Hagere Infotainment

Hagere Infotainment Time is everything | ጊዜ ሁሉም ነገር ይህ የቁምነገርና የመረጃ መለዋወጫ መማማሪያ ገጽ ነው ። ማንኛውንም አስተያየት ወይም ሀሳብ በጨዋነት መግለጽ የሀገራችን ሰው ባህል ነውና ካልተገባ ንግግር እንቆጠብ፣

ዝክረ ጥላሁን ገሠሠ !
09/27/2025

ዝክረ ጥላሁን ገሠሠ !

የሐበሻው የሙዚቃ ንጉሥ ጥላሁን ገሠሠ ክፍል 1ጥላሁን ያለፈበትን ጊዜ አስመልክቶ በአድማስ ሬድዮ ከዓመታት በፊት የተላለፈ ዝግጅት ነው።Tilahun Gessesse, Tilahun Gessesse songs, Tilahun Gessesse music, Tilahu...

የሐበሻው የሙዚቃው ንጉሥ !የዚህ ሰው ነገር ይገርማል! አስገራሚነቱ ከውልደቱ ይጀምራል። የተወለደው በዕለተ መስቀል መስከረም 17 ቀን 1933 ዓ.ም ነው። ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው ደግሞ ...
09/26/2025

የሐበሻው የሙዚቃው ንጉሥ !

የዚህ ሰው ነገር ይገርማል! አስገራሚነቱ ከውልደቱ ይጀምራል። የተወለደው በዕለተ መስቀል መስከረም 17 ቀን 1933 ዓ.ም ነው። ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው ደግሞ የፋሲካ በዓል ዕለት ሚያዝያ 11 ቀን 2001 ዓ.ም ነው። የዚያን ዓመት የፋሲካ በዓል በሀዘን ድባብ የተዋጠ እንዲሆን አድርጎታል። በዘፈኑ ደግሞ በዓላትን ሲያደምቅ ኖሯል። በሕያው ሥራው የወደፊት በዓላትንም ያደምቃል። ይህ ሰው የሙዚቃው ንጉሥ የክብር ዶክተር አርቲስት ጥላሁን ገሠሠ ነው።

ከጋዜጠኛ ታደሠ ሙሉነህ ጋር በ70 ዎቹ ያደረገውን ቃለምልልስ ያዳምጡ https://youtu.be/GkJQ2E6uqWc

(ከመስከረም 17 ቀን 1933 ዓ.ም - ሚያዚያ 11 ቀን 2001 ዓ.ም) ከዚህ ዓለም ከተለየ 16 ዓመታት ሆኑ በህይወት ቢኖር መስከረም 17 ቀን 85 ዓመት ይሆነው ነበር።

ለክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን አደረሳችሁ !FELEG ETHIOPIAFELEG ETHIOPIA
09/26/2025

ለክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን አደረሳችሁ !

FELEG ETHIOPIAFELEG ETHIOPIA

09/26/2025

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ እንዲሁም ለደመራ ክብረ በዓል በሠላም አደረሳችሁ !!

የመጀመሪያው የጠፈር ጉዞና ያልተነገሩ ክስተቶች "ይኸው ከዓለም ርቄ ትንሽዬ ኩባያ መሳይ ዕቃ ውስጥ እገኛለሁ። መሬት ሰማያዊ ናት። ምንም ማድረግ አልችልም።" ይህ መስመር የተወሰደው ከድምፃዊ...
09/14/2025

የመጀመሪያው የጠፈር ጉዞና ያልተነገሩ ክስተቶች

"ይኸው ከዓለም ርቄ ትንሽዬ ኩባያ መሳይ ዕቃ ውስጥ እገኛለሁ። መሬት ሰማያዊ ናት። ምንም ማድረግ አልችልም።" ይህ መስመር የተወሰደው ከድምፃዊ ዴቪድ ቦዊ ዘፈን ነው። ድምፃዊው ዩሪ ጋጋሪን ወደ ጨረቃ በተጓዘ ወቅት የተሰማው ይህ ሳይሆን አይቀርም ሲል ነው የገጠመው።

ጋጋሪን ወደ ሕዋ የተጓዘው ሁለት ሜትር ስፋት ባላት መንኮራኩር ነው። የተጓዘው እንደ ጠፈር ተመራማሪ ሳይሆን እንደ መንገደኛ ነበር። በወቅቱ መንኮራኩሯ ውስጥ ያሉ ቁልፎችን መነካካት ክልክል ነበር።

ያኔ ጋጋሪን ምድር ላይ ካሉ ተቆጣጣሪዎች ጋር ያደረገው ንግግር ተተይቦ ተቀምጧል። ጽሑፉ ጋጋሪን ባየው ነገር ቀልቡ እንደተሰረቀ ያትታል። ጋጋሪን በፈረንጆቹ ሚያዚያ 12፣1961 ያደረገው ጉዞ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ለሶቪዬት ሕብረት ትልቅ ድል ነበር።

ነገር ግን ታሪክ ለመፃፍ ቆርጦ የተነሳው ጋጋሪን ትልቅ ብርታት የሚጠይቅ ሥራ ሠራ። ጋጋሪን ጥልቅ ወደሆነው ሚስጢራዊው ሕዋ ያለማንም እርዳታ ተጓዘ። ጠፈርተኛው ወደ ሕዋ ያደረገው ጉዞ ብዙ ጥያቄዎችን ለመመለስ ያቀደ ነበር። አንደኛው ጥያቄ ሰው ሕዋ ላይ መቆየት ይችላል ወይ የሚለው ነበር።

ሌላኛው ዓላማ መንኩራኩሯ ሕዋ ላይ ምን ያህል መቆየት ትችላለች የሚለውን መፍታት ነው። የዛኔ መንኮራኩሮች ምን ያህል ደህንነታቸው የተጠበቀ ነው? ከምድር ጋር ግንኙነት ማድረግ ይቻላል? የምር ሰዎች ሕዋ ላይ መቆየት ይችላሉን? የሚሉት ጥያቄዎች ምላሽ አልነበራቸውም።

