Hagere Infotainment

Hagere Infotainment Time is everything | ጊዜ ሁሉም ነገር ይህ የቁምነገርና የመረጃ መለዋወጫ መማማሪያ ገጽ ነው ። ማንኛውንም አስተያየት ወይም ሀሳብ በጨዋነት መግለጽ የሀገራችን ሰው ባህል ነውና ካልተገባ ንግግር እንቆጠብ፣

የአርቲመስ ጠፈርተኞች ከምድር ጋር ግንኙነታቸው ተቋርጦ የሚቆይባቸው 40 ደቂቃዎች፦በአርቲመስ ጠፈር ቪ ሲጀምሩ በጨረቃ መንኮራኩሩ እስከ 40 ደቂቃ በመሬት እና በተጠፈሩት በኩል የግንኙነት መ...
04/06/2026

የአርቲመስ ጠፈርተኞች ከምድር ጋር ግንኙነታቸው ተቋርጦ የሚቆይባቸው 40 ደቂቃዎች፦

በአርቲመስ ጠፈር ቪ ሲጀምሩ በጨረቃ መንኮራኩሩ እስከ 40 ደቂቃ በመሬት እና በተጠፈሩት በኩል የግንኙነት መቋረጥ ይከሰናል። ጠፈርተኞቹ በራሳቸው ሀሳብ እና ስሜት እንዲቆይ ግንኙነቱ ስለሚቋረጥ ተናግኝባቸዋል። ይህ ውድድሩ በ1969 የአፖሎ 11 ጠፈር ላይም ተደረጉ ሰፊ ብቸኝነቶችን የሚጠቃለል።

መሬት መንኮራኩራቸው ውስጥ ባለው የኋለኛ መስታወት ስትታይ እያነሰች እየሄደችም ቢሆን ሂውስተን ቴክሳስ ከሚገኘው የቁጥጥር ማዕከል ጋር የማያቋርጥ ግንኙነት ነበራቸው። ከናሳ ባለሙያዎች የሚሰማው የተረጋጋ ድምፅ ለጠፈር ቡድኑ ከቤታቸው ከምድር ጋር የሚያፅናና ግንኙነትን ፈጥሯል።

ይህ ግንኙነት አሁን ሊቋረጥ ነው። ጠፈርተኞቹ ሰኞ ሌሊት ላይ በጨረቃ ጀርባ በኩል ለማለፍ ሲቃረቡ በመንኮራኩሩ እና በመሬት መካከል ግንኙነት እንዲኖር የሚያስችለው የራዲዮ እና የጨረር ግንኙነት በራሷ በጨረቃ ይጋረዳል።ለ40 ደቂቃ ያህል አራቱ ጠፈርተኞች ብቻቸውን ይሆናሉ፤ በጨለማው ሕዋ ጉዟቸውን ሲቀጥሉ በራሳቸው ሀሳብ እና ስሜት ውስጥ ብቻ ይሆናሉ። ይህም ጥልቅ የዝምታ እና የብቸኝነት ጊዜ ሆኖ ይመዘገባል።

የአርቲመስ አብራሪ ቪክተር ግሎቨር ይህን ጊዜ ዓለም ለመቀራረብ ይጠቀምበታል የሚል ተስፋ እንዳለው ተናግሯል።"ከጨረቃ ጀርባ ስንሆን፤ ከሁሉም ሰው ጋር ግንኙነት ስናቋርጥ ይህን እንደ ዕድል እንውሰደው" በማለት የጠፈር ጉዟቸውን ከማድረጋቸው አስቀድሞ ለቢቢሲ ተናግሯል።

"እንፀልይ፤ ተስፋ እንሰንቅ፤ ከባልደረቦቻችን ጋር ዳግም ግንኙነት እንድንቀጥል መልካም ሀሳባችሁን እና ስሜታችሁን ላኩልን" በማለትም አክሏል።ከ50 ዓመታት በፊትም የአፖሎ ጠፈርተኞችም ወደ ጨረቃ በነበራቸው ተልዕኮ በተፈጠረ የግንኙነት መቋረጥ ተመሳሳይ ብቸኝነት ገጥሟቸው ነበር።

