሁ።
ተፈጥሮ ለብዙው አላስፈላጊ ነገር መውጫ የሰጠችን ቢሆንም እኛ መርጠኝ መውጫ የከለከልናቸው፤ (እኔው በገዛጄ መውጫ አሳጥቼ ሊገለኝ አስቦ እንደነበረው ጢስ) በየቀኑ የሚገሉን ብዙ ነገሮች ተሸክመናል።

ምግብ አስፈላጊነቱን ሲጨርስ ከሰውነታችን እንዲላቀቅ ተፈጥሮ መውጫ አዘጋጂቶለታል። ውሐም በዚሁ መልክ የተለገሰው መውጫ አለው። ብዙዎች ነዳጂ የሚያቃጥሉ ነገሮች በሙሉ ጥስ መውጫ አላቸው። ለምሳሌ መኪና፣ አይሮፕላን፣ ባቡር እያልን ልንደረድራቸው እንችላለን።
የሚያሳዝነው ግን ለብዙ ህመሞች ቀስቃሽ ለሆነው ነገር መውጫ አለመስጠታችን ነው። ብዙዎቻችን መርጠንም ይሁን ወይም እንደኔ ከሰል ሳናስበው አዘናግቶ ወደ ውስጣችን ለገባው ጥላቻ መውጫ አጥተንለታል።

በቅርብ ያነበብኩት አንድ የሳይንስ ምርምር፤ አንድ ሰው ከውስጡ ሰላም ባጣ ቁጥር ወይም እራሱን ወደ ጥላቻ፣ በቀል እና ቅያሜ በመራ ቁጥር የደሙን ባላነሰ ይቀይረዋል ይላል። ቀስ በቀስ በጥላቻ መመረዝ ሌላውን ከሚጎዳው የላቀ እኛኑ ያዳክመናል።
ታዲያ እንዲህ ላለው ከባድ ነገር መውጫ እንዴት አጣንለት? ለጥላቻስ እራሳችንን እንዴት አሳልፈን ሰጠን? በቀልና ቅያሜስ በውስጣችን ያለ ከልካይና ያለ መውጫ እንዲዘዋወሩ እና መልሰው እኛኑ እንዲያጠቁን ለምን ፈቀድንላቸው?
ጭስ መውጫ፣ ነገር መውጫ ወይም የሰላም በር ልንለው የምንችለው እራሳችንን ከአላስፈላጊ እና አስጨናቂ ከዚያም አደገኛ ነገር የምናላቅቅበት የፍቅር በር ለሁላችንም አስፈላጊ ነው። እንዴት እና ወዴት እንደምናገኘው ለያንዳንዳችን የተለያየ መንገድ ቢኖረውም! መውጫ መሻቱ ግን ለሁላችንም መጀመሪያ ስራችን ብናደርገው መልካም ነው እላለሁ።

እመቤት መንግስቴ
#ዝምከምልብዬ #አብረን

09/20/2022

።።። ከአንባቢያን የተሰጡ አስተያየቶች።።።

አብረን
ደራሲ እመቤት መንግስቴ

የልብ-ወለድ መጻሕፍት ማንበብ ካቆምሁ ብዙ ጊዜ ሆኖኝ ነበር:: ከብዙ ዓመታት ወዲህ የሚስበኝ ግለ ታሪኮችና የዕውነተኛ ኹነቶች ዘገባ ቢሆንም፣ ይኽ የእመቤት መንግስቴ አብረን የተሰኘ ልብ-ወለድ መጽሐፍ ግን ስሜቴን ሊስብና አእምሮዬን ሊሰቅዝ ቻለ:: የ 8 ምናባዊ ሴት ጓደኛሞች ታሪክ ነው:: የተዋወቁት ኢትዮጵያ ውስጥ ገና ተማሪ ልጆች ሆነው ነው:: የገጸ ባህርያቱ ተክለ ሰውነት አሳሳል የተዋጣለት ነው::
የእመቤት የባህርያት አቀራረጽ ሥልት፣ በባለ ታሪኮቹ ላይ እውነተኛ የሚመስል ሕይወትና ነፍስ ይዘራባቸዋል:: አንባቢ በምናብ ያያቸዋል::

