Founding Vision/የአመሠራረት ራዕይ
የእግዚአብሔር ፍጹም ሙላት አመሰራረት:-ቤተክርስቲያኒቷ ለእግዚአብሔር ሰዎቸ ለፓስተር ብርሃን ጫነና ለፓስተር መርሲ መሰፍን በተሰጣቸው ራዕይ መሠረት በመኖሪያ ቤታቸው የተጀመረ ሲሆን፣ ዓላማና አፈጻጸሙ አብረዋቸው በእግዚአብሔር ፈቃድ ከሚሰሩ ፓስተሮችና አብሮ ሠራተኞች ጋር ነው::
የቤ/ክንዋም ዋናው ሥራም በኤፌሶን 3፡19 መሠረት ትውልድን ወደ እግዚአብሔር ፍጹም ሙላት ማምጣት ነው:: ይህንንም ለማድረግ በማስተማር፣ በመገሰጽ በመጸለይና አስፈላጊውን ግብዓት ሁሉ በመጠቀም ወደ እግዚአብሔር ፍጹም ሙላት
ውስጥ ማስገባት ነው::
ይህንን ሥራ ለመሥራት ግን እግዚአብሔር ምንም እንኳል በባሪያ
ው ፓስተር ብርሃን ጫነ በኩል ይጀምር እንጂ፣ በራሱና በጥቂት ተባባሪ አብሮ ሠራተኞች ብቻ ከግብ ሊደርስ ስለማይችል ብዙዎችን እግዚአብሔር በራሱ አሠራርና አደራረስ የዚህ ራዕይ ባለቤትና ሥራ አስፈጻሚዎች እያደረገ ይቀጥላል፡፡
የፍጥረት አለም አሰራር አስገራሚና ድንቅ የሆነውና ውጤቱም እስከዛሬ ያልጠፋው እግዚአብሔር አብ፣ ወልድና መንፈስ ቅዱስ አብረው ስለሠሩት ነው፡፡ (ዘፍ1፡26)
እግዚአብሔር በሕብረት ከሠራ ሰው ደግሞ ይህንኑ አርአያ በመከተል ለአንድ ዓላማ ተባብሮና ሕብረት ፈጥሮ ቢሠራ ውጤቱ እርሰ በርስ አፈቃቅሮና አደጋግፎ ከማኖሩም በላይ የእግዚአብሔር መንግስት የበለጠ ማስፋት እንደሚስችል ሳይታለም የተፈታ እውነታ ነው፡፡ (ዘፍ.2፡18)፣ (መክ. 4፡9-10)
Alerts
Be the first to know and let us send you an email when Fullness of God International Church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.