"ያኔ ጋጋሪን የተወነጨፋባትን መንኮራኩር ለዘንድሮ ሳይንቲስቶች ብናቀርብ ማንም ሰው በዚህች ተስፋ በሌላት መንኮራኩር ለመብረር አይደፍርም" ይላሉ ኢንጅነር ቦሪስ ቼርቶክ። "በወቅቱ ሁሉም ነገር ሰላም ነው ብዬ ብዙ ሰነዶች ላይ ፈርሚያለሁ። ጉዞው ሊሳካ ይችላል ብዬም ማስረገጫ ሰጥቻለሁ። አሁን ዞር ብዬ ሳየው ብዙ አደጋ እንደተጋፈጥን ይሰማኛል።"

ቮስቶክ የተሰኘው መንኮራኩር አስተኳሽ መሣሪያ አር-7 በተባለው ሮኬት ላይ ተመሥርቶ የተሠራ ነው። ሮኬቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የተተኮሰው በፈረንጆቹ 1957 ነበር። በዛው ዓመት የመጀመሪያው ሰው ሰራሽ ሳተላይት ስፑትኒክ 1 አር-7 ላይ ተመስርቶ ተተኩሶ ነበር።

አር-7 አሁንም ሩስያ ወደ ጠፈር ሳይንቲስቶችን ለመላክ የምትጠቀምበት ሮኬት ነው። የመጀመሪያው የቮስቶክ ፕሮግራም የተወነጨፈው ግንቦት 1960 ነበር። ይህ ደግሞ ከጋጋሪን ጉዞ አንድ ዓመት ቀደም ብሎ የተካሄደ ነው።

ለመጀመጀሪያ ጊዜ በቮስቶክ አማካይነት የተተኮሰችው ሳተላይት ከምድር ውጭ መውጣት ብትችልም ባጋጠማት ችግር ምክንያት አልተመለሰችም። ይህ በ1960ዎቹ ከተካሄዱ ሙራዎች ብቸኛው ስኬታማ ጉዞ ነበር። ታኅሣሥ 1 ደግሞ ሌላ ሙከራ ተደረገ። አሁንም ተጓዦቹ ውሾች ነበሩ። ሙሽካ እና ፕቼልካ።

ነገር ግን ይህ ጉዞ ስኬታማ አልነበረም። ውሾቹን የጫነችው ሳተላይት ስትመለስ ከታቀደላት ቦታ ውጭ በመሄዷ ምክንያት አየር ላይ እያለች ከነውሾቹ እንድትደመሰስ ተደረገ።ሶቪዬት ሕብረት ይቺን ሳተላይት ከጥቅም ውጭ ያደረገችው ቴክኖሎጂዋ ለሌላ አገር ተላልፎ እንዳይሰጥ በመስጋት ነበር።

ጋጋሪን ሚያዝያ 12፣1961 ወደ ሕዋ ሲመጥቅ ጉዞው ከሞላ ጎደል ስኬታማ ነበር።

በወቅቱ አጋጥመው ከነበሩ ችግሮች መካከል አንዱ መንኮራኩሯ ከታሰበላት ከፍታ [አልቲትዩድ] በላይ መውጣቷ ነው። መንኮራኩሯ 'ፍሬን' ባይኖራት ኖሮ ጋጋሪን ማድረግ የሚችለው ሳተላይቷ በራሷ ጊዜ ወደ ምድር እንድትወርድ መጠበቅ ብቻ ነው።

ምንም እንኳ ጋጋሪን ከሳምንት በላይ ለሚሆን ጊዜ ምግብና መጠጥ ይዞ ቢሄድም መንኮራኩሯ ከፍታዋን ጥላ ብትሄድ ኖሮ ወደ ታች የምትወርደው በራሷ ጊዜ ስለሆነ ምግብና መጠጡ ላይበቃው ይችል ነበር። ሌላኛው ሳተላይቷ የገጠማት ችግር ውስጥ የነበረው ሙቀት መጠን እጅግ መጨመር ነው። ጋጋሪን ወደ ምድር ሲመለስ በጣም ይወዛወዝ ስለነበር ራሱን ሊስት ይችል ነበር።

ጋጋሪን ወደ ምድር ሲመለስ መንኮራኩሯ ከምድር ጋር ተላትማ ከመፈራረሷ በፊት በፓራሹት ወርዶ ነው የተረፈው። አንድ የሕዋ ጉዞ ስኬታማ ነው የሚባለው ጠፈርተኛው መንኮራኩሯ ውስጥ ሆኖ ምድር ላይ ማረፍ ሲችል ነው።

ይህንን ተከትሎ ባለሥልጣናት ጋጋሪን የመጨረሻዎቹን ኪሎ ሜትሮች ከመንኩራኩሯ ጋር አልተጓዘም በሚል ጉዞው ስኬታማ አልነበረም ብለው ነበር። ኋላ ላይ ግን በትክክል ተወንጭፎ ምድርን ዞሮ ከነጠፈርተኛው በመመለሱ የጋጋሪን ጉዞ ስኬታማ ተብሎ እንዲመዘገብ ተደረገ።

ቢቢሲ ሩስኪ፤ ለበርካታ ሩስያዊያን ሳይንቲስቶች ጋጋሪን በተጓዘባት መንኮራኩር ዘንድሮ ትጓዛላችሁ ወይ? ብሎ ላቀረበው ጥያቄ፤ ብዙዎቹ ጋጋሪን ያኔ የተጓዘው ስለተጋረጠበት አደጋ ብዙም ስላላወቁ ነው ሲሉ መልሰዋል። የገበሬ ልጅ የሆነው ጋጋሪን ወደ ጠፈር ሲመነጠቅ ማንም አያውቀውም ነበር። ሲመለስ ግን የምድራችን ታዋቂው ሰው ሆነ።