ደራሲ እመቤት በገጸ-ባህርያቱ አማካይነት በዕውን ዓለም የሚኖሩ ጓደኛሞች ከልብ እንዲረዳዱና ለችግሮቻቸው መፍትሔ እንዲፈልጉ መልዕክት ታስተላልፋለች:: የተዋጣላትም ይመስለኛል:: የሥነ-ጽሑፍ ጥበብ የሕይወት ለዋጭነቱና የሚመሰገን የአጻጻፍ ዘይቤም በመጽሐፉ አተራረክ ውስጥ ይታያል::

ዶ/ር ፈቃዱ ፉላስ (ፒ.ኤች.ዲ.)
ሲልቨር ስፕሪንግ፣ ሜሪላንድ፣ ዪ.ኤስ.ኤ.

።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

አብረን
ደራሲ እመቤት መንግስቴ

ይህ መፅሀፍ በግልፅነት ላይ ተመስርተን በችግሮቻችን ላይ በጋራ ብንዘምት በተለይ በብቸኝነት እሚጨምቀን ን ችግር ለማቃለል ያግዘናል ።

ደግ ሰዎች ሞተውም እንደሚያኖሩን ሁሉ ይገለፅልናል ።

እሙዬ ድንቅ በረከት ነው ። ለደጓ ሰዊ እኔም ዋንጫዬን አንስቻለሁ ።

በራሱ ላይ መንቃት እሚሻ ይዝመትበት !

ደራሲ ስንዱ አበበ

።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

የእመቤት መንግሥቴ የአብረን መጽሐፍ

አነቃቂ – ሥራ ፈጣሪ – የዓለም ዓቀፋዊ ሰላምና አብሮነት አቀንቃኝ – ሴቶች መሪ እንዲሆኑ ሞጋች ሆኖ አግኝቼዋለሁ።

ኑሮዋችንን እንዲያቀላጥፍ የተዳበልነው ቴክኖሎጂ ልብ ካላልነው ልንገታ የማንችለው አጉል ሱስና እኛኑ መልሶ የሚዋጋ የጦር መሥሪያ መሆን ይችላል:: የእመቤት መንግሥቴ የእብረን መጽሐፍ የሕይወታችንን ቃናና ስብዓዊ አብሮነታችንን ነቅተን እንድናጠናክር አንቂ ደውላችን ነው::

ይህችን ሙገሳ ከመጻፌ በፊት የእመቤት መንግሥቴን የአብረን መጽሐፍ አምብቤ የመጽሐፉን መልዕክት ተግባራዊ ማድረግ ፈለግሁ:: አወንታዊ ለውጥ በዘላቂ የእስተሳሰብና የባሕሪ ለውጥ (habit formation) ይረጋገጣል::አልፎ አልፎ የምናደርገው የሞቅታ የአስተሳስብና የባሕሪ ለውጥ ጠቃሚነቱ ወደ ዘላቂነት ሲሸጋገር ብቻ ነው::

ታዲያ መጵሐፉ የሚጠቁማቸውን የአስተሳሰብና የባሕሪይ ለውጦችን ማጤን ጀመርኩ:: መለወጥ የምችለው እኔን ስለሆነ የኔን አስተሳሰብና ባሕሪ ማሰላሰልና መገምግም ላይ እገኛለሁ::

እኔን እንደገባኝ የአብሮነት መልዕክት በሚከተሉት ተግባራት ይገለጻል:: የሚቀርቡንን ሰዎች በውስጣዊ ጆርዋችን ማዳመጥ:: በውይይታችን ወቅት ግንዛቤያችንን የሚጨምሩ ጥያቄዎችን መጠየቅ:: ለጥያቄ መልስ ከመስጠታችን በፊት ጥያቄውን መረዳት:: ከእለታዊ የሩጫ ሕይወት መካከል ሰከን ያለ ጊዜን መፍጠር:: ስንገናኝ ውይይታችን ከወቅታዊ ጉዳዩች ይልቅ ለበለጠ የእርስ በርስ ትውውቅ ጊዜ መስጠት:: ከሚቀርቡን ሰዎች ጋር ስንጨዋወት በሚያስማሙን ነገሮች ላይ ማተኮርና የመሳሰሉት ናቸው:::

