Hagere Infotainment

Hagere Infotainment Time is everything | ጊዜ ሁሉም ነገር ይህ የቁምነገርና የመረጃ መለዋወጫ መማማሪያ ገጽ ነው ። ማንኛውንም አስተያየት ወይም ሀሳብ በጨዋነት መግለጽ የሀገራችን ሰው ባህል ነውና ካልተገባ ንግግር እንቆጠብ፣

" የበሽታዉ መንስኤ ማርበርግ ቫይረስ (Marburg Virus) መሆኑን መለየት ተችሏል " - ጤና ሚኒስቴር የጤና ሚኒስቴር በደቡበ ኢትዮጵያ ክልል በጅንካ ከተማ የሄሞራጅከ ፊቨር (Viral ...
11/14/2025

" የበሽታዉ መንስኤ ማርበርግ ቫይረስ (Marburg Virus) መሆኑን መለየት ተችሏል " - ጤና ሚኒስቴር

የጤና ሚኒስቴር በደቡበ ኢትዮጵያ ክልል በጅንካ ከተማ የሄሞራጅከ ፊቨር (Viral Hemorragic Fever) በሽታ መከሰቱን እና የበሽታዉን ምንነት በማረጋገጥ ላይ መሆኑን መግለጹ ይታወቃል፡፡

ሚኒስትሩ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ የበሽታዉ መንስኤ ማርበርግ ቫይረስ (Marburg Virus) መሆኑን መለየት ተችሏል ብሏል።

የዘረመል ምርመራው የተከናወነው በኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ብሄራዊ ሪፈረንስ ላብራቶሪ ነው።

መግለጫው "በዚህም የዘረመል ምርመራ በአሁኑ ሰዓት ኢትዮጵያ ውስጥ የተገኘዉ ቫይረስ ሌሎች ምስራቅ አፍሪካ ሃገራት ላይ ከዚህ በፊት ከተከሰቱት ጋር ተመሳሳይ ዝርያ ያለዉ መሆኑ ታዉቋል" ነው ያለው።

በተጨማሪም በዛሬው እለትም አዲስ የበሽታውን ምልክት ያሳየ ወይም በቫይረሱ የተጠረጠረ ሰው ያልተገኘ መሆኑን ሚኒስትሩ ያሳወቀ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት የተለያዩ የሙያ ስብጥር ያካተተ ከፍተኛ ፈጣን ምላሽ ሰጭ ቡድን ወደ ከልሉ በመላከ በሽታዉን የመከላከል እና የመቆጣጠር ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ ብሏል።

ከነዚህም ውስጥ :-

° የማህበረሰብ አቀፍ የቅኝት ስራዎች፣

° በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን ለይቶ ማከም፣

° የማህበረሰብ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች እና ከተጠረጠሩ ሰዎች ጋር ንክኪ ያላቸዉን ሰዎች የመለየት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተገልጿል።

በሃገር አቀፍ እንዲሁም በክልል ደረጃ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች የክስተት አስተዳደር ስርዓት (Incident Management System) ተቋሞ የፈጣን ምላሽ ስራዎችን በማስተባበር ላይ ይገኛል ተብሏል።

Hagere Infotainment

በኢትዮ ሳት የሚተላለፈው የቴሌቪዥን ስርጭት በሙሉ ተቋርጧል ! Hagere Infotainment
11/14/2025

በኢትዮ ሳት የሚተላለፈው የቴሌቪዥን ስርጭት በሙሉ ተቋርጧል !



Hagere Infotainment

ከፍተኛ ጥንቃቄ ይደረግ !ጂንካ ሆስፒታል ለጊዜው ምንነቱ ያልታወቀ ገዳይ በሽታ የጤና ባለሙያዎችን ጨምሮ ታማሚዎችን መግደሉ የሆስፒታሉ ሀኪሞች ገለፁ።በሽታው በትኩሳት ይጀምርና የውስጥ አካላት...
11/12/2025

ከፍተኛ ጥንቃቄ ይደረግ !