ጋጋሪን ወደ ምድር ከተመለሰ በኋላ የሶቪዬት ሕብረትን የሕዋ ፕሮግራም ለማስተዋወቅ ወደ ቼኮስሎቫኪያ፣ ቡልጌሪያ፣ ፊንላንድ፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ አይስላንድ፣ ኩባ፣ ብራዚል፣ ካናዳ፣ ሃንጋሪና ሕንድ ተጉዟል።

ጋጋሪን በድጋሚ ወደ ሕዋ ሊሄድ ዕቅድ ተይዞለት የነበረ ቢሆንም የአገር ጀግና በመሆኑ ምክንያት እንዳይበር ታግዷል። ነገር ግን በርካታ ጠፈርተኞችን አሰልጥኗል። ጋጋሪን 1968 ላይ በአውሮፕላን አደጋ ምክንያት በ34 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።(ቢቢሲ)

ቴሌግራም https://t.me/felegethiopia

የፀሐይና የጨረቃ መጨለም በኢትዮጵያ ሰነዶች🌞✍️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ🌓 የሥነ ፈለክ ተመራማሪዎች ሊቃውንት ስለ ግርዶሽ በመርሐ ዕውር፣ በአቡሻህር ይልቁኑ በትርጓሜ ሚጠተ ብርሃና...
09/06/2025

የፀሐይና የጨረቃ መጨለም በኢትዮጵያ ሰነዶች

🌞✍️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
🌓 የሥነ ፈለክ ተመራማሪዎች ሊቃውንት ስለ ግርዶሽ በመርሐ ዕውር፣ በአቡሻህር ይልቁኑ በትርጓሜ ሚጠተ ብርሃናት ዘሔኖክ ጋር ከመራቀቅ ባለፈ በኢትዮጵያ የተከሠቱ ግርዶሾችን የመመዝገብ ልምድ ነበራቸው።

🌒 ለምሳሌ ያህል ስመ መንግሥታቸው መሲሕ ሰገድ በተባሉት በዐጼ በካፋ ዘመነ መንግሥት ስለተደረገው ግርዶሽ በታሪከ ነገሥት የብራናው ጽሑፍ ላይ፡-

🌛 “ወበስድስቱ ዓመተ መንግሥቱ አመ ሰብዑ ለመስከረም በዕለተ ሰኑይ በጊዜ ሠለስቱ ሰዓት ፀልመ ፀሓይ ወተርእዩ ከዋክብት ወተሐውኩ ኲሉ ሰብእ ወተማሕለሉ ወኮነት ከመ ቀዳሚሃ ብርህት” (ዐጼ በካፋ በነገሠ በስድስተኛው ዓመት በመስከረም ሰባት በዕለተ ሰኞ ሦስት ሰዓት ላይ ፀሓይ ጨለመች ከዋክብት ታዩ ሰው ሁሉ ታወከ፤ ለመኑ፤ ፀሓይም እንደ ቀደመው በራች) በማለት የፀሓይ ግርዶች በተገለጠ ጊዜ በተከሰተው ክስተት የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደደነገጠ ጭምር አስፍረዋል፡፡

🌒 ከደርቡሽ ጋር በተደረገው ፍልሚያ በዐጼ ዮሐንስ ዕረፍት ጊዜ ግርዶሽ እንደነበረ ታሪከ ነገሥት ሲያስረዳ፡-

☄️ “አመ አሚሩ ለመጋቢት በዕለተ ቀዳሚት ሰንበት አሜሃ ኮነ ድልቅልቅ ሌሊተ ኮነ ቀትር ወጸልመ ፀሓይ ወኲሉ ዓለም ሠለስተ መዓልተ ወንጉሥ ዮሐንስ አዕረፈ ውስተ ሐይመቱ”
(መጋቢት 1 በቀዳሚት ሰንበት ዕለት ያን ጊዜ ንውጽውጽታ ሆነ በቀትር ጊዜ ፀሓይ በመላው ዓለም ጨልሞ እንደ ሌሊት ሆነ፤ ንጉሥ ዮሐንስም በድንኳኑ ውስጥ ዐረፈ) ይላል፡፡

🌞 ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ በባሕረ ሐሳብ መጽሐፋቸው ላይ በኢትዮጵያ በየዘመናቱ የተደረጉ ታሪኮችን ታሪከ ነገሥትንና በኢትዮጵያ ያሉ የነገሥታት ዜና መዋዕሎችን አመሳክረው በዳሰሰቡት ክፍል ላይ በኢትዮጵያ የተደረጉትን የፀሓይና የጨረቃ ግርዶሾችና የሥነ ፈለክ ክስተቶችን በእኛ በኢትዮጵያ አቈጣጠር እንዲህ አስፍረውታል፡-

🌖 ➢ በዐጼ ገላውዴዎስ (አጽናፍ ሰገድ ዘመነ መንግሥት) በ1545 ዓ.ም. ፀሓይ ጨለመች፡፡

🌑 ➢ በጻድቁ ዮሐንስ (አእላፍ ሰገድ) ዘመነ መንግሥት በ1661 ዓ.ም. ኅዳር 5 (ጥቅምት 28 የሚልም አለ) በ9 ሰዓት ላይ ፀሓይ ጨለመች፤ በዚህ ምክንያት ንጉሡ በዕለቱ ሞት ተፈርዶባቸው የነበሩት ወንጀሎቹ እንዳይነኩ አዘዘ፡፡፡ ➢ በጻድቁ ዮሐንስ (አእላፍ ሰገድ) ዘመነ መንግሥት በድጋሚ በ1672 መጋቢት 24 ፀሓይ ጨለመች፡፡

🌑☄️ ➢ በዐጼ ኢያሱ አድያም ሰገድ ዘመነ መንግሥት በ1682 ዓ.ም. ኅዳር 1 ጅራታማ ኮከብ ታየ፡፡

🌟 ➢ በዐጼ በካፋ (ዳግማዊ እስክንድር) ዘመነ መንግሥት ጊዜ በ1720 ዓ.ም. ፀሓይ ጨለመ፡፡

🌒☄️ በዐጼ ኢያሱ (ብርሃን ሰገድ) ዘመነ መንግሥት በ1735 ዓ.ም. ጅራታማ ኮከብ ታየ፡፡

⛅️ ➢ በዘመነ መሳፍንት ጊዜ በ1792 ዓ.ም. ተክለ ጊዮርጊስ ለስድስተኛ ጊዜ ከዙፋኑ ላይ በወጣበት ዓመት በ1792 ዓ.ም. በሚያዝያ ወር ጨረቃ ጨለመች፡፡