መጽሐፉ ተለቅ ተለቅ ያሉና የሚያስማሙን ምልከታዎችንና ትርጉሞችን ይጠቁማል:: ከነዚህ ተለቅ ያሉ መልዕክቶች አንዳንዶቹ የሚከተሉት ናቸው:: አብረን ይሻለናል:: አንዳችን ለሌላችን መድሃኒት ነን:: አንዳችን ስንወድቅ ሌላው ያነሳናል:: መደማመጥ ግንዛቤን ያመጣል:: አብሮነት እንድ መሆን ማለት አይደለም:: አብሮነት አንዳችን የሌላውን ብሶት ሳንፈርድ ማዳመጥና ነገሮችን በተናጋሪው ዓይን ማየት ነው::

የመጽሐፉን የአብሮነት ሚስጥረ መልዕክቶች እያንዳንዱ አንባቢ በተረዳውና በመረጠው መንገድ ተግባራዊ ማድርግ ይገባዋል በሚል እምንት እኔም የሚከተሉትን ባሕሪያት አጉልቼ እንድለማመድ አነሳስቶኛል:::

ለማጠቃለል የእመቤት መንግሥቴ የእብረን መጽሐፍ በመተጋገዝ በመደማመጥ በመቀራረብና በመተሳሰብ ሕይወትን በአብሮነት እንዳጣጥም አነቃቅቶኛል::

ዶ/ር ጌብ ሐምዳ (ፒ ኤቺ ዲ)
ደራሲ

።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

አብረን
ደራሲ እመቤት መንግስቴ

በተለየ መንገድ ማድረግ የምንችላቸው ብዙ ነገሮች አሉ ፤ ነገር ግን ወደ ኋላ ተመልሰን የማንለውጣቸው ግን ደግሞ ተምረንባቸው እኛነታችንን የሚሰሩ ነገ'ችንን ቆም ብለን እንድናስብ የሚያደርጉ ይሆናሉ፡፡

ደራሲና ገጣሚ እመቤት መንግስቴ አብረን በተሰኘወው አዲስ መጽሐፏ ይህን ሃሳብ ለነፍሳችን በቀረቡ ስምንቱ ሴቶች ውስጥ እንድናየው ፈልጋለች፡፡ ‘አትሄጂም’ እና ‘ዝም ከምል ብዬ’ በሚሉት መጽሐፎቿ ውስጥ ሴትነትን በተለየ መነጽር እንድናየው አግዛን ነበር፡፡

በአብረን መጽሀፏ ውስጥ ግን በሽንፈት ውስጥ ጥንካሬ ፤ ባለማስተዋል ውስጥ ጥበብን፤ በጠፋ ማንነት ውስጥ ሰው የመሆን ሚስጥርን ከሴትነት ጀርባ እንድንፈልግ ጋብዛናለች፡፡ ስምንቱ ሴቶች በጓደኝነት ብቻ የሚታሰር ማንነት እንደሌለ በእያንዳንዱ ምዕራፍ ውስጥ ይነግሩናል፡፡ ጓደኝነት ይገዝፍና የምንናፍቀውን ሰውነትን…ሰው የመሆን ሚስጥርን ይገልጽልናል፡፡

በዚህ እህል በተውደደበት ሰው በረከሰበት ዓለም ሰው ሰው የሚሸት ህይወት እንዲኖረን ፤ ከምንም በላይ ሴቶች የተሰራንበትን ማንነት እንድንፈትሽ፤ ፈተናችንና ውጣ ውረዳችንን በልባችን ይዘን አንዳችን በአንዳችን ውስጥ መኖር እንድንችል በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ሌላ ዕድል እንደተሰጠን አድርጌ እቆጥረዋለሁ፡፡ መልካም ንባብ!