ምን አልባትም ከአፖሎ 11ዱ ጠፈርተኛ ማይክል ኮለንስ በላይ ብቸንነቱ የተሰማው አይኖርም።እ.አ.አ በ1969 ኒል አርምስትሮንግ እና በዝ አልድሪን በጨረቃ ወለል ላይ በመራመድ ታሪክ ሲሰሩ ኮለንስ ብቻውን ጨረቃን እየዞረ ነበር።

መንኮራኩሩ ራቅ ባለው ጎን ሲያልፍ ጨረቃ ላይ ከነበሩት ባልደረቦቹ እና ከተልዕኮው ተቆጣጣሪዎች ጋር ግንኙነቱ ተቋርጦ የነበረ ሲሆን፤ ጠፈርተኛው ለ48 ደቂቃ ጠፍቶ ነበር። እ.አ.አ በ1947 ባሳተመው ግለ ታሪኩ በዚያ ወቅት "እውነተኛ ብቸኝነት"እና "ከሚታወቅ ሕይወት መነጠል" እንደተሰማው ገልጿል። ሆኖም ፍርሃትም እንዳልተሰማው ጽፏል።

ከተልዕኮው በኋላ በሰጣቸው ቃለ ምልልሶች ራዲዮው ዝም ሲል ምን ያህል ሰላም እና ፀጥታ እንደተሰማው እንዲሁም ከማዕከላዊ ቁጥጥሩ አፍታ እና እረፍት ማግኘቱን ገልጿል።ከመሬት ጋር የሚደረግ ግንኙነት ፀጥ ረጭ የሚልበት ጊዜ ከመንኮራኩሩ ጋር የሚደረገውን ግንኙነትን መመለስ ሥራቸው ለሆነ ባለሙያዎች የጭንቀት ጊዜ ነው።

በደቡብ ምዕራብ እንግሊዝ በሚገኘው የጉንሂሊ የመሬት ጣቢያ በመንኮራኩሯ ጉዞ ሁሉ በግዙፉ አንቴና ምልክቶችን በመሰብሰብ ወደ ናሳ ዋና መስሪያ ቤት መረጃውን ይልካል።የጣቢያው የቴክኖሎጂ ኃላፊ የሆነው ማት ካስቢ "ሰው ያለበትን መንኮራኩር ስንከታተል ይህ የመጀመሪያው ነው" ሲል ለቢቢሲ ተናግሯል።

"በጨረቃ ጀርባ መንኮራኩሩ ሲጓዝ የተወሰነ ፍርሃት ይሰማናል እናም ዳግም ስናየው ደግሞ በጣም ደስ እንሰኛለን። ምክንያቱም ደህና እንደሆኑ እናውቃለን።"እንደዚህ አይነቱ የግንኙነት መስተጓጉል በቅርቡ ታሪክ እንደሚሆን ተስፋ አለ። ናሳ እና ሌሎችም የሕዋ ተቋማት በጨረቃ ቤዝ ሲከፍቱ እና ፍለጋው ከዚህ በበለጠ ሲጠናከር አስፈላጊ ነው ይላል።

"በጨረቃ ዘላቂነት ላለው ቆይታ ሙሉ ለሙሉ ግንኙነት ያስፈልጋል። በሩቁ ጫፍም ቢሆን በቀን ለ24 ሰዓታት ያስፈልጋል። ምክንያቱም ሩቁ ጫፍንም ማየት ስለምንፈልግ" ሲል አክሏል።በአውሮፓ የሕዋ ኤጀንሲ ስር ያሉ መርሃ ግብሮች ወደፊት ቀጣይነት ያለው እና አስተማማን ግንኙነት ለመፍጠር ተከታታይ መንኮራኩሮችን በጨረቃ ዙሪያ ለመላክ እቅድ ይዘዋል።

ለአርቲመስ ጠፈርተኞች ከመሬት ጋር ካለ ግንኙነት የሚያሳልፉት ጊዜ ሙሉ ትኩረታቸውን ጨረቃ ላይ እንዲያሳርፉ ይፈቅድላቸዋል። 40ውን ደቂቃ ምስሎችን በመውሰድ፣ የጨረቃን ስነምድር በማጥናት እና የጨረቃን ግርማ ሞገስ በማየት ያሳልፋሉ። ታሪክ ሰሪ የሆኑት ጠፈርተኞች ልዩ የሆነውን ምልከታቸውን ለሁሉም ወደ ምድር በመላክ ያጋራሉ። (ቢቢሲ)



FELEG ETHIOPIA Hagere Infotainment

አመል !◉ አመል፣ ያወጣል ከመሀል። ● አመል ያላት አገልጋይ፣ ከእመቤቷ እኩል ት'ቀባለች። ● የተለመደ አመል፣ ቁምነገረኛ መምሰል። ● አመል ቤት አይጠብቅ። ● አመልህን በጉያህ፣ ስንቅህን ...
04/02/2026

አመል !