💥 ➢ በዐጼ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት ጊዜ በ1902 ዓ.ም. በሚያዝያ ወር ለጥቂት ቀናት ጅራታም ኮከብ ታየ በማለት አስቀምጠውታል፡፡

🌞 በዘመናችን ደግሞ የሠኔ 14/ 2012 ዓ.ም. የቀለበታማ የፀሐይ ግርዶሽ እንደተመዘገበ፤ የጳጉሜ 2/ 2017 ዓ.ም የሙሉ ጨረቃ መጨለም (የደም ጨለማ) በክብር ይመዘገባል። 🌒 መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ

FELEG ETHIOPIA

እጅጋየሁ ሽባባው(ጂጂ) እና እንግጫ ነቀላየእንግጫ ነቀላ በዓል ቀደም ባሉ ዓመታት በአብዛኛው የአማራ ክልል አካባቢዎች ሲከበር እንደነበር የማህበረሰብ ታሪክ አዋቂዎች ይናገራሉ፡፡ እንግጫ ነቀ...
09/06/2025

እጅጋየሁ ሽባባው(ጂጂ) እና እንግጫ ነቀላ

የእንግጫ ነቀላ በዓል ቀደም ባሉ ዓመታት በአብዛኛው የአማራ ክልል አካባቢዎች ሲከበር እንደነበር የማህበረሰብ ታሪክ አዋቂዎች ይናገራሉ፡፡ እንግጫ ነቀላ ልዩ በሆነ ዝማሬና ጭፈራ ደምቆ የሚከበር በዓል ቢሆንም፣ በበዓሉ ጊዜ የሚሰሙ ግጥምና ዜማዎችን በመጠቀም የተሰሩ ወጥ ባህላዊ ሙዚቃዎች ጥቂት ናቸው፡፡

ከ27 ዓመታት በፊት ግን ተወዳጇ ድምጻዊ እጅጋየሁ ሽባባው(ጂጂ) ሰለ እንገጫ ነቀላ በዓል ዘመን የማይሽረው ድንቅ ሙዚቃ ሰርታልናለች። በዚህም በዓሉ በትውልዱ እንዳይረሳና በዓለም ዙሪያ እንዲታወቅ የግሏን ከፍተኛ ሚና ተጫውታለች፡፡

አንተ የከንፈር ወዳጅ፣ በጊዜ ሳመኝ
ጤፍ አበጥራለሁ፣ የሰው ግዙ ነኝ
የሰው ግዙ ሁኖ፣ የሰው ግዙ መውደድ
እሳት በገለባ እፍ ብሎ ማንደድ።

እጅጋየሁ በተስረቅራቂ ድምጿ ልጃገረዶችን ሁና እንገጫ ነቅላ፣ በአደይ አበባ ጎንጉና ለአዲስ ዓመት ስጦታ ለወዳጇ ታበረክታለች፤ አዲሱን ዓመት በተስፋና ደስታ ስለመቀበልም ተሰምቶ በማይጠገብ ዜማ ትተርክልናች።

እንግጫ ጎንጉኘ፣ በአደይ በሶሪት
እንቁጣጣሽ ብየ፣ ቤቱ ላክሁለት
መስከረም ለምለሙ፣ መስከረም ለምለሙ
ብሩህ እንቁጣጣሽ፣ ደስታ ለዓለሙ።

ድምጻዊ፣ ባለቅኔ፣ ተዋናይት፣ የዜማና ግጥም ደራሲ የሆነችው እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ) የአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ባካሄደው 15ኛው የባህልና ኪነ-ጥበብ ፌስቲቫል፣ "ለባህልና ኪነ-ጥበብ እድገት" ለአበረከተችው የላቀ አስተዋጽኦ የሕይወት ዘመን የእውቅና ሽልማት የሰጣት ሲሆን፤ የእንጅባራ ዩኒቨርስቲ ደግሞ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጥቷታል።

እጅጋየሁ ሽባባው እናመሰግናለን!

FELEG ETHIOPIA

"ሂድን ፊገርስ (Hidden Figures)"የናሳ የጠፈር ምርምር ተቋም ባለደረባ እና የሂሳብ ሊቅ በነበረችው በጥቁር አሜሪካዊቷ ካትሪን ጆንሰን ህይወት ዙሪያ የተሰራ ፊልም።ሂድን ፊገርስ፦ የ...
08/26/2025

"ሂድን ፊገርስ (Hidden Figures)"

የናሳ የጠፈር ምርምር ተቋም ባለደረባ እና የሂሳብ ሊቅ በነበረችው በጥቁር አሜሪካዊቷ ካትሪን ጆንሰን ህይወት ዙሪያ የተሰራ ፊልም።

ሂድን ፊገርስ፦ የአሜሪካዊያን ህልም እውን እንዲሆን እና በጠፈር ውድድር እንዲያሸንፉ ያደረጉት ያልተነገረው የጥቁር ሴቶች እውነተኛ ታሪክ እአአ በ2016 ዓም በማርጎት ሊ ሼተርሊ የተጻፈ መጽሐፍ ሲሆን በፊልምም ተሰርቶ ብዙዎች ተመልክተውታል።

ከ54 ዓመታት በፊት እአአ በ1969 ዓም አፖሎ 11 የተባለች መንኮራኩር ወደ ህዋ ስትመጥቅና ኒል አርምስትሮንግ ለመጀመሪያ ጊዜ ጨረቃ ላይ ሲያርፍ ከዚህ ስኬት ጀርባ የአንዲት ጥቁር አሜሪካዊት ሴት ሚና እጅግ በጣም ከፍተኛ ነበር።

