Hagere Infotainment

Hagere Infotainment Time is everything | ጊዜ ሁሉም ነገር ይህ የቁምነገርና የመረጃ መለዋወጫ መማማሪያ ገጽ ነው ። ማንኛውንም አስተያየት ወይም ሀሳብ በጨዋነት መግለጽ የሀገራችን ሰው ባህል ነውና ካልተገባ ንግግር እንቆጠብ፣

07/25/2025

አብዬ መንግሥቱ ለማ በ1970 ዎቹ ከጋዜጠኛ ታደሠ ሙሉነህ ጋር ካደረጉት ቃለምልልስ የተወሰደ !


ንግግራችሁ መሀል እንግሊዝኛ የምትቀላቅሉ ወንዶች፦በርገር እና ኬክ የምትበሉ ፦ጥሬ አይመቸኝም የምትሉ  / ሽሮ አይመቸኝም የምትሉ፦አይፎን ያላችሁ፦ማስቲካ የምትበሉ፦ኳስ የማትወዱ፦ካልሲ በነጠላ...
07/25/2025

ንግግራችሁ መሀል እንግሊዝኛ የምትቀላቅሉ ወንዶች

፦በርገር እና ኬክ የምትበሉ

፦ጥሬ አይመቸኝም የምትሉ / ሽሮ አይመቸኝም የምትሉ

፦አይፎን ያላችሁ

፦ማስቲካ የምትበሉ

፦ኳስ የማትወዱ

፦ካልሲ በነጠላ ጫማ የምታደርጉ

፦ኢንስታግራም ላይ ከ 10 በላይ ተከታይ ያላችሁ

፦ዣንጥላ የምትይዙ

፦ስትስቁ የምታሽካኩ

፦ ዝናብ ፈርታችሁ እሮጣችሁ የምትጠለሉ

፦ለንፅህናችሁ የምትጨነቁ

፦ከለሊቱ 7ሰዓት በፊት የምትተኙ

፦ለቲኒሽ ህመም ሀኪምቤት የምትሄዱ

፦ለፊልም የምታለክሱ

፦ፊሊተር ስናፕ ቻት የምትጠቀሙ

፦ኮከቤ ምናምን የምትሉ

፦በ40 አመታችሁ ትዳርም ፍቅረኛም የሌላችሁ

፦አዶናይ የምትሉ

፦ብLፅgና የምትደግፉ

゚viralfbreelsfypシ゚viral

አይረሴው ድምፃዊ ኬነዲ መንገሻ !በ1955 ዓ.ም ኬኔዲ መንገሻ ከተወለደ 3ት ቀን በኋላ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆን ኤፍ ኬኔዲ ተገደሉ። አባቱ አቶ አጥናፉ መንገሻ የጆን ኤፍ ኬኔዲ አድናቂ ስ...
07/25/2025

አይረሴው ድምፃዊ ኬነዲ መንገሻ !

በ1955 ዓ.ም ኬኔዲ መንገሻ ከተወለደ 3ት ቀን በኋላ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆን ኤፍ ኬኔዲ ተገደሉ። አባቱ አቶ አጥናፉ መንገሻ የጆን ኤፍ ኬኔዲ አድናቂ ስለነበሩ ለእሱ ማስታወሻ ይሆን ዘንድ የልጃቸውን ስም ኬነዲ እንዳሉት በአንድ ወቅት ለአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ ተናግረው ነበረ።

የኬኔዲ ትክክለኛ የአባቱ ስም አጥናፋ ሲሆን መንገሻ አያቱ ናቸው። ኬኔዲ የተወለደው አሳይታ በምትባል በወሎ ግዛት ውስጥ አሁን በአፋር ክልል በምትገኝ ከተማ ቢሆንም ያደገው አዲስ አበባ አያቱ ዘንድ ተክለሃይማኖት ተብሎ የሚጠራው አካባቢ ነበረ።

ኬኔዲ መንገሻ ገና በወጣትነት እድሜው ባወጣው የመጀመሪያ ካሴት ከፍተኛ ተቀባይነትን ከማግኘት አልፎ እውቅናን ለመቀዳጀት ችሏል። ኬኔዲ መንገሻን ብዙዎች በአመለ ሸጋነቱ ብሎም በመልከ መልካምነቱ በቅርበት የሚያውቁት ደግሞ በለጋስነቱ ያስታውሱታል።

እንዲያውም በአንድ ወቅት ኢትዮጵያ ቴሌቭዥን በአንድ ሙዚቃ ስራው ቀረጻ ያደረገበትን አዲስ ልብስ ከስቱዲዮ ሲወጣ በር ላይ ላገኘው የጥበቃ ሰራተኛ ያለስስት ሰጥቶት እንዳለፈ ይህ ባህሪው የለበሰውን እንኳ አውልቆ እስከመስጠት የሚያደርሰው እንደነበረ ወዳጆቹ የሚመሰክሩት ነገር ነው።