◉ አመል፣ ያወጣል ከመሀል።

● አመል ያላት አገልጋይ፣ ከእመቤቷ እኩል ት'ቀባለች።

● የተለመደ አመል፣ ቁምነገረኛ መምሰል።

● አመል ቤት አይጠብቅ።

● አመልህን በጉያህ፣ ስንቅህን ባህያህ።

● የአመል ታናሽ፣ ይጥላል ጭራሽ።

● ሰውና አመሉ፣ ሳይተዋወቁ ይኖራሉ።

● አመልህ፣ በጥፊ ይበልህ።

● መልኳ ባያምር፣ አመሏ ያምር።

● የቤት አመል፣ ገበያ ይወጣል።

● አመልና ጅራት፣ በስተኋላ ይበቅላል።

● የሰው አመሉ፣ ዳውላ ሙሉ።

● አመል ያላት አይጥ፣ ከባለቤቱ እኩል ትበላለች።

● ከእትብት ጋር የመጣ አመል፣ ከከፈን ጋር ይቀበራል።

● አመል ከሌላት፣ አይቀርም መፍታት።

● ሰውን ከነአመሉ፣ ድሪቶን ከነቅማሉ፣ ወዲያ በሉ።


FELEG ETHIOPIA

በ 90ዎቹ በጣም ይነበቡ የነበሩ መጽሔቶች !
03/29/2026

በ 90ዎቹ በጣም ይነበቡ የነበሩ መጽሔቶች !

"ነፃነት ወርቅነህ በትዳሩ ደስተኛ አልነበረም "    >         (ዘሪሁን ተዝናኑ እንደጻፈዉ)               እህቱ ሚሚ ወርቅነህ ፦★ ነፃነት የዛሬ አራት ዓመት ወድቆ ሀኪም ቤት...
03/17/2026

"ነፃነት ወርቅነህ በትዳሩ ደስተኛ አልነበረም "
>
(ዘሪሁን ተዝናኑ እንደጻፈዉ)

እህቱ ሚሚ ወርቅነህ ፦

★ ነፃነት የዛሬ አራት ዓመት ወድቆ ሀኪም ቤት ሲሄድ
ICMC ሆስፒታል የአንጀት መድማት ነው አሉኝ
ብሎ ነገረኝ።

★ አሜሪካ ጥሩ ህክምና አለ ሂድ አልነው። አሜሪካ
ሄደ። አሜሪካ ሄዶም ሚስቱ ቤት ውስጥ ወደቀብኝ
አለች። አሜሪካ ያልተመቻቹለት ነገሮች ነበሩ።

★ ከአሜሪካ የተመለሰው በጣም ከፍቶት ነው።
ጉበቱ እንደታመመ የተነገረውም አሜሪካ ሀገር ነው።

★ አሜሪካ ሀገር ከሚስቱ ጋር ተጋጭተው ለእኔ
ደወለልኝ። ስመጣ የምናወራው ነገር አለ አለኝ።
ሲመጣ ስለመከተው በጣም ጠቋቁሮ የሚያሳዝን
ሆኖ ነው ያገኘሁት። ተመልሼ ወደ አሜሪካ አልሄድም
አለኝ።