ይች ሴት ካትሪን ጆንሰን ትባላለች። ካትሪን የሂሳብ ሊቅ ስትሆን በአሜሪካዉ የጠፈር ምርምር ማዕከል ናሳ ለበርካታ ዓመታት አገልግላለች።

በ101 ዓመቷ እአአ የካቲት 24 ቀን 2020 ዓም ከዚህ ዓለም በሞት የተለየችው የሂሳብ ሊቅ በአሁኑ ወቅት በልዩ ኮምፒዩተር የሚከናወነውን ዉስብስብ የሂሳብ ስሌት በጭንቅላቷና የዚያን ዘመኑን የስሌት መርጃ ወይም «ስላይድ ሩል» ተጠቅማ የናሳን የሮኬት የጉዞ አቅጣጫ ያሰላች ሊቅ ነበረች።

በእሷ የሂሳብ ስሌት የአሜሪካ የሕዋ ምርምር ኤጀንሲ ናሳ ጨረቃ ላይ ጠፈረተኞችን አሳርፎ ማምጣት የቻለ ሲሆን በ1961 ዓም አሜሪካ በአለን ሼፓርድ አማካኝነት ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ሕዋ ላደረገችው ጉዞ የሮኬቱን የሒሳብ ስሌት ያዘጋጀችው ካትሪን ነበረች። በቀጣዩ ዓመት በ1962 ዓም ጆን ግሌይ ለተባለዉ አሜሪካዊ ጠፈርተኛ ተመሳሳይ ስራ ሰርታለች።

«ጆን ግሌይ የመጀመሪያዉ መሬትን የዞረ አሜሪካዊ ጠፈርተኛ ነዉ። እሱ ትክክለኛዉን ስሌት እንዲሰራለት ይፈልግ ስለነበር ያንን አደረኩለት። እናም የበረራዉን አቅጣጫ ስሌት ሰራሁለት።» ነበር ያለችዉ ካትሪን።

ሥራው ከፍተኛ ጥንቃቄን የሚጠይቅ ና ትንሽ ስህተት ቢፈጠር ለናሳ ጠፈርተኛ ቡድን ከባድ ኪሳራ ነበር። ነገር ግን ካትሪን በሚያስደንቅ ብቃት ጠፈርተኞቹ ጨረቃ ላይ ደርሰዉ በስኬት ወደ መሬት እንዲመለሱ በማድረግ ሙያዊ ሀላፊነቷንና ችሎታዋን አሳይታለች።

የአሜሪካው የህዋ ምርምር ማዕከል ናሳ ለጠፈር ፕሮግራሙ የሮኬቶቹን የጉዞ አቅጣጫና እንቅስቃሴ እንዲያሰሉለት በ1960ዎቹ በርካት የሂሳብ ሊቃዉንትን አሰማርቶ ነበር።

ቡድኑ የፃታና የዘር ስብጥር ያለበት ቢሆንም ፤በወቅቱ በአሜሪካ በነበረው የዘርና የፃታ መድልዎ የተነሳ ወንድ የሂሳብ ሊቆች ቡድን ከሴቶቹ ተለይተዉ የሚሰሩ ሲሆን ካትሪን ጆንሰን የነበረችበት ጥቁር ሴት የሂሳብ ሊሂቃን ቡድን ደግሞ ከነጭ ሴት የሂሳብ ሊቆች ጋር እንዳይገናኝ በተለያዩ ቦታዎች ተለይተው ነበር የሚሰሩት።

እነዚህ ሴት የሂሳብ ሊቃዉንት በእርሳስ፣ በእጅናና በስላይድ ሩል ተጠቅመው ያሰሉ ስለነበር በወቅቱ “ኮምፕዩተር” ተብለዉ የሚጠሩ ሲሆን ካትሪን ጆንሰን አንዷና ዋነኛዋ ነበረች። ካትሪን በአሜሪካ በዘመናዊ መልኩ የሴቶች ንቅናቄ ከመጀመሩ በፊት የናሳ የሂሳብ ሊቅ ሆነዉ ካገለገሉ በመቶዎች ከሚቆጠሩና ዕዉቅና ካላገኙ ሴቶች መካከል አንዷ ናት።

በአሜሪካዉ የጠፈር ምርምር ጣቢያ ናሳ ለ33 ዓመታት በበረራ ምርምር ክፍል የሰራች ቢሆንም ስራዋም ይሁን ስሟ በወጉ የሚታወቅ አልነበረም። ዉሎ አድሮ ግን፣ የእሷ እና ለናሳ ይሰሩ የነበሩ ሌሎች ጥቁር ሴት የሒሳብ ሊቃውንት አስተዋፅኦ መታወቅ ጀመረ።

እአአ 2015 ዓም ካትሪን በናሳ ላበረከተችዉ አስተዋፅኦ በቀድሞዉ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ፕሬዝዳንታዊ የነፃነት ሜዳሊያ ተሸልማለች። ባራክ ኦባማ በወቅቱ ባደረጉት ንግግርም ካትሪን በአሜሪካ የጠፈር ምርምር ስራ ለአዲሱ ትዉልድ ተምሳሌት ነች ብለዉ ነበር።

«ካትሪን በ33 ዓመታት የናሳ ቆይታዋ የዘር፣ የፃታና የቀለም መሰናክል ሁሉ በመስበር እያንዳንዱ ሰዉ ሂሳብንና ሳይንስን በማጥናት ወደ ኳክብት መድረስ እንደሚችል በማሳየት ለአዲሱ ለትዉልድ ፈር ቀዳጅ ሆናለች።»

ቆይቶም ይህ ያልተነገረ የሴቶች ታሪክ እእአ 2016 ዓም «ሂድን ፊገርስ» በሚል ርዕስ ሆሊዉድ ዉስጥ ፊልም የተሰራበት ሲሆን በዚሁ አመት በተመሳሳይ ርዕስ ሽተርሊ መፅሀፍ ተፅፎበታል።