ከፍተኛ የሆነ የሞተር ብስክሌት ፍቅር ስለነበረው አዘውትሮ ያሽክክር እንደነበረ ወዳጅ ዘመዶቹ ይገልፃሉ። ተወዳጁ ድምጻዊ ኬኔዲ መንገሻ ሐምሌ 19 ቀን 1985 ዓ.ም ገና በ29 ዓመቱ ዕድሜው ላይ ነበረ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው። ዛሬም የኬኔዲ ሙዚቃ ሲደመጥ የወዳጆቹ ልብ በሀዘን ይሞላዋል።

ኬኔዲ መንገሻ ከ1979-1985 በነበሩት ዓመታት “በመላ ነው” (1979) “እንዲያው የሆዴ” (1980)፣ “ቀፎኛል” (1982) “ልሁን ደህና” (1984) እና “እምባ ስንቅ አይሆነኝ” (1985) የተሰኙ አልበሞችን ሰርቷል፡፡ በ1981 ከአሰፉ ደባልቄ፣ ከራሄል ዮሐንስ እና ከተሾመ አሰገድ ጋር፣ 1982 ከየሺመቤት ዱባለ ጋር እንዲሁም በ1983 ከብርቱካን ዱባለ ጋር በህብረት በሠራቸው ስራዎችም በርካታ ተወዳጅ ዜማዎችን ተጫውቷል፡፡

Hagere Infotainment
FELEG ETHIOPIA

07/21/2025

ደርባባው አቡኑ | ሽርሽር



07/21/2025

Celebrating my 13th year on Facebook. Thank you for your continuing support. I could never have made it without you. 🙏🤗🎉

07/21/2025

አበበ ቀበታ | ጀምበሬ ነሽ



07/21/2025

አስቴር አወቀ | ሽርሽር




07/21/2025

ጌታቸው ካሳ | ችዬ አልፌዋለሁ



07/21/2025

ፋንቱ ማንዶዬ | አትንኩብኝ




07/21/2025

Tewodros Tadesse | Lady | Ethio Version



ከብዙ ዘመን አይሽሬ ዜማዎች ጀርባ ታላቅ ተግባር የከወኑት ሳህሌ ደጋጎ !በ1973 ዓም ሻምበል ሳህሌ ደጋጎ ያደረገውን ቃለምልልስ ያዳምጡ https://youtu.be/dGRDrIkv_Cchttps...
07/21/2025

ከብዙ ዘመን አይሽሬ ዜማዎች ጀርባ ታላቅ ተግባር የከወኑት ሳህሌ ደጋጎ !

በ1973 ዓም ሻምበል ሳህሌ ደጋጎ ያደረገውን ቃለምልልስ ያዳምጡ https://youtu.be/dGRDrIkv_Cc
https://youtu.be/dGRDrIkv_Cc
https://youtu.be/dGRDrIkv_Cc

ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ በ1923 ዓ/ም በምዕራብ ወለጋ ልዩ ስሙ ነጆ ከተባለው ሥፍራ ተወለዱ። እድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በነቀምት አንደኛ ደረጃ እና በአዲስ አበባ ተፈሪ መኮንን ት/ቤት ዘመናዊ ትምህርቱን ከተከታተለ በኋላ በነበረው ልዩ የውትድርና ፍቅር በቀድሞ 1ኛ ክፍለ ጦር በኋላም ማዕከላዊ ዕዝ ተብሎ በተጠራው የክ/ዘበኛ የጦር ክፍል ውስጥ በ1942 ዓ/ም ተቀጥሯል።

በነበረው ሙያዊ ብቃትና ወታደራዊ ሥነ ሥርዓት አክባሪነት ከተራ ወታደርነት በአንድ ጊዜ የሃምሳ አለቅነት ማዕረግ ማግኘት የቻለው ሣህሌ፤ በሂደት እስከ ኮሎኔል ደረጃ ደርሷል። ወደ ሙዚቃ ቀማሪነት፣ ዜማና ግጥም ደራሲነት እንደዚሁም ወደ የማዕከላዊ ዕዝ የሙዚቃ ባንድ ኃላፊነት ከመሸጋገሩ በፊት በእግረኛ ባንድ ውስጥ “ክላርኔት” የተሰኘውን የሙዚቃ መሣሪያ ተጫዎች የነበረው ሣህሌ ደጋጎ፣ የሙዚቃን ትምህርት የቀሰመው ከፈረንሣዊው መምህሩ ሙሴ ኒኮ እንደሆነ ይነገራል።

ከክላርኔት በተጨማሪ “አኮርዲዮን፣ አልቶ-ሳክስ፣ ፒያኖ” የተሰኙትን የሙዚቃ መሣሪያዎችንም በብቃት ይጫወት ነበር። በጠቅል ራዲዮ ጣቢያ በአኮርዲዮን ጥዑም ዜማ ለጣቢያው አድማጮች ሲያንቆረቁሩ ከነበሩት የሙዚቃ ሰዎች መካከል ሣህሌ ደጋጎ የመጀመሪያው ነበር።