★ በትዳሩ ደስተኛ አልነበረም። የሚስቱ እናት ከዚህ ሆና
ነገር ታቀብላለች። አሜሪካ ሀገር ላይ ሚስቱ አትረዳውም
ነበር።

★ የራሷንና የልጆቿን ምግብ ሰርታ ነፃነትን ራስህ
ተነስተህ ሰርተህ ብላ ትለው ነበር።

★ ህንድ ሀገር ለህክምና የሄድን ጊዜ ሚስቱ ደውላ
ስለጤንነቱ ሳይሆን የምትጠይቀው
ቤት ስለመግዛት ነበር የምታወራው።

★ በየወሩ የሚልክልኝ ሁለት ሺህ ዳላር አይበቃኝም።
አይጠቅመኝም ብላኛለች።

★ አስናቀ የቀብሩ ዕለት ታገስ ጋር ቀጠሮ ነበረን ሲል
የሆነ የጀመሩት ፕሮጀክት ነበር የመሰለን።
መጠጥ ቤት አልመሰለንም ነበር። በጣም
ነው የሚያሳፍረው።

★ አስናቀ ደውሎልኝ ነፂ መኪና ሲገዛ ሸሸኝ አለኝ።

★ ነፃነት መኪና የለውም ያለው ለጎፈንድሚ እያመቻቸው
ስለነበር ነው። ነፃነት ከተገዛ ስምንት ወር የሞላው
መኪና አለው።

★ አስናቀ በ29 ዓመታት አንድ ወር ብቻ ነው የተለያየነው
የሚለውን አላምንበትም። መንታ ነኝ ቢልም ችግር
የለብኝም።

★ እውነቸኛ ወዳጅ ማለት ከእናንተ ሀዘን የኔ ይበልጣል
እያለ ወከባ መፍጠር ሳይሆን ለጓደኛ መስዋዕት
መሆን ነው። እንዳይጠጣ እንዳይጎዳ ማድረግ
ነበረበት።

★ ነፃነት ለልጆቹ ብር ይልካል። እዚህ የሚኖሩበት ቤት
ደግሞ የቤት ኪራይ ይከፍላል። ለዛ ነው ገንዘብ
የሌለው።

★ ሶስት ሚሊዮን ብር የሰጠንን ባለሃብት እናመሰግናለን።
ከጭንቅ ነው ያዳነን።

★ አሁን እስከማውቀው በስሙ ምንም ብር
እንዳይሰበሰብ በስሙ ልመና እንዳይደረግ ብለናል።
የሰጡ ሰዎች ካሉ ያሳውቁን።

★ የሀውልት ምርቃት መቄዶንያ ያበላል። የተረፈው
ብር ደግሞ ሚስቱ በአካውንቴ ይግባልኝ ብላለች።
__________________//___________________