በዚህ ፊልም ቶራ ጂፒ የተባለች ተዋናይት የሂሳብ ሊቋን ካትሪን ጆንሰንን ገጸ ባህሪ ወክላ የተጫወተች ሲሆን የፊልሙ ማዕከላዊ ጭብጥም በዚህችው የሂሳብ ሊቅ ላይ ያተኮረ ነበር።

ሂድን ፊገርስ ፊልም ላይ ዝነኛው የፊልም ሰው ኬቨን ኮስትነርን(Kevin Costner) ጨምሮ ብዙ ታዋቂ ተዋናዮች የተሳተፉበት ሲሆን እነሱም፦
• Taraji P. Henson
• Octavia Spencer
• Janelle Monáe
• Kirsten Dunst
• Jim Parsons
• Mahershala Ali
• Aldis Hodge
• Glen Powell

ሂድን ፊገርስ እአአ በ2017 ዓም በ3 ት ዘርፍ ለ89ኛው አካዳሚ (ኦስካር) ሽልማትን ጨምሮ በቢፍታ፣ በጎልደን ግሎብ እና በሌሎችም ብዙ ሽልማቶች በተለያዩ ዘርፎች ታጭቶ የነበረ ሲሆን በተንቀሳቃሽ ምስል ትግበራ የተዋንያን የአፈፃጸም ብቃት (Screen Actors Guild Award - Outstanding Performance) ተሸላሚ መሆን ችሏል። በሽልማቱ ወቅት ካትሪን ጆንሰን በ98 ዓመቷ ብቸኛዋ በህይወት ያለች የታሪኩ አካል በመሆን በሽልማት ስነስርዓቱ ላይ ተገኝታ ነበር።

ጥቁር አሜሪካዊቷ ካትሪን ኮልማን ጎብል ጆንሰን ነሀሴ 26 ቀን 1918 ዓም በምዕራብ ቨርጂኒያ ግዛት ዋይት ሰልፈር ስፕሪንግ በተባለቦታ የተወለደች ሲሆን አባቷ በግብርና ስራ እናቷ ደግሞ በመምህርነት ሙያ የተሰማሩ ነበሩ።

ለቤተሰቧ 4ኛ ልጅ ስትሆን በልጅነቷ በቁጥር መጫወት ትወድ ነበር። ካትሪን ትምህርት ቤት ገብታ ጂኦሜትሪና አልጀብራ እስክትማር አልጠበቀችም። ቤት ዉስጥ መደርደሪያ ላይ ያሉ ሳህኖችን፣ የሰማይ ክዋክብትን ፣የቤት መወጣጫ ደረጃዎችን በመቁጠር ነበር የልጅነት ጊዜዋን ያሳለፈችዉ።

ያም ሆኖ እሷና ቤተሰቦቿ ይኖሩበት የነበረዉ ከተማ በወቅቱ ለጥቁር ህፃናት የሚፈቀደዉ እስከ ስድስተኛ ክፍል ብቻ እንዲማሩ ስለነበር ቤተሰቦቿ ከተማዋን ለቀቀዉ እሷና ሶስት ታላላቆቿ ሊማሩ ወደ ሚችሉበት በ125 ማይል ርቀት ላይ ወደሚገኘዉ ምዕራብ ቨርጅኒያ የትምህርት ማዕከል ወሰዷቸዉ። ከዚህ የትምህርት ማዕከል ጋር ከተቀናጀ አንድ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትም ካትሪንና ታላላቆቿ ትምህርታቸዉን መከታተል ችለዋል።

ካትሪን በ10 ዓመቷ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቷን ያጠናቀቀች ሲሆን በ14 ዓመቷ ወደ የአሁኑ በምዕራብ ቨርጂኒያ ዩንቨርሲቲ የቀድሞዉ ምዕራብ ቨርጂኒያ ኮሌጅ ገብታ የሂሳብ ትምህርቷን ተከታትላለች። «ሁሌም በመስከረም ወደ ኮሌጁ እንሄዳለን። በሀምሌ ደግሞ ቤታችን እንመለሳለን። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርትና የኮሌጅ ትምህርት ለመከታተል በዚህ ሁኔታ ለስምንት ዓመታት እንመላለስ ነበር» በማለት ካትሪን በአንድ ወቅት ተናግራለች።

በወቅቱም የመጀመሪያ ዓመት ተማሪ እያለች በኮሌጁ ይሰጡ የነበሩ ሁሉንም የሂሳብ ትምህርቶች ተምራ ጨርሳለች። ያበመሆኑ አማካሪዋ በነበረዉና በ1940ዎቹ በሂሳብ የዶክትሬት ዲግሪያቸዉን ከያዙ ሶስት ጥቁር አሜሪካዉያን መካከል አንዱ በነበረዉ ዊልያም ዋልድሮን የተዘጋጀ የተለየ የሂሳብ ትምህርት በተጨማሪ ክፍለ ጊዜ ይሰጣት ነበር።

በ1937 ዓም በሂሳብና በፈረንሳይኛ ቋንቋ የመጀመሪያ ዲግሪዋን በመያዝ መምህር ሆና ተቀጠረች። በ1940 ዓም የበጋ ወቅት ከፍተኛ የሂሳብን ትምህርትን ለማጥናት ምዕራብ ቨርጂኒያ ዩንቨርሲቲ ተመልሳ የገባች ቢሆንም በወቅቱ ለእሷ ችሎታ የሚመጥን የትምህርት ዓይነት የማግኘት ፈተና ገጥሟት ነበር።

ከበጋዉ የትምህርት ወቅት በኋላም ነብሰጡር በመሆኗ ትምህርቱን ለማቋረጥ ተገዳለች። ከዚያም ከአስር ዓመታት በላይ ከባለቤቷ ከጀምስ ፍራንሲስ ጎብል ጋር ልጅ በማሳደግና በመምህርነት ሙያ የቆየች ሲሆን በ1952 ዓም ናሳ ጥቁር የሂሳብ ባለሙያ ሴቶችን እንደሚቀጥር በመስማቷ ወደዚያዉ አመራች።

ከዚያም በናሳ የፅህፈት ስራ ከሚሰሩና «ኮምፒዩተር» በመባል የሚታወቁትን አነስተኛ የጥቁር ሴት አሜሪካዉያን ቡድንን ተቀላቀለች። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በጡረታ እስከተገለለችበት እስከ 1986 ዓም ድረስ ጠፈርተኞችን ወደ ህዋ በመላክ ከ33 ዓመታት በላይ ናሳን ያገለገለች ሲሆን በ101 ዓመቷ በ101 ዓመቷ እአአ የካቲት 24 ቀን 2020 ዓም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች።

ዕውቀት ዘርም ሀይማኖትም ሀገርም የለውም፣ ምንም ይሁን ብቻ ለትውልድ የሚጠቅም ነገር ሰርቶ ማለፍ ሁሌም ስምህን ሲያስጠራ ይኖራል !