ከእነ ሻለቃ ግርማ ይህደጎ፣ ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ እና ከሻለቃ ባሻ ገብረዓብ ተፈሪ ጋር በመሆን የክቡር ዘበኛ ኦርኬስትራን ስም እፁብ ድንቅ በማድረጉ በኩል የበኩሉን ሚና ተጫውቷል። ግጥምና ዜማ ደራሲ ከመሆኑም ባሻገር የአጫጭር እና ረዣዥም ድራማዎች ፀሐፊ የነበረው ሣህሌ «ሁለገብ የታሪክ ማኅደር» ያሰኘውን ተግባር በሕይወት ዘመኑ አከናውኗል።

ክቡር ዶ/ር ጥላሁን ገሠሠ ከተጫወታቸው ሙዚቃዎች ውስጥ “ስቆ መኖር”፣ “እውነት ማሪኝ”፣ የሚሉትን ግጥሞች፣ “ዋይ ዋይ ሲሉ”፣ “ውሸት ለመናገር”፣ “ልብሽን ለአፈርሰው”፣ “ኮቱሜ”፣ የሚሉትን ዘፈኖች ግጥምና ዜማዎች የደረሰው ሌ /ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ ነው፡፡

ከዚህም ሌላ ለድምፃዊት ብዙነሽ በቀለ “አይወጣኝም ክፉ ነገር” በሚል የዘፈነችውና በብዙኀን ዘንድ ተወዳጅነት ያለውን (“ወደመጣሁበት ምድር፣ እስክመለስባት በክብር፣ ሰውን ከማስደሰት በቀር፣ አይወጣኝም ክፉ ነገር፣ ሙዚቃውን ያቀናበረው ሌ /ኮሎኔል ሣህሌ ነው።

ሌ /ኮሎኔል ሣህሌ “ፍላጎቴ”፣ “ምን ነበር”፣ “ምንድነው ትዝታህ”፣ ... የተሰኙትን የብዙነሽ በቀለን ዘፈኖች ያቀናበረ ሲሆን፣ “ከንቱ ሥጋ” የሚለውንና ሌሎችንም ዘፈኖችዋን ግጥም ደርሶላታል። “አታሳየኝ ጭንቁን”፣ “የፍቅር ወጋገን”፣ “ቃልኪዳን”፣ “በብር አይጋዛም”፣ “ፍቅርህ ቀሰቀሰኝ”፣ የተሰኙትን ዜማና ግጥሞች ያዘጋጀው ሣህሌ ደጋጎ ነው፡፡ “ሰው ከተሰማራ” በተሰኘው ዘፈኗ ለምትታወቀው ለድምፃዊት መንበረ በየነ ደግሞ “እንዴት ከረማችሁ” የሚለውን ዘፈን ግጥም የደረሰው ሌ /ኮ /ል ሣህሌ ነበር።

“የቆራጡ መሪ ፍሬው ጎመራ” የተሰኘውንና ለቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት መንግሥቱ ኃይለማርያም ላቀነቀነችው ለድምፃዊት ውብሻው ስለሺ ደግሞ “ይህ ነው ጌትነት”፣ “የምድር ፈተና” የተሰኙትንና በ 1966 ዓ.ም የታተሙትን ዘፈኖችዋን ያቀናበረላት ሌ /ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ ነበር።

በዕድሜ ዘመን የኪነ ጥበብ አገልግሎት የክብር ሜዳሊያ እና የ 20 ሺህ ብር ተሸላሚ የሆነው ሣህሌ ደጋጎ፤ የ 30፣ የ20 እና የ10 ዓመት የረዥም ዘመን አገልግሎት የወርቅ፣ የብርና የነኀስ እንደዚሁም የተዋጊ ወታደርነት የደረት ዓርማ ኒሻን ተሸለሚም ነበር።

ዋይ ዋይ ሲሉ የሚለው ዘፈን የተሰራበት አጋጣሚን አስመልክቶ ሳህሌ ደጋጎ የተናገሩትን ያዳምጡ
https://youtu.be/kXMs4Hl3QNE
https://youtu.be/kXMs4Hl3QNE
https://youtu.be/kXMs4Hl3QNE

በዚህ ቃለምልልስ ላይ ሻምበል የነበሩት በኋላም ኮሎኔል የሆኑት የሙዚቃ ሊቅ ሳህሌ ደጋጎ በ1973 ዓም ከጋዜጠኛ ኃይሉ አበበ ጋር ያደረገው ቃለምልስሰ። ዋይ ዋይ ሲሉ የሚለው ጥላሁን ገሠሠ የ...

07/18/2025

ምኒልክ ወስናቸው



Address

Tucker, GA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hagere Infotainment posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Hagere Infotainment:

Share