ታላቅ ወንድሙ ወንድወሰን ወርቅነህ ፦

★ አሜሪካ ሀገር ሆስፒታል እያለ አንድም ሰው አጠገቡ
አልነበረም።

★ ሚስቱ እዚህ ከእናቷ ጋር ተከራይቶ ከሚኖርበት ቤት
ቡትቶህንና መፅሐፍህን ይዘህ መሄድ ትችላለህ
ብላዋለች።

★ አሜሪካ ያልታከመበት ምክንያት ባለቤቱ ስላልተረዳችውና
ፈቃደኛ ስላልነበረች ነው።

★ በዙሪያህ ያሉ ጓደኞችህ ጥሩ ምቾት እየሰጡኝ
አይደለም ብዬ መክሬዋለሁ።

★ ነፃነትም በዙሪያዬ ብዙ ሰዎች አሉ። ሰው ግን የለኝም
ብሎኛል።

★ እውነተኛ ጓደኛ ነኝ የሚል ሰው ካለ ነፃነትን
ሊያግዘው ይገባ ነበር።

★ አስናቀ እኛን ሁላችሁም ከኔ በላይ አልተጎዳችሁም
ይለን ነበር።

★ ለነፃነት የሚያስቡ ጓደኛ ቢሆኑ ኖሮ ለህይወቱ
የሚጠነቀቁለት በሆነ ነበር። ግን አብረው
ይጠጡ ነበር።

____________________//__________________


ታናሽ ወንድሙ ኤርሚያስ ወርቅነህ ፦

★ ትክክለኛ ጓደኞቹን አላየናቸውም። ለገፅታ ግንባታ
የሚሰሩትን ግን እያንዳንዱ ሚዲያ ላይ ቀርበው
አሳይተዋል።

★ በህክምና ላይ የነበሩ ሰዎችን አላመሰገንም።

★ ተዋናይት ኤልሳቤጥ ( ቀጮ ) እና ባዩሽ ከበደ ( ሚጡ )
አልተመሰገኑም።

★ አስናቀ ነፃነትን የሚመጥን ንግግር አይደለም እየተናገረ
የነበረው።

★ የነፃነት ሰርግ ላይ አስናቀ ጭራሽ አልነበረም።

★ ከእናንተ በላይ እኔ አውቀዋለሁ። እቀርበዋለሁም
እያለን ነው።

__________________//__________________

ክቡራትና ክቡራን ፦ የነፃነት ወርቅነህ ቤተሰቦች
እርቅ ሚዲያ ላይ ቀርበው የዘረገፉት ጉድ ይኽንን
ይመስላል።

ቃለ - መጠይቅ ያደረጋቸው እንዳልክ አሰፋ
መስቀለኛ ጥያቄዎቹ አስገራሚ ነበሩ።
ፍፁም ተረጋግቶ ነበር በብቃት ቃለ - መጠይቁን
የሰራው።

እንዳልክ አንተን የምናውቅህ በዚህ ብቃትህ ነው።
እየፎረሽክ አስቸግረህ ነበር።
ጥሩ ስትሰራም ማመስገን አለብን !

ዘሪሁን ተዝናኑ
ከማይነበብ ፊርማ ጋር !!!

03/13/2026
03/01/2026

እንኳን ለታላቁ የዓድዋ ድል 130 ኛ ዓመት ክብረ በዓል አደረሳችሁ!


FELEG ETHIOPIA

03/01/2026

እንኳን ለታላቁ የዓድዋ ድል 130 ኛ ዓመት ክብረ በዓል አደረሳችሁ! ኮምቦልቻ !

ከጧቱ 1:00 ሰአት ላይ 130 ኛው የዓድዋ የድል በዓልን ምክንያት በማድረግ በኮምቦልቻ ከተማ መነሻውን ቢራሮ አዳራሽ መድረሻውን ንግድ ባንክ አደባባይ ያደረገ የጎዳና ላይ ትእይንትና ዓድዋን የሚዘክሩ ኪነ ጥበብ ዝግጅቶች ይቀርባሉ ሁሉም ሰው እንዲገኝ በክብር ተጋብዟል !


Vivan V Vivan FELEG ETHIOPIA

03/01/2026

እንኳን ለታላቁ የዓድዋ ድል 130 ኛ ዓመት ክብረ በዓል አደረሳችሁ!


FELEG ETHIOPIA

ወርቅ - በምሳሌ !● "ወርቅ ለአንጣሪ፣ በቅሎ ላሰጋሪ" ● "ወርቅ በእሳት፣ መሬት በጣት" ● "ወርቅ የያዘ ሳጥን በወርቅ አልተለበጠም"● "ወርቅ ያለው ቀበዝባዛ፣ እህል ያለው ፈዛዛ" ● "...
02/11/2026

ወርቅ - በምሳሌ !

● "ወርቅ ለአንጣሪ፣ በቅሎ ላሰጋሪ"
● "ወርቅ በእሳት፣ መሬት በጣት"
● "ወርቅ የያዘ ሳጥን በወርቅ አልተለበጠም"
● "ወርቅ ያለው ቀበዝባዛ፣
እህል ያለው ፈዛዛ"
● "የተቆለፈ ወርቅ፣ ያልተቆለፈ ጨርቅ"
● "ወርቅና ሰም፣ ፈትልና ቀለም"
● "ወርቅና ጨዋ አስታራቂ ነው"
● "እንደ ወርቅ አንከብሎ፣
እንደ ጨርቅ ጠቅሎ"
● "ወርቅ ይረክሳል፣ መዳብ ይነሳሳል"
● "ሰምና ወርቅ፣ እንጀራና መረቅ"
● "ወርቁ ቢጠፋ፣ ሚዛኑ አይጠፋ"
● "ወርቁ ከዳኛ ይቅረብ፣
መፃፉ ከቄስ ፊት ይነበብ"
● "ወርቅ ለዝና፣ እህል ለቀጠና"
● "የሚያብረቀርቅ ሁሉ ወርቅ አይደለም"
● "በጅ የያዙት ወርቅ ከመዳብ ይቆጠራል"
● "ወርቅ ላበደረ ጠጠር፣
እህል ላበደረ አፈር"
● "የሰው ወርቅ አያደምቅ"