ክብር ለጀግኖች ይሁን !

FELEG ETHIOPIA Hagere Infotainment

ዓባይ በጂጂ ዜማ እነሆ የዓባይ ቁጭት ወደ ፈንጠዝያ ሊቀየር ጥቂት ቀናት ቀርተውታል። ከተጓጓለት ብስራት አስቀድሞ ቁጭትን ወስውሰው፤ የተዳፈነውን ረመጥ ቀስቅሰው እጆቻችንን ለሥራ ያበረቱ በር...
08/25/2025

ዓባይ በጂጂ ዜማ

እነሆ የዓባይ ቁጭት ወደ ፈንጠዝያ ሊቀየር ጥቂት ቀናት ቀርተውታል።

ከተጓጓለት ብስራት አስቀድሞ ቁጭትን ወስውሰው፤ የተዳፈነውን ረመጥ ቀስቅሰው እጆቻችንን ለሥራ ያበረቱ በርካቶች ናቸው።

ሀ ሳይባል ሁ ብለው አንድ ሳይባል ተሻግረው ሩጫውን ጀምረው ያስጀመሩ፤ በዜማቸው የቆሙትን ያንደረደሩ ምሥጋና ይገባቸዋል።

ቁጭት ለዘመናት የተንቆረቆረባቸው፤ እነኛ አንጎራጓሪዎች ዛሬ ላይ የደስታ ዜማ ሊቀኙ ነው።

ዓባይ ባዕድነቱን አቁሞ በትውልድ ሀገሩ ጎጆውን ቀልሷል። ኢትዮጵያም የእናትነት ወጓ ደርሷት በልጇ ልትጦር የመስከረም ጠባትን እየተጠባበቀች ነው።

ኢትዮጵያን የዓባይን ታሪክ ግርማውንና ምስጢሩን ይተርካሉ። ከተረክ ተሻግረውም በመረዋ ድምፅ ያዜሙታል።

ስለ ዓባይ ዕልፎች በየትየለሌ ስልተ ምቶች ሁሉ አዚመዋል። ከኢትዮጵያ በገና እና ከበሮ ጋር ተደባልቆ እንደ ዥረት እንዲፈስ ጠብታቸውን አዋጥተዋል።

የሷ ግን ከሁሉ ይልቃል ለማለት የሚያስደፍር ነው። ገለባ የሌለበት የቅኔ ፍሬ በውሃ መልክ ለሚፈሰው ጥቁር ወርቅ አንካችሁ ብላለች።
ብቻዋን ሀገር ሆነ ሄደብኝ ብላ አልቅሳለች። ለዓባይ ንግስቱ ናት፤ እንዳሻት የምታዘው። በእሷ ራሳችንን እናያለን። ደስታን እንቃርማለን። ዓባይን በዜማ ከሰከላ ተነስታ እዚያ በረሀ ድረስ ትሸኘዋለችና፡፡

ሀሳቧን፣ አመክንዮዋን፣ ቁጭቷን፣ ተስፋዋንና ችሎታዋን በዓባይ ውስጥ እንደጅረት ታፈሰዋለች፡፡

ዜማዋ በጊዜና ታሪክ ሰርክ እንደ አዲስ እያደር የሚናፈቅ፤ በይደር የሚጎመራ፣ በቃል የሚገለጽ ሳይሆን ለዘመን የጸና ሀሴት የታመቀበት ነው። በረቀቀ ቅኔ በአዲስ አስተሳሰብ በዓባይ በውበት ተገለጠች፡፡ ስለዓባይ ሲነሳ አብራ ትነሳለች እጅጋየሁ ሺባባ ወይም ጂጂ፡፡

እሷ እንደዓባይ የሀገር ሀብት ናት፡፡ የሀገር ጸጋ። የሀገሬው መኩሪያ። እሷ ማለት ጥበብ ለራሷ መኖሪያነት ወገቧን ታጥቃ የኳለቻት ሴት ናት።

በማይነቃነቅ መሰረት ጥበብ ጎጆዋን የቀለሰችባት። የኢትዮጵያዊነት ገድል መፍሰሻ መንገድ ናት። በዜማዋ ለአፍታ እንኳን የማይናወጥ እንደአለት የፀና አንድነት ሰጠችን።

በግጥሞቿ ውስጥ እልፍ ጉዳዮችን፣ የጥበብን ጥግ በሰላ ብዕሯና በዜማ ዓይናችንን ገለጠች፡፡ ጠያቂም አደረገችን፡፡

ሀገር በተሰራችባቸው ጽንሰ ሀሳቦች ሁሉ ሀገርን አየንባት፡፡ ስለ ዓባይ አዜመች የማያረጀውን ውበት የማያልቀውን ቁንጅናውን አሳየችን፡፡

‹‹ትናገር አድዋ›› እያለች በወኔ ሞላችን የተከፈለልንን መስዋዕትነት ፍንትው አድርጋ በልባችን አተመች፡፡ የወንዙን አውራ ዓባይን የእሷ፤ የብቻዋ አደረገችው፡፡

‹‹ፍልቅልቅ ፍልቅልቅ አንች ውብ ከተማ
ዓባይ ባልሽነው ወይ ሰማሁኝ ሲታማ
ሀብታም ባል እያለሽ ምነው ደህይተሻል
ብራንባር አልቦሽን ሽጠሽው በልተሻል››