ጂንካ ሆስፒታል ለጊዜው ምንነቱ ያልታወቀ ገዳይ በሽታ የጤና ባለሙያዎችን ጨምሮ ታማሚዎችን መግደሉ የሆስፒታሉ ሀኪሞች ገለፁ።

በሽታው በትኩሳት ይጀምርና የውስጥ አካላትን ያጠቃል። ቀጥሎ የውስጥ አካል የሚያደማ ሲሆን የሰውነት አካላት ተግባራቸውን እንዳያከናውኑ በማድረግ ለሞት እንደሚዳርግ ተገልጿል።

እስካሁን አንድ ሀኪም፣ አንዲት ነርስና ሦስት ታማሚዎች ለሞት መዳረጋቸውን የሆስፒታሉ ሀኪሞች ተናግረዋል።

የበሽታው ምንነት እስኪታወቅ ድረስ ዜጎች ለኮሮና አይነት ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ያሳሰቡ ሲሆን ከሟቾቹ ጋር ግንኙነት ያላቸው ግለሰቦችን ከመቅረብ መታቀብ እንደሚያስፈልግም አሳስበዋል።

የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጥም አበክረው ጠይቀዋል።

Hagere Infotainment FELEG ETHIOPIA

11/09/2025

መልካም ጊዜ ይሁንላችሁ 😂😅 ሁሉንም መሞከር ግዴታ አይደለም !




11/09/2025

መልእክተኛው ዛሬ ማታ በሰይፉ ሾው Seifu on EBS @ [1008833494586184:49210:]





゚viralシ ゚viralシalシ

11/09/2025

አባታችን ብጹዕ አቡነ ኤርምያስ ከሌሎች ከብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጋር ዛሬ ኮምቦልቻ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የተደረገላቸው አቀባበል እንዲሁም ከኮምቦልቻ ወደ ደሴ የተደረገው ጉዞ እጅግ በጣም ደስ የሚል ነበረ።





በአርሲው ጥቃት 8 ቤተሰብ የተገደለበት ቤተሰብ 😥ባለፈው ሳምንት ረዕቡ እና ሐሙስ ዕለት በተፈጸመው የመጀመሪያው ጥቃት ከተገደሉ ሰዎች ውስጥ "ስምንቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት" እንደሆኑ ሦስት...
10/31/2025

በአርሲው ጥቃት 8 ቤተሰብ የተገደለበት ቤተሰብ 😥

ባለፈው ሳምንት ረዕቡ እና ሐሙስ ዕለት በተፈጸመው የመጀመሪያው ጥቃት ከተገደሉ ሰዎች ውስጥ "ስምንቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት" እንደሆኑ ሦስት ምንጮች ለቢቢሲ ገልጸዋል። በአንድ ሳምንት ውስጥ ተከታታይ ጥቃቶች የተፈጸሙባቸው በአርሲ ዞን ውስጥ በሚገኙት ጉና፣ ሽርካ እና ሆንቆሎ ዋቤ ወረዳዎች ነው።

ቢቢሲ ጥቃቶቹን በተመለከተ ያነጋገራቸው ሁለት የተጎጂዎች ቤተሰብ አባላት እና ሦስት የቤተክርስቲያን ኃላፊዎች በደኅንነት ስጋት ምክንያት ስማቸው እንዳይጠቀስ ጠይቀዋል። ምንጮቹ እንደሚገልጹት በዞኑ በሚገኙት ጉና፣ ሽርካ እና ሆንቆሎ ዋቤ ወረዳዎች ተከታታይ ግድያዎች የተፈጸመው ካለፈው ሳምንት ረቡዕ ዕለት ጥቅምት 12/2018 ዓ.ም. አንስቶ ነው። ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሰዎች የተገደሉት ሰሞነኛው ጥቃት በጀመረበት ጉና ወረዳ ነው። ታጣቂዎች ባለፈው ሳምንት ረቡዕ እና ሐሙስ በፈጸሟቸው ጥቃቶች 14 ሰዎች መገደላቸውን ሁለት የተጎጂዎች ቤተሰብ አባላት እና የአካባቢው የቤተክርስቲያን አመራር ለቢቢሲ ተናግረዋል።

https://bbc.in/4nyRIwO

በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ውስጥ በአንድ ሳምንት ውስጥ በተፈጸሙ ጥቃቶች ሕጻናትን ጨምሮ "25 ሰዎች" መገደላቸውን የተጎጂዎች ቤተሰቦች እና በአካባቢው የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋ....