FELEG ETHIOPIA

ቴዲ ለህክምና 5 መቶ ሺ ብር ያስፈልገዋል  ለድጋፍ መሰብሰቢያ በሁለት ወንድሞች አዲስ አካውንት ተከፍቷል።እናም ደጋጎች አነሰ በዛ ሳትሉ ለዚሁ ሲባል በተከፈተው አካውንት የቻላችሁትን ያህል ...
01/25/2026

ቴዲ ለህክምና 5 መቶ ሺ ብር ያስፈልገዋል ለድጋፍ መሰብሰቢያ በሁለት ወንድሞች አዲስ አካውንት ተከፍቷል።

እናም ደጋጎች አነሰ በዛ ሳትሉ ለዚሁ ሲባል በተከፈተው አካውንት የቻላችሁትን ያህል በማስገባት ወንድማችሁ ጤናውን ይገበይ ዘንድ እርዱት።

ንግድ ባንክ በጋራ የተከፈተ አካውንት አንተነህ አብርሃም እና አደም መሃመድ
የሂሳብ ቁጥር 1000742459873

ይህ የቴዲ የእጂ ስልኩ ነው እየደወላችሁ አለንልህ በሉት ።
+251913283808

" የበሽታዉ መንስኤ ማርበርግ ቫይረስ (Marburg Virus) መሆኑን መለየት ተችሏል " - ጤና ሚኒስቴር የጤና ሚኒስቴር በደቡበ ኢትዮጵያ ክልል በጅንካ ከተማ የሄሞራጅከ ፊቨር (Viral ...
11/14/2025

" የበሽታዉ መንስኤ ማርበርግ ቫይረስ (Marburg Virus) መሆኑን መለየት ተችሏል " - ጤና ሚኒስቴር

የጤና ሚኒስቴር በደቡበ ኢትዮጵያ ክልል በጅንካ ከተማ የሄሞራጅከ ፊቨር (Viral Hemorragic Fever) በሽታ መከሰቱን እና የበሽታዉን ምንነት በማረጋገጥ ላይ መሆኑን መግለጹ ይታወቃል፡፡

ሚኒስትሩ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ የበሽታዉ መንስኤ ማርበርግ ቫይረስ (Marburg Virus) መሆኑን መለየት ተችሏል ብሏል።

የዘረመል ምርመራው የተከናወነው በኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ብሄራዊ ሪፈረንስ ላብራቶሪ ነው።

መግለጫው "በዚህም የዘረመል ምርመራ በአሁኑ ሰዓት ኢትዮጵያ ውስጥ የተገኘዉ ቫይረስ ሌሎች ምስራቅ አፍሪካ ሃገራት ላይ ከዚህ በፊት ከተከሰቱት ጋር ተመሳሳይ ዝርያ ያለዉ መሆኑ ታዉቋል" ነው ያለው።

በተጨማሪም በዛሬው እለትም አዲስ የበሽታውን ምልክት ያሳየ ወይም በቫይረሱ የተጠረጠረ ሰው ያልተገኘ መሆኑን ሚኒስትሩ ያሳወቀ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት የተለያዩ የሙያ ስብጥር ያካተተ ከፍተኛ ፈጣን ምላሽ ሰጭ ቡድን ወደ ከልሉ በመላከ በሽታዉን የመከላከል እና የመቆጣጠር ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ ብሏል።

ከነዚህም ውስጥ :-

° የማህበረሰብ አቀፍ የቅኝት ስራዎች፣

° በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን ለይቶ ማከም፣

° የማህበረሰብ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች እና ከተጠረጠሩ ሰዎች ጋር ንክኪ ያላቸዉን ሰዎች የመለየት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተገልጿል።

በሃገር አቀፍ እንዲሁም በክልል ደረጃ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች የክስተት አስተዳደር ስርዓት (Incident Management System) ተቋሞ የፈጣን ምላሽ ስራዎችን በማስተባበር ላይ ይገኛል ተብሏል።

Hagere Infotainment

Address

Tucker, GA

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hagere Infotainment posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Hagere Infotainment:

Share