ይህ ግጥም ዓባይ በሚለው ለእጅጋየሁ ሺባባ ሙዚቃ ውስጥ ሊካተት ተጽፎ ቢዘጋጅም በሙዚቃው ላይ ማካተት እንዳልተቻለ በአንድ ወቅት ከኢትዮጵያ ሬድዮ ጋር በነበራት ቃለመጠይቋ ተናግራለች፡፡

ፍልቅልቅ በዓባይ በረሃ ውስጥ የምትገኝ ከተማ ናት፡፡ ዓባይ በስሯ እየሄደ ብራንባሯን ሽጣ የምትጠማ ከተማ እንደሆነች ለመግለጽ፡፡

‹‹ዓባይ አስተምሮኝ አጉል ደግነት፤
ቤቴ እየተራበ ሳበላ ጎረቤት፤
ምን ይለኛል ሀገር
ምን ይለኛል ሰው
ዓባይ ወንዛ ወንዙ
ብዙ ነው መዘዙ››

በተጨማሪም በዚሁ ቃለ መጠይቋ በዜማዋ እያንጎራጎረች ‹‹ይህን ዘፈን ስሰራ በርካታ ግጥሞች ነበረው፤ ግጥሙ በዝቶ አወጣነው›› ስትልም ተናግራለች፡፡

“የማያረጅ ውበት የማያልቅ ቁንጅና፣
የማይደርቅ፣ የማይነጥፍ ለዘመን የጸና፣
ከጥንት ከፅንሰ አዳም ገና ከፍጥረት ፣
የፈሰሰ ውሃ ፈልቆ ከገነት” ብላ ትጀምራለች፡፡

የዓባይን ዘላለማዊነት በሚገልጹ ቃላት እያሽሞነሞነች፤ ˝የማይነጥፍ፣ የማይደርቅ˝ እያለች የዓባይ መነሻ ከኤደን ገነት እንደሆነ ትነግረናለች፡፡

የዓባይን ውበት፣ ቁንጅናና ዘላለማዊነት ከመጀመሪያ እስከመጨረሻ ድረስም በሙዚቃው ውስጥ ትገልጸዋለች፡፡

ቀጠለች ˝ለዘመን የጸና˝ አለችው፡፡ የጎመራውን የዓባይ ውበት ህይወት ዘራችበት ለትላንት፣ ለዛሬ፣ ለነገም ይሰራ ዘንድ፡፡

‹‹ግርማ ሞገስ ፣
የሀገር ፀጋ፣ የሀገር ልብስ…
ግርማ ሞገስ…ዓባይ፣
የበረሀው ሲሳይ››

በስርቅርቅ ድምጿ ‹‹ግርማ ሞገስ›› አለችን የሀገር ፀጋነቱን፣ የሀገር ልብስነቱን አስረዳችን።

ዓባይ ከእግዜሩ የተቸረን እንደሆነ ነገረችን፡፡ ዓባይ መኩሪያችን ነው አለች፡፡ ዓባይ ሲርበን ሲጠማን መሸሸጊያ ልብሳችን ነው አለችን፡፡ በዚያ ግን አላበቃችም ቀጠለች፡፡

‹‹ብነካው ተነኩ! አንቀጠቀጣቸው፣
መሆንህን ሳላውቅ፣ ስጋና ደማቸው፡፡
የሚበሉት ውሀ፣ የሚጠጡት ውሀ፣
ዓባይ ለጋሲ ነው በዚያ በበረሀ፡፡
ዓባይ… ዓባይ… ዓባይ… ዓባይ፣
ዓባይ ወንዛ ወንዙ፣ ብዙ ነው መዘዙ››

˝ዓባይ ወንዛወንዙ ብዙ ነው መዘዙ˝ የሚለውን የዜማውን ግጥም ስትደጋግመው ትስተዋላለች፡፡ ሀረጉ ዓባይ ለእኛ ለኢትዮጵያውን የሚሰጠውን ጥቅም ብቻ ሳይሆን፤ ያለውን ፓለቲካዊ አንድምታም ጠቁማለች፡፡

ለማይደርቅ፣ ለማይነጥፍ ውበትና ቁንጅና ቋማጩ እልፍ ነው፡፡ በዚህ ዜማም የጎረቤቶቻችንን ፍላጎትና መቋመጥ ነገረችን፡፡ እንዲሁም ዘመን ተሻጋሪ በሆነ መልኩ የዚያኛውን ወገን የፍርሃት ስሜት እና ፍላጎት ገልጣለች፡፡ "የሚበሉት ውሃ የሚጠጡት ውሃ" አለችን ዓባይ ለእነኛ ሰዎች ህይወታቸው እንደሆነ ሹክም አለችን፡፡

‹‹ዓባይ የወንዝ ውሀ፣ አትሆንም እንደሰው፣
‘ተራብን፣ ተጠማን'… ‘ተቸገርን' ብለው፣
አንተ ወራጅ ውሀ …ቢጠሩህ አትሰማ፣
ምን አስቀምጠሀል ከግብፆች ከተማ››

ስትል በዜማዋ ዓባይን አናገረችው "ዓባይ ወንዛ ወንዙ - ብዙ ነው መዘዙ" ብላም ልክ እንደ ሸማኔ በውብ ግጥሟን ቋጨችው።

ስለ ዓባይ ውበት እና ጉልበት እጅጋየሁ ሽባባው ዘመን ተሻጋሪ የኪነጥበብ አሻራዋን አሳረፈች፡፡

ዓባይን የገለጸችበት መንገድ በኢትዮጵያውያን ልብ እንደእንቦሳ እንድትቦርቅ አድርጓታል።

ዛሬም ድረስ ስለዓባይ ሲነሳ ቃላት ያጥረን እንደሆን ወደ ጂጂ ዘፈን ጎራ ማለታችን አይቀርም።

በቃልኪዳን አሳየ ጋዜጣ ፕላስ


Address

Tucker, GA

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hagere Infotainment posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Hagere Infotainment:

Share