የክቡር ዶ/ር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩየሀገራችን ዋርካ እና የሁሉም አባት የነበሩት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ባጋጠማቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው...
10/19/2025

የክቡር ዶ/ር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የሀገራችን ዋርካ እና የሁሉም አባት የነበሩት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ባጋጠማቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

ነፍስ ይማር !

የወንዝ ዳር ልማት እየተባለ እየተነገረ በሌላ በኩል የወንዝ ብክለት ለ Kombolcha city  communication ወሎ ኮሞቦልቻ በቦርከና   ወርቃ ወንዝ ተብሎ በሚጠራው ወደ ቦርከና ወን...
10/17/2025

የወንዝ ዳር ልማት እየተባለ እየተነገረ በሌላ በኩል የወንዝ ብክለት ለ Kombolcha city communication

ወሎ ኮሞቦልቻ በቦርከና ወርቃ ወንዝ ተብሎ በሚጠራው ወደ ቦርከና ወንዝ በቀጥታ የሚቀላቀል፣ የከተማ ነዋሪዎቹንም ሆነ የታችኛውን ተፋሰስ ማህበረሰብ የሚጎዳ ኬሚካል ሳይጣራ ወይ EIA ⏩ ( Environmental Impact Assessment) እያቀረቡ፣ Industrial treatment plant ከወረቀት ዲዛይን ባለፈ የግንባታው ወጭን በመፍራት አለመስራት ፣ ቢሰራም ወደ ስራ አለማስገኘት የፈጠረው ችግር ነው ።

⏩➠➢ ከፋብሪካዎች የሚለቀቅ የተሸከመው wasted water በታከም አለበት፣ ይህ በአካባቢው ላይ ከፍተኛ ጫና ይፈጥራል ፣ ለጤናም ጠንክ ይሆናል ። ይልቁን በአካባቢው ያሉ ፋብሪካዎች ለማህበረሰቡ የጋራ ጠቃሚ የሆኑ ጤና ጣቢያ፣ ትምህርት ቤት፣ መንገድ የመሳሰሉ መስራት ባይችሉ የሚለቁትን ያልታከመ ኬሚካል መልቀቅ የለባቸውም ። አሁን የሚታየውን ጨለማን ተገን አድርገው መልቀቅ ትክክል አይመስለኝም። https://www.facebook.com/share/17UwghbFEy/

 #የእርዳታ ጥሪየኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ከተማ እና መሰረተ ልማት መምሪያ የስራ ባልደረባ የሆኑት አቶ አብዱልአዚዝ በቀለ ኃ/ማሪያም በደረሰባቸው ድንገተኛ የነርቭ ህመም በደሴ ከተማ  በተ...
10/17/2025

#የእርዳታ ጥሪ

የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ከተማ እና መሰረተ ልማት መምሪያ የስራ ባልደረባ የሆኑት አቶ አብዱልአዚዝ በቀለ ኃ/ማሪያም በደረሰባቸው ድንገተኛ የነርቭ ህመም በደሴ ከተማ በተለያዩ የህክምና ማዕከላት ህክምና ሲከታተሉ ቢቆዩም ህመሙ ሊሻለው ባለመቻሉ ለአስቸኳይ ህክምና ወደ አዲስ አበባ ሪፈር ተብለዋል።

አዲስ አበባ የሚገኘው የህክምና ማዕከልም የቀዶ ህክምና ማድረግ እንደለባቸው ስለተነገራቸው ለቀዶ ህክምናው ወጭ 300ሽህ ብር በላይ በመሆኑ የተጠየቀውን ወጭ በራሳቸው ለመሸፈን አቅም ስለሌላቸው የገንዘብ ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ ተቋቁሞ ገንዘብ እየተሰባሰበ ይገኛል።

በመሆኑ የገንዘብ አሰባሳቢ ኮሚቴው ሁሉም የቻለውን የገንዘብ ድጋፍ እንድታደርጉለት እና ፈጣሪ እንዲያነው በዱአና በፀጥሎት እናድታግዙት ጠይቀዋል ።

የማሰባሰቢያ አካውንቱ አብዱልአዚዝ በቀለ ኀ/ ማሪያም

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000192471827
አባይ ባንክ 6067411072141013 መሆኑን የተቋቋመው ገቢ አሰባሳቢ ከሚቴ ገልጿል።

Kombolcha city communication

Address

Tucker, GA

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hagere Infotainment posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Hagere Infotainment:

Share