ትዕግስት ካሳ
ጋዜጠኛ፣ የኮሙዩኒኬሽንና የአድቮኬሲ ባለሙያ

።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

አብረን
ደራሲ እመቤት መንግስቴ

የእመቤት መንግሥቴ ፅሁፎች ከሰው ልጅ ሕይወት ጋር ቅርብ ናቸው። በየአንዳዳችን ኑሮ ውስጥ በየዕለቱ የሚያጋትጥሙንና፣ ግን ደግሞ ልብ ብለን ሳናጤን የምናልፋቸው እውነታዎች ናቸው። የምትስላቸው ገፅ ባህርያት ሃሳባቸውና ቁመናቸው እንደምናውቃቸው ሰዎች ሥጋ ተላብሰው እንዲንቀሳቀሱ በማድረግ ከጅምሩ እስከመጨረሻው እንድንከተላቸው ታደርጋለች ።
"በአብሮነት" ድርሳን ውስጥ የምናያቸው ጓደኛሞች የእርስ በእርስ ፍቅር፣ አለሁልሽ የማለት መቆርቆር ፣ በየግል ያላቸው የባህሪ ልዩነት እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ለማህበራዊ መደጋገፍ ሊኖራቸው ስለሚገባ እሳቤ ጉልህ የአኗኗር መርሆዎችን በተገቢው ልኬት እያነሳች ለማንኛችንም የሚበጁ የሞራል እሴቶችን አበክራ ታስተላልፋለች። ቆም ብለንም ገፀባህርያቱን እራሳችን ውስጥ በመፈለግ ጥንካሬያችንን እና ድክመታችንን እንድንመረምር ትጋብዘናለች። ለተዋከበ ኑሮ የሚደረግ ሩጫንና ለጋራ መተሳሰብ ሊኖር የሚጋባውን ሚዛናዊ የተረጋጋ የሕይወት ጉዞ በረቀቀ መንገድ አስታርቃ የአብሮነትን ዋጋ ታጎላዋለች። ፅሁፎቿን ላነብ በመቻሌ ክብር ይሰማኛል።

ሰሎሞን ገብሬ
ገጣሚ

--
" ገዥው ስሜት ፍቅር ብቻ ነው "
" Love Is All There Is "

።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

አብረን
ደራሲ እመቤት መንግስቴ

በአብረን የተሰኘው መጸሐፍ እመቤት መንግስቴ የምታካፍለን በልጅነት ዘመን ከሚያጋጥሙን እና ምልክት ትተው የሚያልፉ እውነታዎችን ነው።

የሰነ ጽሁፍ ችሎታዋን የምታደምቅባቸው ገፅ ባሕርያት ማለትም ሴቶች፣ አብሮ አደጎች እንዲሁም በለጋ እድሜያቸው ውጭ ሃገር ኑሮ የመሰረቱ ሲሆኑ፤ በእለት ኑሮዋቸው ከትውልድ ሃገር ጋር ያላቸወን ትስስር ዘጋቢ በሆነ ውይይትና የአእምሮ ጥያቄ ምልልስ በማቅረብ አንባቢውን የገጠመኞቹ ተካፋይ እንዲሆኑ ትጋብዛለች።

ከአዲስ በሐል እና ኑሮ ጋር ስንጋጭ የሚገጥሙንን የኑሮ ግብግብ በተለይ ብቸኝነትን እና የአእምሮ መታወክን ደራሲዋ በዚህ ጽሁፍ ውስጥ በደንብ ታሳየዋለች።

መልካም ንባብ

ቪነስ ኢሽዋረን
የኮምዩኒኬሽንና ትርጉም ባለሙያ

09/12/2022

Saturday, September 17 at 5:00pm EAT with Martha H. Kidane, Emebet Mengiste. ከእመቤት ጋር የአዲሱን ሥራዋን ምክንያት አድርገን ስለ መጽሐፏ ለመወያየት ተመልሰናል።

Address

4325 Firs Avenue Suite # 3083
Tucker, GA
30084

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ABREN MEDIA & Entertainment posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ABREN MEDIA & Entertainment:

Share